፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨
(((እኔም #ገጣሚ_ነኝ)))
ስሙኝ.......
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
በሶሻል ሚዲያ
ስሜ ያልተጠራ
ብዙም ያልታወኩኝ....
በደሳሳ ጎጆ
ህልሜን ያጠበብኩኝ
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
*
*
*
ከምሁራን ተርታ
ፈፅሞ ያልተሰለፍኩ
ከእውቅ ፀሀፊያን
መሀል ያልተካተትኩ
እኔም #ደራሲ_ነኝ!
በሰላች ብእሬ
ስሜቴን የገለፅኩ
*
*
ነገር ግን......
እንደነ እንትና
እስካርፕ አልጠመጠምኩ
እንደ ሀያሲያን
ሸሚዝ በከረባት
ታጥቄ አለበስኩ
በአምስቱ ጣቶቼ
የእከሌን መፅሀፍ
ይዤ አልተሽከረከርኩ....
በሄድኩበት ሁሉ
#ደራሲ_ነኝ እኔ
እውቅ ነው ሀሳቤ
ብዬም አልተናዘዝኩ.....
*
*
.........ግናም እፅፋለሁ........
ብእር ከወረቀት
እያዋደድኳቸው
ለሰው የማይገባ
ዝብርቅርቅ ሀሳባት
እኔም አፈሳለሁ ...
በሀሳቤ አርግዤው
ለአእላፉ ቀናት
እያብሰለሰልኩት
ይዤው እከርማለሁ...
የቁርጥ ቀን መቶ
እስክገላገለው
ወረቀት ከብእር
እስከማጋጥመው
ብዙ አምጣለሁ...
ያማጥኩት ተባርኮ
በመድብል ሲወለድ
ማየትን እሻለሁ..
*
*
እና እንደሌሎቹ.....
#እኔም_ገጣሚ ነኝ!
ብዬ አልዘባርቅም...
የገጠምኩት #ግጥም
የደረስኩት ድርሰት
የከሌ ነው ታሪክ ነው
ብዬ አልናገርም...
*
*
እውነቱ ገብቷቸው
አንተ #ደራሲ_ነክ
የሰዎችን እውነት
በብእር የገለፅክ
ብለው እስኪረዱኝ
በቤቴ የምኖር
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
✍ተፃፈ በ @Mak_bale
ግንቦት 1,2012
@getem
@getem
@getem
(((እኔም #ገጣሚ_ነኝ)))
ስሙኝ.......
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
በሶሻል ሚዲያ
ስሜ ያልተጠራ
ብዙም ያልታወኩኝ....
በደሳሳ ጎጆ
ህልሜን ያጠበብኩኝ
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
*
*
*
ከምሁራን ተርታ
ፈፅሞ ያልተሰለፍኩ
ከእውቅ ፀሀፊያን
መሀል ያልተካተትኩ
እኔም #ደራሲ_ነኝ!
በሰላች ብእሬ
ስሜቴን የገለፅኩ
*
*
ነገር ግን......
እንደነ እንትና
እስካርፕ አልጠመጠምኩ
እንደ ሀያሲያን
ሸሚዝ በከረባት
ታጥቄ አለበስኩ
በአምስቱ ጣቶቼ
የእከሌን መፅሀፍ
ይዤ አልተሽከረከርኩ....
በሄድኩበት ሁሉ
#ደራሲ_ነኝ እኔ
እውቅ ነው ሀሳቤ
ብዬም አልተናዘዝኩ.....
*
*
.........ግናም እፅፋለሁ........
ብእር ከወረቀት
እያዋደድኳቸው
ለሰው የማይገባ
ዝብርቅርቅ ሀሳባት
እኔም አፈሳለሁ ...
በሀሳቤ አርግዤው
ለአእላፉ ቀናት
እያብሰለሰልኩት
ይዤው እከርማለሁ...
የቁርጥ ቀን መቶ
እስክገላገለው
ወረቀት ከብእር
እስከማጋጥመው
ብዙ አምጣለሁ...
ያማጥኩት ተባርኮ
በመድብል ሲወለድ
ማየትን እሻለሁ..
*
*
እና እንደሌሎቹ.....
#እኔም_ገጣሚ ነኝ!
ብዬ አልዘባርቅም...
የገጠምኩት #ግጥም
የደረስኩት ድርሰት
የከሌ ነው ታሪክ ነው
ብዬ አልናገርም...
*
*
እውነቱ ገብቷቸው
አንተ #ደራሲ_ነክ
የሰዎችን እውነት
በብእር የገለፅክ
ብለው እስኪረዱኝ
በቤቴ የምኖር
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
✍ተፃፈ በ @Mak_bale
ግንቦት 1,2012
@getem
@getem
@getem
#ይነበብ
ውድ የቴሌግራምና ፌስቡክ ጓዶች እንዴት ናችሁ?
መቼም በዚህ ሰዓት 'ሰላም ነው?' የሚለውን ቃል ከአንደበታችን እንዳናወጣ በሀገራችን እየሆነ ያለው ነገር ያስረናል፡፡
አዎ፡፡ እኛ ከኢትዮጵያ እና ከኢትዮጵያውያን ጎን ነን !!! ኢትዮጵያ ምንጊዜም ድል ታደርጋለች፡፡ አዎ እኛ ከንግግር በዘለለ አንድ ነገር በጋራ ብናደርግስ ፡ ብለን ወሳኝ ጉዳይ ለማከናወን ተነስተናል፡፡
ይህ ጥሪ ለሁላችሁም ነው ህዳር 20 እሁድ እለት #የግጥም_አብዮት እና የ #ግጥም_ብቻ ከተሰኙት ግሩፕ ጋር ለመልካም ነገር ዘምታችሁ #ደሜን_ለሀገሬ እያላችሁ ትለግሱ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
እኔ ከኢትዮጵያ ጎን ነኝ የሚል ሁሉ ደሙን ሰጥቶ አለሁልሽ ይበላት፡፡ መልካምነት ዋጋው ትልቅ ነው ወደ ህይወታችን ይዞ የሚመጣው በረከትም አያልቅም፡፡ ኑ ለመልካም እንዝመት! ሩቅ ያላችሁ በየትኛውም ክፍለ ሀገራት የሚገኙ #ለመልካም_ዘማቾች ቀኑን በአቅራቢያቸው ወደሚገኝ ቀይ መስቀል በመሄድ እለቱን ያስቡ፡፡
በዚህም መሰረት ፦
ህዳር 20 (እሁድ )
ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ
ስቴዲየም ወደሚገኘው የቀይ መስቀል ማህበር ግቢ ውስጥ እንገናኝ 🙏🙏🙏
*
Telegram
@Tkida and @gebriel19
#ለመልካም_ዘማቾች
#የግጥም_አብዮት
#ግጥም_ብቻ
📍📍📍 በዚህ ዘመቻ ላይ አብረን እንዘምታለን የምትሉ ሁሉ ድምፃችሁን አሰሙ ፡፡ #Share
📍📍📍 ኢትዮጵያዊ ነን የምንል ሁሉ ቢያንስ ለ10 ሰው ይህንን በማካፈል ዘመቻውን እንቀላቀል/እንደግፍ 🙏
@getem
@TkYEGITMABIYOT
ውድ የቴሌግራምና ፌስቡክ ጓዶች እንዴት ናችሁ?
መቼም በዚህ ሰዓት 'ሰላም ነው?' የሚለውን ቃል ከአንደበታችን እንዳናወጣ በሀገራችን እየሆነ ያለው ነገር ያስረናል፡፡
አዎ፡፡ እኛ ከኢትዮጵያ እና ከኢትዮጵያውያን ጎን ነን !!! ኢትዮጵያ ምንጊዜም ድል ታደርጋለች፡፡ አዎ እኛ ከንግግር በዘለለ አንድ ነገር በጋራ ብናደርግስ ፡ ብለን ወሳኝ ጉዳይ ለማከናወን ተነስተናል፡፡
ይህ ጥሪ ለሁላችሁም ነው ህዳር 20 እሁድ እለት #የግጥም_አብዮት እና የ #ግጥም_ብቻ ከተሰኙት ግሩፕ ጋር ለመልካም ነገር ዘምታችሁ #ደሜን_ለሀገሬ እያላችሁ ትለግሱ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
እኔ ከኢትዮጵያ ጎን ነኝ የሚል ሁሉ ደሙን ሰጥቶ አለሁልሽ ይበላት፡፡ መልካምነት ዋጋው ትልቅ ነው ወደ ህይወታችን ይዞ የሚመጣው በረከትም አያልቅም፡፡ ኑ ለመልካም እንዝመት! ሩቅ ያላችሁ በየትኛውም ክፍለ ሀገራት የሚገኙ #ለመልካም_ዘማቾች ቀኑን በአቅራቢያቸው ወደሚገኝ ቀይ መስቀል በመሄድ እለቱን ያስቡ፡፡
በዚህም መሰረት ፦
ህዳር 20 (እሁድ )
ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ
ስቴዲየም ወደሚገኘው የቀይ መስቀል ማህበር ግቢ ውስጥ እንገናኝ 🙏🙏🙏
*
Telegram
@Tkida and @gebriel19
#ለመልካም_ዘማቾች
#የግጥም_አብዮት
#ግጥም_ብቻ
📍📍📍 በዚህ ዘመቻ ላይ አብረን እንዘምታለን የምትሉ ሁሉ ድምፃችሁን አሰሙ ፡፡ #Share
📍📍📍 ኢትዮጵያዊ ነን የምንል ሁሉ ቢያንስ ለ10 ሰው ይህንን በማካፈል ዘመቻውን እንቀላቀል/እንደግፍ 🙏
@getem
@TkYEGITMABIYOT
😢1
ጀመኣው ቅድም ማታ ላይ ምርጥ ቀደዳ አለ ብያቹ ነበር በቃሌ መሰረት ይዤው መጥቻለሁ ያው #ግጥም ባይሆንም ሁላችንንም በቀጥታ የሚመለከት ስለሆነ ነው! #በደንብ ይነበብ!!
የሰንበት ረፋድ ምርጥ ቀደዳ!!
💚
.
.
እንደምነህ ጌታዬ? እንዴት ነሽ እናቴ? የዚህ ሳምንት ቀደዳችን ደግሞ ይለያል! የፀዳ ነው! ይጠቅምሃል አንብበው!😀
.
.
ጠዋት ስትነሳ ግራ እግርህ ይስራ አይስራ ሳታረጋግጥ መጀመርያ ስልክህን አንስተህ "facebook" ቼክ ታደርጋለህ። ሽንት ቤት ቁጭ ብለህ "Instagram" ላይ ቆንጆ ቆንጆ ሴቶችን "scroll" እያደረክ ትኮሞኩማለህ። ስልክህ ካርድ ከሌለው ቶሎ ገዝተህ "ማህበራዊ ሚድያ" ላይ እስክትጣድ ያንቀለቅልሃል! የሆነ ፅሁፍ ለጥፈህ ምን ያህል "like" እና "comment" እንዳገኘህ ለማወቅ በየደቂቃው "Refresh" እያደረክ ታያለህ። የለጠፍሽው ፎቶ ምን ያህል "like" እንዳገኘ ለማወቅ ያቅበዘብዝሻል። የጠበቅሽውን ያህል "Reaction" ካላገኘ ተበሳጭተሽ ፎቶውን ታጠፊዋለሽ። "ማህበራዊ ሚድያ" ላይ የምታውቃቸው ሰዎች ለተወሰነ ግዜ ሲጠፉብህ ይጨንቅሃል። ስማቸውን ሳይቀር ፅፈህ ትፈልጋቸዋለህ። ፎቶሽ ላይ ሁል ግዜ "...የኔ ቆንጆ፣ የኔ ልዕልት፣ ስታምሪ.." ምናምን እያለ "comment" የሚያደርግልሽ ልጅ በሆነ አጋጣሚ አዲስ የለጠፍሽው ፎቶ ላይ "comment" ካላደረገ ያሳስብሻል። የለጠፍከው ፎቶ ወይም ፅሁፍ "like" ብዙም ካላገኘ እራስህ "like" ታደርጋለህ። መስሪያ ቤትህ በሰጠህ ኮምፒውተር "facebook" ትጠቀማለህ። ከሰዓት ማስገባት ያለብህ ወሳኝ ስራ እያለ አንተ "tiktok" ላይ ትጣዳለህ። ጠዋት ተነስተህ ወደ ስራ መሄድ እንዳለብህ እያወቅ ማታ ላይ አንድ ሰላሳ ደቂቃ "Tiktok" ልይ ብለህ እስከ ለሊቱ 9 ሰዓት ድረስ ተጥደሃል። በንጋታው ስራ ረፍዶብሃል ወይም "Tiktok" ላይ ለሊቱን ሙሉ ተጥደህ በቂ እንቅልፍ ባለማግኘትህ ምክንያት ጠዋት ታክሲ ውስጥ አንቀላፍተሃል፣ ቀንህ ተጦልቧል። አንድ ቪድዮ "YouTube" ላይ አያለው ብለህ የገባህ ሰውዬ ሳታስበው "30 ቪድዮ" አይተሃል። "Facebook" ላይ ተጀናጅናችሁ፣ የባጥ የቆጡን ሳትተፋፈሩ አውርታችሁ፣ ተዋዳችሁ፣ ሳትገናኙ እዛው "Facebook" ላይ ተጣብሳችሁ በመጨረሻም በአካል ስትገናኙ ተሽኮርምመሃል፣ አፍረሃል፣ መሬት መሬት አይተሃል፣ ተንተባትበሃል። ከጓደኞችህ ጋር ምሳ ለመብላት ተገናኝታችሁ ምግቡ እስኪመጣ በፊት ስለ ውሏቹ፣ ገጠመኞቻችሁ፣ ስለ ቤተሰቦቻችሁ፣ ስለ ስራችሁ ምናምን በሰፊው የምትቀዱ ሰዎች አሁን ሁላችሁም ስልካችሁ ላይ አቀርቅራችኃል። እየበላችሁ ሳይቀር ከስልኩ ጋር የሚበላ ከመካከላችሁ አይጠፋም። ስልክህን አብዝተህ ከመውደድህ የተነሳ ትራስህ ስር ወሽቀኸው ትተኛለህ። መብራት ሲጠፋ መጀመርያ የሚያሳስብህ ምግብ ማብሰል አለመቻልህ፣ ቴሌቪዥን ማየት አለመቻልህ ወይም ጨለማ መሆኑ ሳይሆን ስልክህን ቻርጅ ማድረግ አለመቻልህ ነው። ስልክህ ላይ ተጥደህ በመዋልህ ምክንያት ለሚስትህ የምትሰጣት ግዜ ቀንሷል፣ የምትተኙበት እና የምትነሱበት ሰዓት ተለያይቷል፣ ከልጅህ ጋር የምትጫወትበት ግዜ ወርዳል። ማህበራዊ ህይወትህ ተመቷል። ሰዎችን በአካል አግኝተህ ከምታወራቸው ይልቅ በ "Telegram" ወይም "Messanger" ብታወራቸው ይቀልሃል፣ በአካል መገናኘት ይጨንቅሃል። ጆሮህ ላይ የምትተክለው "Earphone" መገለጫህ እስኪሆን ድረስ ተጣብቆብሃል። የ "Internet' መቋረጥ ሞት እስኪመስልሽ ድረስ ያስጨንቅሻል። ብቻ ምን አለፋህ ስልክህ ህይወት ሆኗል!
አባዬ! ወደ ዋናው ጉዳይ ላምጣህ!
ዓለማችን ካላት ወደ 7 ቢልዮን ከሚገመት ህዝብ ቁጥር ውስጥ ወደ 3 ቢልዮን የሚሆነው ማህበራዊ ሚድያ(facebook, Instagram, snapchat, twitter, tiktok.....) ይጠቀማል። በቅርቡ በ"Netflix" የተሰራ "The Social Dilemma" የሚል ዶክመንተሪ አየሁ። ተራ ዶክመንተሪ አይደለም ጌታዬ! እዚህ ዶክመንተሪ ላይ ቃለ መጠይቅ የሚደረግላቸው ግለሰቦች ከባድ ሚዛን ናቸው። "Instagram" መጀመርያ ላይ ሃሳቡ ሲጠነሰስ አብረው የነበሩ ፣ "Twitter" ውስጥ ለአመታት በኢንጅነርነት ያገለገሉ፣ "pintrest" የመጣ ሰሞን ፕሬዝዳንት ሆኖ የሰራ፣ "Facebook" ውስጥ የ "monetization" ክፍል ዳይሬክተር የነበረ፣ "Google Drive"ን የፈጠሩ፣ "Facebook" ላይ ያለችውን "Like button" የሰራ፣ "Google" ውስጥ በዲዛይነርነት የሰሩ ፣" Gmail" መጀመርያ ሲፈጠር አብረው የነበሩ እና የ "Facebook" ስራ አስፈፃሚ(Executive) ቡድን ውስጥ ሳይቀር የነበሩ ሰዎች ናቸው።
ከነዚህ ከባባድ ሰዎች ውስጥ አንዳንዶቹ በፍቃደኝነት ስራቸውን የለቀቁ ሲሆን ሌሎቹ ደግሞ እነዚህ ማህበራዊ ሚድያዎች የሚሰሩት ትውልድን ሽባ የሚያደርግ ስራ ስለቀፈፋቸው ተጣልተው ወይ ተባረው የወጡ ናቸው።
የሚያስደነግጥ ነገር!
ሁሉም የሚያወሩት አንድ አይነት ነገር ነው። ምን ይላሉ መሰለህ ጌታዬ!
"....የየትኛውም ማህበራዊ ሚድያ የ " Business Model" እንዴት ተጠቃሚዎቻችንን ስክሪን ላይ ማቆየት እንችላለን የሚል ነው! አንድን ተጠቃሚ "Facebook" ወይም "Youtube" ላይ ለማቆየት እና በይበልጥ ትኩረቱን ለመሳብ ምን እናድርግ? የህይወቱን ስንት አመታት ለኛ እንዲሰጠን እናድርግ? የሚለውን ታሳቢ አድርገው ነው የሚሰሩት! እነዚህ "Tech ካምፓኒዎች" ተጠቃሚዎቻቸው "Online" የሚመለከቱትን ማንኛውንም ነገር ያያሉ፣ ይከታተላሉ፣ ይመዝናሉ፣ ያጠናሉ። አንድን ፎቶ ለምን ያህል ደቂቃ ቆም ብለህ እንዳየህ እና የሆነን ቪድዮ እስከ ስንተኛው ደቂቃ ድረስ እንደተከታተልክ ሳይቀር ያውቃሉ! ሲከፋህ ያውቃሉ፣ ሲጨንቅህ ያውቃሉ፣ ስትጓዝ ያውቃሉ፣ ማታ ማታ ምን እንደምታይ ያውቃሉ፣ ቀን ቀን ምን አዘውትረህ እንደምታይ ያውቃሉ። እኛ ከምናስበው በላይ እነዚህ ካምፓኒዎች ጋር ስለኛ ብዙ መረጃ አለ!...."
አባዬ! "Youtube" ልትገዛው ያሰብከውን እቃ መሃል ላይ አስተዋውቆት አስደንግጦህ ያውቃል? የሆነ ልትማር ያሰብለውን ትምህርት በምታየው "Video" መሃል በማስታወቂያ መልክ አምጥቶብህ አልተገረምክም? "Facebook" የዛሬ 10 ዓመት የምታውቀውን እና ከዛ በኃላ አግኝተኸው የማታውቀውን ሰውዬ "people you may know" ላይ ገጭ አድርጎት አይተህ ገርሞህ አታውቅም? "Google" ላይ የሆነ "lipstick" "Search" አድርገሽ ከወጣሽ በኃላ በንጋታው ሌሎች ማህበራዊ ሚድያዎችን ስትከፍቺ የ"lipstick" ማስታወቂያዎች አስሬ እየመጡ አዝገውሽ አያውቁም?
ሰዎቹ እንዲህ ይላሉ!
"...አብዛኛዎቻችን የምንጠቀማቸው የማህበራዊ ሚድያ መተግበርያዎች ነፃ ይመስሉናል! ነገር ግን አይደሉም! ለነዚህ ማህበራዊ ሚድያዎች ማስታወቂያ ድርጅቶች ብዙ ሚልዮን ዶላሮችን ይከፍላሉ! እኛ ልክ እንደ እቃ(product) ነን! እነዚህ ማህበራዊ ሚድያዎች የምንወደውን፣ የምንጠላውን፣ የምናደርገውን እና ያቀድነውን ስለሚያውቁ ለነዚህ ማስታወቂያ ድርጅቶች የኛን መረጃ(data) ይሸጡላቸዋል!...በቀላሉ ካሌንደርህ ላይ በቀጣይ ወር መነፅር እንደምትገዛ ከፃፍክ ቀኑ እየቀረበ ሲመጣ ብዙ የመነፅር ማስታወቂያዎች ይመጡብሃል! ኢሜልክ ላይ የሆነ ሃገር የምትሄድበት ትኬት ካለ እዛ የምትሄድበት ሃገር ላይ ያሉ የሆቴሎች ማስታወቂያ
የሰንበት ረፋድ ምርጥ ቀደዳ!!
💚
.
.
እንደምነህ ጌታዬ? እንዴት ነሽ እናቴ? የዚህ ሳምንት ቀደዳችን ደግሞ ይለያል! የፀዳ ነው! ይጠቅምሃል አንብበው!😀
.
.
ጠዋት ስትነሳ ግራ እግርህ ይስራ አይስራ ሳታረጋግጥ መጀመርያ ስልክህን አንስተህ "facebook" ቼክ ታደርጋለህ። ሽንት ቤት ቁጭ ብለህ "Instagram" ላይ ቆንጆ ቆንጆ ሴቶችን "scroll" እያደረክ ትኮሞኩማለህ። ስልክህ ካርድ ከሌለው ቶሎ ገዝተህ "ማህበራዊ ሚድያ" ላይ እስክትጣድ ያንቀለቅልሃል! የሆነ ፅሁፍ ለጥፈህ ምን ያህል "like" እና "comment" እንዳገኘህ ለማወቅ በየደቂቃው "Refresh" እያደረክ ታያለህ። የለጠፍሽው ፎቶ ምን ያህል "like" እንዳገኘ ለማወቅ ያቅበዘብዝሻል። የጠበቅሽውን ያህል "Reaction" ካላገኘ ተበሳጭተሽ ፎቶውን ታጠፊዋለሽ። "ማህበራዊ ሚድያ" ላይ የምታውቃቸው ሰዎች ለተወሰነ ግዜ ሲጠፉብህ ይጨንቅሃል። ስማቸውን ሳይቀር ፅፈህ ትፈልጋቸዋለህ። ፎቶሽ ላይ ሁል ግዜ "...የኔ ቆንጆ፣ የኔ ልዕልት፣ ስታምሪ.." ምናምን እያለ "comment" የሚያደርግልሽ ልጅ በሆነ አጋጣሚ አዲስ የለጠፍሽው ፎቶ ላይ "comment" ካላደረገ ያሳስብሻል። የለጠፍከው ፎቶ ወይም ፅሁፍ "like" ብዙም ካላገኘ እራስህ "like" ታደርጋለህ። መስሪያ ቤትህ በሰጠህ ኮምፒውተር "facebook" ትጠቀማለህ። ከሰዓት ማስገባት ያለብህ ወሳኝ ስራ እያለ አንተ "tiktok" ላይ ትጣዳለህ። ጠዋት ተነስተህ ወደ ስራ መሄድ እንዳለብህ እያወቅ ማታ ላይ አንድ ሰላሳ ደቂቃ "Tiktok" ልይ ብለህ እስከ ለሊቱ 9 ሰዓት ድረስ ተጥደሃል። በንጋታው ስራ ረፍዶብሃል ወይም "Tiktok" ላይ ለሊቱን ሙሉ ተጥደህ በቂ እንቅልፍ ባለማግኘትህ ምክንያት ጠዋት ታክሲ ውስጥ አንቀላፍተሃል፣ ቀንህ ተጦልቧል። አንድ ቪድዮ "YouTube" ላይ አያለው ብለህ የገባህ ሰውዬ ሳታስበው "30 ቪድዮ" አይተሃል። "Facebook" ላይ ተጀናጅናችሁ፣ የባጥ የቆጡን ሳትተፋፈሩ አውርታችሁ፣ ተዋዳችሁ፣ ሳትገናኙ እዛው "Facebook" ላይ ተጣብሳችሁ በመጨረሻም በአካል ስትገናኙ ተሽኮርምመሃል፣ አፍረሃል፣ መሬት መሬት አይተሃል፣ ተንተባትበሃል። ከጓደኞችህ ጋር ምሳ ለመብላት ተገናኝታችሁ ምግቡ እስኪመጣ በፊት ስለ ውሏቹ፣ ገጠመኞቻችሁ፣ ስለ ቤተሰቦቻችሁ፣ ስለ ስራችሁ ምናምን በሰፊው የምትቀዱ ሰዎች አሁን ሁላችሁም ስልካችሁ ላይ አቀርቅራችኃል። እየበላችሁ ሳይቀር ከስልኩ ጋር የሚበላ ከመካከላችሁ አይጠፋም። ስልክህን አብዝተህ ከመውደድህ የተነሳ ትራስህ ስር ወሽቀኸው ትተኛለህ። መብራት ሲጠፋ መጀመርያ የሚያሳስብህ ምግብ ማብሰል አለመቻልህ፣ ቴሌቪዥን ማየት አለመቻልህ ወይም ጨለማ መሆኑ ሳይሆን ስልክህን ቻርጅ ማድረግ አለመቻልህ ነው። ስልክህ ላይ ተጥደህ በመዋልህ ምክንያት ለሚስትህ የምትሰጣት ግዜ ቀንሷል፣ የምትተኙበት እና የምትነሱበት ሰዓት ተለያይቷል፣ ከልጅህ ጋር የምትጫወትበት ግዜ ወርዳል። ማህበራዊ ህይወትህ ተመቷል። ሰዎችን በአካል አግኝተህ ከምታወራቸው ይልቅ በ "Telegram" ወይም "Messanger" ብታወራቸው ይቀልሃል፣ በአካል መገናኘት ይጨንቅሃል። ጆሮህ ላይ የምትተክለው "Earphone" መገለጫህ እስኪሆን ድረስ ተጣብቆብሃል። የ "Internet' መቋረጥ ሞት እስኪመስልሽ ድረስ ያስጨንቅሻል። ብቻ ምን አለፋህ ስልክህ ህይወት ሆኗል!
አባዬ! ወደ ዋናው ጉዳይ ላምጣህ!
ዓለማችን ካላት ወደ 7 ቢልዮን ከሚገመት ህዝብ ቁጥር ውስጥ ወደ 3 ቢልዮን የሚሆነው ማህበራዊ ሚድያ(facebook, Instagram, snapchat, twitter, tiktok.....) ይጠቀማል። በቅርቡ በ"Netflix" የተሰራ "The Social Dilemma" የሚል ዶክመንተሪ አየሁ። ተራ ዶክመንተሪ አይደለም ጌታዬ! እዚህ ዶክመንተሪ ላይ ቃለ መጠይቅ የሚደረግላቸው ግለሰቦች ከባድ ሚዛን ናቸው። "Instagram" መጀመርያ ላይ ሃሳቡ ሲጠነሰስ አብረው የነበሩ ፣ "Twitter" ውስጥ ለአመታት በኢንጅነርነት ያገለገሉ፣ "pintrest" የመጣ ሰሞን ፕሬዝዳንት ሆኖ የሰራ፣ "Facebook" ውስጥ የ "monetization" ክፍል ዳይሬክተር የነበረ፣ "Google Drive"ን የፈጠሩ፣ "Facebook" ላይ ያለችውን "Like button" የሰራ፣ "Google" ውስጥ በዲዛይነርነት የሰሩ ፣" Gmail" መጀመርያ ሲፈጠር አብረው የነበሩ እና የ "Facebook" ስራ አስፈፃሚ(Executive) ቡድን ውስጥ ሳይቀር የነበሩ ሰዎች ናቸው።
ከነዚህ ከባባድ ሰዎች ውስጥ አንዳንዶቹ በፍቃደኝነት ስራቸውን የለቀቁ ሲሆን ሌሎቹ ደግሞ እነዚህ ማህበራዊ ሚድያዎች የሚሰሩት ትውልድን ሽባ የሚያደርግ ስራ ስለቀፈፋቸው ተጣልተው ወይ ተባረው የወጡ ናቸው።
የሚያስደነግጥ ነገር!
ሁሉም የሚያወሩት አንድ አይነት ነገር ነው። ምን ይላሉ መሰለህ ጌታዬ!
"....የየትኛውም ማህበራዊ ሚድያ የ " Business Model" እንዴት ተጠቃሚዎቻችንን ስክሪን ላይ ማቆየት እንችላለን የሚል ነው! አንድን ተጠቃሚ "Facebook" ወይም "Youtube" ላይ ለማቆየት እና በይበልጥ ትኩረቱን ለመሳብ ምን እናድርግ? የህይወቱን ስንት አመታት ለኛ እንዲሰጠን እናድርግ? የሚለውን ታሳቢ አድርገው ነው የሚሰሩት! እነዚህ "Tech ካምፓኒዎች" ተጠቃሚዎቻቸው "Online" የሚመለከቱትን ማንኛውንም ነገር ያያሉ፣ ይከታተላሉ፣ ይመዝናሉ፣ ያጠናሉ። አንድን ፎቶ ለምን ያህል ደቂቃ ቆም ብለህ እንዳየህ እና የሆነን ቪድዮ እስከ ስንተኛው ደቂቃ ድረስ እንደተከታተልክ ሳይቀር ያውቃሉ! ሲከፋህ ያውቃሉ፣ ሲጨንቅህ ያውቃሉ፣ ስትጓዝ ያውቃሉ፣ ማታ ማታ ምን እንደምታይ ያውቃሉ፣ ቀን ቀን ምን አዘውትረህ እንደምታይ ያውቃሉ። እኛ ከምናስበው በላይ እነዚህ ካምፓኒዎች ጋር ስለኛ ብዙ መረጃ አለ!...."
አባዬ! "Youtube" ልትገዛው ያሰብከውን እቃ መሃል ላይ አስተዋውቆት አስደንግጦህ ያውቃል? የሆነ ልትማር ያሰብለውን ትምህርት በምታየው "Video" መሃል በማስታወቂያ መልክ አምጥቶብህ አልተገረምክም? "Facebook" የዛሬ 10 ዓመት የምታውቀውን እና ከዛ በኃላ አግኝተኸው የማታውቀውን ሰውዬ "people you may know" ላይ ገጭ አድርጎት አይተህ ገርሞህ አታውቅም? "Google" ላይ የሆነ "lipstick" "Search" አድርገሽ ከወጣሽ በኃላ በንጋታው ሌሎች ማህበራዊ ሚድያዎችን ስትከፍቺ የ"lipstick" ማስታወቂያዎች አስሬ እየመጡ አዝገውሽ አያውቁም?
ሰዎቹ እንዲህ ይላሉ!
"...አብዛኛዎቻችን የምንጠቀማቸው የማህበራዊ ሚድያ መተግበርያዎች ነፃ ይመስሉናል! ነገር ግን አይደሉም! ለነዚህ ማህበራዊ ሚድያዎች ማስታወቂያ ድርጅቶች ብዙ ሚልዮን ዶላሮችን ይከፍላሉ! እኛ ልክ እንደ እቃ(product) ነን! እነዚህ ማህበራዊ ሚድያዎች የምንወደውን፣ የምንጠላውን፣ የምናደርገውን እና ያቀድነውን ስለሚያውቁ ለነዚህ ማስታወቂያ ድርጅቶች የኛን መረጃ(data) ይሸጡላቸዋል!...በቀላሉ ካሌንደርህ ላይ በቀጣይ ወር መነፅር እንደምትገዛ ከፃፍክ ቀኑ እየቀረበ ሲመጣ ብዙ የመነፅር ማስታወቂያዎች ይመጡብሃል! ኢሜልክ ላይ የሆነ ሃገር የምትሄድበት ትኬት ካለ እዛ የምትሄድበት ሃገር ላይ ያሉ የሆቴሎች ማስታወቂያ
👍2
#አንቺ እና ግጥም
....
ልማዴ እንዲህ ነው ...
ከጀምበር መግለጥ ጋር
አንቺንና ግጥምን ስንቅ ነው 'ምውለው።
.
#ግጥም ያስጠላኛል!
አንድ ሀሳብ ለመግለፅ መዞር ዙሪያ ጥምጥም
ቃላት ማሰካካት ... ምኑም እኮ አይጥምም።
እወድሻለሁ ለማለት
መመሰል በፀሀይ... ማሞገስ ጨረቃ
እዬዬ ማለት ነው ... ማውረድ ልቅሶ ሲቃ
በቃ !
.
#ግጥም!
ለመግለጥ ቁንጅናን ...
ሰውን ማድረግ መልዐክ...ማጋነን ...መጨመር
መወጠር.. .መቆለል ... ቅኔያት መከመር
ከዚህ ሁሉ ስቃይ
ቁንጅናዋን ነግሮ ወደድኩሽ እያሉ በዝርው መናገር
አይቀልም ማሳጠር?
ስከርቭን ጠምጥሞ ጠቢብ ነኝ እያሉ ጉራ ከመቸርቸር?
እያልኩ አስባለሁ ...
.
አንቺም እንደዚያው ነሽ !
እንደ ግጥም ሁሉ በኔ ትጠያለሽ
ሁሉንም አልወድም ያንቺን ነገራቶች
ጨዋታና ሳቅሽ እንዲሁም ቃላቶች
መስማት ይቀፈኛል የድምፅሽን መውጣት
ቅብጥብጥ ዓመልሽ ይመስለኛል መዓት
ጠጉርሽ ዞማ ቢሆን ቢመስል ፀሀዳ
ከብዶኛል እንደ እዳ!
.
ይብላኝልሽ ላንቺ
ቁንጅና በሚሉት ሰንሰለት ለታሰርሽ
ራስን በመውደድ ኩራት ለተጠመድሽ
እንጂ እኔ ሳይገርመኝ የውበትሽ ግርማ
ጠልቼሽ አለሁኝ
ታምራለች ከሚሉኝ ሰዎች ሳልስማማ ።
.
እያልኩኝ ቢሆንም ...
እንደዚህ ባስብም...
ግጥምን እየጠላሁ መግጠም ግን አልተውም።
.
አንቺም እንደዛው ነሽ
ቅኔ ነሽ ወርቅ ያለሽ
ጠላኋት እያልኩኝ.. .
አደባባይ መሀል ቆሜ ብፎክርም
አንቺን ላለማሰብ ሞልቶልኝ አያውቅም።
.
#ግጥምና አንቺ
አንቺ እና ግጥም
የልክፍት ጥርቅም
አቃጣይ ተብለው እጅን ለመሰብሰብ
ማባያም ተብለው ደርሶ ለመንገብገብ
እንደማይመቹት ...
አዋዜ ፣ ሰናፍጭ ... ሚጥሚጣ አይነት ናችሁ
አቃጣይ ቢሆንም ቅመም ነው ፍቅራችሁ።
.
@getem
@getem
@getem
#ሚካኤል አስጨናቂ
የሚካኤል አስጨናቂ ተጨማሪ ግጥሞችን ለማግኘት።
https://tttttt.me/MichaelAschenakipoems
....
ልማዴ እንዲህ ነው ...
ከጀምበር መግለጥ ጋር
አንቺንና ግጥምን ስንቅ ነው 'ምውለው።
.
#ግጥም ያስጠላኛል!
አንድ ሀሳብ ለመግለፅ መዞር ዙሪያ ጥምጥም
ቃላት ማሰካካት ... ምኑም እኮ አይጥምም።
እወድሻለሁ ለማለት
መመሰል በፀሀይ... ማሞገስ ጨረቃ
እዬዬ ማለት ነው ... ማውረድ ልቅሶ ሲቃ
በቃ !
.
#ግጥም!
ለመግለጥ ቁንጅናን ...
ሰውን ማድረግ መልዐክ...ማጋነን ...መጨመር
መወጠር.. .መቆለል ... ቅኔያት መከመር
ከዚህ ሁሉ ስቃይ
ቁንጅናዋን ነግሮ ወደድኩሽ እያሉ በዝርው መናገር
አይቀልም ማሳጠር?
ስከርቭን ጠምጥሞ ጠቢብ ነኝ እያሉ ጉራ ከመቸርቸር?
እያልኩ አስባለሁ ...
.
አንቺም እንደዚያው ነሽ !
እንደ ግጥም ሁሉ በኔ ትጠያለሽ
ሁሉንም አልወድም ያንቺን ነገራቶች
ጨዋታና ሳቅሽ እንዲሁም ቃላቶች
መስማት ይቀፈኛል የድምፅሽን መውጣት
ቅብጥብጥ ዓመልሽ ይመስለኛል መዓት
ጠጉርሽ ዞማ ቢሆን ቢመስል ፀሀዳ
ከብዶኛል እንደ እዳ!
.
ይብላኝልሽ ላንቺ
ቁንጅና በሚሉት ሰንሰለት ለታሰርሽ
ራስን በመውደድ ኩራት ለተጠመድሽ
እንጂ እኔ ሳይገርመኝ የውበትሽ ግርማ
ጠልቼሽ አለሁኝ
ታምራለች ከሚሉኝ ሰዎች ሳልስማማ ።
.
እያልኩኝ ቢሆንም ...
እንደዚህ ባስብም...
ግጥምን እየጠላሁ መግጠም ግን አልተውም።
.
አንቺም እንደዛው ነሽ
ቅኔ ነሽ ወርቅ ያለሽ
ጠላኋት እያልኩኝ.. .
አደባባይ መሀል ቆሜ ብፎክርም
አንቺን ላለማሰብ ሞልቶልኝ አያውቅም።
.
#ግጥምና አንቺ
አንቺ እና ግጥም
የልክፍት ጥርቅም
አቃጣይ ተብለው እጅን ለመሰብሰብ
ማባያም ተብለው ደርሶ ለመንገብገብ
እንደማይመቹት ...
አዋዜ ፣ ሰናፍጭ ... ሚጥሚጣ አይነት ናችሁ
አቃጣይ ቢሆንም ቅመም ነው ፍቅራችሁ።
.
@getem
@getem
@getem
#ሚካኤል አስጨናቂ
የሚካኤል አስጨናቂ ተጨማሪ ግጥሞችን ለማግኘት።
https://tttttt.me/MichaelAschenakipoems
#አንቺ እና ግጥም
....(ሚካኤል አስጨናቂ)
ልማዴ እንዲህ ነው ...
ከጀምበር መግለጥ ጋር
አንቺንና ግጥምን ስንቅ ነው 'ምውለው።
.
#ግጥም ያስጠላኛል!
አንድ ሀሳብ ለመግለፅ መዞር ዙሪያ ጥምጥም
ቃላት ማሰካካት ... ምኑም እኮ አይጥምም።
እወድሻለሁ ለማለት
መመሰል በፀሀይ... ማሞገስ ጨረቃ
እዬዬ ማለት ነው ... ማውረድ ልቅሶ ሲቃ
በቃ !
.
#ግጥም!
ለመግለጥ ቁንጅናን ...
ሰውን ማድረግ መልዐክ...ማጋነን ...መጨመር
መወጠር.. .መቆለል ... ቅኔያት መከመር
ከዚህ ሁሉ ስቃይ
ቁንጅናዋን ነግሮ ወደድኩሽ እያሉ በዝርው መናገር
አይቀልም ማሳጠር?
ስከርቭን ጠምጥሞ ጠቢብ ነኝ እያሉ ጉራ ከመቸርቸር?
እያልኩ አስባለሁ ...
.
አንቺም እንደዚያው ነሽ !
እንደ ግጥም ሁሉ በኔ ትጠያለሽ
ሁሉንም አልወድም ያንቺን ነገራቶች
ጨዋታና ሳቅሽ እንዲሁም ቃላቶች
መስማት ይቀፈኛል የድምፅሽን መውጣት
ቅብጥብጥ ዓመልሽ ይመስለኛል መዓት
ጠጉርሽ ዞማ ቢሆን ቢመስል ፀሀዳ
ከብዶኛል እንደ እዳ!
.
ይብላኝልሽ ላንቺ
ቁንጅና በሚሉት ሰንሰለት ለታሰርሽ
ራስን በመውደድ ኩራት ለተጠመድሽ
እንጂ እኔ ሳይገርመኝ የውበትሽ ግርማ
ጠልቼሽ አለሁኝ
ታምራለች ከሚሉኝ ሰዎች ሳልስማማ ።
.
እያልኩኝ ቢሆንም ...
እንደዚህ ባስብም...
ግጥምን እየጠላሁ መግጠም ግን አልተውም።
.
አንቺም እንደዛው ነሽ
ቅኔ ነሽ ወርቅ ያለሽ
ጠላኋት እያልኩኝ.. .
አደባባይ መሀል ቆሜ ብፎክርም
አንቺን ላለማሰብ ሞልቶልኝ አያውቅም።
.
#ግጥምና አንቺ
አንቺ እና ግጥም
የልክፍት ጥርቅም
አቃጣይ ተብለው እጅን ለመሰብሰብ
ማባያም ተብለው ደርሶ ለመንገብገብ
እንደማይመቹት ...
አዋዜ ፣ ሰናፍጭ ... ዳጣ አይነት ናችሁ
አቃጣይ ቢሆንም ቅመም ነው ፍቅራችሁ
ጠልቼ አልጠላችሁ!
@getem
@getem
@paappii
#Mikael aschenaki
....(ሚካኤል አስጨናቂ)
ልማዴ እንዲህ ነው ...
ከጀምበር መግለጥ ጋር
አንቺንና ግጥምን ስንቅ ነው 'ምውለው።
.
#ግጥም ያስጠላኛል!
አንድ ሀሳብ ለመግለፅ መዞር ዙሪያ ጥምጥም
ቃላት ማሰካካት ... ምኑም እኮ አይጥምም።
እወድሻለሁ ለማለት
መመሰል በፀሀይ... ማሞገስ ጨረቃ
እዬዬ ማለት ነው ... ማውረድ ልቅሶ ሲቃ
በቃ !
.
#ግጥም!
ለመግለጥ ቁንጅናን ...
ሰውን ማድረግ መልዐክ...ማጋነን ...መጨመር
መወጠር.. .መቆለል ... ቅኔያት መከመር
ከዚህ ሁሉ ስቃይ
ቁንጅናዋን ነግሮ ወደድኩሽ እያሉ በዝርው መናገር
አይቀልም ማሳጠር?
ስከርቭን ጠምጥሞ ጠቢብ ነኝ እያሉ ጉራ ከመቸርቸር?
እያልኩ አስባለሁ ...
.
አንቺም እንደዚያው ነሽ !
እንደ ግጥም ሁሉ በኔ ትጠያለሽ
ሁሉንም አልወድም ያንቺን ነገራቶች
ጨዋታና ሳቅሽ እንዲሁም ቃላቶች
መስማት ይቀፈኛል የድምፅሽን መውጣት
ቅብጥብጥ ዓመልሽ ይመስለኛል መዓት
ጠጉርሽ ዞማ ቢሆን ቢመስል ፀሀዳ
ከብዶኛል እንደ እዳ!
.
ይብላኝልሽ ላንቺ
ቁንጅና በሚሉት ሰንሰለት ለታሰርሽ
ራስን በመውደድ ኩራት ለተጠመድሽ
እንጂ እኔ ሳይገርመኝ የውበትሽ ግርማ
ጠልቼሽ አለሁኝ
ታምራለች ከሚሉኝ ሰዎች ሳልስማማ ።
.
እያልኩኝ ቢሆንም ...
እንደዚህ ባስብም...
ግጥምን እየጠላሁ መግጠም ግን አልተውም።
.
አንቺም እንደዛው ነሽ
ቅኔ ነሽ ወርቅ ያለሽ
ጠላኋት እያልኩኝ.. .
አደባባይ መሀል ቆሜ ብፎክርም
አንቺን ላለማሰብ ሞልቶልኝ አያውቅም።
.
#ግጥምና አንቺ
አንቺ እና ግጥም
የልክፍት ጥርቅም
አቃጣይ ተብለው እጅን ለመሰብሰብ
ማባያም ተብለው ደርሶ ለመንገብገብ
እንደማይመቹት ...
አዋዜ ፣ ሰናፍጭ ... ዳጣ አይነት ናችሁ
አቃጣይ ቢሆንም ቅመም ነው ፍቅራችሁ
ጠልቼ አልጠላችሁ!
@getem
@getem
@paappii
#Mikael aschenaki
👍1