ግጥም ብቻ 📘
67.6K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
#የኔ_ሌላ_ምስል
:
እንቅፋት አግኝቶኝ ፥ ስጓዝ በዱር በመንገድ
ከወገቤ ቢያጥፈኝ ፥ ሰላምታ እንደ መስገድ፣
ዘመዴ እጄን ሲይዝ ፥ 'እኔን!' ሲለኝ ፈጥኖ
'ይድፋህ!' ሲል ጠላቴ ፥ ሲረግመኝ ጨክኖ፣
ጓዴ ግን ሳቀብኝ ፥ አንጀቱ እስኪቆስል
እርሱ ነው ወዳጄ ፥ የኔው ሌላ ምስል።
--------------------//--------------------------
( በርናባስ ከበደ )

@getem
@getem
@getem
ዛሬ ከግጥም ውጪ በሆነ ጉዳይ ....ነው ብቅ ያልነው....👇👇

ብሔራዊ ጀግና💚💛❤️

የአንድ ሀገር የፓለቲካ ሁኔታ ሲበላሽ ሌባ እንደ ጀግና ይቆጠራል ። ሀገር አፍራሽ ጀግና ይባላል። በመሠረቱ ብሔራዊ ጀግና ማለት የራሱን ጥቅም ትቶ ፤ ያለፈውን የሀገር ታሪክ አስጠብቆ ፤ የዛሬውንና የነገውን መንገድ ብሩህ የሚያደርግ ነው። ጀግና ትሁት ነው ፤ ከራሱ አልፎ ለሌሎችም ከዚያም አልፎ ለመጪው ትውልድ የሚያስብ ነው ጀግና የሚባለው።

ኢትዮጵያ ጀግኖች ነበሯት። እንደ አብነ ጴጥሮስ ያሉ ለእምነታቸው፣ለወገናቸው ለሀገራቸው ሲሉ መከራን ለመቀበል የቆረጡ የመንፈስ መሪነት የተላበሱ ብሔራዊ ጀግኖች ነበሩ። ጀግንነታቸው በጊዜ ሂደት ዋጋ ያጣል የማይባል ነው። አንዲት ሀገር በመቶ ዓመታት ውስጥ አንድ ብሔራዊ ጀግና ካገኘች የታደለች ናት። ኢትዮጵያ አድዋ ላይ የጥቁር ህዝብ ነፃነትን የፈነጠቀ ድል ያስመዘገቡ ጀግኖች ሀገር ናት። ይህን ድል የመሩት ዐጤ ምኒሊክ ብሔራዊ ጀግናችን ተብለው ብቻ አይገልጹም፤ የጥቁር ህዝብ ኩራት ናቸው። ምኒልክ ለጀግና ከተቀመጠው ትርጉም አንፃር፤ ከፍ ያሉ ብሔራዊ ጀግና ናቸው።

ብሔራዊ ጀግኖች በህይወት ሳይኖሩም፤በስራቸው ህያው ሆነው አቅጣጫ አመላካች ናቸው። ዐጤ ምኒልክ ፣ እቴጌ ጣይቱ ፣ አሉላ አባ ነጋ፣ፊትውራሪ ገበየሁ ፣ ባልቻ አባነፍሶ እና ሌሎችም የአድዋ ድል ያስመዘገቡ ኢትዮጵያን በሰሯቸው ብሔራዊ ጀግና ሆነዋል።

ፓለቲካውን በጥላቻ የሚሰሩ ቡድኖች ዐጤ ምኒሊክን እና ተከታዮቻቸው የነበሩትን ጥላሸት ሲቀቡ እና ሊያቃልሉ ሲሞክሩ ይስተዋላሉ። ይህ የትውልዱን ሞራል እና የሀገር ፍቅር ስሜቱን ዝቅ ማድረግ ነው። ምኒሊክ በጦር ሊወጓቸው የተነሱትን ርህራሄ ያልነፈጉ ሰው ነበሩ። ይህንን በአርዓያነት ልንከተለው የሚገባ እንጂ ልናጣጥለው መድፈር አይገባንም። ጀግንነታቸው እሴታችን ነው። ዐጤ ቴድሮስም በራዕያቸው ብሔራዊ ጀግናችን ሆነዋል።

በአጠቃላይ፣ ኢትዮጵያ በታሪኳ ብሔራዊ ጀግኖች እንደነበሯት መካድ አይቻልም። ሆኖም አሁን ላይ እንደ ቀደሙት ከፍ ያለ ቦታ የምንሰጣቸው ብሔራዊ ጀግኖች የሉንም። በበኩሌ፣ በዚህ ወቅት አሉን የምንላቸው ጀግኖች ፣ ብሔራዊ ጀግኖቻችን የመሆን ደረጃ የደረሱ ናቸው ለማለት እቸገራለሁ።

በሌላ በኩል ፣ ብሔራዊ ጀግኖቻችን እንደ ነቀዝ ታሪካቸውን የመቦርቦር ስራ ይስተዋላል። ይህ አሳፋሪ ብቻ ሳይሆን ፣ ትንሽነትም ነው። ብሔራዊ ጀግኖቻችን የሚከተል፤አርዓያነታቸውን ለበጎ ሥራ መነሻነት የሚጠቀም ትውልድ ነው ሀገር የሚገነባው። ጀግናን ማንኳሰስ ጀግንነትን መሸሽ ነው። የአሁኑ ትውልድ ያለፉትን ጀግኖቻችን አለማክበርና ላነሰ ተግባር መሰለፍ፤ <<ወይራ ዶግ ይወልዳል >> እንደሚባለው ከአያት እና ቅድመ አያት ማነስ ይሆናል። ያለፈውን ያለፈውን ጉልህ አስተዋጽኦ በመካድ ወደፊት መራመድ አይቻልም። በለጸጉ የሚባሉ ሀገራት ህዝቦች ብሔራዊ ጀግኖቻቸውን ሲያከብሩ ነው የሚታዮት። የጀግኖቻችን ምልክት ስንከተል ነው ራዕይ የሚኖረን። ካለፋት ጀግኖች የተሻለ ታሪክ ለማስመዝገብ ሥራዎቻቸውን እውቅና ሰጥተን መመርመርና ለመማር ዝግጁ መሆንንን ይጠይቃል።

((( ዶ/ር ባይለኝ ጣሰው ))

ምንጭ:- ኢትዮጲስ ጋዜጣ ቁጥር 10 ኀዳር 16 ቀን 2011 ( ተቀንጭቦ የቀረበ )
---------------------------------------------------


የኛስ ትውልድ የሚያስማሙን ብሔራዊ ጀግኖች አሉት..? እነማን..?

ብሔራዊ ጀግናቹን አስተዋውቁን ህይወታቸው የሚማርከን አገልግሎታቸው ቀልባችንን የሚገዛው፤ትግላቸው ወይ ብልሀታቸው በፈለጋቹት መስፈርት ሊሆን ይችላል #የኔ ብሔራዊ ጀግና ብለን ልዩ ስፍራ የሰጠናቸውን ግለሰቦች አስተዋውቁን

#እንደማሳሰብያ
1 የጀግናችንን ማንንነት
2 ያበረከቱት አስተዋፆ
3 በጥበብ ያለፉትን መሰናክል
4ያሳለፉትንት ፅናት ወይም መከራ
5 ያላቸው ብቃት
6.ወ.ዘ.ተ......ቢዘረዘር ስለ ብሔራዊ ጀግኖቻቹ ያለን ምስል ሙሉ ይሆናል

#እየጠበቅናቹ ነው !!!!!

ሸጋ ሸጊቱ ምሽት 💚💛❤️

👇👇👇👇
@balmbaras
@Lula_al_greeko
@wegoch
@wegoch
👍1
#የኔ ዓለም
(ማዶ)

ሰማዩ አለቅጥ - አጎንብሼም ቀርቦኝ
ምድሩም ላ'ሳቤ - ተሰብስቤም ጠቦኝ
እንደዚህ አንሼ
እንዲህ አጎንብሼ
ከ'ርጅናዬም ብሼ
ቀና ማለት ከብዶኝ - መሬት ፥ መሬት ስቃኝ
የማስተዋል ልምሻ - ዘውትር እየደቃኝ
በነበርኩኝ ጊዜ - አንቺ ብቅ ብለሽ
ሰ...ፊ መሬት ሆነሽ - ጥልቅ ሰማይ ሰቅለሽ
አዲስ ዓለም ሰርተሽ - ስላ'ረግሽኝ ቀና
( ያው ብዙ አይደለሽ-)
ግራና ቀኝ ቁሜ - አንዴ ሹመት ላፅና ...
( በእቅፍሽ ስሆን -- )
እስትንፋስሽ ንፋስ - ውበትሽ ዳመና !

ፍርድ እና እርድ
( አበረ አያሌው )

@getem
@getem
@getem
#የኔ_ሴት
#ከውሰር[ጋዜጠኛው ዶክተር]
.
በተስፋ ባህር ጉዞ፣ወደ ፊት ነጎድኩኝ፤
የኔን ሴት ፍለጋ፣መልህቄን ያዝኩና፣ወደፊት ቀዘፍኩኝ፤
ግጣሜን ስስላት፣ሀዋዬን አፈቀርኩ፣ነገን ዛሬ አስቤ፤
ያላወኳት ሚስቴን ሳላዉቃት ወደድኳት፣ማፍቀሯን ተርቤ።
ስለሷ እያሰብኩኝ፤
በተስፋው ባህር ላይ፣ፍቅሬ ተንሳፈፈ፤
ጨለማው ነግቶልኝ፣ደስታዬም ገዘፈ፤
ብእሬም አድምቆ፦
የኔ ሴት እያለ፣ብዙ ግጥም ፃፈ።
.
ሌሎች ከሴታቸው፣አሉታውን ገልጠው፤
የሚስትነት ጣእም፣የላትም ይላሉ፣ጥፍጥናዋን ሽጠው።
የታል ሚስትነቷ?የታል ሴትነቷ?ይላሉ በትዝብት፤
ሚስትነቷን አጥተው፣ሴትነቷን ሸሽተው፣ዘውትረው በግርምት።
.
የብሶት ዜማቸው፣ጎልቶ ውስጤ ቢገባ፤
መልህቄን ቀዝፌ፣የኔን ሴት አየዋት፣ሠመመን ስገባ፤
በተስፋው አለም ውስጥ ጎጆዬን ስቀልስ፣የኔ ሴት ውስጥ አለች፤
እራሷን አፅድታ፣በስራ ተጠምዳ፣ሽር ጉድ እያለች፤
ሠላምታዬን ሳቀርብ፣ምላሹን መልሳ ግንባሬን ሳመችኝ፤
እንኳን ደህና መጣህ፣አረፍ በል ፍቅሬ፣ፍቅሯን ለገሠችኝ፤
የሚስትነት ለዛን፣የሴትነት ጣእሙን፣ግቱን አሳየችኝ፤
.
ጠባብ ቤቴ ያኔ አማረ፤
ሳቋ ጎልቶ ጭንቀት ቀረ፤
መዉደቅ መክሰር ተሰበረ፤
ፍቅር ነግሶ ጎልቶ ኖረ፤
መንገሳችን ተበሰረ፤
ልቦናችን በፍቅራችን፣አካላችን ተሳሠረ።
በሷ ብርታት ጠነከርኩኝ፣ፀባይ ገዛው በፍቅር ላቅኩኝ፤
በስግደቴ በረታሁኝ፣በንግስቴ ንጉስ ሆንኩኝ።
እሷ ማለት እኮ፦
የሷ መኖር የሚያኖረኝ፤
እሷ ማለት በቃ እኔ ነኝ፤
ብለው እንዳዜሙት፣ግነትን ቀላቅለው፤
በሷነት መንፈስ ውስጥ፣የኔ መንፈስ አለው፤
ገላዋ የኔው ነው፣ለሌላው ሽፍን ነው፤
የኔ ደስታ ማለት፣ስለሷ መኖር ነው።
የኔ ሴት ለእኔ፦
አይኗ እያነባ ልቧ እያዘነ፤
ቃሏ ከእውነት ውጭ፣ለሀሠት የቦዘነ፤
"ህይወቴ ባዶ ናት አንድ ቀን ያለርሡ፤"
ብላ ምትፀልይ ናት፣ቆማ ከመጅሊሡ፤
.
ፍቅሯ ያስነባኛል፣ምክሯ ይሠራኛል፤
የእሷነት ተግሳፅ፣እኔን ያኖረኛል፤
ያኔ ኮራሁ በማግባቴ፤
ውሀ አጣጬን በማግኘቴ፤
ደመቀልኝ እኔነቴ፤
አስከበረኝ ባልነቴ፤
በሀሳቤ አለች ለኔ ሚስቴ።

[KEWSER]

@getem
@getem
@Alkewsism
#የኔ_ሌላ_ምስል
:
እንቅፋት አግኝቶኝ ፥ ስጓዝ በዱር በመንገድ
ከወገቤ ቢያጥፈኝ ፥ ሰላምታ እንደ መስገድ፣
ዘመዴ እጄን ሲይዝ ፥ 'እኔን!' ሲለኝ ፈጥኖ
'ይድፋህ!' ሲል ጠላቴ ፥ ሲረግመኝ ጨክኖ፣
ጓዴ ግን ሳቀብኝ ፥ አንጀቱ እስኪቆስል
እርሱ ነው ወዳጄ ፥ የኔው ሌላ ምስል።
--------------------//--------------------------
( በርናባስ ከበደ )

@getem
@getem
@lula_al_greeko
#ዝም_ያለ_መሸታ

#አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)

የተጋባ ዋንጫ
ተደቅኖ ፊትሽ ፥ ጠላሽን ስጠማ
ቦለቲካው ይዞሽ
በሆዴ አመሀኝተሽ ፥ ጆሮዬ ሲደማ
በሰዎች ቋምጬ ፥ በዋጥኩት አረፋ
ከሳባ ጀምሮ
የነገርሽኝ ታሪክ ፥ በኔ ዘመን ጠፋ ።
ኧ........ረ #ቅጅልኝ !!
#ሆ !!......
እገሌ....... እንዲህ አደረገ
እገሌ........ ይህን አመጣ
በዚያን ዘመን ........የተገፋ
በዚህ ግዜ........ ቀኑ ወጣ
ይሄኛው ለሾርኒ ፥ ለቧልት ተቆጣ
ይህኛው ደንገጡር ፥ ጭን-ገረድ አወጣ
#የኔ_ዘር ....
#ያንተ_ዘር...
ይህን አወደመ
ይህን አመረተ
አትበይኝ ................ #ወ_ዘ_ተ
በሄድኩበት ሁሉ
ዘር ሽሉ እያደገ ፥ ወላድ እየሞተ
ቅርናት ቅርናት ቃና ፥ ሀገር እሳት ገብታ ፥ ስለተሻተተ
ልጠጣነው የመጣሁ...
እራሴን ልረሳ
የጆሮዬን ቅርሚያ ፥ ሳይወድል ላከሳ
ዝ.........ም ብለሽ ቅጅልኝ
ዝ..........ም ብዬ ልጠጣ
ለመሳም ካልሆነ በቀር
ከንፈርሽ አይንቀላወስ ፥ ምላስሽ ጉልበት አያውጣ።

@Abr_sh

@getem
@getem
@GETEM
#አንቺ #የኔ #ሽንኩርት
የቁሌቴ ጅምር ~ የጤንነቴ ፍንጭ
የጣእሜ መሰረት ~ የጥፍጥናዬ ምንጭ
አይተሽ ስትዘጊኝ ~ ሳይሽ ተቅለስልሼ
ስልጥሽ አነባሁ ~ ስገዛሽ አልቅሼ
#ደሞ
ሽንኩርቴ ነሽ ስልሽ ~ አትስጊ ግድ የለም
ውድነትሽን እንጂ ~ እድሜሽን አይደለም
===||===
ከሙሉቀን ሰ•

@getem
@getem
@getem
👍1
Recording (2)
Voice Recorder
#የኔ ሀሳብ
#የእኔ ፅሁፍ
#የእኔ ድምፅ
#2
#ምሉዕመገኘት
ርብቂ🥰

አስተያየት እንዲሁም የእናንተን ድምፅ
👇
@Ribki
@getem
@getem
#የኔ_ሌላ_ምስል
:
እንቅፋት አግኝቶኝ ፥ ስጓዝ በዱር በመንገድ
ከወገቤ ቢያጥፈኝ ፥ ሰላምታ እንደ መስገድ፣
ዘመዴ እጄን ሲይዝ ፥ 'እኔን!' ሲለኝ ፈጥኖ
'ይድፋህ!' ሲል ጠላቴ ፥ ሲረግመኝ ጨክኖ፣
ጓዴ ግን ሳቀብኝ ፥ አንጀቱ እስኪቆስል
እርሱ ነው ወዳጄ ፥ የኔው ሌላ ምስል።
--------------------//--------------------------
( በርናባስ ከበደ )

@getem
@getem
@lula_al_greeko
👍1
#የኔ_እጩ_ጄነራል

ነበልባሉ ~ ️ ፍቅሬ
ትንታግ ~️ ንግግሬ
ነጎድጓዱ ~ ️ድምፄ
ልበ ቆራጥ ~ ገፄ
ሳተናው ~️ መውደዴ
አንቀጥቅጡ ~ ክንዴ
ድል ቁርሱ ~ አንጀቴ
ቆራጡ ~ ️ እኔነቴ
ጀግናዉ ~ ️ማንነቴ
ሀገር ወዳድ ~️ ነብሴ
ሎጂስቲክሱ ~ ኪሴ
ግስላው ~ ️መንፈሴ
አቅም ገንቢ ~ ሀሳቤ
ማይበገር ~ ️ ልቤ
ሊቁ ~ አስተሳሰቤ
ካርታ አንባቢዉ ~️ አይኔ
የሰው ሀይሉ ~ ️ጎኔ
ንስሩ ~ እይታዬ
በአይኖችሽ ~ ካልታዬ
አልገለፅ ካለሽ ~ ከሰው ተለይቶ
ድሮን ግዢ ውዴ ~ ያሳይሽ አጉልቶ
===||===

@getem
@getem
@peppa


ከሙሉቀን ሰ•
👍1
#የኔ_ሴት
.
.
.
ያየኝ የለም ቆላ አልወጣሁም ደጋ፣
አልንከራተትም የኔን ሴት ፍለጋ።
ይሁን ካለ አምላክ ከፈቀደው ጌታ፣
ያመጣት የለም ወይ ካለሁበት ቦታ።

✍️ ዓቢይ ( @abiye12 )


@getem
@getem
@getem
67👍29🔥7🎉4🤩2