ግጥም ብቻ 📘
67.3K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
የሃሳብ መዲና የቀናቶች ወጉ
ማታ በእንቅልፍ ሰበብ ሸለብ ከማድረጉ
        ብቅ እልም...ብቅ እልም
       እውን አይሏት ወይ ህልም
   ዳበስ...ጨበጥ....ፈገግ...እቅፍ
               አይ እንቅልፍ
ታተራምሳለች ያረጋጋሁትን የቀልቤን ቀልበ ህግ
    ከተኛው በድኔ ምንድንነው ምትፈልግ
እየደጋገመች ሱስ ሆናብኝ ስትቀር በሌት ተ ሌት ድምር
መንቃቴን አቆምኩኝ ፈንጂ ቢፈነዳም ቢወርድብኝ ክምር
ትላንት ሆነ ዛሬ...
በህልም አያታለሁ እስኪበቃት ድረስ አይኗን እስክትሰብረው
በስመአብ.....እንዴት ነው ምታምረው።


ዮኒ
     ኣታን  @Yonatozz

@getem
@getem
@getem
👍2520🔥3
/ስምኝማ እኔም ናፍቀሽኛል!/
እረፍት ባጣም እንኳን ካንቺ ሚያገናኘኝ
በቀናቶች መሀል ላንቺ ቀኖች አሉኝ፤
እመኚኝ የኔ ውድ አይጠፋም ለኛ ቀን
በአንድ አገናኝቶ በፍቅር ሚያዋድቀን፤
ናፍቆት አይሎብን ቢረዝም መገናኛችን
እውነት አንድ ቀን አለ የብቻ የሁለታችን፤
ሰመመን ነው ናፍቆት ከሃሳብ ይከታል
አይሎም ሲበረታ ለራስ ይታክታል፤
እናማ በመናፈቅ ብዛት ሳልታክት ደክሜ
በቅርቡ አይሻለው ሳይበረታ እመሜ
😍😍😍
# M.G


@getem
@getem
👍426😱6😢4🔥1
Forwarded from ሥዕል ብቻ © (Leul M.)
Exhibition titled, “መልክ”
By Surafel Alemneh

Artawi Gallery
opened for public.

The galley opened  until 20 July 2024 starting from 2 PM - 6 PM bole, around British international school or 250m in from Yod Abyssinia, Kkare Homes, 2nd Floor


@seiloch
👍102
...
ይሆንልሽ እንደሁ እንደሰርፍ
ቦታን አጥፎ ማንጠፍ
ጨረቃ ድንቡል ቦቃ
ከሰማይ ሳይሆን ከኩሬ ስትወጣ
ማየት እንቻል ፤
ልጅ ነፍሰ ጡር ሲያይ እንደሚለው
« በጣም ጠግባለች ማለት ነው »
እንባባል?
ልጅ አይነ ስውር ሲያይ እንደሚለው
« ዐይኑን በዱላ የሚፈልግ ሰው »
እንባባል?
ትችይ እንደሆነ ጊዜን ታግሎ መጣል
ትችይ እንደሆነ ልጅነትን መቻል
ነይ በጉሎ ጥላ ፥ ቼ! በጉቶ ፈረስ
ከኋላዬ ሁኚ ፣ ወደፊት እንድረስ
.....

መዘክር ግርማ

@getem
@getem
@paappii
24👍13🔥1
አንጋፋው ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቶናል። ነቢይ ተርጓሚ ፣ ገጣሚ ወግ አዋቂ የጥበብ ሰው ነበር🥀


በሰላም እረፍ ጋሽ ነብይ መኮንን

@getem
😢51👍64🔥1😱1
ግጥምም ዝም አለ። ጨዋታም ዝም አለ።
ሰው መውደድ ዝም አል። ትሕትና ዝም አለ።
ነቢይ ያልነው ዋርካ፥ በአገሩ የት አለ !!

ነፍስ ሄር ጋሼ ! በደግ እረፍ!

#ሰይፉ_ወርቁ

@getem
😢39👍118
ገጣሚ ተሰፋሁን ከበደ እንዲህ ጋሸ ነብይን ተሰናብቷል!

ጋሽ ነባ ሳቅና ጨዋታህ ይናፍቀኛል
በብዙ ደግፈኸኛልና ስንብትህ ያጎድለኛል
አባቴም ጏደኛዬም መምህሬም ነህና እስከዘላለም በነፍሴ እድሜ ልክ እወድኻለሁ! አከብርኻለሁ!
መሰናበት እንኳን አልቻልኩም!
መልካም እረፍት
Rest in peace😢 farewell my friend
🙏😭🙏

እስረኛውና የሰጠመችው ፀሀይ
(ነቢይ መኮንን)

እድሜዬን በሙሉ
በአፌ ፈረስ ልጓም
እጄ ላይ ሰንሰለት
             ሲያኖሩ ስላየች
ፀሃይ ሰማይ በቅቷት
         ውሃ ሰጥማ ሞተች

ውሃ ውስጥ ተኝታ
ከኔ ትዋሳለች፣ ይኸው ብርሃን አጥታ።


@getem
😢21👍206
ትንሽ ቦታ
....................
በዚህ ዓመት፣
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሽ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ብቻ መሠደጃ።
ምናለበት፣
ለምን አልባት ብንተውለት?
ፍፁም መሆን ስለማንችል
ትንሽ ባዶ እንዋዋል፣በልባችን ደግ በኩል።
ለአንጎላችን መላወሻ
ትንሽ ቦታ እንተውለት
''ምናልባት'' የምንልበት !!
ልክ እንደ አምና - በዚህ ዓመት ።
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብለን መታሰሪያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ
ጥግ ድረስ የለም ስራ፣ጥግ ድረስ የለም ፋታ።
በልባችን ደግ በኩል፣እንፈልግ ባዶ ቦታ፣
የጳጉሜ አይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለወጫ።

ነብይ መኮንን!

@getem
42👍16🔥1
ነፍስ ደጃፍ ከርመው በድንን የረሱ
ጥቂት ሰዎች አሉ ከሞቱም ብሃላ
የሚተነፍሱ !
~~
ጋሽ ነብይ መኮንን ከጥቂቶቹ መሀል ነው በሰላም እረፍ የመንገዴ ሰው !!!

( ካሊድ አቅሉ)

@getem
@getem
@paappii
😢179👍7
😭


በትዝታ ወደ ኋላ
ወደ አማልዕክት ገላ
ገብቶ ለመሸቅ
በላብ ለዠመዋዠቅ
አንድት ነጥብ መዞ
በጉም ተፈናጦ በትዝታ ጉዞ

ወደ አንድት ቅፅበት
ሲቃ ወደተሞላበት
ወደ ናርዶስ ጠረን
ወደ ብልግና መረን
ወደ ራቁት ገላ
ወደ ሸት ዘለላ
ወደ እኔ አማልዕክ
አንድ ቀን የመኖሬ ምልክት
ወደ ዛች ማስረጃ
በደመና መጋረጃ
ወደ ዛች አቅጣጫ


ያችኑ ቀን መርጦ
መጋረጃ ገልጦ
ከእግዜር ፍጥረት በልጦ
ጉዞ ወደ ኋላ
ወደ ሚሹት ገላ


ወደ ዛቹ ቅፅበት
ነፍሴ ካለችበት
በትዝታ ፈረስ
ወደዛው መገስገስ


አወዬው ተዝታ ከአሁን መብለጡ
የተዳፈነ እሳት ረመጥ መግለጡ



by kerim

@getem
@getem
@getem
👍255🤩1
ምን አይነት ውበት ነው

ዕፁብ ቁንጅናዋን እግዚሄሯ ሲፈጥራት
እንደ ፅጌረዳ አስውቦ ያሳመራት
የሀገር ቅብ ማዛን አላብሶ የሰራት
. ምን አይነት ውበት ነው
በውበቷ ድምቀት አዋፋት ተገርመው
በግቢዋ አጥር ላይ በደጇ በር ቆመው
ሀረጋትን ፅፈው መጥነው ቀመሩ
ለሷ ዜማን ሰርተው ለፍቅሯ ዘመሩ
ምን አይነት ውበት ነው
ጨረቃና ፀሀይ ኩባኩብት ጨምረው
ፍፁም አይደርሷትም ከሷ ተወዳድረው
መልኳ ፊደል ሰርቶ ጎልቶ ይነበባል
እልፍ ቅኔን ፅፎ ቃላትን ያዘንባል
ፊደልን ከፊደል
ሰምና ወርቅ አርጎ አዋዝቶ ያግባባል
ሰንደቅ አይሰቀል ትኑር በመቅደሷ
የሀገርን ቀለም
ጎልታ ለማሳዬት ትበቃለች እሷ
በሀገር ውብ ቀለም የተሰራው ልብሷ
ከሩቅ ጎልቶ ሚታይ ሰንደቋ ነው ለሷ

By @Habtishe01

@getem
@getem
@getem
👍2515🔥1
-------

እዚህ ፎቶ ስር ሶስት ሰዎች ይታዩታኛል..
ገብሬ ፣ አብዬ መንግስቱ እና ጋሽ ነብይ!

አይ ማማር
አይ ውበት
አይ ግዜ
አይ ዘመን....

''They bared their brains to heaven..'' ይላል allen የታላላቆቹን ሞት ማለፍ ከሰሟ በኋላ!

የታላላቆቹ ማለፍ ምድር ላይ ለቀሩ ዋይታ
ለሰማይ ደግሞ ደስ የሚል ፈገግታ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም።
ሚቀበሏቸውን ፣ ሚገናኟቸውን ማሰብ አካሄዳቸውን መከተል ያስመኛል።
እጆቻቸውን ይዞ ወደ ሚሄዱበት አብሮ መጎዝ...
ወደዛ ደስ ወደሚሉት ሰዎች...

የታላላቆቹ ማለፍ ታላቅ ሀዘን ብቻ ሳይሆን የሚጥልብን እነሱን የመከተል ፣ እነሱን የመፈለግ መሪር ናፍቆት ያሸክመናል።
ደጋጎቹ ሁሉ ጥለውን አንዲት ትንሽ ቦታ ይበሰባሉ።
እዚህ የኖሩትን ተሰብስበው ይደግሙታል።
ዘላለም የሚያምር ነገር መስራት አይደክማቸው እነሱ እንደሆነ...

እንደ ነብይ ያሉ ሰዎች በሰማይ እና በምድር መሀከል ያለውን ወግ የሚያገነኙ ድልድዮች ነበሩ።
ከእንግዲህ ስለ ትናንት ማን ይነግረናል?
ስለ ሚያማምሩት ሰዎች ማን ያጫውተናል?

በህይወት ያሉት በሞቱት ይቀናሉ! ማለት ይሄ ነው።

ነፍስ ይማር ጋሽ ነብይ!

#ይስሃቅ_አብርሃም

@getem
😢21👍203
ለናዝሬት ( አዳማ ) ልጆች!
****
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ

የናዝሬቱ ምልክት ፣ የአጼ ገላውዲዮሱ ጥበበኛ ነብይ መኮንን አዲስ አበባ ቢሆን የሚቀበረው ሥላሴ ይቀበራል።
የሚያውቀውም የሚያደንቀውም ይሄዳል። ራሱ ሰውየው ግን ናዝሬትን ፣ ማሪያም ቤተክርስቲያንን ፣ ከእናቱ አጠገብ ማረፍን መረጠ ። እኛን መረጠ ። እንግዲህ ነብይ ራሱ የለም። ቤተሰቦቹም የሉም። ታዛቢ የለም። ቀብሩ በክብሩ ልክ ላይደምቅ ይችላል። ከአዲስ አበባ ናዝሬት ለቀብር የሚሄደው ሰው በጣም ላይበዛ ይላል ( ከበዛ እሰየው )። እስቲ የናዝሬት ልጆች ፣ አዋቂ አዛውንቱ እንደ አፋር ዳጉ ስርዓት ተጠራሩና ወንድማችሁን ሸኙት ። እስቲ ተደዋወሉና 9:00 ሰዓት ማሪያም ቤተክርስቲያን ኑ ። አንድ ሰዓት አይወስድም ። ነብይን ብትወዱትም ፣ ባትወዱትም ፣ ብትቀርቡትም ባታውቁትም እስቲ ኑ ። እስቲ ተደዋወሉና " 9:00 ሰዓት ማሪያም ቤተክርስቲያን ነብይን እነሸኘው " ተባባሉ ።
እስቲ ኑ !!!!!!!!!

#SHARE በማድረግ ይህን መልዕክት ያዳርሱልን።

@getem
@getem
37👍21😢6
ጥቁር ነጭ ግራጫ
(ነብይ መኮንን)

...ሰው እያለ አጠገባችን
ቅንነቱን ማየት ሲያመን
ከኛ አብሮ በሕይወት ቆሞ ፤ መልካሙን ስምን
መጥራት ሲያንቀን
"ሰው ካልሞተ ወይ ካልሄደ አይነሳም" እንላለን
እንዲህ እያልን፤
ስንቱን ጠቢብ እየሸኘን፤
አበባውን ቀጥፈን ጥለን፤ አበባ (እ)ናስቀምጣለን።



@getem
22👍19😱1
እድሜ ነዉ እንጂ
ግዜ ያጠረኝ፣
ፍቅር የሚሻ
ልብ ነበረኝ።

By Adab

@getem
@getem
@paappii
42👍16😱1
መሔጃ የለኝ !
ካይኖችሽ ብሸሽ ፥ ቅንድብሽ ስር ነኝ ።
ወዴትም ብዞር
ገላሽ ብቻ ነው ፥ የሚያዋስነኝ ።
ቅርቤም - ሩቄ
ኩነኔም - ጽድቄ
ከህጎች በልጦ ፥ ልብሽ የሚያዘኝ
ሙዚቃሽ ብቻ የሚያስደንሰኝ ።

ጠዋት ብጠላሽ ፥ ማታ ምወድሽ
ምንም ቢሰማኝ ፥ የማላመልጥሽ
ወስልቼ ብሄድ ከገላሽ ምሕዋር
ተኝቼ ምገኝ ፥ ከትዝታሽ ጋር ፥
ወዲህም ሳራ ፥ ወዲህም አጋር !

አይንሽ እንደ ጥላ
ከኋላ ከኋላ
ሳይከታተለኝ
እምነትሽ ብቻውን ሸብቦ 'ሚያስቀረኝ
ያንቺው ግዞተኛ ፥ ያንቺው ታሳሪ ነኝ !

@getem
@getem
@paappii

By Habtamu Hadera
40👍20
የፊቱን እያየ የኋላውን ትቶ
ማንነቱ ጠፍቶት እልህ ጋ ተጋብቶ
          ጎጆውን ቀልሶ
ማን እንደነበረ ረስቶት ጨርሶ
የገዛ እልሁ ደፋው ከፊት ደርሶ።

ብላችሁ ንገሩ
ላገር ለመንደሩ
በምን ጠፋ ቢሉ!


ዮኒ
     ኣታን   @yonatoz

@getem
@getem
@getem
👍345
የህይዎት ጣዕም
የህይዎት ጠረን

ውብ ብርጭቆ
ቆንጆ ሲኒ ፤
ትኩስ ቡና
ቀዝቃዛ ወይን ፤
የሞላበት ።

ቀዝቃዛ እድሜ
ወጣት ደረት ፤
ትኩስ ሌሊት
የሚያድግበት ።

ቀዝቃዛ እኔ
በረዶ እኔ ፤
ትኩስ አንቺ ያለሽበት ።

የህይዎት ጣዕም
የህይዎት ውበት

ቀዝቃዛ ሻይ
እጅሽ መሃል የበረደ ፤

ግማሽ እድሜ
አንቺን ሲያስብ የነጎደ ፤

ጅምር ሀሳብ
ጅምር ግጥም
ጠርቶ ያመጣው ፤

ውብ ወዘና
ጎረምሳ ሌት የሚጠጣው ።

የህይዎት መልክ
የህይዎት እድሜ

የአንቺ በራፍ
የአንቺ መስኮት ፤

የዓይን ፍቅር
በዓይን ስርቆት ፤

ትንሽ ቁስል
እድሜን ሙሉ ትዝ የምትል ፤

የአንቺ ፍቅር
ስር የሚሰድድ ከጅማት ስር ፤

የህይዎት ጣዕም
የህይዎት ውበት

መኖር ሳስቶ
ፍቅርን መስሎ ፤

መኖር ሳስቶ
ገላን ጥሎ
' የለምን' ያህል አክሎ ።

#ቴዎድሮስ_ካሳ

@getem
@getem
👍4542🔥1😱1
#በቅንነት__በኩል
#ትንሽ__እንቸኩል

እንኳን መ'ረንበት
_ እሬት ሆነን ለሰው . . .
ለመክሰል ለመቁሰል
____ ኑሮ መች አነሰው ?

ለዕለት ጉርስ
ለዓመት ጨርቅ ____ ለአንዲት ቁራጭ ታዛ
ደም እየገበረ
ላብ እየሠፈረ ____ ተስፋ ለሚገዛ

ያለ'ድሜ
ለሚጎብጥ ____ ለመልካችን አምሣል
ለመክሰል
ለመቁሰል ____ ሕይወት መቼ ያንሳል ?

ምናለበት ታድያ
__ ከሁሉ ዓይኖች ጋራ __ በቅን መተያየት ?
ሸክም ላለ'በት ሰው
__ ውለታ ሳይቆጥሩ _ ትንሽ ይቅር ማለት ?


°°
ትንሽ : ለፈገግታ
ምክንያት : ማፈላለግ
በደግነት : ማከም
የሕመምን : ፈለግ
ቃል : አለማ'ራገብ
የምላስን : እሳት
እየሰሙ : ማለፍ
ቶሎ : ቶሎ : መርሳት

ከአፍ : እየቀደሙ ____ ፍቅር : ብቻ : መልቀም
ሰውን : በዚህ : መውደድ
ሰውን : በዚህ : ማከም
በሰዎች : ድካም : ውስጥ ___ እራስን : ማየት : መቻል
ለእግዜርም _ ለእራስም __ ለሰውም : ይመቻል

°°

መውቀስ
መክሰስ
መርገም
የሳቱትን : መድገም
እንኳን : ድኩም : ገላን ____ነፍስን : ያሰለቻል !

ዓለምም
ፍጥረትም
ዘመንም
ሕይወትም
እውነትም
እምነትም
___ ሳይደርሱበት : ያልቃል ፤
አንድ : ሰው
አንድ : ልብ
አንድ : ዕድሜ
አንድ : አካል
እንኳንስ : ለክፋት ____ ለፍቅር : መች : ይበቃል ?

°°
ታዲያ . . .

ለዚህ : ሁሉ : መግቻ
ለዚህ : ሁሉ : መፍቻ
ለዚህ : ሁሉ : መርቻ

| ቶሎ : ቶሎ : መውደድ ____ ይቅር : ማለት : ብቻ |

••
የበለዙ ልቦች
___ በተስፋ እንድንኩል
በቅንነት በኩል
___ ትንሽ እንቸኩል ።
••
°°
Seifu Worku

@getem
@getem
👍8245🔥6🎉3👎1😱1
---- ---- ---- ---- ---- ----- ----- ----- ----- ----- -----
---- ---- ---- ---- ---- ----- ----- ----- ----- ----- -----
ምን አዲስ? አትበሉኝ

ማሳሳም ያቆምኩት፤ ጆሮዬን ከስልኪቱ
ሳልወጣ ከጎጆዬ፤ የዋልኩት በከንቱ
ገልመጥ ገልመጥ፤ የሚያደርገኝ እኔን
አዪኝ አላዪኝ፤ ምጫወት ብቻዬን

ብታሸብረኝ፤ አንዲት ጥያቄ
ምጨነቅባት፤ መልሷን ባለማወቄ

ምን አዲስ? አትበሉኝ፤
አዲስ የለም ከኔ
ፀሀይ አርቃለች፤ ስርዓቷን ከጎኔ
ጊዜው ተገትሯል አይነጋም አይመሽም
አለም እየዞረች፤ እኔጋ አትደርስም

ምን አዲስ? አትበሉኝ፤
አትጠብቁ መልስም
አዲስ አይገኝም፤ ከራቀችው አለም
ፊቷን ካዞረችም፤ አድርጋውም ባዳ
አዲስ አይገኝም፤ ለዛ ሰው እንግዳ።


        ✍️ ኒቆዲሞስ
                        @niko_nikodimos1

---- ---- ---- ---- ---- ----- ----- ----- ----- ----- ----
---- ---- ---- ---- ---- ----- ----- ----- ----- ----- ----
     @getem
                   @getem
                                  @getem
👍5124🔥1