[የሌሊት ራዕይ....]
🌟
አሮጊት ኮከቦች....
እንደ ፍም አብርተው....
ከሌሊቱ ሰማይ— ረከቦት ሰርተው ፤
(ነጭ ጉም — ስኒ ዘርግተው ፤)
በጨለማ በራድ — በድቅድቅ ጀበና
(ከሩቅ ተጠራርተው ይሰበሰቡና....)
ያፈላሉ — ቡና ።
🌟
በስብሰባው መሀል....
አቦል እየጠጡ — ጨረቃን ያሟታል ፤
(እንደዚህ ይሏታል....)
“አብራን እየኖረች እኛን ያልመሰለች
ከህብረት ከቡድን የተገነጠለች
ይቺ ' ቅርፀ ጥፉ ' የተድቦለቦለች....!”
🌒
እሷም ትሰማለች...
(ጎረቤት አይደለች?!)
መልኳ ያስጠላታል ፤
እንደ`ነሱ ሆና...
(ያፈሉትን ቡና...)
መጠጣት ይምራታል ።
(ቀረብ ትላለች....)
“አምራለሁ ብላ ነው ከእኛ መለየቷ?!
እኛን ለመብለጥ ነው ገዝፋ መታየቷ?!”
(ሲሉ ትሰማለች...)
አንገት ትደፋለች ....
(ብቻዋን አይደለች!?)
ሀሜት ይሰብራታል
አንሳ ትጠፋለች ።
🌒
[በራስ መንገድ መቆም ...
የሚያኖር አይደለም ፥
መንጋ መልቀቅ የለም!
'መለየት'-- 'ማፈንገጥ' ...
በሆነበት ዓለም...
በልዩነት መኖር — መቼ ይወደዳል!?
የህላዌ ህጉ — መምሰል ያስገድዳል ።]
🌒
(እኒህ አሮጊቶች....)
ሽሙጥ ሀሜታቸው በርዶ ካላበቃ ፤
ተፈጥሮ ስሪቷን
(ልዩ ማንነቷን)
ገላዋን አውልቃ ፤
ኮከብ ትሆናለች — አንድቀን ጨረቃ ።
_
ህዳር ፳፮—፪፼፲፮ ዓ.ም
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
🌟
አሮጊት ኮከቦች....
እንደ ፍም አብርተው....
ከሌሊቱ ሰማይ— ረከቦት ሰርተው ፤
(ነጭ ጉም — ስኒ ዘርግተው ፤)
በጨለማ በራድ — በድቅድቅ ጀበና
(ከሩቅ ተጠራርተው ይሰበሰቡና....)
ያፈላሉ — ቡና ።
🌟
በስብሰባው መሀል....
አቦል እየጠጡ — ጨረቃን ያሟታል ፤
(እንደዚህ ይሏታል....)
“አብራን እየኖረች እኛን ያልመሰለች
ከህብረት ከቡድን የተገነጠለች
ይቺ ' ቅርፀ ጥፉ ' የተድቦለቦለች....!”
🌒
እሷም ትሰማለች...
(ጎረቤት አይደለች?!)
መልኳ ያስጠላታል ፤
እንደ`ነሱ ሆና...
(ያፈሉትን ቡና...)
መጠጣት ይምራታል ።
(ቀረብ ትላለች....)
“አምራለሁ ብላ ነው ከእኛ መለየቷ?!
እኛን ለመብለጥ ነው ገዝፋ መታየቷ?!”
(ሲሉ ትሰማለች...)
አንገት ትደፋለች ....
(ብቻዋን አይደለች!?)
ሀሜት ይሰብራታል
አንሳ ትጠፋለች ።
🌒
[በራስ መንገድ መቆም ...
የሚያኖር አይደለም ፥
መንጋ መልቀቅ የለም!
'መለየት'-- 'ማፈንገጥ' ...
በሆነበት ዓለም...
በልዩነት መኖር — መቼ ይወደዳል!?
የህላዌ ህጉ — መምሰል ያስገድዳል ።]
🌒
(እኒህ አሮጊቶች....)
ሽሙጥ ሀሜታቸው በርዶ ካላበቃ ፤
ተፈጥሮ ስሪቷን
(ልዩ ማንነቷን)
ገላዋን አውልቃ ፤
ኮከብ ትሆናለች — አንድቀን ጨረቃ ።
_
ህዳር ፳፮—፪፼፲፮ ዓ.ም
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
👍91❤40🔥6😁5🤩2
ለማታዉቀኝ 2 ✍️በዔደን
<unknown>
❤18👍10
ስንኩልኩል ተራማጅ በኃጥያት ቦይ ፈሳሽ
ቀና ብዬ ማላይ የህይወቴን ቀያሽ፤
እንደነገሩ ሂያጅ
እንዳሻኝ ወራጅ
ነጥዬ ማላውቅ ጠላት እና ወዳጅ፡
ስንፏቀቅ የምኖር ውድቀት ተንተርሼ
ዘመኔን የበላሁ
ራሴን የጎዳሁ አዳኜን ነክሼ።
የእውር ድንብር ተጓዥ ስንኩልኩል ወልካፋ
እየሄድኩ አልነበር ራሴን ላስጠፋ
ታዲያ እንዴት ተረፍኩ?
እስትንፋስን ታቀፍኩ?
መውደቂያዬን ሚያቆም መጥፊያዬን ሚያድን
ምን ነበር እኔጋ ፈዋሽ የቁም በድን?
ምንም!
ማንም!
እንዴ...
ወይ ጉዴ
ረስቼህ አልነበር ... እንዴት አስታወስከኝ
ንቀት ግፌን ትተህ እንደምን ታደግከኝ
ጥል ምርኩዝ ሲጥለኝ እንደምን ደገፍከኝ።
እንዴት ታዘዘልህ ክንፍህ እኔን ሊጋርድ
ገፍትሬህ አይደለ እንዲህ ምንገዳገድ።
ሚካኤል አባቴ
ጉዞዬ ወደ ምሬት መንገዴ ወደ ሞት
የት አግኝተህ ቀየርክ የኔን ስብር ህይወት
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
ቀና ብዬ ማላይ የህይወቴን ቀያሽ፤
እንደነገሩ ሂያጅ
እንዳሻኝ ወራጅ
ነጥዬ ማላውቅ ጠላት እና ወዳጅ፡
ስንፏቀቅ የምኖር ውድቀት ተንተርሼ
ዘመኔን የበላሁ
ራሴን የጎዳሁ አዳኜን ነክሼ።
የእውር ድንብር ተጓዥ ስንኩልኩል ወልካፋ
እየሄድኩ አልነበር ራሴን ላስጠፋ
ታዲያ እንዴት ተረፍኩ?
እስትንፋስን ታቀፍኩ?
መውደቂያዬን ሚያቆም መጥፊያዬን ሚያድን
ምን ነበር እኔጋ ፈዋሽ የቁም በድን?
ምንም!
ማንም!
እንዴ...
ወይ ጉዴ
ረስቼህ አልነበር ... እንዴት አስታወስከኝ
ንቀት ግፌን ትተህ እንደምን ታደግከኝ
ጥል ምርኩዝ ሲጥለኝ እንደምን ደገፍከኝ።
እንዴት ታዘዘልህ ክንፍህ እኔን ሊጋርድ
ገፍትሬህ አይደለ እንዲህ ምንገዳገድ።
ሚካኤል አባቴ
ጉዞዬ ወደ ምሬት መንገዴ ወደ ሞት
የት አግኝተህ ቀየርክ የኔን ስብር ህይወት
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
❤37👍25👎1
#ህመም_አሞኝ_ያውቃል!
የሚያስጨንቅ የሚከፋ
አለ ሲሉት የሚጠፋ
የለም ሲሉት አለው የሚል
ስቃይ ሲሉት ደስ ደስ የሚል
የሚያደቀኝ በስልብ ቃል
ህመም ሚሉት አሞኝ ያውቃል።
#በድኔንም_ልክ_እንደዛው!
ያወሩኝ 'ለት አልነበርኩም
ሲጠላልፉኝ አልወደኩም
አታለሉኝ በመሃል ላይ በድን በድን በሚለው ቃል
አዎን ልክ እንደዛው...በድኔንም አሞኝ ያውቃል።
#እራሴንም_ምታት_መታው!
ስንለያይ ስትጨክን በጌታ ቃል ተማምላ
ከቆምኩበት ጥላኝ ስትሄድ ስትመልሰኝ ወደኋላ
ጭንቀት ቢጤ ሲጫርብኝ አስጨፍነው ለሚቀብሩት
ራሴንም ምታት ነገር ጠጋ ብለው አወራሩት።
#ማመኔንም_እምነት_ነሳው!
"አፈቀርኩህ" ስትል "አፈቀርኩሽ" ያልኳት
"ትበልጣለህ" ስትል በጭፍን ያመንኳት
ሳወራላት ስኖር የሚቆጨኝን ቃል
ማመኔንም አሞኝ ያውቃል።
#ህይወቴንም_አሞኝ_ነበር!
አጨብጭቤ ያስጨበትኳት
ስጦታ ነው ብዬ የላኳት
የሚሰማኝ እየጫረ
ከጓድ በላይ እኔን ለኔ የመከረ
ህይወቴንም ታምሜ ነበረ።
#ህሊናዬን_ጎድቻለሁ!
ወሰንኩና ውሳኔዎች ተናገርኳት እስኪበቃት
የተጠጋት ቆሌ መንፈስ ካጠገቧ እስኪርቃት
ተናደድኩኝ ከልክ በላይ አናደድኳት ልክ እንደኔው
ህሊናዬን ጎድቻለው በንዴት ቃል እኔው ለኔው።
የድባቴ መንፈስ ሲከናነብ አካላቴን
እንባ ሚሉት ውሃ ተናንቆት ህይወቴን
ገደል ገደል ሚያስመኝ የክፉ መንፈስ ቃል
#ተፈጥሮዬም_ታሞ_ያውቃል!
#mikiyas_feyisa
ዮኒ
ኣታን @yonatozz
@getem
@getem
@getem
የሚያስጨንቅ የሚከፋ
አለ ሲሉት የሚጠፋ
የለም ሲሉት አለው የሚል
ስቃይ ሲሉት ደስ ደስ የሚል
የሚያደቀኝ በስልብ ቃል
ህመም ሚሉት አሞኝ ያውቃል።
#በድኔንም_ልክ_እንደዛው!
ያወሩኝ 'ለት አልነበርኩም
ሲጠላልፉኝ አልወደኩም
አታለሉኝ በመሃል ላይ በድን በድን በሚለው ቃል
አዎን ልክ እንደዛው...በድኔንም አሞኝ ያውቃል።
#እራሴንም_ምታት_መታው!
ስንለያይ ስትጨክን በጌታ ቃል ተማምላ
ከቆምኩበት ጥላኝ ስትሄድ ስትመልሰኝ ወደኋላ
ጭንቀት ቢጤ ሲጫርብኝ አስጨፍነው ለሚቀብሩት
ራሴንም ምታት ነገር ጠጋ ብለው አወራሩት።
#ማመኔንም_እምነት_ነሳው!
"አፈቀርኩህ" ስትል "አፈቀርኩሽ" ያልኳት
"ትበልጣለህ" ስትል በጭፍን ያመንኳት
ሳወራላት ስኖር የሚቆጨኝን ቃል
ማመኔንም አሞኝ ያውቃል።
#ህይወቴንም_አሞኝ_ነበር!
አጨብጭቤ ያስጨበትኳት
ስጦታ ነው ብዬ የላኳት
የሚሰማኝ እየጫረ
ከጓድ በላይ እኔን ለኔ የመከረ
ህይወቴንም ታምሜ ነበረ።
#ህሊናዬን_ጎድቻለሁ!
ወሰንኩና ውሳኔዎች ተናገርኳት እስኪበቃት
የተጠጋት ቆሌ መንፈስ ካጠገቧ እስኪርቃት
ተናደድኩኝ ከልክ በላይ አናደድኳት ልክ እንደኔው
ህሊናዬን ጎድቻለው በንዴት ቃል እኔው ለኔው።
የድባቴ መንፈስ ሲከናነብ አካላቴን
እንባ ሚሉት ውሃ ተናንቆት ህይወቴን
ገደል ገደል ሚያስመኝ የክፉ መንፈስ ቃል
#ተፈጥሮዬም_ታሞ_ያውቃል!
#mikiyas_feyisa
ዮኒ
ኣታን @yonatozz
@getem
@getem
@getem
👍53❤30🔥3👎1
አምላኬ
አይኖችሽ ይሉኛል እንደምትወጂኝ
አፍሽ ይነግረኛለ እንደማትወጂኝ
ታድያ የቱን ልመን
አፍሽ አዬገፋኝ አይንሽ ሲጎትተኝ
ልብሽ ምን እንደሚል ማወቅ ሲያዳግተኝ
ልቤን ልመን ይሆን ?
ልቤ የሚለኝን ወደ አምላክ ቅረብ
አንድት እፁብ ለምን ድልድይህን ጥረብ
ስትራምድ እንዳይጎዳህ ስትሻገር ወደ እሷ
መለያዬት እንዲያከትም ተጓዝ ወደ ነፍሷ
ከአንድ ልብ አንድ ነፍስ እንዲያጣምርህ
ተጠጋ ወደ አላህ ቅረብ ወደ እግዜርህ
ይለኛል
አምላኬ
ታነብልኚ ይሆን የአይኖቿን ሚስጥር
ሰብረህ ትገባለህ ወደ ልቧ ቅጥር?
አምላኬ
By kerim
@getem
@getem
@getem
አይኖችሽ ይሉኛል እንደምትወጂኝ
አፍሽ ይነግረኛለ እንደማትወጂኝ
ታድያ የቱን ልመን
አፍሽ አዬገፋኝ አይንሽ ሲጎትተኝ
ልብሽ ምን እንደሚል ማወቅ ሲያዳግተኝ
ልቤን ልመን ይሆን ?
ልቤ የሚለኝን ወደ አምላክ ቅረብ
አንድት እፁብ ለምን ድልድይህን ጥረብ
ስትራምድ እንዳይጎዳህ ስትሻገር ወደ እሷ
መለያዬት እንዲያከትም ተጓዝ ወደ ነፍሷ
ከአንድ ልብ አንድ ነፍስ እንዲያጣምርህ
ተጠጋ ወደ አላህ ቅረብ ወደ እግዜርህ
ይለኛል
አምላኬ
ታነብልኚ ይሆን የአይኖቿን ሚስጥር
ሰብረህ ትገባለህ ወደ ልቧ ቅጥር?
አምላኬ
By kerim
@getem
@getem
@getem
👍61❤11👎3
¹
“ግፋ” ብለኸው — እግርህን
እያፈስስከው — ላብህን
ስታሯሩጣት — ወደ ፊት...
(ስትከተላት ህልምህን ...)
አሁን ግን በቃህ — ደክሞሃል
አየሁህ መንገድ — ወድቀሃል ።
•
“በርታ - ተነስ” — አልልህም
“” ደግመህ ሩጥ” — አልልህም
(“ውደቅ እረፍ” — ግዴለህም ።)
♟️
ያቺን ብሩህ ጊዜ...
(ያቺን ፍፁም ደስታ....)
ሮጠህ ብታጣት፤
ወድቀህ ፋታ ስጣት ።
(ወይም ደግሞ ቆመህ
በሩቅ ተመልከታት....)
ወዴትም አትሄድም....
ክብ ነው መሮጫው.....
(ምድርስ ክብ አይደለች?!)
ት ደ ር ስ ል ሃ ለ ች — ባትደርስባትም ፤
ወደ ፊት መሄድ ነው — እርምጃ መግታትም።
---
(አትልፋ ደጋግመህ ....)
እጅ ስጥ ግዴለም — “በቃኝ” በል አንዳንዴ ፤
ተስፋ ካልቆረጡት — ይቀጠላል እንዴ ?!
♟️
[ተራራ ሲገፉ....
ወደ ላይ ሲከንፉ...
ሰማይ የፈለጉት...
መሬት ወድቆ እንደሆን
መች ያስተውሉታል !?
(ዕድሜ ይስጠው ድካም)
ሲሮጡ ያጡትን — ሲያርፉ ያገኙታል ። ]
——
²
አንተም ወዳጄ ምስኪኑ እረኛ ፤
(ፍሬ ለማውረድ....)
መዝለልህ ይብቃ....
ዛፉ ስር ተኛ ።
•
(መተው መልካም ነው....)
“አልቻልኩም” ማለት ያስችልልሃል ፤
(ሽቅብ ወደ ላይ ስትንጠራራ...)
ያልደረስክበት ጣፋጩ ፍሬ....
ሲበስል መሬት — ይወድቅልሃል ።
“ተነስ” — አልልህም...
“ሩጥ” — አልልህም....
“እረፍ” — ግዴለህም ።
_
@Bekalushumye
ታህሳስ ፪ — ፳፲፮ ዓ.ም
@getem
@getem
@getem
“ግፋ” ብለኸው — እግርህን
እያፈስስከው — ላብህን
ስታሯሩጣት — ወደ ፊት...
(ስትከተላት ህልምህን ...)
አሁን ግን በቃህ — ደክሞሃል
አየሁህ መንገድ — ወድቀሃል ።
•
“በርታ - ተነስ” — አልልህም
“” ደግመህ ሩጥ” — አልልህም
(“ውደቅ እረፍ” — ግዴለህም ።)
♟️
ያቺን ብሩህ ጊዜ...
(ያቺን ፍፁም ደስታ....)
ሮጠህ ብታጣት፤
ወድቀህ ፋታ ስጣት ።
(ወይም ደግሞ ቆመህ
በሩቅ ተመልከታት....)
ወዴትም አትሄድም....
ክብ ነው መሮጫው.....
(ምድርስ ክብ አይደለች?!)
ት ደ ር ስ ል ሃ ለ ች — ባትደርስባትም ፤
ወደ ፊት መሄድ ነው — እርምጃ መግታትም።
---
(አትልፋ ደጋግመህ ....)
እጅ ስጥ ግዴለም — “በቃኝ” በል አንዳንዴ ፤
ተስፋ ካልቆረጡት — ይቀጠላል እንዴ ?!
♟️
[ተራራ ሲገፉ....
ወደ ላይ ሲከንፉ...
ሰማይ የፈለጉት...
መሬት ወድቆ እንደሆን
መች ያስተውሉታል !?
(ዕድሜ ይስጠው ድካም)
ሲሮጡ ያጡትን — ሲያርፉ ያገኙታል ። ]
——
²
አንተም ወዳጄ ምስኪኑ እረኛ ፤
(ፍሬ ለማውረድ....)
መዝለልህ ይብቃ....
ዛፉ ስር ተኛ ።
•
(መተው መልካም ነው....)
“አልቻልኩም” ማለት ያስችልልሃል ፤
(ሽቅብ ወደ ላይ ስትንጠራራ...)
ያልደረስክበት ጣፋጩ ፍሬ....
ሲበስል መሬት — ይወድቅልሃል ።
“ተነስ” — አልልህም...
“ሩጥ” — አልልህም....
“እረፍ” — ግዴለህም ።
_
@Bekalushumye
ታህሳስ ፪ — ፳፲፮ ዓ.ም
@getem
@getem
@getem
❤46👍42🔥6👎1
¹
ፍቅርንስ ያፍቅሯት ጌቶች ....
(መውደድ በእነሱ ያምራል )
በልዑላኑ — በሀያላኑ —
በንጉሦቹ ፤
(በፈላጭ በቆራጮቹ )
ጊዜም ስልጣንም ባላቸው ፤
ሁሉን በሚቻላቸው ።
(እንደ እኔ አይደሉም እነሱ....)
የልብን መሻት ይሞላሉ ....
እንባን ማበስ ይችላሉ ....
(ለሚጠሉት ባይሆን እንኳን )
ለሚወዱት ይደርሳሉ ።
(ለምን ወደድኩሽ እኔ ግን?)
“መውደድ” (የንጉሥ ዘመድ)
በባሪያ ልብ ምን ይሰራል?
ላፈቀሩት ካልደረሱ ....
ማፍቀር ብቻ ምኑ ያምራል?
•
ባይሽም በእሳት መካከል
ባለጊዜ ሲያንገላታሽ
ቢሰማኝ ጩኸት እሪታሽ
አድንሽ ዘንድ ....
(አተርፍሽ ዘንድ )
አቅመቢስ ነኝ ድኩም ባሪያ
ስስ ጉልበቴ አንሶብኛል ፤
ታዲያ ....
(“ደረስኩልሽ” ማለት አቅቶኝ)
“ወደድኩሽ” ብል ያምርብኛል?
•
ለወደዱት አካል ለወደዱት ገላ ....
ለመድረስ የሚችል ከሌለበት አቅም
ያሳምማል እንጂ መውደድ ምን ሊጠቅም?
ካላበስኩልሽ እንባሽን
ካላከምኩት ህመምሽን
ካላተርፍኩት....
ቆሜ ካየሁት ልብሽ ሲሰበር ፤
ባልወድሽ ይሻለኝ ነበር ።
²
ፍቅርንስ ያፍቅሯት ጌቶች....
(መውደድ ያምራል በእነሱ ፤)
ቀላል ነው እንባ ማበሱ ፤
(ላፈቀሩት ሰው መድረሱ ። )
ጌታም ራሱ ሁሉን የሚችል....
(የማርያም ልጇ) የዓለም ንጉሥ ነው
ስለመውደዱ ተሰቅሎ ያልፋል ፤
ደሙን አፍስሶ ፍቅሩን ያተርፋል ፤
ሞቱ እንኳን ሚዛን ይደፋል ።
(ታውቂያለሽ ይሄንን)
የንጉሥ ነው እንጂ
የጌታ ነው እንጂ
ምንም ለውጥ የለውም
(ተዓምር አይፈጥርም ) የአንድ ባሪያ መጉደል
እኔ ብሞትልሽ አትተርፊም አይደል !?
_
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
ፍቅርንስ ያፍቅሯት ጌቶች ....
(መውደድ በእነሱ ያምራል )
በልዑላኑ — በሀያላኑ —
በንጉሦቹ ፤
(በፈላጭ በቆራጮቹ )
ጊዜም ስልጣንም ባላቸው ፤
ሁሉን በሚቻላቸው ።
(እንደ እኔ አይደሉም እነሱ....)
የልብን መሻት ይሞላሉ ....
እንባን ማበስ ይችላሉ ....
(ለሚጠሉት ባይሆን እንኳን )
ለሚወዱት ይደርሳሉ ።
(ለምን ወደድኩሽ እኔ ግን?)
“መውደድ” (የንጉሥ ዘመድ)
በባሪያ ልብ ምን ይሰራል?
ላፈቀሩት ካልደረሱ ....
ማፍቀር ብቻ ምኑ ያምራል?
•
ባይሽም በእሳት መካከል
ባለጊዜ ሲያንገላታሽ
ቢሰማኝ ጩኸት እሪታሽ
አድንሽ ዘንድ ....
(አተርፍሽ ዘንድ )
አቅመቢስ ነኝ ድኩም ባሪያ
ስስ ጉልበቴ አንሶብኛል ፤
ታዲያ ....
(“ደረስኩልሽ” ማለት አቅቶኝ)
“ወደድኩሽ” ብል ያምርብኛል?
•
ለወደዱት አካል ለወደዱት ገላ ....
ለመድረስ የሚችል ከሌለበት አቅም
ያሳምማል እንጂ መውደድ ምን ሊጠቅም?
ካላበስኩልሽ እንባሽን
ካላከምኩት ህመምሽን
ካላተርፍኩት....
ቆሜ ካየሁት ልብሽ ሲሰበር ፤
ባልወድሽ ይሻለኝ ነበር ።
²
ፍቅርንስ ያፍቅሯት ጌቶች....
(መውደድ ያምራል በእነሱ ፤)
ቀላል ነው እንባ ማበሱ ፤
(ላፈቀሩት ሰው መድረሱ ። )
ጌታም ራሱ ሁሉን የሚችል....
(የማርያም ልጇ) የዓለም ንጉሥ ነው
ስለመውደዱ ተሰቅሎ ያልፋል ፤
ደሙን አፍስሶ ፍቅሩን ያተርፋል ፤
ሞቱ እንኳን ሚዛን ይደፋል ።
(ታውቂያለሽ ይሄንን)
የንጉሥ ነው እንጂ
የጌታ ነው እንጂ
ምንም ለውጥ የለውም
(ተዓምር አይፈጥርም ) የአንድ ባሪያ መጉደል
እኔ ብሞትልሽ አትተርፊም አይደል !?
_
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
❤65👍39🔥2👎1
አሚን አሚን አሚን
እስኪ ልነሳና እንዝርቴን ላስላዉ
ምን ያቦዝነዋል ፈትሎ አዳሪ ሰዉ
እንደ ጊዜው ክፋት
እንደሰዉ ክዳት
እንደኔ አንድ መሆን
ምን ይበጀኝ ነበር አንተ ከኔ ባትሆን።
የዘመናችን ሰው ምንኛ ተጎዳ
በአፉ እየወደደ በሆዱ እየከዳ፤
እኔማ ረግሜ ምንኛ ልጎዳው
እሱም ይውደድና ያመነው ሰው ይክዳው።
አሚን አሚን እማዋየው አሚን
ጌትዬ እጄን አውዛው
እጁ የወዛ ነው ሚዜው የሚበዛው።
የወሎ ደመና አይጥልም ከየጁ
ገልግለኝ ህመሜን ከነእግዴ ልጁ።
ብሶቴ ችግሬ ገለል በል ከፊቴ
እግሬን ልዘርጋበት
አሞኛል ጉልበቴን የኮረተምኩበት።
አቤት አቤት አቤት
እማማ ዚነት🖤
@getem
@getem
እስኪ ልነሳና እንዝርቴን ላስላዉ
ምን ያቦዝነዋል ፈትሎ አዳሪ ሰዉ
እንደ ጊዜው ክፋት
እንደሰዉ ክዳት
እንደኔ አንድ መሆን
ምን ይበጀኝ ነበር አንተ ከኔ ባትሆን።
የዘመናችን ሰው ምንኛ ተጎዳ
በአፉ እየወደደ በሆዱ እየከዳ፤
እኔማ ረግሜ ምንኛ ልጎዳው
እሱም ይውደድና ያመነው ሰው ይክዳው።
አሚን አሚን እማዋየው አሚን
ጌትዬ እጄን አውዛው
እጁ የወዛ ነው ሚዜው የሚበዛው።
የወሎ ደመና አይጥልም ከየጁ
ገልግለኝ ህመሜን ከነእግዴ ልጁ።
ብሶቴ ችግሬ ገለል በል ከፊቴ
እግሬን ልዘርጋበት
አሞኛል ጉልበቴን የኮረተምኩበት።
አቤት አቤት አቤት
እማማ ዚነት🖤
@getem
@getem
👍24❤23😢2
ተጋፈጥኩ መከራዬን
ተፋላምኩ ፈተናዬን
ኃይሌን ጨረስኩ እንጂ መች አገኙሁ ውጤት
እኔ አለቅኩ እንጂ መች በቃሁ ለስኬት
ሩጫዬን ገታሁ አቆምኩ ትግሌን ላፍታ
ቃኘሁ ድክመቴን የሽንፈቴን ቃታ
ለካ
ብቻዬን ነው ምጓዝ እርቃኔን ወጥቼ
መከታ ጋሻዬን ረዳቴን ትቼ
ለካ
ውልክፍክፍ ስንኩልኩል ነበር አሯሯጤ
እውር ድንብር ነበር ሚወነጨፍ ውስጤ
ለካ
በዜሮ ተባዝቷል ሙከራ ጥረቴ
አንቺን ሳልይዝ ሂጄ ድንግል እመቤቴ
አፈገፈግኩ ወደ ኋላ
ተመለስኩ ወደ ቀልቤ
ሰአሊ ለነ እያልኩ ታጠቅኩሽ በልቤ
ይኸው ነጻ ጥርጊያው
ይኸው ቀና መንገዱ
ገና ሳልጠጋው
ሲያዘቀዝቅ አየሁ የመከራ ቀንዱ
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
ተፋላምኩ ፈተናዬን
ኃይሌን ጨረስኩ እንጂ መች አገኙሁ ውጤት
እኔ አለቅኩ እንጂ መች በቃሁ ለስኬት
ሩጫዬን ገታሁ አቆምኩ ትግሌን ላፍታ
ቃኘሁ ድክመቴን የሽንፈቴን ቃታ
ለካ
ብቻዬን ነው ምጓዝ እርቃኔን ወጥቼ
መከታ ጋሻዬን ረዳቴን ትቼ
ለካ
ውልክፍክፍ ስንኩልኩል ነበር አሯሯጤ
እውር ድንብር ነበር ሚወነጨፍ ውስጤ
ለካ
በዜሮ ተባዝቷል ሙከራ ጥረቴ
አንቺን ሳልይዝ ሂጄ ድንግል እመቤቴ
አፈገፈግኩ ወደ ኋላ
ተመለስኩ ወደ ቀልቤ
ሰአሊ ለነ እያልኩ ታጠቅኩሽ በልቤ
ይኸው ነጻ ጥርጊያው
ይኸው ቀና መንገዱ
ገና ሳልጠጋው
ሲያዘቀዝቅ አየሁ የመከራ ቀንዱ
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
❤96👍37👎1
ሌላኛው ሊስት ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቅ ምርጥ 5 ውስጥ ያለ የክሪፕቶ ቢዝነስ ነው።
እድሎን ይሞክሩ!
https://tttttt.me/tapswap_mirror_2_bot?start=r_454803628 🎁 +2.5k Shares as a first-time gift
እድሎን ይሞክሩ!
https://tttttt.me/tapswap_mirror_2_bot?start=r_454803628 🎁 +2.5k Shares as a first-time gift
👍5❤1
ይድረስልኝ ላንቺ ✍️በዔደን_ታደሰ
<unknown>
👍21😢4❤2👎1
የተዘለለ የታሪክ ገጽ
(በእውቀቱ ስዩም)
ግዙፉ ጎልያድ፥ ያህዛብ ጀግና
-አስገመገመ
ዳዊትም ሰምቶ ፥ጎንበሰ አለና
-ጠጠር ለቀመ፤
እናም በእለቱ
ገበጣው ቀርቦ፤ ገጥመው ሁለቱ
ከግድግዳው ላይ፥ ሳይወርድ ወንጭፉ
ከየሰገባው፥ ሳይወጣ ሰይፉ
ተሸናነፉ;;
የቆፈሩትን፥ ጉድጓዱን ደፍነው
የገበጣውን ፥ጠጠር በትነው
ያወጁት አዋጅ ፥ አንድ ላይ ሆነው፥
ይሄ ነው ቃሉ ፦
“ የተከተልኸኝ ሰራዊት ሁሉ
ዋንጫህን አንሳ ፤ጦር ጋሻህን ጣል
የትኛው ሀገር
የትኛው ሀሳብ
ከህይወት በልጦ አንገት ያሰጣል?
@getem
@getem
@paappii
(በእውቀቱ ስዩም)
ግዙፉ ጎልያድ፥ ያህዛብ ጀግና
-አስገመገመ
ዳዊትም ሰምቶ ፥ጎንበሰ አለና
-ጠጠር ለቀመ፤
እናም በእለቱ
ገበጣው ቀርቦ፤ ገጥመው ሁለቱ
ከግድግዳው ላይ፥ ሳይወርድ ወንጭፉ
ከየሰገባው፥ ሳይወጣ ሰይፉ
ተሸናነፉ;;
የቆፈሩትን፥ ጉድጓዱን ደፍነው
የገበጣውን ፥ጠጠር በትነው
ያወጁት አዋጅ ፥ አንድ ላይ ሆነው፥
ይሄ ነው ቃሉ ፦
“ የተከተልኸኝ ሰራዊት ሁሉ
ዋንጫህን አንሳ ፤ጦር ጋሻህን ጣል
የትኛው ሀገር
የትኛው ሀሳብ
ከህይወት በልጦ አንገት ያሰጣል?
@getem
@getem
@paappii
👍33❤22🔥6