-------
እዚህ ፎቶ ስር ሶስት ሰዎች ይታዩታኛል..
ገብሬ ፣ አብዬ መንግስቱ እና ጋሽ ነብይ!
አይ ማማር
አይ ውበት
አይ ግዜ
አይ ዘመን....
''They bared their brains to heaven..'' ይላል allen የታላላቆቹን ሞት ማለፍ ከሰሟ በኋላ!
የታላላቆቹ ማለፍ ምድር ላይ ለቀሩ ዋይታ
ለሰማይ ደግሞ ደስ የሚል ፈገግታ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም።
ሚቀበሏቸውን ፣ ሚገናኟቸውን ማሰብ አካሄዳቸውን መከተል ያስመኛል።
እጆቻቸውን ይዞ ወደ ሚሄዱበት አብሮ መጎዝ...
ወደዛ ደስ ወደሚሉት ሰዎች...
የታላላቆቹ ማለፍ ታላቅ ሀዘን ብቻ ሳይሆን የሚጥልብን እነሱን የመከተል ፣ እነሱን የመፈለግ መሪር ናፍቆት ያሸክመናል።
ደጋጎቹ ሁሉ ጥለውን አንዲት ትንሽ ቦታ ይበሰባሉ።
እዚህ የኖሩትን ተሰብስበው ይደግሙታል።
ዘላለም የሚያምር ነገር መስራት አይደክማቸው እነሱ እንደሆነ...
እንደ ነብይ ያሉ ሰዎች በሰማይ እና በምድር መሀከል ያለውን ወግ የሚያገነኙ ድልድዮች ነበሩ።
ከእንግዲህ ስለ ትናንት ማን ይነግረናል?
ስለ ሚያማምሩት ሰዎች ማን ያጫውተናል?
በህይወት ያሉት በሞቱት ይቀናሉ! ማለት ይሄ ነው።
ነፍስ ይማር ጋሽ ነብይ!
#ይስሃቅ_አብርሃም
@getem
እዚህ ፎቶ ስር ሶስት ሰዎች ይታዩታኛል..
ገብሬ ፣ አብዬ መንግስቱ እና ጋሽ ነብይ!
አይ ማማር
አይ ውበት
አይ ግዜ
አይ ዘመን....
''They bared their brains to heaven..'' ይላል allen የታላላቆቹን ሞት ማለፍ ከሰሟ በኋላ!
የታላላቆቹ ማለፍ ምድር ላይ ለቀሩ ዋይታ
ለሰማይ ደግሞ ደስ የሚል ፈገግታ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም።
ሚቀበሏቸውን ፣ ሚገናኟቸውን ማሰብ አካሄዳቸውን መከተል ያስመኛል።
እጆቻቸውን ይዞ ወደ ሚሄዱበት አብሮ መጎዝ...
ወደዛ ደስ ወደሚሉት ሰዎች...
የታላላቆቹ ማለፍ ታላቅ ሀዘን ብቻ ሳይሆን የሚጥልብን እነሱን የመከተል ፣ እነሱን የመፈለግ መሪር ናፍቆት ያሸክመናል።
ደጋጎቹ ሁሉ ጥለውን አንዲት ትንሽ ቦታ ይበሰባሉ።
እዚህ የኖሩትን ተሰብስበው ይደግሙታል።
ዘላለም የሚያምር ነገር መስራት አይደክማቸው እነሱ እንደሆነ...
እንደ ነብይ ያሉ ሰዎች በሰማይ እና በምድር መሀከል ያለውን ወግ የሚያገነኙ ድልድዮች ነበሩ።
ከእንግዲህ ስለ ትናንት ማን ይነግረናል?
ስለ ሚያማምሩት ሰዎች ማን ያጫውተናል?
በህይወት ያሉት በሞቱት ይቀናሉ! ማለት ይሄ ነው።
ነፍስ ይማር ጋሽ ነብይ!
#ይስሃቅ_አብርሃም
@getem
😢21👍20❤3