#ቴዎድሮስ_ካሳ
ኦ ፍቅሬ ፀደይ ኾይ !
.
፥
ምን በወጣዉና ፥
በነፍሴ ፍም እሳት ገላየ ይንገብገብ
በመንፈሴ ዚሎሽ ፥ ሁለንታየ ይርገብ ።
-
በልጅ ንፁህ ገላ ፥ የጥያቄ መንፈስ እንደሚለቆጠዉ ፣
ከሽማግሌ ልብ ፥ የሞት ሀያል በትር ፥ የህይዎት ከንቱ ማር እንደሚቆረጠዉ ፣
ፍቅርሽ እንደዚያ ነዉ !
መጣሁ መጣሁ ይላል ~ መሄጃዉ ሲጨንቀዉ !!
-
በበድን ገላየ አዚም አንተርሶ
ከዓለም ያስተኛኛል፥ ከነፍሴ ቀስቅሶ ።
፥
ከልቦናየ ባህር ፊት የሚቆም ፥ የጊዜን አሳ አስጋሪ
ተሻሚና ፤ ጎልብችና
ለጎጆሽ ጎጆ ስሪ ።
...ኦ ዉዴ ፀደይ ኾይ ...
ደንባራ ፥ ድንጉላ ፈረስሽን ፡ በጥላቻሽ ጅራፍ ግሪዉ
የፍቅርን ሀያል ህመም ፥ ቁስሉን ፥ ስቃዩን እንድታዉቂዉ ።
ደግሞም ዝም ብለሽ
የጥላቻሽን ጦር ስበቂና ፥ የፍቅርሽን ጋኑን ስበሪዉ
በተወጋሽዉ ልክ ነዉና ፥ የምትመግይዉ የምትደሚዉ ።
ኦ ፍቅሬ ፀደይ ኾይ !
ለማይጎህ ለልቤ ፅልመት
ለማይቆም ለአይኖቸ ጅረት
ሞክንያት ባይኾን ምናለ
ጣዖቱ ፥ የልብሽ ዉበት ።
አታዉቂና...
ከፍቅርሽ ጉድጓድ እንደማያንስ የጥላቻየም ጥልቀት ።
ደግሞም ፥
@getem
@getem
@getem
ኦ ፍቅሬ ፀደይ ኾይ !
.
፥
ምን በወጣዉና ፥
በነፍሴ ፍም እሳት ገላየ ይንገብገብ
በመንፈሴ ዚሎሽ ፥ ሁለንታየ ይርገብ ።
-
በልጅ ንፁህ ገላ ፥ የጥያቄ መንፈስ እንደሚለቆጠዉ ፣
ከሽማግሌ ልብ ፥ የሞት ሀያል በትር ፥ የህይዎት ከንቱ ማር እንደሚቆረጠዉ ፣
ፍቅርሽ እንደዚያ ነዉ !
መጣሁ መጣሁ ይላል ~ መሄጃዉ ሲጨንቀዉ !!
-
በበድን ገላየ አዚም አንተርሶ
ከዓለም ያስተኛኛል፥ ከነፍሴ ቀስቅሶ ።
፥
ከልቦናየ ባህር ፊት የሚቆም ፥ የጊዜን አሳ አስጋሪ
ተሻሚና ፤ ጎልብችና
ለጎጆሽ ጎጆ ስሪ ።
...ኦ ዉዴ ፀደይ ኾይ ...
ደንባራ ፥ ድንጉላ ፈረስሽን ፡ በጥላቻሽ ጅራፍ ግሪዉ
የፍቅርን ሀያል ህመም ፥ ቁስሉን ፥ ስቃዩን እንድታዉቂዉ ።
ደግሞም ዝም ብለሽ
የጥላቻሽን ጦር ስበቂና ፥ የፍቅርሽን ጋኑን ስበሪዉ
በተወጋሽዉ ልክ ነዉና ፥ የምትመግይዉ የምትደሚዉ ።
ኦ ፍቅሬ ፀደይ ኾይ !
ለማይጎህ ለልቤ ፅልመት
ለማይቆም ለአይኖቸ ጅረት
ሞክንያት ባይኾን ምናለ
ጣዖቱ ፥ የልብሽ ዉበት ።
አታዉቂና...
ከፍቅርሽ ጉድጓድ እንደማያንስ የጥላቻየም ጥልቀት ።
ደግሞም ፥
@getem
@getem
@getem
#እምወድሽዋ!❤ ቅዳሜዋ!❤ ሸጋዬዋ!❤
ዛሬ ከድር ናቸዉ ይሏል ወሎየ !
ከቅዳሜ ቆሌ የተዳረ ለታ ፥
የትኛዉ ቀን ይደብርሃል ብባል ፥ የትኛዉም ልል እችላለሁ ። ሸገር ካለሁ ግን ምን መዓት
ቢመጣ ቅዳሜ አይደብረኝም ።
የአዲስ አበባ ቡና ቅዳሜ ቅዳሜ ይለያል ፥ ወላ ለምን በጨዉ አትጠጣዉም ( ሃሃ ወዮ
ክባድ ! ) ። የለመድከዉን አሰልች ሰዉ እየተመለከትክ ፥ ያን ሰዉ በቅዳሜ ስትመለከተዉ
አትጠግበዉም ፥ ብርቅ ይኾንብሃል ። መፅሔቱ ፣ ጋዜጣዉ ይጎርፋል ፥ በቅዳሜ ። ሳምንቱን
በስራ ተጠፍሮ የነበረዉ ከተሜ ፥ በእለተ ቅዳሜ የወሬ ጋኑን ይፈታል ፣ ወገቡን ለሳቅ እና
ለጨዋታ ያዘጋጃል ። ሀብታም ከባንኮኒዉ ፤ ድሀም ከስኒዉ ስር ይለገታል ፥ በቅዳሜ ።
እንደኛ ያለ የገጠር ልጅ አዲሲቷን ልብሱን የሚለብሰዉ ለበዓል ነዉ ሃሃ ፥ የአዲስ አበቤ
ቆንጆዎችስ በቅዳሜ ቀሚስ ላይ የፈሰሱ የአልማዝ ፈርጦች መስለዉ ይዉላሉ ።
በቅዳሜ የጓደኞች ሳቅ ይጎርፋል ፣ ከሩቅ ሀገር ጨዋታ ይሰማል ። ሁላማ ስትራመድ
ትነጥራለህ ስልህ ፥ ስለምነጥር ነዉ ።
የዛሬዉ ቅዳሜ ደግሞ በቃ ይለያል ፥ አይንህ ስትገልጥ ሀገሩ ፍስለታን ሞሽሮ ቁሟል ።
አንተስ ምን ታደርጋለህ ደጀ ሰላሙን ትሳለምና ፣ ከመፀሀፍት ደንበኛህ አለላ መፅሔትን
ትገዛና ( ፍትህ የምትሉ ፥ ነገር አትፈልጉኝ ) ፣ የኤፍሬም ስዩምን 'ምክንያቱም ዛሬ ቀኑ
ቅዳሜ ነዉ ግጥም ' በቃልህ ትወጣዉና ፣ የጠዋት አጃኢበኛ የዶሮ አይን ቡናህን ትልፍና ፣
ከሰዐት ሸገር ኤፍ ኤምን አሻግረህ እየናፈቅህ ፥ ቀኑን የሚያረዝምልህን አምላክ
ትጋተተዋለህ ።
ኤፍሬምን ትንሽ እናዉርደዉ እስኪ
-
ቀጭን ወገቧ ላይ
ከእንብርቷ በላይ ልብሷ ተንጠልጥሏል
የወርቅ መስቀሏ
ጡቶቿ መካከል ዘንበል ብሎ ወድቋል
መንገድ ላይ ያየኃት
የማላዉቃት ሴት ናት ።
ወዴት እንደምትሄድ ባሳቤ ገመትኩኝ
አንድ የቀጠራትን ወንደላጤ አሰብኩኝ
ሠባት እንቁላሎች
ግማሽ ኪሎ ሥጋ....( ገዝቶ )
ከርሷ ጋር ካልሆነ
ቡና አልጠጣም ብሎ አሥሬ እያዛጋ
መጽሐፏን ከፍቶ
በሩን ክፍት ትቶ
መልሶ መላልሶ ሠዓቱን እያየ
የሚጠብቃት ሠዉ
ሐሳቤ ዉል አለዉ
ምክንያቱም ዛሬ ቀኑ ቅዳሜ ነዉ ።
-
ይችን የቅዳሜ ከረሜላ እንዳታልቅብኝ እየሳሳሁ መምጠጥ ጀምሬያለሁ ፥ መልካም ቅዳሜ
ይሁንላችሁ ወዳጆች ።
አለላን አንብቡት ፣ በቃ ምርጥ ነዉ
ወላ ከመፀሀፍ እኩል ነዉ
አጃኢበኛ ብዕረኞች ዘምተዉበታል
ጋብዣለሁ ።
ደግሞ ደግሞ " ማርሲላስ " የሚል መፀሀፍ ገዝታችኃል ፥ በሉ ቶሎ ግዙ ። ደራሲዉ ነፍሱን
ሰጥቷል። በአንድ ሰሞን ሙሉጌታ ተስፋየ ለቅሶ ሄዶ ማስተዛዘኛ " ግጥም ሰጠ " ሲባል
ሰምቸ ጉድ ብያለሁ ። የዚህኛዉ ደግሞ ባሰ ፥ ጊዜዉን ፣ ነፍሱን ፣ መጣፈጡን ሁሉ ነዉ
የቸረዉ ። አህመድ ሁስ ፥ መልካም ቅዳሜ ኸይር አሳብየዋ ። የቅዳሜን ቡና በጋበዝኩህ
በወደድኩ ነበር ።
#ቴዎድሮስ ካሳ
@getem
@getem
@balmbaras
ዛሬ ከድር ናቸዉ ይሏል ወሎየ !
ከቅዳሜ ቆሌ የተዳረ ለታ ፥
የትኛዉ ቀን ይደብርሃል ብባል ፥ የትኛዉም ልል እችላለሁ ። ሸገር ካለሁ ግን ምን መዓት
ቢመጣ ቅዳሜ አይደብረኝም ።
የአዲስ አበባ ቡና ቅዳሜ ቅዳሜ ይለያል ፥ ወላ ለምን በጨዉ አትጠጣዉም ( ሃሃ ወዮ
ክባድ ! ) ። የለመድከዉን አሰልች ሰዉ እየተመለከትክ ፥ ያን ሰዉ በቅዳሜ ስትመለከተዉ
አትጠግበዉም ፥ ብርቅ ይኾንብሃል ። መፅሔቱ ፣ ጋዜጣዉ ይጎርፋል ፥ በቅዳሜ ። ሳምንቱን
በስራ ተጠፍሮ የነበረዉ ከተሜ ፥ በእለተ ቅዳሜ የወሬ ጋኑን ይፈታል ፣ ወገቡን ለሳቅ እና
ለጨዋታ ያዘጋጃል ። ሀብታም ከባንኮኒዉ ፤ ድሀም ከስኒዉ ስር ይለገታል ፥ በቅዳሜ ።
እንደኛ ያለ የገጠር ልጅ አዲሲቷን ልብሱን የሚለብሰዉ ለበዓል ነዉ ሃሃ ፥ የአዲስ አበቤ
ቆንጆዎችስ በቅዳሜ ቀሚስ ላይ የፈሰሱ የአልማዝ ፈርጦች መስለዉ ይዉላሉ ።
በቅዳሜ የጓደኞች ሳቅ ይጎርፋል ፣ ከሩቅ ሀገር ጨዋታ ይሰማል ። ሁላማ ስትራመድ
ትነጥራለህ ስልህ ፥ ስለምነጥር ነዉ ።
የዛሬዉ ቅዳሜ ደግሞ በቃ ይለያል ፥ አይንህ ስትገልጥ ሀገሩ ፍስለታን ሞሽሮ ቁሟል ።
አንተስ ምን ታደርጋለህ ደጀ ሰላሙን ትሳለምና ፣ ከመፀሀፍት ደንበኛህ አለላ መፅሔትን
ትገዛና ( ፍትህ የምትሉ ፥ ነገር አትፈልጉኝ ) ፣ የኤፍሬም ስዩምን 'ምክንያቱም ዛሬ ቀኑ
ቅዳሜ ነዉ ግጥም ' በቃልህ ትወጣዉና ፣ የጠዋት አጃኢበኛ የዶሮ አይን ቡናህን ትልፍና ፣
ከሰዐት ሸገር ኤፍ ኤምን አሻግረህ እየናፈቅህ ፥ ቀኑን የሚያረዝምልህን አምላክ
ትጋተተዋለህ ።
ኤፍሬምን ትንሽ እናዉርደዉ እስኪ
-
ቀጭን ወገቧ ላይ
ከእንብርቷ በላይ ልብሷ ተንጠልጥሏል
የወርቅ መስቀሏ
ጡቶቿ መካከል ዘንበል ብሎ ወድቋል
መንገድ ላይ ያየኃት
የማላዉቃት ሴት ናት ።
ወዴት እንደምትሄድ ባሳቤ ገመትኩኝ
አንድ የቀጠራትን ወንደላጤ አሰብኩኝ
ሠባት እንቁላሎች
ግማሽ ኪሎ ሥጋ....( ገዝቶ )
ከርሷ ጋር ካልሆነ
ቡና አልጠጣም ብሎ አሥሬ እያዛጋ
መጽሐፏን ከፍቶ
በሩን ክፍት ትቶ
መልሶ መላልሶ ሠዓቱን እያየ
የሚጠብቃት ሠዉ
ሐሳቤ ዉል አለዉ
ምክንያቱም ዛሬ ቀኑ ቅዳሜ ነዉ ።
-
ይችን የቅዳሜ ከረሜላ እንዳታልቅብኝ እየሳሳሁ መምጠጥ ጀምሬያለሁ ፥ መልካም ቅዳሜ
ይሁንላችሁ ወዳጆች ።
አለላን አንብቡት ፣ በቃ ምርጥ ነዉ
ወላ ከመፀሀፍ እኩል ነዉ
አጃኢበኛ ብዕረኞች ዘምተዉበታል
ጋብዣለሁ ።
ደግሞ ደግሞ " ማርሲላስ " የሚል መፀሀፍ ገዝታችኃል ፥ በሉ ቶሎ ግዙ ። ደራሲዉ ነፍሱን
ሰጥቷል። በአንድ ሰሞን ሙሉጌታ ተስፋየ ለቅሶ ሄዶ ማስተዛዘኛ " ግጥም ሰጠ " ሲባል
ሰምቸ ጉድ ብያለሁ ። የዚህኛዉ ደግሞ ባሰ ፥ ጊዜዉን ፣ ነፍሱን ፣ መጣፈጡን ሁሉ ነዉ
የቸረዉ ። አህመድ ሁስ ፥ መልካም ቅዳሜ ኸይር አሳብየዋ ። የቅዳሜን ቡና በጋበዝኩህ
በወደድኩ ነበር ።
#ቴዎድሮስ ካሳ
@getem
@getem
@balmbaras
የህይዎት ጣዕም
የህይዎት ጠረን
ውብ ብርጭቆ
ቆንጆ ሲኒ ፤
ትኩስ ቡና
ቀዝቃዛ ወይን ፤
የሞላበት ።
ቀዝቃዛ እድሜ
ወጣት ደረት ፤
ትኩስ ሌሊት
የሚያድግበት ።
ቀዝቃዛ እኔ
በረዶ እኔ ፤
ትኩስ አንቺ ያለሽበት ።
የህይዎት ጣዕም
የህይዎት ውበት
ቀዝቃዛ ሻይ
እጅሽ መሃል የበረደ ፤
ግማሽ እድሜ
አንቺን ሲያስብ የነጎደ ፤
ጅምር ሀሳብ
ጅምር ግጥም
ጠርቶ ያመጣው ፤
ውብ ወዘና
ጎረምሳ ሌት የሚጠጣው ።
የህይዎት መልክ
የህይዎት እድሜ
የአንቺ በራፍ
የአንቺ መስኮት ፤
የዓይን ፍቅር
በዓይን ስርቆት ፤
ትንሽ ቁስል
እድሜን ሙሉ ትዝ የምትል ፤
የአንቺ ፍቅር
ስር የሚሰድድ ከጅማት ስር ፤
የህይዎት ጣዕም
የህይዎት ውበት
መኖር ሳስቶ
ፍቅርን መስሎ ፤
መኖር ሳስቶ
ገላን ጥሎ
' የለምን' ያህል አክሎ ።
#ቴዎድሮስ_ካሳ
@getem
@getem
የህይዎት ጠረን
ውብ ብርጭቆ
ቆንጆ ሲኒ ፤
ትኩስ ቡና
ቀዝቃዛ ወይን ፤
የሞላበት ።
ቀዝቃዛ እድሜ
ወጣት ደረት ፤
ትኩስ ሌሊት
የሚያድግበት ።
ቀዝቃዛ እኔ
በረዶ እኔ ፤
ትኩስ አንቺ ያለሽበት ።
የህይዎት ጣዕም
የህይዎት ውበት
ቀዝቃዛ ሻይ
እጅሽ መሃል የበረደ ፤
ግማሽ እድሜ
አንቺን ሲያስብ የነጎደ ፤
ጅምር ሀሳብ
ጅምር ግጥም
ጠርቶ ያመጣው ፤
ውብ ወዘና
ጎረምሳ ሌት የሚጠጣው ።
የህይዎት መልክ
የህይዎት እድሜ
የአንቺ በራፍ
የአንቺ መስኮት ፤
የዓይን ፍቅር
በዓይን ስርቆት ፤
ትንሽ ቁስል
እድሜን ሙሉ ትዝ የምትል ፤
የአንቺ ፍቅር
ስር የሚሰድድ ከጅማት ስር ፤
የህይዎት ጣዕም
የህይዎት ውበት
መኖር ሳስቶ
ፍቅርን መስሎ ፤
መኖር ሳስቶ
ገላን ጥሎ
' የለምን' ያህል አክሎ ።
#ቴዎድሮስ_ካሳ
@getem
@getem
👍45❤42🔥1😱1