#እምነት_ተስፋ_ፍቅር_አብረው_ይኖራሉ_ከሁሉም_የሚበልጠው_ፍቅር_ነው!!!
በጋራችን ቤት ውሾች ይጮዋሉ
አትመጥንክም እያሉ
አትመጥናትም እያሉ
ፍቅርን መለካት መመዘን ይሻሉ
የሚመጥን ፍቅር ዋጋው ምን ያህል ነው
የፍቅርስ መለኪያ ሚዛኑ ምንድን ነው
ሃይማኖት የሌለው!
ዘር የማይወክለው!
ፍቅር ብቻውን ሌላ ፕላኔት ነው
እውነት እና ተስፋ ፍቅርን ካልበለጡ
በፍቅር አርማ መንገድ በስሜት ከወጡ
መዋደድ ነው ደስታ
መፋቀር ነው ፌሽታ
ሺ ጊዜ ብለይሽ ውሏችን ባይገጥም
ሃይማኖት እምነትሽ ግርግዳው ቢቆምም
አሻግሬ እያየው ናፍቆቱን አልችልም
ግንቡ ይፍረስና ድልድዩ ይሰራ
ሂጃብና መስቀል በአንድ ላይ ይጠራ
አራም ይሉ ሃጢያት
ለገደሉ እንጂ ላፈቀሩ ያቁም ቅጣት
ጎጆሽን ቀልሺ መቀነት ልሁንሽ
አላን ከሚፈራው ከሰጋጁ ልብሽ
ነይ አንቺም ግቢ ቀበቶዬ ሆነሽ
ፍቅርን ካስተማረኝ በእየሱስ ልውደድሽ
አጎቴ ሼህ ናቸው ከመስጊድ ያደሩ
አክስትሽ መነኩሴ ገዳም የቆጠሩ
ታዲያ በአንድ ጣራ ሕግ እያሰፉ
ከፍቅር ጎዳና እኛን እየገፉ
አረም ያበቅላሉ ዘሩን እያጠፉ
እናም ፍቅሬ አትገረሚ
ይጮዋሉ ውሾች በአላፊ አግዳሚው
እየጮዉ መብላት ነውና ኑሮዋቸው
አፈቅርሽው ብለው ሲጮዉ አትስሚ
ጆሮሽን ጠርቅመሽ የልብሽን ስሚ
እኔም ወድሻለው መስቀሌን ሳልበጥስ
ሂጃብሽ ይቀመጥ መስገድሽ ይቀደስ
ፍቅርን አስቀድመን ሕግጋቱን እንጣስ
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
:- #ተክለ_ዮሀንስ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
በጋራችን ቤት ውሾች ይጮዋሉ
አትመጥንክም እያሉ
አትመጥናትም እያሉ
ፍቅርን መለካት መመዘን ይሻሉ
የሚመጥን ፍቅር ዋጋው ምን ያህል ነው
የፍቅርስ መለኪያ ሚዛኑ ምንድን ነው
ሃይማኖት የሌለው!
ዘር የማይወክለው!
ፍቅር ብቻውን ሌላ ፕላኔት ነው
እውነት እና ተስፋ ፍቅርን ካልበለጡ
በፍቅር አርማ መንገድ በስሜት ከወጡ
መዋደድ ነው ደስታ
መፋቀር ነው ፌሽታ
ሺ ጊዜ ብለይሽ ውሏችን ባይገጥም
ሃይማኖት እምነትሽ ግርግዳው ቢቆምም
አሻግሬ እያየው ናፍቆቱን አልችልም
ግንቡ ይፍረስና ድልድዩ ይሰራ
ሂጃብና መስቀል በአንድ ላይ ይጠራ
አራም ይሉ ሃጢያት
ለገደሉ እንጂ ላፈቀሩ ያቁም ቅጣት
ጎጆሽን ቀልሺ መቀነት ልሁንሽ
አላን ከሚፈራው ከሰጋጁ ልብሽ
ነይ አንቺም ግቢ ቀበቶዬ ሆነሽ
ፍቅርን ካስተማረኝ በእየሱስ ልውደድሽ
አጎቴ ሼህ ናቸው ከመስጊድ ያደሩ
አክስትሽ መነኩሴ ገዳም የቆጠሩ
ታዲያ በአንድ ጣራ ሕግ እያሰፉ
ከፍቅር ጎዳና እኛን እየገፉ
አረም ያበቅላሉ ዘሩን እያጠፉ
እናም ፍቅሬ አትገረሚ
ይጮዋሉ ውሾች በአላፊ አግዳሚው
እየጮዉ መብላት ነውና ኑሮዋቸው
አፈቅርሽው ብለው ሲጮዉ አትስሚ
ጆሮሽን ጠርቅመሽ የልብሽን ስሚ
እኔም ወድሻለው መስቀሌን ሳልበጥስ
ሂጃብሽ ይቀመጥ መስገድሽ ይቀደስ
ፍቅርን አስቀድመን ሕግጋቱን እንጣስ
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
:- #ተክለ_ዮሀንስ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
#የልቤ....#እምነት_ክደት_ቃል
፨፨፨፨
፨፨፨
፨፨
✍ #አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
የልክ ሚዛኔ ፥ ላንቺ ተሰበረ
ሰው ሲመዝን ኖሮ
በገለባ አለም ፥ ወርቅ አንቺን ሰፈረ
እቱ ለግላጋዋ !!
እንዶድ ፍቅርሽ ደርሶት
ቅምሻን የታደለ ፥ ካዘኔታሽ ጥዋ
እንኳን እኔ ቀርቶ
መውደድ ያልሸተተው
ለበቀል መሀላ ፥ እራሱን የሰዋ
ሳጥናኤል ይገራል
ሰውነት ሰው ሲሆን
ካንቺ መዲያ ላሳር ፥ ሰው ማለም ይከብዳል ።
#አየሽ
ልኬት ለሰበረ ፥ የፍቅር ናሙና
ቃል እየቀረፁ ፥ መቀኞ ቢወርዱ
ምላስ ያነክሳል
አልማዝ ባየ ግዜ
ኮምቼ ሲቆልል ፥ ለከረመ ልምዱ
ጨለማ ተዘግቶ ፥ አዘቅት የከረመ
ብርሀን ቢግቱት ፥ አይኑ እንደታመመ
#ያ' ሰውዬሽ....................... ነኝ እኔ
በወገግታው ዳፍንት ፥ ያጣሁሽ ከጎኔ ።
ቀሽም ቃላቶቼ ፥ ቃልኪዳን አድሰው
ለሰበርኩት ልብሽ ፥ ካሳ ባይሆንሽም
በመምጣትሽ ስካር ፥ ደስታን ባላሟሽም
ያዘገየሽ ግዜ ፥ ቀድሞ ቢወስድሽም
ከኔ ለፈቀቀ ፥ ያንቺ ልዕልና
ጎረበጠኝ ብዬ ፥ አንቺን አልወቅስሽም
አንዳንዴ ባይገርምሽ
ፅጌሬዳ አበባ ፥ ውበቷ ሳያንሳት
ሳይነኳት የሚደርስ
ያንን ሁሉ እሾህ ፥ ለጉድ ያሸከምካት
በለስ....ሺ ምንተሺ
እሾህ ቆዳ ስፌት ፥ ጣሟን ያለበስካት
ም'ነው .... አልክ እግዜሩ ?
እላለው
ለሰውነት ህመም
መድህኒት የምትሆን ፥ እንዲት እግሯ ልጅህ
ሰርክ ጠዋት ማታ ፥ ሳትለይ ከደጅህ
በቁም ከሞቱ ጎን ፥ በመስክ አውለሀት
እንዳረጀ ቀብር ፥ በሙታን ወረዳ ፥ ሳማ የከበባት
ምንኛ....ብትወዳት ?
ምንኛ...ብታምናት ?
#እላለው !!
ይሄም ውጣ ውረድ ፥ እያብሰከሰከ ሆዴን ቢበላኝም
ንስር ማንነትሽ
መውጫ ቢያጣ ፥ ብዬ አያሳስበኝም
#ይልቅ
ኩፍኩፍ ይመስል
ትዝታሽ በግዜ ፥ በዋዛ ባይለቅም
መጣሽ ከማለቴ
ለመለመ ያልኩት ፥ በቅፅበት ቢደርቅም
ሞገስሽን ያዬ ልቤ
ምን እንደሚልሽ አያውቅም።
✍@Abr_sh
@getem
@getem
@getem
፨፨፨፨
፨፨፨
፨፨
✍ #አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
የልክ ሚዛኔ ፥ ላንቺ ተሰበረ
ሰው ሲመዝን ኖሮ
በገለባ አለም ፥ ወርቅ አንቺን ሰፈረ
እቱ ለግላጋዋ !!
እንዶድ ፍቅርሽ ደርሶት
ቅምሻን የታደለ ፥ ካዘኔታሽ ጥዋ
እንኳን እኔ ቀርቶ
መውደድ ያልሸተተው
ለበቀል መሀላ ፥ እራሱን የሰዋ
ሳጥናኤል ይገራል
ሰውነት ሰው ሲሆን
ካንቺ መዲያ ላሳር ፥ ሰው ማለም ይከብዳል ።
#አየሽ
ልኬት ለሰበረ ፥ የፍቅር ናሙና
ቃል እየቀረፁ ፥ መቀኞ ቢወርዱ
ምላስ ያነክሳል
አልማዝ ባየ ግዜ
ኮምቼ ሲቆልል ፥ ለከረመ ልምዱ
ጨለማ ተዘግቶ ፥ አዘቅት የከረመ
ብርሀን ቢግቱት ፥ አይኑ እንደታመመ
#ያ' ሰውዬሽ....................... ነኝ እኔ
በወገግታው ዳፍንት ፥ ያጣሁሽ ከጎኔ ።
ቀሽም ቃላቶቼ ፥ ቃልኪዳን አድሰው
ለሰበርኩት ልብሽ ፥ ካሳ ባይሆንሽም
በመምጣትሽ ስካር ፥ ደስታን ባላሟሽም
ያዘገየሽ ግዜ ፥ ቀድሞ ቢወስድሽም
ከኔ ለፈቀቀ ፥ ያንቺ ልዕልና
ጎረበጠኝ ብዬ ፥ አንቺን አልወቅስሽም
አንዳንዴ ባይገርምሽ
ፅጌሬዳ አበባ ፥ ውበቷ ሳያንሳት
ሳይነኳት የሚደርስ
ያንን ሁሉ እሾህ ፥ ለጉድ ያሸከምካት
በለስ....ሺ ምንተሺ
እሾህ ቆዳ ስፌት ፥ ጣሟን ያለበስካት
ም'ነው .... አልክ እግዜሩ ?
እላለው
ለሰውነት ህመም
መድህኒት የምትሆን ፥ እንዲት እግሯ ልጅህ
ሰርክ ጠዋት ማታ ፥ ሳትለይ ከደጅህ
በቁም ከሞቱ ጎን ፥ በመስክ አውለሀት
እንዳረጀ ቀብር ፥ በሙታን ወረዳ ፥ ሳማ የከበባት
ምንኛ....ብትወዳት ?
ምንኛ...ብታምናት ?
#እላለው !!
ይሄም ውጣ ውረድ ፥ እያብሰከሰከ ሆዴን ቢበላኝም
ንስር ማንነትሽ
መውጫ ቢያጣ ፥ ብዬ አያሳስበኝም
#ይልቅ
ኩፍኩፍ ይመስል
ትዝታሽ በግዜ ፥ በዋዛ ባይለቅም
መጣሽ ከማለቴ
ለመለመ ያልኩት ፥ በቅፅበት ቢደርቅም
ሞገስሽን ያዬ ልቤ
ምን እንደሚልሽ አያውቅም።
✍@Abr_sh
@getem
@getem
@getem
#ያልተወለደ ... #ቃል
ከ ደብሬ ቅጥር....
ላርባ ፆም ምህላ...
ነጠላ ለብሼ ...ካንጋፋ ዛፍ ጥላ...
#ሽው....#ሽው....ከሚለው አፀድ
ከሚንቆረቆረው
የወፍ ዜማ ሞገድ...
ስርአተ ቤተስኪያን....አብሮ ተጨምሮ
በታንቡሬ መስኮት ...
ያገልጋይ ጥዑም ቃል...ሰናይ ተንቆርቁሮ
አቤቱ....የሚሉት ቃል
አለወትሮ ከበደኝ...
እማፀነው ዘንዳ
የት ብዬ ጅማሮ ፥ ማሰሪያው ጨነቀኝ።
ይሄንን እሱም ታዝቧል....
የሆዴ #ጉትምትም
ምን ቃል እንዲወጣው ፥ አፌን ይጠብቃል
እኔም ቃሌ #ታንቋል...
የምላሴ ፍሬ ...ወረቴ እንደሆነ ..ልቦናዬ ያውቃል።
መቅሰፍት የሞላውን ፥ የህይወትን ጋሪ እንደተሳፈረ
አለም ሰፊ መስሎት የተደናገረ
ያልጠረጠረ ነው..... የተመነጠረ
ይላል የውስጤ ቃል...
ሺዎች የበላ አፈር ...አዕላፍ ይጠብቃል
ለዛሬው ይመስገን....ለነገ እርሱ ያውቃል
#ምርምረ.... #ፀሎት
የኔና እሷ ፍቅር .....ጣፍጦልን በለዛ
ከንፈር መሳም አልፈን
ጉልቻ ሳንጎልት ፥ #ኮሮላ ሳንገዛ
እድሜ ለቻይናዎች ....የማያነካካ ... #ኮሮና ተነዛ...
#ኮ_ሮ_ና...
#አቤቱ አንድ...
ጥፋትህን መልስ ፥ምድርህን ጠብቃት ፥ ሰው አይለፍ ከንቱ
የእጅ ስራህ ውጤት ...እንዳሸን ቢዋደቅ ፥ ላንተ ነው ፀፀቱ
ብዬ እንዳልማጠን
ሰው ከፍቶ ፥ በሰው ላይ ፥ለሞት ባቃጠረን
የቀናሾች ሴራ .....እርሱን ቢያስገምተን
በሰው ደባ ተንኮን ....ሰዎች ለታመሱ
ምን በወጣው እርሱ !!!
እላለው....
#አቤቱ ...ሁለት
እንግዲህ ካልቀረ ...ተወራራሽ ቫይረስ ፥ አለምን መዞሩ
ወዳጅ እና #ሚስቴ
አትንካኝ ....አትንካኝ......ማለት ሳይጀምሩ
ያለቃዬን አንጀት ....አራርተህ አንድዬ
የአመት እረፍቴን ...ያሁኑን ከቀደም ፥ ባንድነት ጠቅልዬ
ግዜ ሳላጠፋ ፥ ከስራዬ ልውጣ
ቶሎ ቶሎ ምጪ.....ቶሎ ቶሎ ልምጣ...
ብለን ተቀጣጥረን ...
ከአልጋ ሳንወርድ ..ካንሶላ ሳንወጣ
ሲነጋና ሲመሽ....ሳትነካኝ ፣ ሳልነካት...ነቀርሳው አይምጣ!!
ደሞ ውስጤ....ይላል
#ቱ....
ይህን መሰል ፀሎት...እንዲህ ያለ ጥሪ ፥ ያውም ...ለፋሲካ
ከበሽታው ቀድሞ ...
በመላኩ መጅ ነው ...እያገላበጠ ቀድሞ #የሚያስከካ ።
#ስብሀት_ለአብ
አቤት ውስጤ #ግሙ
አወየው... #ምላሴ
ስፍር የሌለውን
የበደል ስልቻ ፥ በተቸራት ስጋ ፥ ለታቀፈች ነብሴ
አርምሞሽ ነው #ፅድቄ ፥ ዝምታሽ ነው #ዋሴ
ይሄን ፀሎት ብለሽ...
እምነትሽ መንምኖ ፥ በተስፋ ማጣት ውስጥ ፥ ከምትላወሺ
መለመኑ ይቅር...
ቃል ማውጣቱም ይብቃሽ ..... ለዛሬ ለምሺ ።
ብዬ ወደ ቀልቤ ስመለስ...
እራሴን ሳነቃ..
ሰላም ግቡ ተብሎ .....
ምዕመኑ በፊናው ፥ መላወስ ጀመረ
የጨመትኩት ልሳን ፥ ማዕልተ ፀሎቱ ፥ እዲህ ሲል ቋጠረ !!
በሸከፍነው ከንቱነት...ለሚገጥመን ፈተና
ስናውቅም ...ሳናውቅም ...አስቸጋሪ ነን እና
ምዕንተ እግዝዕትነ ማርያም ....እግዚኦ....መሀረና
#እምነት_ሰው_ያቆማል....እንኳንስ ኮሮና
✍ #አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
✍ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
ከ ደብሬ ቅጥር....
ላርባ ፆም ምህላ...
ነጠላ ለብሼ ...ካንጋፋ ዛፍ ጥላ...
#ሽው....#ሽው....ከሚለው አፀድ
ከሚንቆረቆረው
የወፍ ዜማ ሞገድ...
ስርአተ ቤተስኪያን....አብሮ ተጨምሮ
በታንቡሬ መስኮት ...
ያገልጋይ ጥዑም ቃል...ሰናይ ተንቆርቁሮ
አቤቱ....የሚሉት ቃል
አለወትሮ ከበደኝ...
እማፀነው ዘንዳ
የት ብዬ ጅማሮ ፥ ማሰሪያው ጨነቀኝ።
ይሄንን እሱም ታዝቧል....
የሆዴ #ጉትምትም
ምን ቃል እንዲወጣው ፥ አፌን ይጠብቃል
እኔም ቃሌ #ታንቋል...
የምላሴ ፍሬ ...ወረቴ እንደሆነ ..ልቦናዬ ያውቃል።
መቅሰፍት የሞላውን ፥ የህይወትን ጋሪ እንደተሳፈረ
አለም ሰፊ መስሎት የተደናገረ
ያልጠረጠረ ነው..... የተመነጠረ
ይላል የውስጤ ቃል...
ሺዎች የበላ አፈር ...አዕላፍ ይጠብቃል
ለዛሬው ይመስገን....ለነገ እርሱ ያውቃል
#ምርምረ.... #ፀሎት
የኔና እሷ ፍቅር .....ጣፍጦልን በለዛ
ከንፈር መሳም አልፈን
ጉልቻ ሳንጎልት ፥ #ኮሮላ ሳንገዛ
እድሜ ለቻይናዎች ....የማያነካካ ... #ኮሮና ተነዛ...
#ኮ_ሮ_ና...
#አቤቱ አንድ...
ጥፋትህን መልስ ፥ምድርህን ጠብቃት ፥ ሰው አይለፍ ከንቱ
የእጅ ስራህ ውጤት ...እንዳሸን ቢዋደቅ ፥ ላንተ ነው ፀፀቱ
ብዬ እንዳልማጠን
ሰው ከፍቶ ፥ በሰው ላይ ፥ለሞት ባቃጠረን
የቀናሾች ሴራ .....እርሱን ቢያስገምተን
በሰው ደባ ተንኮን ....ሰዎች ለታመሱ
ምን በወጣው እርሱ !!!
እላለው....
#አቤቱ ...ሁለት
እንግዲህ ካልቀረ ...ተወራራሽ ቫይረስ ፥ አለምን መዞሩ
ወዳጅ እና #ሚስቴ
አትንካኝ ....አትንካኝ......ማለት ሳይጀምሩ
ያለቃዬን አንጀት ....አራርተህ አንድዬ
የአመት እረፍቴን ...ያሁኑን ከቀደም ፥ ባንድነት ጠቅልዬ
ግዜ ሳላጠፋ ፥ ከስራዬ ልውጣ
ቶሎ ቶሎ ምጪ.....ቶሎ ቶሎ ልምጣ...
ብለን ተቀጣጥረን ...
ከአልጋ ሳንወርድ ..ካንሶላ ሳንወጣ
ሲነጋና ሲመሽ....ሳትነካኝ ፣ ሳልነካት...ነቀርሳው አይምጣ!!
ደሞ ውስጤ....ይላል
#ቱ....
ይህን መሰል ፀሎት...እንዲህ ያለ ጥሪ ፥ ያውም ...ለፋሲካ
ከበሽታው ቀድሞ ...
በመላኩ መጅ ነው ...እያገላበጠ ቀድሞ #የሚያስከካ ።
#ስብሀት_ለአብ
አቤት ውስጤ #ግሙ
አወየው... #ምላሴ
ስፍር የሌለውን
የበደል ስልቻ ፥ በተቸራት ስጋ ፥ ለታቀፈች ነብሴ
አርምሞሽ ነው #ፅድቄ ፥ ዝምታሽ ነው #ዋሴ
ይሄን ፀሎት ብለሽ...
እምነትሽ መንምኖ ፥ በተስፋ ማጣት ውስጥ ፥ ከምትላወሺ
መለመኑ ይቅር...
ቃል ማውጣቱም ይብቃሽ ..... ለዛሬ ለምሺ ።
ብዬ ወደ ቀልቤ ስመለስ...
እራሴን ሳነቃ..
ሰላም ግቡ ተብሎ .....
ምዕመኑ በፊናው ፥ መላወስ ጀመረ
የጨመትኩት ልሳን ፥ ማዕልተ ፀሎቱ ፥ እዲህ ሲል ቋጠረ !!
በሸከፍነው ከንቱነት...ለሚገጥመን ፈተና
ስናውቅም ...ሳናውቅም ...አስቸጋሪ ነን እና
ምዕንተ እግዝዕትነ ማርያም ....እግዚኦ....መሀረና
#እምነት_ሰው_ያቆማል....እንኳንስ ኮሮና
✍ #አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
✍ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
#ኢትዮጵያ የታጠቡ እጆችዋን ወደ ፈጣሪ ትዘረጋለች!!!💚💛❤️
ሶስት ወፎች ዛፍ ላይ አርፈዋል ፤ ከሶስቱ መካከል አንዱ ለመብረር ወሰነ ።ምን ያክል ወፎች ዛፉ ላይ እንደቀሩ ይገምታሉ ?
… መልስ ስጡኝ ! በእርግጠኝነት አብዛኞቻችን ሁለት ወፎች እንደቀሩ ነው የምናስበው። ግን እንዲያ አይደለም። ከሶስቱ ወፎች መካከል አንደኛው ለመብረር ወሰነ እንጂ በተጨባጭ አልበረረም ፤ ስለዚህ ዛፉ ላይ የቀሩት ወፎች ሶስቱም ናቸው ። በሌላ አገላለፅ አንዳች የተለወጠ ነገር የለም ማለት ነው ። … ውድ የፌስቡክ ወዳጆቼ ! አሁን እያንዳንዳችን ራሳችንን እንጠይቅ ።ለምን ያክል ጊዜ ይሆናል አንዳች ነገር ለመፈፀም ወስነህ ሳትተገብረው የቀረነው ? ያ ከግብ ለማድረስ ያሰብከው ጉዳይ ሳንሰራው በመቅረታችን ብቻ እንዳለ በመቅረቱ እና ባለመተግበራችን ምናልባትም የከፋ ሌላ ነገር ያመጣብንስ አጋጣሚ ምን ያክል ነው ? የአንድን ነገር ፍሬ ለመልቀም …. መመኘት ÷ ማቀድና የስኬቱን መዳረሻ መንገድ መቀየስ ብቻውን በቂ አይሆንም … ይልቁንም ወደ ትግበራው መስክ በተጨባጭ መዝለቁ ነው ስኬታማ ሊያደርግ የሚችለው !!!!
ወፏም በተግባር ሳትበር ለመብረር በታሳበ እቅድ ብቻ ሶስትነትን ወደ ሁለትነት ፈፅሞ መቀየር እንዳልተቻለ ሁሉ አንተም አድርግ በህክምና ባለሙያዎች አድርግ የተባልከው ወደ ተግባር የማትለውጥ ከሆነ በማሰብ ፣ ፌስቡክ ላይ በማውራት የምትለውጠው ነገር ፈፅሞ ሊኖር
አይችልም … ይባስ ብሎ የምታጣው ነገር ይኖር ይሆናል እንጂ !!! ይቅር በለኝ … እኔም የናንተው ቢጤ ስለሆንኩ ስድቡ የወል ነው አይዞን … በል አሁን ራሳችንን ካለንበት ተጨባጭ ለማውጣት በህክምና ባለሙያዎች የሚነግሩንን ምክር ወደ #ተግባር የምንለውጥበት ጊዜ አሁን ነው!! … ያኔ በዙሪያችን ያሉት አብረውን እንዲበሩተምሳሌት ሆንናቸው ማለት ነው ፣ ያኔ በዙሪያችን ያሉትን ቤተሰቦቻችንን ፣ ጓደኞችቻችንን ፣ ጎረቤቶቻችንን ፣ ሀገራችንን አዳንን ማለት ነው። እበራለሁ ብሎ ብቻ ማሰቡ፣አደርጋለሁ በሎ ማሰቡ በዙሪያህ ያሉትን ማዳከም ነው። የንድፈ-ሀሳብ ሀገር ነው የምትፈጥረው … በሉ እንብረር … ፋና ወጊ እንሁን … ብርር እያልን ሌሎችም ክንፍ ፣ ሌሎችም ማድረግ እንደሚችሉ እናሳያቸው …ኑ እንብረር … ኑ ተግባር የሚያመጣውን ለውጥ እናሳይ .... አርዓያ እንሁን ........
#"ግመልህን እሰርና በአላህ ተመካ" (ነብዩ መሀመድ ሰዐወ❤️)
#እምነት የምግባር ውጤት ነች!!
ጥንቃቄ ይጠብቅሃል÷ማስተዋል ይጋርድሃል።
ምሳሌ2÷11
@getem
@getem
@Nagayta
ሶስት ወፎች ዛፍ ላይ አርፈዋል ፤ ከሶስቱ መካከል አንዱ ለመብረር ወሰነ ።ምን ያክል ወፎች ዛፉ ላይ እንደቀሩ ይገምታሉ ?
… መልስ ስጡኝ ! በእርግጠኝነት አብዛኞቻችን ሁለት ወፎች እንደቀሩ ነው የምናስበው። ግን እንዲያ አይደለም። ከሶስቱ ወፎች መካከል አንደኛው ለመብረር ወሰነ እንጂ በተጨባጭ አልበረረም ፤ ስለዚህ ዛፉ ላይ የቀሩት ወፎች ሶስቱም ናቸው ። በሌላ አገላለፅ አንዳች የተለወጠ ነገር የለም ማለት ነው ። … ውድ የፌስቡክ ወዳጆቼ ! አሁን እያንዳንዳችን ራሳችንን እንጠይቅ ።ለምን ያክል ጊዜ ይሆናል አንዳች ነገር ለመፈፀም ወስነህ ሳትተገብረው የቀረነው ? ያ ከግብ ለማድረስ ያሰብከው ጉዳይ ሳንሰራው በመቅረታችን ብቻ እንዳለ በመቅረቱ እና ባለመተግበራችን ምናልባትም የከፋ ሌላ ነገር ያመጣብንስ አጋጣሚ ምን ያክል ነው ? የአንድን ነገር ፍሬ ለመልቀም …. መመኘት ÷ ማቀድና የስኬቱን መዳረሻ መንገድ መቀየስ ብቻውን በቂ አይሆንም … ይልቁንም ወደ ትግበራው መስክ በተጨባጭ መዝለቁ ነው ስኬታማ ሊያደርግ የሚችለው !!!!
ወፏም በተግባር ሳትበር ለመብረር በታሳበ እቅድ ብቻ ሶስትነትን ወደ ሁለትነት ፈፅሞ መቀየር እንዳልተቻለ ሁሉ አንተም አድርግ በህክምና ባለሙያዎች አድርግ የተባልከው ወደ ተግባር የማትለውጥ ከሆነ በማሰብ ፣ ፌስቡክ ላይ በማውራት የምትለውጠው ነገር ፈፅሞ ሊኖር
አይችልም … ይባስ ብሎ የምታጣው ነገር ይኖር ይሆናል እንጂ !!! ይቅር በለኝ … እኔም የናንተው ቢጤ ስለሆንኩ ስድቡ የወል ነው አይዞን … በል አሁን ራሳችንን ካለንበት ተጨባጭ ለማውጣት በህክምና ባለሙያዎች የሚነግሩንን ምክር ወደ #ተግባር የምንለውጥበት ጊዜ አሁን ነው!! … ያኔ በዙሪያችን ያሉት አብረውን እንዲበሩተምሳሌት ሆንናቸው ማለት ነው ፣ ያኔ በዙሪያችን ያሉትን ቤተሰቦቻችንን ፣ ጓደኞችቻችንን ፣ ጎረቤቶቻችንን ፣ ሀገራችንን አዳንን ማለት ነው። እበራለሁ ብሎ ብቻ ማሰቡ፣አደርጋለሁ በሎ ማሰቡ በዙሪያህ ያሉትን ማዳከም ነው። የንድፈ-ሀሳብ ሀገር ነው የምትፈጥረው … በሉ እንብረር … ፋና ወጊ እንሁን … ብርር እያልን ሌሎችም ክንፍ ፣ ሌሎችም ማድረግ እንደሚችሉ እናሳያቸው …ኑ እንብረር … ኑ ተግባር የሚያመጣውን ለውጥ እናሳይ .... አርዓያ እንሁን ........
#"ግመልህን እሰርና በአላህ ተመካ" (ነብዩ መሀመድ ሰዐወ❤️)
#እምነት የምግባር ውጤት ነች!!
ጥንቃቄ ይጠብቅሃል÷ማስተዋል ይጋርድሃል።
ምሳሌ2÷11
@getem
@getem
@Nagayta
👍1
#የልቤ....#እምነት_ክህደት_ቃል
የልክ ሚዛኔ ፥ ላንቺ ተሰበረ
ሰው ሲመዝን ኖሮ ፥
በገለባ አለም ፥ ወርቅ አንቺን ሰፈረ
እቱ ለግላጋዋ !!
እንዶድ ፍቅርሽ ደርሶት
ቅምሻን የታደለ ፥ ካዘኔታሽ ጥዋ
እንኳን እኔ ቀርቶ
መውደድ ያልሸተተው ፥
ለበቀል መሀላ ፥ እራሱን የሰዋ
............. ሳጥናኤል ይገራል
ሰውነት ሰው ሲሆን ፥
ካንቺ መዲያ ላሳር ፥ ሰው ማለም ይከብዳል ።
#አየሽ
ልኬት ለሰበረ ፥ የፍቅር ናሙና
ቃል እየቀረፁ ፥ መቀኞ ቢወርዱ
ምላስ ያነክሳል
አልማዝ ባየ ግዜ ፥ ኮምቼ ሲቆልል ፥ ለከረመ ልምዱ
ጨለማ ተዘግቶ ፥ አዘቅት የከረመ
ብርሀን ቢግቱት ፥ አይኑ እንደታመመ
#ያ' ሰውዬሽ....................... ነኝ እኔ
በወገግታው ዳፍንት ፥ ያጣሁሽ ከጎኔ ።
ቀሽም ቃላቶቼ ፥ ቃልኪዳን አድሰው
ለሰበርኩት ልብሽ ፥ ካሳ ባይሆንሽም
በመምጣትሽ ስካር ፥ ደስታን ባላሟሽም
ያዘገየሽ ግዜ ፥ ቀድሞ ቢወስድሽም
ከኔ ለፈቀቀ ፥ ያንቺ ልዕልና
ጎረበጠኝ ብዬ ፥ አንቺን አልወቅስሽም ።
አንዳንዴ ባይገርምሽ
ፅጌሬዳ አበባ ፥ ውበቷ ሳያንሳት
ሳይነኳት የሚደርስ
ያንን ሁሉ እሾህ ፥ ለጉድ ያሸከምካት
በለስ....ሺ ምንተሺ
እሾህ ቆዳ ስፌት ፥ ጣሟን ያለበስካት
ም'ነው .... አልክ እግዜሩ ?
እላለው
ለሰውነት ህመም
መድህኒት የምትሆን ፥ እንዲት እግሯ ልጅህ
ሰርክ ጠዋት ማታ ፥ ሳትለይ ከደጅህ
በቁም ከሞቱ ጎን ፥ በመስክ አውለሀት
እንዳረጀ ቀብር ፥ በሙታን ወረዳ ፥ ሳማ የከበባት
ምንኛ....ብትወዳት ?
ምንኛ...ብታምናት ?
#እላለው !!
ይሄም ውጣ ውረድ ፥ እያብሰከሰከ ሆዴን ቢበላኝም
ንስር ማንነትሽ ፥
መውጫ ቢያጣ ፥ ብዬ አያሳስበኝም ።
#ይልቅ
ኩፍኩፍ ይመስል ፥
ትዝታሽ በግዜ ፥ በዋዛ ባይለቅም
መጣሽ ከማለቴ
ለመለመ ያልኩት ፥ በቅፅበት ቢደርቅም
ሞገስሽን ያዬ ልቤ
ምን እንደሚልሽ አያውቅም።
2012
#አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
@Abrham_teklu
@getem
@getem
@getem
የልክ ሚዛኔ ፥ ላንቺ ተሰበረ
ሰው ሲመዝን ኖሮ ፥
በገለባ አለም ፥ ወርቅ አንቺን ሰፈረ
እቱ ለግላጋዋ !!
እንዶድ ፍቅርሽ ደርሶት
ቅምሻን የታደለ ፥ ካዘኔታሽ ጥዋ
እንኳን እኔ ቀርቶ
መውደድ ያልሸተተው ፥
ለበቀል መሀላ ፥ እራሱን የሰዋ
............. ሳጥናኤል ይገራል
ሰውነት ሰው ሲሆን ፥
ካንቺ መዲያ ላሳር ፥ ሰው ማለም ይከብዳል ።
#አየሽ
ልኬት ለሰበረ ፥ የፍቅር ናሙና
ቃል እየቀረፁ ፥ መቀኞ ቢወርዱ
ምላስ ያነክሳል
አልማዝ ባየ ግዜ ፥ ኮምቼ ሲቆልል ፥ ለከረመ ልምዱ
ጨለማ ተዘግቶ ፥ አዘቅት የከረመ
ብርሀን ቢግቱት ፥ አይኑ እንደታመመ
#ያ' ሰውዬሽ....................... ነኝ እኔ
በወገግታው ዳፍንት ፥ ያጣሁሽ ከጎኔ ።
ቀሽም ቃላቶቼ ፥ ቃልኪዳን አድሰው
ለሰበርኩት ልብሽ ፥ ካሳ ባይሆንሽም
በመምጣትሽ ስካር ፥ ደስታን ባላሟሽም
ያዘገየሽ ግዜ ፥ ቀድሞ ቢወስድሽም
ከኔ ለፈቀቀ ፥ ያንቺ ልዕልና
ጎረበጠኝ ብዬ ፥ አንቺን አልወቅስሽም ።
አንዳንዴ ባይገርምሽ
ፅጌሬዳ አበባ ፥ ውበቷ ሳያንሳት
ሳይነኳት የሚደርስ
ያንን ሁሉ እሾህ ፥ ለጉድ ያሸከምካት
በለስ....ሺ ምንተሺ
እሾህ ቆዳ ስፌት ፥ ጣሟን ያለበስካት
ም'ነው .... አልክ እግዜሩ ?
እላለው
ለሰውነት ህመም
መድህኒት የምትሆን ፥ እንዲት እግሯ ልጅህ
ሰርክ ጠዋት ማታ ፥ ሳትለይ ከደጅህ
በቁም ከሞቱ ጎን ፥ በመስክ አውለሀት
እንዳረጀ ቀብር ፥ በሙታን ወረዳ ፥ ሳማ የከበባት
ምንኛ....ብትወዳት ?
ምንኛ...ብታምናት ?
#እላለው !!
ይሄም ውጣ ውረድ ፥ እያብሰከሰከ ሆዴን ቢበላኝም
ንስር ማንነትሽ ፥
መውጫ ቢያጣ ፥ ብዬ አያሳስበኝም ።
#ይልቅ
ኩፍኩፍ ይመስል ፥
ትዝታሽ በግዜ ፥ በዋዛ ባይለቅም
መጣሽ ከማለቴ
ለመለመ ያልኩት ፥ በቅፅበት ቢደርቅም
ሞገስሽን ያዬ ልቤ
ምን እንደሚልሽ አያውቅም።
2012
#አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
@Abrham_teklu
@getem
@getem
@getem