ግጥም ብቻ 📘
67.6K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
#የልቤ....#እምነት_ክደት_ቃል
፨፨፨፨
፨፨፨
፨፨
#አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)

የልክ ሚዛኔ ፥ ላንቺ ተሰበረ
ሰው ሲመዝን ኖሮ
በገለባ አለም ፥ ወርቅ አንቺን ሰፈረ
እቱ ለግላጋዋ !!
እንዶድ ፍቅርሽ ደርሶት
ቅምሻን የታደለ ፥ ካዘኔታሽ ጥዋ
እንኳን እኔ ቀርቶ
መውደድ ያልሸተተው
ለበቀል መሀላ ፥ እራሱን የሰዋ
ሳጥናኤል ይገራል
ሰውነት ሰው ሲሆን
ካንቺ መዲያ ላሳር ፥ ሰው ማለም ይከብዳል ።
#አየሽ
ልኬት ለሰበረ ፥ የፍቅር ናሙና
ቃል እየቀረፁ ፥ መቀኞ ቢወርዱ
ምላስ ያነክሳል
አልማዝ ባየ ግዜ
ኮምቼ ሲቆልል ፥ ለከረመ ልምዱ
ጨለማ ተዘግቶ ፥ አዘቅት የከረመ
ብርሀን ቢግቱት ፥ አይኑ እንደታመመ
#ያ' ሰውዬሽ....................... ነኝ እኔ
በወገግታው ዳፍንት ፥ ያጣሁሽ ከጎኔ ።
ቀሽም ቃላቶቼ ፥ ቃልኪዳን አድሰው
ለሰበርኩት ልብሽ ፥ ካሳ ባይሆንሽም
በመምጣትሽ ስካር ፥ ደስታን ባላሟሽም
ያዘገየሽ ግዜ ፥ ቀድሞ ቢወስድሽም
ከኔ ለፈቀቀ ፥ ያንቺ ልዕልና
ጎረበጠኝ ብዬ ፥ አንቺን አልወቅስሽም
አንዳንዴ ባይገርምሽ
ፅጌሬዳ አበባ ፥ ውበቷ ሳያንሳት
ሳይነኳት የሚደርስ
ያንን ሁሉ እሾህ ፥ ለጉድ ያሸከምካት
በለስ....ሺ ምንተሺ
እሾህ ቆዳ ስፌት ፥ ጣሟን ያለበስካት
ም'ነው .... አልክ እግዜሩ ?
እላለው
ለሰውነት ህመም
መድህኒት የምትሆን ፥ እንዲት እግሯ ልጅህ
ሰርክ ጠዋት ማታ ፥ ሳትለይ ከደጅህ
በቁም ከሞቱ ጎን ፥ በመስክ አውለሀት
እንዳረጀ ቀብር ፥ በሙታን ወረዳ ፥ ሳማ የከበባት
ምንኛ....ብትወዳት ?
ምንኛ...ብታምናት ?
#እላለው !!
ይሄም ውጣ ውረድ ፥ እያብሰከሰከ ሆዴን ቢበላኝም
ንስር ማንነትሽ
መውጫ ቢያጣ ፥ ብዬ አያሳስበኝም
#ይልቅ
ኩፍኩፍ ይመስል
ትዝታሽ በግዜ ፥ በዋዛ ባይለቅም
መጣሽ ከማለቴ
ለመለመ ያልኩት ፥ በቅፅበት ቢደርቅም
ሞገስሽን ያዬ ልቤ
ምን እንደሚልሽ አያውቅም።

@Abr_sh

@getem
@getem
@getem
#የልቤ....#እምነት_ክህደት_ቃል


የልክ ሚዛኔ ፥ ላንቺ ተሰበረ
ሰው ሲመዝን ኖሮ ፥
በገለባ አለም ፥ ወርቅ አንቺን ሰፈረ
እቱ ለግላጋዋ !!
እንዶድ ፍቅርሽ ደርሶት
ቅምሻን የታደለ ፥ ካዘኔታሽ ጥዋ
እንኳን እኔ ቀርቶ
መውደድ ያልሸተተው ፥
ለበቀል መሀላ ፥ እራሱን የሰዋ
............. ሳጥናኤል ይገራል
ሰውነት ሰው ሲሆን ፥
ካንቺ መዲያ ላሳር ፥ ሰው ማለም ይከብዳል ።

#አየሽ
ልኬት ለሰበረ ፥ የፍቅር ናሙና
ቃል እየቀረፁ ፥ መቀኞ ቢወርዱ
ምላስ ያነክሳል
አልማዝ ባየ ግዜ ፥ ኮምቼ ሲቆልል ፥ ለከረመ ልምዱ
ጨለማ ተዘግቶ ፥ አዘቅት የከረመ
ብርሀን ቢግቱት ፥ አይኑ እንደታመመ
#ያ' ሰውዬሽ....................... ነኝ እኔ
በወገግታው ዳፍንት ፥ ያጣሁሽ ከጎኔ ።
ቀሽም ቃላቶቼ ፥ ቃልኪዳን አድሰው
ለሰበርኩት ልብሽ ፥ ካሳ ባይሆንሽም
በመምጣትሽ ስካር ፥ ደስታን ባላሟሽም
ያዘገየሽ ግዜ ፥ ቀድሞ ቢወስድሽም
ከኔ ለፈቀቀ ፥ ያንቺ ልዕልና
ጎረበጠኝ ብዬ ፥ አንቺን አልወቅስሽም ።

አንዳንዴ ባይገርምሽ
ፅጌሬዳ አበባ ፥ ውበቷ ሳያንሳት
ሳይነኳት የሚደርስ
ያንን ሁሉ እሾህ ፥ ለጉድ ያሸከምካት
በለስ....ሺ ምንተሺ
እሾህ ቆዳ ስፌት ፥ ጣሟን ያለበስካት
ም'ነው .... አልክ እግዜሩ ?
እላለው
ለሰውነት ህመም
መድህኒት የምትሆን ፥ እንዲት እግሯ ልጅህ
ሰርክ ጠዋት ማታ ፥ ሳትለይ ከደጅህ
በቁም ከሞቱ ጎን ፥ በመስክ አውለሀት
እንዳረጀ ቀብር ፥ በሙታን ወረዳ ፥ ሳማ የከበባት
ምንኛ....ብትወዳት ?
ምንኛ...ብታምናት ?
#እላለው !!
ይሄም ውጣ ውረድ ፥ እያብሰከሰከ ሆዴን ቢበላኝም
ንስር ማንነትሽ ፥
መውጫ ቢያጣ ፥ ብዬ አያሳስበኝም ።

#ይልቅ
ኩፍኩፍ ይመስል ፥
ትዝታሽ በግዜ ፥ በዋዛ ባይለቅም
መጣሽ ከማለቴ
ለመለመ ያልኩት ፥ በቅፅበት ቢደርቅም
ሞገስሽን ያዬ ልቤ
ምን እንደሚልሽ አያውቅም።

2012

#አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)

@Abrham_teklu
@getem
@getem
@getem