ከላይ!!!!!
የታች ሰፈር ልጆች ፤
የታች ቤት ግርደኞች፤
ደግሞ ይኸን ሰሞን፤
በጭራቅ ፉከራ፤
እየወዘወዙን ፤
ቁ
\
ል
\
ቁ
\
ል
እየሳቡን ፤ ይዘዋል ጉተታ፤
አላወቁም መሰል፤
ከ"ላይኛው" ሆነው፤ አገር እንዳፀኑ ሃጅና መርጌታ።
መገን የላይኛው!!"
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
ሸጋ ሸጊቱ ጁምኣ!💚
@getem
@getem
@balmbaras
የታች ሰፈር ልጆች ፤
የታች ቤት ግርደኞች፤
ደግሞ ይኸን ሰሞን፤
በጭራቅ ፉከራ፤
እየወዘወዙን ፤
ቁ
\
ል
\
ቁ
\
ል
እየሳቡን ፤ ይዘዋል ጉተታ፤
አላወቁም መሰል፤
ከ"ላይኛው" ሆነው፤ አገር እንዳፀኑ ሃጅና መርጌታ።
መገን የላይኛው!!"
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
ሸጋ ሸጊቱ ጁምኣ!💚
@getem
@getem
@balmbaras
👍1
አደይ ሚክስድ አርት !
ዩቶጵያ ቪዥዋል አርትስ ክለብ ከ አዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር በወጣት የስነ-ጥበብ ባለሙያዎች የተከሸነ የድብልቅ ጥበባት (Mixed art) ኤግዝቢሽን ከመስከረም 14-20 ደረስ በአዲስ አበባ ሙዚየም ለእይታ ይበቃል ፡፡ የጥበብ ድግሳችን ተካፋይ እንዲሆኑ ተጋብዘዋል !
መክፈቻ ሰዓት ፡- 11:30
ለበለጠ መረጃ
0984871096
0942600644
0973950532
@Utopiavisualarts
@utopiavisualarts
ዩቶጵያ ቪዥዋል አርትስ ክለብ ከ አዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር በወጣት የስነ-ጥበብ ባለሙያዎች የተከሸነ የድብልቅ ጥበባት (Mixed art) ኤግዝቢሽን ከመስከረም 14-20 ደረስ በአዲስ አበባ ሙዚየም ለእይታ ይበቃል ፡፡ የጥበብ ድግሳችን ተካፋይ እንዲሆኑ ተጋብዘዋል !
መክፈቻ ሰዓት ፡- 11:30
ለበለጠ መረጃ
0984871096
0942600644
0973950532
@Utopiavisualarts
@utopiavisualarts
(✍ አለሙ አዳፋ)
አክባሪ ተንቆ - ተከባሪ ልቆ
አዳማጭ ተረስቶ - ተናጋሪ ደምቆ
ከማወቅ - መታወቅ
ከማየት - መታየት...
ከመውደድ - መወደድ
ከመስማት - መሰማት...
ከሚመኝ ኗሪ ጋር
በምጓዘው መንገድ - በማልፋቸው ቀናት
ካንቺ ውጭ ለሌላ
ልቤ ቀጣፊ ነች - ነፍሴም ዱርየ ናት፡፡
.
አድባሬ ...
ሀገሬ❤️
@getem
@getem
@kaleab_1888
አክባሪ ተንቆ - ተከባሪ ልቆ
አዳማጭ ተረስቶ - ተናጋሪ ደምቆ
ከማወቅ - መታወቅ
ከማየት - መታየት...
ከመውደድ - መወደድ
ከመስማት - መሰማት...
ከሚመኝ ኗሪ ጋር
በምጓዘው መንገድ - በማልፋቸው ቀናት
ካንቺ ውጭ ለሌላ
ልቤ ቀጣፊ ነች - ነፍሴም ዱርየ ናት፡፡
.
አድባሬ ...
ሀገሬ❤️
@getem
@getem
@kaleab_1888
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
መውደድ በዝምታ
_____________
የኔ ልብ እንዲሁ ነው...
ዝምታ ያነቀው
ተጓዥ መስሎ ፈሪ፣
ለፍቅር ሸፍቶ፣
ተመልሶ ደግሞ፣
ፍቅርን አባራሪ።
ያንቺን ብርቅዬ ልብ፣
አጠምዳለሁ ብሎ፣
አሰሳ ፍለጋ
ሲንከራተት ውሎ፣
ኢምንት ስትቀረው፣
ፍርሀት የሚያጠምደው
ቆርጦ ይነሳና፣
አለሁኝ ይልና፣
የዝምታ ነፋስ፣
መልሶ የሚሰደው።
አይኖቼም ያው ናቸው....
አንቺ የሌለሽ ጊዜ፣
አንቺን ያልማሉ፣
ፀጥ ባለው ሌሊት
ከዕንቅልፍ ይሸሻሉ።
ካይኖችሽ ተዋደው፣
በፍቅር እሳት ነደው፣
ልተኛ ስላቸው፣
እምቢ ነው መልሳቸው።
ወዲያ ወዲህ እያሉ፣
በድቅድቅ ጨለማ፣
ያንከራትቱኛል፣
ጥርት አርገው ስለው፣
ከነ መላው አካልሽ፣
አንቺን ያሳዩኛል።
ድንገት ስትመጪ ግን...
ውልብልብ አይኖቼ፣
እንዳልተርክልሽ፣
የልቤን አውጥቼ፣
አይንሽን እንዳላይ፣
ፍርሀቴን እንዳልተው፣
ይከለክሉኛል፣
አትያት ይሉኛል፣
ገላጣው መሬት ላይ፣
ቁልቁል ተሰክተው።
አንደበቴም ያው ነው....
ሲያገኝሽ ይዘጋል፣
ሲያጣሽ ይከፈታል፣
ቀን ቀን ዝም ይልና፣
ሌሊት ይበረታል።
ማንም በሌለበት
ያለ አንዳች ፍራቻ፣
እልፍ አእላፍ ቃላት፣
እየደረደርኩኝ፣
አንቺን ማሰብ ብቻ።
ድንገት ሳገኝሽግን...
ከንፈሬ ታትሞ፣
ምላሴ ይታሰራል፣
ድንጉጥ አንደበቴ፣
"ምን ልበል" እያለ፣
በቃላቶች መሐል፣
ተለጉሞ ይቀራል።
እጆቼም ያው ናቸው....
አንቺን ያዩ ጊዜ፣
ከሁዋላዬ ዞረው፣
ይቆላለፋሉ፣
ቀጭኑ ወገቤን፣
ምሽግ ያደርጋሉ፣
ለስላሳ ጉንጭሽን፣
ሊዳብሱ ብለው፣
ፈርተው ይመለሳሉ።
ደግሞ አንቺ ሳትኖሪ...
ድንግርግር እጆቼ፣
"ብዕር አምጣ" ይሉኛል
ስንኝ አሰባስበው፣
ለሚያሰቃይ ፍቅርሽ፣
ግጥም ያፅፉኛል።
የኔ ፍቅር እንዲህ ነው...
ብቻዬን በመሆን፣
ያለአንዳች ፍራቻ፣
እልፍ አእላፍ ቃላት፣
እየደረደርኩኝ፣
አንቺን ማሰብ ብቻ።
በቃ እንዲህ ልውደድሽ....
ከጥርሶችሽ ጋራ፣
የሚስቅ ፊትሽን፣
በማያዩ አይኖቼ፣
አካልሽን መንካት፣
በሚፈሩ እጆቼ፣
በህልፍ አክናፍ ብቻ፣
በሩቁ እያሰብኩሽ፣
ሳልቀርብሽ ሸሽቼ።
ግን አንድ ተስፋ አለኝ....
በጨለማው አለም፣
አጥርተው የሚያዩሽን፣
አይኖቼን ከፍቼ ፣
ታትመው የቆዩትን፣
ፈሪ ከንፈሮቼን፣
ለቃላት ፈትቼ፣
ልብሽን መማረክ፣
የተሳነው ልቤን፣
በግድ አበርትቼ፣
እንቀፋት ብለው፣
ይንደረደሩና፣
ደረስን ይሉና፣
ፈርተው የሚደበቁ፣
ተሸናፊ እጆቼን፣
እንደ አሞራ ክንፍ፣
በሰፊው ዘርግቼ፣
በህይወት እስካለሽ ፣
በህይወት እስካለሁ፣
ግድ የለም ጠብቂኝ ፣
የሚርቅ ቢመስልም፣
አንድ ቀን መጣለሁ።
( ጠብቂኝ)
✍ ዮሐንስ ገርማሜ
@getem
@getem
@getem
መውደድ በዝምታ
_____________
የኔ ልብ እንዲሁ ነው...
ዝምታ ያነቀው
ተጓዥ መስሎ ፈሪ፣
ለፍቅር ሸፍቶ፣
ተመልሶ ደግሞ፣
ፍቅርን አባራሪ።
ያንቺን ብርቅዬ ልብ፣
አጠምዳለሁ ብሎ፣
አሰሳ ፍለጋ
ሲንከራተት ውሎ፣
ኢምንት ስትቀረው፣
ፍርሀት የሚያጠምደው
ቆርጦ ይነሳና፣
አለሁኝ ይልና፣
የዝምታ ነፋስ፣
መልሶ የሚሰደው።
አይኖቼም ያው ናቸው....
አንቺ የሌለሽ ጊዜ፣
አንቺን ያልማሉ፣
ፀጥ ባለው ሌሊት
ከዕንቅልፍ ይሸሻሉ።
ካይኖችሽ ተዋደው፣
በፍቅር እሳት ነደው፣
ልተኛ ስላቸው፣
እምቢ ነው መልሳቸው።
ወዲያ ወዲህ እያሉ፣
በድቅድቅ ጨለማ፣
ያንከራትቱኛል፣
ጥርት አርገው ስለው፣
ከነ መላው አካልሽ፣
አንቺን ያሳዩኛል።
ድንገት ስትመጪ ግን...
ውልብልብ አይኖቼ፣
እንዳልተርክልሽ፣
የልቤን አውጥቼ፣
አይንሽን እንዳላይ፣
ፍርሀቴን እንዳልተው፣
ይከለክሉኛል፣
አትያት ይሉኛል፣
ገላጣው መሬት ላይ፣
ቁልቁል ተሰክተው።
አንደበቴም ያው ነው....
ሲያገኝሽ ይዘጋል፣
ሲያጣሽ ይከፈታል፣
ቀን ቀን ዝም ይልና፣
ሌሊት ይበረታል።
ማንም በሌለበት
ያለ አንዳች ፍራቻ፣
እልፍ አእላፍ ቃላት፣
እየደረደርኩኝ፣
አንቺን ማሰብ ብቻ።
ድንገት ሳገኝሽግን...
ከንፈሬ ታትሞ፣
ምላሴ ይታሰራል፣
ድንጉጥ አንደበቴ፣
"ምን ልበል" እያለ፣
በቃላቶች መሐል፣
ተለጉሞ ይቀራል።
እጆቼም ያው ናቸው....
አንቺን ያዩ ጊዜ፣
ከሁዋላዬ ዞረው፣
ይቆላለፋሉ፣
ቀጭኑ ወገቤን፣
ምሽግ ያደርጋሉ፣
ለስላሳ ጉንጭሽን፣
ሊዳብሱ ብለው፣
ፈርተው ይመለሳሉ።
ደግሞ አንቺ ሳትኖሪ...
ድንግርግር እጆቼ፣
"ብዕር አምጣ" ይሉኛል
ስንኝ አሰባስበው፣
ለሚያሰቃይ ፍቅርሽ፣
ግጥም ያፅፉኛል።
የኔ ፍቅር እንዲህ ነው...
ብቻዬን በመሆን፣
ያለአንዳች ፍራቻ፣
እልፍ አእላፍ ቃላት፣
እየደረደርኩኝ፣
አንቺን ማሰብ ብቻ።
በቃ እንዲህ ልውደድሽ....
ከጥርሶችሽ ጋራ፣
የሚስቅ ፊትሽን፣
በማያዩ አይኖቼ፣
አካልሽን መንካት፣
በሚፈሩ እጆቼ፣
በህልፍ አክናፍ ብቻ፣
በሩቁ እያሰብኩሽ፣
ሳልቀርብሽ ሸሽቼ።
ግን አንድ ተስፋ አለኝ....
በጨለማው አለም፣
አጥርተው የሚያዩሽን፣
አይኖቼን ከፍቼ ፣
ታትመው የቆዩትን፣
ፈሪ ከንፈሮቼን፣
ለቃላት ፈትቼ፣
ልብሽን መማረክ፣
የተሳነው ልቤን፣
በግድ አበርትቼ፣
እንቀፋት ብለው፣
ይንደረደሩና፣
ደረስን ይሉና፣
ፈርተው የሚደበቁ፣
ተሸናፊ እጆቼን፣
እንደ አሞራ ክንፍ፣
በሰፊው ዘርግቼ፣
በህይወት እስካለሽ ፣
በህይወት እስካለሁ፣
ግድ የለም ጠብቂኝ ፣
የሚርቅ ቢመስልም፣
አንድ ቀን መጣለሁ።
( ጠብቂኝ)
✍ ዮሐንስ ገርማሜ
@getem
@getem
@getem
👍2
ወንዘኛ!!!!!!!
በቆሙበት መሬት ፤
የተደበቀውን፤
ያንን የውሃ ጋን፤
ቆፈር ቆፈር አርገው ፤
የእርሻውን ማጠጫ በውሃ እንዳይሞሉ፤
የኛ አገር ጥመኞች፤
ወደ ገዛ እርሻቸው፤
ውሃ እንፈልግ ብለው ፤ ጠልቀው ሳይቆፍሩ፤
በአጀብ በሆሆታ፤
ወንዝ እናምጣ ብለው ፤
የገዛ እርሻቸውን፤ ጥለው ኮበለሉ፤
ውሃ ባልጠፋበት፤
ወንዝ እንፈልግ ብለው፤ ወንዝ ገብተው ቀሩ።
ባለሁበት ቀየ ፤
የመሬት ስር ውሃ፤
ቆፍሩኝ እያለ ቁሞ በተጠንቀቅ፤ ልክ እንደበረኛ፤
ወንዝ አምጡልኝ ብሎ ይኸው ይናውዛል ስስታም ወንዘኛ።
በቆምኩበት ምድር ፤
የቆመ ውሃ አለኝ፤
ዶማየን አምጡልኝ ፤
ወንዝ እፈልግ ብየ፤ውሃየን አልሰጥም፤
ግን እስከዚያ ድረስ፤
ውሃ ጠማኝ ብየ ወንዝና ወንዘኛን አልለማመጥም።
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
ሸጋዋ እምወድሽዋ ቅዳሜ!❤ ለናተም ያማረ ቅዳሜ ይሁንላቹ!❤
@getem
@getem
@balmbaras
በቆሙበት መሬት ፤
የተደበቀውን፤
ያንን የውሃ ጋን፤
ቆፈር ቆፈር አርገው ፤
የእርሻውን ማጠጫ በውሃ እንዳይሞሉ፤
የኛ አገር ጥመኞች፤
ወደ ገዛ እርሻቸው፤
ውሃ እንፈልግ ብለው ፤ ጠልቀው ሳይቆፍሩ፤
በአጀብ በሆሆታ፤
ወንዝ እናምጣ ብለው ፤
የገዛ እርሻቸውን፤ ጥለው ኮበለሉ፤
ውሃ ባልጠፋበት፤
ወንዝ እንፈልግ ብለው፤ ወንዝ ገብተው ቀሩ።
ባለሁበት ቀየ ፤
የመሬት ስር ውሃ፤
ቆፍሩኝ እያለ ቁሞ በተጠንቀቅ፤ ልክ እንደበረኛ፤
ወንዝ አምጡልኝ ብሎ ይኸው ይናውዛል ስስታም ወንዘኛ።
በቆምኩበት ምድር ፤
የቆመ ውሃ አለኝ፤
ዶማየን አምጡልኝ ፤
ወንዝ እፈልግ ብየ፤ውሃየን አልሰጥም፤
ግን እስከዚያ ድረስ፤
ውሃ ጠማኝ ብየ ወንዝና ወንዘኛን አልለማመጥም።
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
ሸጋዋ እምወድሽዋ ቅዳሜ!❤ ለናተም ያማረ ቅዳሜ ይሁንላቹ!❤
@getem
@getem
@balmbaras
We do have a Turkey scholarship opportunities in advance for each department. Hopefully students who take their Entrance exam in 2011 can benefit alot from this chance. Wait us for the detail of scholarship.
@foreignwork
@Coolrepublic
@foreignwork
@Coolrepublic
Any one who is university or college graduate who wants to work in Poland can contact us now. For this round we need individual who do have a renewed Ethiopian passport and willing to work in a factory with a granted safety and reasonable payment. This will enables you to get two years work permit and Schengen VISA.
@foreignwork
@Coolrepublic
@foreignwork
@Coolrepublic
ግራ ነው መንገዴ
°°°
፰\፩\፪፳፲፪ ©ዘርዓሰብ
°°°
ሰዎች ይመክራሉ በለመዱት መንገድ በዚህ ሂድ እያሉ
የቀደመውን ሰው ያልተመረመረ ህይወት ሳያሰሉ፤
እኔ ግራ ተጓዥ፣ ብቻ ጉዞ መራጭ፣
ሰው የማይደርስብኝ፣ ከሰው የማልጋጭ፤
የግራውን መንገድ ማንም አልሄደበት፤
ከሊቅ እስከ ደቂቅ በቀኙ ብቻ ነው ሁሌ የሚጋፉበት።
አምላክን በጸሎት ግራ አውለኝ አልኩት፣ አዋለኝ በግራ
ቃሌ አከበረችኝ የጸሎቴን ምላሽ ቃልህን አክብራ።
አይዝልም ጉልበቴ ምን ቢርቅ መንገዱ
አጀብ ይቅርብኝ ቀኝ በሚል ሰበብ በጅምላ መሄዱ
ሁሉ በቀኝ ብሎ ግራውን ቢተወው
ፍኖቱ ባይሰምር ባይሄዱበት ቀድመው
ጠልፎ ጣይ የለውም መንገዱ ቀና ነው።
ጻድቁም እርኩሱም፣ ደግም ይሁን ክፉ
ሁሉም በቀኝ ነው ታትረው የሚጋፉ።
ከሰይጣን ሰይጥነው የሚጠላለፉ።
ከመተራመስ ውጭ አልታየኝም ትርፉ።
በኑሮ ትጋት ውስጥ፣ ግራው ቀንቶልኛል፣ ይመስክር ጅማቴ
በርምጃ ነው እንጂ፣ በጠልፎ ጣይ ሰዎች፣ አልዛለም ጉልበቴ።
ከሚተመው ጋራ በቀኝ ለመብረር ከማብቀል ይልቅ ክንፍ
ለብቻ ባርምሞ ባልተሄደበት ላይ ያደርሳል እግር ጽንፍ።
\ዘርዓሰብ\
@getem
@getem
@getem
°°°
፰\፩\፪፳፲፪ ©ዘርዓሰብ
°°°
ሰዎች ይመክራሉ በለመዱት መንገድ በዚህ ሂድ እያሉ
የቀደመውን ሰው ያልተመረመረ ህይወት ሳያሰሉ፤
እኔ ግራ ተጓዥ፣ ብቻ ጉዞ መራጭ፣
ሰው የማይደርስብኝ፣ ከሰው የማልጋጭ፤
የግራውን መንገድ ማንም አልሄደበት፤
ከሊቅ እስከ ደቂቅ በቀኙ ብቻ ነው ሁሌ የሚጋፉበት።
አምላክን በጸሎት ግራ አውለኝ አልኩት፣ አዋለኝ በግራ
ቃሌ አከበረችኝ የጸሎቴን ምላሽ ቃልህን አክብራ።
አይዝልም ጉልበቴ ምን ቢርቅ መንገዱ
አጀብ ይቅርብኝ ቀኝ በሚል ሰበብ በጅምላ መሄዱ
ሁሉ በቀኝ ብሎ ግራውን ቢተወው
ፍኖቱ ባይሰምር ባይሄዱበት ቀድመው
ጠልፎ ጣይ የለውም መንገዱ ቀና ነው።
ጻድቁም እርኩሱም፣ ደግም ይሁን ክፉ
ሁሉም በቀኝ ነው ታትረው የሚጋፉ።
ከሰይጣን ሰይጥነው የሚጠላለፉ።
ከመተራመስ ውጭ አልታየኝም ትርፉ።
በኑሮ ትጋት ውስጥ፣ ግራው ቀንቶልኛል፣ ይመስክር ጅማቴ
በርምጃ ነው እንጂ፣ በጠልፎ ጣይ ሰዎች፣ አልዛለም ጉልበቴ።
ከሚተመው ጋራ በቀኝ ለመብረር ከማብቀል ይልቅ ክንፍ
ለብቻ ባርምሞ ባልተሄደበት ላይ ያደርሳል እግር ጽንፍ።
\ዘርዓሰብ\
@getem
@getem
@getem
#ጥላዬ
ፊን-ፊን ስትይ ፥ በሰማዩ ጋሪ
ሽቦ የታደለ ፥ ዣንጥላ ወጣሪ
ጥበብ ከነ መርፌ ፥ መጨበጡን ረሳሽ
ያገው ጥላ መሰል
ከፍ ያልሽበት ሰማይ ፥ ለዝንት የዘረጋሽ።
ይልቅ ተመከሪ ፥ ገርነት አይግፋሽ
አውታርሽ መብዛቱ
ገትሮ የሚውል ፥ የሚጥል ቃሬዛ
አይምሰልሽ ዋዛ !!!
ዝናብ ካላስጣለ ፥ ሽንቁሩ እየበዛ
ፀሀይ ካልከለለ ፥ ማድያት ከነዛ
ማን ወዶ ሊጠለል ...ማን ስርሽ ሊገዛ
የከበበ ሳይሆን
ያስተዳደረ ነው ፥ እድሜ የሚገዛ።
ነሀሴ 2011
✍ #አብርሀም_ተክሉ
@getem
@getem
@getem
ፊን-ፊን ስትይ ፥ በሰማዩ ጋሪ
ሽቦ የታደለ ፥ ዣንጥላ ወጣሪ
ጥበብ ከነ መርፌ ፥ መጨበጡን ረሳሽ
ያገው ጥላ መሰል
ከፍ ያልሽበት ሰማይ ፥ ለዝንት የዘረጋሽ።
ይልቅ ተመከሪ ፥ ገርነት አይግፋሽ
አውታርሽ መብዛቱ
ገትሮ የሚውል ፥ የሚጥል ቃሬዛ
አይምሰልሽ ዋዛ !!!
ዝናብ ካላስጣለ ፥ ሽንቁሩ እየበዛ
ፀሀይ ካልከለለ ፥ ማድያት ከነዛ
ማን ወዶ ሊጠለል ...ማን ስርሽ ሊገዛ
የከበበ ሳይሆን
ያስተዳደረ ነው ፥ እድሜ የሚገዛ።
ነሀሴ 2011
✍ #አብርሀም_ተክሉ
@getem
@getem
@getem
#ቸል እያሉ መጉደል!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።
ለቅፅበት ህላዌ ፥ ተግተው 'ሚባትሉ
በህብር ታጅበው ፥ ጭረው የሚውሉ
ዶሮዎች!
ለቅመው አዳሪዎች...
ከእጀባው ወጥታ.. .. ከመንጋው ተጠቅታ
በታደነች ጫጩት.. .
ሀዘን ተሸብረው ፥ ለስጋት ተድረው ፥ ጮኸው ይንጫጫሉ
ከአፍታ በኋላ.. .
ዳግም ፍርሀት ሽረው ፥ በኗሪነት ተስፋ ፥ ጥሬ ይለቅማሉ ።
#እነዛ ዶሮዎች.. .
አንድም በፍርሀት
አንድም በቸልታ
አንድ ጊዜ በጩኸት
አንዴ በፀጥታ...
ጥሬ ሲናጠቁ ፥ መሬት እየጫሩ
ከቁጥር ተናንሰው ...
ከመንጋነት ጎድለው ፥ ምንም ሆነው ቀሩ።
#አሁን በዛ መሬት!
ለቅፅበት ህላዌ ፥ ተግተው 'ሚባትሉ
በህብር ታጅበው ፥ ጭረው የሚውሉ
አዳዲስ ዶሮዎች.. .
ጭሮ አዳሪዎች.. .
አንድም በፍርሀት
አንድም በቸልታ
አንድ ጊዜ በጩኸት
አንዴ በፀጥታ...
ኗሪ ነን እያሉ ... ጥሬ ይለቅማሉ ።
#እኔ
#ድመት ይታየኛል!
እንደ ሙት መልዓክ ፥ ጥፍሮቹን ያሾለ
ነፍስን ጌጥ አድርጎ ፥ አይኖቹን የኳለ
ጨለማውን ህልፈት ፥ ጀርባው ላይ ያዘለ
ቀስ እያለ ይቀርባል.. .
...........................፥ ቸልታቸው አለ ።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።
ለቅፅበት ህላዌ ፥ ተግተው 'ሚባትሉ
በህብር ታጅበው ፥ ጭረው የሚውሉ
ዶሮዎች!
ለቅመው አዳሪዎች...
ከእጀባው ወጥታ.. .. ከመንጋው ተጠቅታ
በታደነች ጫጩት.. .
ሀዘን ተሸብረው ፥ ለስጋት ተድረው ፥ ጮኸው ይንጫጫሉ
ከአፍታ በኋላ.. .
ዳግም ፍርሀት ሽረው ፥ በኗሪነት ተስፋ ፥ ጥሬ ይለቅማሉ ።
#እነዛ ዶሮዎች.. .
አንድም በፍርሀት
አንድም በቸልታ
አንድ ጊዜ በጩኸት
አንዴ በፀጥታ...
ጥሬ ሲናጠቁ ፥ መሬት እየጫሩ
ከቁጥር ተናንሰው ...
ከመንጋነት ጎድለው ፥ ምንም ሆነው ቀሩ።
#አሁን በዛ መሬት!
ለቅፅበት ህላዌ ፥ ተግተው 'ሚባትሉ
በህብር ታጅበው ፥ ጭረው የሚውሉ
አዳዲስ ዶሮዎች.. .
ጭሮ አዳሪዎች.. .
አንድም በፍርሀት
አንድም በቸልታ
አንድ ጊዜ በጩኸት
አንዴ በፀጥታ...
ኗሪ ነን እያሉ ... ጥሬ ይለቅማሉ ።
#እኔ
#ድመት ይታየኛል!
እንደ ሙት መልዓክ ፥ ጥፍሮቹን ያሾለ
ነፍስን ጌጥ አድርጎ ፥ አይኖቹን የኳለ
ጨለማውን ህልፈት ፥ ጀርባው ላይ ያዘለ
ቀስ እያለ ይቀርባል.. .
...........................፥ ቸልታቸው አለ ።
@getem
@getem
@getem
ጊዜ ልጠይቅህ
°°°
ጉልበት ክንፍህ አይዝል የማትደክም በራር
ቅንጣት ድጭ አይልብህ ህይወት ስትሸበር።
በዘይቤ ፈሊጥ ሰው ሁን ልጠይቅህ
ሳታስጠብቅ መልስ በየትም ስላለህ
ለሰቆቃ ረዝመህ፣ ለሀሴት ማጠርህ
ለኛ የማይገባን ምንድነው ምሥጥርህ?
ጭንቀት ለጠናበት፣ ሀዘን ላናወዘው
ለምን ይሆን ቀኑ ካመት የሚረዝመው?
በመፈንጠዝ ሰዓት፣ በሀሴት በፍቅር
ለምን ይሆን ቀኑ ከደቂቃ የሚያጥር?
ራስገዝ ነህና አስኳለ ኅላዌ ማዕከለ ሁሉ
የግዑዝ የህይወት የዳር የማህሉ
ንገረን ምሥጢሩን፣ የሁለንታ ጥጉን
የማይሆን በማሰስ በከንቱ እንዳንባክን
ጊዜ ሆይ እባክህ ወዲ በል መልስህን።
°°°
ከዘርዓሰብ ሣጌጥ
፲፩-፩-፪፳፲፪ ዓ.ም
@getem
@getem
@getem
°°°
ጉልበት ክንፍህ አይዝል የማትደክም በራር
ቅንጣት ድጭ አይልብህ ህይወት ስትሸበር።
በዘይቤ ፈሊጥ ሰው ሁን ልጠይቅህ
ሳታስጠብቅ መልስ በየትም ስላለህ
ለሰቆቃ ረዝመህ፣ ለሀሴት ማጠርህ
ለኛ የማይገባን ምንድነው ምሥጥርህ?
ጭንቀት ለጠናበት፣ ሀዘን ላናወዘው
ለምን ይሆን ቀኑ ካመት የሚረዝመው?
በመፈንጠዝ ሰዓት፣ በሀሴት በፍቅር
ለምን ይሆን ቀኑ ከደቂቃ የሚያጥር?
ራስገዝ ነህና አስኳለ ኅላዌ ማዕከለ ሁሉ
የግዑዝ የህይወት የዳር የማህሉ
ንገረን ምሥጢሩን፣ የሁለንታ ጥጉን
የማይሆን በማሰስ በከንቱ እንዳንባክን
ጊዜ ሆይ እባክህ ወዲ በል መልስህን።
°°°
ከዘርዓሰብ ሣጌጥ
፲፩-፩-፪፳፲፪ ዓ.ም
@getem
@getem
@getem
👍1
ኢትዮጵያ
(ደሱ ፍቅርኤል)
ያገራችን ስሪት
ሁለት መልክ አለው ወተትና ቡና
ግማሽ ክርስትና ፥ ግማሽ እስልምና
ኢትዮጵያዊነት - ማንኪያ የምንለው
የሚጣፍጥ ፍቅር - ስኳር የምንለው
ሁሉን አቀፍ ሀገር - ስኒ የምንለው
ቡናውን ከወተት
አማስለው ቀየጡት
እናም
ቡና መሆን ቀርቶ ጥቁርነት ጠፍቶ
ወተት መሆን ቀርቶ ነጭነት ተረስቶ
ባለ ቡላ ቀለም ሆነዋል ማኪያቶ
ታድያ.............
ማንም እጁን ሰዶ ውህዱን ሊደፋ ስኒ ሲያዘነብል
ያየኸው እንደሆን - ይህን ቃል ልብ በል
የሆነውን ሁሉ ለልጅህ ስትነግር
ማኪያቶውን እንጅ ቡናውን ደፋ አትበል
ወተቱን ደፋ አትበል
@getem
@getem
@getem
(ደሱ ፍቅርኤል)
ያገራችን ስሪት
ሁለት መልክ አለው ወተትና ቡና
ግማሽ ክርስትና ፥ ግማሽ እስልምና
ኢትዮጵያዊነት - ማንኪያ የምንለው
የሚጣፍጥ ፍቅር - ስኳር የምንለው
ሁሉን አቀፍ ሀገር - ስኒ የምንለው
ቡናውን ከወተት
አማስለው ቀየጡት
እናም
ቡና መሆን ቀርቶ ጥቁርነት ጠፍቶ
ወተት መሆን ቀርቶ ነጭነት ተረስቶ
ባለ ቡላ ቀለም ሆነዋል ማኪያቶ
ታድያ.............
ማንም እጁን ሰዶ ውህዱን ሊደፋ ስኒ ሲያዘነብል
ያየኸው እንደሆን - ይህን ቃል ልብ በል
የሆነውን ሁሉ ለልጅህ ስትነግር
ማኪያቶውን እንጅ ቡናውን ደፋ አትበል
ወተቱን ደፋ አትበል
@getem
@getem
@getem
👍2