ራያ ነኝ ወራባየ፤
የአናዎቹ ልጅ የነ ሸህየ፤
አይነግረኝም ወይ፤
በዋጃ ግድም ያነን ልጅ ያየ።
እርጎየ ሙሄ፤ የራያይቱ፤
ቆቦ አላማጣ፤
መውደድ ገደለኝ እኔ ልጅቱ።
ቀልቤ ሲሳከር ግራ ገብቷቸው፤
አረዳው ሁሉ ዱኣ ገብተዋል አላህ ይርዳቸው፤
ላዩን መሆኒ ታቹን በዋጃ፤
ይኸው እግር በእግር፤
ያመላልሰኛል የነካኝን እንጃ።
ትፍትፌ ማይ ማይ ጉፍታየ ሸጋ፤
ይኸው ይዣለሁ ፤
በየመንገዱ ያንን ገምሻራ እሱን ፍለጋ።
መገን መውደድ!!""
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
የአናዎቹ ልጅ የነ ሸህየ፤
አይነግረኝም ወይ፤
በዋጃ ግድም ያነን ልጅ ያየ።
እርጎየ ሙሄ፤ የራያይቱ፤
ቆቦ አላማጣ፤
መውደድ ገደለኝ እኔ ልጅቱ።
ቀልቤ ሲሳከር ግራ ገብቷቸው፤
አረዳው ሁሉ ዱኣ ገብተዋል አላህ ይርዳቸው፤
ላዩን መሆኒ ታቹን በዋጃ፤
ይኸው እግር በእግር፤
ያመላልሰኛል የነካኝን እንጃ።
ትፍትፌ ማይ ማይ ጉፍታየ ሸጋ፤
ይኸው ይዣለሁ ፤
በየመንገዱ ያንን ገምሻራ እሱን ፍለጋ።
መገን መውደድ!!""
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
👍1
ለውብ ቀን!
💚
የሚያተኩሱ ግጥሞች!
Written by ደረጀ በላይነህ
ግጥም በስሜት እየናጠ፣ ሀሳብ ሰብስቦ፣ በዜማ ጥፍጥና ወደ ጆሮና ነፍስ
የሚደርስ ጥበብ ነው:: ይሁን እንጂ ስሜት ብቻውን ግጥም አይሆንም፡፡ ኢ.
ኤ. ግሪኒንግ ላምቦርን የሚሉትም እንደዚያ ነው፡፡ እኔም በዚያ እስማማለሁ፡፡
ማዕበል ያናወጠው ባህር ሁሉ አሳ ይዞ ብቅ አይልምና።
ሀሳብ በስሜት ውስጥ ሊሳሳና ሊደድር እንደሚችል ግን መናገር ይቻላል።
አንዳንዴ በሰከነ ስሜት ከፍ ያለ አተያይ፣ የረቀቀ ስልት፣ የሚኮረኩር ቋንቋ፣
የጠነነ ምናብ ሊነጠብ ይችላል፤ አንዳንዴ ደግሞ ተቃራኒው፡፡
የዘላለም ገበየሁ ‹‹በገሃነም ሥር መፅደቅ›› የሚለውን የግጥም መጽሐፍ
ሳነበው፤ የስሜት ሃያልነት የከባቢ ጠረን፣ የዘመን ሀሳቦች ጠረን
አይቼበታለሁ፡፡ ከዚህ ቀደም ‹‹ዳሞትራ›› የሚል የግጥም መጽሐፍ
ያሳተመው ይህ ወጣት ገጣሚ፤ ጥሩ ጥሩ ሀሳቦች መንቀስ፣ ዜማው ባልተናጋ
ስልትና በልከኛ/አጫጭር አርኬዎች ማስቀመጥ እንደሚችል ታዝቤአለሁ፡፡
በሚያዝናና ስሜት፣ የቆረፈዱ ሀሳቦችንና ምሬቶችን ለአንባቢ በማድረሱ
ተደስቼ ነበር፡፡ ብዙ የግጥም ሊቃውንት እንደሚስማሙበት፤ የግጥም ግቡ
መፈላሰፍ ወይም መስበክ ሳይሆን ነፍስን ወደ ፈንጠዝያ ማሳፈር ነውና
‹‹ዳሞትራ›› እንዲያ ነበር፡፡
አዲሱ መጽሐፉ ግን እንደ ‹‹ዳሞትራ›› አይደለም፤ አንዳንዴ በቁጣና ምሬት
ትካዜው አፍጥጦ ይታያል:: አጥንቱ ላይ ያለበሰው ሥጋ የአደይ አበባ ያህል
ቀለሙ አልደመቀም፣ የህጻን ልብ ያህል ጣፋጭ ሳቅ አልሳቀም፡፡ ግን ደግሞ
ለዛ ቢስና አስቀያሚ አይደለም፤ ኮርካሪ ስሜቶች ያንጠለጠሉት ወዛም ጥበብ
አለው፡፡ እስቲ የተወሰኑትን እንይ፡-
‹‹አማራነት ዛሬ››
የሚዘርፉት አልማዝ የሚያፈርሱት አድባር
የሚሸጡት ርስት የሚያደርቁት ባህር፡፡
*
ጠባቂ ያጣ ዛፍ የሚቆርጡት ዋርካ
የሚያረግፉት ቅጠል የሚያሄዱት ጫካ፡፡
*
በገነባት አገር ጧት ማታ ’ሚገደል
የተረሳ ታሪክ የተናቀ ገድል፡፡
(አማራነት ዛሬ)
ገጣሚው ሀዘን ውስጥ ነው፡፡ ‹‹አማራ››ን በለዋጭ ዘይቤ ውስጥ እየሳለ፣
ብሶቱን ቁጭቱንና ክሱን በስንኝ ዜማ ይዘምራል፡፡ ወይም ግራና ቀኙን
ይወቅሳል፡፡ ይህ የገጣሚው የራሱ ሀቅ፣ የግሉ ሚዛን ነው። ምናልባትም
ገጠመኞች ሊጠቅስ፣ ታሪክ ከወደ ኋላ ሊተነትን ይችላል፡፡ ብቻ ሀሳቡን
እየተነፈሰ ነው:: የጋለ ልቡን ወላፈን በስንኝ ቋጥሮ ለአንባቢው በዜማና
በውበት ማዕድ እየፈተፈተ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ከቅርብ ጊዜው የፖለቲካ አየር፣
የአገሪቱ የለውጥ ማዕበልና የብሔር ግጭቶች ቀለም የሰጠው ሀሳብ ነው፡፡
ግጥም እንዲህ ነው፤ ከስሜት ይነሳና በስሜት ንፋስ ውስጥ የጊዜውን
ቀለም ያሳያል፤ የትርታውን ከበሮ ይደልቃል፡፡ የዘላለም ግጥሞች ባብዛኛው
የፖለቲካ ደጅ የሚያንኳኩ፣ ብሶት የሞላባቸው ናቸው፡፡ ቢሆንም ማስጠሎና
ምንቅርቅር አይደሉም:: አስተዋይ ሀሳቦችም አሉት፡፡
‹‹ሀገሬ መልሽ?!››
ጥቁር አፈር ይዘሽ ሳይቸግር ማዕድኑ
ልጅሽ ለምን ከሳ? ለምንስ ሳሳ ጎኑ?
ድህነት ’ሚባል ትልቅ ባላጋራ
ምነው አብሮ ኖረ ከልጆችሽ ጋራ
በአጉል ወሬ ናዳ በጭምብል ተጋርደን
በጥላቻ ናውዘን ፍቅር ገድለን ሄደን
ምንድነው ትርፋችን
በባዶ ቤታችን??
በማለት… ለምን ባዶ ሆንን እያለ ነው፡፡ የዳዊት ልጅ አምኖንን አፍቅሮ
በየዕለቱ ሲከሳ ‹‹የንጉሥ ልጅ ሆይ ለምን ከሳህ?›› እንዳለው የመጽሐፍ
ቅዱስ ታሪክ፤ ምንም ሳናጣ ለምን ከሳን? ለምን ሳሳን? ድህነት ለምን
በቆርፋዳ እጆቹ አቅፎ ያንገላታናል?... ለምን በገጠጠ ጥርሱ ይነጨናል?...
እያለ አገሩን ይጠይቃታል። በወሬ ናዳ እየፈረሰች፣ በፍቅር ረሀብ የምንሳቀቀው
ልጆችዋ፤ የጥፋቱ ሁሉ መነሾ ራሳችን ነን፤ የምናገኘው ትርፍ ግን ምንድነው?
የሚል አንደምታ አለው፡፡ ከሁሉ ከሁሉ ቤታችን ባዶ ነው፤ በባዶ ቤት ምን
ያናጨናል? በሚል ቁጭት ከንፈሩን የሚነክስ ይመስላል፡፡ ግጥሙ ሊሪክ
ስለሆነ ስሜቱ ላቅ ያለ፣ ቁጭቱ የመረረ ነው፡።
‹‹ሞት ወይም ሕይወት››
ህዝቤ ሲያሳድዱት ለምን ይሰደዳል
ንብረትና አድባሩን ለምን ጥሎ ይሄዳል?
ንገሩት ወገኔን
እንደያዙት አሳ ባህር እንደከበደው
በሞቱ ብቻ ነው የሚድን ከፍዳው፡፡
ይህም ግጥም ባሳለፍነው አንድ አመት ውስጥ ያለውን አታካች ስደትና
መፈናቀል የሚያሳይ ነው፡፡ ‹‹ከዚህ ኑሮ ሞት ይሻላል!›› የሚል ይመስላል፡፡
ሰው የኖረባትን ቀዬ፣ ንብረቱንና ደብሩን ለቅቆ ከሚሄድ፤ ከዚህ ፍዳ ይልቅ
ሞት መቅመስ ከሰቀቀን መዳን ነው አይነት ነው፡፡ ግጥሙ አሁንም በሬት
የተነከረ፣ እንባ ያነቀው ነው፡፡ ግን ደግሞ የምንኖርበት በአይናችን ያየነው፣
በጆሯችን የሰማነው ሀቅ ነው። አንድ የስነ ግጥም ፕሮፌሰር፤ ‹‹ምሬትን
ሀዘንንና ልቅሶን ወደ ዘና አርጌ ለውጦ ሞቱን በተስፋ ቀለም ለብጦ ማቅረብ
የጥሩ ገጣሚ ሚና ነው›› ይላሉ፡፡ ቀጥታ እየጎፈነነ እየቧጠጠ ባይሆን
ይመረጣል፡። ዘላለም፤ እንደ ‹‹ዳሞትራው›› ዘመን ሁን ባይባልም፣ የተስፋ
ጥርሶቻችንን፣ የፈገግታችንንና የነገአችንን ቀለም፣ ፅልመት ጥርስ ላይ
አትሰካቸው መባል አለበት፡፡
የደረቁ የሀሳብ ገፆችን በሌላ የሕይወት መልክ የገለጠበት በቀጣዩ ግጥም
አይነት ለዛ ጠምቋቸዋል:: (ግን ጥቂት ሆኑ)
ከከንፈሮችሽ ዳር እድሜ ይወለዳል
ከእቅፍሽ ሲያነጉ መሞት ይሰደዳል
በጭኖችሽ መሀል ገነት ተገንብቷል
የፀደቀው ብቻ የኔ ገላ ላልቷል
ሀጣን ተዳፍረውሽ ሰብረው እንዳይገቡ የገነትሽን በር
የኔ ውድ ቅጠሪኝ ስጠብቅሸ ውዬ ስጠብቅሽ ልደር፡፡
ይህ የፍቅር ፍካሬ፣ የፍቅር አለም ውበት ነው:: የአለምን ኮተት አስጥሎ
በገነት ወንዞች ዋና የሚያስተምር ሊቅ! ሞትን እየገረፈ የሚያባርር የሕይወት
ንጉስ! ሀጢአን የማይደፍሩት፣ በቅድስና የተጠበቀ የድድቅ ቅጥር!
ከከንፈሮችዋ ማህጸን ውስጥ እድሜ የሚያረዝም መድሃኒት የሀሴት ነበልባል
ብቅ ይላል፡፡ አለም መአዛዋን ትቀይራለች፡፡ ታዲያ ይህቺ የሕይወት ቅመም
እድል ትስጠኝና ቀጠሮ ብታረፍድ እንኳ ሳልመረር ልጠብቃት፤ አንድ ቀን
አይደለም፤ ደግሜ ደጋግሜ ሌትና ቀን ልጠብቃት ይላል፡፡ ይህ የሕይወት
ሌላኛው የውበትና የተስፋ ክንፍ ነው፡፡ በዚህ መብረር እድሜ ያረዝማል!...
‹‹ሀገሬ አርጅታለች››
ሀገሬ አርጅታለች ጃርቶች በቀሉባት
እሾህ እያፀደቁ ወይን ነቀሉባት
ሀገሬ አርጅታለች
ከመታመን ክፍሏ
ከፍቅር ወለሏ
ጥላቻ ከተተ
እምነትና አንድነት በምድሯ ከሰሙ
ሰው መሆን ሻገተ፡፡
ወይን ተነቅሎ እሾህ ሲተከል መኖሩ ሀቅ ነው። ጃርቶች በቅለው ቀስት
ማስወንጨፋችንን ባለፉት አመታት አይተናል፡፡ ዛሬም እሳቱ እየላሰን፣ ክፋቱ
እያፈረሰን ነው፡፡ መታመን ጠፍቶ የጎሪጥ መተያየት ውስጥ ነን፡፡ አይናችንን
ጨፍነን ካልካድን በቀር ጥላቻ አንቆ ይዞናል፡። ታንኳችን በማዕበል
እየተናጠች ነው፡፡ እምነትና አንድነት ከስሞ፣ መለያየትና መናቆር ሰማይ ጥግ
ደርሷል፡፡ ይሁንና ሌላም ተስፋ አለ - እሸት ያንጠለጠሉ፣ ብሩህ ቀን ያረገዙ
ዜጎችም አሉን፡፡ ነፍሳቸውን ስለ ጎዶላችን ቤዛ ለማድረግ የተዘጋጁ ሕሩያን
አልታጡም፡፡ በረሀብ እያዛጋን በጥላቻ እየነፈርን እንዳንኖር፣ የታሪካችን
ምዕራፍ በሀዘን እንዳይዘጋ፤ አደባባያችን ላይ አበባ የሚነሰንሱ ከታሪክ ገጽ
አልተፋቁም፡፡
‹‹ንጉሳችንና ያንቺ መዘናጋት›› የሚለው ግጥሙም ይህንኑ የሀገር ነገር
ያዜማል፡፡
እንኳንስ አንድ ሰው
እንባሽን ሊያብሰው
መቶ ሚሊየን ሕዝብ ሊያድንሽ ቢተጋ
ሕመሙ ጽኑ ነው የቆሰለ ጉበት በጦር የተወጋ
እናልሽ እናቴ…
ጋብቻ ማፍረስ ነው የመዳንሽ ውሉ
አንቺን በልቶ መግደል
አንቺን መጥባት ብቻ
ችጋራም ማድረግ ነው የባልሽ
💚
የሚያተኩሱ ግጥሞች!
Written by ደረጀ በላይነህ
ግጥም በስሜት እየናጠ፣ ሀሳብ ሰብስቦ፣ በዜማ ጥፍጥና ወደ ጆሮና ነፍስ
የሚደርስ ጥበብ ነው:: ይሁን እንጂ ስሜት ብቻውን ግጥም አይሆንም፡፡ ኢ.
ኤ. ግሪኒንግ ላምቦርን የሚሉትም እንደዚያ ነው፡፡ እኔም በዚያ እስማማለሁ፡፡
ማዕበል ያናወጠው ባህር ሁሉ አሳ ይዞ ብቅ አይልምና።
ሀሳብ በስሜት ውስጥ ሊሳሳና ሊደድር እንደሚችል ግን መናገር ይቻላል።
አንዳንዴ በሰከነ ስሜት ከፍ ያለ አተያይ፣ የረቀቀ ስልት፣ የሚኮረኩር ቋንቋ፣
የጠነነ ምናብ ሊነጠብ ይችላል፤ አንዳንዴ ደግሞ ተቃራኒው፡፡
የዘላለም ገበየሁ ‹‹በገሃነም ሥር መፅደቅ›› የሚለውን የግጥም መጽሐፍ
ሳነበው፤ የስሜት ሃያልነት የከባቢ ጠረን፣ የዘመን ሀሳቦች ጠረን
አይቼበታለሁ፡፡ ከዚህ ቀደም ‹‹ዳሞትራ›› የሚል የግጥም መጽሐፍ
ያሳተመው ይህ ወጣት ገጣሚ፤ ጥሩ ጥሩ ሀሳቦች መንቀስ፣ ዜማው ባልተናጋ
ስልትና በልከኛ/አጫጭር አርኬዎች ማስቀመጥ እንደሚችል ታዝቤአለሁ፡፡
በሚያዝናና ስሜት፣ የቆረፈዱ ሀሳቦችንና ምሬቶችን ለአንባቢ በማድረሱ
ተደስቼ ነበር፡፡ ብዙ የግጥም ሊቃውንት እንደሚስማሙበት፤ የግጥም ግቡ
መፈላሰፍ ወይም መስበክ ሳይሆን ነፍስን ወደ ፈንጠዝያ ማሳፈር ነውና
‹‹ዳሞትራ›› እንዲያ ነበር፡፡
አዲሱ መጽሐፉ ግን እንደ ‹‹ዳሞትራ›› አይደለም፤ አንዳንዴ በቁጣና ምሬት
ትካዜው አፍጥጦ ይታያል:: አጥንቱ ላይ ያለበሰው ሥጋ የአደይ አበባ ያህል
ቀለሙ አልደመቀም፣ የህጻን ልብ ያህል ጣፋጭ ሳቅ አልሳቀም፡፡ ግን ደግሞ
ለዛ ቢስና አስቀያሚ አይደለም፤ ኮርካሪ ስሜቶች ያንጠለጠሉት ወዛም ጥበብ
አለው፡፡ እስቲ የተወሰኑትን እንይ፡-
‹‹አማራነት ዛሬ››
የሚዘርፉት አልማዝ የሚያፈርሱት አድባር
የሚሸጡት ርስት የሚያደርቁት ባህር፡፡
*
ጠባቂ ያጣ ዛፍ የሚቆርጡት ዋርካ
የሚያረግፉት ቅጠል የሚያሄዱት ጫካ፡፡
*
በገነባት አገር ጧት ማታ ’ሚገደል
የተረሳ ታሪክ የተናቀ ገድል፡፡
(አማራነት ዛሬ)
ገጣሚው ሀዘን ውስጥ ነው፡፡ ‹‹አማራ››ን በለዋጭ ዘይቤ ውስጥ እየሳለ፣
ብሶቱን ቁጭቱንና ክሱን በስንኝ ዜማ ይዘምራል፡፡ ወይም ግራና ቀኙን
ይወቅሳል፡፡ ይህ የገጣሚው የራሱ ሀቅ፣ የግሉ ሚዛን ነው። ምናልባትም
ገጠመኞች ሊጠቅስ፣ ታሪክ ከወደ ኋላ ሊተነትን ይችላል፡፡ ብቻ ሀሳቡን
እየተነፈሰ ነው:: የጋለ ልቡን ወላፈን በስንኝ ቋጥሮ ለአንባቢው በዜማና
በውበት ማዕድ እየፈተፈተ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ከቅርብ ጊዜው የፖለቲካ አየር፣
የአገሪቱ የለውጥ ማዕበልና የብሔር ግጭቶች ቀለም የሰጠው ሀሳብ ነው፡፡
ግጥም እንዲህ ነው፤ ከስሜት ይነሳና በስሜት ንፋስ ውስጥ የጊዜውን
ቀለም ያሳያል፤ የትርታውን ከበሮ ይደልቃል፡፡ የዘላለም ግጥሞች ባብዛኛው
የፖለቲካ ደጅ የሚያንኳኩ፣ ብሶት የሞላባቸው ናቸው፡፡ ቢሆንም ማስጠሎና
ምንቅርቅር አይደሉም:: አስተዋይ ሀሳቦችም አሉት፡፡
‹‹ሀገሬ መልሽ?!››
ጥቁር አፈር ይዘሽ ሳይቸግር ማዕድኑ
ልጅሽ ለምን ከሳ? ለምንስ ሳሳ ጎኑ?
ድህነት ’ሚባል ትልቅ ባላጋራ
ምነው አብሮ ኖረ ከልጆችሽ ጋራ
በአጉል ወሬ ናዳ በጭምብል ተጋርደን
በጥላቻ ናውዘን ፍቅር ገድለን ሄደን
ምንድነው ትርፋችን
በባዶ ቤታችን??
በማለት… ለምን ባዶ ሆንን እያለ ነው፡፡ የዳዊት ልጅ አምኖንን አፍቅሮ
በየዕለቱ ሲከሳ ‹‹የንጉሥ ልጅ ሆይ ለምን ከሳህ?›› እንዳለው የመጽሐፍ
ቅዱስ ታሪክ፤ ምንም ሳናጣ ለምን ከሳን? ለምን ሳሳን? ድህነት ለምን
በቆርፋዳ እጆቹ አቅፎ ያንገላታናል?... ለምን በገጠጠ ጥርሱ ይነጨናል?...
እያለ አገሩን ይጠይቃታል። በወሬ ናዳ እየፈረሰች፣ በፍቅር ረሀብ የምንሳቀቀው
ልጆችዋ፤ የጥፋቱ ሁሉ መነሾ ራሳችን ነን፤ የምናገኘው ትርፍ ግን ምንድነው?
የሚል አንደምታ አለው፡፡ ከሁሉ ከሁሉ ቤታችን ባዶ ነው፤ በባዶ ቤት ምን
ያናጨናል? በሚል ቁጭት ከንፈሩን የሚነክስ ይመስላል፡፡ ግጥሙ ሊሪክ
ስለሆነ ስሜቱ ላቅ ያለ፣ ቁጭቱ የመረረ ነው፡።
‹‹ሞት ወይም ሕይወት››
ህዝቤ ሲያሳድዱት ለምን ይሰደዳል
ንብረትና አድባሩን ለምን ጥሎ ይሄዳል?
ንገሩት ወገኔን
እንደያዙት አሳ ባህር እንደከበደው
በሞቱ ብቻ ነው የሚድን ከፍዳው፡፡
ይህም ግጥም ባሳለፍነው አንድ አመት ውስጥ ያለውን አታካች ስደትና
መፈናቀል የሚያሳይ ነው፡፡ ‹‹ከዚህ ኑሮ ሞት ይሻላል!›› የሚል ይመስላል፡፡
ሰው የኖረባትን ቀዬ፣ ንብረቱንና ደብሩን ለቅቆ ከሚሄድ፤ ከዚህ ፍዳ ይልቅ
ሞት መቅመስ ከሰቀቀን መዳን ነው አይነት ነው፡፡ ግጥሙ አሁንም በሬት
የተነከረ፣ እንባ ያነቀው ነው፡፡ ግን ደግሞ የምንኖርበት በአይናችን ያየነው፣
በጆሯችን የሰማነው ሀቅ ነው። አንድ የስነ ግጥም ፕሮፌሰር፤ ‹‹ምሬትን
ሀዘንንና ልቅሶን ወደ ዘና አርጌ ለውጦ ሞቱን በተስፋ ቀለም ለብጦ ማቅረብ
የጥሩ ገጣሚ ሚና ነው›› ይላሉ፡፡ ቀጥታ እየጎፈነነ እየቧጠጠ ባይሆን
ይመረጣል፡። ዘላለም፤ እንደ ‹‹ዳሞትራው›› ዘመን ሁን ባይባልም፣ የተስፋ
ጥርሶቻችንን፣ የፈገግታችንንና የነገአችንን ቀለም፣ ፅልመት ጥርስ ላይ
አትሰካቸው መባል አለበት፡፡
የደረቁ የሀሳብ ገፆችን በሌላ የሕይወት መልክ የገለጠበት በቀጣዩ ግጥም
አይነት ለዛ ጠምቋቸዋል:: (ግን ጥቂት ሆኑ)
ከከንፈሮችሽ ዳር እድሜ ይወለዳል
ከእቅፍሽ ሲያነጉ መሞት ይሰደዳል
በጭኖችሽ መሀል ገነት ተገንብቷል
የፀደቀው ብቻ የኔ ገላ ላልቷል
ሀጣን ተዳፍረውሽ ሰብረው እንዳይገቡ የገነትሽን በር
የኔ ውድ ቅጠሪኝ ስጠብቅሸ ውዬ ስጠብቅሽ ልደር፡፡
ይህ የፍቅር ፍካሬ፣ የፍቅር አለም ውበት ነው:: የአለምን ኮተት አስጥሎ
በገነት ወንዞች ዋና የሚያስተምር ሊቅ! ሞትን እየገረፈ የሚያባርር የሕይወት
ንጉስ! ሀጢአን የማይደፍሩት፣ በቅድስና የተጠበቀ የድድቅ ቅጥር!
ከከንፈሮችዋ ማህጸን ውስጥ እድሜ የሚያረዝም መድሃኒት የሀሴት ነበልባል
ብቅ ይላል፡፡ አለም መአዛዋን ትቀይራለች፡፡ ታዲያ ይህቺ የሕይወት ቅመም
እድል ትስጠኝና ቀጠሮ ብታረፍድ እንኳ ሳልመረር ልጠብቃት፤ አንድ ቀን
አይደለም፤ ደግሜ ደጋግሜ ሌትና ቀን ልጠብቃት ይላል፡፡ ይህ የሕይወት
ሌላኛው የውበትና የተስፋ ክንፍ ነው፡፡ በዚህ መብረር እድሜ ያረዝማል!...
‹‹ሀገሬ አርጅታለች››
ሀገሬ አርጅታለች ጃርቶች በቀሉባት
እሾህ እያፀደቁ ወይን ነቀሉባት
ሀገሬ አርጅታለች
ከመታመን ክፍሏ
ከፍቅር ወለሏ
ጥላቻ ከተተ
እምነትና አንድነት በምድሯ ከሰሙ
ሰው መሆን ሻገተ፡፡
ወይን ተነቅሎ እሾህ ሲተከል መኖሩ ሀቅ ነው። ጃርቶች በቅለው ቀስት
ማስወንጨፋችንን ባለፉት አመታት አይተናል፡፡ ዛሬም እሳቱ እየላሰን፣ ክፋቱ
እያፈረሰን ነው፡፡ መታመን ጠፍቶ የጎሪጥ መተያየት ውስጥ ነን፡፡ አይናችንን
ጨፍነን ካልካድን በቀር ጥላቻ አንቆ ይዞናል፡። ታንኳችን በማዕበል
እየተናጠች ነው፡፡ እምነትና አንድነት ከስሞ፣ መለያየትና መናቆር ሰማይ ጥግ
ደርሷል፡፡ ይሁንና ሌላም ተስፋ አለ - እሸት ያንጠለጠሉ፣ ብሩህ ቀን ያረገዙ
ዜጎችም አሉን፡፡ ነፍሳቸውን ስለ ጎዶላችን ቤዛ ለማድረግ የተዘጋጁ ሕሩያን
አልታጡም፡፡ በረሀብ እያዛጋን በጥላቻ እየነፈርን እንዳንኖር፣ የታሪካችን
ምዕራፍ በሀዘን እንዳይዘጋ፤ አደባባያችን ላይ አበባ የሚነሰንሱ ከታሪክ ገጽ
አልተፋቁም፡፡
‹‹ንጉሳችንና ያንቺ መዘናጋት›› የሚለው ግጥሙም ይህንኑ የሀገር ነገር
ያዜማል፡፡
እንኳንስ አንድ ሰው
እንባሽን ሊያብሰው
መቶ ሚሊየን ሕዝብ ሊያድንሽ ቢተጋ
ሕመሙ ጽኑ ነው የቆሰለ ጉበት በጦር የተወጋ
እናልሽ እናቴ…
ጋብቻ ማፍረስ ነው የመዳንሽ ውሉ
አንቺን በልቶ መግደል
አንቺን መጥባት ብቻ
ችጋራም ማድረግ ነው የባልሽ
አመሉ፡፡
***
እንዲያው ቢሆን እንኳ…
ንጉሱን ብናምነው
የበዙ እባቦችን እንደምን አድርጎ አንድ ርግብ ይመራል
አንድ ሻማ ብቻ የጨለመ ሀገርን እንደምን ያበራል
ቤተ እምነቶች ዱዳ ሽማግሌው ዱጋ ጋዜጠኛው ዱዳ
እንዳልተወለደ እንዳልኖረ ሁሉ ሕዝብሽም እንግዳ፡፡
…ግጥሙ ይቀጥላል፡፡ የዚህ ግጥም ወቀሳ ብዙ እውነት አለው። ፍርሃትና
ጥርጣሬው፣ ነባራዊው እውነትም አሳማኝ ነው፡፡ በተለይ ሁለተኛው አንጓ ላይ
ያለው ሀሳብ በእምነት ተቋማቶቻችን፣ በጋዜጠኞቻችን… በአጠቃላይ
በሽንቁሮቻችን ላይ አተኩሯል፡፡
መጽሐፉ አሁን ባለንበት አገራዊ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ነው፡፡ መረር ያለና
የሚያሳዝንም ነው፡፡ አንዳንዱ ደግሞ ሚዛን የሳተ ይመስላል፡፡ ወደ አንድ ጥግ
የሄዱ ግጥሞች አሉ፡፡ ገጣሚ የአገር ወገን፣ የሕዝቦች ተገን መሆኑን ግን
መርሳት የለበትም፡፡ እንደ መጽሐፍ ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆን ጭብጦቹ ከአንድ
ድንኳን የተመዘዙ፣ ባለ ተመሳሳይ ጭብጥና ድምጽ መሆን የለባቸውም፡፡
ስሜት የጥበቡን ዋልታዎች እንዳይበትን መጠንቀቅና ምሰሶውን ሁለንታዊ
ማድረግ ያስፈልገዋል፡፡ በተረፈ ገጣሚው ክፍተቶቹን ሞልቶ፣ በግሩም
ሥራዎች እንደሚመለስ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
#ምንጭ አዲስ አድማስ ጋዜጣ
ውብ ቀን!💚
@getem
@getem
@balmbaras
***
እንዲያው ቢሆን እንኳ…
ንጉሱን ብናምነው
የበዙ እባቦችን እንደምን አድርጎ አንድ ርግብ ይመራል
አንድ ሻማ ብቻ የጨለመ ሀገርን እንደምን ያበራል
ቤተ እምነቶች ዱዳ ሽማግሌው ዱጋ ጋዜጠኛው ዱዳ
እንዳልተወለደ እንዳልኖረ ሁሉ ሕዝብሽም እንግዳ፡፡
…ግጥሙ ይቀጥላል፡፡ የዚህ ግጥም ወቀሳ ብዙ እውነት አለው። ፍርሃትና
ጥርጣሬው፣ ነባራዊው እውነትም አሳማኝ ነው፡፡ በተለይ ሁለተኛው አንጓ ላይ
ያለው ሀሳብ በእምነት ተቋማቶቻችን፣ በጋዜጠኞቻችን… በአጠቃላይ
በሽንቁሮቻችን ላይ አተኩሯል፡፡
መጽሐፉ አሁን ባለንበት አገራዊ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ነው፡፡ መረር ያለና
የሚያሳዝንም ነው፡፡ አንዳንዱ ደግሞ ሚዛን የሳተ ይመስላል፡፡ ወደ አንድ ጥግ
የሄዱ ግጥሞች አሉ፡፡ ገጣሚ የአገር ወገን፣ የሕዝቦች ተገን መሆኑን ግን
መርሳት የለበትም፡፡ እንደ መጽሐፍ ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆን ጭብጦቹ ከአንድ
ድንኳን የተመዘዙ፣ ባለ ተመሳሳይ ጭብጥና ድምጽ መሆን የለባቸውም፡፡
ስሜት የጥበቡን ዋልታዎች እንዳይበትን መጠንቀቅና ምሰሶውን ሁለንታዊ
ማድረግ ያስፈልገዋል፡፡ በተረፈ ገጣሚው ክፍተቶቹን ሞልቶ፣ በግሩም
ሥራዎች እንደሚመለስ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
#ምንጭ አዲስ አድማስ ጋዜጣ
ውብ ቀን!💚
@getem
@getem
@balmbaras
❤1
እንደ... እያልኩኝ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እንደ በርሃ ሰው ውሃ እንድተጠማ፤
እንደተራበ ጅብ ጩኸቱ ሚሰማ፤
ስራ እንደሚወደው ታታሪ ገበሬ፤
እኔ ያንች ወዳጅ ምወድሽ አምርሬ፤
እንኳን አሁንቀርቶ በይወት እያለው፤
ድምፅሽን ሰሰማ አይንሽን እያየው፤
ህይወቴን በሙሉ ዘመኔን ይቅርና፤
እኔ ያንች ወዳጅ ሙቼም ያውነኝና፤
እሁን እንዳለሁኝ ያሁኑን ልንገርሽ፤
ምላሴ እስኪዝል ፍቅሬን ላዚምልሽ፤
ምክንያቱም ከሞትኩኝ ምንም ባፈቅርሽም፤
እንችን መውደድ እንጂ መናገር እልችልም።
እናም ውዴ እኔ እንዳልኩሽ፤
ከዚ ቀደም እንዳወራሁልሽ፤
ወተት እንዳየ ህጻን እየሰሰትኩልሽ፤
አበባ እንዳየ ንብ ሁሌ እየጓጓሁሽ፤
ምድር አፏን ከፍታ እስክትውጠኝ ድርስ፤
ሰማይ አለት ሆኖ እላዬላይ ቢፈስ፤
እኔ ያንችወዳጅ ምንም የማይመስለኝ፤
የወዳጆችሽ ዋና አናቱ እኔነኝ።
የኔ ቆንጆ እውነት እልሻለው፤
እንደበቴ ደክሞ መግልጽ እስኪያቅተው፤
እስኪፈጠር ድረስ አዲስቃል ስላንቺ ቃላት ሁሉ አልቀው፤
ከምነግርሽ በላይ ከልብ ወድሻለው።
ናት ዘኢትዮጽያ
@getem
@getem
@getem
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እንደ በርሃ ሰው ውሃ እንድተጠማ፤
እንደተራበ ጅብ ጩኸቱ ሚሰማ፤
ስራ እንደሚወደው ታታሪ ገበሬ፤
እኔ ያንች ወዳጅ ምወድሽ አምርሬ፤
እንኳን አሁንቀርቶ በይወት እያለው፤
ድምፅሽን ሰሰማ አይንሽን እያየው፤
ህይወቴን በሙሉ ዘመኔን ይቅርና፤
እኔ ያንች ወዳጅ ሙቼም ያውነኝና፤
እሁን እንዳለሁኝ ያሁኑን ልንገርሽ፤
ምላሴ እስኪዝል ፍቅሬን ላዚምልሽ፤
ምክንያቱም ከሞትኩኝ ምንም ባፈቅርሽም፤
እንችን መውደድ እንጂ መናገር እልችልም።
እናም ውዴ እኔ እንዳልኩሽ፤
ከዚ ቀደም እንዳወራሁልሽ፤
ወተት እንዳየ ህጻን እየሰሰትኩልሽ፤
አበባ እንዳየ ንብ ሁሌ እየጓጓሁሽ፤
ምድር አፏን ከፍታ እስክትውጠኝ ድርስ፤
ሰማይ አለት ሆኖ እላዬላይ ቢፈስ፤
እኔ ያንችወዳጅ ምንም የማይመስለኝ፤
የወዳጆችሽ ዋና አናቱ እኔነኝ።
የኔ ቆንጆ እውነት እልሻለው፤
እንደበቴ ደክሞ መግልጽ እስኪያቅተው፤
እስኪፈጠር ድረስ አዲስቃል ስላንቺ ቃላት ሁሉ አልቀው፤
ከምነግርሽ በላይ ከልብ ወድሻለው።
ናት ዘኢትዮጽያ
@getem
@getem
@getem
❤2
Forwarded from Abel Almaz ቲዩብ
አቤል አልማዝ ትዝታ'ና ሙዚቃ:
ግጥምን በጃዝ ታዋቂ አርቲስቶች ይታደማሉ ትኬት ከvip ጀምሮ እኛ ዘንድ ይገኛለ @dipeluwa1122 ከ ሙሌ ጎን እንሁን ገቢው ለ ሙላለም ታከለ
ግጥምን በጃዝ ታዋቂ አርቲስቶች ይታደማሉ ትኬት ከvip ጀምሮ እኛ ዘንድ ይገኛለ @dipeluwa1122 ከ ሙሌ ጎን እንሁን ገቢው ለ ሙላለም ታከለ
‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የኪነ
ጥበብ ምሽት ሰኞ ይካሄዳል
የኢፌዲሪ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ከተስፋ ፊልም
ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በተፈጥሮ፣ በዘመንና የሰው ልጆች
ግንኙነትና መስተጋብር ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገው ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ››
የተሰኘ የኪነ-ጥበብ ምሽት የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በብሄራዊ
ቴአትር ይካሄዳል፡፡
በዝግጅቱ ላይ #ደራሲና ሀያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ ሥነ-ጽሑፍና ተፈጥሮ፣
#የሙዚቃ ባለሙያ ሰርፀ ፍሬ ስብሃት ሙዚቃና ተፈጥሮ፣# ሀኪም አበበች
ሽፈራው የባህል ሕክምናና እፅዋት፣ #ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ኢስላምና
ተፈጥሮ፣ #ፕ/ር ሽብሩ ተድላ ደግሞ በእንስሳት ዙሪያ፣ #ደራሲ አለማየሁ ዋሴ
(ዶ/ር) ቤተ ክርስቲያንና ተፈጥሮ፣ #ፕ/ር ታደሰ ደሴ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ
አለማት በእንስሳትና በእጽዋት አያያዝና ተሞክሯቸው ዙሪያ በሚል
ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን #ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም፣ #ደራሲና ጋዜጠኛ
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ #ፕ/ር ሰብስቤ ደምሴ፣ በተመሳሳይ ርዕስ ስራዎቻቸውን
ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
#ገጣሚ ረድኤት ተረፈና ገጣሚ #ተዋናይ ተፈሪ አለሙ ግጥሞቻቸውን የሚያነቡ
ሲሆን፣ ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የተሰኘ የ15 ደቂቃ አጭር ተውኔት
እንደሚቀርብም አዘጋጆቹ ገልጸዋል::
@getem
@balmbaras
ጥበብ ምሽት ሰኞ ይካሄዳል
የኢፌዲሪ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ከተስፋ ፊልም
ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በተፈጥሮ፣ በዘመንና የሰው ልጆች
ግንኙነትና መስተጋብር ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገው ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ››
የተሰኘ የኪነ-ጥበብ ምሽት የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በብሄራዊ
ቴአትር ይካሄዳል፡፡
በዝግጅቱ ላይ #ደራሲና ሀያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ ሥነ-ጽሑፍና ተፈጥሮ፣
#የሙዚቃ ባለሙያ ሰርፀ ፍሬ ስብሃት ሙዚቃና ተፈጥሮ፣# ሀኪም አበበች
ሽፈራው የባህል ሕክምናና እፅዋት፣ #ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ኢስላምና
ተፈጥሮ፣ #ፕ/ር ሽብሩ ተድላ ደግሞ በእንስሳት ዙሪያ፣ #ደራሲ አለማየሁ ዋሴ
(ዶ/ር) ቤተ ክርስቲያንና ተፈጥሮ፣ #ፕ/ር ታደሰ ደሴ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ
አለማት በእንስሳትና በእጽዋት አያያዝና ተሞክሯቸው ዙሪያ በሚል
ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን #ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም፣ #ደራሲና ጋዜጠኛ
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ #ፕ/ር ሰብስቤ ደምሴ፣ በተመሳሳይ ርዕስ ስራዎቻቸውን
ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
#ገጣሚ ረድኤት ተረፈና ገጣሚ #ተዋናይ ተፈሪ አለሙ ግጥሞቻቸውን የሚያነቡ
ሲሆን፣ ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የተሰኘ የ15 ደቂቃ አጭር ተውኔት
እንደሚቀርብም አዘጋጆቹ ገልጸዋል::
@getem
@balmbaras
... "እችለዋለሁኝ!"...
------------- (ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ)
...
... የሠፈር ሳተና ብላቴና ሳለን፤
... ያኔ በልጅነት በየዋሁ ዘመን
... ድብድብን እንጂ ጥላቻን መቼ አውቀን?
...
... "እችለዋለሁኝ" እየተባባልን፤
... ስንቱ ጋር ጀግነን እየተጋጠምን
... ኮሌታ ጨምድደን እየተናነቅን፥
... በማግስቱ በፍቅር እንዳልተቃቀፍን፥
... በቀጣዩ ቀን ግን...
... አባረን... አባረን... አባረን ካቃተን
ድንጋዩን ወርውረን - ከኋላ ፈንክተን - ደም እያፈሰስን፥
ቤትም ስንገባ... "ጠግበሐል" ተብለን - እየተገረፍን፤
...
... ደግሞ በማግስቱ ተፈንካችን አቅፈን...
... አብረን ባንድ ቡድን
... አኩኩሉ፣ አባሮሽ እየተጫወትን፤
...
... ደግሞ በሳምንቱ...
... ቦቸራ አለቃችን ኳስ ሜዳ ሰብስቦ...
... "ትችለዋለህ!?" ሲል - አንዱን ልጅ አስቁሞ፥
... "ባ'ናቱ ይዘቅዘቅ" እንዳላላን ከርሞ
... አጅሬ... ካቅማችን በላይ ሆኖ እየተገኘ፥
... በቴስታ ነርቶን ቢፈሰንም ነስር፥
... ባ'ናታችን ቆመን ብንወድቅም ከስር
... በንዴትና እልህ እያለቃቀስን
... "ሰኔ 30" እንገናኝ - ብለንም ብንቀጥር፥
... በንፁህ ልባችን መቼ ቂም ቀበርን?
...
... ብንችልም ባንችልም
... በፍቅር ውስጥ ነው .. የተደባደብን።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
..... (አንድ ሃገር - ገጽ 19)
@getem
@getem
@EliasGebru
------------- (ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ)
...
... የሠፈር ሳተና ብላቴና ሳለን፤
... ያኔ በልጅነት በየዋሁ ዘመን
... ድብድብን እንጂ ጥላቻን መቼ አውቀን?
...
... "እችለዋለሁኝ" እየተባባልን፤
... ስንቱ ጋር ጀግነን እየተጋጠምን
... ኮሌታ ጨምድደን እየተናነቅን፥
... በማግስቱ በፍቅር እንዳልተቃቀፍን፥
... በቀጣዩ ቀን ግን...
... አባረን... አባረን... አባረን ካቃተን
ድንጋዩን ወርውረን - ከኋላ ፈንክተን - ደም እያፈሰስን፥
ቤትም ስንገባ... "ጠግበሐል" ተብለን - እየተገረፍን፤
...
... ደግሞ በማግስቱ ተፈንካችን አቅፈን...
... አብረን ባንድ ቡድን
... አኩኩሉ፣ አባሮሽ እየተጫወትን፤
...
... ደግሞ በሳምንቱ...
... ቦቸራ አለቃችን ኳስ ሜዳ ሰብስቦ...
... "ትችለዋለህ!?" ሲል - አንዱን ልጅ አስቁሞ፥
... "ባ'ናቱ ይዘቅዘቅ" እንዳላላን ከርሞ
... አጅሬ... ካቅማችን በላይ ሆኖ እየተገኘ፥
... በቴስታ ነርቶን ቢፈሰንም ነስር፥
... ባ'ናታችን ቆመን ብንወድቅም ከስር
... በንዴትና እልህ እያለቃቀስን
... "ሰኔ 30" እንገናኝ - ብለንም ብንቀጥር፥
... በንፁህ ልባችን መቼ ቂም ቀበርን?
...
... ብንችልም ባንችልም
... በፍቅር ውስጥ ነው .. የተደባደብን።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
..... (አንድ ሃገር - ገጽ 19)
@getem
@getem
@EliasGebru
ቅኔ ናት ሀገሬ !
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።
ጠፍጥፎ የሰራት ፥ ያበጃት ይመስል
ይሄ የቀለም ቀንድ ፥ የህሊና ስንኩል
ትፈርሳለች ይላል ፦
ሟርቱን ከሀገሬ ደጅ ፥ በራፏ ላይ ሊጥል ።
ደግሞም ...
ወዲህ ለቅርሻቱ ፥ ሊጠቅስ ማስረጃ
ምሳሌ አስታኮ ፥ ሊያቆም የቃል ፍርጃ!
መጥሀፉን ሊያብል ፥ ቃልኪዳኗን ሽሮ
ዓይኑ ሩቅ ማትሮ ...
ሶሪያን ይጠራል ፥ ድንበሯን ተሻግሮ ።
# እኔ
የቃል ግንዝ አይጥ ፥ የጠቆረ ዶሮ
የሚከረፋ ደም ፥ የሟርት እንጉርጉሮ
ትፈርሳለች የሚል ፥ የምሁር ደንቆሮ
በሚዘራው ክፋት ፥ በሚያቆየው በደል
ልቤ ሳይሸነገል !
ፈገግ ብዬ አልፋለሁ ፥ ዥልነቱን ላቀል ።
አትፈርስም ሀገሬ !
የቃል ኪዳን ቅጥሬ.. .
ምን ዳሷ ቢያጋድል ፥ መሰረቷ ዘሞ
ምንም ታላቅ ባትሆን ፥ እንዲያ እንደቀድሞ
መቶ ቅጠል በጣሽ ፥ ሚልዩን ደፍተራ
እልፍ ባለ ጋኔን ፥ የእርኩሰት ደመራ
ልበትናት ብሎ.. .
በየ አዳራሹ ... ቢፎክር ቢያቅራራ
ማንነቷን ሊያሽር ...
ንጉስ ብረት ይዞ ፥ በሰይፍ ቢሸልል
ሀገሬ ቢላል ናት ...
በስጋዋ ቁስል ፥ እምነቷን የማጥል ።
አትፈርስም ኢትዮጵያ!
የአዳም መጀመሪያ.. .
ጠኔ ክንዱ ቢያይል ፥ ውሀ ጥም ቢያደብናት
የማጣት ቀንበሩ ፥ ወገቧን ቢያጎብጣት
የወደቀች ብትመስል ፥ ከሁሉ ተናንሳ
በርባን ከስር ወጥቶ ፥ ደንፍቶ ቢያገሳ
ዓለሙ ሊሳለቅ ፥ እንጨቱን አጣምሮ ፥ መስቀሉን ቢያነሳ
ሀገሬ መሲህ ናት ...
የክርስቶስ ሀምሳል ፥ ቀብረናታል ሲሉ ፥ ሞታ ምትነሳ ።
አትፈርስም!
አትፈርስም !
ኢትዮጵያ አትፈርስም...
ቢፈጡሩ ጥያቄ ፥ የሰይጣን ካህናት ፥ ሳንቲም እያነሱ
የዘረጉት ወጥመድ ...
የሚምሱት ጉድጓድ ፥ ሀገሬን ሳይጥላት ፥ ይተርፋል ለነሱ።
#አዎን ማህደር ናት !
ማንም እሳት ቢጭር ፥ ማገዶ ቢከምር ፥ ሊያከስላት አሳሮ
ሀገሬ ሚስጥር ናት !
የፈጣሪ ቅኔ ፥ የስንኞች ግማድ ፥ የፍቅር ቋጠሮ
አፍራሿ ይፈርሳል.. .
በለኮሰው እሳት ፥ በቁሙ እያለቀ ፥ አካሉ ቀንጭሮ ።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።
ጠፍጥፎ የሰራት ፥ ያበጃት ይመስል
ይሄ የቀለም ቀንድ ፥ የህሊና ስንኩል
ትፈርሳለች ይላል ፦
ሟርቱን ከሀገሬ ደጅ ፥ በራፏ ላይ ሊጥል ።
ደግሞም ...
ወዲህ ለቅርሻቱ ፥ ሊጠቅስ ማስረጃ
ምሳሌ አስታኮ ፥ ሊያቆም የቃል ፍርጃ!
መጥሀፉን ሊያብል ፥ ቃልኪዳኗን ሽሮ
ዓይኑ ሩቅ ማትሮ ...
ሶሪያን ይጠራል ፥ ድንበሯን ተሻግሮ ።
# እኔ
የቃል ግንዝ አይጥ ፥ የጠቆረ ዶሮ
የሚከረፋ ደም ፥ የሟርት እንጉርጉሮ
ትፈርሳለች የሚል ፥ የምሁር ደንቆሮ
በሚዘራው ክፋት ፥ በሚያቆየው በደል
ልቤ ሳይሸነገል !
ፈገግ ብዬ አልፋለሁ ፥ ዥልነቱን ላቀል ።
አትፈርስም ሀገሬ !
የቃል ኪዳን ቅጥሬ.. .
ምን ዳሷ ቢያጋድል ፥ መሰረቷ ዘሞ
ምንም ታላቅ ባትሆን ፥ እንዲያ እንደቀድሞ
መቶ ቅጠል በጣሽ ፥ ሚልዩን ደፍተራ
እልፍ ባለ ጋኔን ፥ የእርኩሰት ደመራ
ልበትናት ብሎ.. .
በየ አዳራሹ ... ቢፎክር ቢያቅራራ
ማንነቷን ሊያሽር ...
ንጉስ ብረት ይዞ ፥ በሰይፍ ቢሸልል
ሀገሬ ቢላል ናት ...
በስጋዋ ቁስል ፥ እምነቷን የማጥል ።
አትፈርስም ኢትዮጵያ!
የአዳም መጀመሪያ.. .
ጠኔ ክንዱ ቢያይል ፥ ውሀ ጥም ቢያደብናት
የማጣት ቀንበሩ ፥ ወገቧን ቢያጎብጣት
የወደቀች ብትመስል ፥ ከሁሉ ተናንሳ
በርባን ከስር ወጥቶ ፥ ደንፍቶ ቢያገሳ
ዓለሙ ሊሳለቅ ፥ እንጨቱን አጣምሮ ፥ መስቀሉን ቢያነሳ
ሀገሬ መሲህ ናት ...
የክርስቶስ ሀምሳል ፥ ቀብረናታል ሲሉ ፥ ሞታ ምትነሳ ።
አትፈርስም!
አትፈርስም !
ኢትዮጵያ አትፈርስም...
ቢፈጡሩ ጥያቄ ፥ የሰይጣን ካህናት ፥ ሳንቲም እያነሱ
የዘረጉት ወጥመድ ...
የሚምሱት ጉድጓድ ፥ ሀገሬን ሳይጥላት ፥ ይተርፋል ለነሱ።
#አዎን ማህደር ናት !
ማንም እሳት ቢጭር ፥ ማገዶ ቢከምር ፥ ሊያከስላት አሳሮ
ሀገሬ ሚስጥር ናት !
የፈጣሪ ቅኔ ፥ የስንኞች ግማድ ፥ የፍቅር ቋጠሮ
አፍራሿ ይፈርሳል.. .
በለኮሰው እሳት ፥ በቁሙ እያለቀ ፥ አካሉ ቀንጭሮ ።
@getem
@getem
@getem
👍1
የፀጋችን መንገድ
~
~
ፈገግ ስትይ . . .
ሀገር ነሽ!
የቡና ታርቲም ላይ ከተሰበሰቡት
የእናቶች ሳቅ ላይ የተኮረጀ ሳቅ . . .
ስተክዥ . . .
ሀገር ነሽ!
በውርስ በተጣሉ ልጆቹ ያዘነ
የአንድ አዛውንት ሃቅ . . .
ዝም ስትይ . . .
ሀገር ነሽ!
ሰሜን ተራራ ላይ እንደሚንጎማለል
ጥቅጥቅ የጉም ክምር፣
ከተራራ ጀርባ እንደተደበቀ
የዋሻ ውስጥ ደብር።
፨፨፨
ስታዝኝ ያመኛል
ከዛሬ ሃዘንሽ የነገ አባዜ
ስትስቂ ያመኛል
ከፈገግታሽ ቅርኒያ ረቂቅ ትካዜ
ቀድሞ ይታየኛል ቀድሞ ይሰማኛል፣
ከውብ ሳቅሽ ገዝፎ ህመሜን በትኖ ዝምታሽ ማርኮኛል።
.
.
.
ዝም . . . በይ!
(ከሰባተኛው)
@getem
@getem
@getem
~
~
ፈገግ ስትይ . . .
ሀገር ነሽ!
የቡና ታርቲም ላይ ከተሰበሰቡት
የእናቶች ሳቅ ላይ የተኮረጀ ሳቅ . . .
ስተክዥ . . .
ሀገር ነሽ!
በውርስ በተጣሉ ልጆቹ ያዘነ
የአንድ አዛውንት ሃቅ . . .
ዝም ስትይ . . .
ሀገር ነሽ!
ሰሜን ተራራ ላይ እንደሚንጎማለል
ጥቅጥቅ የጉም ክምር፣
ከተራራ ጀርባ እንደተደበቀ
የዋሻ ውስጥ ደብር።
፨፨፨
ስታዝኝ ያመኛል
ከዛሬ ሃዘንሽ የነገ አባዜ
ስትስቂ ያመኛል
ከፈገግታሽ ቅርኒያ ረቂቅ ትካዜ
ቀድሞ ይታየኛል ቀድሞ ይሰማኛል፣
ከውብ ሳቅሽ ገዝፎ ህመሜን በትኖ ዝምታሽ ማርኮኛል።
.
.
.
ዝም . . . በይ!
(ከሰባተኛው)
@getem
@getem
@getem
ዛሬ!
የአደይ ሚክስድ አርት ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ሙዚየም ዛሬ መስከረም 14 ከ 11:30 ጀምሮ ለእይታ ይበቃል ።
ጥበብ ለለውጥ !
@Utopiavisualarts
የአደይ ሚክስድ አርት ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ሙዚየም ዛሬ መስከረም 14 ከ 11:30 ጀምሮ ለእይታ ይበቃል ።
ጥበብ ለለውጥ !
@Utopiavisualarts
የማሳበብ መዘዝ
____________
በፍርዱ ሸንጎ ፊት ፣
ስትቆም በክስ ወጥመድ፣
ብርቱ ፀፀት አስሮህ፣
ካቃተህ መራመድ፣
እገሌ ነው ብለህ፣
ማሳበብ አትልመድ።
ሟች ሞቶ እንዲገኝ፣
ሀሳብ አመንጭተህ፣
ግብር አበሮችህን፣
በወኔ አበርትተህ፣
ጥይቱ እንዲተኮስ ፣
ጥይት አቀብለህ፣
የገዳዮች አውራ፣
አንተ ራስህ እያለህ፣
ታድያ በፍርዷ ቀን ፣
"ገዳይ አይደለሁም"
ስለምን ትላለህ?
ይኸውልህ ስማኝ...
ተባብረህ ከነበር፣
ካጥቂዎቹ መሀል፣
የማያልፈው ቅጣት፣
አንተም ይገባሀል።
…………… ………………
✍ ዮሐንስ ገርማሜ
@getem
@getem
@getem
____________
በፍርዱ ሸንጎ ፊት ፣
ስትቆም በክስ ወጥመድ፣
ብርቱ ፀፀት አስሮህ፣
ካቃተህ መራመድ፣
እገሌ ነው ብለህ፣
ማሳበብ አትልመድ።
ሟች ሞቶ እንዲገኝ፣
ሀሳብ አመንጭተህ፣
ግብር አበሮችህን፣
በወኔ አበርትተህ፣
ጥይቱ እንዲተኮስ ፣
ጥይት አቀብለህ፣
የገዳዮች አውራ፣
አንተ ራስህ እያለህ፣
ታድያ በፍርዷ ቀን ፣
"ገዳይ አይደለሁም"
ስለምን ትላለህ?
ይኸውልህ ስማኝ...
ተባብረህ ከነበር፣
ካጥቂዎቹ መሀል፣
የማያልፈው ቅጣት፣
አንተም ይገባሀል።
…………… ………………
✍ ዮሐንስ ገርማሜ
@getem
@getem
@getem
ለውብ ቀን!
💚
ባለቅኔው ደበበ ሰይፉ ከ1942 - 1992
በኢትዮጵያ የሥነ-ጽሑፍ ዓለም ውስጥ በሥነ-ግጥም ችሎታቸው አንቱ ተብለው ባለቅኔ
ወደመባል ደረጃ ከደረሱ ልሒቃን /elites/ መካከል አንዱ ነው። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
ውሰጥ ለረጅም ዓመታት ከማስተማሩም በላይ የኢትዮጵያን ቋንቋ በተለይም አማርኛን
የሥነ-ጽሑፍና የመደበኛ ትምህርት ማካሄጃ ለማድረግ በነበረው እንቅስቃሴ ውስጥ
ያበረከተው አስተዋፅኦ በእጅጉ ግዙፍ ነው። የኢትዮጵያን የሥነ-ጽሑፍ፣ የሥነ-ግጥም እና
የቴአትር ጥበብን ታሪክ በማጥናትና በመመራመር ረገድ ለትውልድ አቆይቶት ያለፈው
መረጃ ለዘላለም ስሙ እንዲነሳ ያደርገዋል። የአያሌ ታላላቅ ሰብዕናዎች ባለቤት የሆነውን
ምሁር ዛሬ በጥቂቱ እናነሳሳዋለን። መምህሩን፣ ገጣሚውን፣ ፀሐፌ-ተውኔቱን፣
ተመራማሪውን ሰው ደበበ ሰይፉን!
ደበበ ሰይፉ ሐምሌ 5 ቀን 1942 ዓ.ም የተወለደባት እና ያደገባት ከተማ ይርጋለም
ትባላለች። ይርጋለም በደቡብ ኢትዮጵያ ከሚገኙ ጥንታዊ ከተሞች መካከል አንዷ ነች።
ከአዋሳ ከተማ በአጭር ርቀት ውስጥ ያለችው ይርጋለም ሲዳማ ውስጥ ዝነኛ ከሆኑ
ከተሞች መካከል ግንባር ቀደሟ ናት። ይርጋለም ጥንታዊት ናት። ከዚያም አልፎ ጥንት
የደቡብ ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ሆና የልዩ ልዩ ህዝቦች መናሃርያ ነበረች። ይህች ከተማ
በ1940ዎቹ፣ 50ዎቹ እና 60ዎቹ ውስጥ ከልዩ ልዩ የደቡብ ከተሞች ተማሪዎች እየመጡ
የመካከለኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የሚከታተሉባት ማዕከል ሆና ቆይታለች።
ይርጋለም ኅብረ ህዝብ ያለባት የኢትዮጵያ ምሳሌ ነች። እናም በዚህች ከተማ ውስጥ
ተወልዶ ያደገው ደበበ ሰይፉ ለኢትዮጵያ ኪነ-ጥበብ ሰፊ ብርሃን ሰጥቶ ያለፈ የኪነት ፀሐይ
ነበር።
ደበበ ሰይፉ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን እዚህ አዲስ አበባ ውስጥ በኮከበ ጽባሕ ት/ቤት
ካጠናቀቀ በኋላ ወደ ቀድሞ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ተብሎ ከሚታወቀውና በአሁኑ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመግባት ሥነ-ጽሑፍን መማር ጀመረ። ከዚያም በ1965 ዓ.ም
ከዚሁ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ማዕረግ ተመረቀ። ቀጥሎም በዚያው በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሥነ-
ጽሑፍን ማስተማር ጀመረ።
እንደ ደበበ ሰይፉ ያሉ መምህራን በዚህ ትምህርት ክፍል ውስጥ መቀላቀል ሲጀምሩ
ዲፓርትመንቱም እያደገና እየተስፋፋ የመጣበት ዘመን እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ምክንያቱም የጥናትና የምርምር ውጤቶች በስፋት መሠራት ጀመሩ።
ለምሳሌ ደበበ ሰይፉ የኢትዮጵያ የሥነ-ግጥም እና የሥነ-ጽሁፍ ታሪክን እና በዚህ ታሪክ
ውስጥ ደግሞ ኪነታዊ አስተዋፅኦዋቸው ሰፊ የሆነውን ጐምቱ አበው ፀሐፊያንን ታሪክና
የአፃፃፍ ቴክኒካቸውንም ጭምር እያጠና ማቅረብ ጀመረ። ያለፈው የጥበብ አሻራ
ለመጪው ጥበብ የሚያቀብለውን መረጃ እየወሰደ ትውልድን በጥበብ ማስተሳሰር አንዱ
ተግባሩ ነበር።
የአንዲት ሀገር ማንነት ተቀርጾ ከሚኖርባቸው ጉዳዮች ዋነኛው ሥነ-ጽሁፍ ነው። በሥነ-
ጽሑፍ ውስጥ ደግሞ ታሪክ አለ፣ ሥነ-ግጥም አለ፣ ቴአትር አለ፣ ፍልስፍና አለ፣ አስተሳሰብ
አለ፣ ፖለቲካ አለ፣ ህዝብ አለ፣ ኧረ ብዙ ብዙ ነገሮች አሉት። ደበበ ሰይፉ ደግሞ እነዚህን
የኢትዮጵያን የማንነት መገለጫዎች ከጥንታዊ ሰነዶች ውስጥ እየፈተሸ በማውጣት
ትውልድ እንዲህ ነበር፣ እንዲህም ኖሯል፣ እንዲህም አስቧል …. እያለ የዘመን ርቀታችን
እንዳያለያየን ከትውልዶች ጋር ያገናኘን ነበር። ደበበ በስነ-ጽሁፍ ውስጥ የትውልድ
የመሸጋገሪያ ድልድይ ሆኖ አገልግሏል።
ደበበ ሰይፉ በቀላል አነጋገር ሐያሲ ነበር። ሐያሲ ታሪክ አዋቂ ነው። ያለፈውን ከአሁኑ ጋር
እያነፃፀረ የሚያስረዳ፣ የሚተነትን ባለሙያ ነው። የሒስ ጥበብን ደግሞ እንደ ሙያ
ከታደሉት ሰዎች መካከል ደበበ ሰይፉ አንዱ ነው። በኢትዮጵያ የዘመናዊ ሂስ ጥበብ ውስጥ
በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ሰው ቢኖር አንዱ ደበበ ሰይፉ ነው።
ደበበ ገጣሚ ነው። በአገጣጠም ችሎታው ውብ እና ማራኪነት የተነሳ ብዙዎች ባለቅኔው
ደበበ ሰይፉ እያሉ ይጠሩታል። ይህ በስነ-ግጥም ዓለም ውስጥ የተሰጠው ፀጋ ከሌሎች
ጉዳዮች ሁሉ ገዝፎ የሚነገርለትም ነው። ደበበ ሲነሳ ገጣሚነቱ አብሮ ብቅ የሚልለት
የጥበብ ሰው ነው። እነዚህን የግጥም ትሩፋቶቹን በ1980 ዓ.ም የብርሐን ፍቅር በሚል
ርዕስ ሰብስቦ አሳትሟቸዋል። በዚህች የብርሐን ፍቅር በተሰኘችው የሥነ-ግጥም ስብስቡ
መፅሐፍ ውስጥ ቀደም ሲል በተማሪነት እና በአስተማሪነት ዘመኑ ሲፅፋቸው የነበሩትን
ግጥሞች የምናገኝበት ድንቅ መፅሐፉ ነች።
ከዚህች መፅሐፉ በተጨማሪ በ1992 ዓ.ም በሜጋ አሳታሚ ድርጅት አማካይነት ለራስ
የተፃፈ ደብዳቤ በሚል ርዕስ ሁለተኛዋ የሥነ-ግጥም መፅሐፉ ለንባብ በቃች። ነገር ግን
በዚህ ወቅት ደበበ በሕይወት የለም ነበር። ስራዎቹ ዘላለማዊ ናቸውና እርሱ በህይወት
በሌለበት ወቅትም የትውልድ ሀሴት በመሆናቸው ይታተሙለታል። እናም ለራስ የተፃፈ
ደብዳቤ በምትሰኘው መፅሐፉም የደበበን የሥነ-ግጥም ርቀት እና ጥልቀት የምናይበት
ሥራ ነው። ለዚህች ለደበበ መፅሐፍ አጠቃላይ ገፅታዋን በተመለከተ አስተያየት የፃፈው
ታዋቂው ወገኛ እና የደበበ ጓደኛ የሆነው መስፍን ኃብተማርያም ነው። መስፍንም
ስለዚህችው መፅሐፍ የሚከተለውን ብሏል።
“ደበበ ሰይፉ በርዕስ አመራረጡና በሚያስተላልፋቸው ልብ የሚነኩ መልዕክቶች ብቻ
ሳይሆን በስንኞቹ አወራረድና የቤት አመታቱ በአጠቃላይ በውብ አቀራረቡ ተደራሲያንን
የሚመስጥ ገጣሚ ነው። ስለ ተፈጥሮ ሲገጥም ፀሐይና ጨረቃ፣ ቀስተ ደመናና የገደል
ማሚቶ ያጅቡታል። ስለ ፍቅር ስንኞች ሲቋጥር የፍቅረኞችን ልብ እንደ ስዕል ቆንጆ አድርጐ
በቃላት ቀለማት ያሳያል። ክህደት ላይ እንደ አንዳንድ ገጣሚያን አያላዝንም። ይልቁንም
ውበትና ህይወትን አገናዝቦ ያውላችሁ ስሙት፣ እዩት፣ ማለትን ይመርጣል። ….. እኔ
እንደማውቀው ደበበ ሰይፉ በገጣሚነቱ ሁሌም ዝምተኛ ነው። አይጮህም። ጮሆም
አያስበረግግም። ይልቁንስ ለዘብ ለስለስ አድርጐ “እስቲ አጢኑት” ይለናል። ደግመን
እንድናነብለት የሚያደርገንም ይኸው ችሎታው ነው።” በማለት የወግ ፀሐፊውና ጓደኛው
መስፍን ሐብተማርያም ደበበን ይገልፀዋል።
ደበበ ሰይፉ በስነ-ግጥም ተሰጥኦው እና በሚያነሳቸው ርዕሰ ጉዳዮች በኢትዮጵያ የሥነ-
ጽሑፍ ታሪክ ውስጥ ስማቸው ጐልቶ ከሚነሱ ከያኒያን መካከል አንዱ መሆኑን ቀደም ያሉት
ሃያሲያን ጽፈውታል።
የደበበ ችሎታ በዚህ ብቻም አያበቃም። ደበበ የቴአትር ጥበብ መምህር ከመሆኑም በላይ
በዘርፉ ውስጥ ግዙፍ የሚባል አስተዋፅኦ አበርክቶ አልፏል። ደበበ በመድረክ ላይ የሚሰሩ
ቴአትሮችን እና የቴአትር ፅሁፎችን የያዟቸውን ሃሳቦች በመተንተን እና ሒስ በመስጠት
ለዘርፉ እድገት የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ደበበ የቃላት ፈጣሪም ነው። ለምሳሌ በቴአትር
ዓለም በአጠቃላይ በሥነ-ጽሑፉ ዓለም ውስጥ በእንግሊዝኛ ቋንቋ መጠሪያ የሆኑ ሙያዊ
ቃላትን ወደ አማርኛ በማምጣት አቻ የሆነ የአማርኛ ትርጉም በመስጠት ይታወቃል።
በኢትዮጵያ ሥነ-ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ እስከ አሁን ድረስ መጠሪያ የሆኑትን ለምሳሌ ገፀ-
ባህሪ፣ ሴራ፣ መቼት፣ ቃለ-ተውኔት ወዘተ እየተባሉ የሚገለፁትን መጠሪያዎች የፈጠረው
ደበበ ሰይፉ ነው።
- Character የሚለውን የእንግሊዝኛ መጠሪያ “ገፀ-ባህሪ” በማለት አቻ ትርጉም
ሰጥቶታል፣
- Sefting የሚለውን የእንግሊዝኛ መጠሪያ በውስጡ ጊዜ እና ቦታን መያዙን በመረዳት
ወደ አማርኛ ቋንቋ ‘መቼት’ ብሎ ደበበ ተረጐመው። መቼት ማለት ‘መች’ እና ‘የት’ ማለት
ሲሆን፤ ጊዜንና ቦታን ይገልፃል።
- Dialogue የሚለው የእንገሊዝኛ ቃል ተዋናዮ
💚
ባለቅኔው ደበበ ሰይፉ ከ1942 - 1992
በኢትዮጵያ የሥነ-ጽሑፍ ዓለም ውስጥ በሥነ-ግጥም ችሎታቸው አንቱ ተብለው ባለቅኔ
ወደመባል ደረጃ ከደረሱ ልሒቃን /elites/ መካከል አንዱ ነው። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
ውሰጥ ለረጅም ዓመታት ከማስተማሩም በላይ የኢትዮጵያን ቋንቋ በተለይም አማርኛን
የሥነ-ጽሑፍና የመደበኛ ትምህርት ማካሄጃ ለማድረግ በነበረው እንቅስቃሴ ውስጥ
ያበረከተው አስተዋፅኦ በእጅጉ ግዙፍ ነው። የኢትዮጵያን የሥነ-ጽሑፍ፣ የሥነ-ግጥም እና
የቴአትር ጥበብን ታሪክ በማጥናትና በመመራመር ረገድ ለትውልድ አቆይቶት ያለፈው
መረጃ ለዘላለም ስሙ እንዲነሳ ያደርገዋል። የአያሌ ታላላቅ ሰብዕናዎች ባለቤት የሆነውን
ምሁር ዛሬ በጥቂቱ እናነሳሳዋለን። መምህሩን፣ ገጣሚውን፣ ፀሐፌ-ተውኔቱን፣
ተመራማሪውን ሰው ደበበ ሰይፉን!
ደበበ ሰይፉ ሐምሌ 5 ቀን 1942 ዓ.ም የተወለደባት እና ያደገባት ከተማ ይርጋለም
ትባላለች። ይርጋለም በደቡብ ኢትዮጵያ ከሚገኙ ጥንታዊ ከተሞች መካከል አንዷ ነች።
ከአዋሳ ከተማ በአጭር ርቀት ውስጥ ያለችው ይርጋለም ሲዳማ ውስጥ ዝነኛ ከሆኑ
ከተሞች መካከል ግንባር ቀደሟ ናት። ይርጋለም ጥንታዊት ናት። ከዚያም አልፎ ጥንት
የደቡብ ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ሆና የልዩ ልዩ ህዝቦች መናሃርያ ነበረች። ይህች ከተማ
በ1940ዎቹ፣ 50ዎቹ እና 60ዎቹ ውስጥ ከልዩ ልዩ የደቡብ ከተሞች ተማሪዎች እየመጡ
የመካከለኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የሚከታተሉባት ማዕከል ሆና ቆይታለች።
ይርጋለም ኅብረ ህዝብ ያለባት የኢትዮጵያ ምሳሌ ነች። እናም በዚህች ከተማ ውስጥ
ተወልዶ ያደገው ደበበ ሰይፉ ለኢትዮጵያ ኪነ-ጥበብ ሰፊ ብርሃን ሰጥቶ ያለፈ የኪነት ፀሐይ
ነበር።
ደበበ ሰይፉ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን እዚህ አዲስ አበባ ውስጥ በኮከበ ጽባሕ ት/ቤት
ካጠናቀቀ በኋላ ወደ ቀድሞ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ተብሎ ከሚታወቀውና በአሁኑ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመግባት ሥነ-ጽሑፍን መማር ጀመረ። ከዚያም በ1965 ዓ.ም
ከዚሁ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ማዕረግ ተመረቀ። ቀጥሎም በዚያው በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሥነ-
ጽሑፍን ማስተማር ጀመረ።
እንደ ደበበ ሰይፉ ያሉ መምህራን በዚህ ትምህርት ክፍል ውስጥ መቀላቀል ሲጀምሩ
ዲፓርትመንቱም እያደገና እየተስፋፋ የመጣበት ዘመን እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ምክንያቱም የጥናትና የምርምር ውጤቶች በስፋት መሠራት ጀመሩ።
ለምሳሌ ደበበ ሰይፉ የኢትዮጵያ የሥነ-ግጥም እና የሥነ-ጽሁፍ ታሪክን እና በዚህ ታሪክ
ውስጥ ደግሞ ኪነታዊ አስተዋፅኦዋቸው ሰፊ የሆነውን ጐምቱ አበው ፀሐፊያንን ታሪክና
የአፃፃፍ ቴክኒካቸውንም ጭምር እያጠና ማቅረብ ጀመረ። ያለፈው የጥበብ አሻራ
ለመጪው ጥበብ የሚያቀብለውን መረጃ እየወሰደ ትውልድን በጥበብ ማስተሳሰር አንዱ
ተግባሩ ነበር።
የአንዲት ሀገር ማንነት ተቀርጾ ከሚኖርባቸው ጉዳዮች ዋነኛው ሥነ-ጽሁፍ ነው። በሥነ-
ጽሑፍ ውስጥ ደግሞ ታሪክ አለ፣ ሥነ-ግጥም አለ፣ ቴአትር አለ፣ ፍልስፍና አለ፣ አስተሳሰብ
አለ፣ ፖለቲካ አለ፣ ህዝብ አለ፣ ኧረ ብዙ ብዙ ነገሮች አሉት። ደበበ ሰይፉ ደግሞ እነዚህን
የኢትዮጵያን የማንነት መገለጫዎች ከጥንታዊ ሰነዶች ውስጥ እየፈተሸ በማውጣት
ትውልድ እንዲህ ነበር፣ እንዲህም ኖሯል፣ እንዲህም አስቧል …. እያለ የዘመን ርቀታችን
እንዳያለያየን ከትውልዶች ጋር ያገናኘን ነበር። ደበበ በስነ-ጽሁፍ ውስጥ የትውልድ
የመሸጋገሪያ ድልድይ ሆኖ አገልግሏል።
ደበበ ሰይፉ በቀላል አነጋገር ሐያሲ ነበር። ሐያሲ ታሪክ አዋቂ ነው። ያለፈውን ከአሁኑ ጋር
እያነፃፀረ የሚያስረዳ፣ የሚተነትን ባለሙያ ነው። የሒስ ጥበብን ደግሞ እንደ ሙያ
ከታደሉት ሰዎች መካከል ደበበ ሰይፉ አንዱ ነው። በኢትዮጵያ የዘመናዊ ሂስ ጥበብ ውስጥ
በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ሰው ቢኖር አንዱ ደበበ ሰይፉ ነው።
ደበበ ገጣሚ ነው። በአገጣጠም ችሎታው ውብ እና ማራኪነት የተነሳ ብዙዎች ባለቅኔው
ደበበ ሰይፉ እያሉ ይጠሩታል። ይህ በስነ-ግጥም ዓለም ውስጥ የተሰጠው ፀጋ ከሌሎች
ጉዳዮች ሁሉ ገዝፎ የሚነገርለትም ነው። ደበበ ሲነሳ ገጣሚነቱ አብሮ ብቅ የሚልለት
የጥበብ ሰው ነው። እነዚህን የግጥም ትሩፋቶቹን በ1980 ዓ.ም የብርሐን ፍቅር በሚል
ርዕስ ሰብስቦ አሳትሟቸዋል። በዚህች የብርሐን ፍቅር በተሰኘችው የሥነ-ግጥም ስብስቡ
መፅሐፍ ውስጥ ቀደም ሲል በተማሪነት እና በአስተማሪነት ዘመኑ ሲፅፋቸው የነበሩትን
ግጥሞች የምናገኝበት ድንቅ መፅሐፉ ነች።
ከዚህች መፅሐፉ በተጨማሪ በ1992 ዓ.ም በሜጋ አሳታሚ ድርጅት አማካይነት ለራስ
የተፃፈ ደብዳቤ በሚል ርዕስ ሁለተኛዋ የሥነ-ግጥም መፅሐፉ ለንባብ በቃች። ነገር ግን
በዚህ ወቅት ደበበ በሕይወት የለም ነበር። ስራዎቹ ዘላለማዊ ናቸውና እርሱ በህይወት
በሌለበት ወቅትም የትውልድ ሀሴት በመሆናቸው ይታተሙለታል። እናም ለራስ የተፃፈ
ደብዳቤ በምትሰኘው መፅሐፉም የደበበን የሥነ-ግጥም ርቀት እና ጥልቀት የምናይበት
ሥራ ነው። ለዚህች ለደበበ መፅሐፍ አጠቃላይ ገፅታዋን በተመለከተ አስተያየት የፃፈው
ታዋቂው ወገኛ እና የደበበ ጓደኛ የሆነው መስፍን ኃብተማርያም ነው። መስፍንም
ስለዚህችው መፅሐፍ የሚከተለውን ብሏል።
“ደበበ ሰይፉ በርዕስ አመራረጡና በሚያስተላልፋቸው ልብ የሚነኩ መልዕክቶች ብቻ
ሳይሆን በስንኞቹ አወራረድና የቤት አመታቱ በአጠቃላይ በውብ አቀራረቡ ተደራሲያንን
የሚመስጥ ገጣሚ ነው። ስለ ተፈጥሮ ሲገጥም ፀሐይና ጨረቃ፣ ቀስተ ደመናና የገደል
ማሚቶ ያጅቡታል። ስለ ፍቅር ስንኞች ሲቋጥር የፍቅረኞችን ልብ እንደ ስዕል ቆንጆ አድርጐ
በቃላት ቀለማት ያሳያል። ክህደት ላይ እንደ አንዳንድ ገጣሚያን አያላዝንም። ይልቁንም
ውበትና ህይወትን አገናዝቦ ያውላችሁ ስሙት፣ እዩት፣ ማለትን ይመርጣል። ….. እኔ
እንደማውቀው ደበበ ሰይፉ በገጣሚነቱ ሁሌም ዝምተኛ ነው። አይጮህም። ጮሆም
አያስበረግግም። ይልቁንስ ለዘብ ለስለስ አድርጐ “እስቲ አጢኑት” ይለናል። ደግመን
እንድናነብለት የሚያደርገንም ይኸው ችሎታው ነው።” በማለት የወግ ፀሐፊውና ጓደኛው
መስፍን ሐብተማርያም ደበበን ይገልፀዋል።
ደበበ ሰይፉ በስነ-ግጥም ተሰጥኦው እና በሚያነሳቸው ርዕሰ ጉዳዮች በኢትዮጵያ የሥነ-
ጽሑፍ ታሪክ ውስጥ ስማቸው ጐልቶ ከሚነሱ ከያኒያን መካከል አንዱ መሆኑን ቀደም ያሉት
ሃያሲያን ጽፈውታል።
የደበበ ችሎታ በዚህ ብቻም አያበቃም። ደበበ የቴአትር ጥበብ መምህር ከመሆኑም በላይ
በዘርፉ ውስጥ ግዙፍ የሚባል አስተዋፅኦ አበርክቶ አልፏል። ደበበ በመድረክ ላይ የሚሰሩ
ቴአትሮችን እና የቴአትር ፅሁፎችን የያዟቸውን ሃሳቦች በመተንተን እና ሒስ በመስጠት
ለዘርፉ እድገት የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ደበበ የቃላት ፈጣሪም ነው። ለምሳሌ በቴአትር
ዓለም በአጠቃላይ በሥነ-ጽሑፉ ዓለም ውስጥ በእንግሊዝኛ ቋንቋ መጠሪያ የሆኑ ሙያዊ
ቃላትን ወደ አማርኛ በማምጣት አቻ የሆነ የአማርኛ ትርጉም በመስጠት ይታወቃል።
በኢትዮጵያ ሥነ-ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ እስከ አሁን ድረስ መጠሪያ የሆኑትን ለምሳሌ ገፀ-
ባህሪ፣ ሴራ፣ መቼት፣ ቃለ-ተውኔት ወዘተ እየተባሉ የሚገለፁትን መጠሪያዎች የፈጠረው
ደበበ ሰይፉ ነው።
- Character የሚለውን የእንግሊዝኛ መጠሪያ “ገፀ-ባህሪ” በማለት አቻ ትርጉም
ሰጥቶታል፣
- Sefting የሚለውን የእንግሊዝኛ መጠሪያ በውስጡ ጊዜ እና ቦታን መያዙን በመረዳት
ወደ አማርኛ ቋንቋ ‘መቼት’ ብሎ ደበበ ተረጐመው። መቼት ማለት ‘መች’ እና ‘የት’ ማለት
ሲሆን፤ ጊዜንና ቦታን ይገልፃል።
- Dialogue የሚለው የእንገሊዝኛ ቃል ተዋናዮ
😁1
ች በትወና ወቅት የሚናገሩት ሲሆን፤ ይህን
Dialogue የተሰኘውን ቃል ወደ አማርኛ አምጥቶት ቃለ-ተውኔት በማለት የተረጐመው
ደበበ ሰይፉ ነው።
ደበበ እነዚህንና ሌሎችንም ሥነ-ጽሑፋዊ ቃላትን በመፈጠር በትውልዶች አንደበት፣
አእምሮ እና ብዕር ውስጥ ለዘላለም እንዲኖር ያደረገ ጥበበኛ ነው።
ደበበ ሰይፉ ለዚሁ ለቴአትር ትምህርት ዘርፍ ካበረከታቸው አስተዋፅኦዎች መካከል
ለትምህርቱ መጐልበት ይረዳ ዘንድ በ1973 ዓ.ም መፅሐፍም አሳትሟል። መፅሐፏ
የቴአትር ጥበብ ከፀሐፌ-ተውኔቱ አንፃር የምትሰኝ ርዕስ የያዘች ሲሆን፤ ለሀገራችን የቴአተር
ሙያተኞች እንዲበራከቱ እና በእውቀት ላይ የተመሠረተ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ሰፊ ድርሻ
አበርክታለች። ደበበ በዚሁ በቴአትር ዘርፍ ውስጥ የተፃፉ የንባብ መፅሐፍት
ያለመኖራቸውን ክፍተት ተገንዝቦ ያንን ክፍተት ለመሙላት ሙያዊ ጥሪውን የተወጣ
ባለሟል ነው።
ደበበ ሰይፉ ፀሐፌ - ተውኔትም ነው። በርካታ ተውኔቶችን ፅፎ ለመድረክ አብቅቷል።
አንዳንዶቹ ደግሞ ለምሳሌ ክፍተት የተሰኘው ተውኔቱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለበርካታ
ጊዜያት ታይቶለታል። በዚህ
ክፍተት በተሰኘው የደበበ የቴሌቭዥን ድራማው ላይ በመተወን ተፈሪ ዓለሙ፣ አለማየሁ
ታደሰ እና ሙሉአለም ታደሰ ድንቅ የሆነ ብቃታቸውን አሳይተውበታል።
ደበበ ሰይፉ ከፃፋቸውና ከተረጐማቸው ተውኔቶች መካከል የሚከተሉት ዋና ዋናዎቹ
ናቸው፡-
1. ከባህር የወጣ ዓሣ
2. እናትና ልጆቹ
3. እነሱ እነሷ
4. ሳይቋጠር ሲተረተር
5. የህፃን ሽማግሌ
6. ማክቤዝ እና
7. ጋሊሊዮ ጋሊሊ ይገኙበታል።
ከእነዚህ ሌላም በ1973 ዓ.ም ማርክሲዝምና የቋንቋ ችግሮቹ የሚል መፅሐፍ
ከማሳተሙም በላይ በ1960 ዓ.ም ያዘጋጃት የሦስት አጫጭር ልቦለዶች መድብል
የሆነችው ድርሳኑ ትጠቀሳለች።
ደበበ ሰይፉ ከእነዚህ ከረቀቁ እና ከመጠቁ ምሁራዊ አስተዋፅኦው በተጨማሪ በበርካታ
ኪነ-ጥበባዊ ጉዳዮች ላይም አሻራውን ያሳረፈ ነው። ለምሳሌ በቀድሞው ኩራዝ አሳታሚ
ድርጅት ውስጥ በመሳተፍ ለኢትዮጵያ ሥነ-ጽሑፍ መስፋፋት እገዛው ሰፊ ሆኖ ኖሯል።
በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥም የኪነ-ጥበብ ዘርፍ ውስጥ ያሉትን ፕሮግራሞች አማካሪ ሆኖ
ሰርቷል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የቋንቋዎች ተቋም ጆርናል አሳታሚ ኮሚቴ
ሊቀመንበር ሆኖ አገልግሏል። ደበበ ሰይፉ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር ፕሬዚደንት ሆኖ
ሰፊ ድርሻ አበርክቷል። ደበበ ሰይፉ በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዓለም ውስጥ ትልቅ ድርሻውን
አበርክቶ ያለፈ የትውልድ ምሳሌ ነው።
ግን ሁሉም ነገር እንዳማረበት እስከ መጨረሻው አይሄድም፤ እናም ደበበ በዙሪያው ባሉ
ሰዎች በሚያውቃቸው ሰዎች ተበሳጨ። ከ1985 ዓ.ም ጀምሮ ከቤት ዋለ። ታመመ።
መናገርም አቆመ። ለኢትዮጵያ ሥነ-ጽሑፍ በአጠቃላይ ለኪነ-ጥበቧ እድገት የአንበሳውን
ድርሻ ያበረከተው ደበበ ሰይፉ ሚያዚያ 16 ቀን 1992 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
ቀብሩም ቅዱስ ዮሴፍ ቤተ-ክርስትያን ተፈፀመ።
ስለ ደበበ ሰይፉ ምን ተፃፈ?
“ደበበ ሰይፉ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር ፕሬዝዳንት ሆኖ ከ1978 እስከ 1983 ዓ.ም
ድረስ ሰርቷል። ከዚህም በላይ በወቅቱ አያሌ የሙያው ባለቤቶች እንዲሰባሰቡ አድርጓል።
ከውጭ ሀገር በተለይም ከሶቭዬት ኅብረት ጋር ሙያዊ ድጋፍና ትብብር እንዲደረግ
አድርጓል። አንጋፋው ደራሲና ሃያሲ አቶ አስፋው ዳምጤ በአንድ ወቅት ስለ ደበበ የህይወት
ታሪክ ለሚያጠናው ተማሪ፣ ለተክቶ ታደሰ በሰጡት ቃለ-ምልልስ እንዲህ ብለዋል።
“ደበበ ስራ ይወዳል ስራው ጥንቅቅ ያለ ነው። ግን ሰዎችን ለመጋፈጥ ድፍረት ያንሰዋል።
ለቴአትር ዲፓርትመንት ከመከፈቱ ጀምሮ መጽሐፍ ጽፎላቸዋል። ፅንሰ ሃሳቡን እንዲረዱት
አድርጓል። ስለ ደበበ ካስደነቁኝ አንዱ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ችሎታው ነው። የደራሲያን
ማኅበር ሊቀመንበር ሆኖ እኔ ስራ አስፈፃሚ ሆነን ሠርተናል። ቀድሞ ከነበረው የማኅበሩ
የሥራ ዘመን ያልታየ እንቅስቃሴ ደረገ” የሚሉት አቶ አስፋው “እነሆ” የምትሰኘው
የአጫጭር ልቦለዶች መድብልና “ብሌን” የተሰኘችው መጽሔትም መታተሟን ያስረዳሉ።
“የጽጌረዳ ብዕር” የሚል የግጥም መድብል መታተሙንም አስረድተው የደበበን ጥንካሬ
ገልፀዋል።
ታዋቂው የወግ ፀሐፊ መስፍን ኃ/ማርያም ደግሞ ለአጥኚው እንዲህ ብሎ ነግሮታል።
“ደበበ በጣም ጠንካራ፣ ትጉህ ሠራተኛ፣ ለተሰለፈበት ዓላማ ወደኋላ የማይል፣ በማስተማር
ደበበ innovator /ፈጣሪ/ አይነት ነበር። የምናስተምረውን ኮርስ እንዲህ ብናደርገው፣
እንዲህ ብንለው እያለ ከጊዜ ወደ ጊዜ እንድናሻሽል በማድረግ በኩል ፈር ቀዳጅ ነበር።….
ደበበ ደራሲ ብቻ አይደለም። ጥሩ የማስተማር ችሎታ ነበረው” ብሏል።
ደራሲ ታደለ ገድሌም ሚያዚያ 29 ቀን 1992 ዓ.ም በወጣው “አዲስ ዘመን” ጋዜጣ ላይ
“ደበበ ሰይፉና ስራዎቹ ሲታወሱ” በሚለ ርዕስ ስለዚሁ ታላቅ ሰው አስነብቦናል።
ይህች ከተማ ነሐሴ 5 ቀን 1942 ዓ.ም ደበበን ያህል ታላቅ የኪነ-ጥበብ ሰው አፍርታለች።
አባቱ በጅሮንድ ሰይፉ አንተን ይስጠኝ እና እናቱ ወ/ሮ የማርያምወርቅ አስፋው የኢትዮጵያ
የኪነ-ጥበብ ዋልታ ያቆሙት በዚህች ምድር ነው። ደበበ ሰይፉን! ይርጋለም ከተማ ውስጥ።
“ይርጋለም
ዋ… ይርጋለም
የልጅነቴ ህልም ቀለም
ዓይኔን የከፈትሽው ጨረር
ወርቃማይቱ ጀንበር” ብሎ ደበበ ፅፎታል።
ዛሬ በህይወት የሌለው የስነ-ጽሁፍ መምህሩ ብርሃኑ ገበየሁ ትዝ አለኝ። ስለ ደበበ ሰይፉ
በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ሲፅፍ እንዲህ ብሏል። “የደበበ አቀራረቡ ቀላልና የማያሻማ
ነው። ድምፀቱ ደግሞ ሐዘን ከሰበረው ልብ የሚፈልቅ እንጉርጉሮ። የአቀራረብ ቀላልነት
ውበቱ ነው። ይርጋለምና ልጅነቱ በተናጋሪው ህሊና አንድም ሁለትም ናቸው፤ የማይፈቱ”
ብሏል። እናም ይርጋለም ደበበ ሰይፉ ናት!
ሌላኛው የስነ-ጽሁፍ መምህር የሆነው ወዳጄ ገዛኸኝ ጌታቸው፣ ደበበ ሰይፉ እንዳረፈ
በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ እንዲህ ብሎ ነበር። “ዛሬ የኢትዮጵያ ስነ-ጽሁፍ አንድ ለጋ ብዕር
አጣ፤ ነጥፎ አይደለም ታጥፎ ነው። ዛሬ የኢትዮጵያ ስነ-ጽሁፍ የዋህ ሃሳብ አጣ። ከፍቶ
አይደለም በኖ ተኖ እንጂ። ዛሬ ብዙዎቻችን ካወቅነው ብዙ ነገር አጣን። ካላወቅንም
እሰየው፤ ከእንጉርጉሮና ከፀፀት ተረፍን” ብሏል።
ጋዜጠኛ መሠረት አታላይ በፈርጥ መጽሔት ላይ “ለኪነ-ጥበብ ተፈጥሮ ለኪነ-ጥበብ
የሞተ” በሚል ርዕስ የደበበን ጓደኞች ዶ/ር ፍቃደ አዘዘን፤ መስፍን ኃ/ማርያምን እና
አስፋው ዳምጤን ቃለ መጠይቅ አድርጐ ጽፏል። ሁሉም የኪነ-ጥበብ ጋዜጠኞች ማለት
ይቻላል ስለ ደበበ ጽፈዋል። በ1995 ዓ.ም ደግሞ በጀርመን የባህል ተቋም ውስጥ በወ/ሮ
ተናኘ ታደሰ አስተባባሪነት ዶ/ር ፈቃደ አዘዘ፣ ዶ/ር ዮናስ አድማሱ እና ገዛኸኝ ጌታቸው
“የደበበ ሰይፉ ምሽት” ብለው እጅግ የደመቀ ዝግጅት አድርገዋል። ነብይ መኮንን፣ አበራ
ለማ እና አብርሃም ረታ ቅኔዎች ዘርፈውለታል። የወንዙ ልጅ አብርሃም ረታ እንዲህ
ገጥሞለታል፡-
ብናቀጣጥለው ኪነትክን እንደጧፍ
ስምህ ርችት ነበር
ላውዳመት እሚተኮስ
ሰማይ ላይ የሚጣፍ
ሰማይ ላይ የሚጦፍ
ሰማይ ላይ የሚጥፍ።
#ምንጭ ጥበቡ በለጠ
ውብ ቀን!💚
@getem
@getem
@balmbaras
Dialogue የተሰኘውን ቃል ወደ አማርኛ አምጥቶት ቃለ-ተውኔት በማለት የተረጐመው
ደበበ ሰይፉ ነው።
ደበበ እነዚህንና ሌሎችንም ሥነ-ጽሑፋዊ ቃላትን በመፈጠር በትውልዶች አንደበት፣
አእምሮ እና ብዕር ውስጥ ለዘላለም እንዲኖር ያደረገ ጥበበኛ ነው።
ደበበ ሰይፉ ለዚሁ ለቴአትር ትምህርት ዘርፍ ካበረከታቸው አስተዋፅኦዎች መካከል
ለትምህርቱ መጐልበት ይረዳ ዘንድ በ1973 ዓ.ም መፅሐፍም አሳትሟል። መፅሐፏ
የቴአትር ጥበብ ከፀሐፌ-ተውኔቱ አንፃር የምትሰኝ ርዕስ የያዘች ሲሆን፤ ለሀገራችን የቴአተር
ሙያተኞች እንዲበራከቱ እና በእውቀት ላይ የተመሠረተ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ሰፊ ድርሻ
አበርክታለች። ደበበ በዚሁ በቴአትር ዘርፍ ውስጥ የተፃፉ የንባብ መፅሐፍት
ያለመኖራቸውን ክፍተት ተገንዝቦ ያንን ክፍተት ለመሙላት ሙያዊ ጥሪውን የተወጣ
ባለሟል ነው።
ደበበ ሰይፉ ፀሐፌ - ተውኔትም ነው። በርካታ ተውኔቶችን ፅፎ ለመድረክ አብቅቷል።
አንዳንዶቹ ደግሞ ለምሳሌ ክፍተት የተሰኘው ተውኔቱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለበርካታ
ጊዜያት ታይቶለታል። በዚህ
ክፍተት በተሰኘው የደበበ የቴሌቭዥን ድራማው ላይ በመተወን ተፈሪ ዓለሙ፣ አለማየሁ
ታደሰ እና ሙሉአለም ታደሰ ድንቅ የሆነ ብቃታቸውን አሳይተውበታል።
ደበበ ሰይፉ ከፃፋቸውና ከተረጐማቸው ተውኔቶች መካከል የሚከተሉት ዋና ዋናዎቹ
ናቸው፡-
1. ከባህር የወጣ ዓሣ
2. እናትና ልጆቹ
3. እነሱ እነሷ
4. ሳይቋጠር ሲተረተር
5. የህፃን ሽማግሌ
6. ማክቤዝ እና
7. ጋሊሊዮ ጋሊሊ ይገኙበታል።
ከእነዚህ ሌላም በ1973 ዓ.ም ማርክሲዝምና የቋንቋ ችግሮቹ የሚል መፅሐፍ
ከማሳተሙም በላይ በ1960 ዓ.ም ያዘጋጃት የሦስት አጫጭር ልቦለዶች መድብል
የሆነችው ድርሳኑ ትጠቀሳለች።
ደበበ ሰይፉ ከእነዚህ ከረቀቁ እና ከመጠቁ ምሁራዊ አስተዋፅኦው በተጨማሪ በበርካታ
ኪነ-ጥበባዊ ጉዳዮች ላይም አሻራውን ያሳረፈ ነው። ለምሳሌ በቀድሞው ኩራዝ አሳታሚ
ድርጅት ውስጥ በመሳተፍ ለኢትዮጵያ ሥነ-ጽሑፍ መስፋፋት እገዛው ሰፊ ሆኖ ኖሯል።
በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥም የኪነ-ጥበብ ዘርፍ ውስጥ ያሉትን ፕሮግራሞች አማካሪ ሆኖ
ሰርቷል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የቋንቋዎች ተቋም ጆርናል አሳታሚ ኮሚቴ
ሊቀመንበር ሆኖ አገልግሏል። ደበበ ሰይፉ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር ፕሬዚደንት ሆኖ
ሰፊ ድርሻ አበርክቷል። ደበበ ሰይፉ በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዓለም ውስጥ ትልቅ ድርሻውን
አበርክቶ ያለፈ የትውልድ ምሳሌ ነው።
ግን ሁሉም ነገር እንዳማረበት እስከ መጨረሻው አይሄድም፤ እናም ደበበ በዙሪያው ባሉ
ሰዎች በሚያውቃቸው ሰዎች ተበሳጨ። ከ1985 ዓ.ም ጀምሮ ከቤት ዋለ። ታመመ።
መናገርም አቆመ። ለኢትዮጵያ ሥነ-ጽሑፍ በአጠቃላይ ለኪነ-ጥበቧ እድገት የአንበሳውን
ድርሻ ያበረከተው ደበበ ሰይፉ ሚያዚያ 16 ቀን 1992 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
ቀብሩም ቅዱስ ዮሴፍ ቤተ-ክርስትያን ተፈፀመ።
ስለ ደበበ ሰይፉ ምን ተፃፈ?
“ደበበ ሰይፉ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር ፕሬዝዳንት ሆኖ ከ1978 እስከ 1983 ዓ.ም
ድረስ ሰርቷል። ከዚህም በላይ በወቅቱ አያሌ የሙያው ባለቤቶች እንዲሰባሰቡ አድርጓል።
ከውጭ ሀገር በተለይም ከሶቭዬት ኅብረት ጋር ሙያዊ ድጋፍና ትብብር እንዲደረግ
አድርጓል። አንጋፋው ደራሲና ሃያሲ አቶ አስፋው ዳምጤ በአንድ ወቅት ስለ ደበበ የህይወት
ታሪክ ለሚያጠናው ተማሪ፣ ለተክቶ ታደሰ በሰጡት ቃለ-ምልልስ እንዲህ ብለዋል።
“ደበበ ስራ ይወዳል ስራው ጥንቅቅ ያለ ነው። ግን ሰዎችን ለመጋፈጥ ድፍረት ያንሰዋል።
ለቴአትር ዲፓርትመንት ከመከፈቱ ጀምሮ መጽሐፍ ጽፎላቸዋል። ፅንሰ ሃሳቡን እንዲረዱት
አድርጓል። ስለ ደበበ ካስደነቁኝ አንዱ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ችሎታው ነው። የደራሲያን
ማኅበር ሊቀመንበር ሆኖ እኔ ስራ አስፈፃሚ ሆነን ሠርተናል። ቀድሞ ከነበረው የማኅበሩ
የሥራ ዘመን ያልታየ እንቅስቃሴ ደረገ” የሚሉት አቶ አስፋው “እነሆ” የምትሰኘው
የአጫጭር ልቦለዶች መድብልና “ብሌን” የተሰኘችው መጽሔትም መታተሟን ያስረዳሉ።
“የጽጌረዳ ብዕር” የሚል የግጥም መድብል መታተሙንም አስረድተው የደበበን ጥንካሬ
ገልፀዋል።
ታዋቂው የወግ ፀሐፊ መስፍን ኃ/ማርያም ደግሞ ለአጥኚው እንዲህ ብሎ ነግሮታል።
“ደበበ በጣም ጠንካራ፣ ትጉህ ሠራተኛ፣ ለተሰለፈበት ዓላማ ወደኋላ የማይል፣ በማስተማር
ደበበ innovator /ፈጣሪ/ አይነት ነበር። የምናስተምረውን ኮርስ እንዲህ ብናደርገው፣
እንዲህ ብንለው እያለ ከጊዜ ወደ ጊዜ እንድናሻሽል በማድረግ በኩል ፈር ቀዳጅ ነበር።….
ደበበ ደራሲ ብቻ አይደለም። ጥሩ የማስተማር ችሎታ ነበረው” ብሏል።
ደራሲ ታደለ ገድሌም ሚያዚያ 29 ቀን 1992 ዓ.ም በወጣው “አዲስ ዘመን” ጋዜጣ ላይ
“ደበበ ሰይፉና ስራዎቹ ሲታወሱ” በሚለ ርዕስ ስለዚሁ ታላቅ ሰው አስነብቦናል።
ይህች ከተማ ነሐሴ 5 ቀን 1942 ዓ.ም ደበበን ያህል ታላቅ የኪነ-ጥበብ ሰው አፍርታለች።
አባቱ በጅሮንድ ሰይፉ አንተን ይስጠኝ እና እናቱ ወ/ሮ የማርያምወርቅ አስፋው የኢትዮጵያ
የኪነ-ጥበብ ዋልታ ያቆሙት በዚህች ምድር ነው። ደበበ ሰይፉን! ይርጋለም ከተማ ውስጥ።
“ይርጋለም
ዋ… ይርጋለም
የልጅነቴ ህልም ቀለም
ዓይኔን የከፈትሽው ጨረር
ወርቃማይቱ ጀንበር” ብሎ ደበበ ፅፎታል።
ዛሬ በህይወት የሌለው የስነ-ጽሁፍ መምህሩ ብርሃኑ ገበየሁ ትዝ አለኝ። ስለ ደበበ ሰይፉ
በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ሲፅፍ እንዲህ ብሏል። “የደበበ አቀራረቡ ቀላልና የማያሻማ
ነው። ድምፀቱ ደግሞ ሐዘን ከሰበረው ልብ የሚፈልቅ እንጉርጉሮ። የአቀራረብ ቀላልነት
ውበቱ ነው። ይርጋለምና ልጅነቱ በተናጋሪው ህሊና አንድም ሁለትም ናቸው፤ የማይፈቱ”
ብሏል። እናም ይርጋለም ደበበ ሰይፉ ናት!
ሌላኛው የስነ-ጽሁፍ መምህር የሆነው ወዳጄ ገዛኸኝ ጌታቸው፣ ደበበ ሰይፉ እንዳረፈ
በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ እንዲህ ብሎ ነበር። “ዛሬ የኢትዮጵያ ስነ-ጽሁፍ አንድ ለጋ ብዕር
አጣ፤ ነጥፎ አይደለም ታጥፎ ነው። ዛሬ የኢትዮጵያ ስነ-ጽሁፍ የዋህ ሃሳብ አጣ። ከፍቶ
አይደለም በኖ ተኖ እንጂ። ዛሬ ብዙዎቻችን ካወቅነው ብዙ ነገር አጣን። ካላወቅንም
እሰየው፤ ከእንጉርጉሮና ከፀፀት ተረፍን” ብሏል።
ጋዜጠኛ መሠረት አታላይ በፈርጥ መጽሔት ላይ “ለኪነ-ጥበብ ተፈጥሮ ለኪነ-ጥበብ
የሞተ” በሚል ርዕስ የደበበን ጓደኞች ዶ/ር ፍቃደ አዘዘን፤ መስፍን ኃ/ማርያምን እና
አስፋው ዳምጤን ቃለ መጠይቅ አድርጐ ጽፏል። ሁሉም የኪነ-ጥበብ ጋዜጠኞች ማለት
ይቻላል ስለ ደበበ ጽፈዋል። በ1995 ዓ.ም ደግሞ በጀርመን የባህል ተቋም ውስጥ በወ/ሮ
ተናኘ ታደሰ አስተባባሪነት ዶ/ር ፈቃደ አዘዘ፣ ዶ/ር ዮናስ አድማሱ እና ገዛኸኝ ጌታቸው
“የደበበ ሰይፉ ምሽት” ብለው እጅግ የደመቀ ዝግጅት አድርገዋል። ነብይ መኮንን፣ አበራ
ለማ እና አብርሃም ረታ ቅኔዎች ዘርፈውለታል። የወንዙ ልጅ አብርሃም ረታ እንዲህ
ገጥሞለታል፡-
ብናቀጣጥለው ኪነትክን እንደጧፍ
ስምህ ርችት ነበር
ላውዳመት እሚተኮስ
ሰማይ ላይ የሚጣፍ
ሰማይ ላይ የሚጦፍ
ሰማይ ላይ የሚጥፍ።
#ምንጭ ጥበቡ በለጠ
ውብ ቀን!💚
@getem
@getem
@balmbaras
#ከተባበርንእንችላለን!!
#ለጋሽነኝ
እዮብ ሰብስቤ
ሙሉአለም ታከለ ራህዋ ምን ያህል ራሱን ለጥበብ አሳልፎ የሰጠ ድምፃዊ መሆኑን ያወኩት ገና ሎሚ ሽታ የራዲዮ ፕሮግራሜ ላይ እንግድ ሆኖ ሊቀርብ ወደ ስቱዲዮ እየሄድን በነበረን ቆይታ ነበር፡፡ አዲሱ ስራዬን ስማው እስኪ አለኝ ሲበዛ ትሁት ነው ‹‹አምሮብሻል›› የተሰኘውን ዜማ ነበር ያኔ አልተለቀቀም ነበር፡፡ አዳመጥኩት፡፡ በወቅቱ የተሰማኝን ትክክለኛ ስሜት እና አሰተያየቴን ሰጠሁት ሀሳብ ሲቀበል ያስቀናል፡፡ ብዙ ጊዜውን አዲሱ አልበሙ ላይ እያጠፋ እንደሆነ ነገረኝ፡፡ አልበሙን አውጥቶ ህዝቡ ጋር ያለውን ስሜት ለማወቅ እንደጓጓ ፊቱ ላይ ያስታውቃል፡፡ ሙሌ ደስ በሚል ነፃነት ግጥም እና ዜማ የሰጣቸውን ድምፃዊያን እየነገረኝ ከኤፍሬም አማረ ጋርም ተሸንፌያለሁ ቁጥር ሁለትን ሊሰሩ እንዳሰቡ እያጫወተኝ ስቱዲዮ ደረስን፡፡ ፕሮግራሜን የምጀምረው አንተ ቀጥታ ከስቱዲዮ ሆነህ በምታዜመው ዜማ ነው ‹‹ተዘጋጅ›› አልኩት ታዛዥነት ደሙ ውስጥ አለ! በደስታ ‹‹ተሸንፌያለሁን›› ያለ ሙዚቃ መሳሪያ በድምጹ ብቻ አንጎራጎረው ድምፁ የሆነ ምትሀት አለው ሳታውቀው ኤሌክትሪክ የያዘህ እስኪመስልህ ይነዝርሀል፡፡ ሙሌ በቃ ይችላል!! በጣም በሳቅ የታጀበ ቆይታ አድርገን ተለያየን፡፡ ሙሉአለም ስላጋጠመው ህመም ድምጻዊ ደሜ ሉላ ከስቱዲዮ እየወጣን ተደውሎለት ነገረን በጣም ነበር የተረበሽነው፡፡ በቀጣይ ፕሮግራሜ ላይ ከጊልዶ ካሳ (በጣም መመስገን ያለበት ባለሙያ ነው ጊልዶ) ስለሙሌ አጠቃላይ ሁኔታ በስልክ ገብቶ ቆይታ አደረግን በወቅቱ ጊልዶ ካነሳቸው ሃሳቦች መካካል ሙሌን ለማገዝ የተቋቋመው ኮሚቴ ኮንሰርት ሊያዘጋጅ እንደሆነ ነበር በቃላቸውም መሰረት ‹‹ለጋሽ ነኝ›› የተሰኘ የሙዚቃ ኮንሰርት መስከረም 17 በሞዛይክ ሆቴል አሰናድተዋል፡፡ መደበኛ 300 ብር VIP 500 ብር የኮንሰረቱ መግቢያ ዋጋ ነው፡፡ አንድም በተወዳጅ ድምፃዊያን ስራዎች እየተዝናኑ አንድም ተወዳጁን ድምጻዊ ሙሉአለም ታከለ ራህዋን እያገዙ ጥሩ ጊዜ እንዲያሳልፉ ጥሪ ተላልፏል፡፡ ሙሌን ዳግም ሲስቅ እንድናየው እና ጤናው ተመልሶ የጓጓለት አልበሙንም አውጥቶ በጋራ እንድንደሰት አምላክ ይርዳን፡፡
#ከተባበርንእንችላለን!!
#ለጋሽነኝ
እዮብ ሰብስቤ
ሙሉአለም ታከለ ራህዋ ምን ያህል ራሱን ለጥበብ አሳልፎ የሰጠ ድምፃዊ መሆኑን ያወኩት ገና ሎሚ ሽታ የራዲዮ ፕሮግራሜ ላይ እንግድ ሆኖ ሊቀርብ ወደ ስቱዲዮ እየሄድን በነበረን ቆይታ ነበር፡፡ አዲሱ ስራዬን ስማው እስኪ አለኝ ሲበዛ ትሁት ነው ‹‹አምሮብሻል›› የተሰኘውን ዜማ ነበር ያኔ አልተለቀቀም ነበር፡፡ አዳመጥኩት፡፡ በወቅቱ የተሰማኝን ትክክለኛ ስሜት እና አሰተያየቴን ሰጠሁት ሀሳብ ሲቀበል ያስቀናል፡፡ ብዙ ጊዜውን አዲሱ አልበሙ ላይ እያጠፋ እንደሆነ ነገረኝ፡፡ አልበሙን አውጥቶ ህዝቡ ጋር ያለውን ስሜት ለማወቅ እንደጓጓ ፊቱ ላይ ያስታውቃል፡፡ ሙሌ ደስ በሚል ነፃነት ግጥም እና ዜማ የሰጣቸውን ድምፃዊያን እየነገረኝ ከኤፍሬም አማረ ጋርም ተሸንፌያለሁ ቁጥር ሁለትን ሊሰሩ እንዳሰቡ እያጫወተኝ ስቱዲዮ ደረስን፡፡ ፕሮግራሜን የምጀምረው አንተ ቀጥታ ከስቱዲዮ ሆነህ በምታዜመው ዜማ ነው ‹‹ተዘጋጅ›› አልኩት ታዛዥነት ደሙ ውስጥ አለ! በደስታ ‹‹ተሸንፌያለሁን›› ያለ ሙዚቃ መሳሪያ በድምጹ ብቻ አንጎራጎረው ድምፁ የሆነ ምትሀት አለው ሳታውቀው ኤሌክትሪክ የያዘህ እስኪመስልህ ይነዝርሀል፡፡ ሙሌ በቃ ይችላል!! በጣም በሳቅ የታጀበ ቆይታ አድርገን ተለያየን፡፡ ሙሉአለም ስላጋጠመው ህመም ድምጻዊ ደሜ ሉላ ከስቱዲዮ እየወጣን ተደውሎለት ነገረን በጣም ነበር የተረበሽነው፡፡ በቀጣይ ፕሮግራሜ ላይ ከጊልዶ ካሳ (በጣም መመስገን ያለበት ባለሙያ ነው ጊልዶ) ስለሙሌ አጠቃላይ ሁኔታ በስልክ ገብቶ ቆይታ አደረግን በወቅቱ ጊልዶ ካነሳቸው ሃሳቦች መካካል ሙሌን ለማገዝ የተቋቋመው ኮሚቴ ኮንሰርት ሊያዘጋጅ እንደሆነ ነበር በቃላቸውም መሰረት ‹‹ለጋሽ ነኝ›› የተሰኘ የሙዚቃ ኮንሰርት መስከረም 17 በሞዛይክ ሆቴል አሰናድተዋል፡፡ መደበኛ 300 ብር VIP 500 ብር የኮንሰረቱ መግቢያ ዋጋ ነው፡፡ አንድም በተወዳጅ ድምፃዊያን ስራዎች እየተዝናኑ አንድም ተወዳጁን ድምጻዊ ሙሉአለም ታከለ ራህዋን እያገዙ ጥሩ ጊዜ እንዲያሳልፉ ጥሪ ተላልፏል፡፡ ሙሌን ዳግም ሲስቅ እንድናየው እና ጤናው ተመልሶ የጓጓለት አልበሙንም አውጥቶ በጋራ እንድንደሰት አምላክ ይርዳን፡፡
#ከተባበርንእንችላለን!!