#ጥላዬ
ፊን-ፊን ስትይ ፥ በሰማዩ ጋሪ
ሽቦ የታደለ ፥ ዣንጥላ ወጣሪ
ጥበብ ከነ መርፌ ፥ መጨበጡን ረሳሽ
ያገው ጥላ መሰል
ከፍ ያልሽበት ሰማይ ፥ ለዝንት የዘረጋሽ።
ይልቅ ተመከሪ ፥ ገርነት አይግፋሽ
አውታርሽ መብዛቱ
ገትሮ የሚውል ፥ የሚጥል ቃሬዛ
አይምሰልሽ ዋዛ !!!
ዝናብ ካላስጣለ ፥ ሽንቁሩ እየበዛ
ፀሀይ ካልከለለ ፥ ማድያት ከነዛ
ማን ወዶ ሊጠለል ...ማን ስርሽ ሊገዛ
የከበበ ሳይሆን
ያስተዳደረ ነው ፥ እድሜ የሚገዛ።
ነሀሴ 2011
✍ #አብርሀም_ተክሉ
@getem
@getem
@getem
ፊን-ፊን ስትይ ፥ በሰማዩ ጋሪ
ሽቦ የታደለ ፥ ዣንጥላ ወጣሪ
ጥበብ ከነ መርፌ ፥ መጨበጡን ረሳሽ
ያገው ጥላ መሰል
ከፍ ያልሽበት ሰማይ ፥ ለዝንት የዘረጋሽ።
ይልቅ ተመከሪ ፥ ገርነት አይግፋሽ
አውታርሽ መብዛቱ
ገትሮ የሚውል ፥ የሚጥል ቃሬዛ
አይምሰልሽ ዋዛ !!!
ዝናብ ካላስጣለ ፥ ሽንቁሩ እየበዛ
ፀሀይ ካልከለለ ፥ ማድያት ከነዛ
ማን ወዶ ሊጠለል ...ማን ስርሽ ሊገዛ
የከበበ ሳይሆን
ያስተዳደረ ነው ፥ እድሜ የሚገዛ።
ነሀሴ 2011
✍ #አብርሀም_ተክሉ
@getem
@getem
@getem