ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
▶️ ሌላው መጽሀፍ ደግሞ <<ማሪሃም የተባልሽ የተመረጥሽ እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ አንቺን ደግሞ በጠላቶች አንገት #የብረት #ዛንጁር አግቢባቸው የመለከታቸውን ድምጽ #አክብጅው #ደንቆሮም አድርጊው እርሳቸውንም #በቀፎ #በቅርጫት በእግር ብረት #እሰሪያቸው በእግራቸው #ወጥመድ በከንፈራቸውም #ልጓም በአፍንጫቸው #ጉንፋን ላኪባቸው ሊሄዱበትም ወዳልፈቀዱበት መንገድ #መልሻቸው በልቦናቸውም #ፍርሃትን #መንቀጥቀጥን አሳድሪባቸው #መሸበርንና መንቀጥቀጥን ጨምሪባቸው #እንደሴቶች ይሁኑ። ከጽኑ ነፋስ ኃይል የተነሳ ዛፍ ሲንቀሳቀስ ቅጠሉ እንረዲረግፍ እንዲበተን እንዲሁ #ይሁኑ#በርሃብ #በቸነፈር #እህልን #በማጣት ቅሰፊያቸው፣ በሜዳ ሰይፍ ልጆቻቸውን #ያጥፋቸው በቤታቸውም ውስጥ #ፍርሃት ያስጨንቃቸው። #እሳት#በረዶ #ረሀብ፣ ቸነፈር ይፍጃቸው ይህ ሁሉ የእግዚአብሄር #የምጽአቱ #ጽዋ በጠላቶቼ ላይ ይውረድ እድል ፈንታቸው #ጽዋ ትርታቸው ይሁን[1]>>

▶️ እንግዲህ ይህ አይነቱ #ጸሎት #ክርስቶስና #ሐዋሪያቱ #ለገዳዮቻቸው እንኳ <<አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው>> ብለው ከጸለዩት ጋር ይጻረራል። ስለሆነም ይህ አይነት #ጸሎት #የበልዓም ትምህርት {የሰይጣን ትምህርት} እንጂ #የክርስቶስ #ትምህርትና #ጸሎት አይደለም [ዘኃ 22፥17 ፣ ራዕ 2፥14]። አንዳንዶች ለማስተባበል እንደሚሞክሩት <<ይሄ እርግማን ለሰይጣን ነው>> እንዳል እንኳን #አንደኛ <<የሚጠላኝን፣ የሚቃወመኝን ሰው..>> በማለት #ለሰውም ጭምር እንደሆነ ተጽፏል ሁለተኛ #ለሰይጣንም ቢሆን እንኳን እርሱ #መንፈስ ስለሆነ <<የሚለጎም አፍ፣ #ዲዳ የሚሆን #አንደበት፣ የሚዘጋ #ጉሮሮ#የሚደነቁር #ጆሮ፣ የሚቆረጥ #አንገት፣ የሚሰበር #ክንፍ የሉትም። ጌታ ኢየሱስም #አጋንንትን ከሰዎች ሲያስወጣ < #ውጡ!> ብሎ #ከመገሰጽና #ከማስወጣት በስተቀር [ማር 1፤ 25-27] #ዲዳ ሁኑ!፣ #ተቆረጡ!፣ #ተሰበሩ! አላለም። #ደቀመዛሙርቱም ቢሆኑ #አጋንንትን አውጡ ባላቸው መሰረት #በኢየሱስ ስም አስወጡ እንጂ [ማቴ 10፥8] #ቆራርጧቸው#ሰባብሯቸው#አደንቁሯቸው#ሽባ አርጓቸው አላለቸውም። እነርሱም #እርግማንና ሌላ #ቃላትን አልተጠቀሙም። ምክንያቱም ደሞ #አጋንንት #መንፈስ እንጂ #ሥጋዊ #አካላት የላቸውምና [ሐዋ 16፤ 16-18፣ ሉቃ 10፥17፣ ኤፌ 6፥12]። ጌታ በነገር ሁሉ #ማስተዋልን ያድለን [2ጢሞ 2፥7]።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
______________
[1] 📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ አርጋኖን ፤የእመቤታችን ምስጋና ዘሰኑይ፡ ገጽ 33-37፥ ተስፋ ገብረ ስላሴ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፥ 1989 ዓ.ም።

@gedlatnadersanat
(8.6.4▶️) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat