ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
🔽 ለምሳሌ፦
<ቅድስት ድንግል ማርያም> ትኖርበት በነበረበት #ዘመን #እስራኤል #በሮም #መንግስት #ቀኝ ግዛት ስር ስትሆን #ሄሮድስ በወቅቱ #የሮም መሪ ከነበረው <ከአንቶኒ[11]> #ድጋፍ አግኝቶ #በሮም ምክር ቤት <የአይሁድ ንጉስ> በሚል ስያሜ #እስራኤልን #ሲገዛ እንደነበር ይታወቃል። በወቅቱ #አይሁዳውያንም ጠልተውትና #በሮም መንግስት ስር መሆናቸውን #በመቃወም እስራኤል ሁከት የሰፈነባት፣ ጭካኔ የሞላባት፣ የእርስ #በእርስ መጠላላት እንኳን ሳይቀር የነገሠበት ጊዜ ነበር። #ንጉሥ #ሄሮድስም እጅግ #ጨካኝ ከመሆኑ የተነሳ #መንግስቴን #ይወርሱኛል ብሎ የጠረጠራቸውን <2 ሚስቶቹንና 2 ወንድሞቹንም> ሳይቀር #የገደለበት ጊዜ ነበር። #በዚህም #ምክንያት <ከ27 ዓ.ዓ እስከ 14 ዓ.ም> #የሮም ንጉሥ የነበረው <አውግስጦስ[12]> <<የሄሮድስ ልጅ ከመሆን አሳማ መሆን ይሻላል!!>> በማለት በግልጽ ተናግሮ ነበር። #ሄሮድስ #ሰብአ ሰገል የተወለደውን መሲህ #ኢየሱስን <የአይሁድ ንጉስ> ብለው #በመጥራታቸው ነገሩን በጥንቃቄ #መርምሮ #ኢየሱስ #ክርስቶስን ለመግደል ባደረገው ጥረት #በቤተልሔም ውስጥ በወቅቱ የተወለዱትን በጣም #ብዙ #ህጻናት #ከእናቶታቻቸው ጉያ በመንጠቅ #በሰይፍ #ቆራርጦአቸዋል። በዚህም #ምክንያት <በነብዩ በኤርምያስ> የተተነብየው [ኤር 31፤15-16] <ድምጽ በራማ ተሰማ ልቅሶና ብዙ ዋይታ ራሔል ስለልጆቿ አለቀሰች የሉምና መጽናናትን ስለልጆቿ እንቢ አለች> የተባለው ተፈጸመ[13] {ማቲ 2፤16}።

️ማርያም በዘመኗ ሁሉ ብርቱ #የመከራ #ዘመን እንደምታሳልፍ ተነግሯት ነበር [ሉቃ 2፤35]። #ሄሮድስ #ህጻናትን ሲያስገድል በወቅቱ #በመልአኩ #ምሪት #ማርያምና #ዮሴፍ ህጻኑን (ኢየሱስ ክርስቶስን) ይዘው ወደ #ግብጽ ተሰደዋል። #ሄሮድስም እንደ #ሞተ ሰምተው ቢመለሱም #ልጇ #ኢየሱስ ክርስቶስ ባሳለፈው #ህይወትና #ሲሰቃይ ማየቷ #በእንጨት ላይም #ሲሰቅሉት #ማየቷ በአጠቃላይ እንደ ስሟ #ዘመኗ <መራራ ዘመን> ሆኖባታል።

️ በመሆኑም #ማርያም የተባሉ ሁሉ በተመሳሳይ #ሁኔታ #ዘመናቸው #መራር የሆነባቸው #ሰዎች ነበሩ እንጂ ከላይ አንዳንዶች እንደተረጎሙት የተለያየና፣ የተሳሳተ #ከእውነትም #የራቀ አልነበረም። እነዚህ መተርጉማን ስለማርያም የሰጡት ሃተታ #ቋንቋውንና #ታሪካዊ ዳራውን ያላገናዘበ፣ ከልዩ #ባእድ #አምልኮ መሻት #የመነጨና #ከእውነት የራቀ ብቻ ነው።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4፥6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
______________
[1] 📚፤ የኢትዮጵያ መጽሀፍ ቅዱስ ማህበር "የመጽሀፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት" 8ተኛ እትም 1998 ዓ.ም *ገጽ 51።

[2] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ ውዳሴ ማርያም ንባቡና ትርጓሜው፤ ዘሠሉስ *ገጽ 45። ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ 1983 ዓ.ም።

📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ <ወንጌል ቅዱስ ንባቡና ትርጓሜው>፤ ዘሉቃስ ፧ *ገጽ 265፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ 1997 ዓ.ም።

📚፤ <ነገረ ማርያም> *ገጽ 28-31። ተስፋ ገብረ ሥላሴ ማተሚያ ቤት፤ 1991 ዓ.ም።

📚፤ ብርሃኑ ጉበና "አምደ ሃይማኖት" *ገጽ 91። 1985 ዓ.ም።

📚፤ ሚልዮን በለጠ አሰፋ፤ <ቅዱሳት ስዕላት አመጣጥና ታሪክ ከትምህርተ ሃይማኖት ጋር> ፤ *ገጽ 25-26። 1994 ዓ.ም።

[3] 📚፤ <ነገረ ማርያም>፤ *ገጽ 28-30፤ ተስፋ ገብረ ስላሴ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ 1991 ዓ.ም።

[4] 📚፤ ሚሊዮን በለጠ አሰፋ
"ቅዱሳን ሥዕላት አመጣጥና ታሪክ ከትምህርተ ሃይማኖት ጋር" *ገጽ 26። አለም ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፤ መጋቢት፥ 1994 ዓ.ም።

📚፤ <ነገረ ማርያም> ፤ *ገጽ 29፥ ተስፋ ገብረሥላሴ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ 1991 ዓ.ም።

[5] 📚፤ ተአምረ ማርያም፤ መቅድም ቁ.4 *ገጽ 3፤ 3ተኛ ዕትም፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት አ.አ፤ 1989 ዓ.ም።

📚፤ <አርጋኖን> የእመቤታችን ምስጋና፤ ዘሰኑይ ምዕራፍ 6 ክፍል 4፤ ተስፋ ገብረሥላሴ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ 1996 ዓ.ም።

[6] 📚፤ ነገረ ማርያም፤ *ገጽ 34

[7] 📚፤ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ፤ <ማርያም>፤ *ገጽ 610፤ አርቲስቲክ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ 1948።

📚፤ Dr. Strong፥ "Exhaustive Concordance of the Bible" HEBREW AND CHALDEE DICTIONARY፥ pp 72 no.4805፣ 4813

〽️ https://en.m.wikipedia.org/wiki/Miriam_(name)

[8] 📚፤ የኢትዮጽያ መጽሀፍ ቅዱስ ማህበር፤ <የመጽሀፍቅዱስ መዝገበ ቃላት>፤ 7ኛ እትም፤ <ዩሐንስ> *ገጽ 222። ንግድ ማተሚያ ቤት፥ አ.አ 1996 ዓ.ም።

📚፤ Douglas & Tenney by International Bible Society Bible Dictionary፤ John pp. 532, 1987።

📚፤ Truesdale, Lyons, Eby clark, A Dictionary of the Bible & Christian Doctrine in every day English, United Bible Societies, 1978፥ pp 155-156.

[9] 📚፤ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መጽሀፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ፤ <ማርያም> የስም ትርጉም። *ገጽ 610፥ 1948 ዓ.ም።

[10] 📚፤ አለቃ ደስታ ተክለወልድ፤ መጽሀፈ ሰዋሰው ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ፡ <ማርያም>፤ *ገጽ 808 1ኛ ዕትም፥ 1945 ዓ.ም።

[11] 〽️ https://en.m.wikipedia.org/wiki/Mark_Antony

[12] 〽️ https://en.m.wikipedia.org/wiki/Augustus

[13] 📚፤ S I M፤ <የአዲስ ኪዳን ታሪካዊና ባህላዊ መሰረቶች> ፥ *ገጽ 22-23፤ ኤስ አይ ኤም ማተሚያ ቤት፥ አ.አ፤ 1993 ዓ.ም።

(2.1▶️ጥያቄ) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat
▶️ በኢትዮጽያ #የማርያም #ስዕል አመጣጥ #የረጅም ጊዜ #ታሪክ ባይኖረውም #በአጼ #ዳዊት #ዘመነ #መንግስት [በ1365-1395 ዓ.ም] <<ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጽያ ወንጌላዊ ሉቃስ የሳላት የማርያም ስዕል መጣች>> በማለት ለመጀመሪያ ጊዜ #የሥዕል #በር ተከፈተ[8]።

▶️ በ14ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ #የአፄ ዘርዓ ያቆብ ቤተሰቦች #የፊተኛው ልጃቸው ስለሞተባቸው ገና #ሳይወለድ እያለ <<ተወልዶ በጤና ካደገ ለቅድስት ድንግል ማርያም እሰጠዋለው>> ብለው #በስእሉ ፊት ያልተለመደ #ጸሎትና #ስለት አቀረቡ[9]። ይህንንም #ስለት አይነት በተደጋጋሚ ሲሰማ ያደገው #ዘረዓ ያዕቆብ #ስልጣኑን {አፄነቱን} ሲረከብ #ስእሎችን #በከፍተኛ ሁኔታ #እንዲስፋፉና #እንዲሰገድላቸው #የማርያም #ስእልም [ስእለ አድህኖ] ተብሎ እንዲሰየም አደረገ። በዚህም 2ተኛው #ቆስጠንጢኖስ እንዲባል አስችሎታል[10]።

▶️ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ #በሙዚየም በኢትዮጵያ ስላሉ #ስነ ስዕላት አስመልክቶ የሚከተለውን አስፍሯል።

<<በሰሌዳ ላይ (በእንጨት በጨርቅ በብራናና በመሳሰሉት) የመሳል ጥበብ በኢትዮጵያ የተጀመረው በ15ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ እንደሆነ ይገመታል ከዚህ ዘመን በፊት የተሳሉ አንዳንድ የሰሌዳ ላይ ስዕሎች እስካሁን ድረስ አልተገኙም። የታሪክ ተመራማሪዎች እንደሚሉት {ስዕላተ አስህኖ} ድንገት ብቅ ያሉት በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ [1434 እ.አ.አ] ዘመን እንደሆነና ይህም የሆነበት ምክንያት ንጉሱ ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም ከነበረው ልዩ እምነትና ፍቅር ጋር የተያያዘ ነው ይላሉ። ከዚህም የተነሳ በኢትዮጵያ ውስጥ "የስእላተ አድህኖ" ምስሎችን ማክበር በእርሱ መታመንና የስዕላቱ ተፈላጊነት እያደገ የመጣው ከእሱ ዘመነ መንግስት ወዲህ ነው። . . . የዘመኑ ዝነኛና ታዋቂ ሰዓሊ አባ ፍሬ ፅዮን የሚባል መነኩሴ ነበር። የእሱ ልዩና ፈር ቀዳጅ ስልት በዘመኑ የኢትዮጵያ የስነ ስዕል ጥበብ ላይ በእጅጉ ተጽኖ አድርጓል። በ15ኛው ክፍለ ዘመን 2ኛ አጋማሽ በአማራው ሃገር እና በሸዋ የተሳሉ ብዙ የሰሌዳ ስዕሎች ላይ እና በዚያ ዘመን በተሰሩ መስቀሎች ላይ የእሱ ስልት በእጅጉ ተንጻባርቆ ይገኛል።>>

▶️ ሥዕላት የተስፋፉት #ከውጪ ዓለም በተለይም #ከኢየሩሳሌምና #ከካይሮ እንዲሁም #በጣሊያን ሃገር ከምትገኘው #ከቪኒስ እና ከሌሎች #ከተሞች ጋር በተመሰረቱት ግንኙነቶች አማካኝነት ነው። ከእነዚህም በተጨማሪ #የኢትዮጽያ #ሰዓሊዎች #የቤዛንታይን #አሳሳል #ስልትንም በማጥናት የራሳቸውን #አዳዲስ #ስልቶች አዳበሩ።

<<ኢታሎ-ክሬታን>> የሚባለው #ስልተ አሳሳል ደግሞ #የእሬታ #ሰዓሊዎች #የቢዛንታይን #ስልት በመጠቀም #የኢጣልያንም #የስዕላተ #አድህኖ ይዘት #በስዕል የገለጹበት ነው። #ብራንካሎዮን የተባለው ታዋቂው #የቪኒስ #ሰዓሊ ኢትዮጵያ ውስጥ #ለ40 ዓመት በኖረበት ጊዜ #የ15ኛው ክፍለ ዘመን #የኢትዮጵያ አሳሳል #ሂደት እና #እድገት ላይ #ታላቅ #አስተዋጽኦ አድርጓል። በኢትዮጵያም ውስጥ #የጣሊያን #የአሳሳልን #ስልት ያስገባው ይኸው #ሰዓሊ ነው። በዚህ #ጣሊያናዊ #ሰዓሊ የተከናወኑት #ስዕሎች #የካትሮችንቶ አሳሳል ጥበቡን #ባህሪያት #ያንፀባርቃሉ

. . . በኢትዮጵያ #የስዕል ጥበብ ላይ ሌላኛው #የውጭ #አስተዋጽኦ የመጣው #በ17ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ 30 #ዓመታት ወደ #ኢትዮጵያ ከገቡት #ኢየሱሳውያን {ጆስዊታስ}[11] አማካኝነት ነው።

▶️ በኢትዮጵያ ውስጥ ከነበረው #ባህላዊ #የእመቤታችን #ስዕለ #አድህኖ አሳሳል በተጨማሪ <<የማጆ ወሬ ማርያም>> {በሮማ ከተማ ውስጥ የምትገኝ ቤተክርስቲያን} #አሳሳል #ስልት ገባ። ዋነኛው #የጣሊያን #ስዕል ለብዙ #ምዕተ አመታት #ሮማ #ከተማ ይቀመጥ ነበር። #በ1596 እ.ኤ.አ #ኢየሱሳውያን #የሮማውን #ሊቀጳጳሳት በማስፈቀድ #የዋንኛውን #ቅጅ #ስዕሎች በመላው #ዓለም ሊሰብኩ ወደሄዱባቸው #አገሮች ሁሉ ወሰዱ። በዚህ መሰረት #ኢትዮጵያ ውስጥ #ገባ። ከዚያን ጊዜ ወዲህ #የማጆሬዋ #ማርያም #ስዕል <<ምስለ ፍቅር ወልዳ>> ተሰኝቶና #በማርያም ተሰይሞ #በኢትዮጵያ #ጥናትና #ምርምር #ተቋም ከሚገኙት #ስዕላተ #አድህኖ ውስጥ አብዛኛውን ይኸው <<ምስለ ፍቅር ወልዳ>> የተባለው ነው።
@gedlatnadersanat