ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
<< #እግዚአብሔር የመረጣቸውን #የሚከሳቸው ማነው? #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር ነው>> ሮሜ8:33 አለ። < #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር ነው>> አለ። #እግዚአብሔር #የሚያጸድቀው #እነማንን ነው? አግዚአብሔር #የሚያጸድቀው እሱ #የመረጣቸውን ነው። እሱ < #የጠራቸውን እነዚህን #አጸደቃቸው> ሮሜ8:30 እግዚአብሔር #የመረጣቸውን እሱ ራሱ #የሚያጸድቃቸው ከሆነ እንግዲህ በእነዚህ ምርጦች ላይ ክስ ማንሳት…
🔽▶️

*⃣ #ሮሜ 8፥34 እና #የመናፍቃኑ እርስ በእርስ አለመግባባት፦

‹‹ #የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ #በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ #የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው›› (ሮሜ 8፡34)፡፡

#በልማድ ለያዙት #የተሳሳተ ትምህርት አልመች ያለውና #በምንፍቅና #ጎዳና ላይ ሆነው #የአዳኛችንን #የኢየሱስ ክርስቶስ #የማዳን ግብር የሆነው #የምልጃ ሥራውን ሽምጥጥ አድርገው #በመካድ ላሉት #ሰዎች ይህ #ጥቅስ #ራስ ምታት ሆኖባቸው ይታያል፡፡ ከዚህም የተነሳ #ቤተክርስቲያኗ ይህን ጥቅስ " #የሚፈርድ ማን ነው? የሞተው፥ ይልቁንም #ከሙታን ተለይቶ የተነሳው፥ በእግዚአብሄር ቀኝ የተቀመጠው፥ ደግሞም " #ስለእኛ #የሚፈርደው" ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" በሚል አስቀምጣዋለች።
📖 2000 እትም 80 አሀዱ መጽሀፍ ቅዱስ
ለዚህም ደግሞ እንደ #ምክንያት የቀረበው " #የሚማልደው የሚለው ከጊዜ ቡሀላ #መናፍቃን #የጨመሩት ነው እንጂ ቀደም ሲል የነበረው #የግእዙ ትርጉም #የሚፈርደው ነው የሚለው" የሚል ነው።" ይህንንም ተከትሎ ብዙዎች የተለያዩ #ምክንያቶችንና ማስተባበያዎችን ለማቅረብ ሞክረዋል። እስኪ #ከብዙዎች አንዳንዶቹን እንያቸው፤

〽️1፦ ‹‹የጠራው #የግእዙ #የመጽሐፍ ቅዱስ #ኀይለ ቃል ተለውጦና #በዘመናት ሁሉ ለዚህች #ቤተ ክርስቲያን መቼም ቢሆን #መልካም ዐስበው በማያውቁ ይልቁንም #ፈራርሳ #ቢያይዋት ደስ በሚሰኙ #የክርስቶስን #ፈራጅነት በካዱ #በባሕር ማዶ #ቀሣጪዎች ብዙ ጊዜ #ተሰርዞ #ተቀይሮ ይገኛል›› የሚል #አስተያየት ይሰጣሉ። ለዚህም #በ1938 በፊላደልፊያ የታተመው #መጽሀፍ ቅዱስ፣ #በ1975 #በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጊዜ " #ከግእዝ ወደ ዐማርኛ" የተመለሰው ዐዲስ ኪዳን(በግዕዝና በአማርኛ የታተመውን)፣ #በ1953 #በአሥመራ የታተመው ዐዲስ ኪዳን እና #በ1938 የታተመው #የዐማርኛ #ዐዲስ ኪዳን #መጻህፍትን ይጠቅሳሉ።
📖/፤ ሮዳስ ታደሰ (መጋቤ ዐዲስ)፣ ነገረ ክርስቶስ - ክፍል አንድ (የካቲት 2008)፤ ገጽ 479
📖/፤በርሀ ተስፋ መስቀል (መምህር)፣ "አንባቢው ያስተውል" (መቕለ፣2005) ገጽ 33 የግርጌ ማስተወሻ።
📖/፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምዕመናን የቅዱስ እስጢፋኖስ ጉባኤ፤ ፍኖተ ብርሃን(ጥቅምት 1990) ገጽ 51።
( #ደስታ ተክለ ወልድ፤ ዐዲስ ያማርኛ መዝገበ ቃላት
"ቀሠጠ"፦ #በስውር ከፍሎ ሰረቀ፣ #ወሰደ#ዐበለ
"ቀሣጢ"፦ #የቀሠጠ#የሚቀሥጥ ዐባይ #ሌባ፤ ብሎ ያስቀምጠዋል(ገጽ 1093)። በዚህ ትርጉም መሰረት ጸሀፊው " #ቀሣጢዎች" ሲሉ " #የሰውን ነገር #የሚወስድ#የሚሰርቅ#ሌባ ለማለት መሆኑን ልብ ይሏል።)

▶️ #በዚህ ጽሑፍ መሠረት " #ይማልዳል የሚለው #መናፍቃን #የጨመሩት እንጂ ትክክለኛ #ትርጉም አይደለም፡፡" ነገር ግን ጸሐፊው ማስተዋል የተሣናቸው #ሐዋርያው #ግእዝ #የጽሑፍ ቋንቋ ባልነበረበት ዘመን ይህን #መልእክት #ለሮሜ ሰዎች #የላከ መሆኑን ነው፡፡ ሐሳቡን #ግልጽ ለማድረግ ይህ #መልእክት #ወደ ሮሜ ሰዎች ሲላክ #ግእዝ ለጽሑፍ #የማይመችና #አናባቢ የሌለው #ቋንቋ ነበር፡፡ በዚህም #ምክንያት #ግእዝ #የሮሜን #መልእክት ለማስተናገድ #አቅም #አልነበረውምና #በግእዝ የተጻፈውን #ምንጭ ማድረግ #የተበከለ #ምንጭ እንደ #መጠጣት ይሆናል፡፡ ስለዚህ ማንም ብልህ አንባቢ #ቀዳሚውን #ምንጭ መፈለግ ግድ ይለዋል።
ግሪኩ እንዲህ ይላል..

τίς ὁ κατακρινῶν ? Χριστὸς Ἰησοῦς ὁ ἀποθανών , μᾶλλον δὲ ἐγερθείς (ἐκ νεκρῶν) ὅς ‹καί› ἐστιν ἐν δεξι το Θεο ὃς καὶ #ἐντυγχάνει(ኢንቲጋኬኖ) ὑπὲρ ἡμῶν /ሮሜ 8፥34/

*⃣" #entugchanó"፦
to chance upon, by impl. confer with, by ext. entreat
Original Word፦
#ἐντυγχάνω
Part of Speech፦
#Verb
Transliteration: #entugchanó
Phonetic Spelling፦
( #en-toong-khan'-o)
Short Definition፦
I meet, encounter, call upon, to chance upon, confer with, to #entract(in favor or against), deal with, make a #petition, make #intercession
📖/፤ STRONGS GREEK DICTIONARY OF THE NEW TESTAMENT፤ pg 29. No.1793)

👉 http://biblehub.com/greek/5241.htm

👉 https://www.biblestudytools.com/lexicons/greek/nas/entugchano.html

ከተለያዩ የግሪክ ቅጂዎችም ስናይ፦ 👇
http://biblehub.com/texts/romans/8-34.htm

Nestle Greek New Testament 1904

τίς ὁ κατακρινῶν; Χριστὸς Ἰησοῦς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ ἐγερθείς, ὅς ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ Θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

Westcott and Hort 1881

τίς ὁ κατακρινῶν; Χριστὸς Ἰησοῦς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ ἐγερθεὶς ἐκ νεκρῶν, ὅς ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν·

Westcott and Hort / [NA27 variants]

τίς ὁ κατακρινῶν; Χριστὸς Ἰησοῦς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ ἐγερθεὶς (ἐκ νεκρῶν), ὅς [καί] ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν·

RP Byzantine Majority Text 2005

τίς ὁ κατακρίνων; Χριστὸς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ καὶ ἐγερθείς, ὃς καὶ ἔστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

Greek Orthodox Church 1904

τίς ὁ κατακρινῶν; Χριστὸς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ καὶ ἐγερθείς, ὃς καὶ ἔστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ Θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

Tischendorf 8th Edition

τίς ὁ κατακρινῶν; Χριστὸς Ἰησοῦς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ ἐγερθείς, ὃς ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

Scrivener's Textus Receptus 1894

τίς ὁ κατακρίνων; Χριστὸς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ καὶ ἐγερθείς, ὃς καὶ ἔστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ Θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

Stephanus Textus Receptus 1550

τίς ὁ κατακρινῶν Χριστὸς ὁ ἀποθανών μᾶλλον δὲ καί ἐγερθείς ὃς καὶ ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ θεοῦ ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

@gedlatnadersanat
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
Photo


#ስለዚህም ይህ " #መናፍቅ #የጨመሩት ነው" የሚለው ንግግር ሆን ብሎ ሰውን ለማሳሳት #የተፈጠረ መላምት ነው ከማለት ያለፈ ሊባል የሚቻለው ሌላ ነገር የለም። ይህ ራሱ #የአንዳንዶች #የማታለያ #ዘዴ ብቻ ነው እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቃሉ #እውነት እንደሆነ #ከጥንትም እንደነበረ ራሳቸውም ማመናቸው ተራጋግጧል።
ለምሳሌ፦
#ማኅበረ ቅዱሳን #ለተሐድሶ መልስ እሰጥበታለሁ ብሎ በለቀቀው ድምፅ ወምስል (ቪሲዲ) ላይ " #ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ" ይህን ጥቅስ በተመለከተ ‹‹ #ስለ እኛ #የሚማልደው የሚለው ቃሉ አለ፤ #ከጥንቱም #ከግሪኩ አለ›› የሚል #አስተያየታቸውን መስጠታቸውን መመልከት ይቻላል፡፡
(ማኅበረ ቅዱሳን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እናድሳለን ብለው የተነሡ ፕሮቴስታንቶች በሚያነሧቸው ጉዳዮች ላይ የተሰጠ መልስ 2ኛው ድምፅ ወምስል፣ (መስከረም 2010)፣ 8፡11-8፡15 ደቂቃ፡፡)

ዞሮ ዞሮ ይህም የሆነው #እውነትን ደብቆ #መቀመጥ ስለማይቻል ብቻ ነው። ከዚህም በተጨማሪ #አባቶቼ እያሉ የሚጠሯቸው ፣ #መታሰቢያም የሰሩላቸው #አባቶች ይህን ቃል የተረዱት የዛሬዎቹ አንዳንድ መምህር ተብዬዎች ከሚያስቡት በተቃራኒ ነው።
@ ለምሳሌ፦
#ዮሐንስ አፈወርቅን ብንመለከት #የሮሜ መልእክትን በተረጎመበት
/" #ድርሳን 15" ይህን ቃል #እንደወረደ ተጠቅሞታል።
እንዲህ ብሏል ፦
<< #ቅዱስ ጳውሎስ " #ስለ እኛ #የሚማልደው"ብሎ #ለሥጋ እንደሚገባ አድርጎ የተናገረው #ፍቅሩን #ይገልጽ ዘንድ #በታላቅ #ትህትና የገለጸው ነው>>
ብሎ ጽፏል።
#አስተውሉ #ዮሐንስ #አፈወርቅ #የጳውሎስ ጹሕፍ ምን እንደነበረ
#ሲገልጽ እነመለከታለን።
#ጳውሎስ " #የሚማልደው"ብሎ እንደጻፈ ይህም የክርስቶስን #ትሕትና እና #በሥጋው ወይም #በሰውነቱ #አንጻር #የተነገረ እነደሆነ እና #ጌታ ለእኛ ያለውን #ፍቅር #ለሚያስረዳት የተጻፈ #መሆኑን ገልጿል።
አስተውሉ!!
#ዮሐንስ አፈወርቅ #መናፍቅ ነበር እንዴ? ነው ወይስ
#የመናፍቃንን #መጽሐፍ ቅዱስ
ነው የተረጎመው? ነው ወይስ
#እናንተ #አባታችን ከምትሉት #ዮሐንስ አፈወርቅ #ትበልጣላችሁ? ነው ወይስ
#ተሳስቶ ነበር? ምንድን ነው #የምትመልሱት?
*
#ይህም ብቻ አይደለም የክርስቶስ #አማላጅነት #ከአብ #ያንሳል ማለት እንዳልሆነ
፣እኛን ለመርዳት አቅም ስለሌለው #መለመን አስፈልጎት እንዳልሆነ ነገር ግን
ለእኛ ያለውን #ፍቅር ለማሳየት እንደሆነ ገልጿል።
#ይህን ቢገልጽም #የጳውሎስን
#ቃል #መናፍቃን #የጨመሩት ነው አላለም።
ነገር ግን ከጳውሎስ #የሰማውን ቃል #እርሱም ተቀበሎ እየደጋገመ ይናገረዋል ።
ለምሳሌ ፦

<< #ክርስቶስ አሁን #በክብሩ #የሚታይ ቢሆንም #ርኅራኄውን ከእኛ #አላራቀም #ስለእኛ
#ይማልዳል #እንጅ>>


<< #እንግዲህ #መንፈስቅዱስ ራሱ #በማይነገር #መቃተት #የሚማልድልን ከሆነ #ኢየሱስም #ሞቶ #የሚያማልደን ከሆነ #አብም #ለአንተ ሲባል #ለልጁ #ካልራራለት #አንተን #ከመረጠህ #ካጸደቀህ ከዚህ ሌላ በምን #ትፈራለህ?>>


<< #እግዚአብሔር #ዘውዱን አቀዳጅቶናል። #የሚኮንነንስ #ማነው? #ክርስቶስ #ሞቶልናል #መሞት ብቻ አይደለም ከዚህም በኋላ #ለእኛ #ስለሚማልድ ማን
#ይኮንነናል? >>
📖/፤ ሐመረ መጽሄት ሐምሌ 2007 ገጽ 10
በማለት ያብራራዋል።
#ለመሆኑ > #ዮሐንስ #አፈወርቅ< እንዲህ እየገለጸው እያለ
#መናፍቃን #የጨመሩት ነው #የምትሉት ከየት አምጥታቹ ነው? እናንተ #ሰዎች ሆይ #ከስህተታችሁ ታረሙ።
#ይህ " #ዮሐንስ #አፈወርቅ" ዕብራውያን 7:25ን በተረጎመበት ድርሳን 13 ላይ
የሮሜን መልእክት ለማስረጃ ጠቅሶታል።
ሮሜ8:34 ላይ የተጻፈውና ዕብ7:25 ላይ የተጻፈው ቃል #ተመሳሳይ እንደሆነ ያስረዳል። ይህ ዮሐንስ አፈወርቅ
#የክርስቶስን #አማላጅነት #ከፍቅር #አንጻር ይመለከተዋል ለምሳሌ፦
ዮሐ17:9-21
ያለውን #የጌታን #ምልጃ እንዲህ ገልጾታል ፦
*
<< "I pray not that You should take them out of the world, but
that You should keep them from the evil."
Again He simplifies His language; again He renders it more
clear; which is the act of one showing, by making entreaty
for them with exactness, nothing else but this, that He has a
very tender care for them. Yet He Himself had told them,
that the Father would do all things whatsoever they should
ask. How then does He here pray for them? As I said, for
no other purpose than to show His love .>>
በማለት የጸለየው የፍቅር መገለጫ መሆኑን በድርሳን 82 ገልጾታል ።
ራሱን ያለምስክር የማይተው ጌታ በእነዚህ ሰዎች ሞስክር አአስቀምጧል ።

እንግዲህ መጀመሪያ #በግሪክ የጻፈው #ሐዋርያ ስለእኛ #የሚማልደው ካለ አባቶቻችንም ይህንን #እውነት ካጸኑልን ታድያ ይህንን #በመንፈስ ቅዱስ በተሰጠ #ሐዋርያዊ ስልጣን የተጻፈን ቃል #የመለወጥ ስልጣን ያለው አለን? #ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን #እንመን? #ወይስ #እነርሱን?
አስቡበት!!

#ይህም ብቻ ሳይሆን ‹ #ስለ እኛ #ይፈርዳል› ተብሎ የተተረጐመው ቃል #ስሕተት የሆነው ንባቡ በመተርጎሙ ብቻ ሳይሆን፤ #በሕገ #ሰዋስው መሠረት ሲታይ ሐረጉ #በዐረፍተ ነገሩ ውስጥ እንዲገልጽ #የተፈለገውን ሐሳብ ስለማይገልጽና ሌላ #ትርጕም ስለሚሰጥም #ጭምር ነው እንጂ፡፡ በዐማርኛ ሰዋስው ‹ #ስለ እኛ ይፈርዳል› የሚል ንባብ " #ለእኛ ይፈርዳል› ወይም " #በእኛ ይፈርዳል" የሚል #ትርጕም ሊሰጥ አይችልም፡፡ የሚሰጠው #ፍቺ በእኛ ምትክ፣ #እኛን #ወክሎ #ይፈርዳል የሚል ነው፡፡ ይህ ደግሞ ቃሉን የለወጡት ሰዎች ቃሉ እንዲናገርላቸው የፈለጉትን ‹ #ለእኛ ይፈርዳል› ወይም " #በእኛ ይፈርዳል" የሚለውን #ሐሳብ አይጠራላቸውም፡፡ እንዲያውም ያልጠበቁትን #ትርጕም ይሰጥባቸዋል፡፡ የተፈለገውን #ትርጕም ይሰጥ ዘንድ ‹ #ስለ› የሚለው መስተዋድድ #ይፈርዳል ከሚለው ግስ ጋር ሳይሆን #ይማልዳል ወይም #ይከራከራል ከሚለው #ግሥ ጋር ነው ሊሄድ የሚችለው››፡፡

ይቀጥላል..(ሮሜ 8፥34)
@gedlatnadersanat @teeod