❝...#ጌታ_ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያንን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።❞
ያዕቆብ 4: 15
ክፍል 1
ሰላም ወዳጆች...
እንዴት ነው ?
ዓመቱ እንዴት እየተጠናቀቀ ነው?
እግዚአብሔር ፈቅዶ 2014 ዓ.ም ዘመነ ማርቆስን ለማገባደድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ቀርተውናል ። እስቲ ዘወር ብለን ያለፈውን ጊዜያቶች እንዴት እንዳሳለፍን እንመርምር። መመርመር በጥያቄ ይጀምራል እና ይህንን ልጠይቅ... !
ስንቱን አተረፍንበት.... ?
ስንቱን ከሰርንበት.... ? ለምን ?
ስንቱንን በሚጠቅመን ነገር አሳለፍንበት ...?
ስንቱን በማይጠቅም ነገር አሳለፍንበት.... ? ለምን?
ምን ያህሉን ጊዜ አዲስ ዕውቀት ለመጨመር ተጋንበት ?
ስንት መጽሃፍትን አነበብን ? ስንቱን ኖርነው ?
በዚህ ዓመት ልንፈጽመው #ካቀድነቸው ነገሮች ውስጥ ምን ያህሉን አሳካናቸው ? ምን ያህሉን አላሳካነውም? ለምን ?
ከሁሉም ከሁሉም ግን ወሳኙ ጥያቄ ምን ያህሉን ጊዜ ለእግዚአብሔር ሰጠነው ? ምንያህሉን ጊዜ ከእግዚብሔር ጋር ተገናኘንበት ? የሚለው ነው ?
በእርግጥ ይህንን ጥያቄ ሙሉ ለሙሉ ለመመለስ ጊዜ ቢያስፈልገውም እንዲው የግምገማ ጊዜ ቢኖረን ከሚል ወንድማዊ ፍቅር ጠየኩኝ ። በእርግጠኝነት መናገር የምችለው ግን ለሁሉም ላላሳካነቸው ነገሮች ያሳምንም አያሳምንም ? ይብዛም ይነስም አዕምሮአችን ምክንያት ይሰጠናል ።
#ንግባኬ_ሀበ_ጥንተ_ነገር እንዲል ሊቁ ወደ ቀደመ ነገሬ ስመለስ ከላይ ላሉት ጥያቄዎች ለምን ሙሉ ለሙሉ ማሳካት አልቻልኩም ብለን ስንጠይቅ መልሱ ወደ አንድ ነገር ያመራናል ።
የጊዜ አጠቃቀም እና ምክንያታዊነት!
ስለ ጊዜ አጠቃቀም በሌላ ርዕስ ብመለስበት ስለሚሻል ስለ ምክንያታዊነት ይህንን ልበል! ቅዱስ መጽሀፍ እንደሚያስተምረው ለየትኛውም ስንፉናችን ምክንያት ሊያድነን አይችልም።
❝እኔ መጥቼ ባልነገርኋቸውስ ኃጢአት ባልሆነባቸውም ነበር፤ አሁን ግን ለኃጢአታቸው #ምክንያት የላቸውም።❞ ዮሐንስ 15: 22
ጌታችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲያስተም ስላደረገው ተዓምር እስራኤላውያን እንዳይሰናከሉ አንድም ለሰው ልጅ ተዐምራቱ ላይ እንዳንሰናከል ምክንያትን ለማስወገድ አንድን ተዐምር በአራት ወንጌላውያን ሲያስመሰከር ሲያጽፍ እንገኘዋለን። ይህም ተዐምር...
• ቅዱስ ማቴዎስ... ቦታው የተመቸ (ሳር እና ለምለም) እንደነበር ይገልጣል። ለምን ይህንን መግለጥ አስፈለገው ቢሉ አይሁዳውያን ቦታው አልተመችንም ስለዚህም አልበላንም እንዳይሉ!
ማቴዎስ 14 :19
ሕዝቡም #በሣር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፥ አምስቱንም እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ወደ ሰማይ አሻቅቦ አየና ባረከ፥ እንጀራውንም ቆርሶ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ።
• ቅዱስ ማርቆስ ደግሞ ቦታው ምድረ በዳ (ከከተማ ወጣ ያለ ስፍራ) እንደነበር ይገልጻል ። ለምን ይህንን ገለጠ ቢሉ ከከተማ ገዝተው አበረከትን ይላሉ እንዳይሉ!
ማርቆስ 8 ፡ 4
ደቀ መዛሙርቱም፦ በዚህ #በምድረ_በዳ እንጀራ ከየት አግኝቶ ሰው እነዚህን ማጥገብ ይችላል? ብለው መለሱለት።
• ቅዱስ ሉቃስ ወቅቱን ይገልጽልናል። መሽቶ እንደነበር ። ተዐምሩን ለምን በቀን አላደረገም ቢሉ በጠዋት ቢያደርገው በልተን መጥተናል ባሉት ነበር በምሳ ቢያደርገው የጠዋቱ አለ ባሉት ነበር ። ስለዚህ አብረው ውለው ማታ አድርጎ ምክንያት አሳጣን።
ሉቃስ 9: 12
❝ቀኑም ይመሽ ጀመር፤ አሥራ ሁለቱም ቀርበው፦ በዚህ በምድረ በዳ ነንና በዙሪያችን ወዳሉ መንደሮችና ገጠሮች ሄደው እንዲያድሩና ምግብ እንዲያገኙ ሕዝቡን አሰናብት አሉት።❞
• ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ አካባቢውን በመግለጽ ይጀምራል። ምክንያት ቢሉ አይሁድ የማንጻት ለማዳ ነበራቸው እና! ሳይታጠቡ አይበሉም ነበር እና !
ዮሐንስ 6: 1
❝ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ ተሻገረ፤ እርሱም የጥብርያዶስ ባሕር ነው።❞
ይህ የሚያስተምረን ለየትኛውም ድክመታችን ምክንያት እንደሌለን ነው።
ከምክንያተኝነት በመቀጠል ትልቁ ችግር ከእቅዳችን እግዚአብሔርን ማስወጣት ነው ። ምንም ነገር ስንጀምር ፈቃደ እግዚአብሔርን ካላስቀደምን ጦርነት ሳይጀምር እንደተሸነፈ ወታደር ነን !
ሊቁ እንደተናገረው። " እግዚአብሔር የሌለበት ዕቅድ እና መስመር የሳተ መንገደኛ አንድ ነው " ሁለቱም መድረሻቸው አያታወቅም እና!
እንቀጥላለን... !
መ/ር ዲ/ን እስጢፋኖስ ደ.
26/12/2014
ያዕቆብ 4: 15
ክፍል 1
ሰላም ወዳጆች...
እንዴት ነው ?
ዓመቱ እንዴት እየተጠናቀቀ ነው?
እግዚአብሔር ፈቅዶ 2014 ዓ.ም ዘመነ ማርቆስን ለማገባደድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ቀርተውናል ። እስቲ ዘወር ብለን ያለፈውን ጊዜያቶች እንዴት እንዳሳለፍን እንመርምር። መመርመር በጥያቄ ይጀምራል እና ይህንን ልጠይቅ... !
ስንቱን አተረፍንበት.... ?
ስንቱን ከሰርንበት.... ? ለምን ?
ስንቱንን በሚጠቅመን ነገር አሳለፍንበት ...?
ስንቱን በማይጠቅም ነገር አሳለፍንበት.... ? ለምን?
ምን ያህሉን ጊዜ አዲስ ዕውቀት ለመጨመር ተጋንበት ?
ስንት መጽሃፍትን አነበብን ? ስንቱን ኖርነው ?
በዚህ ዓመት ልንፈጽመው #ካቀድነቸው ነገሮች ውስጥ ምን ያህሉን አሳካናቸው ? ምን ያህሉን አላሳካነውም? ለምን ?
ከሁሉም ከሁሉም ግን ወሳኙ ጥያቄ ምን ያህሉን ጊዜ ለእግዚአብሔር ሰጠነው ? ምንያህሉን ጊዜ ከእግዚብሔር ጋር ተገናኘንበት ? የሚለው ነው ?
በእርግጥ ይህንን ጥያቄ ሙሉ ለሙሉ ለመመለስ ጊዜ ቢያስፈልገውም እንዲው የግምገማ ጊዜ ቢኖረን ከሚል ወንድማዊ ፍቅር ጠየኩኝ ። በእርግጠኝነት መናገር የምችለው ግን ለሁሉም ላላሳካነቸው ነገሮች ያሳምንም አያሳምንም ? ይብዛም ይነስም አዕምሮአችን ምክንያት ይሰጠናል ።
#ንግባኬ_ሀበ_ጥንተ_ነገር እንዲል ሊቁ ወደ ቀደመ ነገሬ ስመለስ ከላይ ላሉት ጥያቄዎች ለምን ሙሉ ለሙሉ ማሳካት አልቻልኩም ብለን ስንጠይቅ መልሱ ወደ አንድ ነገር ያመራናል ።
የጊዜ አጠቃቀም እና ምክንያታዊነት!
ስለ ጊዜ አጠቃቀም በሌላ ርዕስ ብመለስበት ስለሚሻል ስለ ምክንያታዊነት ይህንን ልበል! ቅዱስ መጽሀፍ እንደሚያስተምረው ለየትኛውም ስንፉናችን ምክንያት ሊያድነን አይችልም።
❝እኔ መጥቼ ባልነገርኋቸውስ ኃጢአት ባልሆነባቸውም ነበር፤ አሁን ግን ለኃጢአታቸው #ምክንያት የላቸውም።❞ ዮሐንስ 15: 22
ጌታችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲያስተም ስላደረገው ተዓምር እስራኤላውያን እንዳይሰናከሉ አንድም ለሰው ልጅ ተዐምራቱ ላይ እንዳንሰናከል ምክንያትን ለማስወገድ አንድን ተዐምር በአራት ወንጌላውያን ሲያስመሰከር ሲያጽፍ እንገኘዋለን። ይህም ተዐምር...
• ቅዱስ ማቴዎስ... ቦታው የተመቸ (ሳር እና ለምለም) እንደነበር ይገልጣል። ለምን ይህንን መግለጥ አስፈለገው ቢሉ አይሁዳውያን ቦታው አልተመችንም ስለዚህም አልበላንም እንዳይሉ!
ማቴዎስ 14 :19
ሕዝቡም #በሣር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፥ አምስቱንም እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ወደ ሰማይ አሻቅቦ አየና ባረከ፥ እንጀራውንም ቆርሶ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ።
• ቅዱስ ማርቆስ ደግሞ ቦታው ምድረ በዳ (ከከተማ ወጣ ያለ ስፍራ) እንደነበር ይገልጻል ። ለምን ይህንን ገለጠ ቢሉ ከከተማ ገዝተው አበረከትን ይላሉ እንዳይሉ!
ማርቆስ 8 ፡ 4
ደቀ መዛሙርቱም፦ በዚህ #በምድረ_በዳ እንጀራ ከየት አግኝቶ ሰው እነዚህን ማጥገብ ይችላል? ብለው መለሱለት።
• ቅዱስ ሉቃስ ወቅቱን ይገልጽልናል። መሽቶ እንደነበር ። ተዐምሩን ለምን በቀን አላደረገም ቢሉ በጠዋት ቢያደርገው በልተን መጥተናል ባሉት ነበር በምሳ ቢያደርገው የጠዋቱ አለ ባሉት ነበር ። ስለዚህ አብረው ውለው ማታ አድርጎ ምክንያት አሳጣን።
ሉቃስ 9: 12
❝ቀኑም ይመሽ ጀመር፤ አሥራ ሁለቱም ቀርበው፦ በዚህ በምድረ በዳ ነንና በዙሪያችን ወዳሉ መንደሮችና ገጠሮች ሄደው እንዲያድሩና ምግብ እንዲያገኙ ሕዝቡን አሰናብት አሉት።❞
• ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ አካባቢውን በመግለጽ ይጀምራል። ምክንያት ቢሉ አይሁድ የማንጻት ለማዳ ነበራቸው እና! ሳይታጠቡ አይበሉም ነበር እና !
ዮሐንስ 6: 1
❝ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ ተሻገረ፤ እርሱም የጥብርያዶስ ባሕር ነው።❞
ይህ የሚያስተምረን ለየትኛውም ድክመታችን ምክንያት እንደሌለን ነው።
ከምክንያተኝነት በመቀጠል ትልቁ ችግር ከእቅዳችን እግዚአብሔርን ማስወጣት ነው ። ምንም ነገር ስንጀምር ፈቃደ እግዚአብሔርን ካላስቀደምን ጦርነት ሳይጀምር እንደተሸነፈ ወታደር ነን !
ሊቁ እንደተናገረው። " እግዚአብሔር የሌለበት ዕቅድ እና መስመር የሳተ መንገደኛ አንድ ነው " ሁለቱም መድረሻቸው አያታወቅም እና!
እንቀጥላለን... !
መ/ር ዲ/ን እስጢፋኖስ ደ.
26/12/2014
.....የቀጠለ
❝...#ጌታ_ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያንን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።❞
ያዕቆብ 4: 15
ክፍል 2
ሰላም ወዳጆች ? ትላንት በክፍል 1 ቆያታችን እያገባደድን እየመጣን ስላለው ዓመት አጭር የግምገማ እና ለምን አላሳካነውም ለሚሉ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ጀምረን ነበር ።
ምክንያተኝነትን እና ምክንያትን ለዓላማ እንዲሁ ለ መንፈሳዊ እድገት መቀጨጭ ዋና አስተዋጽዖ እንዳለው በግርድፉ ተመልክተን ነበር ።
ዛሬም በዚህ በክፍል ሁለት አንድ አንድ ነገር እንነገራለን ።
ዓመቱን እንዴት እንዳሳለፍን ለራሳችን ስንጠይቅ ብዙ ነገሮች በአእምሯችን እንደተመላለሱ ለመገመት ሊቅነትን አይጠይቅም ። ዋናው ነገር ግን እርሱ አይደለም ።
መልሶቹ ውጫዊው አጋደለ ወይስ ውስጣዊው???
ወደ ሌላ ወይስ ወደራሳችን ?
ወደ ሰፊው ዓለም ወይስ ወደ ራሳችን ዓለም ?
መልሱ ወደ ወጪ ካመዘነ አሁንም ደግመን የምንጠይቅበት ሰዐት ነው ። ምክንያቱም መልሱን አላገኘነውም ! አለቀ።
ብዙ ጊዜ የችግራችን (መንፈሳዊ ይሁን ዓለማዊ) መንስኤ ውጫዊ እንደሆነ ካሰብን ውጫዊ መፍትሔ ስንፈልግለት እንደ ባዘንን ሳንንድን ሌላ የተሰጠንን ጊዜ እናባክናለን ። ቅዱሱ መጽሃፍ ❝...የመዳን ቀን አሁን ነው።❞ 2ኛ ቆሮ 6: 2 ሲል አሁን የመለወጫ የመወሰኛ ጊዜ ነው እያለን እንደሆነ ልብ ይሏል።
ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው
❝ነገር ግን በዚያ በሚመኩበት እንደ እኛ ሆነው ሊገኙ፥ #ምክንያትን ከሚፈልጉቱ #ምክንያትን እቆርጥ ዘንድ አሁን የማደርገውን ከዚህ ወዲህ ደግሞ አደርጋለሁ።❞
—2ኛ ቆሮ 11: 12
ምክንያተኝነትን እያስወገድን ራሳችንን መመልከት ያስፈልጋል። ሌላው ብዙ ስንጠይቅ መራቀቅን ለጊዜው እያስቀመጥን ቢሆን ደግሞ መልካም ያደርገዋል ።
ሁለት የፍልስፉና መጽሀፍ ያነበበ ወዳጄ" ሰላም ነው?" ስለው የመለስልኝ መልስ ፈገግ ቢያሰኘኝ ነው ይህን ማለቴ !
ጓደኛዬ :- ውስጣዊ ነው ውጫዊ ???
በገድለ አቡነ ተክለሃይማኖት ያለች ልትራቀቅ ወድዳ ፍዳ ያመጣች አንዲት መነኩሲት ሰው ላስታውሳት። አባታችን ጸሀይ ዘኢትዮጲያ አቡነ ተክለሃይማኖት በደብረሊባኖስ በነበሩበት ወቅት አራዊት እየመጡ የልጆቻቸውን አዝመራ እየበሉ አስቸገሯቸው ። ልጆቹም ሄደው " አባታችን! እንስሳት አራዊት አትክልታችንን እየበሉ አስቸገሩን " አሏቸው።
ቅዱስ አባታችንም "ልጆቼ ተውአቸው ። እኛ ወደ ጫካ መጣንባቸው እንጂ እነርሱ አልመጡብንም" ሲሉ መለሱላቸው ።
እንዲህ ሆነው ሳለ ከዕለታት በአንድ ቀን አንዲት አረጋዊት መናኝ ስተመገብ አንድ ዝንጀሮ መጥቶ በጥፊ ጠርቅሞ ቀምቷት በላ ። አባታችንም ይህንን አይተው :- " የተሰጡትን ትቶ ሌላ ያልተሰጡትን መሻት የያዙትን ያሳጣል። እኔ በዱር የተዘራውን ትበሉ ዘንድ ብፈቅድ ከሰው እጅ እየቀማችሁ መብላት ጀመራችሁ?" ብለው "ወንጌልን በምሰክለት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አፋችሁን የታሰረ ይሁን! " በቃለ ማእሰር ዘጓቸው ። ከዚያን ቀን ጀምሮ መብላት ተሳናቸው ።
በስተመጨረሻም ሩጫቸውን ጨርሰው ሊያርፉ ሲሉ ልጆቻቸው ጠርተው ሲሰናበቱ መረቋቸው። በዚህ ጊዜ ያች ሴት ልትራቀቅ ወድዳ " አባቴ በጸሎቶ ያሰሩትም ይፍቱ " ብላ ጠየቀች። እርሳቸውም " የታሰረውም ይፈቱ " ሲሉ ዝንጀሮውም አብሮ ተፈታ ። በዚህም ከቀደመው የበዛውን አጠፉ።
ስናጠቃልለው በነገርም ያለ ነገርም # አትራቀቅ ...!
እንቀጥላለን ።
❝...#ጌታ_ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያንን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።❞
ያዕቆብ 4: 15
ክፍል 2
ሰላም ወዳጆች ? ትላንት በክፍል 1 ቆያታችን እያገባደድን እየመጣን ስላለው ዓመት አጭር የግምገማ እና ለምን አላሳካነውም ለሚሉ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ጀምረን ነበር ።
ምክንያተኝነትን እና ምክንያትን ለዓላማ እንዲሁ ለ መንፈሳዊ እድገት መቀጨጭ ዋና አስተዋጽዖ እንዳለው በግርድፉ ተመልክተን ነበር ።
ዛሬም በዚህ በክፍል ሁለት አንድ አንድ ነገር እንነገራለን ።
ዓመቱን እንዴት እንዳሳለፍን ለራሳችን ስንጠይቅ ብዙ ነገሮች በአእምሯችን እንደተመላለሱ ለመገመት ሊቅነትን አይጠይቅም ። ዋናው ነገር ግን እርሱ አይደለም ።
መልሶቹ ውጫዊው አጋደለ ወይስ ውስጣዊው???
ወደ ሌላ ወይስ ወደራሳችን ?
ወደ ሰፊው ዓለም ወይስ ወደ ራሳችን ዓለም ?
መልሱ ወደ ወጪ ካመዘነ አሁንም ደግመን የምንጠይቅበት ሰዐት ነው ። ምክንያቱም መልሱን አላገኘነውም ! አለቀ።
ብዙ ጊዜ የችግራችን (መንፈሳዊ ይሁን ዓለማዊ) መንስኤ ውጫዊ እንደሆነ ካሰብን ውጫዊ መፍትሔ ስንፈልግለት እንደ ባዘንን ሳንንድን ሌላ የተሰጠንን ጊዜ እናባክናለን ። ቅዱሱ መጽሃፍ ❝...የመዳን ቀን አሁን ነው።❞ 2ኛ ቆሮ 6: 2 ሲል አሁን የመለወጫ የመወሰኛ ጊዜ ነው እያለን እንደሆነ ልብ ይሏል።
ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው
❝ነገር ግን በዚያ በሚመኩበት እንደ እኛ ሆነው ሊገኙ፥ #ምክንያትን ከሚፈልጉቱ #ምክንያትን እቆርጥ ዘንድ አሁን የማደርገውን ከዚህ ወዲህ ደግሞ አደርጋለሁ።❞
—2ኛ ቆሮ 11: 12
ምክንያተኝነትን እያስወገድን ራሳችንን መመልከት ያስፈልጋል። ሌላው ብዙ ስንጠይቅ መራቀቅን ለጊዜው እያስቀመጥን ቢሆን ደግሞ መልካም ያደርገዋል ።
ሁለት የፍልስፉና መጽሀፍ ያነበበ ወዳጄ" ሰላም ነው?" ስለው የመለስልኝ መልስ ፈገግ ቢያሰኘኝ ነው ይህን ማለቴ !
ጓደኛዬ :- ውስጣዊ ነው ውጫዊ ???
በገድለ አቡነ ተክለሃይማኖት ያለች ልትራቀቅ ወድዳ ፍዳ ያመጣች አንዲት መነኩሲት ሰው ላስታውሳት። አባታችን ጸሀይ ዘኢትዮጲያ አቡነ ተክለሃይማኖት በደብረሊባኖስ በነበሩበት ወቅት አራዊት እየመጡ የልጆቻቸውን አዝመራ እየበሉ አስቸገሯቸው ። ልጆቹም ሄደው " አባታችን! እንስሳት አራዊት አትክልታችንን እየበሉ አስቸገሩን " አሏቸው።
ቅዱስ አባታችንም "ልጆቼ ተውአቸው ። እኛ ወደ ጫካ መጣንባቸው እንጂ እነርሱ አልመጡብንም" ሲሉ መለሱላቸው ።
እንዲህ ሆነው ሳለ ከዕለታት በአንድ ቀን አንዲት አረጋዊት መናኝ ስተመገብ አንድ ዝንጀሮ መጥቶ በጥፊ ጠርቅሞ ቀምቷት በላ ። አባታችንም ይህንን አይተው :- " የተሰጡትን ትቶ ሌላ ያልተሰጡትን መሻት የያዙትን ያሳጣል። እኔ በዱር የተዘራውን ትበሉ ዘንድ ብፈቅድ ከሰው እጅ እየቀማችሁ መብላት ጀመራችሁ?" ብለው "ወንጌልን በምሰክለት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አፋችሁን የታሰረ ይሁን! " በቃለ ማእሰር ዘጓቸው ። ከዚያን ቀን ጀምሮ መብላት ተሳናቸው ።
በስተመጨረሻም ሩጫቸውን ጨርሰው ሊያርፉ ሲሉ ልጆቻቸው ጠርተው ሲሰናበቱ መረቋቸው። በዚህ ጊዜ ያች ሴት ልትራቀቅ ወድዳ " አባቴ በጸሎቶ ያሰሩትም ይፍቱ " ብላ ጠየቀች። እርሳቸውም " የታሰረውም ይፈቱ " ሲሉ ዝንጀሮውም አብሮ ተፈታ ። በዚህም ከቀደመው የበዛውን አጠፉ።
ስናጠቃልለው በነገርም ያለ ነገርም # አትራቀቅ ...!
እንቀጥላለን ።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
#ጉባኤው
_____
መስከረም :- ለምን እንደሆነ ጉባኤ የጠራነው
አንዳችንም ሳንቀረ የተሰበሰብነው?
ወርኃ ጥቅምት በቶሎ እንዲገልጠው
ሰብሳቢው መስከረም እድል እሰጣለው
ጥቅምት ፦ አዎን ጋሽ መስከረም የወራቶች አውራ
አመሰግናለሁ ዕድል ስለሰጡኝ እኔ እዳወራ
ያሉት ትክክል ነው አንድም ወር አልቀረም
ችግሩ ጥልቅ ቢሆን ባይሆን የማያከርም
ሁሉንም ወር ቀጥረን እዚህ ተጠራቀምን
ኅዳር ፦ ሁሉም እንደመጣ እናረጋግጥና
ጉባኤው ይጀመር በታላቅ ጦሞና
መስከረም :- ጥሩ መልካም አልከን ወንድማችን ኅዳር
ሁሉም በሥርዓቱ ተሰፍሮ ይቆጠር
መቼም ከተያዘ ወግ አይቀርምና
ኅዳር አንተ ትጉ ብዕርን አውጣና
ቃለ ጉባኤ ያዝ ካፍ ካፍ ልቀምና
ኅዳር :- እሺ ታላቁ ወር የመጀመሪያችን
በሙሉ እጥፋለሁን ሳላስቀር አንዳችን
ጥቅምት :- እኔም ጥቅምት አለው የጉባኤው ድምቀት
ጋሽ መስከረም እርሶ ጉባኤውን ሲመሩት
እቀላጠፋለው ሀሳብ እንዳይነጥፍ
ከአንዱ ወደ ሌላው እያልኩኝ ቅልጥፍጥፍ
ማንም እንዳልቀረ ቢያውቅም ልቦናዬ
ወግ መጠበቅ ነውና ዋነኛው ሥራዬ
ማን ማን እንደመጣ ሊታደም ጉባኤ
አሁን እጠራለሁ እርሶን አስቀድሜ
ጋሽ መስከረምዬ ስዩመ ጉባኤ
ታህሳስ ና ጥር የካቲት መጋቢት
እነዝያውናቸው ሚያዝያ ና ግንቦት
ሰኔም ተገኘታለች ይህች አሳባቂ
የክረምቱን መድርሰ ቀድማ አሳዋቂ
ሐምሌ ና ነሐሴም ጉም ድመና ለበሰው
ጋቢ የደረቡ አዛውንትን መስለው
በቀኘ ይታዩናል ዶፍ ዝናብ አርግዘው
/ ይህን ጊዜ ጉባኤው በሳቅ ይታወካለል /
ሐምሌ ፦ ለአነጋገር ልክ ለከት አብጅለት
ምን ብትንቀን ነው ነፍሰ ጡር ያረከን ?
አለዛ ታርመህ አደብን ካልገዛህ
የያዝነውን ውኃ በአንድነት ለቀን
ጉድ እንዳናረገህ በጎርፍ አሶስደን
መስከረም ፦ ጥቅምት አንተም ተው አንተም ታገስ ሐምሌ
እርምጃ እወስዳለሁ እኔ ግን በግሌ
ሌላ ሆኖ ሳለ መነጋገሪያችን
በንቀርት ላይ ደግፍ ሆነ ችግራችን
ደራሽ ጎርፍ ማዘዝ ይቻለኛል ብለህ
አትኩራ በክብር በተሰጠህ ነገር
ልታቅ ይገባሃል ስለሞቃም ወር
መፎከር አይበጅም ጉልበትን ተማምኖ
ለአንዱ ሲሰጠው እንዲወስድ በትኖ
ለሌላው ይሰጠዋለል እጥፍ ድርብ ሆኖ
አሙቆ አፍልቶ የሚያስቀር አትኖ
አሉባልታ ወሬ ቧልቱን እንተውና
የስብሰባው አላማ ይህ አይደለምና
በቶሎ እንመለስ በቀናው ጎዳና
ታኀሳስ :- በሉ አታንቃቁን በቶሎ ጀምሩ
የተጋረጠብን ችግር ካለም አውሩ
አውርተን እንፍታው ነገሩን ከስሩ
ሚያዝያ :- እኔም እስማማለው በሀሳበ ጥር
ቶሎ ተገልጦልን ሰብሰባው ቢያጥር
ምንድ ነው ምሥጢሩ የመታደማችን
ምን ችግር ገጠመን ከመካከላችን?
መስከረም :- እንግዲህ ለማንሳት ከሥሩ ነገሩን
ብርቱ ችግር መቷል የሚነጣጥለን
አንድነትን ፈቶ ለብቻ የሚያቀረን
ስለዚህ ተወያይተን አውርተን በጋራ
ሀሳብ ለማዳመጥ ጉባኤ ተጠራ
ሰኔ : አረ ሰብሳቢያችን ታላቅ ወንድማችን
ምን ይሆን ነገሩ እንዲህ ያሰጨነቀን
ተነፋፋው እኮ ነገር ሆዴ ገብቶ
እኔ እንደው ወሬ አልችል ንገረን በቶሎ
ሰኔን እያወከኝ ለወሬ የሞትኩ ነኝ
በዘንድው እንኳ ክረምት መጣው ቢለኝ
ቀድሜ ዘረገፍኩ ዝናበ በረከቱን
ገና ሳይጠጋ ዘመነ ክረምቱ
እናማ ንገሩን ነገር ሳታረዝሙ
ብሶ እንዳይገለኝ የወሬ ጥማቱ
መስከረም : -እስቲ ተረጋጊ ሰኔ አትጣደፊ
አንዳንዴ ወሬውን ሰምተሽም እለፊ
ችግርና ሐዘን የገጠሙ ለታ
መቅደም ይገባዋል ሁል ጊዜም እርጋታ
ነሩን ስጀምር ማስረዳት ሀ ብዬ
ሐዘኔ ጥልቅ ነው ይህን በማለቴ
13 ሆነን
በስካሁን ኑሯች በምድረ ኢትዮጲያ
እንዳችን የጌታ ሌሎቻን የ12ቱ ሐዋርያ
ምሳሌዎች ሆነን ኖረናል በአራያ
ጥቅምት :- አፌ ቁርጥ ይበል መስከም ሊቃችን
ምሥጢር አርገህ መሰልከን
መስከረም :-አመሰግናለሁ አክባሪዬ ጥቅምት
ግን ግን ታዝን ነበር ብትታገስ ጥቂት
እንዲሁ ቢያዛልቀን ነበረ በቀና
ዛሬ ግን በዓለም ዕውቀት በዛችና
ዋዜማ ላይ ሆንን ለመለየት ዜና
(ይህን ጊዜ ጉባኤው በጫጫታ ይታወካል ዋዜማ ለመለየት ዜና ሆሆሆ ወዘተ በሚሉ ወሬዎች )
ጷጉሜ :- አንዳችን የጌታ ሌሎቻን የ12ቱሐዋርያ
ምሳሌዎች ሆነን ከኖርን በምድረ በኢትዮጲያ
አሁን ደርሶ የሚለይ ምን ተአምር መጣ?
ግንቦት :- አይ ጷጉሜ የዋህ እህት
የሐዋርያትም ሕብረት ከጌታችን ጋራ
ተፈቶ የለም ወይ በአይሁድ ፉከራ
ፈሪሳዊ ዕውቀት እርሾዎ ሲንሰራፋ
የሥላሴ አምሳል የሰው ልጅም ከፋ
እስካልተቆጠብን ከፈሪሳኢ እርሾ
መፈጠሩ አይቀርም በፍቅር ላይ ቁርሾ
ጷጉሜን :- የሆነውስ ሆኖ እኛን የሚለያይ ምን እርሾ ተገኘ
የሰው ልጅ አይደለን ዘር ቋን ቋ አለየን
ለያይቶ ከፋፍሎ ለብቻ የሚያደርገን ?
መስከረም :- እንግዲህ ጷጉሜያችን ትንሿ እህታችን ችግሩ ይህ ነው
ያንቺ ከኛ ጋራ አብሮ መቆጠር ነው
አንዳንድ ዕውቀት ገባን ታረቀቅን ያሉ
ጷጉሜ ከወራቶች ትቀነስ ነው ያሉ
#ጉባኤው
_____
መስከረም :- ለምን እንደሆነ ጉባኤ የጠራነው
አንዳችንም ሳንቀረ የተሰበሰብነው?
ወርኃ ጥቅምት በቶሎ እንዲገልጠው
ሰብሳቢው መስከረም እድል እሰጣለው
ጥቅምት ፦ አዎን ጋሽ መስከረም የወራቶች አውራ
አመሰግናለሁ ዕድል ስለሰጡኝ እኔ እዳወራ
ያሉት ትክክል ነው አንድም ወር አልቀረም
ችግሩ ጥልቅ ቢሆን ባይሆን የማያከርም
ሁሉንም ወር ቀጥረን እዚህ ተጠራቀምን
ኅዳር ፦ ሁሉም እንደመጣ እናረጋግጥና
ጉባኤው ይጀመር በታላቅ ጦሞና
መስከረም :- ጥሩ መልካም አልከን ወንድማችን ኅዳር
ሁሉም በሥርዓቱ ተሰፍሮ ይቆጠር
መቼም ከተያዘ ወግ አይቀርምና
ኅዳር አንተ ትጉ ብዕርን አውጣና
ቃለ ጉባኤ ያዝ ካፍ ካፍ ልቀምና
ኅዳር :- እሺ ታላቁ ወር የመጀመሪያችን
በሙሉ እጥፋለሁን ሳላስቀር አንዳችን
ጥቅምት :- እኔም ጥቅምት አለው የጉባኤው ድምቀት
ጋሽ መስከረም እርሶ ጉባኤውን ሲመሩት
እቀላጠፋለው ሀሳብ እንዳይነጥፍ
ከአንዱ ወደ ሌላው እያልኩኝ ቅልጥፍጥፍ
ማንም እንዳልቀረ ቢያውቅም ልቦናዬ
ወግ መጠበቅ ነውና ዋነኛው ሥራዬ
ማን ማን እንደመጣ ሊታደም ጉባኤ
አሁን እጠራለሁ እርሶን አስቀድሜ
ጋሽ መስከረምዬ ስዩመ ጉባኤ
ታህሳስ ና ጥር የካቲት መጋቢት
እነዝያውናቸው ሚያዝያ ና ግንቦት
ሰኔም ተገኘታለች ይህች አሳባቂ
የክረምቱን መድርሰ ቀድማ አሳዋቂ
ሐምሌ ና ነሐሴም ጉም ድመና ለበሰው
ጋቢ የደረቡ አዛውንትን መስለው
በቀኘ ይታዩናል ዶፍ ዝናብ አርግዘው
/ ይህን ጊዜ ጉባኤው በሳቅ ይታወካለል /
ሐምሌ ፦ ለአነጋገር ልክ ለከት አብጅለት
ምን ብትንቀን ነው ነፍሰ ጡር ያረከን ?
አለዛ ታርመህ አደብን ካልገዛህ
የያዝነውን ውኃ በአንድነት ለቀን
ጉድ እንዳናረገህ በጎርፍ አሶስደን
መስከረም ፦ ጥቅምት አንተም ተው አንተም ታገስ ሐምሌ
እርምጃ እወስዳለሁ እኔ ግን በግሌ
ሌላ ሆኖ ሳለ መነጋገሪያችን
በንቀርት ላይ ደግፍ ሆነ ችግራችን
ደራሽ ጎርፍ ማዘዝ ይቻለኛል ብለህ
አትኩራ በክብር በተሰጠህ ነገር
ልታቅ ይገባሃል ስለሞቃም ወር
መፎከር አይበጅም ጉልበትን ተማምኖ
ለአንዱ ሲሰጠው እንዲወስድ በትኖ
ለሌላው ይሰጠዋለል እጥፍ ድርብ ሆኖ
አሙቆ አፍልቶ የሚያስቀር አትኖ
አሉባልታ ወሬ ቧልቱን እንተውና
የስብሰባው አላማ ይህ አይደለምና
በቶሎ እንመለስ በቀናው ጎዳና
ታኀሳስ :- በሉ አታንቃቁን በቶሎ ጀምሩ
የተጋረጠብን ችግር ካለም አውሩ
አውርተን እንፍታው ነገሩን ከስሩ
ሚያዝያ :- እኔም እስማማለው በሀሳበ ጥር
ቶሎ ተገልጦልን ሰብሰባው ቢያጥር
ምንድ ነው ምሥጢሩ የመታደማችን
ምን ችግር ገጠመን ከመካከላችን?
መስከረም :- እንግዲህ ለማንሳት ከሥሩ ነገሩን
ብርቱ ችግር መቷል የሚነጣጥለን
አንድነትን ፈቶ ለብቻ የሚያቀረን
ስለዚህ ተወያይተን አውርተን በጋራ
ሀሳብ ለማዳመጥ ጉባኤ ተጠራ
ሰኔ : አረ ሰብሳቢያችን ታላቅ ወንድማችን
ምን ይሆን ነገሩ እንዲህ ያሰጨነቀን
ተነፋፋው እኮ ነገር ሆዴ ገብቶ
እኔ እንደው ወሬ አልችል ንገረን በቶሎ
ሰኔን እያወከኝ ለወሬ የሞትኩ ነኝ
በዘንድው እንኳ ክረምት መጣው ቢለኝ
ቀድሜ ዘረገፍኩ ዝናበ በረከቱን
ገና ሳይጠጋ ዘመነ ክረምቱ
እናማ ንገሩን ነገር ሳታረዝሙ
ብሶ እንዳይገለኝ የወሬ ጥማቱ
መስከረም : -እስቲ ተረጋጊ ሰኔ አትጣደፊ
አንዳንዴ ወሬውን ሰምተሽም እለፊ
ችግርና ሐዘን የገጠሙ ለታ
መቅደም ይገባዋል ሁል ጊዜም እርጋታ
ነሩን ስጀምር ማስረዳት ሀ ብዬ
ሐዘኔ ጥልቅ ነው ይህን በማለቴ
13 ሆነን
በስካሁን ኑሯች በምድረ ኢትዮጲያ
እንዳችን የጌታ ሌሎቻን የ12ቱ ሐዋርያ
ምሳሌዎች ሆነን ኖረናል በአራያ
ጥቅምት :- አፌ ቁርጥ ይበል መስከም ሊቃችን
ምሥጢር አርገህ መሰልከን
መስከረም :-አመሰግናለሁ አክባሪዬ ጥቅምት
ግን ግን ታዝን ነበር ብትታገስ ጥቂት
እንዲሁ ቢያዛልቀን ነበረ በቀና
ዛሬ ግን በዓለም ዕውቀት በዛችና
ዋዜማ ላይ ሆንን ለመለየት ዜና
(ይህን ጊዜ ጉባኤው በጫጫታ ይታወካል ዋዜማ ለመለየት ዜና ሆሆሆ ወዘተ በሚሉ ወሬዎች )
ጷጉሜ :- አንዳችን የጌታ ሌሎቻን የ12ቱሐዋርያ
ምሳሌዎች ሆነን ከኖርን በምድረ በኢትዮጲያ
አሁን ደርሶ የሚለይ ምን ተአምር መጣ?
ግንቦት :- አይ ጷጉሜ የዋህ እህት
የሐዋርያትም ሕብረት ከጌታችን ጋራ
ተፈቶ የለም ወይ በአይሁድ ፉከራ
ፈሪሳዊ ዕውቀት እርሾዎ ሲንሰራፋ
የሥላሴ አምሳል የሰው ልጅም ከፋ
እስካልተቆጠብን ከፈሪሳኢ እርሾ
መፈጠሩ አይቀርም በፍቅር ላይ ቁርሾ
ጷጉሜን :- የሆነውስ ሆኖ እኛን የሚለያይ ምን እርሾ ተገኘ
የሰው ልጅ አይደለን ዘር ቋን ቋ አለየን
ለያይቶ ከፋፍሎ ለብቻ የሚያደርገን ?
መስከረም :- እንግዲህ ጷጉሜያችን ትንሿ እህታችን ችግሩ ይህ ነው
ያንቺ ከኛ ጋራ አብሮ መቆጠር ነው
አንዳንድ ዕውቀት ገባን ታረቀቅን ያሉ
ጷጉሜ ከወራቶች ትቀነስ ነው ያሉ
ጷጉሜ :- ምን ?? አጥብቆ ጠያቂ የእናቱን ሞት ይረዳል አሉ
ለካ ለኔ ኖሯል ስብሰባ የተጠራው
እኔማ መቼ አወኩ እንዲ እንደተጠላው
የሁልሽን ጉለት ሳሟላ ቆይቼ
አንዳንዴ 4 ቀን ሌላ ግዜ 5 ገፋ ሲልም 7 ቀን እኮ የምሆነው
የናንተን ትራፊ በፍቅር ሰብስቤ ነው
እናንተ እዳታንሱ ከ30 ቀናት
ልቃቹም እዳቴዱ ከሰሌዳ ወራት
እራሴን ስቀንስ ሳባዛ ሁልግዜ
አመሰግናለሁ ይህ ከሆነ ደሞዜ
ደግሞም አዝ ኛለው ይዞኛል ትካዜ
(ከቀድሞ የበለጠ ጉባኤው ለሁለት ተከፍሎ በታላቅ ጫጫታ ይታወካል)
አዎ ትቀነስ ! አይ የለም ለምን ሲባል ትቀነሳለች! ትቀነስ! አይ በጭራሽ !ወዘተ)
መስከረም :- ፀጥታ ፀጥታ ጸጥታ ይከበር
በጥሞና ሆነን በተራ እንምከር
(ጫጫታው እየጋለ ይሄዳል ሰብሳቢው መስከረም ቆም ብሎ ያጨበጭባል )
በመካከል የጷጉሜ የለቅሶ ድምጽ ይሰማል /
ጥቅምት :- ጷጉሜ እህታች በቶሎ አትከፊ
ሁሉን የሚቻለውን እርሱን ተደገፊ
ጉባኤው ተማክሮ አልወሰነምና
ፊትሽ እንዳይጨልም በሐምሌ ደመና
መስከረም :- እሺ አሁን ሁሉም በየተራ
ሀሳቡን ይሰጣል ገልጦ እያብራራ
ጥቅምት በሥርዓቱ በቅደም ተከተል ተራ ያሲዝና
ኅዳር ይጥፈዋል ሁሉን በጥሞና
ስለዚህ ወስኑ መክንያትን ይዛችሁ
ትቀነስ ትቀመጥ ጷጉሜን እህታችሁ?
(አሁንም ጫጫታው ይጀምራል )
መስከረም :- ሀሳብ ያለው ብቻ እጁ እያወጣ
ዕድሉን ሰሰጠው መልካም ምክሩን የምጣ
ከዛ በተረፈ ነውና ጉባኤ
ጫጫታን አልፈቅድም የጎንዮሽ ወሬ
ጥቅምት :- አዎን እሺ እዛ ጋር ወርኃ መጋቢት እጁን ስላወጣ
ታላቁ መስከረም ዕድል ይስጡትና ቆንጆ ሀሳብ ያምጣ
መስከረም :- እሺ መልካም ቀጥል
መጋቢት :- አመሰግናለው ሰብሳቢው መስከረም
ዕድል ስለሰጡኝ ከሁሉ በማቅደም
ክብረቴም ይድረሰው ለአሳላፊው ጥቅምት
የኔ እንኳን ሀሳቤ በጷጉሜ ወራችን
አትቀነስ ባይ ነኝ ትሩን ከጎናችን
እርሷ ብትለየን ከመካከላችን
እኩልነት ቀርቶ ይከራል ጠባችን
እኔ በበኩሌ ከ30ው ዕድሜዬ
መቀነስ አልሻም ከየወር ድርሻዬ
መስከረም :- መልካም ሌላ ባለ ሀሳብ
ጥቅምት :- እዛ ጋር ጥግ ላይ ሰኔ እያወጣች ነው
መስከረም :-እስቲ ሰኔ ተንፍሽ
ሰኔ :- አመሰግናለሁ ዕድል በመቸሬ
እኔ አላረዝምም አጭር ነች ነገሬ
ጷጉሜ ትቀነስ ወይ በሚለው ሀሳባችሁ
እኔ እስማማለው አጠቅምም ባካችሁ
ወይ ሞልታ ላትሞላ ይህቺ የቀን ጎደሎ
ውሳኔው ይወሰን ትወገድ በቶሎ
መስከረም : - እሺ ተቀበልንሽ ሰኔ ታዳሚያችን
ግን ግን ለመለየት ሳይሆን መሰባሰባችን
አንድ መሆን ነበር የኛ ዓላማችን
የሆነው ሆነና ሰብሳቢ ነኝና
ሁሉንም ሀሳቦች ልስማ በየፊና
አሁንም ቀጥዬ ዕድልን ልስጣችሁ
ከስካሁኑ ሁሉ የተለየ ሀሳብ ካለ መሃላችሁ
እጅ ክንዳችሁን አሳዮን አጉልታችሁ
ጥቅምት :- በዚ ጥግ ደግሞ ከተደረደሩት
የጥር እጅ እታያል ጋሼ ዕድል ይስጡት
መስከረም :- በል እሺ ተናገር ዕድል ሰጥቻለሁ
የሚያስማማን ሀሳብ ካንተ ዘንድ እሻለው
ጥር :- አመሰግናለሁ ወርሃ መስከረም
እኔም ባጭሩ ነው ነገር አላረዝምም
ትንሽ ሰው ትንሽ ነው ይላሉ ሰዎቹ
ዕውቀት የገባቸው ነገር አዋቆቹ
ማለቴ እነዛ ነጮቹ
ምንድነው ለማለት ባጭሩ የፈለኩ
ምንም አይመስለኝም ጷጉሜንም ብትነኩ
ትቀነስ ካላቹም ትቀነስ ግድ የለም
በኔ ሕልውና ላይ ለውጥን አያመጣም
ጥቅምት :- ጷጉሜን ሀሳብ አላት መስለኝ ቆማለች
ዕድል እንዲሰጣች ፍቃድ ከጅላለች
መስከረም :- እሺ አድምጠናል የጥርን ሀሳብ
ግን እንደታሰበው ውኃ አያነሳም
ጷጉሜ ስለቆመች ዕድልን ፈልጋ
እስቲ እናዳምጣት እንሁን ከእርሷ ጋር
ጷጉሜን :- ለሰው ሀገር ተሽጠው
ወርቅና ዋንጫው ያመጡ ሮጠው
ያናድደኝ ነበር እዚህ ሆኜ ሳየው
ለካ ተገፍተው ነው ፍቅርን ተነፍገው
እንዲህ ካሴራቹ እኔን ለማስቀረት
አብሮ አደግ ጓደኛን መለየት ነውር ከሌለበት
እኔም እሄዳለሁ ፍቅር ወዳለበት
( ብላ ጷጉሜ እያለቀሰች ስብሰባውን እረግጣ ትወጣለች )
ጥር :- ይህው አላልኳቹም ትንሽ ሰው ትንሽ ነው
እረግጣን የወጣች ቢናቅ ነው ጉባኤው
መስከረም :- መቋቋም ካልቻለች የመለየትዜንን
ብትወጣ ገድ የለም
ተገፍታም ተይዛመ ሁለት በደል የለም
(በጣም ተበሳጭቶ ዕድል ሳይሰጠው የካቲት ይነሳና)
የካቲት :- ጷጉሜ አትቀነስም እኔ ቆሜ ሳለሁ
በእርሷ ከመጣችሁ ሞቴን እመርጣለሁ
መኖር እየቻልን ሁላችን ተካተን
በነጭ ዲስኩር ወሬ እንዴት እናምናለን
እስቲ እነርሱ ራሱ ከወራቶቻቸው
በ11ዱ ይቅሩ አንዱን ወር ቀንሰው
ፊደሉ ይቀነስ ወራቱ ይቀነስ
ምን የሚሉት እብደት ምን ዐይነት መቃወስ
ዓለም እየሳቀ በጅጉ እንዳይንቀን
እንቀነስ ስንል በመደመር ዘመን
እግዚአብሔር ለማለት God ን ስትጽፉ
Gን ካቲታል አርጓት ከእውቀት እንዳትነጥፉ
እግዚአብሔር ለማለት ጣዖት እዳጥፉ
ብለው የሚነተርኩን በነጋ በጠባ
የእነርሱ ፊደል ነው ምሥጢር ትርጉሜ አልባ
ለካ ለኔ ኖሯል ስብሰባ የተጠራው
እኔማ መቼ አወኩ እንዲ እንደተጠላው
የሁልሽን ጉለት ሳሟላ ቆይቼ
አንዳንዴ 4 ቀን ሌላ ግዜ 5 ገፋ ሲልም 7 ቀን እኮ የምሆነው
የናንተን ትራፊ በፍቅር ሰብስቤ ነው
እናንተ እዳታንሱ ከ30 ቀናት
ልቃቹም እዳቴዱ ከሰሌዳ ወራት
እራሴን ስቀንስ ሳባዛ ሁልግዜ
አመሰግናለሁ ይህ ከሆነ ደሞዜ
ደግሞም አዝ ኛለው ይዞኛል ትካዜ
(ከቀድሞ የበለጠ ጉባኤው ለሁለት ተከፍሎ በታላቅ ጫጫታ ይታወካል)
አዎ ትቀነስ ! አይ የለም ለምን ሲባል ትቀነሳለች! ትቀነስ! አይ በጭራሽ !ወዘተ)
መስከረም :- ፀጥታ ፀጥታ ጸጥታ ይከበር
በጥሞና ሆነን በተራ እንምከር
(ጫጫታው እየጋለ ይሄዳል ሰብሳቢው መስከረም ቆም ብሎ ያጨበጭባል )
በመካከል የጷጉሜ የለቅሶ ድምጽ ይሰማል /
ጥቅምት :- ጷጉሜ እህታች በቶሎ አትከፊ
ሁሉን የሚቻለውን እርሱን ተደገፊ
ጉባኤው ተማክሮ አልወሰነምና
ፊትሽ እንዳይጨልም በሐምሌ ደመና
መስከረም :- እሺ አሁን ሁሉም በየተራ
ሀሳቡን ይሰጣል ገልጦ እያብራራ
ጥቅምት በሥርዓቱ በቅደም ተከተል ተራ ያሲዝና
ኅዳር ይጥፈዋል ሁሉን በጥሞና
ስለዚህ ወስኑ መክንያትን ይዛችሁ
ትቀነስ ትቀመጥ ጷጉሜን እህታችሁ?
(አሁንም ጫጫታው ይጀምራል )
መስከረም :- ሀሳብ ያለው ብቻ እጁ እያወጣ
ዕድሉን ሰሰጠው መልካም ምክሩን የምጣ
ከዛ በተረፈ ነውና ጉባኤ
ጫጫታን አልፈቅድም የጎንዮሽ ወሬ
ጥቅምት :- አዎን እሺ እዛ ጋር ወርኃ መጋቢት እጁን ስላወጣ
ታላቁ መስከረም ዕድል ይስጡትና ቆንጆ ሀሳብ ያምጣ
መስከረም :- እሺ መልካም ቀጥል
መጋቢት :- አመሰግናለው ሰብሳቢው መስከረም
ዕድል ስለሰጡኝ ከሁሉ በማቅደም
ክብረቴም ይድረሰው ለአሳላፊው ጥቅምት
የኔ እንኳን ሀሳቤ በጷጉሜ ወራችን
አትቀነስ ባይ ነኝ ትሩን ከጎናችን
እርሷ ብትለየን ከመካከላችን
እኩልነት ቀርቶ ይከራል ጠባችን
እኔ በበኩሌ ከ30ው ዕድሜዬ
መቀነስ አልሻም ከየወር ድርሻዬ
መስከረም :- መልካም ሌላ ባለ ሀሳብ
ጥቅምት :- እዛ ጋር ጥግ ላይ ሰኔ እያወጣች ነው
መስከረም :-እስቲ ሰኔ ተንፍሽ
ሰኔ :- አመሰግናለሁ ዕድል በመቸሬ
እኔ አላረዝምም አጭር ነች ነገሬ
ጷጉሜ ትቀነስ ወይ በሚለው ሀሳባችሁ
እኔ እስማማለው አጠቅምም ባካችሁ
ወይ ሞልታ ላትሞላ ይህቺ የቀን ጎደሎ
ውሳኔው ይወሰን ትወገድ በቶሎ
መስከረም : - እሺ ተቀበልንሽ ሰኔ ታዳሚያችን
ግን ግን ለመለየት ሳይሆን መሰባሰባችን
አንድ መሆን ነበር የኛ ዓላማችን
የሆነው ሆነና ሰብሳቢ ነኝና
ሁሉንም ሀሳቦች ልስማ በየፊና
አሁንም ቀጥዬ ዕድልን ልስጣችሁ
ከስካሁኑ ሁሉ የተለየ ሀሳብ ካለ መሃላችሁ
እጅ ክንዳችሁን አሳዮን አጉልታችሁ
ጥቅምት :- በዚ ጥግ ደግሞ ከተደረደሩት
የጥር እጅ እታያል ጋሼ ዕድል ይስጡት
መስከረም :- በል እሺ ተናገር ዕድል ሰጥቻለሁ
የሚያስማማን ሀሳብ ካንተ ዘንድ እሻለው
ጥር :- አመሰግናለሁ ወርሃ መስከረም
እኔም ባጭሩ ነው ነገር አላረዝምም
ትንሽ ሰው ትንሽ ነው ይላሉ ሰዎቹ
ዕውቀት የገባቸው ነገር አዋቆቹ
ማለቴ እነዛ ነጮቹ
ምንድነው ለማለት ባጭሩ የፈለኩ
ምንም አይመስለኝም ጷጉሜንም ብትነኩ
ትቀነስ ካላቹም ትቀነስ ግድ የለም
በኔ ሕልውና ላይ ለውጥን አያመጣም
ጥቅምት :- ጷጉሜን ሀሳብ አላት መስለኝ ቆማለች
ዕድል እንዲሰጣች ፍቃድ ከጅላለች
መስከረም :- እሺ አድምጠናል የጥርን ሀሳብ
ግን እንደታሰበው ውኃ አያነሳም
ጷጉሜ ስለቆመች ዕድልን ፈልጋ
እስቲ እናዳምጣት እንሁን ከእርሷ ጋር
ጷጉሜን :- ለሰው ሀገር ተሽጠው
ወርቅና ዋንጫው ያመጡ ሮጠው
ያናድደኝ ነበር እዚህ ሆኜ ሳየው
ለካ ተገፍተው ነው ፍቅርን ተነፍገው
እንዲህ ካሴራቹ እኔን ለማስቀረት
አብሮ አደግ ጓደኛን መለየት ነውር ከሌለበት
እኔም እሄዳለሁ ፍቅር ወዳለበት
( ብላ ጷጉሜ እያለቀሰች ስብሰባውን እረግጣ ትወጣለች )
ጥር :- ይህው አላልኳቹም ትንሽ ሰው ትንሽ ነው
እረግጣን የወጣች ቢናቅ ነው ጉባኤው
መስከረም :- መቋቋም ካልቻለች የመለየትዜንን
ብትወጣ ገድ የለም
ተገፍታም ተይዛመ ሁለት በደል የለም
(በጣም ተበሳጭቶ ዕድል ሳይሰጠው የካቲት ይነሳና)
የካቲት :- ጷጉሜ አትቀነስም እኔ ቆሜ ሳለሁ
በእርሷ ከመጣችሁ ሞቴን እመርጣለሁ
መኖር እየቻልን ሁላችን ተካተን
በነጭ ዲስኩር ወሬ እንዴት እናምናለን
እስቲ እነርሱ ራሱ ከወራቶቻቸው
በ11ዱ ይቅሩ አንዱን ወር ቀንሰው
ፊደሉ ይቀነስ ወራቱ ይቀነስ
ምን የሚሉት እብደት ምን ዐይነት መቃወስ
ዓለም እየሳቀ በጅጉ እንዳይንቀን
እንቀነስ ስንል በመደመር ዘመን
እግዚአብሔር ለማለት God ን ስትጽፉ
Gን ካቲታል አርጓት ከእውቀት እንዳትነጥፉ
እግዚአብሔር ለማለት ጣዖት እዳጥፉ
ብለው የሚነተርኩን በነጋ በጠባ
የእነርሱ ፊደል ነው ምሥጢር ትርጉሜ አልባ
የኛን ፊደላት ሀሌንታዋ "ሀ " ብናይ
ጊዜ አይበቃኝም ግን ለምሳሌው ለጉባኤው
ሀሌታ ሀ ማለት ብሒል ሀልቱ ለአብ እም ቅድመ ዓለም
የአብ አኗኗሩ የቀደመ ካለም
መክሼ ሆና ሳለ ካሌታዋ ጋር
ሐ መሩሐ ሐ ግን ልዩ ናት በምሥጢር
ሐመ ሞተ በእንአነ ስለኛ ሞተ ብላ የምታመሰጥ
ስለዚህ ወንድሞቼ ሁላችን ሁላችን
የፈረንጅ ነገር ክፉ ምክርን ትተን
የባቶቻችንን ቃል ወንጌል ተምኩዘን
በጭኸወት የማይፈርስ በከንቱ ማላዘን
ባንድነት እንኑር በፍቅር ኢያሪኮ ዙሪያችንን አጥረን
(ጭብጨባው ከዳር እስከዳር አዳራሹን ያናጋዋል
መስከረም :- እድሉን ሳልሰጥህ ያወራህ ቢሆንም
ፍቅርን ስለሰበክ አልቃወምህም
ሰለዚህ እግዚአብሔር ያክብርህ የካቲት አስተዋይ
የአባቶችን ትዕዛዝ አደራ ተቀባይ
ጷጉሜን ርቃ ሳትሄድ በኛ ተበሳጭታ
ይቅርታ ትጠየቅ በክብር ተጠርታ
ጠቡ ይቅርና መናናቅ ተረስቶ
መኖሩ ይሻለላል በአናድነት ተካቶ
ጥቅምት ፍጠንና ይዘአት ና ቶሎ
መስከረም ፦ በመስከረም
ወራት ፦ ስፍራው ሁሉ ለምለም
መስከረም ፦ በጥቅምት
ወራት ፦ አንድ አጥንት
መስከረም ፦ በኅዳር
ወራት ፦ እሸት ከእዳር እዳር
መስከረም ፦ በታህሳስ
ወራት ፦ ጎተራህን አብስ
መስከረም ፦ በጥር
ወራት ፦ ምርትህን አበጥር
መስከረም ፦ የካቲት
ወራት ፦ አዝመራህን ክተት
መስከረም ፦ መጋቢት
ወራት ፦ እረስ ለወደፊት
መስከረም ፦ በሚያዝያ
ወራት ፦ ፀሐይ እዚህ እዛህ
መስከረም ፦ ግንቦት
ወራት ፦ ፀሐይ አናት አናት
መስከረም ፦ በሰኔ
ወራት ፦ ዝናቡን ወደኔ
መስከረም ፦ በሐምሌ
ወራት ፦ ልኑር እነደ አመሌ
መስከረም ፦ በነሐሴ
ወራት ፦ ትንፍስ አለች ነፍሴ
መስከረም ፦ በጷጉሜ
ወራት ፦ እስቲ ልዘጋጀው አዲስ ሕልም አልሜ
(ጭብጨባው ከዳር እስከዳር አዳራሹን ያናጋዋል)
ተፈጸመ
ከ ተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
ሰኔ 19/2014 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
ጊዜ አይበቃኝም ግን ለምሳሌው ለጉባኤው
ሀሌታ ሀ ማለት ብሒል ሀልቱ ለአብ እም ቅድመ ዓለም
የአብ አኗኗሩ የቀደመ ካለም
መክሼ ሆና ሳለ ካሌታዋ ጋር
ሐ መሩሐ ሐ ግን ልዩ ናት በምሥጢር
ሐመ ሞተ በእንአነ ስለኛ ሞተ ብላ የምታመሰጥ
ስለዚህ ወንድሞቼ ሁላችን ሁላችን
የፈረንጅ ነገር ክፉ ምክርን ትተን
የባቶቻችንን ቃል ወንጌል ተምኩዘን
በጭኸወት የማይፈርስ በከንቱ ማላዘን
ባንድነት እንኑር በፍቅር ኢያሪኮ ዙሪያችንን አጥረን
(ጭብጨባው ከዳር እስከዳር አዳራሹን ያናጋዋል
መስከረም :- እድሉን ሳልሰጥህ ያወራህ ቢሆንም
ፍቅርን ስለሰበክ አልቃወምህም
ሰለዚህ እግዚአብሔር ያክብርህ የካቲት አስተዋይ
የአባቶችን ትዕዛዝ አደራ ተቀባይ
ጷጉሜን ርቃ ሳትሄድ በኛ ተበሳጭታ
ይቅርታ ትጠየቅ በክብር ተጠርታ
ጠቡ ይቅርና መናናቅ ተረስቶ
መኖሩ ይሻለላል በአናድነት ተካቶ
ጥቅምት ፍጠንና ይዘአት ና ቶሎ
መስከረም ፦ በመስከረም
ወራት ፦ ስፍራው ሁሉ ለምለም
መስከረም ፦ በጥቅምት
ወራት ፦ አንድ አጥንት
መስከረም ፦ በኅዳር
ወራት ፦ እሸት ከእዳር እዳር
መስከረም ፦ በታህሳስ
ወራት ፦ ጎተራህን አብስ
መስከረም ፦ በጥር
ወራት ፦ ምርትህን አበጥር
መስከረም ፦ የካቲት
ወራት ፦ አዝመራህን ክተት
መስከረም ፦ መጋቢት
ወራት ፦ እረስ ለወደፊት
መስከረም ፦ በሚያዝያ
ወራት ፦ ፀሐይ እዚህ እዛህ
መስከረም ፦ ግንቦት
ወራት ፦ ፀሐይ አናት አናት
መስከረም ፦ በሰኔ
ወራት ፦ ዝናቡን ወደኔ
መስከረም ፦ በሐምሌ
ወራት ፦ ልኑር እነደ አመሌ
መስከረም ፦ በነሐሴ
ወራት ፦ ትንፍስ አለች ነፍሴ
መስከረም ፦ በጷጉሜ
ወራት ፦ እስቲ ልዘጋጀው አዲስ ሕልም አልሜ
(ጭብጨባው ከዳር እስከዳር አዳራሹን ያናጋዋል)
ተፈጸመ
ከ ተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
ሰኔ 19/2014 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
#እራስህን ፈትሽ
የዛሬ ዓመት አካባቢ ነው ወቅቱ እንደ አሁኑ የሽብር ቡድኑ እና የcovid 19 ስጋት መንግስትን ያስጨነቀበት ወቅት ነው። ምሽት አካባቢ አገልገሎት ጨርሰን ወደ ሰፈር እያመራን ነው። የጸጥታ ኃይሎች (የፌደራል ፖሊሶች) በየ አስፋልቱ መዐዘናት ቆመው አላፊ አግዳዊውን አስቁመው እንደ መፈተሽ ዐይነት ነገር ይሰራሉ።
#እኛም ወደ ሰፈር ለመግባት ጥቂት ኪሎ ሜትሮች ሲቀሩን በአንዱ አስፋልት ላይ መንገዱን አጥረውት አገኘንና ለመፈተሽ ተበታትነት ወደ ጸጥታ ኃይሎቹ ቀረብን ።እኔ በበኩሌ እጄን ከኪሴ አውጥቼ ወደ ግራና ወደ ቀኝ ዘርግቼ የመስቀል ምልክት ሰርቼ ለመፈተሽ ተዘጋጀው ፊት ለፊቴ ያለው ፖሊስ ግን ምንም የመፈተሽ አዝማሚያ ሳያሳይ የሆነ ነገር ተናገረ ግራ ገባኝና ይህው አልኩት ዝግጁ መሆኔን ለማሳወቅ #እራስህን_ፈትሺ አትሰሚም እንዴ? ሲል ጮክ ብሎ ደገመው አንደኛ እና ሁለተኛ መደብ እንዲሁም ጾታ ነጠላና ብዙ ቁጥር የማይለየው ንግግሩ ከወዴት እንደሆነ ጠቆመኝ ያው የወድሄት ነህ ዘመን ላይ አይደለን ?!
እውነት ለመናገር እራስህን ፈትሽ እንዳለኝ መጀመሪያውኑ ሰምቼዋለው ግን እራሴን ፈትሼ ንጹዑ ነኝ ምንም አልያስኩም ነው የምለው? ወይስ ይህው ሁለት ስለትና አንድ ተቀጣጣይ ፈንጂ ከኋላ ኪሴ ይዣለሁ ብዬ እራሴን እንዳጋልጥ ነው የፈለገው ብዬ ግራ ስለገባኝ ነው።
#እንዴት እራስህን ፈትሽ ሊለኝ ይችላል ብዬ እርግጠኛ ለመሆን ለሦስተኛ ጊዜ በድጋሚ እህህ ልል አሰብኩና ወዲያው ማዳመጫዬን ከማላመጫዬ ሲደባልቀው ስለታየኝ ተውኩት ከዛም የሰማሁትን ግን ያልገባኝን ንግግሩን መተግበር ጀመርኩ ።እራሴን እንደነገሩ ዳባበስኩና ይህው የለም ስለው መንገዱን ከፍቶ እንዳልፍ ፈቀደልኝ።
እስከ ዛሬ ድረስ ማለትም ለ365 ቀናት ከ 91ኬክሮስ ድረስ ፖሊሱን እንደ ሞኝ ቆጥሬ ስስቅ ነበር። ያሳቀኝ ለcovid 19 ተዛማችነት ያሳየውን ጥንቃቄ ከግምት ውስጥ በለማስገባት አይደለም ። በዚህች በራስ ወዳድ ዓለም ሳለን ማን እራሱን ፈትሾ ጥፋተኛ ነኝ ልቀጣ ይገባኛል ሊል ይችላል ቤዬ ስላሰብኩ ነው እንጂ።
#አሁን ግን ዓመቱን ሙሉ ስስቅ የከረምኩት በራሴ መሆኑ ዘግይቶ ገባኝ ።ሰው ለራሱ ታማኝ ከሆነ በፍጹም ለሌላው መታመን አያቅተውም። አንባቢ ሆይ አንተ እራስህን በታማኝነት ስራው ከዛ በብዙ አማኞች ትከበባለህ አንተ ቀድመህ እራስህን ከፈተሽክ ማንም አንተን ሊፈትሽህ አይችልም ቢፈትሽ እንኳ ትርፉ ድካም ብቻ ነው ።ምንም አይገኝብህምና !
“እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ።”
|1ኛ #ጴጥ 2፥5
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጳጉሜ 2/2014 ዓ.ም
የዛሬ ዓመት አካባቢ ነው ወቅቱ እንደ አሁኑ የሽብር ቡድኑ እና የcovid 19 ስጋት መንግስትን ያስጨነቀበት ወቅት ነው። ምሽት አካባቢ አገልገሎት ጨርሰን ወደ ሰፈር እያመራን ነው። የጸጥታ ኃይሎች (የፌደራል ፖሊሶች) በየ አስፋልቱ መዐዘናት ቆመው አላፊ አግዳዊውን አስቁመው እንደ መፈተሽ ዐይነት ነገር ይሰራሉ።
#እኛም ወደ ሰፈር ለመግባት ጥቂት ኪሎ ሜትሮች ሲቀሩን በአንዱ አስፋልት ላይ መንገዱን አጥረውት አገኘንና ለመፈተሽ ተበታትነት ወደ ጸጥታ ኃይሎቹ ቀረብን ።እኔ በበኩሌ እጄን ከኪሴ አውጥቼ ወደ ግራና ወደ ቀኝ ዘርግቼ የመስቀል ምልክት ሰርቼ ለመፈተሽ ተዘጋጀው ፊት ለፊቴ ያለው ፖሊስ ግን ምንም የመፈተሽ አዝማሚያ ሳያሳይ የሆነ ነገር ተናገረ ግራ ገባኝና ይህው አልኩት ዝግጁ መሆኔን ለማሳወቅ #እራስህን_ፈትሺ አትሰሚም እንዴ? ሲል ጮክ ብሎ ደገመው አንደኛ እና ሁለተኛ መደብ እንዲሁም ጾታ ነጠላና ብዙ ቁጥር የማይለየው ንግግሩ ከወዴት እንደሆነ ጠቆመኝ ያው የወድሄት ነህ ዘመን ላይ አይደለን ?!
እውነት ለመናገር እራስህን ፈትሽ እንዳለኝ መጀመሪያውኑ ሰምቼዋለው ግን እራሴን ፈትሼ ንጹዑ ነኝ ምንም አልያስኩም ነው የምለው? ወይስ ይህው ሁለት ስለትና አንድ ተቀጣጣይ ፈንጂ ከኋላ ኪሴ ይዣለሁ ብዬ እራሴን እንዳጋልጥ ነው የፈለገው ብዬ ግራ ስለገባኝ ነው።
#እንዴት እራስህን ፈትሽ ሊለኝ ይችላል ብዬ እርግጠኛ ለመሆን ለሦስተኛ ጊዜ በድጋሚ እህህ ልል አሰብኩና ወዲያው ማዳመጫዬን ከማላመጫዬ ሲደባልቀው ስለታየኝ ተውኩት ከዛም የሰማሁትን ግን ያልገባኝን ንግግሩን መተግበር ጀመርኩ ።እራሴን እንደነገሩ ዳባበስኩና ይህው የለም ስለው መንገዱን ከፍቶ እንዳልፍ ፈቀደልኝ።
እስከ ዛሬ ድረስ ማለትም ለ365 ቀናት ከ 91ኬክሮስ ድረስ ፖሊሱን እንደ ሞኝ ቆጥሬ ስስቅ ነበር። ያሳቀኝ ለcovid 19 ተዛማችነት ያሳየውን ጥንቃቄ ከግምት ውስጥ በለማስገባት አይደለም ። በዚህች በራስ ወዳድ ዓለም ሳለን ማን እራሱን ፈትሾ ጥፋተኛ ነኝ ልቀጣ ይገባኛል ሊል ይችላል ቤዬ ስላሰብኩ ነው እንጂ።
#አሁን ግን ዓመቱን ሙሉ ስስቅ የከረምኩት በራሴ መሆኑ ዘግይቶ ገባኝ ።ሰው ለራሱ ታማኝ ከሆነ በፍጹም ለሌላው መታመን አያቅተውም። አንባቢ ሆይ አንተ እራስህን በታማኝነት ስራው ከዛ በብዙ አማኞች ትከበባለህ አንተ ቀድመህ እራስህን ከፈተሽክ ማንም አንተን ሊፈትሽህ አይችልም ቢፈትሽ እንኳ ትርፉ ድካም ብቻ ነው ።ምንም አይገኝብህምና !
“እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ።”
|1ኛ #ጴጥ 2፥5
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጳጉሜ 2/2014 ዓ.ም