ዐውደ ምሕረት
3.68K subscribers
930 photos
24 videos
271 files
193 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
በዚህ ዘመን ዶሮ መሆን በራሱ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ መታደል ነው።
#እንዴት?
በውድ ነዋ የምትሸጪው !
#በውድ ተሸጭክም ፤ በርካሽ ያው መታረድህ አይቀር
ቢሆንም በክብር ተሽጦ ክብርን በሚመጥን መንገድ መሞት ሰማዕትነት ነው ።
#በርኳሽ ስትሸጥ መቆየትህ ቁጭት አሳድሮብሃል ማለት ነው?
እንዴታ ለምን አያሳድርብኝም የዛሬን አያድርገውና ኮ እኛ የነ አይደፈሩ የነ ዳይኖንሰር ዘር እኮነን። ዶሮ የዳይነንሰር የመጨረሻ ዝርያው ነው ያሉትን የሳይንቲስቶች ምርምር አልሰማሽምን?
#ዶሮን ሲያታልሏት ዳይኖሰር ነሽ አሏት ኩኩኩኩኩኩኩ
ምን ያስካካሻል ውሸት ነው ልትይ ነው ዳይኖንሰርም ዶሮም ተመሳሳይ አቆም እንዳላቸው እራስሽ ማረጋገጥ ትቺያለሽ
#እንዴት አረጊ?
ላባው የተራገፈ አንድ ዶሮና አንድ ዳይኖንሰር በአምሮሽ ሳይ በሁለት እግራቸው የቆሙ
ሁለት እጃቸው አጠር ብሎ ወደ ደረታቸው የተጠጋ በመጠን ብቻ የሚለያዮ ተመሳሳይ ፍጥረት ይመጣልሻል።
#አስብኩት..... በእውነቱ እውነት ይመስላል ። ቆይ ግን አንተ መታረድህ ነው ወይስ የነ ዳይኖንሰር ዘር ሆኜ እንዴት በርኳሽ ተሽጬ እታረዳለሁ የሚለው ነው የሚያሳስብህ ?
ሁለቱም ያሳስቡኛል ክብሬም ሕይወቴም
#ወገኛ የቱ ክብርህ የክብር ባለቤት እንኳ በሰላሳ ዲናር ተሽጦ ያለ እርራዬ መታረዱን አትዘንጋ።
ዛሬ ጥሬ ስትለቅሚ የነበረው ከ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ነበር እንዴ?
#እንዴ አዎ ለምን ጠየከኝ?
ሰባኪ መሰልሽኛ!
#እእእእ_በነገራችን ላይ ላስተዋለው ሁሉም ፍጥረት በራሱ ሰባኪ ነው “ሰማያት #የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ ” እንዳለ መጻሕፉ መዝ 19፥1

አሁን ከካህናቱ ጋር ሰንበቴ እንደምትቀመጪ ጭምር አረጋገጥኩ። ለነገሩ እታች ሰፈር ጥሬ ፍለጋ እያልሽ ገብስማው ዶሮጋ ከምትሄዲብኝ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መሄድሽ ይሻለኛል።

" #የአውራ ዶሮ ወዳጅ መች ጠርቶ ሊጠራ
ሲወጡ ሲገቡ ሁል ጊዜ ጥርጠራ"

ምን አልሽ አንቺ ??

#አረ ጌታው ምንም አላልኩም ወዲ ነው
እኔ የምለው እስከ ዛሬ መታረዴ ሳይሆን በርኳሽ ስሸጥ መቆየቴ የግር እሳት ሆኖብኛል እያልክ ነው።
#አዎን
ለምን ይመስልሃል ግን ዋጋችን እንዲህ ውድ የሆነው?
#እኔ ምን አውቃለሁ አንቺን ልጠይቅሽ እንጂ ግን ፈጣሪ መናቃችንን አይቶ እየካሰን ይመስለኛል

አይደለም ባክህ ሰው ስለረከሰ ነው።
#አታመጪው ጉድ የለ !። ምን?
አዎ ወዳጄ ሰው ሲረክስ ለሰው የተዘጋጁት ነገረሮች ሁሉ ይወደዱበታል በስግብግብነት ሲረክስ በአቋራጭ ለመበልጸግ ሲረክስ ነገሮች ሁሉ ውድ ይሆኑበታል።

#ይልቁኑ በበዓላት ሁሉም ሲወደድ ካየህ የሰው ልጅ እረክሷል ማለት ነው

ስኳር ውስጥ ሩዝ ፣በርበሬ ውስጥ ሸክላ ፣ቅቤ ውስጥ ሙዝ ፣እንጀራ ወስጥ ጀሶ የሚጨምረው ቢረክስ አይደለምን??!
#ሊጡ ውስጥ እንኳ ጀሶ መኖሩ አሁን አሁን ሳስበው ጥሩ መሰለኝ
እንዴት?
#ያው ያ ሀገር አቆርቋዥ ጁንታ እንደልማዱ ሰርቆ ሲጠጣ አድርቆ ያስቀርልናል።

የሚገርመው እንደዚህ በዐድ ነገር ቀላቅሎ እንኳን የሚሸጭበት ዋጋ የትዬ ለሌ ነው። ይህ እጅግ በጣም መውረዱን ነው የሚያሳየው።
#የኔ_ውድ ምን አልባት እኛም የተወደድነው እንተ እንዳልከው የዳይኖሰር ዘሮች ስለሆንን ሳይሆን ከሆነ በዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ሊሆን ይችላል ። በዘርህ ማሰብህ አቁም
ምን ? ከብዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ይሆናል? ለዛነው ሣር ሳይ ጋጥ ጋጥ ፣ሜዳ ሳይ ደግሞ ተደባለል ተደባለል የሚለኝ ?
#አዎን የሐበሻውን ዶሮ ከፈረንጅ ዶሮ ጋር የፈረንጁን ዶሮ ከሰጎን እዋስ ጋር መቀላቀሉ ሳይንስ ዐዋቂነት ሆኟል።
ሰው ግን ለምን እንዲህ ከፋ ?
#ያወቀ እየመሰለው አንድም ጽድቅና ኩነኔን ቢረሳ ነዋ እኛኸ ታላቅ ሰው ያሉትን የሚያስተውል መቼ ይሆን ? "ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፉት ደግነት ሳይሻል አይቀርም"
አ.አ ኢትዮጵያ
ኃ/ማርያም ተርቢኖስ ሰብስቤ
ታኅሣሥ 28 ቀን 2014 ዓ.ም
በዚህ ዘመን ዶሮ መሆን በራሱ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ መታደል ነው።
#እንዴት?
በውድ ነዋ የምትሸጪው !
#በውድ ተሸጭክም ፤ በርካሽ ያው መታረድህ አይቀር
ቢሆንም በክብር ተሽጦ ክብርን በሚመጥን መንገድ መሞት ሰማዕትነት ነው ።
#በርኳሽ ስትሸጥ መቆየትህ ቁጭት አሳድሮብሃል ማለት ነው?
እንዴታ ለምን አያሳድርብኝም ? አታስታውሺም ፈንግል የተባለ በርድ ፍሎ የወፍ ጉንፋን በሽታ የመጣ ጊዜ ሁለት ዶሮ በ1ብር የተሸጠበትን የቅርብ ጊዜ ታሪክ? ይህው ዛሬ የሰው ጉንፋን covid 19 መጣና ሰው ረክሶ እኛ ተወደድን ለነገሩ የ ዛሬን አያድርገውና ከጅምሩ እኛኮ እኛ የነ አይደፈሩ የነ ዳይኖንሰር ዘር እኮነን ። ዶሮ የዳይነንሰር የመጨረሻ ዝርያው ነው ያሉትን የሳይንቲስቶች ምርምር አልሰማሽምን?
#ዶሮን ሲያታልሏት ዳይኖሰር ነሽ አሏት ኩኩኩኩኩኩኩ
ምን ያስካካሻል ውሸት ነው ልትይ ነው ዳይኖንሰርም ዶሮም ተመሳሳይ አቆም እንዳላቸው እራስሽ ማረጋገጥ ትቺያለሽ
#እንዴት አረጊ?
ላባው የተራገፈ አንድ ዶሮና አንድ ዳይኖንሰር በአምሮሽ ሳይ በሁለት እግራቸው የቆሙ
ሁለት እጃቸው አጠር ብሎ ወደ ደረታቸው የተጠጋ በመጠን ብቻ የሚለያዮ ተመሳሳይ ፍጥረት ይመጣልሻል።
#አስብኩት..... በእውነቱ እውነት ይመስላል ። ቆይ ግን አንተ መታረድህ ነው ወይስ የነ ዳይኖንሰር ዘር ሆኜ እንዴት በርኳሽ ተሽጬ እታረዳለሁ የሚለው ነው የሚያሳስብህ ?
ሁለቱም ያሳስቡኛል ክብሬም ሕይወቴም
#ወገኛ የቱ ክብርህ የክብር ባለቤት እንኳ በሰላሳ ዲናር ተሽጦ ያለ እርራዬ መታረዱን አትዘንጋ።
ዛሬ ጥሬ ስትለቅሚ የነበረው ከ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ነበር እንዴ?
#እንዴ አዎ ለምን ጠየከኝ?
ሰባኪ መሰልሽኛ!
#እእእእ_በነገራችን ላይ ላስተዋለው ሁሉም ፍጥረት በራሱ ሰባኪ ነው “ሰማያት #የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ ” እንዳለ መጻሕፉ መዝ 19፥1

አሁን ከካህናቱ ጋር ሰንበቴ እንደምትቀመጪ ጭምር አረጋገጥኩ። ለነገሩ እታች ሰፈር ጥሬ ፍለጋ እያልሽ ገብስማው ዶሮጋ ከምትሄዲብኝ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መሄድሽ ይሻለኛል።

" #የአውራ ዶሮ ወዳጅ መች ጠርቶ ሊጠራ
ሲወጡ ሲገቡ ሁል ጊዜ ጥርጠራ"

ምን አልሽ አንቺ ??

#አረ ጌታው ምንም አላልኩም ወዲ ነው
እኔ የምለው እስከ ዛሬ መታረዴ ሳይሆን በርኳሽ ስሸጥ መቆየቴ የግር እሳት ሆኖብኛል እያልክ ነው።
#አዎን
ለምን ይመስልሃል ግን ዋጋችን እንዲህ ውድ የሆነው?
#እኔ ምን አውቃለሁ አንቺን ልጠይቅሽ እንጂ ግን ፈጣሪ መናቃችንን አይቶ እየካሰን ይመስለኛል

አይደለም ባክህ ሰው ስለረከሰ ነው።
#አታመጪው ጉድ የለ !። ምን?
አዎ ወዳጄ ሰው ሲረክስ ለሰው የተዘጋጁት ነገረሮች ሁሉ ይወደዱበታል በስግብግብነት ሲረክስ በአቋራጭ ለመበልጸግ ሲረክስ ነገሮች ሁሉ ውድ ይሆኑበታል።

#ይልቁኑ በበዓላት ሁሉም ሲወደድ ካየህ የሰው ልጅ እረክሷል ማለት ነው

ስኳር ውስጥ ሩዝ ፣በርበሬ ውስጥ ሸክላ ፣ቅቤ ውስጥ ሙዝ ፣እንጀራ ወስጥ ጀሶ የሚጨምረው ቢረክስ አይደለምን??!
#ሊጡ ውስጥ እንኳ ጀሶ መኖሩ አሁን አሁን ሳስበው ጥሩ መሰለኝ
እንዴት?
#ያው ያ ሀገር አቆርቋዥ ጁንታ እንደልማዱ ሰርቆ ሲጠጣ አድርቆ ያስቀርልናል።

የሚገርመው እንደዚህ በዐድ ነገር ቀላቅሎ እንኳን የሚሸጭበት ዋጋ የትዬ ለሌ ነው። ይህ እጅግ በጣም መውረዱን ነው የሚያሳየው።
#የኔ_ውድ ምን አልባት እኛም የተወደድነው እንተ እንዳልከው የዳይኖሰር ዘሮች ስለሆንን ሳይሆን ከሆነ በዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ሊሆን ይችላል ። በዘርህ ማሰብህ አቁም
ምን ? ከብዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ይሆናል? ለዛነው ሣር ሳይ ጋጥ ጋጥ ፣ሜዳ ሳይ ደግሞ ተደባለል ተደባለል የሚለኝ ?
#አዎን የሐበሻውን ዶሮ ከፈረንጅ ዶሮ ጋር የፈረንጁን ዶሮ ከሰጎን እዋስ ጋር መቀላቀሉ ሳይንስ ዐዋቂነት ሆኟል።
ሰው ግን ለምን እንዲህ ከፋ ?
#ያወቀ እየመሰለው አንድም ጽድቅና ኩነኔን ቢረሳ ነዋ እኛኸ ታላቅ ሰው ያሉትን የሚያስተውል መቼ ይሆን ? "ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፉት ደግነት ሳይሻል አይቀርም"
አ.አ ኢትዮጵያ
ኃ/ማርያም ተርቢኖስ ሰብስቤ
ታኅሣሥ 28 ቀን 2014 ዓ.ም
#እራስህን ፈትሽ

የዛሬ ዓመት አካባቢ ነው ወቅቱ እንደ አሁኑ የሽብር ቡድኑ እና የcovid 19 ስጋት መንግስትን ያስጨነቀበት ወቅት ነው። ምሽት አካባቢ አገልገሎት ጨርሰን ወደ ሰፈር እያመራን ነው። የጸጥታ ኃይሎች (የፌደራል ፖሊሶች) በየ አስፋልቱ መዐዘናት ቆመው አላፊ አግዳዊውን አስቁመው እንደ መፈተሽ ዐይነት ነገር ይሰራሉ።

#እኛም ወደ ሰፈር ለመግባት ጥቂት ኪሎ ሜትሮች ሲቀሩን በአንዱ አስፋልት ላይ መንገዱን አጥረውት አገኘንና ለመፈተሽ ተበታትነት ወደ ጸጥታ ኃይሎቹ ቀረብን ።እኔ በበኩሌ እጄን ከኪሴ አውጥቼ ወደ ግራና ወደ ቀኝ ዘርግቼ የመስቀል ምልክት ሰርቼ ለመፈተሽ ተዘጋጀው ፊት ለፊቴ ያለው ፖሊስ ግን ምንም የመፈተሽ አዝማሚያ ሳያሳይ የሆነ ነገር ተናገረ ግራ ገባኝና ይህው አልኩት ዝግጁ መሆኔን ለማሳወቅ #እራስህን_ፈትሺ አትሰሚም እንዴ? ሲል ጮክ ብሎ ደገመው አንደኛ እና ሁለተኛ መደብ እንዲሁም ጾታ ነጠላና ብዙ ቁጥር የማይለየው ንግግሩ ከወዴት እንደሆነ ጠቆመኝ ያው የወድሄት ነህ ዘመን ላይ አይደለን ?!
እውነት ለመናገር እራስህን ፈትሽ እንዳለኝ መጀመሪያውኑ ሰምቼዋለው ግን እራሴን ፈትሼ ንጹዑ ነኝ ምንም አልያስኩም ነው የምለው? ወይስ ይህው ሁለት ስለትና አንድ ተቀጣጣይ ፈንጂ ከኋላ ኪሴ ይዣለሁ ብዬ እራሴን እንዳጋልጥ ነው የፈለገው ብዬ ግራ ስለገባኝ ነው።
#እንዴት እራስህን ፈትሽ ሊለኝ ይችላል ብዬ እርግጠኛ ለመሆን ለሦስተኛ ጊዜ በድጋሚ እህህ ልል አሰብኩና ወዲያው ማዳመጫዬን ከማላመጫዬ ሲደባልቀው ስለታየኝ ተውኩት ከዛም የሰማሁትን ግን ያልገባኝን ንግግሩን መተግበር ጀመርኩ ።እራሴን እንደነገሩ ዳባበስኩና ይህው የለም ስለው መንገዱን ከፍቶ እንዳልፍ ፈቀደልኝ።

እስከ ዛሬ ድረስ ማለትም ለ365 ቀናት ከ 91ኬክሮስ ድረስ ፖሊሱን እንደ ሞኝ ቆጥሬ ስስቅ ነበር። ያሳቀኝ ለcovid 19 ተዛማችነት ያሳየውን ጥንቃቄ ከግምት ውስጥ በለማስገባት አይደለም ። በዚህች በራስ ወዳድ ዓለም ሳለን ማን እራሱን ፈትሾ ጥፋተኛ ነኝ ልቀጣ ይገባኛል ሊል ይችላል ቤዬ ስላሰብኩ ነው እንጂ።

#አሁን ግን ዓመቱን ሙሉ ስስቅ የከረምኩት በራሴ መሆኑ ዘግይቶ ገባኝ ።ሰው ለራሱ ታማኝ ከሆነ በፍጹም ለሌላው መታመን አያቅተውም። አንባቢ ሆይ አንተ እራስህን በታማኝነት ስራው ከዛ በብዙ አማኞች ትከበባለህ አንተ ቀድመህ እራስህን ከፈተሽክ ማንም አንተን ሊፈትሽህ አይችልም ቢፈትሽ እንኳ ትርፉ ድካም ብቻ ነው ።ምንም አይገኝብህምና !
“እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ።”
|1ኛ #ጴጥ 2፥5

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጳጉሜ 2/2014 ዓ.ም