#ረቡዕ #የምክር_ቀን
" #ምስጉን_ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ"
_______________________
#መዝ 1÷1
ይህ ዕለት የምክር ቀን ይባላል፣ ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጻሕፋት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር የጀመሩበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ ወቅቱ አይሁድ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት በመሆኑና ብዙ ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረከ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለነበር ምናልባት ሁከት ይፈጠራል ብለው ሕዝብን እየፈሩ ሊይዙት ያመነቱ ነበር። ተሳክቶላቸው እንያዘው ቢሉ እንኳን ኢየሱስ ክርስቶስን ከደቀ መዛሙርቱ ለይተው አያውቁትም ስለዚህ እርሱን በቅርብ የሚያውቅ ሰው ያስፈልጋቸዋልና በክፉ ምክራቸው እጅግ ተጨነቁ። ትንሽ ቆይቶ ግን ከደቀመዛሙርቱ መካከል አንዱ የሆነው የአስቆሮቱ ይሁዳ በክፉ ምክራቸው በመሳተፍ ጌታን በመሳም አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ቃል ገባላቸው ። ለምልክት ይሁናቸውም ዘንድም እኔ ሄጄ የምስመው ሰው እርሱ ክርስቶስ ነውና ያዙት ብሎ ተማከረ ጭንቀታቸው ተወገደ ለወረታውም ሰላሣ ብር መዘኑለት (ማቴ 26፡1-5 ፣ ማቴ26፡14-15 ፣ ማር 14፡1-2፣ ሉቃ 22፡1-6)
#ዕለተ_ረቡዕ_መልካም_መዓዛ_ያለው_ቀንም_ይባላል፣ ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት (ባለ ሽቶዋ ማርያም) ከእንግዲህ ወዲህ በኅጢዓት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ፣ ኀጢዓትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ፣ በአልባሲጥሮስ ብልቃጥ የሞላ ሽቱ ይዛ በመሄድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ነው፡፡ የእንባ ቀን ይባላል ይህም ስያሜ የተሰጠበት ምክንያት ይህችው ማርያም እንተእፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢዓቷን ይቅር እንዲልላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና፣ በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና፡፡ በጠጉሯም ማበሶ አክሊሌ ነክ ስትል ነው ። የማርያም እንተእፍረትን ኃጢዓት ይቅር ብሎ መባዋን የተቀበለ አምላክ ዛሬ በመካከላችን አለና በማንኛውም ጊዜና ሰዓት የራሳችንን ኃጢዓት በማሰብ በማልቀስና የተወደደ መስዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር በማቅረብ በመልካም ሥራዋ ልንመስላት ይገባል፡፡ (ማቴ 26፡6-13 ፣ ሉቃ 7፡36 ፣ ማር 14፡3-9 ፣ ዮሐ 12፡1-8)
...........ይቆየን…..........
#ዐውደ_ምሕረት_የእናንተ
" #ምስጉን_ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ"
_______________________
#መዝ 1÷1
ይህ ዕለት የምክር ቀን ይባላል፣ ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጻሕፋት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር የጀመሩበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ ወቅቱ አይሁድ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት በመሆኑና ብዙ ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረከ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለነበር ምናልባት ሁከት ይፈጠራል ብለው ሕዝብን እየፈሩ ሊይዙት ያመነቱ ነበር። ተሳክቶላቸው እንያዘው ቢሉ እንኳን ኢየሱስ ክርስቶስን ከደቀ መዛሙርቱ ለይተው አያውቁትም ስለዚህ እርሱን በቅርብ የሚያውቅ ሰው ያስፈልጋቸዋልና በክፉ ምክራቸው እጅግ ተጨነቁ። ትንሽ ቆይቶ ግን ከደቀመዛሙርቱ መካከል አንዱ የሆነው የአስቆሮቱ ይሁዳ በክፉ ምክራቸው በመሳተፍ ጌታን በመሳም አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ቃል ገባላቸው ። ለምልክት ይሁናቸውም ዘንድም እኔ ሄጄ የምስመው ሰው እርሱ ክርስቶስ ነውና ያዙት ብሎ ተማከረ ጭንቀታቸው ተወገደ ለወረታውም ሰላሣ ብር መዘኑለት (ማቴ 26፡1-5 ፣ ማቴ26፡14-15 ፣ ማር 14፡1-2፣ ሉቃ 22፡1-6)
#ዕለተ_ረቡዕ_መልካም_መዓዛ_ያለው_ቀንም_ይባላል፣ ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት (ባለ ሽቶዋ ማርያም) ከእንግዲህ ወዲህ በኅጢዓት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ፣ ኀጢዓትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ፣ በአልባሲጥሮስ ብልቃጥ የሞላ ሽቱ ይዛ በመሄድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ነው፡፡ የእንባ ቀን ይባላል ይህም ስያሜ የተሰጠበት ምክንያት ይህችው ማርያም እንተእፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢዓቷን ይቅር እንዲልላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና፣ በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና፡፡ በጠጉሯም ማበሶ አክሊሌ ነክ ስትል ነው ። የማርያም እንተእፍረትን ኃጢዓት ይቅር ብሎ መባዋን የተቀበለ አምላክ ዛሬ በመካከላችን አለና በማንኛውም ጊዜና ሰዓት የራሳችንን ኃጢዓት በማሰብ በማልቀስና የተወደደ መስዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር በማቅረብ በመልካም ሥራዋ ልንመስላት ይገባል፡፡ (ማቴ 26፡6-13 ፣ ሉቃ 7፡36 ፣ ማር 14፡3-9 ፣ ዮሐ 12፡1-8)
...........ይቆየን…..........
#ዐውደ_ምሕረት_የእናንተ
📢ዓውደ ምህረት 🎤
#ዕለተ_ሐሙስ
#ሕፅበተ_ሐሙስ_ይባላል
__________________
በዚህ ዕለት መምህራቸው ሆኖ ሳለ ክርስቶስ በአጭር ታጥቆ አደግድጓ ወገቡን አስሮ የደቀመዛሙርቱን እግር ያጥብ ዘንድ በትህትና ዝቅ አለ:: ቅዱስ ጴጥሮስም እንዴት የእኛን እግር ታጥባለህ አንተኮ ጌታዬ ነኘ ብሎ ላላመታጠብ በትህትና እግሮቹን ሰበሰበ ጌታችንም በጥምቀት አክብሮ ልጅነትን ሊሰጣቸው ወዶ ነበርና ዛሬ ያልታጠበ ከእኔ ጋር ጽዋ ተርታ ዕድል ፍንታ የለውም አለው። ይህን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ደንግጦ እንደዛማ ከሆነ እንሬን ብቻ ሳይሆን ሰውነቴንም ጭምር እጠበኝ ብሎ ተናገረ ጌታችን ግን እግሩን የታጠበ ሰውነቱ ንፁዕ ነው ነገር ግን ሁላችሁ ንፁዕ አይደላቹሁም አላቸው አሳልፎ የሚሰጠው ይሁዳ በመካከላቸው ነበርና ዮሐ13÷10 ይህን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ታጠበ::
ይህም የሚያሳየው ከትህትናው ባሸገር የዓለምን ኃጢዓት ለማጠብ የመጣ መሆኑን ነው ‹‹ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘያአትት ኃጢዓተ ዓለም›› የዓለምን አጢኃት የሚስወግድ የእግዚአብሔር በግ ዮሐ 1÷29 እንዲል፡፡ ይህንን ለማስታወስ ዛሬም ካህናት በተለይም ሊቃነ ጳጳሳትና የደብር አስተዳዳሪዎች በመካከላችን ተገኝተህ የእኛንና የሕዝብህን ኃጢዓት እጠብ ሲሉ በዕለቱ በአጸደ ቤተክርስቲያን የተገኙትን ምዕመናንን እግር በወይንና በወይራ ቅጠል ሲያጥቡያረፍዳሉ፡፡
#የምሥጢር_ቀንም_ይባላል
____________________
ለደቀ መዛሙርቱ ይህ ስለ እናንተ የሚፈሰው ደሜ ነው ይህ ደግሞ ስለ እናንተ የሚቆረሰው ሥጋዬ ነው ብሎ ዕብስቱን ባርኮ ወይኑንም ቀድሶ ለሐዋርያት የሰጠበት ቀን ነው ሐዋርያትም ከእጁ ተቀብለው በልተዋል ጠጥተዋል በዚህም ምስጢረ ቁርባንን ፈጽሞላችዋልና ዕለቲቱ የምስጢር ቀን ተብሎ ይጠራል ። #ማቴ 26÷ 26-28
#ጸሎተ_ሐሙስ_ይባላል
__________________
በፍጥረታት የሚለመንና የሚመሰገን አምላክ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚለምንና አላዋቂ የሆነውን ሥጋ የተዋሐደ አምላክ፣ ፍጹም ሰው መሆኑን ለመግለጥ አንድም የስጋ ሞት እጅግ አስፈሪ መሆኑን ለማጠየቅና በመከራቹ ጊዜ ወደ ሰማይ አባታችሁ ጸሎትን ጸልዮ ሲል ለአርያነት ጠላቶቹ መጥተው እስኪይዙት ድረስ በጌቴ ሰማኔ በአታክልቱ ሥፍራ ሲጸልይ አድሮል በዚህም ዓብይ ምክንያት ይህ ዕለት ጸሎተ ሐሙስ ተብሏል፡፡ (#ማቴ 26፡36-46 ፣ ዮሐ 17)
. ......ይቆየን.........
👇👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
@YEAWEDIMERITE
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
📢 @AwediMeherit📢
📢 @AwediMeherit📢
📢📢📢📢📢📢📢📢
#ዕለተ_ሐሙስ
#ሕፅበተ_ሐሙስ_ይባላል
__________________
በዚህ ዕለት መምህራቸው ሆኖ ሳለ ክርስቶስ በአጭር ታጥቆ አደግድጓ ወገቡን አስሮ የደቀመዛሙርቱን እግር ያጥብ ዘንድ በትህትና ዝቅ አለ:: ቅዱስ ጴጥሮስም እንዴት የእኛን እግር ታጥባለህ አንተኮ ጌታዬ ነኘ ብሎ ላላመታጠብ በትህትና እግሮቹን ሰበሰበ ጌታችንም በጥምቀት አክብሮ ልጅነትን ሊሰጣቸው ወዶ ነበርና ዛሬ ያልታጠበ ከእኔ ጋር ጽዋ ተርታ ዕድል ፍንታ የለውም አለው። ይህን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ደንግጦ እንደዛማ ከሆነ እንሬን ብቻ ሳይሆን ሰውነቴንም ጭምር እጠበኝ ብሎ ተናገረ ጌታችን ግን እግሩን የታጠበ ሰውነቱ ንፁዕ ነው ነገር ግን ሁላችሁ ንፁዕ አይደላቹሁም አላቸው አሳልፎ የሚሰጠው ይሁዳ በመካከላቸው ነበርና ዮሐ13÷10 ይህን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ታጠበ::
ይህም የሚያሳየው ከትህትናው ባሸገር የዓለምን ኃጢዓት ለማጠብ የመጣ መሆኑን ነው ‹‹ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘያአትት ኃጢዓተ ዓለም›› የዓለምን አጢኃት የሚስወግድ የእግዚአብሔር በግ ዮሐ 1÷29 እንዲል፡፡ ይህንን ለማስታወስ ዛሬም ካህናት በተለይም ሊቃነ ጳጳሳትና የደብር አስተዳዳሪዎች በመካከላችን ተገኝተህ የእኛንና የሕዝብህን ኃጢዓት እጠብ ሲሉ በዕለቱ በአጸደ ቤተክርስቲያን የተገኙትን ምዕመናንን እግር በወይንና በወይራ ቅጠል ሲያጥቡያረፍዳሉ፡፡
#የምሥጢር_ቀንም_ይባላል
____________________
ለደቀ መዛሙርቱ ይህ ስለ እናንተ የሚፈሰው ደሜ ነው ይህ ደግሞ ስለ እናንተ የሚቆረሰው ሥጋዬ ነው ብሎ ዕብስቱን ባርኮ ወይኑንም ቀድሶ ለሐዋርያት የሰጠበት ቀን ነው ሐዋርያትም ከእጁ ተቀብለው በልተዋል ጠጥተዋል በዚህም ምስጢረ ቁርባንን ፈጽሞላችዋልና ዕለቲቱ የምስጢር ቀን ተብሎ ይጠራል ። #ማቴ 26÷ 26-28
#ጸሎተ_ሐሙስ_ይባላል
__________________
በፍጥረታት የሚለመንና የሚመሰገን አምላክ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚለምንና አላዋቂ የሆነውን ሥጋ የተዋሐደ አምላክ፣ ፍጹም ሰው መሆኑን ለመግለጥ አንድም የስጋ ሞት እጅግ አስፈሪ መሆኑን ለማጠየቅና በመከራቹ ጊዜ ወደ ሰማይ አባታችሁ ጸሎትን ጸልዮ ሲል ለአርያነት ጠላቶቹ መጥተው እስኪይዙት ድረስ በጌቴ ሰማኔ በአታክልቱ ሥፍራ ሲጸልይ አድሮል በዚህም ዓብይ ምክንያት ይህ ዕለት ጸሎተ ሐሙስ ተብሏል፡፡ (#ማቴ 26፡36-46 ፣ ዮሐ 17)
. ......ይቆየን.........
👇👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
@YEAWEDIMERITE
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
📢 @AwediMeherit📢
📢 @AwediMeherit📢
📢📢📢📢📢📢📢📢
"ሰው ሆይ ከሰው ተጠበቅ"
#ማቴ 10÷17
#ዕለቱ_የዕሣዕና ዕለት ነው ! አህያ የያዙ የቤተክርስቲያን ወጣቶች ወደ አንድ ካህን አባት ቀረቡና አባታችን እርሶ እንደ ጌታ አምሳል በአህያዋ ላይ ይቀመጡና በዓለ ሆሣዕናን በምሳሌ ከሕዝቡ ጋር በድምቀት እናክብረው አሏቸው። አባም ዛሬስ እሺ ብዬ ብቀመጥላችሁ ችግር አልነበረውም ግን በሳምንቱ ማንን ስቀለው ስቀለው ልትሉ ነው አሏቸውና በአህያዋ መቀመጥን እንቢ አሏቸው ይባላል። #የዛሬን_ሳይሆን_የነገን አስብ !
#ሁለት ዓሣና አምስት የገብስ እንጀራ አበርክቶ ቢያበላቸው ካላነገስንክ አሉት በአህያ ውርንጭላ ተቀምጦ ሲመጣም "ሆሣዕና በአርያም ለዳዊት ልጅ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው" እያሉ ልብሳቸውን ጭምር በማንጠፍ አመሰገኑት። #ማቴ 21 ÷ 9 በሳምንቱ ጲላጦስ አስሮ ምን ላድርገው ቢላቸው ሕዝቡ ሁሉ " ስቀለው ስቀለው ስለቀው " እያሉ ጮሁ #ሉቃ 23÷21 የሐሰት ከሳሾች ጸሐፍት ፈሪሳዊያንን በጭፍን ተከትለው ሌባ ሌባ ሲባል ሰሙና ሌባ ሌባ ማለት አማራቸው ሳይመረምሩ ምን አጠፋ ሳይሉ ስቀለው ስቀለው እያሉ ጮኹ የኛ የሰው ልጆች መዋደዳችን የቀናት ነው መፋቀራችም ከአንድ ሳምንት አያልፍም ። እናም ሰው ሆይ ከሰው ተጠበቅ! “ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ በምኩራቦቻቸውም ይገርፉአችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ፤” #ማቴ 10፥17 ዛሬ ያጨበጨበልን ነገ ያጨበጭብብናል ፣ ዛሬ የሳቀልን ነገ ይስቅብናል እርሱ ግን ሁሉን ያውቅ ነበረና አስቀደሞ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ ብሎ መክሮ ነበር #ማቴ 16÷6
#ከአንድ_ሳምንት_ፍቅርስ_ይሰውረን!
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሚያዝያ ፳ ፪/ ፳ ፻ ፲ ፫ .ዓ.ም
#ማቴ 10÷17
#ዕለቱ_የዕሣዕና ዕለት ነው ! አህያ የያዙ የቤተክርስቲያን ወጣቶች ወደ አንድ ካህን አባት ቀረቡና አባታችን እርሶ እንደ ጌታ አምሳል በአህያዋ ላይ ይቀመጡና በዓለ ሆሣዕናን በምሳሌ ከሕዝቡ ጋር በድምቀት እናክብረው አሏቸው። አባም ዛሬስ እሺ ብዬ ብቀመጥላችሁ ችግር አልነበረውም ግን በሳምንቱ ማንን ስቀለው ስቀለው ልትሉ ነው አሏቸውና በአህያዋ መቀመጥን እንቢ አሏቸው ይባላል። #የዛሬን_ሳይሆን_የነገን አስብ !
#ሁለት ዓሣና አምስት የገብስ እንጀራ አበርክቶ ቢያበላቸው ካላነገስንክ አሉት በአህያ ውርንጭላ ተቀምጦ ሲመጣም "ሆሣዕና በአርያም ለዳዊት ልጅ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው" እያሉ ልብሳቸውን ጭምር በማንጠፍ አመሰገኑት። #ማቴ 21 ÷ 9 በሳምንቱ ጲላጦስ አስሮ ምን ላድርገው ቢላቸው ሕዝቡ ሁሉ " ስቀለው ስቀለው ስለቀው " እያሉ ጮሁ #ሉቃ 23÷21 የሐሰት ከሳሾች ጸሐፍት ፈሪሳዊያንን በጭፍን ተከትለው ሌባ ሌባ ሲባል ሰሙና ሌባ ሌባ ማለት አማራቸው ሳይመረምሩ ምን አጠፋ ሳይሉ ስቀለው ስቀለው እያሉ ጮኹ የኛ የሰው ልጆች መዋደዳችን የቀናት ነው መፋቀራችም ከአንድ ሳምንት አያልፍም ። እናም ሰው ሆይ ከሰው ተጠበቅ! “ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ በምኩራቦቻቸውም ይገርፉአችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ፤” #ማቴ 10፥17 ዛሬ ያጨበጨበልን ነገ ያጨበጭብብናል ፣ ዛሬ የሳቀልን ነገ ይስቅብናል እርሱ ግን ሁሉን ያውቅ ነበረና አስቀደሞ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ ብሎ መክሮ ነበር #ማቴ 16÷6
#ከአንድ_ሳምንት_ፍቅርስ_ይሰውረን!
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሚያዝያ ፳ ፪/ ፳ ፻ ፲ ፫ .ዓ.ም
“ #እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የዋይታና የመራራ ልቅሶ ድምፅ በራማ ተሰማ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች፤ የሉምና ስለ ልጆችዋ መጽናናትን እንቢ አለች።”
— #ኤርምያስ 31፥15
ራሔል ወልዳ ስላልሳመቻቸው ፣ጡቶቿን ስላላጠባቻቸው ፣ በደርባዋ ስላላዘለቻቸው ፣ሌላው ቀርቶ ስም እንኳ ስላላወጣችላቸው ልጆቿ መጽናናትን ሳትወድ አምርራ ካለቀሰች።
በድንግልና ጸንሳ በድንግልና የወለደችው፣የድንግልና ጡቶቿን ያጠባችሁ፣ በእጆቿ የዳሰሰችሁ ፣በከንፈሮቿ የሳመችው፣ በጀርባዋ ያዘለችሁ፣ በጎኗ የታቀፈችሁ ፣ ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላው ይዛው ስትሰደድ አንዴ #ኢየሱስ አንዴ #መድኃኔአለም አንዴ #አማኑኤል እያለች አፈራርቃ የሰየመችው 33 ዓመት አብራው የኖረች ምንትያ ቅጥያ ተቀዳዊ ተከታይ የሌለው አንድያ ልጆን ያጣች ራሔል እመቤታችን ሐዘኟ እንዴት የጠለቀ ይሆን ???🙏
#ድንግል_ሆይ ብሩቱሀን የሆኑ አምስቱ ሐዘኖችሽን አሳስቢ🙏 ለጻድቃንም አይደል ለኛ ለኃጥያን እንጂ!
— #ኤርምያስ 31፥15
ራሔል ወልዳ ስላልሳመቻቸው ፣ጡቶቿን ስላላጠባቻቸው ፣ በደርባዋ ስላላዘለቻቸው ፣ሌላው ቀርቶ ስም እንኳ ስላላወጣችላቸው ልጆቿ መጽናናትን ሳትወድ አምርራ ካለቀሰች።
በድንግልና ጸንሳ በድንግልና የወለደችው፣የድንግልና ጡቶቿን ያጠባችሁ፣ በእጆቿ የዳሰሰችሁ ፣በከንፈሮቿ የሳመችው፣ በጀርባዋ ያዘለችሁ፣ በጎኗ የታቀፈችሁ ፣ ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላው ይዛው ስትሰደድ አንዴ #ኢየሱስ አንዴ #መድኃኔአለም አንዴ #አማኑኤል እያለች አፈራርቃ የሰየመችው 33 ዓመት አብራው የኖረች ምንትያ ቅጥያ ተቀዳዊ ተከታይ የሌለው አንድያ ልጆን ያጣች ራሔል እመቤታችን ሐዘኟ እንዴት የጠለቀ ይሆን ???🙏
#ድንግል_ሆይ ብሩቱሀን የሆኑ አምስቱ ሐዘኖችሽን አሳስቢ🙏 ለጻድቃንም አይደል ለኛ ለኃጥያን እንጂ!
በዚህ ዘመን ዶሮ መሆን በራሱ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ መታደል ነው።
#እንዴት?
በውድ ነዋ የምትሸጪው !
#በውድ ተሸጭክም ፤ በርካሽ ያው መታረድህ አይቀር
ቢሆንም በክብር ተሽጦ ክብርን በሚመጥን መንገድ መሞት ሰማዕትነት ነው ።
#በርኳሽ ስትሸጥ መቆየትህ ቁጭት አሳድሮብሃል ማለት ነው?
እንዴታ ለምን አያሳድርብኝም ? አታስታውሺም ፈንግል የተባለ በርድ ፍሎ የወፍ ጉንፋን በሽታ የመጣ ጊዜ ሁለት ዶሮ በ1ብር የተሸጠበትን የቅርብ ጊዜ ታሪክ? ይህው ዛሬ የሰው ጉንፋን covid 19 መጣና ሰው ረክሶ እኛ ተወደድን ለነገሩ የ ዛሬን አያድርገውና ከጅምሩ እኛኮ እኛ የነ አይደፈሩ የነ ዳይኖንሰር ዘር እኮነን ። ዶሮ የዳይነንሰር የመጨረሻ ዝርያው ነው ያሉትን የሳይንቲስቶች ምርምር አልሰማሽምን?
#ዶሮን ሲያታልሏት ዳይኖሰር ነሽ አሏት ኩኩኩኩኩኩኩ
ምን ያስካካሻል ውሸት ነው ልትይ ነው ዳይኖንሰርም ዶሮም ተመሳሳይ አቆም እንዳላቸው እራስሽ ማረጋገጥ ትቺያለሽ
#እንዴት አረጊ?
ላባው የተራገፈ አንድ ዶሮና አንድ ዳይኖንሰር በአምሮሽ ሳይ በሁለት እግራቸው የቆሙ
ሁለት እጃቸው አጠር ብሎ ወደ ደረታቸው የተጠጋ በመጠን ብቻ የሚለያዮ ተመሳሳይ ፍጥረት ይመጣልሻል።
#አስብኩት..... በእውነቱ እውነት ይመስላል ። ቆይ ግን አንተ መታረድህ ነው ወይስ የነ ዳይኖንሰር ዘር ሆኜ እንዴት በርኳሽ ተሽጬ እታረዳለሁ የሚለው ነው የሚያሳስብህ ?
ሁለቱም ያሳስቡኛል ክብሬም ሕይወቴም
#ወገኛ የቱ ክብርህ የክብር ባለቤት እንኳ በሰላሳ ዲናር ተሽጦ ያለ እርራዬ መታረዱን አትዘንጋ።
ዛሬ ጥሬ ስትለቅሚ የነበረው ከ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ነበር እንዴ?
#እንዴ አዎ ለምን ጠየከኝ?
ሰባኪ መሰልሽኛ!
#እእእእ_በነገራችን ላይ ላስተዋለው ሁሉም ፍጥረት በራሱ ሰባኪ ነው “ሰማያት #የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ ” እንዳለ መጻሕፉ መዝ 19፥1
አሁን ከካህናቱ ጋር ሰንበቴ እንደምትቀመጪ ጭምር አረጋገጥኩ። ለነገሩ እታች ሰፈር ጥሬ ፍለጋ እያልሽ ገብስማው ዶሮጋ ከምትሄዲብኝ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መሄድሽ ይሻለኛል።
" #የአውራ ዶሮ ወዳጅ መች ጠርቶ ሊጠራ
ሲወጡ ሲገቡ ሁል ጊዜ ጥርጠራ"
ምን አልሽ አንቺ ??
#አረ ጌታው ምንም አላልኩም ወዲ ነው
እኔ የምለው እስከ ዛሬ መታረዴ ሳይሆን በርኳሽ ስሸጥ መቆየቴ የግር እሳት ሆኖብኛል እያልክ ነው።
#አዎን
ለምን ይመስልሃል ግን ዋጋችን እንዲህ ውድ የሆነው?
#እኔ ምን አውቃለሁ አንቺን ልጠይቅሽ እንጂ ግን ፈጣሪ መናቃችንን አይቶ እየካሰን ይመስለኛል
አይደለም ባክህ ሰው ስለረከሰ ነው።
#አታመጪው ጉድ የለ !። ምን?
አዎ ወዳጄ ሰው ሲረክስ ለሰው የተዘጋጁት ነገረሮች ሁሉ ይወደዱበታል በስግብግብነት ሲረክስ በአቋራጭ ለመበልጸግ ሲረክስ ነገሮች ሁሉ ውድ ይሆኑበታል።
#ይልቁኑ በበዓላት ሁሉም ሲወደድ ካየህ የሰው ልጅ እረክሷል ማለት ነው
ስኳር ውስጥ ሩዝ ፣በርበሬ ውስጥ ሸክላ ፣ቅቤ ውስጥ ሙዝ ፣እንጀራ ወስጥ ጀሶ የሚጨምረው ቢረክስ አይደለምን??!
#ሊጡ ውስጥ እንኳ ጀሶ መኖሩ አሁን አሁን ሳስበው ጥሩ መሰለኝ
እንዴት?
#ያው ያ ሀገር አቆርቋዥ ጁንታ እንደልማዱ ሰርቆ ሲጠጣ አድርቆ ያስቀርልናል።
የሚገርመው እንደዚህ በዐድ ነገር ቀላቅሎ እንኳን የሚሸጭበት ዋጋ የትዬ ለሌ ነው። ይህ እጅግ በጣም መውረዱን ነው የሚያሳየው።
#የኔ_ውድ ምን አልባት እኛም የተወደድነው እንተ እንዳልከው የዳይኖሰር ዘሮች ስለሆንን ሳይሆን ከሆነ በዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ሊሆን ይችላል ። በዘርህ ማሰብህ አቁም
ምን ? ከብዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ይሆናል? ለዛነው ሣር ሳይ ጋጥ ጋጥ ፣ሜዳ ሳይ ደግሞ ተደባለል ተደባለል የሚለኝ ?
#አዎን የሐበሻውን ዶሮ ከፈረንጅ ዶሮ ጋር የፈረንጁን ዶሮ ከሰጎን እዋስ ጋር መቀላቀሉ ሳይንስ ዐዋቂነት ሆኟል።
ሰው ግን ለምን እንዲህ ከፋ ?
#ያወቀ እየመሰለው አንድም ጽድቅና ኩነኔን ቢረሳ ነዋ እኛኸ ታላቅ ሰው ያሉትን የሚያስተውል መቼ ይሆን ? "ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፉት ደግነት ሳይሻል አይቀርም"
አ.አ ኢትዮጵያ
ኃ/ማርያም ተርቢኖስ ሰብስቤ
ታኅሣሥ 28 ቀን 2014 ዓ.ም
#እንዴት?
በውድ ነዋ የምትሸጪው !
#በውድ ተሸጭክም ፤ በርካሽ ያው መታረድህ አይቀር
ቢሆንም በክብር ተሽጦ ክብርን በሚመጥን መንገድ መሞት ሰማዕትነት ነው ።
#በርኳሽ ስትሸጥ መቆየትህ ቁጭት አሳድሮብሃል ማለት ነው?
እንዴታ ለምን አያሳድርብኝም ? አታስታውሺም ፈንግል የተባለ በርድ ፍሎ የወፍ ጉንፋን በሽታ የመጣ ጊዜ ሁለት ዶሮ በ1ብር የተሸጠበትን የቅርብ ጊዜ ታሪክ? ይህው ዛሬ የሰው ጉንፋን covid 19 መጣና ሰው ረክሶ እኛ ተወደድን ለነገሩ የ ዛሬን አያድርገውና ከጅምሩ እኛኮ እኛ የነ አይደፈሩ የነ ዳይኖንሰር ዘር እኮነን ። ዶሮ የዳይነንሰር የመጨረሻ ዝርያው ነው ያሉትን የሳይንቲስቶች ምርምር አልሰማሽምን?
#ዶሮን ሲያታልሏት ዳይኖሰር ነሽ አሏት ኩኩኩኩኩኩኩ
ምን ያስካካሻል ውሸት ነው ልትይ ነው ዳይኖንሰርም ዶሮም ተመሳሳይ አቆም እንዳላቸው እራስሽ ማረጋገጥ ትቺያለሽ
#እንዴት አረጊ?
ላባው የተራገፈ አንድ ዶሮና አንድ ዳይኖንሰር በአምሮሽ ሳይ በሁለት እግራቸው የቆሙ
ሁለት እጃቸው አጠር ብሎ ወደ ደረታቸው የተጠጋ በመጠን ብቻ የሚለያዮ ተመሳሳይ ፍጥረት ይመጣልሻል።
#አስብኩት..... በእውነቱ እውነት ይመስላል ። ቆይ ግን አንተ መታረድህ ነው ወይስ የነ ዳይኖንሰር ዘር ሆኜ እንዴት በርኳሽ ተሽጬ እታረዳለሁ የሚለው ነው የሚያሳስብህ ?
ሁለቱም ያሳስቡኛል ክብሬም ሕይወቴም
#ወገኛ የቱ ክብርህ የክብር ባለቤት እንኳ በሰላሳ ዲናር ተሽጦ ያለ እርራዬ መታረዱን አትዘንጋ።
ዛሬ ጥሬ ስትለቅሚ የነበረው ከ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ነበር እንዴ?
#እንዴ አዎ ለምን ጠየከኝ?
ሰባኪ መሰልሽኛ!
#እእእእ_በነገራችን ላይ ላስተዋለው ሁሉም ፍጥረት በራሱ ሰባኪ ነው “ሰማያት #የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ ” እንዳለ መጻሕፉ መዝ 19፥1
አሁን ከካህናቱ ጋር ሰንበቴ እንደምትቀመጪ ጭምር አረጋገጥኩ። ለነገሩ እታች ሰፈር ጥሬ ፍለጋ እያልሽ ገብስማው ዶሮጋ ከምትሄዲብኝ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መሄድሽ ይሻለኛል።
" #የአውራ ዶሮ ወዳጅ መች ጠርቶ ሊጠራ
ሲወጡ ሲገቡ ሁል ጊዜ ጥርጠራ"
ምን አልሽ አንቺ ??
#አረ ጌታው ምንም አላልኩም ወዲ ነው
እኔ የምለው እስከ ዛሬ መታረዴ ሳይሆን በርኳሽ ስሸጥ መቆየቴ የግር እሳት ሆኖብኛል እያልክ ነው።
#አዎን
ለምን ይመስልሃል ግን ዋጋችን እንዲህ ውድ የሆነው?
#እኔ ምን አውቃለሁ አንቺን ልጠይቅሽ እንጂ ግን ፈጣሪ መናቃችንን አይቶ እየካሰን ይመስለኛል
አይደለም ባክህ ሰው ስለረከሰ ነው።
#አታመጪው ጉድ የለ !። ምን?
አዎ ወዳጄ ሰው ሲረክስ ለሰው የተዘጋጁት ነገረሮች ሁሉ ይወደዱበታል በስግብግብነት ሲረክስ በአቋራጭ ለመበልጸግ ሲረክስ ነገሮች ሁሉ ውድ ይሆኑበታል።
#ይልቁኑ በበዓላት ሁሉም ሲወደድ ካየህ የሰው ልጅ እረክሷል ማለት ነው
ስኳር ውስጥ ሩዝ ፣በርበሬ ውስጥ ሸክላ ፣ቅቤ ውስጥ ሙዝ ፣እንጀራ ወስጥ ጀሶ የሚጨምረው ቢረክስ አይደለምን??!
#ሊጡ ውስጥ እንኳ ጀሶ መኖሩ አሁን አሁን ሳስበው ጥሩ መሰለኝ
እንዴት?
#ያው ያ ሀገር አቆርቋዥ ጁንታ እንደልማዱ ሰርቆ ሲጠጣ አድርቆ ያስቀርልናል።
የሚገርመው እንደዚህ በዐድ ነገር ቀላቅሎ እንኳን የሚሸጭበት ዋጋ የትዬ ለሌ ነው። ይህ እጅግ በጣም መውረዱን ነው የሚያሳየው።
#የኔ_ውድ ምን አልባት እኛም የተወደድነው እንተ እንዳልከው የዳይኖሰር ዘሮች ስለሆንን ሳይሆን ከሆነ በዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ሊሆን ይችላል ። በዘርህ ማሰብህ አቁም
ምን ? ከብዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ይሆናል? ለዛነው ሣር ሳይ ጋጥ ጋጥ ፣ሜዳ ሳይ ደግሞ ተደባለል ተደባለል የሚለኝ ?
#አዎን የሐበሻውን ዶሮ ከፈረንጅ ዶሮ ጋር የፈረንጁን ዶሮ ከሰጎን እዋስ ጋር መቀላቀሉ ሳይንስ ዐዋቂነት ሆኟል።
ሰው ግን ለምን እንዲህ ከፋ ?
#ያወቀ እየመሰለው አንድም ጽድቅና ኩነኔን ቢረሳ ነዋ እኛኸ ታላቅ ሰው ያሉትን የሚያስተውል መቼ ይሆን ? "ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፉት ደግነት ሳይሻል አይቀርም"
አ.አ ኢትዮጵያ
ኃ/ማርያም ተርቢኖስ ሰብስቤ
ታኅሣሥ 28 ቀን 2014 ዓ.ም
ዐውደ ምሕረት
Audio