ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
"ሰው ሆይ ከሰው ተጠበቅ"
#ማቴ 10÷17

#ዕለቱ_የዕሣዕና ዕለት ነው ! አህያ የያዙ የቤተክርስቲያን ወጣቶች ወደ አንድ ካህን አባት ቀረቡና አባታችን እርሶ እንደ ጌታ አምሳል በአህያዋ ላይ ይቀመጡና በዓለ ሆሣዕናን በምሳሌ ከሕዝቡ ጋር በድምቀት እናክብረው አሏቸው። አባም ዛሬስ እሺ ብዬ ብቀመጥላችሁ ችግር አልነበረውም ግን በሳምንቱ ማንን ስቀለው ስቀለው ልትሉ ነው አሏቸውና በአህያዋ መቀመጥን እንቢ አሏቸው ይባላል። #የዛሬን_ሳይሆን_የነገን አስብ !
#ሁለት ዓሣና አምስት የገብስ እንጀራ አበርክቶ ቢያበላቸው ካላነገስንክ አሉት በአህያ ውርንጭላ ተቀምጦ ሲመጣም "ሆሣዕና በአርያም ለዳዊት ልጅ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው" እያሉ ልብሳቸውን ጭምር በማንጠፍ አመሰገኑት። #ማቴ 21 ÷ 9 በሳምንቱ ጲላጦስ አስሮ ምን ላድርገው ቢላቸው ሕዝቡ ሁሉ " ስቀለው ስቀለው ስለቀው " እያሉ ጮሁ #ሉቃ 23÷21 የሐሰት ከሳሾች ጸሐፍት ፈሪሳዊያንን በጭፍን ተከትለው ሌባ ሌባ ሲባል ሰሙና ሌባ ሌባ ማለት አማራቸው ሳይመረምሩ ምን አጠፋ ሳይሉ ስቀለው ስቀለው እያሉ ጮኹ የኛ የሰው ልጆች መዋደዳችን የቀናት ነው መፋቀራችም ከአንድ ሳምንት አያልፍም ። እናም ሰው ሆይ ከሰው ተጠበቅ! “ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ በምኩራቦቻቸውም ይገርፉአችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ፤” #ማቴ 10፥17 ዛሬ ያጨበጨበልን ነገ ያጨበጭብብናል ፣ ዛሬ የሳቀልን ነገ ይስቅብናል እርሱ ግን ሁሉን ያውቅ ነበረና አስቀደሞ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ ብሎ መክሮ ነበር #ማቴ 16÷6

#ከአንድ_ሳምንት_ፍቅርስ_ይሰውረን!

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሚያዝያ ፳ ፪/ ፳ ፻ ፲ ፫ .ዓ.ም
"ሰው ሆይ ከሰው ተጠበቅ"
#ማቴ 10÷17

#ዕለቱ_የዕሣዕና ዕለት ነው ! አህያ የያዙ የቤተክርስቲያን ወጣቶች ወደ አንድ ካህን አባት ቀረቡና አባታችን እርሶ እንደ ጌታ አምሳል በአህያዋ ላይ ይቀመጡና በዓለ ሆሣዕናን በምሳሌ ከሕዝቡ ጋር በድምቀት እናክብረው አሏቸው። አባም ዛሬስ እሺ ብዬ ብቀመጥላችሁ ችግር አልነበረውም ግን በሳምንቱ ማንን ስቀለው ስቀለው ልትሉ ነው አሏቸውና በአህያዋ መቀመጥን እንቢ አሏቸው ይባላል። #የዛሬን_ሳይሆን_የነገን አስብ !
#ሁለት ዓሣና አምስት የገብስ እንጀራ አበርክቶ ቢያበላቸው ካላነገስንክ አሉት በአህያ ውርንጭላ ተቀምጦ ሲመጣም "ሆሣዕና በአርያም ለዳዊት ልጅ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው" እያሉ ልብሳቸውን ጭምር በማንጠፍ አመሰገኑት። #ማቴ 21 ÷ 9 በሳምንቱ ጲላጦስ አስሮ ምን ላድርገው ቢላቸው ሕዝቡ ሁሉ " ስቀለው ስቀለው ስለቀው " እያሉ ጮሁ #ሉቃ 23÷21 የሐሰት ከሳሾች ጸሐፍት ፈሪሳዊያንን በጭፍን ተከትለው ሌባ ሌባ ሲባል ሰሙና ሌባ ሌባ ማለት አማራቸው ሳይመረምሩ ምን አጠፋ ሳይሉ ስቀለው ስቀለው እያሉ ጮኹ የኛ የሰው ልጆች መዋደዳችን የቀናት ነው መፋቀራችም ከአንድ ሳምንት አያልፍም ። እናም ሰው ሆይ ከሰው ተጠበቅ! “ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ በምኩራቦቻቸውም ይገርፉአችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ፤” #ማቴ 10፥17 ዛሬ ያጨበጨበልን ነገ ያጨበጭብብናል ፣ ዛሬ የሳቀልን ነገ ይስቅብናል እርሱ ግን ሁሉን ያውቅ ነበረና አስቀደሞ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ ብሎ መክሮ ነበር #ማቴ 16÷6

#ከአንድ_ሳምንት_ፍቅርስ_ይሰውረን!

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሚያዝያ ፳ ፪/ ፳ ፻ ፲ ፫ .ዓ.ም