ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
በዚህ ዘመን ዶሮ መሆን በራሱ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ መታደል ነው።
#እንዴት?
በውድ ነዋ የምትሸጪው !
#በውድ ተሸጭክም ፤ በርካሽ ያው መታረድህ አይቀር
ቢሆንም በክብር ተሽጦ ክብርን በሚመጥን መንገድ መሞት ሰማዕትነት ነው ።
#በርኳሽ ስትሸጥ መቆየትህ ቁጭት አሳድሮብሃል ማለት ነው?
እንዴታ ለምን አያሳድርብኝም የዛሬን አያድርገውና ኮ እኛ የነ አይደፈሩ የነ ዳይኖንሰር ዘር እኮነን። ዶሮ የዳይነንሰር የመጨረሻ ዝርያው ነው ያሉትን የሳይንቲስቶች ምርምር አልሰማሽምን?
#ዶሮን ሲያታልሏት ዳይኖሰር ነሽ አሏት ኩኩኩኩኩኩኩ
ምን ያስካካሻል ውሸት ነው ልትይ ነው ዳይኖንሰርም ዶሮም ተመሳሳይ አቆም እንዳላቸው እራስሽ ማረጋገጥ ትቺያለሽ
#እንዴት አረጊ?
ላባው የተራገፈ አንድ ዶሮና አንድ ዳይኖንሰር በአምሮሽ ሳይ በሁለት እግራቸው የቆሙ
ሁለት እጃቸው አጠር ብሎ ወደ ደረታቸው የተጠጋ በመጠን ብቻ የሚለያዮ ተመሳሳይ ፍጥረት ይመጣልሻል።
#አስብኩት..... በእውነቱ እውነት ይመስላል ። ቆይ ግን አንተ መታረድህ ነው ወይስ የነ ዳይኖንሰር ዘር ሆኜ እንዴት በርኳሽ ተሽጬ እታረዳለሁ የሚለው ነው የሚያሳስብህ ?
ሁለቱም ያሳስቡኛል ክብሬም ሕይወቴም
#ወገኛ የቱ ክብርህ የክብር ባለቤት እንኳ በሰላሳ ዲናር ተሽጦ ያለ እርራዬ መታረዱን አትዘንጋ።
ዛሬ ጥሬ ስትለቅሚ የነበረው ከ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ነበር እንዴ?
#እንዴ አዎ ለምን ጠየከኝ?
ሰባኪ መሰልሽኛ!
#እእእእ_በነገራችን ላይ ላስተዋለው ሁሉም ፍጥረት በራሱ ሰባኪ ነው “ሰማያት #የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ ” እንዳለ መጻሕፉ መዝ 19፥1

አሁን ከካህናቱ ጋር ሰንበቴ እንደምትቀመጪ ጭምር አረጋገጥኩ። ለነገሩ እታች ሰፈር ጥሬ ፍለጋ እያልሽ ገብስማው ዶሮጋ ከምትሄዲብኝ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መሄድሽ ይሻለኛል።

" #የአውራ ዶሮ ወዳጅ መች ጠርቶ ሊጠራ
ሲወጡ ሲገቡ ሁል ጊዜ ጥርጠራ"

ምን አልሽ አንቺ ??

#አረ ጌታው ምንም አላልኩም ወዲ ነው
እኔ የምለው እስከ ዛሬ መታረዴ ሳይሆን በርኳሽ ስሸጥ መቆየቴ የግር እሳት ሆኖብኛል እያልክ ነው።
#አዎን
ለምን ይመስልሃል ግን ዋጋችን እንዲህ ውድ የሆነው?
#እኔ ምን አውቃለሁ አንቺን ልጠይቅሽ እንጂ ግን ፈጣሪ መናቃችንን አይቶ እየካሰን ይመስለኛል

አይደለም ባክህ ሰው ስለረከሰ ነው።
#አታመጪው ጉድ የለ !። ምን?
አዎ ወዳጄ ሰው ሲረክስ ለሰው የተዘጋጁት ነገረሮች ሁሉ ይወደዱበታል በስግብግብነት ሲረክስ በአቋራጭ ለመበልጸግ ሲረክስ ነገሮች ሁሉ ውድ ይሆኑበታል።

#ይልቁኑ በበዓላት ሁሉም ሲወደድ ካየህ የሰው ልጅ እረክሷል ማለት ነው

ስኳር ውስጥ ሩዝ ፣በርበሬ ውስጥ ሸክላ ፣ቅቤ ውስጥ ሙዝ ፣እንጀራ ወስጥ ጀሶ የሚጨምረው ቢረክስ አይደለምን??!
#ሊጡ ውስጥ እንኳ ጀሶ መኖሩ አሁን አሁን ሳስበው ጥሩ መሰለኝ
እንዴት?
#ያው ያ ሀገር አቆርቋዥ ጁንታ እንደልማዱ ሰርቆ ሲጠጣ አድርቆ ያስቀርልናል።

የሚገርመው እንደዚህ በዐድ ነገር ቀላቅሎ እንኳን የሚሸጭበት ዋጋ የትዬ ለሌ ነው። ይህ እጅግ በጣም መውረዱን ነው የሚያሳየው።
#የኔ_ውድ ምን አልባት እኛም የተወደድነው እንተ እንዳልከው የዳይኖሰር ዘሮች ስለሆንን ሳይሆን ከሆነ በዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ሊሆን ይችላል ። በዘርህ ማሰብህ አቁም
ምን ? ከብዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ይሆናል? ለዛነው ሣር ሳይ ጋጥ ጋጥ ፣ሜዳ ሳይ ደግሞ ተደባለል ተደባለል የሚለኝ ?
#አዎን የሐበሻውን ዶሮ ከፈረንጅ ዶሮ ጋር የፈረንጁን ዶሮ ከሰጎን እዋስ ጋር መቀላቀሉ ሳይንስ ዐዋቂነት ሆኟል።
ሰው ግን ለምን እንዲህ ከፋ ?
#ያወቀ እየመሰለው አንድም ጽድቅና ኩነኔን ቢረሳ ነዋ እኛኸ ታላቅ ሰው ያሉትን የሚያስተውል መቼ ይሆን ? "ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፉት ደግነት ሳይሻል አይቀርም"
አ.አ ኢትዮጵያ
ኃ/ማርያም ተርቢኖስ ሰብስቤ
ታኅሣሥ 28 ቀን 2014 ዓ.ም
በዚህ ዘመን ዶሮ መሆን በራሱ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ መታደል ነው።
#እንዴት?
በውድ ነዋ የምትሸጪው !
#በውድ ተሸጭክም ፤ በርካሽ ያው መታረድህ አይቀር
ቢሆንም በክብር ተሽጦ ክብርን በሚመጥን መንገድ መሞት ሰማዕትነት ነው ።
#በርኳሽ ስትሸጥ መቆየትህ ቁጭት አሳድሮብሃል ማለት ነው?
እንዴታ ለምን አያሳድርብኝም ? አታስታውሺም ፈንግል የተባለ በርድ ፍሎ የወፍ ጉንፋን በሽታ የመጣ ጊዜ ሁለት ዶሮ በ1ብር የተሸጠበትን የቅርብ ጊዜ ታሪክ? ይህው ዛሬ የሰው ጉንፋን covid 19 መጣና ሰው ረክሶ እኛ ተወደድን ለነገሩ የ ዛሬን አያድርገውና ከጅምሩ እኛኮ እኛ የነ አይደፈሩ የነ ዳይኖንሰር ዘር እኮነን ። ዶሮ የዳይነንሰር የመጨረሻ ዝርያው ነው ያሉትን የሳይንቲስቶች ምርምር አልሰማሽምን?
#ዶሮን ሲያታልሏት ዳይኖሰር ነሽ አሏት ኩኩኩኩኩኩኩ
ምን ያስካካሻል ውሸት ነው ልትይ ነው ዳይኖንሰርም ዶሮም ተመሳሳይ አቆም እንዳላቸው እራስሽ ማረጋገጥ ትቺያለሽ
#እንዴት አረጊ?
ላባው የተራገፈ አንድ ዶሮና አንድ ዳይኖንሰር በአምሮሽ ሳይ በሁለት እግራቸው የቆሙ
ሁለት እጃቸው አጠር ብሎ ወደ ደረታቸው የተጠጋ በመጠን ብቻ የሚለያዮ ተመሳሳይ ፍጥረት ይመጣልሻል።
#አስብኩት..... በእውነቱ እውነት ይመስላል ። ቆይ ግን አንተ መታረድህ ነው ወይስ የነ ዳይኖንሰር ዘር ሆኜ እንዴት በርኳሽ ተሽጬ እታረዳለሁ የሚለው ነው የሚያሳስብህ ?
ሁለቱም ያሳስቡኛል ክብሬም ሕይወቴም
#ወገኛ የቱ ክብርህ የክብር ባለቤት እንኳ በሰላሳ ዲናር ተሽጦ ያለ እርራዬ መታረዱን አትዘንጋ።
ዛሬ ጥሬ ስትለቅሚ የነበረው ከ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ነበር እንዴ?
#እንዴ አዎ ለምን ጠየከኝ?
ሰባኪ መሰልሽኛ!
#እእእእ_በነገራችን ላይ ላስተዋለው ሁሉም ፍጥረት በራሱ ሰባኪ ነው “ሰማያት #የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ ” እንዳለ መጻሕፉ መዝ 19፥1

አሁን ከካህናቱ ጋር ሰንበቴ እንደምትቀመጪ ጭምር አረጋገጥኩ። ለነገሩ እታች ሰፈር ጥሬ ፍለጋ እያልሽ ገብስማው ዶሮጋ ከምትሄዲብኝ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መሄድሽ ይሻለኛል።

" #የአውራ ዶሮ ወዳጅ መች ጠርቶ ሊጠራ
ሲወጡ ሲገቡ ሁል ጊዜ ጥርጠራ"

ምን አልሽ አንቺ ??

#አረ ጌታው ምንም አላልኩም ወዲ ነው
እኔ የምለው እስከ ዛሬ መታረዴ ሳይሆን በርኳሽ ስሸጥ መቆየቴ የግር እሳት ሆኖብኛል እያልክ ነው።
#አዎን
ለምን ይመስልሃል ግን ዋጋችን እንዲህ ውድ የሆነው?
#እኔ ምን አውቃለሁ አንቺን ልጠይቅሽ እንጂ ግን ፈጣሪ መናቃችንን አይቶ እየካሰን ይመስለኛል

አይደለም ባክህ ሰው ስለረከሰ ነው።
#አታመጪው ጉድ የለ !። ምን?
አዎ ወዳጄ ሰው ሲረክስ ለሰው የተዘጋጁት ነገረሮች ሁሉ ይወደዱበታል በስግብግብነት ሲረክስ በአቋራጭ ለመበልጸግ ሲረክስ ነገሮች ሁሉ ውድ ይሆኑበታል።

#ይልቁኑ በበዓላት ሁሉም ሲወደድ ካየህ የሰው ልጅ እረክሷል ማለት ነው

ስኳር ውስጥ ሩዝ ፣በርበሬ ውስጥ ሸክላ ፣ቅቤ ውስጥ ሙዝ ፣እንጀራ ወስጥ ጀሶ የሚጨምረው ቢረክስ አይደለምን??!
#ሊጡ ውስጥ እንኳ ጀሶ መኖሩ አሁን አሁን ሳስበው ጥሩ መሰለኝ
እንዴት?
#ያው ያ ሀገር አቆርቋዥ ጁንታ እንደልማዱ ሰርቆ ሲጠጣ አድርቆ ያስቀርልናል።

የሚገርመው እንደዚህ በዐድ ነገር ቀላቅሎ እንኳን የሚሸጭበት ዋጋ የትዬ ለሌ ነው። ይህ እጅግ በጣም መውረዱን ነው የሚያሳየው።
#የኔ_ውድ ምን አልባት እኛም የተወደድነው እንተ እንዳልከው የዳይኖሰር ዘሮች ስለሆንን ሳይሆን ከሆነ በዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ሊሆን ይችላል ። በዘርህ ማሰብህ አቁም
ምን ? ከብዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ይሆናል? ለዛነው ሣር ሳይ ጋጥ ጋጥ ፣ሜዳ ሳይ ደግሞ ተደባለል ተደባለል የሚለኝ ?
#አዎን የሐበሻውን ዶሮ ከፈረንጅ ዶሮ ጋር የፈረንጁን ዶሮ ከሰጎን እዋስ ጋር መቀላቀሉ ሳይንስ ዐዋቂነት ሆኟል።
ሰው ግን ለምን እንዲህ ከፋ ?
#ያወቀ እየመሰለው አንድም ጽድቅና ኩነኔን ቢረሳ ነዋ እኛኸ ታላቅ ሰው ያሉትን የሚያስተውል መቼ ይሆን ? "ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፉት ደግነት ሳይሻል አይቀርም"
አ.አ ኢትዮጵያ
ኃ/ማርያም ተርቢኖስ ሰብስቤ
ታኅሣሥ 28 ቀን 2014 ዓ.ም