ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#ረቡዕ #የምክር_ቀን
" #ምስጉን_ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ"
_______________________
#መዝ 1÷1

ይህ ዕለት የምክር ቀን ይባላል፣ ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጻሕፋት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር የጀመሩበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ ወቅቱ አይሁድ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት በመሆኑና ብዙ ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረከ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለነበር ምናልባት ሁከት ይፈጠራል ብለው ሕዝብን እየፈሩ ሊይዙት ያመነቱ ነበር። ተሳክቶላቸው እንያዘው ቢሉ እንኳን ኢየሱስ ክርስቶስን ከደቀ መዛሙርቱ ለይተው አያውቁትም ስለዚህ እርሱን በቅርብ የሚያውቅ ሰው ያስፈልጋቸዋልና በክፉ ምክራቸው እጅግ ተጨነቁ። ትንሽ ቆይቶ ግን ከደቀመዛሙርቱ መካከል አንዱ የሆነው የአስቆሮቱ ይሁዳ በክፉ ምክራቸው በመሳተፍ ጌታን በመሳም አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ቃል ገባላቸው ። ለምልክት ይሁናቸውም ዘንድም እኔ ሄጄ የምስመው ሰው እርሱ ክርስቶስ ነውና ያዙት ብሎ ተማከረ ጭንቀታቸው ተወገደ ለወረታውም ሰላሣ ብር መዘኑለት (ማቴ 26፡1-5 ፣ ማቴ26፡14-15 ፣ ማር 14፡1-2፣ ሉቃ 22፡1-6) 
#ዕለተ_ረቡዕ_መልካም_መዓዛ_ያለው_ቀንም_ይባላል፣ ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት (ባለ ሽቶዋ ማርያም) ከእንግዲህ ወዲህ በኅጢዓት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ፣ ኀጢዓትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ፣ በአልባሲጥሮስ ብልቃጥ የሞላ ሽቱ ይዛ በመሄድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ነው፡፡ የእንባ ቀን ይባላል ይህም ስያሜ የተሰጠበት ምክንያት ይህችው ማርያም እንተእፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢዓቷን ይቅር እንዲልላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና፣ በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና፡፡ በጠጉሯም ማበሶ አክሊሌ ነክ ስትል ነው ። የማርያም እንተእፍረትን ኃጢዓት ይቅር ብሎ መባዋን የተቀበለ አምላክ ዛሬ በመካከላችን አለና በማንኛውም ጊዜና ሰዓት የራሳችንን ኃጢዓት በማሰብ በማልቀስና የተወደደ መስዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር በማቅረብ በመልካም ሥራዋ ልንመስላት ይገባል፡፡ (ማቴ 26፡6-13 ፣ ሉቃ 7፡36 ፣ ማር 14፡3-9 ፣ ዮሐ 12፡1-8)

...........ይቆየን…..........
#ዐውደ_ምሕረት_የእናንተ
#ረቡዕ #የምክር_ቀን
" #ምስጉን_ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ"
_______________________
#መዝ 1÷1

ይህ ዕለት የምክር ቀን ይባላል፣ ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጻሕፋት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር የጀመሩበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ ወቅቱ አይሁድ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት በመሆኑና ብዙ ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረከ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለነበር ምናልባት ሁከት ይፈጠራል ብለው ሕዝብን እየፈሩ ሊይዙት ያመነቱ ነበር። ተሳክቶላቸው እንያዘው ቢሉ እንኳን ኢየሱስ ክርስቶስን ከደቀ መዛሙርቱ ለይተው አያውቁትም ስለዚህ እርሱን በቅርብ የሚያውቅ ሰው ያስፈልጋቸዋልና በክፉ ምክራቸው እጅግ ተጨነቁ። ትንሽ ቆይቶ ግን ከደቀመዛሙርቱ መካከል አንዱ የሆነው የአስቆሮቱ ይሁዳ በክፉ ምክራቸው በመሳተፍ ጌታን በመሳም አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ቃል ገባላቸው ። ለምልክት ይሁናቸውም ዘንድም እኔ ሄጄ የምስመው ሰው እርሱ ክርስቶስ ነውና ያዙት ብሎ ተማከረ ጭንቀታቸው ተወገደ ለወረታውም ሰላሣ ብር መዘኑለት (ማቴ 26፡1-5 ፣ ማቴ26፡14-15 ፣ ማር 14፡1-2፣ ሉቃ 22፡1-6) 
#ዕለተ_ረቡዕ_መልካም_መዓዛ_ያለው_ቀንም_ይባላል፣ ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት (ባለ ሽቶዋ ማርያም) ከእንግዲህ ወዲህ በኅጢዓት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ፣ ኀጢዓትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ፣ በአልባሲጥሮስ ብልቃጥ የሞላ ሽቱ ይዛ በመሄድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ነው፡፡ የእንባ ቀን ይባላል ይህም ስያሜ የተሰጠበት ምክንያት ይህችው ማርያም እንተእፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢዓቷን ይቅር እንዲልላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና፣ በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና፡፡ በጠጉሯም ማበሶ አክሊሌ ነክ ስትል ነው ። የማርያም እንተእፍረትን ኃጢዓት ይቅር ብሎ መባዋን የተቀበለ አምላክ ዛሬ በመካከላችን አለና በማንኛውም ጊዜና ሰዓት የራሳችንን ኃጢዓት በማሰብ በማልቀስና የተወደደ መስዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር በማቅረብ በመልካም ሥራዋ ልንመስላት ይገባል፡፡ (ማቴ 26፡6-13 ፣ ሉቃ 7፡36 ፣ ማር 14፡3-9 ፣ ዮሐ 12፡1-8)

...........ይቆየን…..........
#ዐውደ_ምሕረት_የእናንተ
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
#ረቡዕ #የምክር_ቀን
" #ምስጉን_ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ"
_______________________
#መዝ 1÷1

ይህ ዕለት የምክር ቀን ይባላል፣ ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጻሕፋት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር የጀመሩበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ ወቅቱ አይሁድ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት በመሆኑና ብዙ ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረከ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለነበር ምናልባት ሁከት ይፈጠራል ብለው ሕዝብን እየፈሩ ሊይዙት ያመነቱ ነበር። ተሳክቶላቸው እንያዘው ቢሉ እንኳን ኢየሱስ ክርስቶስን ከደቀ መዛሙርቱ ለይተው አያውቁትም ስለዚህ እርሱን በቅርብ የሚያውቅ ሰው ያስፈልጋቸዋልና በክፉ ምክራቸው እጅግ ተጨነቁ። ትንሽ ቆይቶ ግን ከደቀመዛሙርቱ መካከል አንዱ የሆነው የአስቆሮቱ ይሁዳ በክፉ ምክራቸው በመሳተፍ ጌታን በመሳም አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ቃል ገባላቸው ። ለምልክት ይሁናቸውም ዘንድም እኔ ሄጄ የምስመው ሰው እርሱ ክርስቶስ ነውና ያዙት ብሎ ተማከረ ጭንቀታቸው ተወገደ ለወረታውም ሰላሣ ብር መዘኑለት (ማቴ 26፡1-5 ፣ ማቴ26፡14-15 ፣ ማር 14፡1-2፣ ሉቃ 22፡1-6) 
#ዕለተ_ረቡዕ_መልካም_መዓዛ_ያለው_ቀንም_ይባላል፣ ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት (ባለ ሽቶዋ ማርያም) ከእንግዲህ ወዲህ በኅጢዓት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ፣ ኀጢዓትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ፣ በአልባሲጥሮስ ብልቃጥ የሞላ ሽቱ ይዛ በመሄድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ነው፡፡ የእንባ ቀን ይባላል ይህም ስያሜ የተሰጠበት ምክንያት ይህችው ማርያም እንተእፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢዓቷን ይቅር እንዲልላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና፣ በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና፡፡ በጠጉሯም ማበሶ አክሊሌ ነክ ስትል ነው ። የማርያም እንተእፍረትን ኃጢዓት ይቅር ብሎ መባዋን የተቀበለ አምላክ ዛሬ በመካከላችን አለና በማንኛውም ጊዜና ሰዓት የራሳችንን ኃጢዓት በማሰብ በማልቀስና የተወደደ መስዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር በማቅረብ በመልካም ሥራዋ ልንመስላት ይገባል፡፡ (ማቴ 26፡6-13 ፣ ሉቃ 7፡36 ፣ ማር 14፡3-9 ፣ ዮሐ 12፡1-8)

...........ይቆየን…..........
#ዐውደ_ምሕረት_የእናንተ