#ብሂላዊ #ምክሮች
#ሀሜት:- ያለ መሳሪያ ሰዉን መግደል ነዉ
#ማጉረምረም:- ባገኙት በቃኝ ብሎ አለማመስገን ነው።
#ቁጣ:- ከስድብ የሚያደርስ የክፉ አድራጎት መሰረት ነው።
#ብስጭት:- የተበሳጩበትን ነገር ሳይሆን ተመልሶ ራስን የሚጎዳ መርዝ ከክህደት የሚያደርስ የሀጥያት ምንጭ ጭንቀትን የሚያነድ ትንሽ ክብሪት ነዉ።
#መርገም:- አቅም ሲያንስ ወደ ላይ የሚወረወር የደካማ ሰዎች ቀስት ነው።
#መሳደብ:- ህሊናን የሚያቆስል ቁስሉ ቶሎ የማይድን አቅም የሌላቸዉ ሰዎች ዱለ ነው።
#ዋዛ #ፈዛዛ:- በስልት የሚቃኙት የስራ ፈቶች በገና ነው።
#ዘፈን:-😕ለዝሙት የሚያነቃ ልብ የሚወጋ ፍላፃ ነው።
#ድንፋታ:- የጀግኖች ባልትና የሰነፎች ጫጫታ
ነው።
#በክፉ #ማንሾካሾክ:- ቀስ ብለዉ ሰዉን የሚገድልበት የአሳባቂዎች ጩህት ነው።
#ነገር:- ማመላለስ የሚዋደዱትን የሚለያዬበት የዲያቢሎስ የግብር ልጆች መሳርያ ነው።
#የአደራ #ገንዘብ #መብላት:- ሳይጥሩ ሳይግሩ የሰዉ ላብ ሲበሉ የሚኖሩበት የሰነፍ ሰዎች መሳርያቸዉ ነው።
#ሰዉን #ማስነወር:- ሰዉ የወደደዉን የተከበረዉን ስም ለማጥፋት የሚቀቡት የምቀኞች ቀለም ነው።
#መሳለቅ:- የማይታይ የቀናተኞች ጦር ነው።
#ተስፋ:- ከማጣት ወደ ማግኘት ለመሸጋገር የሚያገለግል ድልድይ ነው።
#ጠብ:- እሳትን ለማንደድ የሚጫር የነገረኞች የኪስ ክብሪት ነዉ።
#ችኮላ:- የትእግስት ጠላት የፀፀት አባት ነው ልጁም ወይኔ ይባላል።
#ሙከራ:- የስራ ጥልቀትን መለኪያና መመጠኛ ነው።
#የጥበብ #መጀመርያ #እግዚአብሔርን #መፍራት #ነው።
ከ ያለ ጭንቀት የመኖር ምስጢር መፅሀፍ የተወሰደ በዲ/ን የሺጥላ ሞገስ
#ሀሜት:- ያለ መሳሪያ ሰዉን መግደል ነዉ
#ማጉረምረም:- ባገኙት በቃኝ ብሎ አለማመስገን ነው።
#ቁጣ:- ከስድብ የሚያደርስ የክፉ አድራጎት መሰረት ነው።
#ብስጭት:- የተበሳጩበትን ነገር ሳይሆን ተመልሶ ራስን የሚጎዳ መርዝ ከክህደት የሚያደርስ የሀጥያት ምንጭ ጭንቀትን የሚያነድ ትንሽ ክብሪት ነዉ።
#መርገም:- አቅም ሲያንስ ወደ ላይ የሚወረወር የደካማ ሰዎች ቀስት ነው።
#መሳደብ:- ህሊናን የሚያቆስል ቁስሉ ቶሎ የማይድን አቅም የሌላቸዉ ሰዎች ዱለ ነው።
#ዋዛ #ፈዛዛ:- በስልት የሚቃኙት የስራ ፈቶች በገና ነው።
#ዘፈን:-😕ለዝሙት የሚያነቃ ልብ የሚወጋ ፍላፃ ነው።
#ድንፋታ:- የጀግኖች ባልትና የሰነፎች ጫጫታ
ነው።
#በክፉ #ማንሾካሾክ:- ቀስ ብለዉ ሰዉን የሚገድልበት የአሳባቂዎች ጩህት ነው።
#ነገር:- ማመላለስ የሚዋደዱትን የሚለያዬበት የዲያቢሎስ የግብር ልጆች መሳርያ ነው።
#የአደራ #ገንዘብ #መብላት:- ሳይጥሩ ሳይግሩ የሰዉ ላብ ሲበሉ የሚኖሩበት የሰነፍ ሰዎች መሳርያቸዉ ነው።
#ሰዉን #ማስነወር:- ሰዉ የወደደዉን የተከበረዉን ስም ለማጥፋት የሚቀቡት የምቀኞች ቀለም ነው።
#መሳለቅ:- የማይታይ የቀናተኞች ጦር ነው።
#ተስፋ:- ከማጣት ወደ ማግኘት ለመሸጋገር የሚያገለግል ድልድይ ነው።
#ጠብ:- እሳትን ለማንደድ የሚጫር የነገረኞች የኪስ ክብሪት ነዉ።
#ችኮላ:- የትእግስት ጠላት የፀፀት አባት ነው ልጁም ወይኔ ይባላል።
#ሙከራ:- የስራ ጥልቀትን መለኪያና መመጠኛ ነው።
#የጥበብ #መጀመርያ #እግዚአብሔርን #መፍራት #ነው።
ከ ያለ ጭንቀት የመኖር ምስጢር መፅሀፍ የተወሰደ በዲ/ን የሺጥላ ሞገስ
👍2
#ተስፋ_እንደ_ምትሐት
የግዜር ስውር መዳፍ
ልክ እንደፓፒረስ፥ እንደግብጦች መጣፍ
ወይም እንደጥንቱ፥ ያባጅፋር ምንጣፍ
ጨለማውን ስቦ፥ በወግ ሸበለለ
ስማይ የጠፈር ዓይን፥ ብርሃን ተኳላ
ከዶሮ ጩኸት ውስጥ፥ አዲስ ጎሕ ተወልዶ
ፍጥረቱ በሙሉ፥ ማርያም ማርያም አለ፤
#ነጋ
አልጋየን ሰብሬ
አንሶላ ተርትሬ
ባዲሱ ጉልበቴ
በታደላ አሞቴ
ልኖር ተዘጋጀሁ
እንደጣዝማ ቅንጣት
ከሚጣፍጥ ሞቴ
ትንሳኤየን ዋጀሁ፤
#ነጋ
እንደምትሐተኛ፥ ተስፋ ሲያታልለኝ
አዲሱ ማለዳ፥ “ዛሬን ሞከር” ሲለኝ
የዛሬው እጣየ
ከትናንት ጣጣየ
የሚለይ መሰለኝ።
የግዜር ስውር መዳፍ
ልክ እንደፓፒረስ፥ እንደግብጦች መጣፍ
ወይም እንደጥንቱ፥ ያባጅፋር ምንጣፍ
ጨለማውን ስቦ፥ በወግ ሸበለለ
ስማይ የጠፈር ዓይን፥ ብርሃን ተኳላ
ከዶሮ ጩኸት ውስጥ፥ አዲስ ጎሕ ተወልዶ
ፍጥረቱ በሙሉ፥ ማርያም ማርያም አለ፤
#ነጋ
አልጋየን ሰብሬ
አንሶላ ተርትሬ
ባዲሱ ጉልበቴ
በታደላ አሞቴ
ልኖር ተዘጋጀሁ
እንደጣዝማ ቅንጣት
ከሚጣፍጥ ሞቴ
ትንሳኤየን ዋጀሁ፤
#ነጋ
እንደምትሐተኛ፥ ተስፋ ሲያታልለኝ
አዲሱ ማለዳ፥ “ዛሬን ሞከር” ሲለኝ
የዛሬው እጣየ
ከትናንት ጣጣየ
የሚለይ መሰለኝ።
#ተስፋ
ወቅቱ ክረምት ነው::
ዝናቡ ይዘንባል፣
በረዶ ይጥላል።
ቀኑ ብርዳማ ነው ፤
ሙቀት የናፈቀው::
በዚህ የቁር ዕለት
ሰው በማይወጣበት
ህይወት ያለው ፍጡር -
በአውራ ጎዳናው ላይ - በማይታይበት::
ቀዝቃዛ ቤቴ ውስጥ - ዱካክ ባናወዛት
የቆንጆ ሴት አምሮት - በሚወዘውዛት ፤
በበረደው ቤቴ - ትኩስ አካል ይዤ
በይሆናል ምኞት - በሃሳብ ናውዤ
በጠባብ መስኮቴ - አንገቴን መዝዤ...
ወደ ውጭ አያለሁ፡-
ምናልባት የኔ ውድ!
የእህል ውሐ ነገር
ምኑ ይታወቃል?
የፍቅር አምላክ ደጉ - ከዝናብ ሊያስጥልሽ
ወደ ተከፈተው - ወደ ባዶው ቤቴ
ያስገባሽ ይሆናል፡፡
ዝናቡ ከባድ ነው፣
ማንም የማይደፍረው፡፡
ወጨፎው ይነፍሳል፣
ውሐና በረዶ በበሬ እየገባ -ወለሌን ያርሳል፡፡
ግን መኖሪያ ቤቴ- መዋኛ ቢመስልም
ውስጤ ተስፋ አለና- በሬን አልዘጋሁም፡፡
“ምናልባት የኔ ውድ! -
የእህል ውሐ ነገር
ምኑ ይታመናል?
ወደ እኔ ስትመጭ-
በሩን ከዘጋሁት -
ሰው ያለበት መስሎሽ-
ትዘይኝ ይሆናል!
ብየ ስለማስብ
አለሁልሽ ውዴ፡-
ዝናብ እየመታኝ - ቤቴ እየበረደው
ትመጫለሽ ብዬ - ደጅ ደጁን እያየሁ፡፡
አለሁልሽ ውዴ....
🔘በሙሉቀን🔘
ወቅቱ ክረምት ነው::
ዝናቡ ይዘንባል፣
በረዶ ይጥላል።
ቀኑ ብርዳማ ነው ፤
ሙቀት የናፈቀው::
በዚህ የቁር ዕለት
ሰው በማይወጣበት
ህይወት ያለው ፍጡር -
በአውራ ጎዳናው ላይ - በማይታይበት::
ቀዝቃዛ ቤቴ ውስጥ - ዱካክ ባናወዛት
የቆንጆ ሴት አምሮት - በሚወዘውዛት ፤
በበረደው ቤቴ - ትኩስ አካል ይዤ
በይሆናል ምኞት - በሃሳብ ናውዤ
በጠባብ መስኮቴ - አንገቴን መዝዤ...
ወደ ውጭ አያለሁ፡-
ምናልባት የኔ ውድ!
የእህል ውሐ ነገር
ምኑ ይታወቃል?
የፍቅር አምላክ ደጉ - ከዝናብ ሊያስጥልሽ
ወደ ተከፈተው - ወደ ባዶው ቤቴ
ያስገባሽ ይሆናል፡፡
ዝናቡ ከባድ ነው፣
ማንም የማይደፍረው፡፡
ወጨፎው ይነፍሳል፣
ውሐና በረዶ በበሬ እየገባ -ወለሌን ያርሳል፡፡
ግን መኖሪያ ቤቴ- መዋኛ ቢመስልም
ውስጤ ተስፋ አለና- በሬን አልዘጋሁም፡፡
“ምናልባት የኔ ውድ! -
የእህል ውሐ ነገር
ምኑ ይታመናል?
ወደ እኔ ስትመጭ-
በሩን ከዘጋሁት -
ሰው ያለበት መስሎሽ-
ትዘይኝ ይሆናል!
ብየ ስለማስብ
አለሁልሽ ውዴ፡-
ዝናብ እየመታኝ - ቤቴ እየበረደው
ትመጫለሽ ብዬ - ደጅ ደጁን እያየሁ፡፡
አለሁልሽ ውዴ....
🔘በሙሉቀን🔘
👍1