#በራ_የመስቀል_ደመራ
በራ የመስቀል ደመራ
የአደይ ችቦ እየፋመ እየጋመ
ኢዮሃ እያስገመገመ እየተመመ
#የመስቀል_ደመራ_በራ
በራ የአዲስ ዘመን ችቦ
በመስከረም ሰብል አብቦ
ከዋክብቱን ፈነጠቀ
ርችቱን አንፀባረቀ
ተኳለ አዲስ ደመቀ
መልኩን በቀለም አዝርእት፤ በጥበብ
አጥለቀለቀ።
ሸለቆው ተንቆጠቆጠ፡ ተራራው አሸበረቀ
ኢዮሃ ኢዮሃ አበባዬ፡ ምድር ሕይወት አፈለቀ፡፡
ነጋ፡ የአዲስ ዘመን ችቦ
ፈካ፡ ፀደይ አረብቦ
ሌሊቱ እንደጎሕ ቀደደ፤ ጨለማው እንደቀን
ጠራ
እንደውቅያኖስ ዕፅዋት፤ እንደጠፈር ኮከብ
ደራ
ምድር ሥጋጃ ለበሰ፤ የጌጥ አልባሳት ተቀባ
ሰማይ በእልልታ አስተጋባ
ኢዮሃ መስከረም ጠባ፡፡
ነጋ የአዲስ ዘመን ችቦ፤ ምድር ሕይወት
አፈለቀች
የምሥራች አዝርእቷን፤ አዲስ ቡቃያ ወሰደች
የአደይ አበባን ለገሠች
ለአዲስ ዘመን አዲስ ብርሃን፤ አዲስ
መስከረም ገበየች
#ነጋ የአዲስ ዘመን ችቦ
#ፈካ ፀደይ አረብቦ
#በራ
የመስቀል ደመራ፡፡
🔘ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን🔘
💚💛❤️
በራ የመስቀል ደመራ
የአደይ ችቦ እየፋመ እየጋመ
ኢዮሃ እያስገመገመ እየተመመ
#የመስቀል_ደመራ_በራ
በራ የአዲስ ዘመን ችቦ
በመስከረም ሰብል አብቦ
ከዋክብቱን ፈነጠቀ
ርችቱን አንፀባረቀ
ተኳለ አዲስ ደመቀ
መልኩን በቀለም አዝርእት፤ በጥበብ
አጥለቀለቀ።
ሸለቆው ተንቆጠቆጠ፡ ተራራው አሸበረቀ
ኢዮሃ ኢዮሃ አበባዬ፡ ምድር ሕይወት አፈለቀ፡፡
ነጋ፡ የአዲስ ዘመን ችቦ
ፈካ፡ ፀደይ አረብቦ
ሌሊቱ እንደጎሕ ቀደደ፤ ጨለማው እንደቀን
ጠራ
እንደውቅያኖስ ዕፅዋት፤ እንደጠፈር ኮከብ
ደራ
ምድር ሥጋጃ ለበሰ፤ የጌጥ አልባሳት ተቀባ
ሰማይ በእልልታ አስተጋባ
ኢዮሃ መስከረም ጠባ፡፡
ነጋ የአዲስ ዘመን ችቦ፤ ምድር ሕይወት
አፈለቀች
የምሥራች አዝርእቷን፤ አዲስ ቡቃያ ወሰደች
የአደይ አበባን ለገሠች
ለአዲስ ዘመን አዲስ ብርሃን፤ አዲስ
መስከረም ገበየች
#ነጋ የአዲስ ዘመን ችቦ
#ፈካ ፀደይ አረብቦ
#በራ
የመስቀል ደመራ፡፡
🔘ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን🔘
💚💛❤️
#ተስፋ_እንደ_ምትሐት
የግዜር ስውር መዳፍ
ልክ እንደፓፒረስ፥ እንደግብጦች መጣፍ
ወይም እንደጥንቱ፥ ያባጅፋር ምንጣፍ
ጨለማውን ስቦ፥ በወግ ሸበለለ
ስማይ የጠፈር ዓይን፥ ብርሃን ተኳላ
ከዶሮ ጩኸት ውስጥ፥ አዲስ ጎሕ ተወልዶ
ፍጥረቱ በሙሉ፥ ማርያም ማርያም አለ፤
#ነጋ
አልጋየን ሰብሬ
አንሶላ ተርትሬ
ባዲሱ ጉልበቴ
በታደላ አሞቴ
ልኖር ተዘጋጀሁ
እንደጣዝማ ቅንጣት
ከሚጣፍጥ ሞቴ
ትንሳኤየን ዋጀሁ፤
#ነጋ
እንደምትሐተኛ፥ ተስፋ ሲያታልለኝ
አዲሱ ማለዳ፥ “ዛሬን ሞከር” ሲለኝ
የዛሬው እጣየ
ከትናንት ጣጣየ
የሚለይ መሰለኝ።
የግዜር ስውር መዳፍ
ልክ እንደፓፒረስ፥ እንደግብጦች መጣፍ
ወይም እንደጥንቱ፥ ያባጅፋር ምንጣፍ
ጨለማውን ስቦ፥ በወግ ሸበለለ
ስማይ የጠፈር ዓይን፥ ብርሃን ተኳላ
ከዶሮ ጩኸት ውስጥ፥ አዲስ ጎሕ ተወልዶ
ፍጥረቱ በሙሉ፥ ማርያም ማርያም አለ፤
#ነጋ
አልጋየን ሰብሬ
አንሶላ ተርትሬ
ባዲሱ ጉልበቴ
በታደላ አሞቴ
ልኖር ተዘጋጀሁ
እንደጣዝማ ቅንጣት
ከሚጣፍጥ ሞቴ
ትንሳኤየን ዋጀሁ፤
#ነጋ
እንደምትሐተኛ፥ ተስፋ ሲያታልለኝ
አዲሱ ማለዳ፥ “ዛሬን ሞከር” ሲለኝ
የዛሬው እጣየ
ከትናንት ጣጣየ
የሚለይ መሰለኝ።