አትሮኖስ
282K subscribers
112 photos
3 videos
41 files
491 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ብሂላዊ #ምክሮች

#ሀሜት:- ያለ መሳሪያ ሰዉን መግደል ነዉ
#ማጉረምረም:- ባገኙት በቃኝ ብሎ አለማመስገን ነው።
#ቁጣ:- ከስድብ የሚያደርስ የክፉ አድራጎት መሰረት ነው።
#ብስጭት:- የተበሳጩበትን ነገር ሳይሆን ተመልሶ ራስን የሚጎዳ መርዝ ከክህደት የሚያደርስ የሀጥያት ምንጭ ጭንቀትን የሚያነድ ትንሽ ክብሪት ነዉ።
#መርገም:- አቅም ሲያንስ ወደ ላይ የሚወረወር የደካማ ሰዎች ቀስት ነው።
#መሳደብ:- ህሊናን የሚያቆስል ቁስሉ ቶሎ የማይድን አቅም የሌላቸዉ ሰዎች ዱለ ነው።
#ዋዛ #ፈዛዛ:- በስልት የሚቃኙት የስራ ፈቶች በገና ነው።
#ዘፈን:-😕ለዝሙት የሚያነቃ ልብ የሚወጋ ፍላፃ ነው።
#ድንፋታ:- የጀግኖች ባልትና የሰነፎች ጫጫታ
ነው።
#በክፉ #ማንሾካሾክ:- ቀስ ብለዉ ሰዉን የሚገድልበት የአሳባቂዎች ጩህት ነው።
#ነገር:- ማመላለስ የሚዋደዱትን የሚለያዬበት የዲያቢሎስ የግብር ልጆች መሳርያ ነው።
#የአደራ #ገንዘብ #መብላት:- ሳይጥሩ ሳይግሩ የሰዉ ላብ ሲበሉ የሚኖሩበት የሰነፍ ሰዎች መሳርያቸዉ ነው።
#ሰዉን #ማስነወር:- ሰዉ የወደደዉን የተከበረዉን ስም ለማጥፋት የሚቀቡት የምቀኞች ቀለም ነው።
#መሳለቅ:- የማይታይ የቀናተኞች ጦር ነው።
#ተስፋ:- ከማጣት ወደ ማግኘት ለመሸጋገር የሚያገለግል ድልድይ ነው።
#ጠብ:- እሳትን ለማንደድ የሚጫር የነገረኞች የኪስ ክብሪት ነዉ።
#ችኮላ:- የትእግስት ጠላት የፀፀት አባት ነው ልጁም ወይኔ ይባላል።
#ሙከራ:- የስራ ጥልቀትን መለኪያና መመጠኛ ነው።
#የጥበብ #መጀመርያ #እግዚአብሔርን #መፍራት #ነው
ከ ያለ ጭንቀት የመኖር ምስጢር መፅሀፍ የተወሰደ በዲ/ን የሺጥላ ሞገስ
👍2
#የጀርባ #ነገር

አንድ ጊዜ የመንደራችን ልጅ በምግብ ዝግጅት ተመርቃ እራት ግብዣ ጠራችን .... ሴቱ ሁሉ እራሱን እስኪስት ዘንጦ ይገባል....(ያው ሴቶች ሰንበቴም ቢጠሩ የእራት ልብስ መልበስ ይወዱ የለ) !
ያልተለበሰ አይነት ልብስ የለም የሚበዛው የተራቆተ ነው ! አጭር ቀሚስ ጫፉ መሬትን እንደመንግስተ ሰማየት የናፈቀ ........ደረቱ ተከፍቶ ከግራና ከቀኝ በጡት ማስያዣ አነሳሽነት ደረት ላይ ለአመፅ የተሰበሰበ ጡት .... ከተመልካች አይን ጋር በእትብት የተያያዘ ይመሰል መሸፈን የጠላ እንብርት ..... ብቻ እራት ተባልን እንጅ የተራቆተ ጅስም እነድናይ የተጠራን ነበር የሚመስለው (ለፍትፍት ተጠርተን ፊት ስናይ አመሸን ቢባል ....ሂሂሂ)
አጠገቤ የተቀመጡት ሰውየ ታዲያ መነፅራቸውን እያስተካከሉ አላፊ አግዳሚወቹን እንደፔንዱለም አንገታቸው እስኪቀጭ እየተወዛወዙ ሲያዮ የሜዳ ቴንስ የሚያዩ ይመስሉ ነበር ...
አንዷ በገባች ቁጥር ‹‹በስማም...እንደው እግዜርን ባትፈራ ብርድ አትፈራም ›› ይላሉ
ትንሽ ቆይተው ደግሞ ሌላኛዋን ያዩና‹‹ ትፍ አሁን ይሄ ተገቢ ነው ...እንደፈጠራት እርቃኗን .....›› ይላሉ ግን ምራቃቸውን ሲውጡ በጉሮሯቸው ላይ እንቅርታቸው ሲያወጣና ሲወርድ በግልፅ ይታይ ነበር
በመጨረሻ የሚያምር ረዥም የእራት ቀሚስ የለበሰች ልጅ ገባች.... ሰውየው ደስ አላቸው እስከአንገቷ የሚደርሰው ቀሚስ ከእጆቿ በቀር ሙሉ ነበር .....እንደውም ባለተረከዝ ጫማ ባታደርግ ቀሚሷ መሬት ይነካ ነበር
‹‹ ተባረኪ! እንዲህ ነው ባህላችን ወጋችን ጨዋ ያሳደጋት...እግዜር ለቁም ነገር ያብቃሽ ››.....እያሉ ማሞገሳቸውን ሳይጨርሱ ልጅቱ እኛ በተቀመጥንበት አለፈች .......ሰውየው ድንገት ሙገሳቸውን አቁመው ‹‹ በስመ አብ›› አሉ ከኋላዋ እያፈጠጡባት .... የልጅቱ ጀርባ ከመቀመጫዋ ከፍ ብሎ ጀምሮ ራቁት ነበር ...
‹‹ ጀርባ ሳናጠና እየሾምን . እና እየባረክን እኮ ነው ትውልድና አገር ሆድና ጀርባ እንዲሆን ምናደርገው ›› አሉና እስከመድረሻዋ በአይናቸው ሸኟት ቆንጆዋን !!

🔘አሌክስ🔘
አብሮነታችሁን በዚ 👍 አሳዩን
👍3
#ነገር_በምሳሌ

#እንበሳ፡-
በራሱ እምነት ስላለው - ስለማይኖር ተደብቆ
ምንን ለምን እንደሚያድን - ያውቀዋልና ጠንቅቆ፣
መዳፎቹን የማይሞሉ - የአይጥ መንጋ ተሰባስበው
ቢርመሰመሱ ቢጮሁ አንበሳውን ዙሪያ ከበው፣
እንዳያመልጠው ዋናው አደን - የአይጥን መንጋ ሲያሯሩጥ
አላርፍም ቢሉም አይጦቹ - ቢጮሁ ቢሉ ሲጥ ሲጥ
ፀጥ!!!

#ውሻ፡-
እፊቱ ላይ ድመት ቆማ - እንደ ነብር ብትጮህበት
አካሏ አብጦ - ጸጉሯ ቆሞ - ተገትራ ብታፈጥበት፣
ያውቀዋልና ውሻው - ድመቷን እንደሚረታ
ጫፉን እስካልነካችው - አፍንጫው ስር ተጠግታ፣
ብትነፋፋ፣ ብትኮፈስ፣ ብትዘል፣ ብትፈርጥ፣ ብትወራጭ
ጭጭ!!!

አንዳንድ #ሰውም፡-
አንዱ በዚህ ሲቦጭቀው
አንዱ በዚያ ሲያመናጭቀው
በጆሮቹ እየሰማ - እየሳቀ ዝም የሚለው፣
አይደለም ቃላት ጠፍቶበት አይደለም ስለበሸቀው
ስራ የፈታ ቢያወራም - እሱ ራሱን ስለሚያውቀው፡፡
እሉ ራሱን ስለሚያውቀው - ሰው ስለሱ ብዙ ቢልም
ዝም!!!

🔘በሙሉቀን🔘