#ቅድስትና_ትዕግስት
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
ቅድስት ልክ ስምንት ሰዕት ከሩብ ሲል ትዕግስት ቤት ደረሰች፡፡
“ውይ ቅድስትዬ...! ምነው እንዲህ ጠቋቆርሽ...? ፀሐይ እንኳን የለ ዛሬ..! አለች፣ ትዕግስት አራት ጊዜ ጉንጭዋን ስማት ስታበቃ....
“ኧረ ተይኝ ባክሽ....ለእንደኔ ያለ ሰው ከነዚያ ሴቶች ጋር ሦስት ሠዐት ሙሉ ስለ ልብስና ጫማ ማውራት ራሱ፣ ከሰባት ፀሐይ በላይ አያከስልም?” አለች ቅድስት፣ ሶፋው ላይ ዝርፍጥ ብላ እየተቀመጠች...
እናም፣ በተገናኙ ቁጥር የሚያደሩት ተመሳሳይ ወሬያቸው በእንዲህ ሁኔታ ተጀመረ፡፡
“አይ ለእኔ ነው ስለነሱ የምትነግሪኝ ቅድስትዬ? እኔስ ምናቸው
አስመርሮኝ ብረንች መምጣት ተውኩና!”
ደግ አደረግሽ... እኔ የምለው? ማስተርስ ድረስ የተማሩ ሴቶችከልብስና ከወንድ ውጪ ሌላ ነገር ማውራት አለመቻላቸው
አያሳዝንም? በጣም ያሳፍራል እኮ!”
በጣም እንጂ... ዐሥር ሴት ሚኒስትር ቢሾም ታች ያለነው ሴቶች
”ትላንት ስለገዛነው፣ ነገ ስለምንገዛው፣ ልንገዛ ፈልገን ስላጣነው ቶፕ ብቻ ምናወራ ከሆነ፣ ይህች ሀገር እንዴት ብላ ቀና ትላለች...? ሲንፏቀቁ መኖር እኮ ነው!”
“ጎሽ... እኔ እኮ አንቺ ጋር መምጣት የምወደው ለዚህ ነው...
ተንፈስ ስለምታደርጊኝ... ቁምነገር ስለምታዋሪኝ እኮ ነው አንቺ ጋር
መምጣት ደስ የሚለኝ ቲጂዬ!”
“እኔስ ብትይ....! እሺ..... ዛሬስ ምን ተፈጠረ ታዲያ?”
“ምን አዲስ ነገር ይፈጠራል... ያው ሴሞ ሴሞ ነው..ሃሚት ሃሜት... ወሬ... ሰው ቡጨቃ…. እይው የገዛሁትን ልብስ... ይሄ
ሽቶ ደስ አይልም...? እገሊት ጂም ጀመረች.. እንትና ዮጋ ጀመረች
ይሄው ነው ቲጂዬ!”
“አይገርመኝም...ዘለዓለም ያው ናቸው... ዘለዓለም.. ማፈሪያዎች!”
“እህስ!...ዛሬ ደግሞ ያቺ ሶሎሜ መጥታ ጭራሽ ስትጠብስኝ አረፈደች... ደህና ተገላግለናት ነበር፡፡”
“መጣች እንዴ? ዱባይ ቫኬሽን ላይ ነኝ ምናምን ብላ ስታናፋ አልነበረም እንዴ?”
“እንግዲህ ያ የግፍ ዶላር ቶሎ አልቆ ይሆናላ! ወር ሳይሞላት ተመለሰች!”
“አዬ! ለዚህችው ነው ያ ሁሉ ጉራ! ...ግን አንቺን ምን አርጋ አናደደችሽ ቅድስትዬ?”
አረ ተይኝ ገና በሥርዓት እንኳን ሳልቀመጥ እየሮጠች መጥታ ቶፕሽ ያምራል... እኔ የዛሬ ሁለት ዓመት በአራት መቶ ብር ገዝቼው ነበር...በቢጫው አለኝ... አሁን ግን ፋሽን ስላለፈበት ለሠራተኛዬ ስጠኋት' አትለኝም?"
“አታደርገውም!”
"አደረገችው እንጂ ትግስትዬ! አደረገችው!"
እና አንቺስ ዝም አልሻት?”
"ማ? እኔ ቅድስት እንዲህ ባደባባይ ሰድባኝ ዝም የምላት ይመስልሻል?"
“እና... እና ምናልሻት?”
የኔ እናት... ተማስሎብሽ ይሆናል... ይሄ ሌተስት ፋሽን ነው... የጣሊያን እቃ ነው! የገዛሁት ደግሞ አንድ ሺህ ስምንት
መቶ ብር ነው ... አልኳታ!”
'ወይኔ አንቺ... አንጀት አርስ እኮ ነሽ!"
“ታዲያስ...የሆነች ባላገር...ትላንት ብረንች ማለት አቅቷት፣
ብራንች የምትል ሴትዮ፤ አንዴ ዱባይ ሄጄ መጣሁ ብላ ትላጥብኛለች እንዴ?”
ሃሃ... አይ ቅድስት!”
ይልቅ እነሱን ተያቸውና ቲጂዬ የሚበላ ነገር አለሽ? ሁሉም ሰው ዳይት ላይ ነኝ ምናምን ብሎ ደህና ነገር አልበላሁም፡፡”
“ተይ እንጂ...! ዛሬም ዳይት ላይ ናቸው?”
“ታዲያስ! ለተቆራረጠ ሙዝ ሰማንያ ብር ይከፍላሉ... ዳይት ላይ ነኝ... መቀነስ አለብኝ ቅብጥርሶ ይላሉ፡፡ ምናለ ስለአንጎላቸው እንዲህ ቢጨነቁ......!”
“እኮ...! እና ታዲያ ምን ላምጣልሽ?"
“ሥጋ... ቅባት ያለው ነገር ምናምን... አታምጪብኝ! ትንሽ ጨምሬያለሁ ሰሞኑን ደግሞ...”
“ኧረ ተይ! ምንም አልጨመርሽም ቅድስትዬ! እንደውም ሳትከሺ አትቀሪም...”
“አይ ቲጂዬ...ቦዲ ሼፐር አርጌ ነው... ቦርጩን ጥፍንግ አድርጎ ስለያዘልኝ ነው...”
“ፓ! አሪፍ ነገር ነው ባክሽ... የት አገኘሽው? እኔ ፈልጌ ፈልጌ የሚሆነኝ አጣሁ...”
“መድኀኔ ዓለም ሞል ግራውንድ ፍሎር ላይ የሆነ ቤት አለ....
መዓት አላቸው... ዘጠኝ መቶ ብር ነው የገዛሁት... ብዙ አይመችም
ግን ቢያንስ ይሰበስብሻል... አብረን ሄደን ትገዣለሽ ሰሞኑን..."
“እሺ... አስታውሺኝ በቃ... ያስፈልገኛል.... በይ በቃ ሽሮ ላምጣልሽ
እንግዲህ....”
እሺ“ ቲጂዬ...”
ቅድስት የቀረበውን ሽሮ መብላት ጀመረች::
“ውይ ቲጂዬ! ሲጣፍጥ ግን ቅቤ ሞጀርሽበት”
“ሃሃ... ለዚያ እኮ ነው ሚጣፍጠው.."
“ልቀንስ እያልኩሽ ቅቤ ትግችኛለሽ አይደል... አንቺ ምን አለብሽ?”
“ብዪ ባክሽ... ከልኩ አያልፍም..."
“ምን? ቦርጭ?”
“አዎ....”
“ሃሃሃ!”
“ኧረ ቅድስትዬ ሳልነግርሽ... ዮጋ እኮ ጀመርኩ.... ቀጥ አላልኩብሽም ትንሽ?”
“ዮጋ?”
“አዎ... "
“ጎበዝ ነሽ ልጄ... እኔ አንዴ ከሰኒ ጋር ጀምሬ እናቴ... ሁለመናዬ ተላቀቀ፡፡ እሱን ለመጠገን አጥሚት እና መረቅ ስበላልሽ ነው ይሄን ቦርጭ እዚህ ያደረስኩት ቲጂዬ!”
ሃሃሃ... ቀልድሽ እኮ ደስ ሲለኝ ቅድስትዬ!”
አሹፊ አንቺ.... ይልቅ ማን በጣም እንደከሳ ገምቺ...”
እሌሊ..
ማ?
“እሌኒ እሌኒ? መርሻ?”
“እህ!”
“እንዴ? እንዴት አርጋ ከሳች በናትሽ?”
“ሙግግ ብላ መጣች ዛሬ... በሳምንት ሁለት ኪሎ እየቀነስኩ አሁን
ዓሥራ ሁለት ኪሎ ቀንሻለሁ አለችን...”
“ተይ ባክሽ... ያን ሁሉ ሰውነት እንዴት አድርጋ ናደችው በናትሽ?”
“የሆነ ቲቪ ላይ የሚታይ የዳይት ሾው አለ አሉ... እሱን አይቼ ሄጄ ነው አለችኝ...”
“ምን ቲቪ ላይ? እዚህ አገር?”
“አዎ...”
“እና ሄዳ ምን አደረጉላት?”
“ምግብ መጥነው ይሠሩልሻል አሉ... በወር አራት ሺህ ብር እከፍልና ምግቤን ይሠሩልኛል... አሽገው ቤቴ ድረስ አምጥተው ይሰጡኛል አለችኝ...”
“ተይ እንጂ... ምን ቲቪ ነው ልጄ?”
“ፋና መሰለኝ...”
“ለነገሩ እኔ እንዲህ ያለ ነገር ብዙም አይመቸኝ... ግን መቼ መቼ
ነው የሚታየው አለችሽ?”
“እንጃ... እሁድ መሰለኝ... ብቻ ምሳና እራት ዐስራ ሁለት መኮረኒ ተቆጥሮ ነው የሚሰጠኝ ብላ አሳቀችኝ!"
“ሃሃሃ... አትይኝም?”
“ሙች!”
“እና ግን አከሳት?”
በጣም... ምግቡ እህል ቅጠል አይልም፤ ግን ካከሳኝ ምን ቸገረኝ ምናምን አለችኝ...”
“ይገርማል... አምሮባታል በይኛ!”
“ያው መቼስ... ትንሽ ሙግግ ብላለች፣ ረኀብተኛ ነው የምትመስለው፤ ግን ቦርጭዋ ጠፍቶላታል፡፡ ለነገሩ ዛሬ ዕድሜ
ለብራዚል ሂውማን ሄር የማታምር ሴት አለች?”
“ልክ ነሽ እሱስ... ሂውማን ሄር ሴቱን ሁሉ እኩል አደረገው
እኮ.... ምን ዋጋ አለው... ጸጉር ጭንቅላት አይሆን!”
“እኮ!”
የሚገርመኝ ግን ብር ኖሯቸው እንኳን ደህናውን አይገዙም እኮ...
የኔን ዕይው አሁን ከጣልያን ነው ያስመጣሁት... ይኸው ሁለት
ዓመቱ ንቅንቅ አላለም... ከገዛሽ ደህና ነገር ነው... የሚልከሰከስ ሰው አልወድም እኔ...”
“እሺ... ሌላስ ምን አዲስ አለ ታዲያ!”
“ዝናሽም በስንት ጊዜዋ ዛሬ መጥታ ነበር!”
“ተይ እንጂ! እንዴት ናት?”
“አረጀችብኝ.... ጉስቁልቁል ብላለች... ያው እሷን ታውቂያታለሽ.በሜካፕ ኀይል ነው እንጂ እኮ ዕድሜዋ ሄዷል..."
“አዎ እሱስ... ምን ሜካፕ ብትለቀለቅ አንገቷ አሳልፎ ይሰጣት የለ...
ያ.. የአውራ ዶሮ ኩልኩልት የመሰለ አንገት..."
“አንቺ ተይ በስማም... ሃሃሃ!”
“ምን ላርግ ብለሽ ነው....? ደግሞ እኮ ሰው መልክ ባይኖረው ፀባይ
አይኖረውም?
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
ቅድስት ልክ ስምንት ሰዕት ከሩብ ሲል ትዕግስት ቤት ደረሰች፡፡
“ውይ ቅድስትዬ...! ምነው እንዲህ ጠቋቆርሽ...? ፀሐይ እንኳን የለ ዛሬ..! አለች፣ ትዕግስት አራት ጊዜ ጉንጭዋን ስማት ስታበቃ....
“ኧረ ተይኝ ባክሽ....ለእንደኔ ያለ ሰው ከነዚያ ሴቶች ጋር ሦስት ሠዐት ሙሉ ስለ ልብስና ጫማ ማውራት ራሱ፣ ከሰባት ፀሐይ በላይ አያከስልም?” አለች ቅድስት፣ ሶፋው ላይ ዝርፍጥ ብላ እየተቀመጠች...
እናም፣ በተገናኙ ቁጥር የሚያደሩት ተመሳሳይ ወሬያቸው በእንዲህ ሁኔታ ተጀመረ፡፡
“አይ ለእኔ ነው ስለነሱ የምትነግሪኝ ቅድስትዬ? እኔስ ምናቸው
አስመርሮኝ ብረንች መምጣት ተውኩና!”
ደግ አደረግሽ... እኔ የምለው? ማስተርስ ድረስ የተማሩ ሴቶችከልብስና ከወንድ ውጪ ሌላ ነገር ማውራት አለመቻላቸው
አያሳዝንም? በጣም ያሳፍራል እኮ!”
በጣም እንጂ... ዐሥር ሴት ሚኒስትር ቢሾም ታች ያለነው ሴቶች
”ትላንት ስለገዛነው፣ ነገ ስለምንገዛው፣ ልንገዛ ፈልገን ስላጣነው ቶፕ ብቻ ምናወራ ከሆነ፣ ይህች ሀገር እንዴት ብላ ቀና ትላለች...? ሲንፏቀቁ መኖር እኮ ነው!”
“ጎሽ... እኔ እኮ አንቺ ጋር መምጣት የምወደው ለዚህ ነው...
ተንፈስ ስለምታደርጊኝ... ቁምነገር ስለምታዋሪኝ እኮ ነው አንቺ ጋር
መምጣት ደስ የሚለኝ ቲጂዬ!”
“እኔስ ብትይ....! እሺ..... ዛሬስ ምን ተፈጠረ ታዲያ?”
“ምን አዲስ ነገር ይፈጠራል... ያው ሴሞ ሴሞ ነው..ሃሚት ሃሜት... ወሬ... ሰው ቡጨቃ…. እይው የገዛሁትን ልብስ... ይሄ
ሽቶ ደስ አይልም...? እገሊት ጂም ጀመረች.. እንትና ዮጋ ጀመረች
ይሄው ነው ቲጂዬ!”
“አይገርመኝም...ዘለዓለም ያው ናቸው... ዘለዓለም.. ማፈሪያዎች!”
“እህስ!...ዛሬ ደግሞ ያቺ ሶሎሜ መጥታ ጭራሽ ስትጠብስኝ አረፈደች... ደህና ተገላግለናት ነበር፡፡”
“መጣች እንዴ? ዱባይ ቫኬሽን ላይ ነኝ ምናምን ብላ ስታናፋ አልነበረም እንዴ?”
“እንግዲህ ያ የግፍ ዶላር ቶሎ አልቆ ይሆናላ! ወር ሳይሞላት ተመለሰች!”
“አዬ! ለዚህችው ነው ያ ሁሉ ጉራ! ...ግን አንቺን ምን አርጋ አናደደችሽ ቅድስትዬ?”
አረ ተይኝ ገና በሥርዓት እንኳን ሳልቀመጥ እየሮጠች መጥታ ቶፕሽ ያምራል... እኔ የዛሬ ሁለት ዓመት በአራት መቶ ብር ገዝቼው ነበር...በቢጫው አለኝ... አሁን ግን ፋሽን ስላለፈበት ለሠራተኛዬ ስጠኋት' አትለኝም?"
“አታደርገውም!”
"አደረገችው እንጂ ትግስትዬ! አደረገችው!"
እና አንቺስ ዝም አልሻት?”
"ማ? እኔ ቅድስት እንዲህ ባደባባይ ሰድባኝ ዝም የምላት ይመስልሻል?"
“እና... እና ምናልሻት?”
የኔ እናት... ተማስሎብሽ ይሆናል... ይሄ ሌተስት ፋሽን ነው... የጣሊያን እቃ ነው! የገዛሁት ደግሞ አንድ ሺህ ስምንት
መቶ ብር ነው ... አልኳታ!”
'ወይኔ አንቺ... አንጀት አርስ እኮ ነሽ!"
“ታዲያስ...የሆነች ባላገር...ትላንት ብረንች ማለት አቅቷት፣
ብራንች የምትል ሴትዮ፤ አንዴ ዱባይ ሄጄ መጣሁ ብላ ትላጥብኛለች እንዴ?”
ሃሃ... አይ ቅድስት!”
ይልቅ እነሱን ተያቸውና ቲጂዬ የሚበላ ነገር አለሽ? ሁሉም ሰው ዳይት ላይ ነኝ ምናምን ብሎ ደህና ነገር አልበላሁም፡፡”
“ተይ እንጂ...! ዛሬም ዳይት ላይ ናቸው?”
“ታዲያስ! ለተቆራረጠ ሙዝ ሰማንያ ብር ይከፍላሉ... ዳይት ላይ ነኝ... መቀነስ አለብኝ ቅብጥርሶ ይላሉ፡፡ ምናለ ስለአንጎላቸው እንዲህ ቢጨነቁ......!”
“እኮ...! እና ታዲያ ምን ላምጣልሽ?"
“ሥጋ... ቅባት ያለው ነገር ምናምን... አታምጪብኝ! ትንሽ ጨምሬያለሁ ሰሞኑን ደግሞ...”
“ኧረ ተይ! ምንም አልጨመርሽም ቅድስትዬ! እንደውም ሳትከሺ አትቀሪም...”
“አይ ቲጂዬ...ቦዲ ሼፐር አርጌ ነው... ቦርጩን ጥፍንግ አድርጎ ስለያዘልኝ ነው...”
“ፓ! አሪፍ ነገር ነው ባክሽ... የት አገኘሽው? እኔ ፈልጌ ፈልጌ የሚሆነኝ አጣሁ...”
“መድኀኔ ዓለም ሞል ግራውንድ ፍሎር ላይ የሆነ ቤት አለ....
መዓት አላቸው... ዘጠኝ መቶ ብር ነው የገዛሁት... ብዙ አይመችም
ግን ቢያንስ ይሰበስብሻል... አብረን ሄደን ትገዣለሽ ሰሞኑን..."
“እሺ... አስታውሺኝ በቃ... ያስፈልገኛል.... በይ በቃ ሽሮ ላምጣልሽ
እንግዲህ....”
እሺ“ ቲጂዬ...”
ቅድስት የቀረበውን ሽሮ መብላት ጀመረች::
“ውይ ቲጂዬ! ሲጣፍጥ ግን ቅቤ ሞጀርሽበት”
“ሃሃ... ለዚያ እኮ ነው ሚጣፍጠው.."
“ልቀንስ እያልኩሽ ቅቤ ትግችኛለሽ አይደል... አንቺ ምን አለብሽ?”
“ብዪ ባክሽ... ከልኩ አያልፍም..."
“ምን? ቦርጭ?”
“አዎ....”
“ሃሃሃ!”
“ኧረ ቅድስትዬ ሳልነግርሽ... ዮጋ እኮ ጀመርኩ.... ቀጥ አላልኩብሽም ትንሽ?”
“ዮጋ?”
“አዎ... "
“ጎበዝ ነሽ ልጄ... እኔ አንዴ ከሰኒ ጋር ጀምሬ እናቴ... ሁለመናዬ ተላቀቀ፡፡ እሱን ለመጠገን አጥሚት እና መረቅ ስበላልሽ ነው ይሄን ቦርጭ እዚህ ያደረስኩት ቲጂዬ!”
ሃሃሃ... ቀልድሽ እኮ ደስ ሲለኝ ቅድስትዬ!”
አሹፊ አንቺ.... ይልቅ ማን በጣም እንደከሳ ገምቺ...”
እሌሊ..
ማ?
“እሌኒ እሌኒ? መርሻ?”
“እህ!”
“እንዴ? እንዴት አርጋ ከሳች በናትሽ?”
“ሙግግ ብላ መጣች ዛሬ... በሳምንት ሁለት ኪሎ እየቀነስኩ አሁን
ዓሥራ ሁለት ኪሎ ቀንሻለሁ አለችን...”
“ተይ ባክሽ... ያን ሁሉ ሰውነት እንዴት አድርጋ ናደችው በናትሽ?”
“የሆነ ቲቪ ላይ የሚታይ የዳይት ሾው አለ አሉ... እሱን አይቼ ሄጄ ነው አለችኝ...”
“ምን ቲቪ ላይ? እዚህ አገር?”
“አዎ...”
“እና ሄዳ ምን አደረጉላት?”
“ምግብ መጥነው ይሠሩልሻል አሉ... በወር አራት ሺህ ብር እከፍልና ምግቤን ይሠሩልኛል... አሽገው ቤቴ ድረስ አምጥተው ይሰጡኛል አለችኝ...”
“ተይ እንጂ... ምን ቲቪ ነው ልጄ?”
“ፋና መሰለኝ...”
“ለነገሩ እኔ እንዲህ ያለ ነገር ብዙም አይመቸኝ... ግን መቼ መቼ
ነው የሚታየው አለችሽ?”
“እንጃ... እሁድ መሰለኝ... ብቻ ምሳና እራት ዐስራ ሁለት መኮረኒ ተቆጥሮ ነው የሚሰጠኝ ብላ አሳቀችኝ!"
“ሃሃሃ... አትይኝም?”
“ሙች!”
“እና ግን አከሳት?”
በጣም... ምግቡ እህል ቅጠል አይልም፤ ግን ካከሳኝ ምን ቸገረኝ ምናምን አለችኝ...”
“ይገርማል... አምሮባታል በይኛ!”
“ያው መቼስ... ትንሽ ሙግግ ብላለች፣ ረኀብተኛ ነው የምትመስለው፤ ግን ቦርጭዋ ጠፍቶላታል፡፡ ለነገሩ ዛሬ ዕድሜ
ለብራዚል ሂውማን ሄር የማታምር ሴት አለች?”
“ልክ ነሽ እሱስ... ሂውማን ሄር ሴቱን ሁሉ እኩል አደረገው
እኮ.... ምን ዋጋ አለው... ጸጉር ጭንቅላት አይሆን!”
“እኮ!”
የሚገርመኝ ግን ብር ኖሯቸው እንኳን ደህናውን አይገዙም እኮ...
የኔን ዕይው አሁን ከጣልያን ነው ያስመጣሁት... ይኸው ሁለት
ዓመቱ ንቅንቅ አላለም... ከገዛሽ ደህና ነገር ነው... የሚልከሰከስ ሰው አልወድም እኔ...”
“እሺ... ሌላስ ምን አዲስ አለ ታዲያ!”
“ዝናሽም በስንት ጊዜዋ ዛሬ መጥታ ነበር!”
“ተይ እንጂ! እንዴት ናት?”
“አረጀችብኝ.... ጉስቁልቁል ብላለች... ያው እሷን ታውቂያታለሽ.በሜካፕ ኀይል ነው እንጂ እኮ ዕድሜዋ ሄዷል..."
“አዎ እሱስ... ምን ሜካፕ ብትለቀለቅ አንገቷ አሳልፎ ይሰጣት የለ...
ያ.. የአውራ ዶሮ ኩልኩልት የመሰለ አንገት..."
“አንቺ ተይ በስማም... ሃሃሃ!”
“ምን ላርግ ብለሽ ነው....? ደግሞ እኮ ሰው መልክ ባይኖረው ፀባይ
አይኖረውም?
👍1
#የቤተሰባችን_ፎቶ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
አቤት የቤተሰብ ፎቶዋችን ማማሩ የጥርሳችን ንጣቱ የሣቃችን ድምቀቱ!
አባዬ እበርበት ይመስል እኔን ጥብቅ አድርጎ አቅፏል፡፡ እማዬ ይበርባት ይመስል ናሆምን ጥብቅ አድርጋ አቅፋለች፡፡ እኔና ናሆም ያለን ጥርስ ሁሉ እስኪታይ ሥቀን ከእናትና አባታችን ሥር
እንደጉልቻ ቁጭ ቁጭ ብለናል፡፡
የሚያስቀና አራት ጉልቻ፡፡ ዕዩት የእማዬን ሣቅ!
አባዬ ሚስቱን ከሚደብደብበት ቀናት በአንድ ቦክስ ሲነርታት ያወለቀው ጥርሷ የት እንደገባ እንጃ፡፡ የሚታየው እህል ነክተው የማያውቁ የሚመስሉት ነጫጭ ጥርሶቿ ብቻ ነው፡፡ ለወትሮው
ዐይኖችዋን እንደ አጥር የሚከበው ደማቅ ጥቁር ብልዝ፤ ፎቶው ላይ የለም፡፡
አባዬ ፣
“ደሞ ምን ለመሆን ነው ልጅ ከወለዱ እንዲህ ዓይነት ልብስ መልበሱ” እያለ ስለሚቆጣት፣ ብዙ ጊዜ የማትለብሰውን ፡ እጅጌው ጥሩምባ አበባን የሚመስል መዐት አበቦች የፈሰሱበት ቀሚስ ለብሳለች፡፡ ቀለሙ ዐይን የሚያደነቁር ቀይ ነው:: ከእድሜዋ ፈጥኖ
ለእርጅናና ማዲያት እጅ የሰጠው ፊትዋ በእጅ ሥራ ቆንጅቷል።
እማ ፍክት ብላለች፡፡ አበባ ነገር ሆናለች፡
አባዬን እዩትማ! ከእማዬ ጥርስ ድምቀት ጋር የሚፎካከር የወርቅ ቀለበቱ ብልጭታ፣ እጁ ላይ ትንሽ ፀሐይ ያለ አስመስሎታል። ይሄ አብረቅራቂ የጋብቻ ቀለበቱ ከማያልቀው ጭቅጨቃቸው ባንዱ ቀን፣እንዲያውም ያውልሽ! ካንቺ ጋር ያለኝ ትዳር በዚህ አብቅቷል”
ብሎ የሽንት ቤት ጉድጓድ የወረወረው ነው፡፡ እማዬ በምልጃና በልመና ጎትታ አወጣችው እንጂ!
የለበሰው ደማቅ ሮዝ ሸሚዝ፣ ከጥቁር በሮዝ መስመር መስመር
ከረቫቱ ጋር ፍጹም ተቀናጅቷል፡፡ ይሄን ከረቫት፣ ካንቺ የማያልቅ ጭቅጭቅ ለመገላገል በእዚህ ተንጠልጥዬ በሞትኩ!” እያለ እማዬን
የሚያስፈራራበትና አብዝቶ የሚለብሰው ነው፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማታ ማታ፣ ያውም በተመሳሳይ ሰዐት ፤ ትልቅ
ስልኩን ይዞ እየተንሾካሾከ ወደ ሽንትቤት ሲሮጥ ሲሮጥ ብቻ የማውቀው ሣቁ ያምራል፡፡
ናሆምዬ፣
ቀኝ እጁ ፎቶው ከመነሳቱ ሰከንዶች በፊት የተቀማውን “ሎሊፖፕ”
ሰመያዝ እንደተስተካከለ ተንከርፍፎ ቀርቷል፡፡ የአባዬን ስልክ ነካክቶ
ለእማዬ መስጠት ከጀመረ ወዲህ፣ አባዬ ሊደልለው በየቀኑ የሚገዛለትን ሎሊፖፕ
ነበር የያዘው - እማዬ ፎቶ ውስጥ አይገባም ብላ እስክትነጥቀው
ክንፍ እስከሚያካክሉት ትልልቅ ጆሮዎቹ በተዘረጋው ሰፊ ፈገግታው መሀል በቀርብ የወለቀው ጥርሱ ትቶት የሄደው ክፍተት ይታየኛል፡፡ የእማዬን ወላቃ ጥርስ በጥበቡ የደፈነው ፎቶ አንሺያችን የናሆምን መርጦ መተዉ ገረመኝ፡፡
“ይሄን ሳተላይት ጆሮ የወረስከው ከአባትህ ነው... እሱን ጠይቀው
ትለዋለች እማዬ ፤ ትምህርት ቤት በጆሮዬ ትልቅነት ሳቁብኝ ብሎ እያለቀሰ ሲነግራት፡፡ ያለችውን አምኖ አባዬን ሲጠይቅ፣ የናሆም ጆሮ የዘር ግንድ፣ አዲስ የጭቅጭቅ ማገዶ ይሆናል፡፡ እነሱ
በጩኸት ሲጨቃጨቁ የሳሎኑን ጥግ ይዞ ሲያለቅስ የማየው ልብ ሰባሪ ፊቱ እዚህ የለም፡፡
እኔ፣
አርቴፊሻል ፈገግታዬ ለፊቴ እንግዳ የሆነበት አይመስልም፡፡ ጥርሴ
እንኳን፣ ከዓመት ጀምሮ ከትምህርት ቤታችን ሦስት አጥር ዘልሎ
ካለው መርኬ ጫት ቤት እየሄድኩ፤ ከብዙ ጎረምሶች ጋር ታጅዬ ጫት ሳሻምድና ሺሻ ሳጨስ እንደምውል አያሳብቅም፡፡
አገጬን ሊነካ ምንም ያልቀረው ቢትልስ ሹራቤ ትላንት መርኬ ጓዳ፣ ጥግ ካለው ፍራሽ ላይ፣ የሰሞኑ ጓደኛዬ መሳይ በአንገቱ ላይ የሰራውን የገድል ማስታወሻ ሸፍኖታል፡፡
አቀማመጤ እንደጨዋ ልጃገረድ ሰብሰብ፣ ቆጠብ ! ከረጅም ቀሚሴ ጋር የሚሄድ ነው፡፡ አባዬ፣ ድሮ ሁሉ ነገር እነግረው በነበረ ጊዜ ያቅፈኝ እንደነበረው ስላቀፈኝ፤ ከአስተቃቀፉ ጋር የድሮን
ንጽሕናዬን ለማምጣት ባደረግኩት ከፍተኛ ጥረት ያመጣሁት
አቀማመጥ አይመስልም፡፡
ያቀፈኝ እጁን አያያዜ፣ ጥብቅ ያለና አትልቀቀኝ የሚል ይመስላል፡፡
“አባዬ መልሰኝ... አባዬ ልጠፋ ነው መልሰኝ” የሚል፡፡ ከቤታችን
ሰላም ጋር አብሮ የጠፋው ጨዋነቴን በአባቴ እቅፍ ውስጥ እፈልግ
ይመስል የምለምነው ይመስላል፡፡
...አቤት የቤተሰብ ፎቶዋችን ማማሩ! የጥርሳችን ንጣቱ! የሣቃችን ድምቀቱ!
.
የምፈልገው ቤተሰብ ፎቶዋችን ላይ ያለውን ነው፡፡
የምመኘው ቤተሰብ ፎቶዋችን ላይ ያለውን ነው፡፡
አሁን አሁን የምጸልየው፤ ፎቶው ላይ እንዳለው ያለ ቤተሰብ
እንዲሰጠኝ ብቻ ነው፡፡
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ቀን። 🙏
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
አቤት የቤተሰብ ፎቶዋችን ማማሩ የጥርሳችን ንጣቱ የሣቃችን ድምቀቱ!
አባዬ እበርበት ይመስል እኔን ጥብቅ አድርጎ አቅፏል፡፡ እማዬ ይበርባት ይመስል ናሆምን ጥብቅ አድርጋ አቅፋለች፡፡ እኔና ናሆም ያለን ጥርስ ሁሉ እስኪታይ ሥቀን ከእናትና አባታችን ሥር
እንደጉልቻ ቁጭ ቁጭ ብለናል፡፡
የሚያስቀና አራት ጉልቻ፡፡ ዕዩት የእማዬን ሣቅ!
አባዬ ሚስቱን ከሚደብደብበት ቀናት በአንድ ቦክስ ሲነርታት ያወለቀው ጥርሷ የት እንደገባ እንጃ፡፡ የሚታየው እህል ነክተው የማያውቁ የሚመስሉት ነጫጭ ጥርሶቿ ብቻ ነው፡፡ ለወትሮው
ዐይኖችዋን እንደ አጥር የሚከበው ደማቅ ጥቁር ብልዝ፤ ፎቶው ላይ የለም፡፡
አባዬ ፣
“ደሞ ምን ለመሆን ነው ልጅ ከወለዱ እንዲህ ዓይነት ልብስ መልበሱ” እያለ ስለሚቆጣት፣ ብዙ ጊዜ የማትለብሰውን ፡ እጅጌው ጥሩምባ አበባን የሚመስል መዐት አበቦች የፈሰሱበት ቀሚስ ለብሳለች፡፡ ቀለሙ ዐይን የሚያደነቁር ቀይ ነው:: ከእድሜዋ ፈጥኖ
ለእርጅናና ማዲያት እጅ የሰጠው ፊትዋ በእጅ ሥራ ቆንጅቷል።
እማ ፍክት ብላለች፡፡ አበባ ነገር ሆናለች፡
አባዬን እዩትማ! ከእማዬ ጥርስ ድምቀት ጋር የሚፎካከር የወርቅ ቀለበቱ ብልጭታ፣ እጁ ላይ ትንሽ ፀሐይ ያለ አስመስሎታል። ይሄ አብረቅራቂ የጋብቻ ቀለበቱ ከማያልቀው ጭቅጨቃቸው ባንዱ ቀን፣እንዲያውም ያውልሽ! ካንቺ ጋር ያለኝ ትዳር በዚህ አብቅቷል”
ብሎ የሽንት ቤት ጉድጓድ የወረወረው ነው፡፡ እማዬ በምልጃና በልመና ጎትታ አወጣችው እንጂ!
የለበሰው ደማቅ ሮዝ ሸሚዝ፣ ከጥቁር በሮዝ መስመር መስመር
ከረቫቱ ጋር ፍጹም ተቀናጅቷል፡፡ ይሄን ከረቫት፣ ካንቺ የማያልቅ ጭቅጭቅ ለመገላገል በእዚህ ተንጠልጥዬ በሞትኩ!” እያለ እማዬን
የሚያስፈራራበትና አብዝቶ የሚለብሰው ነው፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማታ ማታ፣ ያውም በተመሳሳይ ሰዐት ፤ ትልቅ
ስልኩን ይዞ እየተንሾካሾከ ወደ ሽንትቤት ሲሮጥ ሲሮጥ ብቻ የማውቀው ሣቁ ያምራል፡፡
ናሆምዬ፣
ቀኝ እጁ ፎቶው ከመነሳቱ ሰከንዶች በፊት የተቀማውን “ሎሊፖፕ”
ሰመያዝ እንደተስተካከለ ተንከርፍፎ ቀርቷል፡፡ የአባዬን ስልክ ነካክቶ
ለእማዬ መስጠት ከጀመረ ወዲህ፣ አባዬ ሊደልለው በየቀኑ የሚገዛለትን ሎሊፖፕ
ነበር የያዘው - እማዬ ፎቶ ውስጥ አይገባም ብላ እስክትነጥቀው
ክንፍ እስከሚያካክሉት ትልልቅ ጆሮዎቹ በተዘረጋው ሰፊ ፈገግታው መሀል በቀርብ የወለቀው ጥርሱ ትቶት የሄደው ክፍተት ይታየኛል፡፡ የእማዬን ወላቃ ጥርስ በጥበቡ የደፈነው ፎቶ አንሺያችን የናሆምን መርጦ መተዉ ገረመኝ፡፡
“ይሄን ሳተላይት ጆሮ የወረስከው ከአባትህ ነው... እሱን ጠይቀው
ትለዋለች እማዬ ፤ ትምህርት ቤት በጆሮዬ ትልቅነት ሳቁብኝ ብሎ እያለቀሰ ሲነግራት፡፡ ያለችውን አምኖ አባዬን ሲጠይቅ፣ የናሆም ጆሮ የዘር ግንድ፣ አዲስ የጭቅጭቅ ማገዶ ይሆናል፡፡ እነሱ
በጩኸት ሲጨቃጨቁ የሳሎኑን ጥግ ይዞ ሲያለቅስ የማየው ልብ ሰባሪ ፊቱ እዚህ የለም፡፡
እኔ፣
አርቴፊሻል ፈገግታዬ ለፊቴ እንግዳ የሆነበት አይመስልም፡፡ ጥርሴ
እንኳን፣ ከዓመት ጀምሮ ከትምህርት ቤታችን ሦስት አጥር ዘልሎ
ካለው መርኬ ጫት ቤት እየሄድኩ፤ ከብዙ ጎረምሶች ጋር ታጅዬ ጫት ሳሻምድና ሺሻ ሳጨስ እንደምውል አያሳብቅም፡፡
አገጬን ሊነካ ምንም ያልቀረው ቢትልስ ሹራቤ ትላንት መርኬ ጓዳ፣ ጥግ ካለው ፍራሽ ላይ፣ የሰሞኑ ጓደኛዬ መሳይ በአንገቱ ላይ የሰራውን የገድል ማስታወሻ ሸፍኖታል፡፡
አቀማመጤ እንደጨዋ ልጃገረድ ሰብሰብ፣ ቆጠብ ! ከረጅም ቀሚሴ ጋር የሚሄድ ነው፡፡ አባዬ፣ ድሮ ሁሉ ነገር እነግረው በነበረ ጊዜ ያቅፈኝ እንደነበረው ስላቀፈኝ፤ ከአስተቃቀፉ ጋር የድሮን
ንጽሕናዬን ለማምጣት ባደረግኩት ከፍተኛ ጥረት ያመጣሁት
አቀማመጥ አይመስልም፡፡
ያቀፈኝ እጁን አያያዜ፣ ጥብቅ ያለና አትልቀቀኝ የሚል ይመስላል፡፡
“አባዬ መልሰኝ... አባዬ ልጠፋ ነው መልሰኝ” የሚል፡፡ ከቤታችን
ሰላም ጋር አብሮ የጠፋው ጨዋነቴን በአባቴ እቅፍ ውስጥ እፈልግ
ይመስል የምለምነው ይመስላል፡፡
...አቤት የቤተሰብ ፎቶዋችን ማማሩ! የጥርሳችን ንጣቱ! የሣቃችን ድምቀቱ!
.
የምፈልገው ቤተሰብ ፎቶዋችን ላይ ያለውን ነው፡፡
የምመኘው ቤተሰብ ፎቶዋችን ላይ ያለውን ነው፡፡
አሁን አሁን የምጸልየው፤ ፎቶው ላይ እንዳለው ያለ ቤተሰብ
እንዲሰጠኝ ብቻ ነው፡፡
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ቀን። 🙏
🥰1
#ሴት_እና_የነገር_ቱባ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
ቁርሳችንን ለኮፍ ለኮፍ አድርገን ለመውጣት እየተጣደፍን ነው ያለ ቅጥ ረፍዶብናል፡፡
“ብርድ ነው ፀሐይ..? እስቲ ውጣና ዕይልኝ!” አልኩት፡፡ “ሹራብ ልልበስ ሸሚዝ?” በሚል ከተመሣቀለው ቁምሣጥን ልብስ ለመምረጥ
እየተጣደፍኩ፡፡
በቁሙ፧ በግማሽ ልብ ቴሌቪዥን እያየ የሚጠብቀኝ ባሌ፣ መልስ አልሰጠኝም፡
“በረከት!” አልኩት እየጮኽኩ፡፡
“ወ.. ይ...” አለና ከሲ ኤን ኤንዋ ዜና አንባቢ ዐይነን አንስቶ እኔ
ላይ አሳረፈ፡፡
“አትሰማኝም እንዴ?”
“አልሰማሁም...ምን አልሽኝ....?”
“ወይ ጉዴ...! ብርድ ነው ፀሐይ... ውጣና ዕይልኝ... ልብስ እንድመርጥ...”
“ወይ ቆንጂት!... ገና አልለበስሽም እንዴ... ቶሎ ቶሎ በይ እንጂ አለኝ እንደ ነገሩ እያየኝ፡፡
“ወየው.... ከላይ ብቻ ነው የቀረኝ... ዕይልኝ ይልቅ....”
ተበሳጭቻለሁ፡፡
በግብር ይውጣ አካሄድ ወጣና መለስ ብሎ፣ “ደመና ነው... ሹራብ
ያዢ!” አለኝ፡፡
ይሄን ጊዜ ! ከሱሪዬ ጋር የሚሄድ ሹራብ ፍለጋ ቁምሳጥኔን ማተራመስ ጀመርኩ፡፡
“እረ ቆንጂት በፈጠረሽ እንውጣ...! ይቺ ዐሥር ደቂቃ ካለፈች
ታውቂያለሽ የታክሲ ሰልፉ መከራ ነው” አለኝ ቴሌቪዥኑን እያጠፋ፡፡
ሹራብ ፍለጋዬን አቆምኩና ዞር ብዬ ዐየሁት፡፡
ደግሞ ልንጨቃጨቅ ነው፡፡
አሁን አሁን ከምንም ነገር በላይ አብዝተን የምናደርገው ነገር፣
መጨቃጨቅ ነው፡፡
ስለ አለባበሴ እንጨቀጨቃሰን፡፡
ስለ ከጓደኞቹ ጋር ማምሸቱ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለ ገንዘብ አያያዜ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለ ልጆቻችን ጠባይ እንጨቃጨቃለን፡፡
ፐ
ስለ እናቱ እኔን አለመውደድ ጉዳይ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለኔ ታናሽ ወንድም መበላሸት እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለምንም ነገር እንጨቃጨቃለን፡፡
ሹራብ ነው የቀረኝ... ታገሰኝ..." ኣልኩት፤ “ዋ ሌላ ነገር ተናገረኝና
ጉድ ይፈላል” በሚል ዓይነት ድምፅ፡፡
ግን ሌላ ነገር ተናገረኝ፡፡
“ስንት ሰዐት እታገስሻለሁ....? ልብስ ለመልበስ አንድ ሰዓት ሊያውም እንዲህ እረፍዶ?”
አሁን በደንብ ልንጨቃጨቅ ነው፡፡
በኔ በረፈደ ሰዐት ላይ ልብስ ለመልበስ መቆየት መነሻነት የተጀመረው ጭቅጭቅ መዳረሻው የት እንደሆነ አላውቅም..
ጭቅጭቃችን የራሱ ቦይ አለው፡፡ ራሱ እየቀደደ የሚፈስበት ቦይ::
ከቀበና ወንዝ ተነስቶ ሜዲትራኒያን የሚገባበት የራሱ ረጅ....ም....ቦይ፡፡
“አንድ ሰዐት አልፈጀብኝም! አታጋንን፤ ማጋነን ስትወድ "አልኩት፣ ሰማያዊውን ሹራቤን አውጥቼ እየለበስኩ፡፡
“እኔው ነኝ አጋናኙ...?” አለኝ ደክሞት ውሎ እንደመጣ ሰው ሶፋው ላይ ተመልሶ እየተቀመጠ፡፡
“ምን ማለት ነው እኔው ነኝ አጋናኙ..? አንቺ ታጋንኛለሽ ለማለት ነው...?” አልኩት ገንፈል ብዬ፡፡
ዝም አለ፡፡
በአሸናፊነት መንፈስ ሹራቤን ለብሼ የቁምሳጥኑ መስታወት ጋር
ሄጄ ከሱሪዬ ጋር ያለውን ቅንጅት አየሁ፡፡
አያምርም፡፡
ሮዙን ሹራብ ባደርግ ይሻለኛል፡፡
ሰማያዊውን ሹራብ አውልቄ አልጋ ላይ ጣልኩና ሮዙን ሹራብ መፈለግ ስጀምር የሆነ ነገር ሲል ሰማሁት፡፡
“ምን አልክ?”
“ምንም አላልኩም ቆንጂት ”
“ለምን ምንም አላልኩም ትላለህ ...? የሆነ ነገር ስትል
አልሰማሁህም አሁን...?” ወደ ሳሎን መጥቼ አፈጠጥኩበት፡፡
“ምንም አላልኩም.... ....... በይ ይልቅ ፤ ትናንት ብፈልገው አጣሁት... የእዚህ ሪሞት አንዱ ባትሪ የት ገባ...? ወድቆ ጠፍቷል” አለኝ፣ መክደኛ የሌለውን የቴሌቪዥናችንን ሪሞት ኮንትሮል
አገላብጦ እያየ፡፡
“ምን እኔን ትጠይቀኛለህ... አንተ ነህ ተሰክተህበት የምትውልበት
ቲቪውን፤ ...ራስህ አትፈልገውም...?” ሹራቤን ፍለጋ እየተመለስኩ መለስኩ፡፡
“እኔ የት እንዳለ ባውቅ አንቺን ምን አስጠየቀኝ?”
“እንጃ! ምናልባት ለሁሉ ነገር ጥፋተኛ የምታደርገው እኔን ስለሆነ”
“ለሁሉ ነገር?”
አዎ! ....ቲቪ ተበላሸ... ቆንጂት ምን አረግሽው...? የቤቱ ግድግዳ
ለቀቀ ፤ ቆንጂት ምን ስትሰሪ እንዲህ ሆነ..? የልጆቹ ፀባይ ተበላሽ
ቆንጂት አንቺ እኮ ነሽ እያቀበጥሻቸው...? አሁን ደግሞ ሚጢጢ ባትሪ ጠፋ እኔኑ ጥፋተኛ...”
ሳላሰበው ሁለመናዬ ሲግል እየተሰማኝ ተናገርኩ፡፡
“በ...ይ ተይው እገዛለሁ... ሆሆ!” ብሎ ሪሞት ኮንትሮሉን ጠረጴዛው ላይ ሲወረውር ተሰማኝ፡፡
ግዛ አንተ ምን አለብህ...! ሽሮ በርበሬ ብዬ የምሣቀቀው እኔ...
አንተማ መዥረጥ አድርገህ ያሻህን ትገዛለህ..." አልኩ።ግለቴ ሳይበርድ፤ ሮዙን ሹራብ እያደረግኩ፡፡
“ታዲያ ከጠፋ ምን አድርግ ትይኛለሽ...? ደሞ ለባትሪ...”
“ደሞ ለዚች እያልክ ነው ገንዘብ የምታባክነው፡፡ ገንዘብ በትንሹ
ካልተቆጠበ ብዙ ይሆናል...?”
“ደሞ አሁን ገንዘብ አባካኝ ሆንኩ..!.”
ድምፁ ይንቀጠቀጣል፡፡ ድምፁ ከተንቀጠቀጠ ተናዷል ማለት ነው፡፡
“አይ ቆጠብክልኝ እንጂ! ቆጠብክልኝ የኔ ጌታ! ይሄ በየማታው የምትጋተው ድራፍት እንኳን ቢደማመር የልጆቹን አስጠኚ የወር ደሞዝ ቀጥ አድርጎ አይችልም....?” አልኩት ድምጼን ከፍ አድርጌ ፤ ወገቤን በነገረኛ ሴት ቄንጥ ይዤ ወደ ሳሎን እየተመለስኩ፡፡
ፊቱ ቀልቷል፡፡
“በየማታው...? እኔ ነኝ በየማታው ድራፍት የምጋተው....? ከቅዳሜ
ውጪ ...ሊያውም ከሁለት ድራፍት በላይ ስጠጣ አይተሸኛል....?
ደሞ ለነገሩስ ለልጆቹ አስጠኚ ይቀጠር ስልሽ... ተወው ፤ ማቲ እየመጣ እንደፈለጋቸው ያስጠናቸዋል' ብለሽ አይደለም የተውነው እንዴ!”
እሱማ ነበር! ....የሚሆን መስሎኝ፡፡ ገንዘብም እንዲቆጠብ ብዬ .. ግን
ምስኪን ወንድሜን በሳምንት ሦስቱ ለሚመጣው እየገላመጥክ
ከቤቴ አራቅከው... አሁን እስቲ ምን አደረገህ ...? ልጆችህን በነጻ ባስጠናልህ...”
አሁን ቅድም እንደ ዋዛ የጣልኩትን የአንገት ልብሴን እየፈለግኩ
ነው፡፡
“ተይ ቆንጂት ግፍ አትናገሪ፡፡ እኔ ነኝ ወንድምሽን ከዚህ ቤት
ያራቅኩት? ራሱ አይደለም፣ ልጆቹ ማቲ ሲጋራ ሲያጨስ እያዩ እንዳይሰላሹ ምከሪው' ስልሽ ሰምቶ እዚህ ቤት አልመጣም ያለው...? እሱ ዱርዬ በሆነው ለልጆቼ ማሰቤ ነው እኔን
የሚያስወቅሰኝ!”
አሁን በማቲ መጣብኝ፡፡ የማቲ ነገር እንደማይሆንልኝ እያወቀ በጠዋቱ በማቲ መጣብኝ፡፡
“በረከት! ማቲ ዱርዬ አልሆነም... ወጣት ነው….. ሊሳሳት ይችላል...
እንደ ታላቅ ወንድም ልትመክረው ሲገባ እንደ እብድ ውሻ ከገዛ እህቱ ቤት አባረርከው... ይሄ ልክ ነው?” አልኩት የአንገት ልብሴን ፍለጋ ትቼ እያየሁት፡፡
“እህ... ተይው... አንቺ ልጄ..... ታክሲው... ይልቅ በናትሽ ለብሰሽ
ጨርሺ አሁን... እንሂድ፡፡” አሁንም ያንን ሪሞት ኮንትሮል እያገላበጠ ያያል፡፡
እንዲህ በነገር እየለበለብከኝ ምኑን ከምኑ አድርጌ ልልበስ.
ስካርፌ ጠፋብኝ” አልኩት ቀዝቀዝ ብዬ፡፡
“ራስሽ በጀመርሽው ነገር መልሰሽ እኔን... ይልቅ አሁን ጨረስሽ..
እንውጣ?” አለኝ ቦርሳውን እንስቶ እያነገተ፤
“ምነው ስታየኝ ያልጨረስኩ እመስላለሁ....?”
ያለ እቅዱ ነገረኛ ድምፄ ተመለሰ፡፡
“ደሞ ይሄ ምን ማለት ነው?”
“የለበስኩ አልመሰልኩም?... ለነገሩ ስታየኝ አይደል የምታውቀው በጠዋት
ቲቪ ላይ እያፈጠጠክ... ሦስተኛ ጡት አብቅዬ ባድርም እስከ ሁለት ወር የሚታይህ አይመስለኝም”
ሣቀ፡፡
እኔ ግን አልሣቅኩም፡፡ እየተጨቃጨቅን ሲስቅ ያናድደኛል።
“ሶስተኛ ጡት...? ምን?” አለኝ አሁንም እየሣቀ፡፡
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
ቁርሳችንን ለኮፍ ለኮፍ አድርገን ለመውጣት እየተጣደፍን ነው ያለ ቅጥ ረፍዶብናል፡፡
“ብርድ ነው ፀሐይ..? እስቲ ውጣና ዕይልኝ!” አልኩት፡፡ “ሹራብ ልልበስ ሸሚዝ?” በሚል ከተመሣቀለው ቁምሣጥን ልብስ ለመምረጥ
እየተጣደፍኩ፡፡
በቁሙ፧ በግማሽ ልብ ቴሌቪዥን እያየ የሚጠብቀኝ ባሌ፣ መልስ አልሰጠኝም፡
“በረከት!” አልኩት እየጮኽኩ፡፡
“ወ.. ይ...” አለና ከሲ ኤን ኤንዋ ዜና አንባቢ ዐይነን አንስቶ እኔ
ላይ አሳረፈ፡፡
“አትሰማኝም እንዴ?”
“አልሰማሁም...ምን አልሽኝ....?”
“ወይ ጉዴ...! ብርድ ነው ፀሐይ... ውጣና ዕይልኝ... ልብስ እንድመርጥ...”
“ወይ ቆንጂት!... ገና አልለበስሽም እንዴ... ቶሎ ቶሎ በይ እንጂ አለኝ እንደ ነገሩ እያየኝ፡፡
“ወየው.... ከላይ ብቻ ነው የቀረኝ... ዕይልኝ ይልቅ....”
ተበሳጭቻለሁ፡፡
በግብር ይውጣ አካሄድ ወጣና መለስ ብሎ፣ “ደመና ነው... ሹራብ
ያዢ!” አለኝ፡፡
ይሄን ጊዜ ! ከሱሪዬ ጋር የሚሄድ ሹራብ ፍለጋ ቁምሳጥኔን ማተራመስ ጀመርኩ፡፡
“እረ ቆንጂት በፈጠረሽ እንውጣ...! ይቺ ዐሥር ደቂቃ ካለፈች
ታውቂያለሽ የታክሲ ሰልፉ መከራ ነው” አለኝ ቴሌቪዥኑን እያጠፋ፡፡
ሹራብ ፍለጋዬን አቆምኩና ዞር ብዬ ዐየሁት፡፡
ደግሞ ልንጨቃጨቅ ነው፡፡
አሁን አሁን ከምንም ነገር በላይ አብዝተን የምናደርገው ነገር፣
መጨቃጨቅ ነው፡፡
ስለ አለባበሴ እንጨቀጨቃሰን፡፡
ስለ ከጓደኞቹ ጋር ማምሸቱ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለ ገንዘብ አያያዜ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለ ልጆቻችን ጠባይ እንጨቃጨቃለን፡፡
ፐ
ስለ እናቱ እኔን አለመውደድ ጉዳይ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለኔ ታናሽ ወንድም መበላሸት እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለምንም ነገር እንጨቃጨቃለን፡፡
ሹራብ ነው የቀረኝ... ታገሰኝ..." ኣልኩት፤ “ዋ ሌላ ነገር ተናገረኝና
ጉድ ይፈላል” በሚል ዓይነት ድምፅ፡፡
ግን ሌላ ነገር ተናገረኝ፡፡
“ስንት ሰዐት እታገስሻለሁ....? ልብስ ለመልበስ አንድ ሰዓት ሊያውም እንዲህ እረፍዶ?”
አሁን በደንብ ልንጨቃጨቅ ነው፡፡
በኔ በረፈደ ሰዐት ላይ ልብስ ለመልበስ መቆየት መነሻነት የተጀመረው ጭቅጭቅ መዳረሻው የት እንደሆነ አላውቅም..
ጭቅጭቃችን የራሱ ቦይ አለው፡፡ ራሱ እየቀደደ የሚፈስበት ቦይ::
ከቀበና ወንዝ ተነስቶ ሜዲትራኒያን የሚገባበት የራሱ ረጅ....ም....ቦይ፡፡
“አንድ ሰዐት አልፈጀብኝም! አታጋንን፤ ማጋነን ስትወድ "አልኩት፣ ሰማያዊውን ሹራቤን አውጥቼ እየለበስኩ፡፡
“እኔው ነኝ አጋናኙ...?” አለኝ ደክሞት ውሎ እንደመጣ ሰው ሶፋው ላይ ተመልሶ እየተቀመጠ፡፡
“ምን ማለት ነው እኔው ነኝ አጋናኙ..? አንቺ ታጋንኛለሽ ለማለት ነው...?” አልኩት ገንፈል ብዬ፡፡
ዝም አለ፡፡
በአሸናፊነት መንፈስ ሹራቤን ለብሼ የቁምሳጥኑ መስታወት ጋር
ሄጄ ከሱሪዬ ጋር ያለውን ቅንጅት አየሁ፡፡
አያምርም፡፡
ሮዙን ሹራብ ባደርግ ይሻለኛል፡፡
ሰማያዊውን ሹራብ አውልቄ አልጋ ላይ ጣልኩና ሮዙን ሹራብ መፈለግ ስጀምር የሆነ ነገር ሲል ሰማሁት፡፡
“ምን አልክ?”
“ምንም አላልኩም ቆንጂት ”
“ለምን ምንም አላልኩም ትላለህ ...? የሆነ ነገር ስትል
አልሰማሁህም አሁን...?” ወደ ሳሎን መጥቼ አፈጠጥኩበት፡፡
“ምንም አላልኩም.... ....... በይ ይልቅ ፤ ትናንት ብፈልገው አጣሁት... የእዚህ ሪሞት አንዱ ባትሪ የት ገባ...? ወድቆ ጠፍቷል” አለኝ፣ መክደኛ የሌለውን የቴሌቪዥናችንን ሪሞት ኮንትሮል
አገላብጦ እያየ፡፡
“ምን እኔን ትጠይቀኛለህ... አንተ ነህ ተሰክተህበት የምትውልበት
ቲቪውን፤ ...ራስህ አትፈልገውም...?” ሹራቤን ፍለጋ እየተመለስኩ መለስኩ፡፡
“እኔ የት እንዳለ ባውቅ አንቺን ምን አስጠየቀኝ?”
“እንጃ! ምናልባት ለሁሉ ነገር ጥፋተኛ የምታደርገው እኔን ስለሆነ”
“ለሁሉ ነገር?”
አዎ! ....ቲቪ ተበላሸ... ቆንጂት ምን አረግሽው...? የቤቱ ግድግዳ
ለቀቀ ፤ ቆንጂት ምን ስትሰሪ እንዲህ ሆነ..? የልጆቹ ፀባይ ተበላሽ
ቆንጂት አንቺ እኮ ነሽ እያቀበጥሻቸው...? አሁን ደግሞ ሚጢጢ ባትሪ ጠፋ እኔኑ ጥፋተኛ...”
ሳላሰበው ሁለመናዬ ሲግል እየተሰማኝ ተናገርኩ፡፡
“በ...ይ ተይው እገዛለሁ... ሆሆ!” ብሎ ሪሞት ኮንትሮሉን ጠረጴዛው ላይ ሲወረውር ተሰማኝ፡፡
ግዛ አንተ ምን አለብህ...! ሽሮ በርበሬ ብዬ የምሣቀቀው እኔ...
አንተማ መዥረጥ አድርገህ ያሻህን ትገዛለህ..." አልኩ።ግለቴ ሳይበርድ፤ ሮዙን ሹራብ እያደረግኩ፡፡
“ታዲያ ከጠፋ ምን አድርግ ትይኛለሽ...? ደሞ ለባትሪ...”
“ደሞ ለዚች እያልክ ነው ገንዘብ የምታባክነው፡፡ ገንዘብ በትንሹ
ካልተቆጠበ ብዙ ይሆናል...?”
“ደሞ አሁን ገንዘብ አባካኝ ሆንኩ..!.”
ድምፁ ይንቀጠቀጣል፡፡ ድምፁ ከተንቀጠቀጠ ተናዷል ማለት ነው፡፡
“አይ ቆጠብክልኝ እንጂ! ቆጠብክልኝ የኔ ጌታ! ይሄ በየማታው የምትጋተው ድራፍት እንኳን ቢደማመር የልጆቹን አስጠኚ የወር ደሞዝ ቀጥ አድርጎ አይችልም....?” አልኩት ድምጼን ከፍ አድርጌ ፤ ወገቤን በነገረኛ ሴት ቄንጥ ይዤ ወደ ሳሎን እየተመለስኩ፡፡
ፊቱ ቀልቷል፡፡
“በየማታው...? እኔ ነኝ በየማታው ድራፍት የምጋተው....? ከቅዳሜ
ውጪ ...ሊያውም ከሁለት ድራፍት በላይ ስጠጣ አይተሸኛል....?
ደሞ ለነገሩስ ለልጆቹ አስጠኚ ይቀጠር ስልሽ... ተወው ፤ ማቲ እየመጣ እንደፈለጋቸው ያስጠናቸዋል' ብለሽ አይደለም የተውነው እንዴ!”
እሱማ ነበር! ....የሚሆን መስሎኝ፡፡ ገንዘብም እንዲቆጠብ ብዬ .. ግን
ምስኪን ወንድሜን በሳምንት ሦስቱ ለሚመጣው እየገላመጥክ
ከቤቴ አራቅከው... አሁን እስቲ ምን አደረገህ ...? ልጆችህን በነጻ ባስጠናልህ...”
አሁን ቅድም እንደ ዋዛ የጣልኩትን የአንገት ልብሴን እየፈለግኩ
ነው፡፡
“ተይ ቆንጂት ግፍ አትናገሪ፡፡ እኔ ነኝ ወንድምሽን ከዚህ ቤት
ያራቅኩት? ራሱ አይደለም፣ ልጆቹ ማቲ ሲጋራ ሲያጨስ እያዩ እንዳይሰላሹ ምከሪው' ስልሽ ሰምቶ እዚህ ቤት አልመጣም ያለው...? እሱ ዱርዬ በሆነው ለልጆቼ ማሰቤ ነው እኔን
የሚያስወቅሰኝ!”
አሁን በማቲ መጣብኝ፡፡ የማቲ ነገር እንደማይሆንልኝ እያወቀ በጠዋቱ በማቲ መጣብኝ፡፡
“በረከት! ማቲ ዱርዬ አልሆነም... ወጣት ነው….. ሊሳሳት ይችላል...
እንደ ታላቅ ወንድም ልትመክረው ሲገባ እንደ እብድ ውሻ ከገዛ እህቱ ቤት አባረርከው... ይሄ ልክ ነው?” አልኩት የአንገት ልብሴን ፍለጋ ትቼ እያየሁት፡፡
“እህ... ተይው... አንቺ ልጄ..... ታክሲው... ይልቅ በናትሽ ለብሰሽ
ጨርሺ አሁን... እንሂድ፡፡” አሁንም ያንን ሪሞት ኮንትሮል እያገላበጠ ያያል፡፡
እንዲህ በነገር እየለበለብከኝ ምኑን ከምኑ አድርጌ ልልበስ.
ስካርፌ ጠፋብኝ” አልኩት ቀዝቀዝ ብዬ፡፡
“ራስሽ በጀመርሽው ነገር መልሰሽ እኔን... ይልቅ አሁን ጨረስሽ..
እንውጣ?” አለኝ ቦርሳውን እንስቶ እያነገተ፤
“ምነው ስታየኝ ያልጨረስኩ እመስላለሁ....?”
ያለ እቅዱ ነገረኛ ድምፄ ተመለሰ፡፡
“ደሞ ይሄ ምን ማለት ነው?”
“የለበስኩ አልመሰልኩም?... ለነገሩ ስታየኝ አይደል የምታውቀው በጠዋት
ቲቪ ላይ እያፈጠጠክ... ሦስተኛ ጡት አብቅዬ ባድርም እስከ ሁለት ወር የሚታይህ አይመስለኝም”
ሣቀ፡፡
እኔ ግን አልሣቅኩም፡፡ እየተጨቃጨቅን ሲስቅ ያናድደኛል።
“ሶስተኛ ጡት...? ምን?” አለኝ አሁንም እየሣቀ፡፡
👍1
#ገንዘብ_መሆን_የተሳነው_ዕውቀት
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
ከታናሽ ወንድሜ ጋር በዲግሪ ፕሮግራም ተምሮ የተመረቀውን ዳንኤል፣ የኮብልስቶን ሥራን ሲያስተባብር አገኘሁት፡፡
ሻይ ይዘን፤ ስለ የተማሩ ኮብልስቶን ጠራቢና ደርዳሪዎች፤ ተብሎ...
ተብሎ... የተተወውን ክርክር እንደ አዲስ ቀሰቀስነው፡፡
ዳንኤል ፣ “ሥራ አጥተን ቤት ቁጭ ከምንል ገንዘብ እስካገኘን
ብንሠራ ምናለ?” ብሎ ነገሩን ሥራ ከመናቅና ካለመናቅ ጋር አጣብቆት ብዙ ሞገተኝ፡፡
“ሥራ ገንዘብ ማግኛ ነው ፤ ይሄ ደግሞ ገንዘብ ይከፍላል፤ ኀጢአቱ ምንድነው?” ብሎ ተከራከረኝ፡፡
ዳንኤል ልክ ነው፡፡ ድህነት መለዮ ልብሳችን በሆነበት ሀገር ገንዘብ
የሚያስገኝ ነገር ሁሉ እንደ ስኬት እንደሚቆጠር ግልጽ ነው፡፡
ምክንያቱም ገንዘብ እህል ይሆናል፡፡
ምክንያቱም ገንዘብ ቤት ኪራይ ይከፍላል፡፡
ምክንያቱም ገንዘብ የታክሲ ይሆናል፡፡
ያን ያህል ቀላል ነው፤ ይገባኛል፡፡ የእኔ ችግር ከአጠቃላይ ክስረቱ ጋር ነው፡፡ የእኔ ችግር እነዚህ ልጆች ለዓመታት "ሲማሩና ሲመራመሩ" ከርመው፤ ያልተማረና ያልተመራመረ ሰው
በሚችለው ሥራ ላይ መሰማራታቸው... የእነዚያን ሰዎች የሥራ ዕድል ከማጣበባቸው ነው፡፡ ለእኔ ይሄ ክስረት ነው።
ሰለዚህ የመንግሥት ሚዲያዎቻችን፣ እነዚህ ልጆች የምርቃት ሱፋቸውን አውልቀው በሥራ ቱታ ድንጋይ ሲፈልጡ መዋላቸውን እንደ ታላቅ ስኬት ሲያቀርቡት አይገባኝም።
“በሥራ ክቡር ነው!” መልካም አባባል፤ ልሽቀታችንን ሲደብቁት ደስ አይለኝም፡፡ ችግሬ ከልጆቹ መሥራት አይደለም፡፡ ከነገሩ አቀራረብና አረዳድ ነው፡፡
ሥራቸው ልጆቹን ሊያሳፍር ባይገባም፤ እንደ ሀገር ግን ሊያኮራን የሚገባ ነገር አይደለም፡፡ ምክንያቱም ልጆቹ ዲግሪ ለማግኘት ብዙ ከፍለዋል፡፡ ሀገሪቷም ካላት ትንሽ ሀብት ብዙ ከፍላለች፡፡
...እና በረጅሙ ስናስበው፣ ዛሬን በልተው ቢያድሩም የትምህርት ሥርዓታችን ክስረት ባንዲራዎች ናቸው፡፡
ዛሬ ትምህርት ላይ ላሉ፣ ማበረታቻ ሳይሆኑ ማስጠንቀቂያ ናቸው፡፡
ያልተማረ ሰው ሊሠራ የሚችለውን ሥራ ተምረው ስለሚሠሩ፣በልተው ቢያድሩም ለሀገር ውድቀቶች ናቸው፡፡ ነገር ግን፣ ይህ የእነሱ ጥፋት አይደለም፡፡ መብላት አለባቸው፡፡ መኖር አለባቸው፡፡
ስለዚህ ወደ ገንዘብ የሚለወጥ ዕውቀት ልንሰጣቸው ስላልቻልን ወደ ገንዘብ የሚለወጥ ጉልበታቸውን ተጠቀሙ:: በዚህ ደግሞ ልናፍር እንጂ ልንኩራራ የሚገባ አይመስለኝም፡፡
💫አለቀ💫
ምን ትላላችሁ የቻናሌ ተከታታዎች ይሄ ጉዳይ የሚመለከታችሁም ልትኖሩ ትችላላችሁ እስቲ ሃሳባቹህን አድርሱን
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ቀን። 🙏
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
ከታናሽ ወንድሜ ጋር በዲግሪ ፕሮግራም ተምሮ የተመረቀውን ዳንኤል፣ የኮብልስቶን ሥራን ሲያስተባብር አገኘሁት፡፡
ሻይ ይዘን፤ ስለ የተማሩ ኮብልስቶን ጠራቢና ደርዳሪዎች፤ ተብሎ...
ተብሎ... የተተወውን ክርክር እንደ አዲስ ቀሰቀስነው፡፡
ዳንኤል ፣ “ሥራ አጥተን ቤት ቁጭ ከምንል ገንዘብ እስካገኘን
ብንሠራ ምናለ?” ብሎ ነገሩን ሥራ ከመናቅና ካለመናቅ ጋር አጣብቆት ብዙ ሞገተኝ፡፡
“ሥራ ገንዘብ ማግኛ ነው ፤ ይሄ ደግሞ ገንዘብ ይከፍላል፤ ኀጢአቱ ምንድነው?” ብሎ ተከራከረኝ፡፡
ዳንኤል ልክ ነው፡፡ ድህነት መለዮ ልብሳችን በሆነበት ሀገር ገንዘብ
የሚያስገኝ ነገር ሁሉ እንደ ስኬት እንደሚቆጠር ግልጽ ነው፡፡
ምክንያቱም ገንዘብ እህል ይሆናል፡፡
ምክንያቱም ገንዘብ ቤት ኪራይ ይከፍላል፡፡
ምክንያቱም ገንዘብ የታክሲ ይሆናል፡፡
ያን ያህል ቀላል ነው፤ ይገባኛል፡፡ የእኔ ችግር ከአጠቃላይ ክስረቱ ጋር ነው፡፡ የእኔ ችግር እነዚህ ልጆች ለዓመታት "ሲማሩና ሲመራመሩ" ከርመው፤ ያልተማረና ያልተመራመረ ሰው
በሚችለው ሥራ ላይ መሰማራታቸው... የእነዚያን ሰዎች የሥራ ዕድል ከማጣበባቸው ነው፡፡ ለእኔ ይሄ ክስረት ነው።
ሰለዚህ የመንግሥት ሚዲያዎቻችን፣ እነዚህ ልጆች የምርቃት ሱፋቸውን አውልቀው በሥራ ቱታ ድንጋይ ሲፈልጡ መዋላቸውን እንደ ታላቅ ስኬት ሲያቀርቡት አይገባኝም።
“በሥራ ክቡር ነው!” መልካም አባባል፤ ልሽቀታችንን ሲደብቁት ደስ አይለኝም፡፡ ችግሬ ከልጆቹ መሥራት አይደለም፡፡ ከነገሩ አቀራረብና አረዳድ ነው፡፡
ሥራቸው ልጆቹን ሊያሳፍር ባይገባም፤ እንደ ሀገር ግን ሊያኮራን የሚገባ ነገር አይደለም፡፡ ምክንያቱም ልጆቹ ዲግሪ ለማግኘት ብዙ ከፍለዋል፡፡ ሀገሪቷም ካላት ትንሽ ሀብት ብዙ ከፍላለች፡፡
...እና በረጅሙ ስናስበው፣ ዛሬን በልተው ቢያድሩም የትምህርት ሥርዓታችን ክስረት ባንዲራዎች ናቸው፡፡
ዛሬ ትምህርት ላይ ላሉ፣ ማበረታቻ ሳይሆኑ ማስጠንቀቂያ ናቸው፡፡
ያልተማረ ሰው ሊሠራ የሚችለውን ሥራ ተምረው ስለሚሠሩ፣በልተው ቢያድሩም ለሀገር ውድቀቶች ናቸው፡፡ ነገር ግን፣ ይህ የእነሱ ጥፋት አይደለም፡፡ መብላት አለባቸው፡፡ መኖር አለባቸው፡፡
ስለዚህ ወደ ገንዘብ የሚለወጥ ዕውቀት ልንሰጣቸው ስላልቻልን ወደ ገንዘብ የሚለወጥ ጉልበታቸውን ተጠቀሙ:: በዚህ ደግሞ ልናፍር እንጂ ልንኩራራ የሚገባ አይመስለኝም፡፡
💫አለቀ💫
ምን ትላላችሁ የቻናሌ ተከታታዎች ይሄ ጉዳይ የሚመለከታችሁም ልትኖሩ ትችላላችሁ እስቲ ሃሳባቹህን አድርሱን
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ቀን። 🙏
❤1
ጀርመናዊው ጉተ መሰለኝ፣ “ለልጆቻችን መስጠት ያለብን መሠረታዊ ነገሮች ሁለት ናቸው ፤ ሥርና ክንፎች” ያለው:: ሥሩ ማንነታቸውን፤ ክንፎቹ ደግሞ ትልቅ የመሆን ህልማቸውን የሚወክሉ ይመስለኛል።
የዛራ እና ቻንድራ ፊት የታተመበት ልጆቻችን የሚማሩበትን ደብተር ሳይ ነው ይህ ትዝ ያለኝ፡፡ የሚማሩበት ደብተራቸው
እንኳን፣ በህንድ እና ቱርክ የፍቅር ታሪክ እንዲነሆልሉ እንጂ ፤
በባዕድ የእግር ኳስ ተጫዋቾች ስምና ገድል እንዲፈዙ እንጂ፤ “እኔ ማነኝ?” ብለው እንዲጠይቁ የማያደርጋቸውን ልጆች ለማሳደግ እየባዘንን መሆኑን ሳስብ ነው ጉተ ትዝ ያለኝ፡፡
"ምን መሆን እፈልጋለሁ? ምንስ መሆን እችላለሁ?" ብለው መጠየቅ እና ማሰብ የማይችሉ ተማሪዎችን በመፍጠር ላይ ታች እያልን ነው፡፡
አዎ.. . እንዲህ እንደዋዛ ....
በየቤቱ እና በየትምህርት ቤቱ፣ ሥር የሌላቸውን ዛፎች እየተከልን ነው። መብረር የማይችሉ ወፎችን እያረባን ነው።
#በሕይወት_እምሻው
💫ጨረስኩ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
የዛራ እና ቻንድራ ፊት የታተመበት ልጆቻችን የሚማሩበትን ደብተር ሳይ ነው ይህ ትዝ ያለኝ፡፡ የሚማሩበት ደብተራቸው
እንኳን፣ በህንድ እና ቱርክ የፍቅር ታሪክ እንዲነሆልሉ እንጂ ፤
በባዕድ የእግር ኳስ ተጫዋቾች ስምና ገድል እንዲፈዙ እንጂ፤ “እኔ ማነኝ?” ብለው እንዲጠይቁ የማያደርጋቸውን ልጆች ለማሳደግ እየባዘንን መሆኑን ሳስብ ነው ጉተ ትዝ ያለኝ፡፡
"ምን መሆን እፈልጋለሁ? ምንስ መሆን እችላለሁ?" ብለው መጠየቅ እና ማሰብ የማይችሉ ተማሪዎችን በመፍጠር ላይ ታች እያልን ነው፡፡
አዎ.. . እንዲህ እንደዋዛ ....
በየቤቱ እና በየትምህርት ቤቱ፣ ሥር የሌላቸውን ዛፎች እየተከልን ነው። መብረር የማይችሉ ወፎችን እያረባን ነው።
#በሕይወት_እምሻው
💫ጨረስኩ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ሀገሬ_ኀምሳ_እግር_ናት
የሀገሬ ወንዝ ዋናው ካነገባሩ ሲዘረዘር በንዴት እበግናለሁ።ፉት እንለው፣ ለቅለቅ እንልበት ውሃ ፍለጋ ከከተማ እስከ ገጠር
የምንማስነውን እኛን አስቤ ብግን እላለሁ፡፡
የሀገሬ ቀንድ ከብት ቁጥር፣ ከአፍሪካ አንደኛ” ተብሎ ሲጠራ በንዴት እንተከተካለሁ፡፡ ወተት እየተራጨን በማደግ ፈንታ የላም ወተት የዋልያ ወተት ይመስል ብርቅ የሆነብንን እኛን አስቤ ትክን እላለሁ፡፡
የሀገሬን ስፋት ሳስብ እናደዳለሁ፡፡ የእኔ የምንለው ክብሪት ሣጥን ታክል ቦታ አጥተን በየፊውዳሉ ቤት በጭሰኝነት የልጅነት ሀብታችንን ለምንገብረው እኛ ተቆርቁሬ፣ በንዴት እንገረገባለሁ፡፡
ይሄ ሁሉ እያላት ለእኛ ያልተረፈችው ሀገሬ፣ ሀብት እያላት ድሃ ናት፡፡ ሀገሬ ኀምሳ እግር ናት፡፡
ያ..... ሁሉ...... እግር እያለው ዘልአለም እንደሚድኸው ቆሞ እንደማያውቀው ኀምሳ እግር፡፡
ከምትድህበት አንስቶ በኀምሳውም እግሯ የሚያቆማት ጎበዝ እስክታገኝ ሀገሬ ኀምሳ እግር ናት፡፡
#በሕይወት_እምሻው
የሀገሬ ወንዝ ዋናው ካነገባሩ ሲዘረዘር በንዴት እበግናለሁ።ፉት እንለው፣ ለቅለቅ እንልበት ውሃ ፍለጋ ከከተማ እስከ ገጠር
የምንማስነውን እኛን አስቤ ብግን እላለሁ፡፡
የሀገሬ ቀንድ ከብት ቁጥር፣ ከአፍሪካ አንደኛ” ተብሎ ሲጠራ በንዴት እንተከተካለሁ፡፡ ወተት እየተራጨን በማደግ ፈንታ የላም ወተት የዋልያ ወተት ይመስል ብርቅ የሆነብንን እኛን አስቤ ትክን እላለሁ፡፡
የሀገሬን ስፋት ሳስብ እናደዳለሁ፡፡ የእኔ የምንለው ክብሪት ሣጥን ታክል ቦታ አጥተን በየፊውዳሉ ቤት በጭሰኝነት የልጅነት ሀብታችንን ለምንገብረው እኛ ተቆርቁሬ፣ በንዴት እንገረገባለሁ፡፡
ይሄ ሁሉ እያላት ለእኛ ያልተረፈችው ሀገሬ፣ ሀብት እያላት ድሃ ናት፡፡ ሀገሬ ኀምሳ እግር ናት፡፡
ያ..... ሁሉ...... እግር እያለው ዘልአለም እንደሚድኸው ቆሞ እንደማያውቀው ኀምሳ እግር፡፡
ከምትድህበት አንስቶ በኀምሳውም እግሯ የሚያቆማት ጎበዝ እስክታገኝ ሀገሬ ኀምሳ እግር ናት፡፡
#በሕይወት_እምሻው
#ገዳዬ_ገዳዬ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
ፀሐያቸው ጠልቃ በሰው ሀገር መሽቶብኝ ነበር፡፡ ጨልሟል የተለመደውን አውቶብሴን ተሳፈርኩበ።
አዲስ ነገር የለውም፡ ሁሌም የምጠብቀው ያ ሁሌም በጠበቅኩት
ሰዐት የሚመጣው የማይዛነፍ የዕለት ውሎዬን የሚደመድመው አውቶብስ ነው።
እንደተቀመጥኩ፣ ሰንደቅ የሚያሰቅል ቁመት ያለው! ውብም፤ሎጋም ኢትዮጵያዊ ወንበር ሲፈልግ አየሁት።
አውቶብሱ ውስጥ ብዙ ክፍት ወንበሮች ነበሩ፡፡ ወደ መስኮቴ ዞርኩ
እና ጸሎት ብጤ አደረግኩ፡፡ ብታውቁኝ ለዚህ ዓይነት ነገር ጸሎትን ያህል ነገር የማባክን ሰው አይደለሁም ግን... ጸለይኩ፡፡
ጸሎቴ ተሰማ መሰለኝ እጠገቤ መጥቶ ተቀመጠ፡፡
ከዚያ ምን ሆነ?
“ሃ...ይ..." አለኝ፡፡ ዝም ብሎ ሃይ አልነበረም፡፡ ይሄ..አንድ ሃ' እና ስድስት 'ይ ያለው ሃይን ታውቁታላችሁ? እሱ ነው! እንደሱ ነው ሃይ ያለኝ፡፡
ዞር ብዬ ሌላ ትንሽ ጸሎት አደረስኩ፡፡
ፈጣሪ በትንሽ ፀሎት ይሄን መለሎ አጠገቤ አምጥቶ ስላስቀመጠልኝ፣ አስቀምጦም እንዲህ ያለውን ሃይ እንዲለኝ ምላስ እና ከንፈሩን ስላቀናጀልኝ ሌላ ፀሎት አደረስኩ።
አስቡት..የመጀመርያው ጸሎቴ ሳይሰማ ኖሮ ይሄ አማላይ ይሄ ሳያነጣጥር ገዳይ አጠገቤ ይቀመጥ ተቀምጦስ ሰላም ይለኝ ነበር....?
እንዳልኳችሁ አውቶብስ ተሳፍሬ ዐይነ ግቡ ሰው በተሳፈረ ቁጥር፣
ወንበር በፈለገ ቁጥር እንዲህ አይነት ጸሎት የምጸልይ አይነት ሴት
አይደለሁም፡፡
የፈለግኩትን ሰው ለማግኘት ቃላትን የማሰናዳ፣
የከንፈር ቀለሜን የማደምቅ፣
ዐይኖቼን የማስለመልም፣
ጡቶቼን ከካኔተራዬ ገፍትሬ የማወጣ፣
መቀመጫዬን ያለ አቅሙ የማንቀጠቅጥ ሴትም አይደለሁም፡፡
ሴት ነኝ፡፡
ልቤን በልቡ ይቀይረኛል በሚል ተስፋ ወንድኝን በጭኖቼ ክፍተት የማስገባ አለመማረክ የሰለቸኝ ለድርያ እንጂ ለትዳር አለመፈለግ ያቆሰለኝ የትርጉም አልባ አጫጭር ግኑኝነቶች ርዝመት ያታከተኝ ሴት ነኝ
ምክንያቱም ጭርሱን መራመድ ተሳነኝ፡፡
ልድገመው፡፡ የትርጉም አልባ አጫጭር ግንኙነቶች ርዘመት ያታከተኝ ሴት ነኝ።
አልፎ ሂያጆቹን ትቼ ስለዚህ ልጅ ብቻ የማወራችሁ ለዚህ ነው፡፡
ለምን እንደሆነ ባላውቅም በልኬ ተሰፍቶ እዚህ አውቶብስ ውስጥ የተጣለ መሰለኝ፡፡ ያልዳነ ቁስሌን የሚያክመኝ ሰው እሱ መሰለኝ፡፡
..የበደሌ ካሳ በሚያምር ልጅ መልክ ተሠርቶ የተበረከተልኝም መሰለኝ፡፡
መሰለኝ እንግዲህ...
አውቶብስ ላይ ከተዋወቅን በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲደውልልኝ
ያንኑ ባለ አንድ ሃ' እና ባለ ስድስት 'ይ' “ሃይ' አለኝ፡፡
በተቀመጥኩበት አቁነጠነጠኝ፡፡ እንደ ሆነ ነገር ሠራኝ፡፡ ፈተነኝ...ይሄ ልጅ ክፉኛ ፈተነኝ፡፡
በሚቀጥለው ቀን አንዱ ፓርክ ተቀጣጥረን ቁጭ ብሎ እየጠበቀኝ
ነበር፡፡
ጀርባውን ሳየው የሆነ ነገሬ እንደ ጧፍ ይቀልጥ ጀመር፡፡
የቀለጠው...
ይመስለኛል እግሮቼን እንዲሄዱ የሚያደርገው ጡንቻዬ ነው።
ይመስለኛል አጥንቴ ነው ይመስለኛል ሁለተናዬ ነው።
ምክንያቱም ጭርሱን መራመድ ተሳነኝ።
ቀልጬ ከማለቄ በፊት ድንቅፍቅፍ እርምጃዬን ሰምቶ መሰለኝ ወደኔ መጣ።
ፀሐይ ከሰማይ ወርዳ፣ እግር አውጥታ ወደኔ ትመጣ ይመስል የመቅለጥ ፍርሀቴ ይበልጥ ጨመረ፡፡
“የትኛው አካሌ ቀድሞ አመድ ይሆን፣ ይሆን?” እያልኩ ቆሜ ቀረሁ።
አጠገቤ ሲደርስ አውቶብሱ ላይ ያላየሁትን አዲስ ፈገግታ ፊቱ ላይ ተመለከትኩ።
ሚዛኔ ተመለሰ። እግሮቼ በረቱ።
እንጃ ብቻ...ፈገግ ያሉ ዐይኖቹ ውስጥ የለመድኩት ነገር ሁሉ ታየኝ።
ፊቱ ላይ አራት ኪሎ ታየኝ የድል ሃውልት።በተርታ ያሉት ጭማቂ ቤቶች ከጀርባ ያሉት ሻይ ቤቶች ቁልጭ ብለው ታዩኝ።
ፊቱ ላይ ኢትዮጵያ ታየችኝ፡፡
ፈገግታው በሰከንዶች ውስጥ አከመኝ። ሚዛኔ ሲመለስ ተሰማኝ እግሮቼ እንሂድ አሉኝ፡፡ እጄን ያዘኝ እና መራመድ ጀመርን፡፡
እየሄድን....እጄን ስለያዘኝ ብቻ ማንም የማይነካኝ ክፉ የማያገኘኝ መሰለኝ።
ሁሉ ሰው ስሜን የሚያውቀው፣ሁሉ የሚወደኝ ስፍራ
ሃገሬ.... ኢትዮጵያ የሄድኩ መሰለኝ፡፡
አለ አይደል... በአያያዙ ውስጥ የሀገሬን መንገድ ያገኘሁ ያህል ተሰማኝ።
በዙሪያችን ያሉ ሰዎች “ምን እንደሆንኩ ዐውቀው ይሆን?” ብዬ ዞር ዞር ብዬ አየኋቸው።
"ገዳይ ሰውነት ካለው መለሎ ጋር ሆኜ ላለመሞት እየታገልኩ እንደሆነ አስተውለው ይሆን?" ብዬ ዙርያየን ቃኘው።
ቀጥሎ ምን ሆነ?
እልፍ አእላፍ ማታዎች ስንፃፃፍና በስልክ ስናወራ ከረምን።
ተጻጻፍን፡፡ ፎቶ ተላላክን፡፡ አወራን፡፡
ተጻጻፍን፡፡ ፎቶ ተላላክን፡፡ አወራን፡፡
ተጻጻፍን። ፎቶ ተላላክን፡፡ አወራን፡፡
ከዚያ እንደገና ተገናኘን፡፡
እመኑኝ፡፡ በሰው ሃገር ሆናችሁ የወንዛችሁን ልጅ- ያውም እንዲህ
ያለውን ስታገኙ ፈገግታው ሀገራችሁ ነው፡፡
ለዚያ ይሆናል ከፈገግታው መላቀቅ ያቃተኝ፡፡
ለዚያ ይሆናል ዐይኑን ዐይቼ መጥገብ የተሳነኝ፡፡
ዐይኑ ውስጥ ወደ ሃገሬ የሚወስደኝ መንገድ አለ፡፡
ምን ብዬ ላስረዳችሁ እንጂ ...አባቴ ይሙት... እጄን እያያዙ ውስጥ ማንነቴ ሁሉ አለ።
በተገናኘን ምሽት ያን ጃንሜዳን የሚያስንቅ ደረቱን ወለል አድርጎ
የሚያሳይ ጠበቅም -ሳሳም ያለ ሹራብ ለብሶ ነበር።
ወይ ደረቱ! አቤት ደረቱ! ስለ ደረቱ ዐሥር ግጥም በዐሥር ደቂቃ ልፅፍ እችላለሁ። ግን የወሬው አላማ እሱ አይደለም።
እጅ ተያይዘን አብረን ስንራመድ፣ ስንሥቅ፣ ፈገግ ስንል፣ ደረቱ ላይ
ስጋደም፣ ደረቱ ላይ ሲያጋድመኝ፣ በአማርኛ ስናወራ መሸና የሀበሻ
ቤት ሄደን የሀበሻ ቡና በሀበሻ ወግ ጠጣን፡፡
“ቡና እወዳለሁ፡፡” አለኝ፡፡
እኔ ለቡና እስከዚህም ነኝ፣ ግን እሺ ብዬ ጠጣሁ፡፡ ቶና አይደለሃ በረካ አይደለም፡፡
ያን ምሽት ከአቦል ልጅ ጋር ነኝና አምስት ስኒ አቦል ቡና ጠጣሁ።
ስኳር በጨመርኩ ቁጥር፣ “ስኳር ቡናውን ይገድለዋል... ቡና ያለስኳር ነው መጠጣት ያለበት...ሞክሪው፡፡” ሲለኝ፣ ስኳሩን በእሱ ተክቼ ስንት ስኒ ቡና ያለ ስኳር ጠጣሁ?
ስንቱን ስኒ ቡና ባዶውን ሳይመረኝ አንቃረርኩ?
ተለይቼው፣ ቤቴ ገብቼ ከዚህ ቀደም ስለማላዘወትረው ቡና - በተለይ ስለ አቦል ቡና ጀመርኩ። በባዶ ቡና ፍቅር ተንገበገብኩ።
በሚቀጥለው እስካገኘው፣ ያለ ልማዴ በየቀኑ ስለ እሱ እያሰበኩ ስኳር የሌለው ወፍራም ቡና ማፍላት መጠጣት ጀመርኩ
ከዚያስ?
ከነዚያ ምሽቶች በኋላ በድንገት ስልኬን መመለስ፣ ለመልእክቶቼ
መልስ መስጠት አቆመ፡፡ የት ገባ? አላውቅም፡፡ ብቻ…. ብቻ ጠፋብኝ።
እደውላለሁ- አያነሳም፡፡
እጽፋለሁ አይመለስም፡፡
ዐሥራ ሦስት ቀናት አለፉ፡፡
ዐሥራ ሦስት እሱን-አልባ ቀናት ኖርኩ፡፡
ዐሥራ አራተኛው ቀን...
ያ ልጅ... ፈገግታውን፣ እጅ አያያዙን፣ ሳንቃ ደረቱን ይዞብኝ ሲጠፋ...
ያ ልጅ... የሀገሬን መንገድ፣ ኢትዮጵያዬን ይዞብኝ ሲሰወር...
..በላይ በላዩ ባዶውን እጠጣው የነበረው አቦል ቡና በመዐት ማንኪያ ስኳር እንኳን ይመረኝ ጀመር፡፡ ቀረ.. ቀረ.. ቀረ..
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
ፀሐያቸው ጠልቃ በሰው ሀገር መሽቶብኝ ነበር፡፡ ጨልሟል የተለመደውን አውቶብሴን ተሳፈርኩበ።
አዲስ ነገር የለውም፡ ሁሌም የምጠብቀው ያ ሁሌም በጠበቅኩት
ሰዐት የሚመጣው የማይዛነፍ የዕለት ውሎዬን የሚደመድመው አውቶብስ ነው።
እንደተቀመጥኩ፣ ሰንደቅ የሚያሰቅል ቁመት ያለው! ውብም፤ሎጋም ኢትዮጵያዊ ወንበር ሲፈልግ አየሁት።
አውቶብሱ ውስጥ ብዙ ክፍት ወንበሮች ነበሩ፡፡ ወደ መስኮቴ ዞርኩ
እና ጸሎት ብጤ አደረግኩ፡፡ ብታውቁኝ ለዚህ ዓይነት ነገር ጸሎትን ያህል ነገር የማባክን ሰው አይደለሁም ግን... ጸለይኩ፡፡
ጸሎቴ ተሰማ መሰለኝ እጠገቤ መጥቶ ተቀመጠ፡፡
ከዚያ ምን ሆነ?
“ሃ...ይ..." አለኝ፡፡ ዝም ብሎ ሃይ አልነበረም፡፡ ይሄ..አንድ ሃ' እና ስድስት 'ይ ያለው ሃይን ታውቁታላችሁ? እሱ ነው! እንደሱ ነው ሃይ ያለኝ፡፡
ዞር ብዬ ሌላ ትንሽ ጸሎት አደረስኩ፡፡
ፈጣሪ በትንሽ ፀሎት ይሄን መለሎ አጠገቤ አምጥቶ ስላስቀመጠልኝ፣ አስቀምጦም እንዲህ ያለውን ሃይ እንዲለኝ ምላስ እና ከንፈሩን ስላቀናጀልኝ ሌላ ፀሎት አደረስኩ።
አስቡት..የመጀመርያው ጸሎቴ ሳይሰማ ኖሮ ይሄ አማላይ ይሄ ሳያነጣጥር ገዳይ አጠገቤ ይቀመጥ ተቀምጦስ ሰላም ይለኝ ነበር....?
እንዳልኳችሁ አውቶብስ ተሳፍሬ ዐይነ ግቡ ሰው በተሳፈረ ቁጥር፣
ወንበር በፈለገ ቁጥር እንዲህ አይነት ጸሎት የምጸልይ አይነት ሴት
አይደለሁም፡፡
የፈለግኩትን ሰው ለማግኘት ቃላትን የማሰናዳ፣
የከንፈር ቀለሜን የማደምቅ፣
ዐይኖቼን የማስለመልም፣
ጡቶቼን ከካኔተራዬ ገፍትሬ የማወጣ፣
መቀመጫዬን ያለ አቅሙ የማንቀጠቅጥ ሴትም አይደለሁም፡፡
ሴት ነኝ፡፡
ልቤን በልቡ ይቀይረኛል በሚል ተስፋ ወንድኝን በጭኖቼ ክፍተት የማስገባ አለመማረክ የሰለቸኝ ለድርያ እንጂ ለትዳር አለመፈለግ ያቆሰለኝ የትርጉም አልባ አጫጭር ግኑኝነቶች ርዝመት ያታከተኝ ሴት ነኝ
ምክንያቱም ጭርሱን መራመድ ተሳነኝ፡፡
ልድገመው፡፡ የትርጉም አልባ አጫጭር ግንኙነቶች ርዘመት ያታከተኝ ሴት ነኝ።
አልፎ ሂያጆቹን ትቼ ስለዚህ ልጅ ብቻ የማወራችሁ ለዚህ ነው፡፡
ለምን እንደሆነ ባላውቅም በልኬ ተሰፍቶ እዚህ አውቶብስ ውስጥ የተጣለ መሰለኝ፡፡ ያልዳነ ቁስሌን የሚያክመኝ ሰው እሱ መሰለኝ፡፡
..የበደሌ ካሳ በሚያምር ልጅ መልክ ተሠርቶ የተበረከተልኝም መሰለኝ፡፡
መሰለኝ እንግዲህ...
አውቶብስ ላይ ከተዋወቅን በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲደውልልኝ
ያንኑ ባለ አንድ ሃ' እና ባለ ስድስት 'ይ' “ሃይ' አለኝ፡፡
በተቀመጥኩበት አቁነጠነጠኝ፡፡ እንደ ሆነ ነገር ሠራኝ፡፡ ፈተነኝ...ይሄ ልጅ ክፉኛ ፈተነኝ፡፡
በሚቀጥለው ቀን አንዱ ፓርክ ተቀጣጥረን ቁጭ ብሎ እየጠበቀኝ
ነበር፡፡
ጀርባውን ሳየው የሆነ ነገሬ እንደ ጧፍ ይቀልጥ ጀመር፡፡
የቀለጠው...
ይመስለኛል እግሮቼን እንዲሄዱ የሚያደርገው ጡንቻዬ ነው።
ይመስለኛል አጥንቴ ነው ይመስለኛል ሁለተናዬ ነው።
ምክንያቱም ጭርሱን መራመድ ተሳነኝ።
ቀልጬ ከማለቄ በፊት ድንቅፍቅፍ እርምጃዬን ሰምቶ መሰለኝ ወደኔ መጣ።
ፀሐይ ከሰማይ ወርዳ፣ እግር አውጥታ ወደኔ ትመጣ ይመስል የመቅለጥ ፍርሀቴ ይበልጥ ጨመረ፡፡
“የትኛው አካሌ ቀድሞ አመድ ይሆን፣ ይሆን?” እያልኩ ቆሜ ቀረሁ።
አጠገቤ ሲደርስ አውቶብሱ ላይ ያላየሁትን አዲስ ፈገግታ ፊቱ ላይ ተመለከትኩ።
ሚዛኔ ተመለሰ። እግሮቼ በረቱ።
እንጃ ብቻ...ፈገግ ያሉ ዐይኖቹ ውስጥ የለመድኩት ነገር ሁሉ ታየኝ።
ፊቱ ላይ አራት ኪሎ ታየኝ የድል ሃውልት።በተርታ ያሉት ጭማቂ ቤቶች ከጀርባ ያሉት ሻይ ቤቶች ቁልጭ ብለው ታዩኝ።
ፊቱ ላይ ኢትዮጵያ ታየችኝ፡፡
ፈገግታው በሰከንዶች ውስጥ አከመኝ። ሚዛኔ ሲመለስ ተሰማኝ እግሮቼ እንሂድ አሉኝ፡፡ እጄን ያዘኝ እና መራመድ ጀመርን፡፡
እየሄድን....እጄን ስለያዘኝ ብቻ ማንም የማይነካኝ ክፉ የማያገኘኝ መሰለኝ።
ሁሉ ሰው ስሜን የሚያውቀው፣ሁሉ የሚወደኝ ስፍራ
ሃገሬ.... ኢትዮጵያ የሄድኩ መሰለኝ፡፡
አለ አይደል... በአያያዙ ውስጥ የሀገሬን መንገድ ያገኘሁ ያህል ተሰማኝ።
በዙሪያችን ያሉ ሰዎች “ምን እንደሆንኩ ዐውቀው ይሆን?” ብዬ ዞር ዞር ብዬ አየኋቸው።
"ገዳይ ሰውነት ካለው መለሎ ጋር ሆኜ ላለመሞት እየታገልኩ እንደሆነ አስተውለው ይሆን?" ብዬ ዙርያየን ቃኘው።
ቀጥሎ ምን ሆነ?
እልፍ አእላፍ ማታዎች ስንፃፃፍና በስልክ ስናወራ ከረምን።
ተጻጻፍን፡፡ ፎቶ ተላላክን፡፡ አወራን፡፡
ተጻጻፍን፡፡ ፎቶ ተላላክን፡፡ አወራን፡፡
ተጻጻፍን። ፎቶ ተላላክን፡፡ አወራን፡፡
ከዚያ እንደገና ተገናኘን፡፡
እመኑኝ፡፡ በሰው ሃገር ሆናችሁ የወንዛችሁን ልጅ- ያውም እንዲህ
ያለውን ስታገኙ ፈገግታው ሀገራችሁ ነው፡፡
ለዚያ ይሆናል ከፈገግታው መላቀቅ ያቃተኝ፡፡
ለዚያ ይሆናል ዐይኑን ዐይቼ መጥገብ የተሳነኝ፡፡
ዐይኑ ውስጥ ወደ ሃገሬ የሚወስደኝ መንገድ አለ፡፡
ምን ብዬ ላስረዳችሁ እንጂ ...አባቴ ይሙት... እጄን እያያዙ ውስጥ ማንነቴ ሁሉ አለ።
በተገናኘን ምሽት ያን ጃንሜዳን የሚያስንቅ ደረቱን ወለል አድርጎ
የሚያሳይ ጠበቅም -ሳሳም ያለ ሹራብ ለብሶ ነበር።
ወይ ደረቱ! አቤት ደረቱ! ስለ ደረቱ ዐሥር ግጥም በዐሥር ደቂቃ ልፅፍ እችላለሁ። ግን የወሬው አላማ እሱ አይደለም።
እጅ ተያይዘን አብረን ስንራመድ፣ ስንሥቅ፣ ፈገግ ስንል፣ ደረቱ ላይ
ስጋደም፣ ደረቱ ላይ ሲያጋድመኝ፣ በአማርኛ ስናወራ መሸና የሀበሻ
ቤት ሄደን የሀበሻ ቡና በሀበሻ ወግ ጠጣን፡፡
“ቡና እወዳለሁ፡፡” አለኝ፡፡
እኔ ለቡና እስከዚህም ነኝ፣ ግን እሺ ብዬ ጠጣሁ፡፡ ቶና አይደለሃ በረካ አይደለም፡፡
ያን ምሽት ከአቦል ልጅ ጋር ነኝና አምስት ስኒ አቦል ቡና ጠጣሁ።
ስኳር በጨመርኩ ቁጥር፣ “ስኳር ቡናውን ይገድለዋል... ቡና ያለስኳር ነው መጠጣት ያለበት...ሞክሪው፡፡” ሲለኝ፣ ስኳሩን በእሱ ተክቼ ስንት ስኒ ቡና ያለ ስኳር ጠጣሁ?
ስንቱን ስኒ ቡና ባዶውን ሳይመረኝ አንቃረርኩ?
ተለይቼው፣ ቤቴ ገብቼ ከዚህ ቀደም ስለማላዘወትረው ቡና - በተለይ ስለ አቦል ቡና ጀመርኩ። በባዶ ቡና ፍቅር ተንገበገብኩ።
በሚቀጥለው እስካገኘው፣ ያለ ልማዴ በየቀኑ ስለ እሱ እያሰበኩ ስኳር የሌለው ወፍራም ቡና ማፍላት መጠጣት ጀመርኩ
ከዚያስ?
ከነዚያ ምሽቶች በኋላ በድንገት ስልኬን መመለስ፣ ለመልእክቶቼ
መልስ መስጠት አቆመ፡፡ የት ገባ? አላውቅም፡፡ ብቻ…. ብቻ ጠፋብኝ።
እደውላለሁ- አያነሳም፡፡
እጽፋለሁ አይመለስም፡፡
ዐሥራ ሦስት ቀናት አለፉ፡፡
ዐሥራ ሦስት እሱን-አልባ ቀናት ኖርኩ፡፡
ዐሥራ አራተኛው ቀን...
ያ ልጅ... ፈገግታውን፣ እጅ አያያዙን፣ ሳንቃ ደረቱን ይዞብኝ ሲጠፋ...
ያ ልጅ... የሀገሬን መንገድ፣ ኢትዮጵያዬን ይዞብኝ ሲሰወር...
..በላይ በላዩ ባዶውን እጠጣው የነበረው አቦል ቡና በመዐት ማንኪያ ስኳር እንኳን ይመረኝ ጀመር፡፡ ቀረ.. ቀረ.. ቀረ..
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1