#ሴት_እና_የነገር_ቱባ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
ቁርሳችንን ለኮፍ ለኮፍ አድርገን ለመውጣት እየተጣደፍን ነው ያለ ቅጥ ረፍዶብናል፡፡
“ብርድ ነው ፀሐይ..? እስቲ ውጣና ዕይልኝ!” አልኩት፡፡ “ሹራብ ልልበስ ሸሚዝ?” በሚል ከተመሣቀለው ቁምሣጥን ልብስ ለመምረጥ
እየተጣደፍኩ፡፡
በቁሙ፧ በግማሽ ልብ ቴሌቪዥን እያየ የሚጠብቀኝ ባሌ፣ መልስ አልሰጠኝም፡
“በረከት!” አልኩት እየጮኽኩ፡፡
“ወ.. ይ...” አለና ከሲ ኤን ኤንዋ ዜና አንባቢ ዐይነን አንስቶ እኔ
ላይ አሳረፈ፡፡
“አትሰማኝም እንዴ?”
“አልሰማሁም...ምን አልሽኝ....?”
“ወይ ጉዴ...! ብርድ ነው ፀሐይ... ውጣና ዕይልኝ... ልብስ እንድመርጥ...”
“ወይ ቆንጂት!... ገና አልለበስሽም እንዴ... ቶሎ ቶሎ በይ እንጂ አለኝ እንደ ነገሩ እያየኝ፡፡
“ወየው.... ከላይ ብቻ ነው የቀረኝ... ዕይልኝ ይልቅ....”
ተበሳጭቻለሁ፡፡
በግብር ይውጣ አካሄድ ወጣና መለስ ብሎ፣ “ደመና ነው... ሹራብ
ያዢ!” አለኝ፡፡
ይሄን ጊዜ ! ከሱሪዬ ጋር የሚሄድ ሹራብ ፍለጋ ቁምሳጥኔን ማተራመስ ጀመርኩ፡፡
“እረ ቆንጂት በፈጠረሽ እንውጣ...! ይቺ ዐሥር ደቂቃ ካለፈች
ታውቂያለሽ የታክሲ ሰልፉ መከራ ነው” አለኝ ቴሌቪዥኑን እያጠፋ፡፡
ሹራብ ፍለጋዬን አቆምኩና ዞር ብዬ ዐየሁት፡፡
ደግሞ ልንጨቃጨቅ ነው፡፡
አሁን አሁን ከምንም ነገር በላይ አብዝተን የምናደርገው ነገር፣
መጨቃጨቅ ነው፡፡
ስለ አለባበሴ እንጨቀጨቃሰን፡፡
ስለ ከጓደኞቹ ጋር ማምሸቱ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለ ገንዘብ አያያዜ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለ ልጆቻችን ጠባይ እንጨቃጨቃለን፡፡
ፐ
ስለ እናቱ እኔን አለመውደድ ጉዳይ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለኔ ታናሽ ወንድም መበላሸት እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለምንም ነገር እንጨቃጨቃለን፡፡
ሹራብ ነው የቀረኝ... ታገሰኝ..." ኣልኩት፤ “ዋ ሌላ ነገር ተናገረኝና
ጉድ ይፈላል” በሚል ዓይነት ድምፅ፡፡
ግን ሌላ ነገር ተናገረኝ፡፡
“ስንት ሰዐት እታገስሻለሁ....? ልብስ ለመልበስ አንድ ሰዓት ሊያውም እንዲህ እረፍዶ?”
አሁን በደንብ ልንጨቃጨቅ ነው፡፡
በኔ በረፈደ ሰዐት ላይ ልብስ ለመልበስ መቆየት መነሻነት የተጀመረው ጭቅጭቅ መዳረሻው የት እንደሆነ አላውቅም..
ጭቅጭቃችን የራሱ ቦይ አለው፡፡ ራሱ እየቀደደ የሚፈስበት ቦይ::
ከቀበና ወንዝ ተነስቶ ሜዲትራኒያን የሚገባበት የራሱ ረጅ....ም....ቦይ፡፡
“አንድ ሰዐት አልፈጀብኝም! አታጋንን፤ ማጋነን ስትወድ "አልኩት፣ ሰማያዊውን ሹራቤን አውጥቼ እየለበስኩ፡፡
“እኔው ነኝ አጋናኙ...?” አለኝ ደክሞት ውሎ እንደመጣ ሰው ሶፋው ላይ ተመልሶ እየተቀመጠ፡፡
“ምን ማለት ነው እኔው ነኝ አጋናኙ..? አንቺ ታጋንኛለሽ ለማለት ነው...?” አልኩት ገንፈል ብዬ፡፡
ዝም አለ፡፡
በአሸናፊነት መንፈስ ሹራቤን ለብሼ የቁምሳጥኑ መስታወት ጋር
ሄጄ ከሱሪዬ ጋር ያለውን ቅንጅት አየሁ፡፡
አያምርም፡፡
ሮዙን ሹራብ ባደርግ ይሻለኛል፡፡
ሰማያዊውን ሹራብ አውልቄ አልጋ ላይ ጣልኩና ሮዙን ሹራብ መፈለግ ስጀምር የሆነ ነገር ሲል ሰማሁት፡፡
“ምን አልክ?”
“ምንም አላልኩም ቆንጂት ”
“ለምን ምንም አላልኩም ትላለህ ...? የሆነ ነገር ስትል
አልሰማሁህም አሁን...?” ወደ ሳሎን መጥቼ አፈጠጥኩበት፡፡
“ምንም አላልኩም.... ....... በይ ይልቅ ፤ ትናንት ብፈልገው አጣሁት... የእዚህ ሪሞት አንዱ ባትሪ የት ገባ...? ወድቆ ጠፍቷል” አለኝ፣ መክደኛ የሌለውን የቴሌቪዥናችንን ሪሞት ኮንትሮል
አገላብጦ እያየ፡፡
“ምን እኔን ትጠይቀኛለህ... አንተ ነህ ተሰክተህበት የምትውልበት
ቲቪውን፤ ...ራስህ አትፈልገውም...?” ሹራቤን ፍለጋ እየተመለስኩ መለስኩ፡፡
“እኔ የት እንዳለ ባውቅ አንቺን ምን አስጠየቀኝ?”
“እንጃ! ምናልባት ለሁሉ ነገር ጥፋተኛ የምታደርገው እኔን ስለሆነ”
“ለሁሉ ነገር?”
አዎ! ....ቲቪ ተበላሸ... ቆንጂት ምን አረግሽው...? የቤቱ ግድግዳ
ለቀቀ ፤ ቆንጂት ምን ስትሰሪ እንዲህ ሆነ..? የልጆቹ ፀባይ ተበላሽ
ቆንጂት አንቺ እኮ ነሽ እያቀበጥሻቸው...? አሁን ደግሞ ሚጢጢ ባትሪ ጠፋ እኔኑ ጥፋተኛ...”
ሳላሰበው ሁለመናዬ ሲግል እየተሰማኝ ተናገርኩ፡፡
“በ...ይ ተይው እገዛለሁ... ሆሆ!” ብሎ ሪሞት ኮንትሮሉን ጠረጴዛው ላይ ሲወረውር ተሰማኝ፡፡
ግዛ አንተ ምን አለብህ...! ሽሮ በርበሬ ብዬ የምሣቀቀው እኔ...
አንተማ መዥረጥ አድርገህ ያሻህን ትገዛለህ..." አልኩ።ግለቴ ሳይበርድ፤ ሮዙን ሹራብ እያደረግኩ፡፡
“ታዲያ ከጠፋ ምን አድርግ ትይኛለሽ...? ደሞ ለባትሪ...”
“ደሞ ለዚች እያልክ ነው ገንዘብ የምታባክነው፡፡ ገንዘብ በትንሹ
ካልተቆጠበ ብዙ ይሆናል...?”
“ደሞ አሁን ገንዘብ አባካኝ ሆንኩ..!.”
ድምፁ ይንቀጠቀጣል፡፡ ድምፁ ከተንቀጠቀጠ ተናዷል ማለት ነው፡፡
“አይ ቆጠብክልኝ እንጂ! ቆጠብክልኝ የኔ ጌታ! ይሄ በየማታው የምትጋተው ድራፍት እንኳን ቢደማመር የልጆቹን አስጠኚ የወር ደሞዝ ቀጥ አድርጎ አይችልም....?” አልኩት ድምጼን ከፍ አድርጌ ፤ ወገቤን በነገረኛ ሴት ቄንጥ ይዤ ወደ ሳሎን እየተመለስኩ፡፡
ፊቱ ቀልቷል፡፡
“በየማታው...? እኔ ነኝ በየማታው ድራፍት የምጋተው....? ከቅዳሜ
ውጪ ...ሊያውም ከሁለት ድራፍት በላይ ስጠጣ አይተሸኛል....?
ደሞ ለነገሩስ ለልጆቹ አስጠኚ ይቀጠር ስልሽ... ተወው ፤ ማቲ እየመጣ እንደፈለጋቸው ያስጠናቸዋል' ብለሽ አይደለም የተውነው እንዴ!”
እሱማ ነበር! ....የሚሆን መስሎኝ፡፡ ገንዘብም እንዲቆጠብ ብዬ .. ግን
ምስኪን ወንድሜን በሳምንት ሦስቱ ለሚመጣው እየገላመጥክ
ከቤቴ አራቅከው... አሁን እስቲ ምን አደረገህ ...? ልጆችህን በነጻ ባስጠናልህ...”
አሁን ቅድም እንደ ዋዛ የጣልኩትን የአንገት ልብሴን እየፈለግኩ
ነው፡፡
“ተይ ቆንጂት ግፍ አትናገሪ፡፡ እኔ ነኝ ወንድምሽን ከዚህ ቤት
ያራቅኩት? ራሱ አይደለም፣ ልጆቹ ማቲ ሲጋራ ሲያጨስ እያዩ እንዳይሰላሹ ምከሪው' ስልሽ ሰምቶ እዚህ ቤት አልመጣም ያለው...? እሱ ዱርዬ በሆነው ለልጆቼ ማሰቤ ነው እኔን
የሚያስወቅሰኝ!”
አሁን በማቲ መጣብኝ፡፡ የማቲ ነገር እንደማይሆንልኝ እያወቀ በጠዋቱ በማቲ መጣብኝ፡፡
“በረከት! ማቲ ዱርዬ አልሆነም... ወጣት ነው….. ሊሳሳት ይችላል...
እንደ ታላቅ ወንድም ልትመክረው ሲገባ እንደ እብድ ውሻ ከገዛ እህቱ ቤት አባረርከው... ይሄ ልክ ነው?” አልኩት የአንገት ልብሴን ፍለጋ ትቼ እያየሁት፡፡
“እህ... ተይው... አንቺ ልጄ..... ታክሲው... ይልቅ በናትሽ ለብሰሽ
ጨርሺ አሁን... እንሂድ፡፡” አሁንም ያንን ሪሞት ኮንትሮል እያገላበጠ ያያል፡፡
እንዲህ በነገር እየለበለብከኝ ምኑን ከምኑ አድርጌ ልልበስ.
ስካርፌ ጠፋብኝ” አልኩት ቀዝቀዝ ብዬ፡፡
“ራስሽ በጀመርሽው ነገር መልሰሽ እኔን... ይልቅ አሁን ጨረስሽ..
እንውጣ?” አለኝ ቦርሳውን እንስቶ እያነገተ፤
“ምነው ስታየኝ ያልጨረስኩ እመስላለሁ....?”
ያለ እቅዱ ነገረኛ ድምፄ ተመለሰ፡፡
“ደሞ ይሄ ምን ማለት ነው?”
“የለበስኩ አልመሰልኩም?... ለነገሩ ስታየኝ አይደል የምታውቀው በጠዋት
ቲቪ ላይ እያፈጠጠክ... ሦስተኛ ጡት አብቅዬ ባድርም እስከ ሁለት ወር የሚታይህ አይመስለኝም”
ሣቀ፡፡
እኔ ግን አልሣቅኩም፡፡ እየተጨቃጨቅን ሲስቅ ያናድደኛል።
“ሶስተኛ ጡት...? ምን?” አለኝ አሁንም እየሣቀ፡፡
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
ቁርሳችንን ለኮፍ ለኮፍ አድርገን ለመውጣት እየተጣደፍን ነው ያለ ቅጥ ረፍዶብናል፡፡
“ብርድ ነው ፀሐይ..? እስቲ ውጣና ዕይልኝ!” አልኩት፡፡ “ሹራብ ልልበስ ሸሚዝ?” በሚል ከተመሣቀለው ቁምሣጥን ልብስ ለመምረጥ
እየተጣደፍኩ፡፡
በቁሙ፧ በግማሽ ልብ ቴሌቪዥን እያየ የሚጠብቀኝ ባሌ፣ መልስ አልሰጠኝም፡
“በረከት!” አልኩት እየጮኽኩ፡፡
“ወ.. ይ...” አለና ከሲ ኤን ኤንዋ ዜና አንባቢ ዐይነን አንስቶ እኔ
ላይ አሳረፈ፡፡
“አትሰማኝም እንዴ?”
“አልሰማሁም...ምን አልሽኝ....?”
“ወይ ጉዴ...! ብርድ ነው ፀሐይ... ውጣና ዕይልኝ... ልብስ እንድመርጥ...”
“ወይ ቆንጂት!... ገና አልለበስሽም እንዴ... ቶሎ ቶሎ በይ እንጂ አለኝ እንደ ነገሩ እያየኝ፡፡
“ወየው.... ከላይ ብቻ ነው የቀረኝ... ዕይልኝ ይልቅ....”
ተበሳጭቻለሁ፡፡
በግብር ይውጣ አካሄድ ወጣና መለስ ብሎ፣ “ደመና ነው... ሹራብ
ያዢ!” አለኝ፡፡
ይሄን ጊዜ ! ከሱሪዬ ጋር የሚሄድ ሹራብ ፍለጋ ቁምሳጥኔን ማተራመስ ጀመርኩ፡፡
“እረ ቆንጂት በፈጠረሽ እንውጣ...! ይቺ ዐሥር ደቂቃ ካለፈች
ታውቂያለሽ የታክሲ ሰልፉ መከራ ነው” አለኝ ቴሌቪዥኑን እያጠፋ፡፡
ሹራብ ፍለጋዬን አቆምኩና ዞር ብዬ ዐየሁት፡፡
ደግሞ ልንጨቃጨቅ ነው፡፡
አሁን አሁን ከምንም ነገር በላይ አብዝተን የምናደርገው ነገር፣
መጨቃጨቅ ነው፡፡
ስለ አለባበሴ እንጨቀጨቃሰን፡፡
ስለ ከጓደኞቹ ጋር ማምሸቱ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለ ገንዘብ አያያዜ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለ ልጆቻችን ጠባይ እንጨቃጨቃለን፡፡
ፐ
ስለ እናቱ እኔን አለመውደድ ጉዳይ እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለኔ ታናሽ ወንድም መበላሸት እንጨቃጨቃለን፡፡
ስለምንም ነገር እንጨቃጨቃለን፡፡
ሹራብ ነው የቀረኝ... ታገሰኝ..." ኣልኩት፤ “ዋ ሌላ ነገር ተናገረኝና
ጉድ ይፈላል” በሚል ዓይነት ድምፅ፡፡
ግን ሌላ ነገር ተናገረኝ፡፡
“ስንት ሰዐት እታገስሻለሁ....? ልብስ ለመልበስ አንድ ሰዓት ሊያውም እንዲህ እረፍዶ?”
አሁን በደንብ ልንጨቃጨቅ ነው፡፡
በኔ በረፈደ ሰዐት ላይ ልብስ ለመልበስ መቆየት መነሻነት የተጀመረው ጭቅጭቅ መዳረሻው የት እንደሆነ አላውቅም..
ጭቅጭቃችን የራሱ ቦይ አለው፡፡ ራሱ እየቀደደ የሚፈስበት ቦይ::
ከቀበና ወንዝ ተነስቶ ሜዲትራኒያን የሚገባበት የራሱ ረጅ....ም....ቦይ፡፡
“አንድ ሰዐት አልፈጀብኝም! አታጋንን፤ ማጋነን ስትወድ "አልኩት፣ ሰማያዊውን ሹራቤን አውጥቼ እየለበስኩ፡፡
“እኔው ነኝ አጋናኙ...?” አለኝ ደክሞት ውሎ እንደመጣ ሰው ሶፋው ላይ ተመልሶ እየተቀመጠ፡፡
“ምን ማለት ነው እኔው ነኝ አጋናኙ..? አንቺ ታጋንኛለሽ ለማለት ነው...?” አልኩት ገንፈል ብዬ፡፡
ዝም አለ፡፡
በአሸናፊነት መንፈስ ሹራቤን ለብሼ የቁምሳጥኑ መስታወት ጋር
ሄጄ ከሱሪዬ ጋር ያለውን ቅንጅት አየሁ፡፡
አያምርም፡፡
ሮዙን ሹራብ ባደርግ ይሻለኛል፡፡
ሰማያዊውን ሹራብ አውልቄ አልጋ ላይ ጣልኩና ሮዙን ሹራብ መፈለግ ስጀምር የሆነ ነገር ሲል ሰማሁት፡፡
“ምን አልክ?”
“ምንም አላልኩም ቆንጂት ”
“ለምን ምንም አላልኩም ትላለህ ...? የሆነ ነገር ስትል
አልሰማሁህም አሁን...?” ወደ ሳሎን መጥቼ አፈጠጥኩበት፡፡
“ምንም አላልኩም.... ....... በይ ይልቅ ፤ ትናንት ብፈልገው አጣሁት... የእዚህ ሪሞት አንዱ ባትሪ የት ገባ...? ወድቆ ጠፍቷል” አለኝ፣ መክደኛ የሌለውን የቴሌቪዥናችንን ሪሞት ኮንትሮል
አገላብጦ እያየ፡፡
“ምን እኔን ትጠይቀኛለህ... አንተ ነህ ተሰክተህበት የምትውልበት
ቲቪውን፤ ...ራስህ አትፈልገውም...?” ሹራቤን ፍለጋ እየተመለስኩ መለስኩ፡፡
“እኔ የት እንዳለ ባውቅ አንቺን ምን አስጠየቀኝ?”
“እንጃ! ምናልባት ለሁሉ ነገር ጥፋተኛ የምታደርገው እኔን ስለሆነ”
“ለሁሉ ነገር?”
አዎ! ....ቲቪ ተበላሸ... ቆንጂት ምን አረግሽው...? የቤቱ ግድግዳ
ለቀቀ ፤ ቆንጂት ምን ስትሰሪ እንዲህ ሆነ..? የልጆቹ ፀባይ ተበላሽ
ቆንጂት አንቺ እኮ ነሽ እያቀበጥሻቸው...? አሁን ደግሞ ሚጢጢ ባትሪ ጠፋ እኔኑ ጥፋተኛ...”
ሳላሰበው ሁለመናዬ ሲግል እየተሰማኝ ተናገርኩ፡፡
“በ...ይ ተይው እገዛለሁ... ሆሆ!” ብሎ ሪሞት ኮንትሮሉን ጠረጴዛው ላይ ሲወረውር ተሰማኝ፡፡
ግዛ አንተ ምን አለብህ...! ሽሮ በርበሬ ብዬ የምሣቀቀው እኔ...
አንተማ መዥረጥ አድርገህ ያሻህን ትገዛለህ..." አልኩ።ግለቴ ሳይበርድ፤ ሮዙን ሹራብ እያደረግኩ፡፡
“ታዲያ ከጠፋ ምን አድርግ ትይኛለሽ...? ደሞ ለባትሪ...”
“ደሞ ለዚች እያልክ ነው ገንዘብ የምታባክነው፡፡ ገንዘብ በትንሹ
ካልተቆጠበ ብዙ ይሆናል...?”
“ደሞ አሁን ገንዘብ አባካኝ ሆንኩ..!.”
ድምፁ ይንቀጠቀጣል፡፡ ድምፁ ከተንቀጠቀጠ ተናዷል ማለት ነው፡፡
“አይ ቆጠብክልኝ እንጂ! ቆጠብክልኝ የኔ ጌታ! ይሄ በየማታው የምትጋተው ድራፍት እንኳን ቢደማመር የልጆቹን አስጠኚ የወር ደሞዝ ቀጥ አድርጎ አይችልም....?” አልኩት ድምጼን ከፍ አድርጌ ፤ ወገቤን በነገረኛ ሴት ቄንጥ ይዤ ወደ ሳሎን እየተመለስኩ፡፡
ፊቱ ቀልቷል፡፡
“በየማታው...? እኔ ነኝ በየማታው ድራፍት የምጋተው....? ከቅዳሜ
ውጪ ...ሊያውም ከሁለት ድራፍት በላይ ስጠጣ አይተሸኛል....?
ደሞ ለነገሩስ ለልጆቹ አስጠኚ ይቀጠር ስልሽ... ተወው ፤ ማቲ እየመጣ እንደፈለጋቸው ያስጠናቸዋል' ብለሽ አይደለም የተውነው እንዴ!”
እሱማ ነበር! ....የሚሆን መስሎኝ፡፡ ገንዘብም እንዲቆጠብ ብዬ .. ግን
ምስኪን ወንድሜን በሳምንት ሦስቱ ለሚመጣው እየገላመጥክ
ከቤቴ አራቅከው... አሁን እስቲ ምን አደረገህ ...? ልጆችህን በነጻ ባስጠናልህ...”
አሁን ቅድም እንደ ዋዛ የጣልኩትን የአንገት ልብሴን እየፈለግኩ
ነው፡፡
“ተይ ቆንጂት ግፍ አትናገሪ፡፡ እኔ ነኝ ወንድምሽን ከዚህ ቤት
ያራቅኩት? ራሱ አይደለም፣ ልጆቹ ማቲ ሲጋራ ሲያጨስ እያዩ እንዳይሰላሹ ምከሪው' ስልሽ ሰምቶ እዚህ ቤት አልመጣም ያለው...? እሱ ዱርዬ በሆነው ለልጆቼ ማሰቤ ነው እኔን
የሚያስወቅሰኝ!”
አሁን በማቲ መጣብኝ፡፡ የማቲ ነገር እንደማይሆንልኝ እያወቀ በጠዋቱ በማቲ መጣብኝ፡፡
“በረከት! ማቲ ዱርዬ አልሆነም... ወጣት ነው….. ሊሳሳት ይችላል...
እንደ ታላቅ ወንድም ልትመክረው ሲገባ እንደ እብድ ውሻ ከገዛ እህቱ ቤት አባረርከው... ይሄ ልክ ነው?” አልኩት የአንገት ልብሴን ፍለጋ ትቼ እያየሁት፡፡
“እህ... ተይው... አንቺ ልጄ..... ታክሲው... ይልቅ በናትሽ ለብሰሽ
ጨርሺ አሁን... እንሂድ፡፡” አሁንም ያንን ሪሞት ኮንትሮል እያገላበጠ ያያል፡፡
እንዲህ በነገር እየለበለብከኝ ምኑን ከምኑ አድርጌ ልልበስ.
ስካርፌ ጠፋብኝ” አልኩት ቀዝቀዝ ብዬ፡፡
“ራስሽ በጀመርሽው ነገር መልሰሽ እኔን... ይልቅ አሁን ጨረስሽ..
እንውጣ?” አለኝ ቦርሳውን እንስቶ እያነገተ፤
“ምነው ስታየኝ ያልጨረስኩ እመስላለሁ....?”
ያለ እቅዱ ነገረኛ ድምፄ ተመለሰ፡፡
“ደሞ ይሄ ምን ማለት ነው?”
“የለበስኩ አልመሰልኩም?... ለነገሩ ስታየኝ አይደል የምታውቀው በጠዋት
ቲቪ ላይ እያፈጠጠክ... ሦስተኛ ጡት አብቅዬ ባድርም እስከ ሁለት ወር የሚታይህ አይመስለኝም”
ሣቀ፡፡
እኔ ግን አልሣቅኩም፡፡ እየተጨቃጨቅን ሲስቅ ያናድደኛል።
“ሶስተኛ ጡት...? ምን?” አለኝ አሁንም እየሣቀ፡፡
👍1