#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ለቤት ወጪ እያልኩ ከምሰጣት ገንዘብ ላይ እያብቃቃች ልዩ ልዩ ተጨማሪ የማድ ቤት ቁሳቁሶች ገዛች፡፡ ዕቃዎቹ ሳይሆኑ ቁጠባዋ አስደሰተኝ።
የወዲያነሽ' ዛሬ የማድረው ወላጆቼ ቤት ነው፡፡ ስለዚህ እንዳትሠጊ ትፈሪያለሽ እንዴ?» ብያት በምሄድበት ጊዜ «ለእኔ ብለህ እኮ ተሠቃየህ ወይ አበሳህ» በማለት ራሷን ታማርራለች፡፡
ከዋል አደር የወህኒ ቤቱን ሕይወቷን እየረሳች አዲሱን ኑሮ ተላመደች::
ፈገግታዋ" ለዛና ጨዋታዋ ቀስ በቀስ ጎረፈ፡፡ እኔ ግን ወላጆቼ እንዳሰቡትና
እንደ ተመኙት ሳይሆን፣ ማንም ሳያውቅና ሳይሰማ፣ ጠላ ሳይጠመቅ፣ ጠጅና
ፍሪዳ ሳይጣል፣ ድንኳን ሳይተከል፣ ዕልልታና ሆታው ሳይቀልጥ፣ ጉልበት ስማ ሳልመረቅ፣ ከአንዱ የመከራ ጊዜ ጓደኛዬ በስተቀር ሚዜ ሳልመርጥና
ሳልመለምል፣ ሞላ ጎደለ ብዬ ሳልማስን፣ የእኔ ናት ብዬ ያመንኩባትንና ሕሊናዬ
ሙሉ በሙሉ የተቀበላትን የወዲያነሽን የኑሮ ጓደኛዪ ኣድርጌ ጎጆ ወጣሁ፡፡
ወደዱም ጠሉም የወዲያነሽ የሕይወቴ ምሰሶ ሆና በይፋ ብቅ የምትልበት ብሩህ
ቀን መምጣቱ አይቀርም፡፡
የተከራየነው የጉልላት አጎት ቤት አርጀትጀት ያለ በመሆኑ ግድግዳው
ላይ የተለጠፉት የአዲስ ዘመንና የሰንደቅ ዓላማችን ጋዜጦች ተገሽላልጠው ፀሐይ
እንዳጠቃው የሙዝ ቅጠል ዐልፎ ዐልፎ ተሽመልምለዋል። ምርጊቱ ላይ ተለጥፈው የተጋደሙት የጤፍ ጭዶች ይታያሉ፡፡ ያም ሆነ ይህ የወዲያነሽ
አብራኝ ስላለችና አብሬያት ስላለሁ ያለሁትና ያለችው በፍቅር ውብ እልፍኝ
ውስጥ ነው፡፡ ከፋ ሲለኝና ሐሳብ ሲያስጨንቀኝ ግን «የሕይወት ጥቀርሻ» ማለቴ አይቀረም፡፡
ምንጊዜም ቢሆን ጉልላትና የወዲያነሽ ባንድ ላይ ተቀምጠውም ሆነ ቆመው ሲያወሩ ደስ ይላሉ። የናቴ ልጅ እንኳ እንደ ጋሼ ጉልላት አይሆንልኝም፣ ጋሼ ጉልላት! ጋሼ ጉልላት ያንጀት ናቸው» ትላለች፡፡
ዓርብ ማታ ነበር፡፡ የወዲያነሽ ከተፈታች 17 ቀን ሆኗታል፡፡ ጉልላት ጀምሮልኝ የነበረውን ሐሳብ «ያም ሆነ ይህ ያለፈው ሁሉ ዐልፏል። የመጪውን ጊዜ ኑሮ ለማስተካከል ከባድ ጥረት ያስፈልጋል» አለና ዝም አለ። ዝም የማለትም
አመል አለበት። ይህን ተናግሮ እንደ ጨረሰ ሐሳቡን እያሰላሰልኩና እየሸነሸንኩ
በማሰብ በቆምኩባት መሬት ላይ የተተከልኩ ይመስል ውልፍት ሳልል ብዙ
ደቂቃዎች ቆየሁ፡፡ የሰበሰቡን አራት ማዕዘን አግዳሚ ዕንጨት እንደያዝኩ ትንሽ ቀና ብል ምሥራቃዊውን የበጋ ሰማይ ባዘቶ የሚመስል ደመና እዚህና እዚያ ጉች ጉች ብለውበታል። በውስጡ በሚከናወነው የአየር ግፊት ሜክንያት ደመናው ተለዋዋጭ ቅርፆች እየሰራ ወደ ምእራብ ተጓዘ።ደመናው ወደ ምእራብ በገሠገሠ ቁጥር የተለያየ ውበትና መጠን ያላቸው ከወክብት ወደ ምስራቅ የሚጓዙ ይመስላሉ ደመናው ጥርግ ብሎ ከሄደ በኋላ ግን እንደ ነባር አቀማመጣቸው በየነበሩበት ቀጥ ብለው ይቀራሉ።የእኔም ሐሳብ ይጓዝ ይክነፍ ይመጥቅ ይውዘገዘግና አንዲት ተራ የሐሳብ ድንበር ሳያገኝ ቀጥ ይላል።
የእናቱን ጡት እያነፈነፈ እንደሚፈልግ የውሻ ቡችላ ሐሳብ ሲያነፈፍ የቆየው ጉልላት እንግዲህ» ብሉ ንግግሩን ጀመር ሲያደርግ ወደ እርሱ መለስ ብዬ ማዳመጥ ጀመርኩ። በሕይወት ውስጥ ባሉት የኑሮ ጐዳናዎች በምትጓዝበት ጊዜ የሚያጋጥሙህን ፈተናዎችና ትግሎች ሁሉ ሳትሸሽና ሳታመነታ መታገል ይገባሃል፡፡ በዕንባዋ የሚረጥቡት ዐይኖቿ ያሳዝኑኛል፡፡ሥቃይዋ ይመረኛል' ማለት በቂ አይደለም፡፡ ማዘን ቢሉህ ማዘን አይምሰልህ።አንድ ምጽዋት ሰጪ ሃይማኖተኛ የሰማይ በር ያስከፍትልኛል ለሠራሁት ኃጢአት መደምሰሻ ይሆንልኛል ብሎ ለአንድ ለማኝ ቁራሽ ሲሰጥ ያዝናል፤ ያን በማድረጉ የራሱን የማይታይ ሥውር ጥቅም ጨመረ እንጂ ለማኙን ከራሱ
ጋር አላስተካከለውም፡፡ አድርግም ቢባል እሺ አይልም፡፡ አንተ ግን ከዚህ የተለየህ
ሁን። አሁን በምትኖርበት ኅብረተሰብ ውስጥ የመልካም ኑሮዋ ጀንበር
እንድትወጣና እንድትጠልቅ የምታደርጋት አንተ መሆንህን ዕወቅ።
«እኔም ራሲ ማን መሆኔን ለማወቅ የምችለውና ምግባሬን አሻግሬ
በማየት እኔነቴን ለማወቅ የምበቃው የአንተን የትግል አረማመድና ውጤት
እየተመለከትኩ ነው» ብሎ በእኔ ላይ ሙሉ እምነትና ተስፋ እንዳለው ለማረጋገጥ ረጋ ባለ ሁኔታ ምራቁን ውጦ ዝም እለ፡፡ እንደገና ከወደ ምሥራቅ የመጣው ደመና የከዋክብቱን ብርሃን እየጋረደው ሲሄድ አካባቢያችን ግራጫ ጨለማ አለበሰው።
በየወዲያነሽ ሕይወት ላይ የደረሰውን የመጥፎ ልማድ ውጤት ሁሉ በማስወገድ ሌላ አዲስ ትርጉምና ይዞታ እንዲያገኝ ለማድረግ የገባሁትን የተግባር ቃል አሳጥፈውም፡፡ መሸከም የሚገባኝን ቀንበር ከዛሬ ጀምሬ እሸከማለሁ፡፡ ሆኖም
ድል ማድረግ አለብህ ማለት ሳይሆን የሚጠብቀኝን ተቃውሞና የቤተሰብ መራር አንካሰላንትያ እንድታውቅልኝ ያስፈልጋል” አልኩና እንደ አዲስ ትክል የቤት ምሰሶ ቀጥ ብዬ ቆምኩ፡፡
ጉልላት ራሱን እየነቀነቀ ወደ ቤት ገባ፡፡ ተከትዬው ገባሁና አጠገቡ ተቀመጥኩ፡፡ የወዲያነሽ የጣደችው ሻይ እየተንተከተከ እንፋሎቱ አየር ውስጥ እየገባ ይዋጣል፡፡ እሷ እንገቷን ደፍታ በጎድጓዳ ሳህን ውስጥ የሻይ ስኒ ታጥባለች፡፡
አሮጊቷ ሠራተኛ ትንሽ ራቅ ብለው ጉልበታቸውን ኣቅፈው ያንጎላጃሉ፡፡
በጣም ጫን ሲላቸው ለሰስተኛ ንፋስ እንደምታወዛውዛት መቃ ወደ ጎን ወይንም ወደ ፊት ጠንቀስ ይሉና ደንገጥ ብለው ቀና ሲሉ ትናንሽ ዐይኖቻቸው ብልጭ ብለው ይከደናሉ፡፡ ሻዩ ተቀድቶ ቀረበልን፡፡
ጉልላት እንፋሎቱ እየተነነ የሚወጣውን ሻይ እየተመለከተ «እኔ እኮ የምልህ» ብሎ ንግግር ጀመረ የሁለታችን ጠንካራ ፍቅርና አንድነት ብዙ ነገር መጀመርና መፈጸም የሚችል መሆን አለበት፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ እብራችሁ
መታገልና የሚያጋጥማችሁ የጋራ መሰናክል ሁሉ ሽንጣችሁን ገትራችሁ
መቋቋም እንጂ መሽሽና ያላግባብ ማፈግፈግ የእናንተ ድርሻ መሆን የለበትም፡፡
በተለይም አንተ እሷን እያጠናከር ክና ሳትነጠል ለአዲስ ዘላቂ ግብ
የሚገሠግሥ እውነተኛ ዓላማ እንዳለሁ አሳይ። አንተ በኑሮህ እና በትምህርትህ
ምክንያት የተሻለ ዕውቀትና ችሎታ አለህ፡፡ ምሳሌዩ ቅር እንዳያሰኝህ እጂ
ቀላዋጭ የሚቀላውጠው የአስቀልዋጩን ያህል ስለሌለው ወይም በግልጽ በሥውር ስለ ተነጠቀ ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ አግዛት፣ አብራህ ትሠለፋለች::
ዓርማህን በፅናት ለመትከል ካልተጣጣርህና አካባቢህንም ለመለወጥ እምነትህን ካላስፋፋህ የጥንቱ ልማድ እንደ ክፉ አውሬ አሳዶ ይበላሃል። የበሰለ ሕሊና ያለው ሰው የምትሰኘውም ብዙዎችን ላስቸገረ ከባድ ጥያቄ መልስ ለማግኘት ስትል ከራስህ አልፈህ በተግባር የሚተባበሩህን መልካም ሰዎች በማፍራት ለዘላቂ መፍትሔ ስትታገል ነው፡፡ የዚህን የአሁኑን ሕይወት ቅርፅና ይዘት መለወጥ ያስፈልጋል። አሮጌውንና ለሕዝብ የማይጠቅመውን ነገር ሁሉ እያፈራረሱ በአዲስ የአኗኗር ስልት መተካት ይገባል፡፡ ግን አፈጻጸሙ እንደ አወራሩ ቀላል አይደለም» ብሎ በንግግሩ መኻል በረድ ያለችውን ሻይ መጠጣት ጀመረ፡፡
የወዲያነሽ ጉልላት ስለ እኔና ስለ እርሷ እንደ ተናገረ ስለ ገባት የመጨነቅ ሁኔታ ፊቷን ወረረው:: በስኒው ውስጥ የቀረችውን ሻይ ጨለጠና
የወዲያነሽን አሻግሮ እያየ «አንቺም ከእንግዲህ ወዲህ ነቃ ነቃ በይ! ይኸ ዐይን እስኪያብጥ እያለቀሱ አጉል መተከዝ በፍፁም አይጠቅማችሁም፡፡ ምንም እንኳ እንዳንቺ ወህኒ ቤት ገብተን ባንታሰርም እኛም ያንችኑ ያህል ከውጪ ሆነን ተሠቃይተናል። ሐሞትሽን ኮስተር አድርገሽ ለመታገል ከበረታሽ መልካሟ
የቤትሽ እመቤት አንቺ ብቻ ነሽ» ብሎ ጠበል እንዳልጠቀመው በሽተኛ ሻይ
እንዳስሞላለት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ለቤት ወጪ እያልኩ ከምሰጣት ገንዘብ ላይ እያብቃቃች ልዩ ልዩ ተጨማሪ የማድ ቤት ቁሳቁሶች ገዛች፡፡ ዕቃዎቹ ሳይሆኑ ቁጠባዋ አስደሰተኝ።
የወዲያነሽ' ዛሬ የማድረው ወላጆቼ ቤት ነው፡፡ ስለዚህ እንዳትሠጊ ትፈሪያለሽ እንዴ?» ብያት በምሄድበት ጊዜ «ለእኔ ብለህ እኮ ተሠቃየህ ወይ አበሳህ» በማለት ራሷን ታማርራለች፡፡
ከዋል አደር የወህኒ ቤቱን ሕይወቷን እየረሳች አዲሱን ኑሮ ተላመደች::
ፈገግታዋ" ለዛና ጨዋታዋ ቀስ በቀስ ጎረፈ፡፡ እኔ ግን ወላጆቼ እንዳሰቡትና
እንደ ተመኙት ሳይሆን፣ ማንም ሳያውቅና ሳይሰማ፣ ጠላ ሳይጠመቅ፣ ጠጅና
ፍሪዳ ሳይጣል፣ ድንኳን ሳይተከል፣ ዕልልታና ሆታው ሳይቀልጥ፣ ጉልበት ስማ ሳልመረቅ፣ ከአንዱ የመከራ ጊዜ ጓደኛዬ በስተቀር ሚዜ ሳልመርጥና
ሳልመለምል፣ ሞላ ጎደለ ብዬ ሳልማስን፣ የእኔ ናት ብዬ ያመንኩባትንና ሕሊናዬ
ሙሉ በሙሉ የተቀበላትን የወዲያነሽን የኑሮ ጓደኛዪ ኣድርጌ ጎጆ ወጣሁ፡፡
ወደዱም ጠሉም የወዲያነሽ የሕይወቴ ምሰሶ ሆና በይፋ ብቅ የምትልበት ብሩህ
ቀን መምጣቱ አይቀርም፡፡
የተከራየነው የጉልላት አጎት ቤት አርጀትጀት ያለ በመሆኑ ግድግዳው
ላይ የተለጠፉት የአዲስ ዘመንና የሰንደቅ ዓላማችን ጋዜጦች ተገሽላልጠው ፀሐይ
እንዳጠቃው የሙዝ ቅጠል ዐልፎ ዐልፎ ተሽመልምለዋል። ምርጊቱ ላይ ተለጥፈው የተጋደሙት የጤፍ ጭዶች ይታያሉ፡፡ ያም ሆነ ይህ የወዲያነሽ
አብራኝ ስላለችና አብሬያት ስላለሁ ያለሁትና ያለችው በፍቅር ውብ እልፍኝ
ውስጥ ነው፡፡ ከፋ ሲለኝና ሐሳብ ሲያስጨንቀኝ ግን «የሕይወት ጥቀርሻ» ማለቴ አይቀረም፡፡
ምንጊዜም ቢሆን ጉልላትና የወዲያነሽ ባንድ ላይ ተቀምጠውም ሆነ ቆመው ሲያወሩ ደስ ይላሉ። የናቴ ልጅ እንኳ እንደ ጋሼ ጉልላት አይሆንልኝም፣ ጋሼ ጉልላት! ጋሼ ጉልላት ያንጀት ናቸው» ትላለች፡፡
ዓርብ ማታ ነበር፡፡ የወዲያነሽ ከተፈታች 17 ቀን ሆኗታል፡፡ ጉልላት ጀምሮልኝ የነበረውን ሐሳብ «ያም ሆነ ይህ ያለፈው ሁሉ ዐልፏል። የመጪውን ጊዜ ኑሮ ለማስተካከል ከባድ ጥረት ያስፈልጋል» አለና ዝም አለ። ዝም የማለትም
አመል አለበት። ይህን ተናግሮ እንደ ጨረሰ ሐሳቡን እያሰላሰልኩና እየሸነሸንኩ
በማሰብ በቆምኩባት መሬት ላይ የተተከልኩ ይመስል ውልፍት ሳልል ብዙ
ደቂቃዎች ቆየሁ፡፡ የሰበሰቡን አራት ማዕዘን አግዳሚ ዕንጨት እንደያዝኩ ትንሽ ቀና ብል ምሥራቃዊውን የበጋ ሰማይ ባዘቶ የሚመስል ደመና እዚህና እዚያ ጉች ጉች ብለውበታል። በውስጡ በሚከናወነው የአየር ግፊት ሜክንያት ደመናው ተለዋዋጭ ቅርፆች እየሰራ ወደ ምእራብ ተጓዘ።ደመናው ወደ ምእራብ በገሠገሠ ቁጥር የተለያየ ውበትና መጠን ያላቸው ከወክብት ወደ ምስራቅ የሚጓዙ ይመስላሉ ደመናው ጥርግ ብሎ ከሄደ በኋላ ግን እንደ ነባር አቀማመጣቸው በየነበሩበት ቀጥ ብለው ይቀራሉ።የእኔም ሐሳብ ይጓዝ ይክነፍ ይመጥቅ ይውዘገዘግና አንዲት ተራ የሐሳብ ድንበር ሳያገኝ ቀጥ ይላል።
የእናቱን ጡት እያነፈነፈ እንደሚፈልግ የውሻ ቡችላ ሐሳብ ሲያነፈፍ የቆየው ጉልላት እንግዲህ» ብሉ ንግግሩን ጀመር ሲያደርግ ወደ እርሱ መለስ ብዬ ማዳመጥ ጀመርኩ። በሕይወት ውስጥ ባሉት የኑሮ ጐዳናዎች በምትጓዝበት ጊዜ የሚያጋጥሙህን ፈተናዎችና ትግሎች ሁሉ ሳትሸሽና ሳታመነታ መታገል ይገባሃል፡፡ በዕንባዋ የሚረጥቡት ዐይኖቿ ያሳዝኑኛል፡፡ሥቃይዋ ይመረኛል' ማለት በቂ አይደለም፡፡ ማዘን ቢሉህ ማዘን አይምሰልህ።አንድ ምጽዋት ሰጪ ሃይማኖተኛ የሰማይ በር ያስከፍትልኛል ለሠራሁት ኃጢአት መደምሰሻ ይሆንልኛል ብሎ ለአንድ ለማኝ ቁራሽ ሲሰጥ ያዝናል፤ ያን በማድረጉ የራሱን የማይታይ ሥውር ጥቅም ጨመረ እንጂ ለማኙን ከራሱ
ጋር አላስተካከለውም፡፡ አድርግም ቢባል እሺ አይልም፡፡ አንተ ግን ከዚህ የተለየህ
ሁን። አሁን በምትኖርበት ኅብረተሰብ ውስጥ የመልካም ኑሮዋ ጀንበር
እንድትወጣና እንድትጠልቅ የምታደርጋት አንተ መሆንህን ዕወቅ።
«እኔም ራሲ ማን መሆኔን ለማወቅ የምችለውና ምግባሬን አሻግሬ
በማየት እኔነቴን ለማወቅ የምበቃው የአንተን የትግል አረማመድና ውጤት
እየተመለከትኩ ነው» ብሎ በእኔ ላይ ሙሉ እምነትና ተስፋ እንዳለው ለማረጋገጥ ረጋ ባለ ሁኔታ ምራቁን ውጦ ዝም እለ፡፡ እንደገና ከወደ ምሥራቅ የመጣው ደመና የከዋክብቱን ብርሃን እየጋረደው ሲሄድ አካባቢያችን ግራጫ ጨለማ አለበሰው።
በየወዲያነሽ ሕይወት ላይ የደረሰውን የመጥፎ ልማድ ውጤት ሁሉ በማስወገድ ሌላ አዲስ ትርጉምና ይዞታ እንዲያገኝ ለማድረግ የገባሁትን የተግባር ቃል አሳጥፈውም፡፡ መሸከም የሚገባኝን ቀንበር ከዛሬ ጀምሬ እሸከማለሁ፡፡ ሆኖም
ድል ማድረግ አለብህ ማለት ሳይሆን የሚጠብቀኝን ተቃውሞና የቤተሰብ መራር አንካሰላንትያ እንድታውቅልኝ ያስፈልጋል” አልኩና እንደ አዲስ ትክል የቤት ምሰሶ ቀጥ ብዬ ቆምኩ፡፡
ጉልላት ራሱን እየነቀነቀ ወደ ቤት ገባ፡፡ ተከትዬው ገባሁና አጠገቡ ተቀመጥኩ፡፡ የወዲያነሽ የጣደችው ሻይ እየተንተከተከ እንፋሎቱ አየር ውስጥ እየገባ ይዋጣል፡፡ እሷ እንገቷን ደፍታ በጎድጓዳ ሳህን ውስጥ የሻይ ስኒ ታጥባለች፡፡
አሮጊቷ ሠራተኛ ትንሽ ራቅ ብለው ጉልበታቸውን ኣቅፈው ያንጎላጃሉ፡፡
በጣም ጫን ሲላቸው ለሰስተኛ ንፋስ እንደምታወዛውዛት መቃ ወደ ጎን ወይንም ወደ ፊት ጠንቀስ ይሉና ደንገጥ ብለው ቀና ሲሉ ትናንሽ ዐይኖቻቸው ብልጭ ብለው ይከደናሉ፡፡ ሻዩ ተቀድቶ ቀረበልን፡፡
ጉልላት እንፋሎቱ እየተነነ የሚወጣውን ሻይ እየተመለከተ «እኔ እኮ የምልህ» ብሎ ንግግር ጀመረ የሁለታችን ጠንካራ ፍቅርና አንድነት ብዙ ነገር መጀመርና መፈጸም የሚችል መሆን አለበት፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ እብራችሁ
መታገልና የሚያጋጥማችሁ የጋራ መሰናክል ሁሉ ሽንጣችሁን ገትራችሁ
መቋቋም እንጂ መሽሽና ያላግባብ ማፈግፈግ የእናንተ ድርሻ መሆን የለበትም፡፡
በተለይም አንተ እሷን እያጠናከር ክና ሳትነጠል ለአዲስ ዘላቂ ግብ
የሚገሠግሥ እውነተኛ ዓላማ እንዳለሁ አሳይ። አንተ በኑሮህ እና በትምህርትህ
ምክንያት የተሻለ ዕውቀትና ችሎታ አለህ፡፡ ምሳሌዩ ቅር እንዳያሰኝህ እጂ
ቀላዋጭ የሚቀላውጠው የአስቀልዋጩን ያህል ስለሌለው ወይም በግልጽ በሥውር ስለ ተነጠቀ ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ አግዛት፣ አብራህ ትሠለፋለች::
ዓርማህን በፅናት ለመትከል ካልተጣጣርህና አካባቢህንም ለመለወጥ እምነትህን ካላስፋፋህ የጥንቱ ልማድ እንደ ክፉ አውሬ አሳዶ ይበላሃል። የበሰለ ሕሊና ያለው ሰው የምትሰኘውም ብዙዎችን ላስቸገረ ከባድ ጥያቄ መልስ ለማግኘት ስትል ከራስህ አልፈህ በተግባር የሚተባበሩህን መልካም ሰዎች በማፍራት ለዘላቂ መፍትሔ ስትታገል ነው፡፡ የዚህን የአሁኑን ሕይወት ቅርፅና ይዘት መለወጥ ያስፈልጋል። አሮጌውንና ለሕዝብ የማይጠቅመውን ነገር ሁሉ እያፈራረሱ በአዲስ የአኗኗር ስልት መተካት ይገባል፡፡ ግን አፈጻጸሙ እንደ አወራሩ ቀላል አይደለም» ብሎ በንግግሩ መኻል በረድ ያለችውን ሻይ መጠጣት ጀመረ፡፡
የወዲያነሽ ጉልላት ስለ እኔና ስለ እርሷ እንደ ተናገረ ስለ ገባት የመጨነቅ ሁኔታ ፊቷን ወረረው:: በስኒው ውስጥ የቀረችውን ሻይ ጨለጠና
የወዲያነሽን አሻግሮ እያየ «አንቺም ከእንግዲህ ወዲህ ነቃ ነቃ በይ! ይኸ ዐይን እስኪያብጥ እያለቀሱ አጉል መተከዝ በፍፁም አይጠቅማችሁም፡፡ ምንም እንኳ እንዳንቺ ወህኒ ቤት ገብተን ባንታሰርም እኛም ያንችኑ ያህል ከውጪ ሆነን ተሠቃይተናል። ሐሞትሽን ኮስተር አድርገሽ ለመታገል ከበረታሽ መልካሟ
የቤትሽ እመቤት አንቺ ብቻ ነሽ» ብሎ ጠበል እንዳልጠቀመው በሽተኛ ሻይ
እንዳስሞላለት
👍4
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...በደሳሳዋ ጎጆ ውስጥ ከወዲያ ማዶ ጥጉን ይዞ ተቀምጧል። ጋቢውን
አፍንጫው ድረስ ተከናንቦ አረቄውን ይጨልጣል። የሚያውቀው ሰው
ድንገት መጥቶ እንዳያየው እየተጠራጠረ ዐይኑን ብቻ በጋቢው አልሽፈነም እንጂ ሁለመናው ጋቢ ለብሶ እሱነቱን ለማወቅ እጅግ አስቸጋሪ ነበር፡፡ ከፊት ለፊቱ የተገተረውን የአረቄ ጠርሙስ አንገት አሁንም አሁንም እያነቀ በብርጭቆው ውስጥ ከደፈቀው በኋላ እንደ ጠላ አናቱ
ድረስ እየሞላ ቁልቁል ያንደቀድቀዋል፡፡ ጎንቻ ቦሩ በሌብነት ያገኘውን ገንዘብ እንደ ልቡ እየተምነሸነሸበት ነው። የዐይኑ ሲሳይ ዓለሚቱ፥ የልቡ ትኩሳት ዓለሚቱ፣ የስሜቱ ረመጥ ዓለሚቱን በተስፋ እየተመኘ፣ ዐይን ዐይኖቿን በማየት ብቻ ርካታ እያገኘ ስለሚውል ከዚያች ቤት ጠፍቶ አያውቅም፡፡ በውርርድ ከዚያች ቤት አይታጣም። ዋ! የአይን ፍቅር ክፉ...
ጎንቻን ክፉኛ ለክፎት የጎጆዋ ጠባቂ የዓለሚቱ ፍቅር የቁም እስረኛ ሆኖ
ተተብትቧል።
ጎንቻ የቶላን ከብቶች ሰርቆ እጅ ከፍንጅ በመያዙ ከፍተኛ የውርደት ስሜት ተሰምቶታል።የዘረፋቸውን ከብቶች ሳይቸበችባቸው በመቅረቱ በቀል እና ቁጭት ሲያተክኑት ሰንብተዋል። የቶላ ሁኔታ እጅግ አድርጎ አንገብግቦታል፡፡ በህይወቱ ሙሉ የዚያን አይነቱ ክፉ ቅሌት ደርሶበት አያውቅም ነበረና ያንን በአደባባይ ያጋለጠውን፣ ለገበያ በወጣ ህዝብ መሀል የለበሰው ጋቢ በአየር ላይ ብን እስከሚል ድረስ እየወደቀ እየተነሳ እንዲፈረጥጥ ያደረገውን ሰው ለመበቀል ሌላ የወንጀል ጥንስስ ሌላ የውንብድና ስራ ለመፈፀም ተመኘ፡፡ ሌብነቱ የወለደውን ቅሌት ሌብነቱ ያስከተለበትን ውርደት ለማካካስ የሰው ህይወት ማጥፋትን የሰው ጉሮሮ ፈጥርቆ
የመግደል ምኞትን አሳደረበትና የበቀል ካራ በልቡ መሳል ጀመረ፡፡
ቶላ ንብረቱን ለማዳን፣ ትዳሩን ለመታደግና ባሳደጋቸው ከብቶቹ አንገት
ላይ ካራ እንዳይገባባቸው መሯሯጡ በጎንቻ ዘንድ ይቅር የማያስብል
ወንጀል ሆኖ ተገኘና ህይወቱን ሊቀጥፈው በሆዱ ማለ፡፡ ይህን በሚያስብበት ጊዜ ደግሞ የዓለሚቱ ነገር አለና ልቡ ለሁለት ተከፈለ።ግድያ ከፈፀመ አረቄ ቤት ሄዶ ዐይን ዐይኖቿን በማየት የአይን ፍቅሩን መወጣት አይችልምና ልቡ ፈራ። ዓለሚቱ በላይነህ ጠይም የሚያጓጓ መልክ እና ቁመና ያላት የአረቄ ሻጫ የወይዘሮ ባንችይደሩ ልጅ ስትሆን የሁለት ልጆች እናትና ባለትዳር ነች። ዓለሚቱ እናቷን በስራ ለመርዳት ምንጊዜም ከቤታቸው አትጠፋም፡፡ በተለይ መልከ ቀናነቷ የብዙ
ዎቹን ጠጪዎች አይን ስለሚስብ ለገበያቸው መድራት ዓለሚቱ አይነተኛ ምክንያት ነበረች፡፡ ጎንቻ ግን ይህንን ሁሉ አያውቅም ነበር፡፡ ባለትዳር መሆኗን ሳያውቅ በፍቅር ወደቀ፡፡ ያውም በህይወቱ ውስጥ የመጀመሪያው በሆነው የሴት ልጅ ፍቅር ጎንቻ በቶላ ከብቶች ስርቆት ላይ ተይዞ ከደነበረ ጊዜ ጀምሮ በፍፁም ያልቀናው ቢሆንም አረቄ የሚጠጣበት ገንዘብ ግን አላጣም፡፡ ጠዋትና ማታ ከዚያች አረቄ ቤት ውስጥ በመመሸግ በቋሚ ደንበኛነቱ የወይዘሮ ባንቺደሩን ልብ መማረክ ቻለ፡፡ ከዚያም
ዓለሚቱን ቀስ በቀስ እየቀረባት እየተላመዳት ሄደ። አንደበቱን እያፍታታ
የዐይን ፍቅር እስረኛነቱ ቀስ በቀስ እየለቀቀው ድፍረት እያገኘ ያጨዋውታት አልፎ አልፎም ይጋብዛት ጀመር፡፡ እናቷም ቋሚ ደምበኛቸው በመሆኑና ተጋባዦችን ይዞ እየመጣ ገበያቸውን ስላሟሟቀላቸው ለጎንቻ ልዩ አክብሮት እየሰጡት ሄዱ፡፡ በዚህም ምክንያት ዓለሚቱ ቀስ በቀስ ጎንቻን እየቀረበችው መጣች፡፡
ጎንቻ በውበቷ ተማርኮና በፍቅሯ ተለክፎ በመሰቃየት ላይ መሆኑን አላወቀችም ነበር፡፡ እየዋለ ሊያደር ግን ሁኔታዎች ግልፅ እየሆኑ መጡ። በሚያገኘው የስርቆሽ ገንዘብ ለዓለሚቱ ሽቶ፣ቅባት፣ ጌጣጌጥ እየገዛ በድብቅ በገፀበረከትነት ያቀርብላት ጀመር፡፡ ይህ ሁኔታ እየተደጋገመ ሲሄድ የጎንቻ ውለታ
እየከበዳት መጣ፡፡ ቀንና ለሊት ስለሱ ማስብ ጀመረች። ከዚያም ቀስ በቀስ በሱ ላይ መንደድ የጀመረው የፍቅር እሳት እሷንም ሊገርፋት ወላፈኑ በሷም ላይ ተሻግሮ ሊለበልባት እየዳዳው መሆኑ ታወቃት አረቄ ጠጥተው በሞቅታ ውስጥ መጎሻሸሙ፣መተሻሸቱ፣ መላፋቱ እየተዘወተረ ሄደ። ባሏ እርሻ ስለሚውል ዓለሚቱን እንደ ልቡ ለማጫወት
ተመቸው። ዓለሚቱ ባለትዳር መሆኗን
ፍቅሩን ሊያቀዘቅዘው እነደማይችል በመሀላ አረጋገጠላትና በስርቆሽ ለመቀማመስ ተፈቃቀዱ ከዚያም መዳራቱ መላፋቱ የደረጃ እድገቱን ጠበቀና በዚያው በእናቷ ጎጆ በጓዳ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ጨርቅ ለመጋፈፍ በቁ፡፡ ቀስ በቀስ እንቁላል በእግሩ ይሄዳል ነውና ቀስ በቀስ በስውር
በምስኪኑ ባሏ በገበየው ቆጥ ላይ እንደ ዶሮ መስፈር ጀመሩ።
ዓለሚቱ የስርቆሽ ቅምሻው የበለጠ እየጣፈጣት ሲመጣ ጎንቻም በጣፋጫ
ዓለሚቱ ልቡ ተሰወረች…ከዛ በኋላማ ምን ይጠየቃል? ጎንቻ አባወራ ቀረሽ ቅናት እና ፍቅር ያግለበልበው ጀመር፡፡ “የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ” እንዲሉ በፍቅር ከመቃጠሉ የተነሳ የሁለት ልጆች አባትና
የሰማንያ ባሏ ገበየሁ እያለ በዓላሚቱ የሚቀናው ጎንቻ፣ ለዓለሚቱ አሳቢው ጎንቻ፣ ስለዓለሚቱ አድራጊ ፈጣሪው ጎንቻ ሆነና አረፈው። ዓለሚቱም የጎንቻን ድንግልና ከወሰደች በኋላ ትኩስ ጉልበቱ አዲስ የጉርምስና ጠረኑ ቁመናው በልቧ እያደላ ፍቅሯን ለባሏ መሰሰት ጀመረች።
ያለወትሮዋ ንጭንጭ፣ ጭቅጭቅ አመጣች፡፡ ከገበየሁ ሰርቃ ፍቅርን
ለጎንቻ በገፍ መመገብ ጀመረች። ጎንቻም እየተሰረቀ የሚሰጠው ፍቅር ከሚገባው በላይ ጣፈጠውና ገበየሁን የፍቅሩ ተሻሚ አድርጎ መቁጠር ጀመረ። ፍቅሩን ለብቻው በመመገብ ብቻውን ለመጥገብ ፈለገ፡፡ ተስገበገበ፡፡ መቼም የሰው ልጅ በተፈጥሮ ራስ ወዳድ ነውና ጎንቻ ራሱን በጣም
ወደደ። ምርጥ ምርጡን ለግሉ ብቻ ተመኘ፡፡ ከገበየሁ አስበልጣ እንድትወደው ዓለሚቱን እያንበሸበሻት ልቧን እየሰለበው ሄደ፡፡ የሚገዛላት
የጆሮ ጉትቻ የእግር አልቦ የሱዳን ሽቶ ቀሚስ ለጉድ ሆነ፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው? ጌጣጌጡ ሽቶው ሁሉ በብዛት በእናቷ ሙዳይና በሳጥን ውስጥ ተቀምጦ እየዛገ እየተበላሸ ሄደ እንጂ ልታጌጥበት ልትደምቅበት አልቻለችም፡፡ ብታጌጥበት፣ ብታምርበት፣ብትታይበት ደግሞ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ ገመተች፡፡ ባሏ ገበየሁ “ከየት መጣ? እንዴት ሊሆን ቻለ?”
እያለ ሊጠይቅና ጥርጣሬ ውስጥ ሊገባ ነው፡፡ ስለዚህ ይሄንን እንድታምር፣ እንድታጌጥ፣ እንድትደምቅና እንድትሽቀረቀር ስትፈልግ ደንቃራ፣
ምቀኛ የሆነባትን ባሏን እየጠላችው መጣች። በዚህ ላይ ጎንቻ ችሮታው በገፍ ፍቅሩ በእጥፍ እየጨመረ በመሄድ ላይ ነበረና በገበየሁ የድህነት ትዳር ሰንሰለት የፊጥኝ ታስራ የኖረችበትን ጊዜ እያማረረች፣ የምትፈልገውን ማድረግ ባለመቻሏ ትዳሯን የበለጠ እየጠላች፣ ገበየሁን ከልቧ እያስወጣች በምትኩ ጎንቻን እያስገባች መሄዷን ቀጠለች ...
የገበየሁ ጣፋጭነት ወደ ምሬት ሊለወጥ ጎንቻ ወደር የሌለው ጣፋጭነቱንና የበላይነቱን እያረጋገጠ ሄደ።አዲስ እየተወደደ አሮጌው እየተጠላ ይሄዳልና ገበየሁ ተጠላና ጎንቻ ተወደደ። ለትዳሩ ቀን ከለሊት ደፋ ቀና የሚለው ጉዱን ያላወቀው ገበየሁ በጎንቻ በጥባጭነት ንፁህ ትዳሩ እየደፈረስ መጣ:: ባለቤቱ ያልተለመደውን ጭቅጭቋንና ንጭንጫን እያባባስችው ሄደች
“ስማ! ልጆቼን ብዬ በልጆቼ ታስሬ እንጂ ላንተ ገረድ ሆኜ የምቀመጥ ሴት አልነበርኩም! የፈለኩትን ለብሼ! በፈለኩት አጊጬ! ጓደኞቼን በልጬ
እንጂ ከጓደኞቼ በታች ሆኜ የምኖር ሰው እንዳልነበርኩ ማወቅ ይኖርብሀል!አንተ ግን ይሄ ሁሉ አይገባህም!” ይሄ የመረረ ንግግር ይሄ ታይቶ የማይታወቅ የሚስቱ ፀባይ መለወጥ ያሳሰበው ባል ሚስቱ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...በደሳሳዋ ጎጆ ውስጥ ከወዲያ ማዶ ጥጉን ይዞ ተቀምጧል። ጋቢውን
አፍንጫው ድረስ ተከናንቦ አረቄውን ይጨልጣል። የሚያውቀው ሰው
ድንገት መጥቶ እንዳያየው እየተጠራጠረ ዐይኑን ብቻ በጋቢው አልሽፈነም እንጂ ሁለመናው ጋቢ ለብሶ እሱነቱን ለማወቅ እጅግ አስቸጋሪ ነበር፡፡ ከፊት ለፊቱ የተገተረውን የአረቄ ጠርሙስ አንገት አሁንም አሁንም እያነቀ በብርጭቆው ውስጥ ከደፈቀው በኋላ እንደ ጠላ አናቱ
ድረስ እየሞላ ቁልቁል ያንደቀድቀዋል፡፡ ጎንቻ ቦሩ በሌብነት ያገኘውን ገንዘብ እንደ ልቡ እየተምነሸነሸበት ነው። የዐይኑ ሲሳይ ዓለሚቱ፥ የልቡ ትኩሳት ዓለሚቱ፣ የስሜቱ ረመጥ ዓለሚቱን በተስፋ እየተመኘ፣ ዐይን ዐይኖቿን በማየት ብቻ ርካታ እያገኘ ስለሚውል ከዚያች ቤት ጠፍቶ አያውቅም፡፡ በውርርድ ከዚያች ቤት አይታጣም። ዋ! የአይን ፍቅር ክፉ...
ጎንቻን ክፉኛ ለክፎት የጎጆዋ ጠባቂ የዓለሚቱ ፍቅር የቁም እስረኛ ሆኖ
ተተብትቧል።
ጎንቻ የቶላን ከብቶች ሰርቆ እጅ ከፍንጅ በመያዙ ከፍተኛ የውርደት ስሜት ተሰምቶታል።የዘረፋቸውን ከብቶች ሳይቸበችባቸው በመቅረቱ በቀል እና ቁጭት ሲያተክኑት ሰንብተዋል። የቶላ ሁኔታ እጅግ አድርጎ አንገብግቦታል፡፡ በህይወቱ ሙሉ የዚያን አይነቱ ክፉ ቅሌት ደርሶበት አያውቅም ነበረና ያንን በአደባባይ ያጋለጠውን፣ ለገበያ በወጣ ህዝብ መሀል የለበሰው ጋቢ በአየር ላይ ብን እስከሚል ድረስ እየወደቀ እየተነሳ እንዲፈረጥጥ ያደረገውን ሰው ለመበቀል ሌላ የወንጀል ጥንስስ ሌላ የውንብድና ስራ ለመፈፀም ተመኘ፡፡ ሌብነቱ የወለደውን ቅሌት ሌብነቱ ያስከተለበትን ውርደት ለማካካስ የሰው ህይወት ማጥፋትን የሰው ጉሮሮ ፈጥርቆ
የመግደል ምኞትን አሳደረበትና የበቀል ካራ በልቡ መሳል ጀመረ፡፡
ቶላ ንብረቱን ለማዳን፣ ትዳሩን ለመታደግና ባሳደጋቸው ከብቶቹ አንገት
ላይ ካራ እንዳይገባባቸው መሯሯጡ በጎንቻ ዘንድ ይቅር የማያስብል
ወንጀል ሆኖ ተገኘና ህይወቱን ሊቀጥፈው በሆዱ ማለ፡፡ ይህን በሚያስብበት ጊዜ ደግሞ የዓለሚቱ ነገር አለና ልቡ ለሁለት ተከፈለ።ግድያ ከፈፀመ አረቄ ቤት ሄዶ ዐይን ዐይኖቿን በማየት የአይን ፍቅሩን መወጣት አይችልምና ልቡ ፈራ። ዓለሚቱ በላይነህ ጠይም የሚያጓጓ መልክ እና ቁመና ያላት የአረቄ ሻጫ የወይዘሮ ባንችይደሩ ልጅ ስትሆን የሁለት ልጆች እናትና ባለትዳር ነች። ዓለሚቱ እናቷን በስራ ለመርዳት ምንጊዜም ከቤታቸው አትጠፋም፡፡ በተለይ መልከ ቀናነቷ የብዙ
ዎቹን ጠጪዎች አይን ስለሚስብ ለገበያቸው መድራት ዓለሚቱ አይነተኛ ምክንያት ነበረች፡፡ ጎንቻ ግን ይህንን ሁሉ አያውቅም ነበር፡፡ ባለትዳር መሆኗን ሳያውቅ በፍቅር ወደቀ፡፡ ያውም በህይወቱ ውስጥ የመጀመሪያው በሆነው የሴት ልጅ ፍቅር ጎንቻ በቶላ ከብቶች ስርቆት ላይ ተይዞ ከደነበረ ጊዜ ጀምሮ በፍፁም ያልቀናው ቢሆንም አረቄ የሚጠጣበት ገንዘብ ግን አላጣም፡፡ ጠዋትና ማታ ከዚያች አረቄ ቤት ውስጥ በመመሸግ በቋሚ ደንበኛነቱ የወይዘሮ ባንቺደሩን ልብ መማረክ ቻለ፡፡ ከዚያም
ዓለሚቱን ቀስ በቀስ እየቀረባት እየተላመዳት ሄደ። አንደበቱን እያፍታታ
የዐይን ፍቅር እስረኛነቱ ቀስ በቀስ እየለቀቀው ድፍረት እያገኘ ያጨዋውታት አልፎ አልፎም ይጋብዛት ጀመር፡፡ እናቷም ቋሚ ደምበኛቸው በመሆኑና ተጋባዦችን ይዞ እየመጣ ገበያቸውን ስላሟሟቀላቸው ለጎንቻ ልዩ አክብሮት እየሰጡት ሄዱ፡፡ በዚህም ምክንያት ዓለሚቱ ቀስ በቀስ ጎንቻን እየቀረበችው መጣች፡፡
ጎንቻ በውበቷ ተማርኮና በፍቅሯ ተለክፎ በመሰቃየት ላይ መሆኑን አላወቀችም ነበር፡፡ እየዋለ ሊያደር ግን ሁኔታዎች ግልፅ እየሆኑ መጡ። በሚያገኘው የስርቆሽ ገንዘብ ለዓለሚቱ ሽቶ፣ቅባት፣ ጌጣጌጥ እየገዛ በድብቅ በገፀበረከትነት ያቀርብላት ጀመር፡፡ ይህ ሁኔታ እየተደጋገመ ሲሄድ የጎንቻ ውለታ
እየከበዳት መጣ፡፡ ቀንና ለሊት ስለሱ ማስብ ጀመረች። ከዚያም ቀስ በቀስ በሱ ላይ መንደድ የጀመረው የፍቅር እሳት እሷንም ሊገርፋት ወላፈኑ በሷም ላይ ተሻግሮ ሊለበልባት እየዳዳው መሆኑ ታወቃት አረቄ ጠጥተው በሞቅታ ውስጥ መጎሻሸሙ፣መተሻሸቱ፣ መላፋቱ እየተዘወተረ ሄደ። ባሏ እርሻ ስለሚውል ዓለሚቱን እንደ ልቡ ለማጫወት
ተመቸው። ዓለሚቱ ባለትዳር መሆኗን
ፍቅሩን ሊያቀዘቅዘው እነደማይችል በመሀላ አረጋገጠላትና በስርቆሽ ለመቀማመስ ተፈቃቀዱ ከዚያም መዳራቱ መላፋቱ የደረጃ እድገቱን ጠበቀና በዚያው በእናቷ ጎጆ በጓዳ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ጨርቅ ለመጋፈፍ በቁ፡፡ ቀስ በቀስ እንቁላል በእግሩ ይሄዳል ነውና ቀስ በቀስ በስውር
በምስኪኑ ባሏ በገበየው ቆጥ ላይ እንደ ዶሮ መስፈር ጀመሩ።
ዓለሚቱ የስርቆሽ ቅምሻው የበለጠ እየጣፈጣት ሲመጣ ጎንቻም በጣፋጫ
ዓለሚቱ ልቡ ተሰወረች…ከዛ በኋላማ ምን ይጠየቃል? ጎንቻ አባወራ ቀረሽ ቅናት እና ፍቅር ያግለበልበው ጀመር፡፡ “የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ” እንዲሉ በፍቅር ከመቃጠሉ የተነሳ የሁለት ልጆች አባትና
የሰማንያ ባሏ ገበየሁ እያለ በዓላሚቱ የሚቀናው ጎንቻ፣ ለዓለሚቱ አሳቢው ጎንቻ፣ ስለዓለሚቱ አድራጊ ፈጣሪው ጎንቻ ሆነና አረፈው። ዓለሚቱም የጎንቻን ድንግልና ከወሰደች በኋላ ትኩስ ጉልበቱ አዲስ የጉርምስና ጠረኑ ቁመናው በልቧ እያደላ ፍቅሯን ለባሏ መሰሰት ጀመረች።
ያለወትሮዋ ንጭንጭ፣ ጭቅጭቅ አመጣች፡፡ ከገበየሁ ሰርቃ ፍቅርን
ለጎንቻ በገፍ መመገብ ጀመረች። ጎንቻም እየተሰረቀ የሚሰጠው ፍቅር ከሚገባው በላይ ጣፈጠውና ገበየሁን የፍቅሩ ተሻሚ አድርጎ መቁጠር ጀመረ። ፍቅሩን ለብቻው በመመገብ ብቻውን ለመጥገብ ፈለገ፡፡ ተስገበገበ፡፡ መቼም የሰው ልጅ በተፈጥሮ ራስ ወዳድ ነውና ጎንቻ ራሱን በጣም
ወደደ። ምርጥ ምርጡን ለግሉ ብቻ ተመኘ፡፡ ከገበየሁ አስበልጣ እንድትወደው ዓለሚቱን እያንበሸበሻት ልቧን እየሰለበው ሄደ፡፡ የሚገዛላት
የጆሮ ጉትቻ የእግር አልቦ የሱዳን ሽቶ ቀሚስ ለጉድ ሆነ፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው? ጌጣጌጡ ሽቶው ሁሉ በብዛት በእናቷ ሙዳይና በሳጥን ውስጥ ተቀምጦ እየዛገ እየተበላሸ ሄደ እንጂ ልታጌጥበት ልትደምቅበት አልቻለችም፡፡ ብታጌጥበት፣ ብታምርበት፣ብትታይበት ደግሞ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ ገመተች፡፡ ባሏ ገበየሁ “ከየት መጣ? እንዴት ሊሆን ቻለ?”
እያለ ሊጠይቅና ጥርጣሬ ውስጥ ሊገባ ነው፡፡ ስለዚህ ይሄንን እንድታምር፣ እንድታጌጥ፣ እንድትደምቅና እንድትሽቀረቀር ስትፈልግ ደንቃራ፣
ምቀኛ የሆነባትን ባሏን እየጠላችው መጣች። በዚህ ላይ ጎንቻ ችሮታው በገፍ ፍቅሩ በእጥፍ እየጨመረ በመሄድ ላይ ነበረና በገበየሁ የድህነት ትዳር ሰንሰለት የፊጥኝ ታስራ የኖረችበትን ጊዜ እያማረረች፣ የምትፈልገውን ማድረግ ባለመቻሏ ትዳሯን የበለጠ እየጠላች፣ ገበየሁን ከልቧ እያስወጣች በምትኩ ጎንቻን እያስገባች መሄዷን ቀጠለች ...
የገበየሁ ጣፋጭነት ወደ ምሬት ሊለወጥ ጎንቻ ወደር የሌለው ጣፋጭነቱንና የበላይነቱን እያረጋገጠ ሄደ።አዲስ እየተወደደ አሮጌው እየተጠላ ይሄዳልና ገበየሁ ተጠላና ጎንቻ ተወደደ። ለትዳሩ ቀን ከለሊት ደፋ ቀና የሚለው ጉዱን ያላወቀው ገበየሁ በጎንቻ በጥባጭነት ንፁህ ትዳሩ እየደፈረስ መጣ:: ባለቤቱ ያልተለመደውን ጭቅጭቋንና ንጭንጫን እያባባስችው ሄደች
“ስማ! ልጆቼን ብዬ በልጆቼ ታስሬ እንጂ ላንተ ገረድ ሆኜ የምቀመጥ ሴት አልነበርኩም! የፈለኩትን ለብሼ! በፈለኩት አጊጬ! ጓደኞቼን በልጬ
እንጂ ከጓደኞቼ በታች ሆኜ የምኖር ሰው እንዳልነበርኩ ማወቅ ይኖርብሀል!አንተ ግን ይሄ ሁሉ አይገባህም!” ይሄ የመረረ ንግግር ይሄ ታይቶ የማይታወቅ የሚስቱ ፀባይ መለወጥ ያሳሰበው ባል ሚስቱ
👍5
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ባርናባስ የሔዋንን ሁለት እጆች ግጥም እድርጎ ይዟል። ሸዋዬ የአገኘችውን ነገር ሁሉ እያነሳች ትደበድባታለች። ሔዋን ኡኡ ድረሱልኝ እያለች ትጮሀለች።
እጆቿን ከባርናባስ ለማስለቀቅ ትታገላለች። እሱ ደግሞ እንዳታመልጠው ጥርሱን
ንክስ እያረገ ሀይሉን ያጠነክራል። ሸዋዬ አሁንም ትደበድባታለች፡፡ ሔዋንም ትጮሀለች፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን በርካታ ሰው ዙሪያውን ከብቦ ይመለከታል። ግን
“ማንም ሊገላግል አያስብም፡፡ አስቻለው ሊገላግል እየፈለግን ደግሞ መሮጥ ያቅተዋል። ይለፋል ግን አይችልም፡፡ ከያዘው ነገር ራሱን እንድምንም አላቅቆ ወደ
ድብድቡ ቦታ ሊሮጥ ሲል ድንገት ከእንቅልፉ ብንን አለ፡፡ «በስመ አብ ወወልድ መንፈስ ቅዱስ..." ብሎ ከተንጋለለበት ቀና በማለት ፊቱን በሁለት እጆቹ ሽፍን አድርጎ ወደ ፊት ወደ እግሮቹ ድፍት አለ ዝግንን አለው ደርጊቱን ያየው
በቅዠት እንዳልሆነ ሁሉ ሔዋን አሁንም በዚያው ሁኔታ ውስጥ
ሆና ትታየው ጀመር። አሳዘነችው። ከዚያ በኋላ መተኛት አልፈለገም
ከአልጋው ላይ ፈጠን ብሎ ወረደና ልብሱን ለባበሰ።
ምን ሊያግርን እንደሆነ ሳይታወቀው በቀጥታ ወደ ሸዋዬ ቤት መሄድ ፈለገ። ቤቱን ቆለፈና ከግቢ ወጥቶ ቁልቅል ወደሸዋዬ ቤት አቅጣጫ ወረደ ልክ በሸዋዬ ቤት አቅጣጫ ስምንተኛ መንገድ ላይ ሲደርስ መንገድ ላይ ቀጥ ብሎ ቆመና በቀኝ አቅጣጫ ያለውን የወይዘሮ ዘነቡን ግቢ በርቀት ይመለከተው ጀመር በሀሳቡ ሸዋዬ ቤት ገባ ሸዋዬንና በርናባስ ፍራሽ ላይ ቁጭ ብለው
ጫት ሲቅሙ ሔዋን ደሞ በከሰል
ላይ ጀበና ጥዳ የሁለቱ ብና አፋይ ሆና ሁሉም በአንድ ላይ እንደ ስዕል ታዩት።ልቡ ወደዚያው ቤት ሂድ ሂድ አለው። ነገር ግን ድንገት ዘው ቢል ሊፈጠር የሚችለው ሁኔታ ታየው፡፡ ከሁሉም በላይ ሔዋን ትሳቀቅበታለች !
በዚያ ምትክ ከንፈሩን ንክስ አድርጎ ራሱን በቁጭት ወዘወዘ።
በዚሁ ሁኔታ ጥቂት ቆየና ሳይወድ በግድ ሃሳቡን ለወጠ፡፡ በቃ ወደ ሸዋዩ ቤት መግባት አልፈለገም፡፡ ግን ደግሞ ወዴት እንደሚሄድ ጨነቀው ቤቱም ሰለቸው ወደ አንድ ቡና ቤት አይሄድ ነገር እዚያ ሄዶ የሚገጥመው ነገር ለመንፈሱ
አይመቸውም። ግራ ሲገባው ቁልቁል ወደ ከተማዋ ዳርቻ ይራመድ ጀመር ቁርጥ ያለ አድራሻ የለውም። ብቻ መሄድ ብቻ መራመድ፡፡ ብሎ ብሎ ከከተማው ወጣና ወደ እሮሬሳ ገበሬ ማህበር አዋሳኝ ላይ ደረሰ።እያደር ደግሞ
የገጠሩ ሽታ አማለለው፡፡ አሁንም ወደፊት ሊራመድ መሰነና ርምጃውን ቀጠለ። በዚያ መንገድ ላይ በርካታ የገጠር ነዋሪዎች ወደ ከተማ ያመራሉ።ከከተማ ወደ ገጠር ይሄዳሉ፡፡ አስቻለውም ርምጃውን ዝም ብሎ ወደ ፊት ቀጠለ፡፡በልቡ ግን አንድ ነገር ያስላስሳል ዐወደፊት ሐምሌ ላይ የሚጠብቀውን ዝውውርና
ከሔዋን ጋር ስለሚኖረው ግንኙነት። 'ለመሆኑ' ይላል በሀሳቡ። ብዛወር የሐዩ ጉዳይ እንዴት ሊሆን ነው? ይዢያት ልሄድ ወይስ ትቻት? ይልና እንደገና
የታፈሡና የበልሁ ወደ ክብረ መንግስት የመሄድ ዕቅድ ይመጣበታል። ሄደውስ
ይሳካላቸው ይሆን? ወይስ የሔዩ እናትና አባት ሽዋዬ በፃፈችላቸው ደብዳቤ ምክንያት ሁኔታው አስግቷቸው ያንገራግሩ ይሆን እሺ ቢሉም ሰርግ ድግስ ምናምን ሊሉ ይችላሉ። ያ እስከሚሆን ጊዜ ይፈጃል፡፡ ዞሮ ዞሮ ላልተወሰነ ጊዜ
ከሒዩ ጋር መራራቀ አይቀርም፡፡» በማለት ራሱን እንደማረጋጋት አይነት እንግዲህ የሆነው ይሁን ብቻ ሰላምና ጤና ትሁንልኝ፡፡» እያለ አምላኩን ይማፀናል፡፡
ሳያውቀው ብዙ ተጉዟል በለየለት ገጠር ውስጥ ገብቶ ከዲላ ከተማ በግምት ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ርቋል። ከሀሳቡ ብንን በማለት ባለበት ቦታ ላይ ቆሞ ዓይኑን ወደ ቀኝ አቅጣጫ ጣል ሲያደርግ ዙሪያዋን በረጃጅም ዛፎች
የቸከበበችና፣ ሰፋ ያለች ደስ የምትል ገላጣ ሜዳ ታየችው፡፡ ከግጦሽ ከፍ ያለ የእድገት ደረጃ ላይ በደረሰ ለምለም ሳር ተሸፍናለች። በውስጧ አልፎ አልፎ
የደረቁ ጉቶዎች ጉብ ጉብ ብለው ይታያሉ፡ ወደዚያው ታጠፈና ሜዳዋ መሀል ገብቶ ከአንድ ጉቶ ላይ ቁጭ አለ፡፡ ዙሪያውን ሲመለከት ጥቅጥቅ ያለ ጫካ ነው፡፡ ዛፎች ደግሞ ረጃጅም፡ ወደ መሬት ሲያይ ያ ለምለም ሳር፡፡ በአፍንጫው የሚገባው አየር በራሱ የተለየ መዓዛ ያለው፡፡ መንፈስ የሚያድስ፡፡ እጆቹን በደረቱ ላይ አቆላልፎ ወደ ዛፎቹ ሲያይ ከአንዱ ወደ ሌላው እየተዘዋወሩ የሚንጫጬ ወፎች
ቀልቡን ሳቡት ከወፎቹ የጫጫታ ድግግሞሽ የተነሳ የወፍ ድምፅ ፂው ስትል ሲኮንድ አታልፍም:: የድምጻቸው ልዩነት ውበትና ህበሩ በጭንቅ በጥበብ ከተቀመረ
ዘመናዊ ሙዚቃ የበለጠ ስሜት ይማርካል፡፡
«እናንት ወፎች» አለ አስቻለው ሁኔታቸው ሁለ ግርም ብሎት፡፡ ዛፋ ሁሉ የሁላችሁ ለኔ ብቻ ባይ ስግብግብ በመሀላችሁ የለም
አዛዥ የላችሁ ገልማጭ ጠላት የላችሁ ምቀኛ ኑሮአችሁ በራሳችሁ፣ ውሸት አታውቁ ቅጥፈት ክፉ አቶለሙ ክፉ አትናገሩ አትቀየሙ አታስቀይሙ ጨኸታችሁ አይገደብ ጫጫታችሁ አይመዘገብ ቂም አታውቁ በቀል፤ በእናንተ ዘንድ ዛቻ የለ
ማስፈራራት፤ ፍርሀት የለ ጭንቀት፣ በዚች ምድር ሰላም ልትኖሩ የተፈጠራችሁ ሰላማዊ ፍጡሮች! በማለት ብቻውን ሲነጋገር ከቆየ በኋሳ ሀሳቡን ወደ ሰው ልጅ ባህሪና አኗኗር መለስ ሲያደርገው ጭራሽ አስጠላው።
«ያልታደለ ፍጡር»አለ በስጨት ባለ አነጋገር፡፡ ታየው የሰው ልጅ
ክፋቱና ተንኮሉ፣ ቂምና በቀሉ፣ ሸርና ምቀኝነቱ፤ ጠበና ጭቅጭቁ፣ ከሁሉም በላይ
እብሪቱና ጭካኔው፡ በቃሉም ይገልፀው ጀመር «የአሳር ሽክም የተጫነ መከረኛ ፍጡር፥ ሰው! የቱንም ያህል ቢማር ቢመራመር ከራሱ ጋር መታረቅ ያቃተው
ደካማ ፍጡር፡ ሰው ፈጣሪው ራሱ እሱን በመፍጠሩ የተፀፀተበት ብቸኛ እንስሳ ሰው!» ካለ በኋላ ራሱን ወዝወዝ አድርጎ ወደ መሬት ጎንበስ አለና ያን የለመለመ
ሳር ልብ ብሎ ይመለከተው ጀመር፡፡ ከሩቅ ሲያዩት ልምላሜ ያምራል:: ስሩ ሲታይ ግን ብዙ ጥቃንጥት አለበት፡፡ የደረቁ ቅጠሎችና ጭራሮዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ በርካታ ነገሮች ስር ስሩን ትብትብ እድርገው ይዘውታል። ይህ ሁኔታ ሔዋንን አስታወየው፡፡
«አንተ ለምለም ሳርና የኔዋ ሔዋን እንድ ናቸሁ፡ ከሩቅ ሲያዩአቸሁ ውብ ናችሁ:: ፍጹም የደላችሁ ትመስላላችሁ፡፡ ሥር ሥራችሁንና ውስጥ ውስጣችሁን ግን ብዙ ችግር አለባችሁ፡፡ ሳትጠሩት የመጣባችሁ፣ ሳትፈልጉት የተዳበላችሁ፡፡ አቁሳይ ጥገኛ አለባችሁ፡፡ አንተን የጭራሮና የቅጠል ርጋፊዎች ስርህን ተብትበው እንደ ያዘህ ሁሉ የኔዋ ሔዋንም የአፈቀረ ልቧን የሚወ,ጋ የስሜት እሾህ ኣለባት፡፡
ለመውደድና ለመወደድ የተፈጠረች ቆንጆ ነበረች:: ግን እሾሁ ጋሬጣው በዛባትና
መንፈሷ ቆሰለ፡፡ በአፈቀረች ተሰቃየች። ማልቀስና መተከዝ ዕጣ ፋንታዋ ሆነ።
እያለ ሲያስብ በዚያው ያ ቅዠት ውስጥ ያየው ሁኔታ ትዝ አለው፡፡ ድንግጥ ብሎ እንደ መደንበር አረገና በተቀመጠበት ጉቶ ላይ ብድግ አለ ሳያስበው በዚያ
በለመለመ ሳር ላያ ይዘዋወር ጀመር፡፡
እጆቹን በጀርባው ላይ አጣምሮ ጎንበስ በማለት በግምት ከአስር: እስከ አስራ አምስት ርምጃዎችን ከተራመደ በኋላ በግራ በኩል ወደ መንገዱ ዞር ብሎ ሲያይ አንድ ለየት ያለ ነገር አየ፡፡ በመንገዱ ላይ ሰዎች አሁንም ወደ ላይ ወደ ታችም አቅጣጫ ይሄዳሉ፡፡ ነገር ግን መንገደኛ፣ ለየት ባለ እኳኋን አንዲት በጀርባዋ ጓዝ የያዘች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ባርናባስ የሔዋንን ሁለት እጆች ግጥም እድርጎ ይዟል። ሸዋዬ የአገኘችውን ነገር ሁሉ እያነሳች ትደበድባታለች። ሔዋን ኡኡ ድረሱልኝ እያለች ትጮሀለች።
እጆቿን ከባርናባስ ለማስለቀቅ ትታገላለች። እሱ ደግሞ እንዳታመልጠው ጥርሱን
ንክስ እያረገ ሀይሉን ያጠነክራል። ሸዋዬ አሁንም ትደበድባታለች፡፡ ሔዋንም ትጮሀለች፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን በርካታ ሰው ዙሪያውን ከብቦ ይመለከታል። ግን
“ማንም ሊገላግል አያስብም፡፡ አስቻለው ሊገላግል እየፈለግን ደግሞ መሮጥ ያቅተዋል። ይለፋል ግን አይችልም፡፡ ከያዘው ነገር ራሱን እንድምንም አላቅቆ ወደ
ድብድቡ ቦታ ሊሮጥ ሲል ድንገት ከእንቅልፉ ብንን አለ፡፡ «በስመ አብ ወወልድ መንፈስ ቅዱስ..." ብሎ ከተንጋለለበት ቀና በማለት ፊቱን በሁለት እጆቹ ሽፍን አድርጎ ወደ ፊት ወደ እግሮቹ ድፍት አለ ዝግንን አለው ደርጊቱን ያየው
በቅዠት እንዳልሆነ ሁሉ ሔዋን አሁንም በዚያው ሁኔታ ውስጥ
ሆና ትታየው ጀመር። አሳዘነችው። ከዚያ በኋላ መተኛት አልፈለገም
ከአልጋው ላይ ፈጠን ብሎ ወረደና ልብሱን ለባበሰ።
ምን ሊያግርን እንደሆነ ሳይታወቀው በቀጥታ ወደ ሸዋዬ ቤት መሄድ ፈለገ። ቤቱን ቆለፈና ከግቢ ወጥቶ ቁልቅል ወደሸዋዬ ቤት አቅጣጫ ወረደ ልክ በሸዋዬ ቤት አቅጣጫ ስምንተኛ መንገድ ላይ ሲደርስ መንገድ ላይ ቀጥ ብሎ ቆመና በቀኝ አቅጣጫ ያለውን የወይዘሮ ዘነቡን ግቢ በርቀት ይመለከተው ጀመር በሀሳቡ ሸዋዬ ቤት ገባ ሸዋዬንና በርናባስ ፍራሽ ላይ ቁጭ ብለው
ጫት ሲቅሙ ሔዋን ደሞ በከሰል
ላይ ጀበና ጥዳ የሁለቱ ብና አፋይ ሆና ሁሉም በአንድ ላይ እንደ ስዕል ታዩት።ልቡ ወደዚያው ቤት ሂድ ሂድ አለው። ነገር ግን ድንገት ዘው ቢል ሊፈጠር የሚችለው ሁኔታ ታየው፡፡ ከሁሉም በላይ ሔዋን ትሳቀቅበታለች !
በዚያ ምትክ ከንፈሩን ንክስ አድርጎ ራሱን በቁጭት ወዘወዘ።
በዚሁ ሁኔታ ጥቂት ቆየና ሳይወድ በግድ ሃሳቡን ለወጠ፡፡ በቃ ወደ ሸዋዩ ቤት መግባት አልፈለገም፡፡ ግን ደግሞ ወዴት እንደሚሄድ ጨነቀው ቤቱም ሰለቸው ወደ አንድ ቡና ቤት አይሄድ ነገር እዚያ ሄዶ የሚገጥመው ነገር ለመንፈሱ
አይመቸውም። ግራ ሲገባው ቁልቁል ወደ ከተማዋ ዳርቻ ይራመድ ጀመር ቁርጥ ያለ አድራሻ የለውም። ብቻ መሄድ ብቻ መራመድ፡፡ ብሎ ብሎ ከከተማው ወጣና ወደ እሮሬሳ ገበሬ ማህበር አዋሳኝ ላይ ደረሰ።እያደር ደግሞ
የገጠሩ ሽታ አማለለው፡፡ አሁንም ወደፊት ሊራመድ መሰነና ርምጃውን ቀጠለ። በዚያ መንገድ ላይ በርካታ የገጠር ነዋሪዎች ወደ ከተማ ያመራሉ።ከከተማ ወደ ገጠር ይሄዳሉ፡፡ አስቻለውም ርምጃውን ዝም ብሎ ወደ ፊት ቀጠለ፡፡በልቡ ግን አንድ ነገር ያስላስሳል ዐወደፊት ሐምሌ ላይ የሚጠብቀውን ዝውውርና
ከሔዋን ጋር ስለሚኖረው ግንኙነት። 'ለመሆኑ' ይላል በሀሳቡ። ብዛወር የሐዩ ጉዳይ እንዴት ሊሆን ነው? ይዢያት ልሄድ ወይስ ትቻት? ይልና እንደገና
የታፈሡና የበልሁ ወደ ክብረ መንግስት የመሄድ ዕቅድ ይመጣበታል። ሄደውስ
ይሳካላቸው ይሆን? ወይስ የሔዩ እናትና አባት ሽዋዬ በፃፈችላቸው ደብዳቤ ምክንያት ሁኔታው አስግቷቸው ያንገራግሩ ይሆን እሺ ቢሉም ሰርግ ድግስ ምናምን ሊሉ ይችላሉ። ያ እስከሚሆን ጊዜ ይፈጃል፡፡ ዞሮ ዞሮ ላልተወሰነ ጊዜ
ከሒዩ ጋር መራራቀ አይቀርም፡፡» በማለት ራሱን እንደማረጋጋት አይነት እንግዲህ የሆነው ይሁን ብቻ ሰላምና ጤና ትሁንልኝ፡፡» እያለ አምላኩን ይማፀናል፡፡
ሳያውቀው ብዙ ተጉዟል በለየለት ገጠር ውስጥ ገብቶ ከዲላ ከተማ በግምት ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ርቋል። ከሀሳቡ ብንን በማለት ባለበት ቦታ ላይ ቆሞ ዓይኑን ወደ ቀኝ አቅጣጫ ጣል ሲያደርግ ዙሪያዋን በረጃጅም ዛፎች
የቸከበበችና፣ ሰፋ ያለች ደስ የምትል ገላጣ ሜዳ ታየችው፡፡ ከግጦሽ ከፍ ያለ የእድገት ደረጃ ላይ በደረሰ ለምለም ሳር ተሸፍናለች። በውስጧ አልፎ አልፎ
የደረቁ ጉቶዎች ጉብ ጉብ ብለው ይታያሉ፡ ወደዚያው ታጠፈና ሜዳዋ መሀል ገብቶ ከአንድ ጉቶ ላይ ቁጭ አለ፡፡ ዙሪያውን ሲመለከት ጥቅጥቅ ያለ ጫካ ነው፡፡ ዛፎች ደግሞ ረጃጅም፡ ወደ መሬት ሲያይ ያ ለምለም ሳር፡፡ በአፍንጫው የሚገባው አየር በራሱ የተለየ መዓዛ ያለው፡፡ መንፈስ የሚያድስ፡፡ እጆቹን በደረቱ ላይ አቆላልፎ ወደ ዛፎቹ ሲያይ ከአንዱ ወደ ሌላው እየተዘዋወሩ የሚንጫጬ ወፎች
ቀልቡን ሳቡት ከወፎቹ የጫጫታ ድግግሞሽ የተነሳ የወፍ ድምፅ ፂው ስትል ሲኮንድ አታልፍም:: የድምጻቸው ልዩነት ውበትና ህበሩ በጭንቅ በጥበብ ከተቀመረ
ዘመናዊ ሙዚቃ የበለጠ ስሜት ይማርካል፡፡
«እናንት ወፎች» አለ አስቻለው ሁኔታቸው ሁለ ግርም ብሎት፡፡ ዛፋ ሁሉ የሁላችሁ ለኔ ብቻ ባይ ስግብግብ በመሀላችሁ የለም
አዛዥ የላችሁ ገልማጭ ጠላት የላችሁ ምቀኛ ኑሮአችሁ በራሳችሁ፣ ውሸት አታውቁ ቅጥፈት ክፉ አቶለሙ ክፉ አትናገሩ አትቀየሙ አታስቀይሙ ጨኸታችሁ አይገደብ ጫጫታችሁ አይመዘገብ ቂም አታውቁ በቀል፤ በእናንተ ዘንድ ዛቻ የለ
ማስፈራራት፤ ፍርሀት የለ ጭንቀት፣ በዚች ምድር ሰላም ልትኖሩ የተፈጠራችሁ ሰላማዊ ፍጡሮች! በማለት ብቻውን ሲነጋገር ከቆየ በኋሳ ሀሳቡን ወደ ሰው ልጅ ባህሪና አኗኗር መለስ ሲያደርገው ጭራሽ አስጠላው።
«ያልታደለ ፍጡር»አለ በስጨት ባለ አነጋገር፡፡ ታየው የሰው ልጅ
ክፋቱና ተንኮሉ፣ ቂምና በቀሉ፣ ሸርና ምቀኝነቱ፤ ጠበና ጭቅጭቁ፣ ከሁሉም በላይ
እብሪቱና ጭካኔው፡ በቃሉም ይገልፀው ጀመር «የአሳር ሽክም የተጫነ መከረኛ ፍጡር፥ ሰው! የቱንም ያህል ቢማር ቢመራመር ከራሱ ጋር መታረቅ ያቃተው
ደካማ ፍጡር፡ ሰው ፈጣሪው ራሱ እሱን በመፍጠሩ የተፀፀተበት ብቸኛ እንስሳ ሰው!» ካለ በኋላ ራሱን ወዝወዝ አድርጎ ወደ መሬት ጎንበስ አለና ያን የለመለመ
ሳር ልብ ብሎ ይመለከተው ጀመር፡፡ ከሩቅ ሲያዩት ልምላሜ ያምራል:: ስሩ ሲታይ ግን ብዙ ጥቃንጥት አለበት፡፡ የደረቁ ቅጠሎችና ጭራሮዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ በርካታ ነገሮች ስር ስሩን ትብትብ እድርገው ይዘውታል። ይህ ሁኔታ ሔዋንን አስታወየው፡፡
«አንተ ለምለም ሳርና የኔዋ ሔዋን እንድ ናቸሁ፡ ከሩቅ ሲያዩአቸሁ ውብ ናችሁ:: ፍጹም የደላችሁ ትመስላላችሁ፡፡ ሥር ሥራችሁንና ውስጥ ውስጣችሁን ግን ብዙ ችግር አለባችሁ፡፡ ሳትጠሩት የመጣባችሁ፣ ሳትፈልጉት የተዳበላችሁ፡፡ አቁሳይ ጥገኛ አለባችሁ፡፡ አንተን የጭራሮና የቅጠል ርጋፊዎች ስርህን ተብትበው እንደ ያዘህ ሁሉ የኔዋ ሔዋንም የአፈቀረ ልቧን የሚወ,ጋ የስሜት እሾህ ኣለባት፡፡
ለመውደድና ለመወደድ የተፈጠረች ቆንጆ ነበረች:: ግን እሾሁ ጋሬጣው በዛባትና
መንፈሷ ቆሰለ፡፡ በአፈቀረች ተሰቃየች። ማልቀስና መተከዝ ዕጣ ፋንታዋ ሆነ።
እያለ ሲያስብ በዚያው ያ ቅዠት ውስጥ ያየው ሁኔታ ትዝ አለው፡፡ ድንግጥ ብሎ እንደ መደንበር አረገና በተቀመጠበት ጉቶ ላይ ብድግ አለ ሳያስበው በዚያ
በለመለመ ሳር ላያ ይዘዋወር ጀመር፡፡
እጆቹን በጀርባው ላይ አጣምሮ ጎንበስ በማለት በግምት ከአስር: እስከ አስራ አምስት ርምጃዎችን ከተራመደ በኋላ በግራ በኩል ወደ መንገዱ ዞር ብሎ ሲያይ አንድ ለየት ያለ ነገር አየ፡፡ በመንገዱ ላይ ሰዎች አሁንም ወደ ላይ ወደ ታችም አቅጣጫ ይሄዳሉ፡፡ ነገር ግን መንገደኛ፣ ለየት ባለ እኳኋን አንዲት በጀርባዋ ጓዝ የያዘች
👍10❤1
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
... አየ ወለቴ ጠጋ ብየ ባጥናናሁሽ፡፡ እኔ አልረሳሁሽም። የሩቅ ቅርብ ሁኜ ስላንቺ አስባለሁ። ምንግዝየም ኸልቤ አትጠፊም አለ።..
ከለቅሶው በኋላ፣ ሕዝቡ ወደ መኻል ግንብ ለስንብት ሲሄድ አብሮ ሄደ። በግርግሩ መሃል ከነአብርሃ ጋር በመጠፋፋቱ፣ ከተሰናዳው የእዝን ግብር ከሕዝቡ ጋር መካፈል ሆዱ እንቢ ብሎት፣ በሰዎች ተከልሎ ምንትዋብና ኢያሱን እጅ ነስቶ አልፎ ወርቄ ቤት ሄዶ ውጭ ተቀምጦ ጠበቃቸው።
እነወርቄ እንደተመለሱ፣ አብርሃ ለብቻው ከተፍ አለ። “የት ኸዳችሁ
ነው የተጠፋፋን? ወዲህ ብል ወዲያ ብል አጣኋችሁ” አላቸው።
ሁሉም የነበሩበትን ቦታ ከተነጋገሩ በኋላ፣ ውስጥ ገብተው ወርቄ
ምሳ አቀረበች። በልተው ሲጨርሱ፣ ጠላ እየተጎነጩ ስለ ቀኑ ውሎ ማውጋት ጀመሩ።
“መቼም ሰዉ ሁሉ ሚያወራው ስለ እቴጌ ጥንካሬ ነው” አለ፣
አብርሃ። “ቀብሩን ሆነ የቅጥር ልቅሶውን እንዴት አርገው እንዳዘጋጁት ይገርማል ። ባላባቱ፣ ካህናቱና ሊቃውንቱ፣ “በርግጥም በካፋ አልሞቱም ሲሉ ነበር አሉ” አላቸው።
ጥላዬ ዝም አለ። ምንትዋብ በልጅነቷ ባሏን በማጣቷ ጉዳቷ
ተሰምቶታል። አጠገቧ ሆኖ ሊያጽናናት ባይችልም፣ ደብረ ወርቅ መመለስ ከብዶታል። በሩቅም ቢሆን ሐዘኗን መካፈል መርጧል።ምንም ቢሆን ወለቴ እኮ አብሮ አደጌ ናት። ኑሯችን እየቅል ቢሆንም በዕዘኗ ሆነ በደስታዋ የሩቅ ቅርብ ሁኜ መካፈል አለብኝ አለ፣ ለራሱ።
በሌላ በኩል አለቃ ሔኖክን ደግሞ ሳያያቸው ማረፋቸው አሳዘነው።
ደብረ ወርቅ በነበረበት ወቅት ስለእሳቸው ሲያስብ፣ የተማረውን ሁሉ ሊያወራቸው ሲመኝ ቆይቶ፣ እንደ አባት የሚያያቸውን መምህሩን ሞት ስለነጠቀው ከፋው። በሌላ በኩል ወርቄ ወላጆቿ መጥተውላት አጠገቧ
በመሆናቸው ደስ አለው። አርባቸውን ሳላወጣ አልኸድም አለ፣ ለራሱ።
ወርቄ፣ ሐሳብ ውስጥ እንደገባ አስተዋለች። ደብረ ወርቅ እስኪመለስ ድረስ የቀድሞ ቤቱ መክረም እንደሚችል ነገረችው።
አብርሃ፣ ጥላዬን ከስድስት ዓመት በኋላ፣ በማግኘቱ ደስታው መጠን
አጥቶ ነበርና፣ “ኸኔ ዘንድ ይቆያል” አላት።
እኔማ ያው ቤቱ አለ ብየ እንጂ” አለች ወርቄ፣ ጥላዬን እያየች።
“ኸብረሃም ዘንድ እየተጫወትን እንከርማለን። ኸናንተም አልለይም።አልሰማሁ ሁኘ አለቃን ሳልቀብራቸው ቀርቸ እኼው ዛሬ እንጉሥ ለቅሶ ለመድረስ በቃሁ። እንዳው አለቃን ከዛሬ ነገ አያቸዋለሁ ስል አመለጡኝ” አላት።
ወርቄ በዐይኗ ውሃ ሞላ።
“ተይ ልዤ ጠሐይ ላይ ውለሽ መጥተሽ። መቀበል ነው እንጂ ሌላ ምን ማረግ ይቻላል?” አሏት እናቷ።
አብርሃ፣ ትኩር ብሎ አያትና፣ “የአለቃ ሞት ሁላችንንም ነው የጎዳ።መጥናናት ነው እንጂ ሌላ ምን እናረጋለን። ሞት እንደሁ ያለ ነው” አላት።
“የአለቃን ነፍስ በገነት ያኑርልን። የጃንሆይንም ነፍስ እዝጊሃር
ይማር” አሉ፣ የወርቄ አባት።
“አሜን” አሉ፣ ሁለም።
“እቴጌም ቢሆኑ አሳዘኑኝ በልዥነታቸው ባላቸውን አጥተው። ዕጣ ፈንታቸው እንደኔ የሙት ሚስት መሆኑ ያሳዝናል” አለች ወርቄ ለምንትዋብም ለራሷም በማዘን።
ሁሉም አንገታቸውን ደፍተው ዝም አሉ።
አብርሃ፣ እኔማ ትምርቱስ እንዴት ሁኖለት ይሆን እያልሁ ሳስብ”
አለው ጥላዬን፣ ቤቱን የከበበውን የትካዜ ድባብ ለመቀየር።
“ትምርቱማ... ያው ኸዝኽ አንድ ዓመት አርጌ ማልነበር ወደ ደብረ
ወርቅ ማርያም የኸድሁት? ኸዛ ያገኘዃቸው መምህር... ሊቀጠበብት አዳሙ እንዴት ያሉ ሰው መሰሉህ። አለቃ ሔኖክ እሳቸው ዘንድ ስለላኩኝ እንዳመሰገንዃቸው አለሁ። ያው... ኸዝኸ እንደኸድሁ ሥጋ
ለባሾችን ሠራሁ።”
“ሰዎችን ማለቱ ነው” ሲል አብራራ አብርሃ፣ የወርቄ ወላጆች ግር
ሲላቸው አይቶ።
“ቤተስኪያን አካባቢ ያሉ ቀሳውስት፣ መነኮሳት... መምህር
የመሳሰሉትን ማለቴ ነው” አለ፣ ጥላዬ። “ታስታውሳለህ አለቃ ሔኖክ...ነፍሳቸውን ይማርና... ስዠምር ጥቁር ቀለም ብቻ ነው ምትጠቀመው ሲለኝ? ኋላ ሌሎች ዓይነት ቀለሞችም ተጠቅሜያለሁ።”
“ራስህ እያዘጋጀህ?"
ኋላ! ራስህ ነህ እንጂ ሌላ ማን ያዘጋጅልሀል? እና ... የቤተክህነት
ሰዎችን ስትሥል፣ የልብሳቸውን ሆነ የካባቸውን ቀለም አሳምረህ
ትሠራለህ። ጥምጥማቸውንም እንዲሁ ትክክል አርገህ ትሥላለህ። ንድፉ እንዳይንጋደድብህም ትጠነቃቃለህ። የልብሳቸውንና የካባቸውንም ዕጥፋት ሳይቀር ነው በጥንቃቄ ምትሠራው።”
“ስንታቸውን ሣልህ በል?”
“ምን አለፋህ ብዙዎቹን ሥያለሁ። የዠመርሁት በአንድ መነኩሴ
ነበር። መነኩሴው ሲያዩት ደስ አላቸው። ማስታወሻ ብየ ሰጠኋቸው።ሁለተኛ ሊቀጠበብት አዳሙን ነበር የሣልሁት። እሳቸውም እንደዝሁ ደስ አላቸው። እንዲህ እያልሁ ወደሚቀጥለው ተሻገርሁ።”
“ምን ሠራህ?”
“ጻድቃንን ሣልሁ። አቡነ ተክለሃይማኖትን፣ ቅዱስ ያሬድን፣ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስን፣ አቡነ ኪሮስን፣ እናታችንን ክርስቶስ ሣምራን የመሰሉትን ሣልሁ።”
“የሁሉን መልክ አውቃችሁ ነው ምትሥሉ?” ሲሉ ጣልቃ ገቡ፣
የወርቄ አባት።
“የለ... የለ... እነሱን ስንሥል መልካቸውን ስለማናውቅ... የተሰወሩ ስላለባቸውም ... ታሪካቸውን፣ ታምራቸውንና ገድላቸውን ጠንቅቀን
አውቀን ነው ምንሥል። እነሱን ለመሣል ኸመነሣታችን በፊት
ታሪካቸውንና ገድላቸውን ለማወቅ ንባብ አድርገን ነው ምንሥላቸው።
ሥጋ ወደሙን ተቀብለን ስንሠራ ደሞ ትክክለኛ መልካቸው
ይገለጥልናል” አላቸው፣ ጥላዬ።
“እህ” አሉ የወርቄ አባት፣ እንደገባቸው ለማሳወቅ ራሳቸውን
እየነቀነቁ።
“እንደ ቅኔ ነው በለኛ! እኛም እኮ ክብረ ነገሥት፣ ገድላት፣ ድርሳናት
ወንጌል... መጽሐፍ ቅዱስ... ኻላወቅን ቅኔ አንቆጥርም” አለው
አብርሃ።
“አውቀው የለ። ደሞ ሰማዕታትን ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ እንደ መርቆርዮርስና ገላውዲዮስ የመሳሰሉትን ሣልሁ። ሰማዕታት ቤተክሲያን ውስጥ ሲሣሉ በግራ በኩል ነው ሚሣሉ። ሁሉም ሚሣሉበት ቦታ ቦታ አላቸው። ሚሣሉበት ቀለምም እንደዝሁ ይለያያል። ሰማዕታት ለጌታችን ለክርስቶስ ፍቅር ሲሉ፣ ስለአዳኝነቱ ሲመሰክሩ አንገታቸው
በሠይፍ ተቀልቶ፣ ወይ ከእሳት እቶን ተጥለው ማዶል የሞቱት? እናም ያነን ያፈሰሱትን ደም ለመዘከር በቀይ ቀለም ይሣላሉ። መላዕክት የመንፈስ ቅዱስ ሕይወት በነሱ ላይ ስላደረ... ብርሃንና ተስፋ ሰጪዐስለሆኑ፣ እነሱን ለመሣል ምትጠቀመው ቀለም ደማቅ መሆን አለበት።
ደማቅ ቀለም የተስፋ ምልክት ነው። ጻድቃን.. ይኸን ዓለም ንቀው በጽድቅ ኖረው ያለፉ አባቶቻችን ደሞ ፈዘዝ ባለ ቀለም ይሣላሉ።ድንግል ማርያም ደሞ ልብሷ ከላይ በሰማያዊ፣ ከውስጥ በቀይና ምትከናነበው ደሞ በአረንጓዴ ቀለሞች ይሣላል። ምትሥለው ሥዕል
እንደ ተሣዩ ማንነትና ታሪክ ምትመርጠው ቀለም ይለያያል። ሰማያዊ መንፈሳዊ ንፅህናን ያሳያል፤ ነጭ እንደምታውቀው ብርሃን ነው፤ ብጫ
ደሞ የዠግንነት ምልክት ነው።”
“ዘይገርም!” አለ፣ አብርሃ።
“ምን አለፋህ መላዕክትን... ሰባቱን ሊቃነ መላዕክት... እነቅዱስ ገብርኤልንም ሣልሁ” ሲል ቀጠለ ጥላዬ። “መላዕክት እንደምታውቀው መከሠቻ አላቸው። ሚከሠቱበት መንገድም ይለያያል...”
“መከሠቻ?” አሉ፣ ሁሉን በጥሞና ሲያዳምጡ የቆዩት የወርቄ እናት።
“ኣዎ መገለጫ ማለቴ ነው።”
“እንዴት እንዴት ሁነው ነው ሚገለጡ?”
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
... አየ ወለቴ ጠጋ ብየ ባጥናናሁሽ፡፡ እኔ አልረሳሁሽም። የሩቅ ቅርብ ሁኜ ስላንቺ አስባለሁ። ምንግዝየም ኸልቤ አትጠፊም አለ።..
ከለቅሶው በኋላ፣ ሕዝቡ ወደ መኻል ግንብ ለስንብት ሲሄድ አብሮ ሄደ። በግርግሩ መሃል ከነአብርሃ ጋር በመጠፋፋቱ፣ ከተሰናዳው የእዝን ግብር ከሕዝቡ ጋር መካፈል ሆዱ እንቢ ብሎት፣ በሰዎች ተከልሎ ምንትዋብና ኢያሱን እጅ ነስቶ አልፎ ወርቄ ቤት ሄዶ ውጭ ተቀምጦ ጠበቃቸው።
እነወርቄ እንደተመለሱ፣ አብርሃ ለብቻው ከተፍ አለ። “የት ኸዳችሁ
ነው የተጠፋፋን? ወዲህ ብል ወዲያ ብል አጣኋችሁ” አላቸው።
ሁሉም የነበሩበትን ቦታ ከተነጋገሩ በኋላ፣ ውስጥ ገብተው ወርቄ
ምሳ አቀረበች። በልተው ሲጨርሱ፣ ጠላ እየተጎነጩ ስለ ቀኑ ውሎ ማውጋት ጀመሩ።
“መቼም ሰዉ ሁሉ ሚያወራው ስለ እቴጌ ጥንካሬ ነው” አለ፣
አብርሃ። “ቀብሩን ሆነ የቅጥር ልቅሶውን እንዴት አርገው እንዳዘጋጁት ይገርማል ። ባላባቱ፣ ካህናቱና ሊቃውንቱ፣ “በርግጥም በካፋ አልሞቱም ሲሉ ነበር አሉ” አላቸው።
ጥላዬ ዝም አለ። ምንትዋብ በልጅነቷ ባሏን በማጣቷ ጉዳቷ
ተሰምቶታል። አጠገቧ ሆኖ ሊያጽናናት ባይችልም፣ ደብረ ወርቅ መመለስ ከብዶታል። በሩቅም ቢሆን ሐዘኗን መካፈል መርጧል።ምንም ቢሆን ወለቴ እኮ አብሮ አደጌ ናት። ኑሯችን እየቅል ቢሆንም በዕዘኗ ሆነ በደስታዋ የሩቅ ቅርብ ሁኜ መካፈል አለብኝ አለ፣ ለራሱ።
በሌላ በኩል አለቃ ሔኖክን ደግሞ ሳያያቸው ማረፋቸው አሳዘነው።
ደብረ ወርቅ በነበረበት ወቅት ስለእሳቸው ሲያስብ፣ የተማረውን ሁሉ ሊያወራቸው ሲመኝ ቆይቶ፣ እንደ አባት የሚያያቸውን መምህሩን ሞት ስለነጠቀው ከፋው። በሌላ በኩል ወርቄ ወላጆቿ መጥተውላት አጠገቧ
በመሆናቸው ደስ አለው። አርባቸውን ሳላወጣ አልኸድም አለ፣ ለራሱ።
ወርቄ፣ ሐሳብ ውስጥ እንደገባ አስተዋለች። ደብረ ወርቅ እስኪመለስ ድረስ የቀድሞ ቤቱ መክረም እንደሚችል ነገረችው።
አብርሃ፣ ጥላዬን ከስድስት ዓመት በኋላ፣ በማግኘቱ ደስታው መጠን
አጥቶ ነበርና፣ “ኸኔ ዘንድ ይቆያል” አላት።
እኔማ ያው ቤቱ አለ ብየ እንጂ” አለች ወርቄ፣ ጥላዬን እያየች።
“ኸብረሃም ዘንድ እየተጫወትን እንከርማለን። ኸናንተም አልለይም።አልሰማሁ ሁኘ አለቃን ሳልቀብራቸው ቀርቸ እኼው ዛሬ እንጉሥ ለቅሶ ለመድረስ በቃሁ። እንዳው አለቃን ከዛሬ ነገ አያቸዋለሁ ስል አመለጡኝ” አላት።
ወርቄ በዐይኗ ውሃ ሞላ።
“ተይ ልዤ ጠሐይ ላይ ውለሽ መጥተሽ። መቀበል ነው እንጂ ሌላ ምን ማረግ ይቻላል?” አሏት እናቷ።
አብርሃ፣ ትኩር ብሎ አያትና፣ “የአለቃ ሞት ሁላችንንም ነው የጎዳ።መጥናናት ነው እንጂ ሌላ ምን እናረጋለን። ሞት እንደሁ ያለ ነው” አላት።
“የአለቃን ነፍስ በገነት ያኑርልን። የጃንሆይንም ነፍስ እዝጊሃር
ይማር” አሉ፣ የወርቄ አባት።
“አሜን” አሉ፣ ሁለም።
“እቴጌም ቢሆኑ አሳዘኑኝ በልዥነታቸው ባላቸውን አጥተው። ዕጣ ፈንታቸው እንደኔ የሙት ሚስት መሆኑ ያሳዝናል” አለች ወርቄ ለምንትዋብም ለራሷም በማዘን።
ሁሉም አንገታቸውን ደፍተው ዝም አሉ።
አብርሃ፣ እኔማ ትምርቱስ እንዴት ሁኖለት ይሆን እያልሁ ሳስብ”
አለው ጥላዬን፣ ቤቱን የከበበውን የትካዜ ድባብ ለመቀየር።
“ትምርቱማ... ያው ኸዝኽ አንድ ዓመት አርጌ ማልነበር ወደ ደብረ
ወርቅ ማርያም የኸድሁት? ኸዛ ያገኘዃቸው መምህር... ሊቀጠበብት አዳሙ እንዴት ያሉ ሰው መሰሉህ። አለቃ ሔኖክ እሳቸው ዘንድ ስለላኩኝ እንዳመሰገንዃቸው አለሁ። ያው... ኸዝኸ እንደኸድሁ ሥጋ
ለባሾችን ሠራሁ።”
“ሰዎችን ማለቱ ነው” ሲል አብራራ አብርሃ፣ የወርቄ ወላጆች ግር
ሲላቸው አይቶ።
“ቤተስኪያን አካባቢ ያሉ ቀሳውስት፣ መነኮሳት... መምህር
የመሳሰሉትን ማለቴ ነው” አለ፣ ጥላዬ። “ታስታውሳለህ አለቃ ሔኖክ...ነፍሳቸውን ይማርና... ስዠምር ጥቁር ቀለም ብቻ ነው ምትጠቀመው ሲለኝ? ኋላ ሌሎች ዓይነት ቀለሞችም ተጠቅሜያለሁ።”
“ራስህ እያዘጋጀህ?"
ኋላ! ራስህ ነህ እንጂ ሌላ ማን ያዘጋጅልሀል? እና ... የቤተክህነት
ሰዎችን ስትሥል፣ የልብሳቸውን ሆነ የካባቸውን ቀለም አሳምረህ
ትሠራለህ። ጥምጥማቸውንም እንዲሁ ትክክል አርገህ ትሥላለህ። ንድፉ እንዳይንጋደድብህም ትጠነቃቃለህ። የልብሳቸውንና የካባቸውንም ዕጥፋት ሳይቀር ነው በጥንቃቄ ምትሠራው።”
“ስንታቸውን ሣልህ በል?”
“ምን አለፋህ ብዙዎቹን ሥያለሁ። የዠመርሁት በአንድ መነኩሴ
ነበር። መነኩሴው ሲያዩት ደስ አላቸው። ማስታወሻ ብየ ሰጠኋቸው።ሁለተኛ ሊቀጠበብት አዳሙን ነበር የሣልሁት። እሳቸውም እንደዝሁ ደስ አላቸው። እንዲህ እያልሁ ወደሚቀጥለው ተሻገርሁ።”
“ምን ሠራህ?”
“ጻድቃንን ሣልሁ። አቡነ ተክለሃይማኖትን፣ ቅዱስ ያሬድን፣ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስን፣ አቡነ ኪሮስን፣ እናታችንን ክርስቶስ ሣምራን የመሰሉትን ሣልሁ።”
“የሁሉን መልክ አውቃችሁ ነው ምትሥሉ?” ሲሉ ጣልቃ ገቡ፣
የወርቄ አባት።
“የለ... የለ... እነሱን ስንሥል መልካቸውን ስለማናውቅ... የተሰወሩ ስላለባቸውም ... ታሪካቸውን፣ ታምራቸውንና ገድላቸውን ጠንቅቀን
አውቀን ነው ምንሥል። እነሱን ለመሣል ኸመነሣታችን በፊት
ታሪካቸውንና ገድላቸውን ለማወቅ ንባብ አድርገን ነው ምንሥላቸው።
ሥጋ ወደሙን ተቀብለን ስንሠራ ደሞ ትክክለኛ መልካቸው
ይገለጥልናል” አላቸው፣ ጥላዬ።
“እህ” አሉ የወርቄ አባት፣ እንደገባቸው ለማሳወቅ ራሳቸውን
እየነቀነቁ።
“እንደ ቅኔ ነው በለኛ! እኛም እኮ ክብረ ነገሥት፣ ገድላት፣ ድርሳናት
ወንጌል... መጽሐፍ ቅዱስ... ኻላወቅን ቅኔ አንቆጥርም” አለው
አብርሃ።
“አውቀው የለ። ደሞ ሰማዕታትን ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ እንደ መርቆርዮርስና ገላውዲዮስ የመሳሰሉትን ሣልሁ። ሰማዕታት ቤተክሲያን ውስጥ ሲሣሉ በግራ በኩል ነው ሚሣሉ። ሁሉም ሚሣሉበት ቦታ ቦታ አላቸው። ሚሣሉበት ቀለምም እንደዝሁ ይለያያል። ሰማዕታት ለጌታችን ለክርስቶስ ፍቅር ሲሉ፣ ስለአዳኝነቱ ሲመሰክሩ አንገታቸው
በሠይፍ ተቀልቶ፣ ወይ ከእሳት እቶን ተጥለው ማዶል የሞቱት? እናም ያነን ያፈሰሱትን ደም ለመዘከር በቀይ ቀለም ይሣላሉ። መላዕክት የመንፈስ ቅዱስ ሕይወት በነሱ ላይ ስላደረ... ብርሃንና ተስፋ ሰጪዐስለሆኑ፣ እነሱን ለመሣል ምትጠቀመው ቀለም ደማቅ መሆን አለበት።
ደማቅ ቀለም የተስፋ ምልክት ነው። ጻድቃን.. ይኸን ዓለም ንቀው በጽድቅ ኖረው ያለፉ አባቶቻችን ደሞ ፈዘዝ ባለ ቀለም ይሣላሉ።ድንግል ማርያም ደሞ ልብሷ ከላይ በሰማያዊ፣ ከውስጥ በቀይና ምትከናነበው ደሞ በአረንጓዴ ቀለሞች ይሣላል። ምትሥለው ሥዕል
እንደ ተሣዩ ማንነትና ታሪክ ምትመርጠው ቀለም ይለያያል። ሰማያዊ መንፈሳዊ ንፅህናን ያሳያል፤ ነጭ እንደምታውቀው ብርሃን ነው፤ ብጫ
ደሞ የዠግንነት ምልክት ነው።”
“ዘይገርም!” አለ፣ አብርሃ።
“ምን አለፋህ መላዕክትን... ሰባቱን ሊቃነ መላዕክት... እነቅዱስ ገብርኤልንም ሣልሁ” ሲል ቀጠለ ጥላዬ። “መላዕክት እንደምታውቀው መከሠቻ አላቸው። ሚከሠቱበት መንገድም ይለያያል...”
“መከሠቻ?” አሉ፣ ሁሉን በጥሞና ሲያዳምጡ የቆዩት የወርቄ እናት።
“ኣዎ መገለጫ ማለቴ ነው።”
“እንዴት እንዴት ሁነው ነው ሚገለጡ?”
👍11
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...ስለነሱ ስትነግሪኝ ለምን ልቤ እንደሚጠፋ ልንገርሽ»
«ለምንድነው?»
«ከነገርሽኝ ነገሩን አወቅኩት ማለት ነው። ካወቅኩት ደሞ
አያስፈራኝም፡፡ ጭለማ ሲሆን፣ ምን ይመጣብኝ ይሆን? በማለት
እፈራለሁ እንጂ፡ በብርሀን ካየሁት ማንም ሰው ቢሆን አያስፈራኝም፡፡ ማለቴ ሳላውቀው አንድ ሰው ይተኛሽ ይሆን? ብዬ እፈራለሁ እንጂ፣ እያወቅኩ ከሆነ፣ አስር ሰው ቢተኛሽም አልፈራም፡፡
እያወቅኩት ከተደረገ ድርጊቱ የኔ ሆነ ማለት ነው፡፡ የኔ ከሆነ
ሊጎዳኝ አይችልም .. እንዴት እንደተኙሽ ስትነግሪኝ፣ እኔ እነሱን
ሆኜ ተኛሁሽ፣ ተወስዶብኝ የነበረውን ገላሽን፣ ቃላትን መለሱልኝ ማለት ነው። ... ስለዚህ ነው የተኙሽ ወንዶች ቁጥር እንደመብዛቱ መጠን የኔ ደስታ የሚበዛው፡፡»
«አልገባኝም»
«አየሽ፣ ማንም አልተኛሽም ማለት ያስፈራኛል፡፡ ጭለማ ውስጥ
ነኝ ማለት ነው። .. አንድ ሰው ተኝቶኛል ብትይ፡ ትንሽ ይሻለኛል። ግን አሁንም አንድ ሰው ደብቀሽኝ ሊሆን ይችላል። አራት ወንድ ተኛኝ ብትይ የበለጠ ይሻላል። ምክንያቱም የደበቅሽኝ ነገር
የለም ማለት ነው። ስለዚህ መፍራት አያስፈልገኝም፤ ምክንያቱም የተወሰደብኝ ሁሉ ተመልሶልኝ አቅፌዋለሁ ማለት ነው፡፡»
«ገባኝ። አንድ ጥያቄ፡፡»
«ምን?»
«እኔም እነሱም ያው ነን ካልክ፣ ምን እንዳረጉኝ ባታውቅስ ምን
ልዩነት ያመጣል?»
«ይህን አትጠይቂኝ። ላስረዳሽ አልችልም፡፡ እኔም ራሴ
አይገባኝም፡፡ ምናልባት እኔም እነሱም ያው ለመሆን የምንችለው፣ እነሱ ያረጉትን ካወቅኩ ብቻ ይሆናል፡፡»
ዝም ዝም ሆነ፡፡ ታችኛ ከንፈሯን እየነከለች ስታስብ ቆየች
«ልንገርህ?» አለች
«ምን?»
«እኔ በበኩሌ ሌላ ሆኖ ነው የሚታየኝ»
እንዴት ሆኖ ነው ሚታይሽ?»
“በጭራሽ በሽታ አልያዘህም፡፡ እንደሌላ ወንድ ነህ»
ሌሎች ወንዶች ከሌላ ጋር ተኝተሽ ነይልኝ ይሉሻል?»
« አይሉኝም
እኔም የሚሉሽ አልመሰለኝም
«ስማኝ እንግዲህ:: ክርክሩን ተውና አድምጠኝ። በግብረ ስጋ
በኩል ስለሴቶች ታውቃለህ እንጂ፣ በጥቅሉ ስለ ሴቶች ምን
ታውቃለህ? እነሱ ካልነገሩሀ ስለነሱ ለማወቅ አትችልም፡፡ እነሱ ደሞ የውስጡን አይነግሩህም። ለምሳሌ፣ አንተ እኔን ከሌሎች እየተቀበልክ እንደምትደሰትብኝ ለሰው ትነግራለህ ይመስልሀል? ለማንም አትናገርም። ሌሎችም ወንዶች ውስጣዊውን ምስጢር አይነግሩህም፡፡
ስለዚህ ሴት ካልሆንክ ወንዶችን በዚህ በኩል ልታውቃቸው
አትችልም። እኔ ልንገርህ
“ብዙ ጋብቻዎች መቀዝቀዝ ሲጀምሩ፣ ሴትዮዋ ተስፋ
ትቆርጥና ውሽማ ትይዛለች። ባልየው ሲያውቅ ምን እንደሚያደርግ ታውቃለህ? ለጊዜው ይናደዳል፣ ይደበድባታል፣ እንፋታ ይላል።
በኋላ ግን ታርቀው ይቅርታ ያደርግላትና፣ በጣም ሊወዳት
ይጀምራል። ቀዝቅዞ የነበረው ጋብቻ ይሞቃል፣ ይታደሳል። ለምን? ሴትዮዋ ሌላ ወንድ ጋ ስለሄደች ነው
መንገድ ዳር ውጣና ጎረምሶቹን ሴት ሲያድኑ እያቸው።
ሴትዮዋ በጣም ጨዋ ከመሰለቻቸው፣ ምንም ቆንጆ ብትሆን አይከተሏትም፡፡ ትንሽ በመጠኑ ስድ ብጤ ከሆነች ግን
አስተያየቷ፣ አረማመዷ፣ ወይም አለባበሷ በቂ ልቅነት ካሳየ
ጎረምሶቹ ይሻሟታል። በቀላሉ ሊያገኙዋት ስለሚችሉ ብቻ
እንዳይመስልህ፡፡ ዋናው ምክንያት ሌላ ነው። ባለጌ ከመሰለች፣
እንግዲያው ብዙ ወንድ ኣውቃለች ማለት ነው:: ለዚህ ነው
የሚሻሟት
«እየው፣ የሰው ልጅ ፍጥረቱ እንደዚህ ነው:: አንድ የለመድከው ሰው ሊለይህ የሆነ እንደሆነ ልትወደው ትጀምራለህ።
ለህይወትህ የሚያስፈራ በሽታ የያዘህ የመሰለህ እንደሆነ፣ በፊት
ከምንም የማትቆጥራትን ህይወትህን በሀይል ልትወዳት ትጀምራለህ
ሀኪም ጨው እንዳትበላ ያዘዘህ : እንደሆነ፣ ጨው ምንኛ ግሩም
ቅመም እንደሆነ ትገነዘባለህ ሴትህ ወደሌላ የሄደችብህ
እንደሆነ፣ እንዴት ቆንጆ እንደሆነች እንደ አዲስ ሊታይህ ይጀምራል
በራሲ የሚያጋጥመኝን ለምን አልነግርህም? በዚህ ሰሞን
ከማያቸው ወንዶች ሁለቱ እንዴት እንደሚሆኑ ላጫውትህ፡፡ ሁለቱም
ያው ናቸው። ስለዚህ ስለአንዱ ልንገርህ፡፡ ማርሴል ይባላል። በጣም ቆንጆ ነው። ብዙ ሴት ያወቀ ወጣት ነው። ማታ ከእራት በኋላ ካንተ እንደተለየሁ፣ በቀጥታ ወደሱ የሄድኩ እንደሆነ፣ ንፁህ ነኝ፣ የማንም ላብ አልነካኝም፣ ጠረኔ የራሴ ነው፡፡ ልብሴን አስወልቆ ያቅፈኛል! በደምብ ያስደስተኛል፡፡ አንዳንዴ ታድያ፣ ካንተ እንደትለየሁ በቀጥታ ወደሱ እልሄድም፡፡ በፊት ሌላጋ እደርሳለሁ። እና እሱጋ ስሄድ የሌላ ወንድ ላብ ነክቶኛል፣ ጠረኔ የብቻዬ ሳይሆን ከጎረምሳ ጠረን ጋር ተቀላቅሏል። አሁንም ልብሴን ያስወልቀኝና ያቅፈኛል፤ ግን እንደነብር ይሆናል፣ ይጨፈልቀኛል፣ ይነክሰኛል።
ስለሌላ ወንድ አንነጋገርም ግን ሌላጋ እንደነበርኩ በማወቁ የበለጠ እንደሚጣፍጠው ግልፅ ነው፡፡ ይታይሀል?"
«በሚገባ! እና እኔ እንዲህ የምሆንበት ምክንያቱ ምን
ይመስልሻል?» ቀላል ነው። አንደኛ፣ ሌላ ወንድ ከተኛኝ ቆንጆ ነኝ ማለት ነው። ብዙዎች ከተኙኝ እጅግ በጣም ቆንጆ ነኝ፡፡ ስለዚህ የቀለጠ ትፈልገኛለህ፡፡ ሁለተኛ፣ ሌላው ተኝቶኝ አንተ ቀጥለህ ከተኛኸኝ፣ ከሱ ቀምተህ ወሰድከኝ ማለት ነው:: እኔ በሀይል ቆንጆ ሆኜ ከሌሎቹ ሁሉ ቀምተህ ከወሰድከኝ፣ ከሌሎቹ ሁሉ የበለጠ ወንድ ነህ።በወንድነት ከሁሉ በላይ ሆንክ፣ ስለዚህ ደስ ይልሀል፡፡ በጣም ደስ ይልሀል። ወንዶች ሁላችሁም እንደሱ ናችሁ። ግን አየችኝ..
«ግን ምን?» አልኳት
አብዛኛዎቹ ወንዶች ውጪውን ጎበዝ ቢመስሉም ውስጡን ፈሪ
ናቸው፡፡ የውስጥ ስሜታቸውን አይተው መቀበል ይፈራሉ። ስለዚህ ከራሳቸው ይደብቁታል። ሁሉም ወንድ አብዛኛው ወንድ ልበል የራሱን ሴት ሌሎች ሲቀምሱበትና እሱ ነጥቋቸው መልሶ የራሱ ሲያረጋት፣ የበለጠ ወንድነት ይሰማዋል። በሀይል ደስ ይለዋል። ግን ይህን እንደ ጉድ አርጎ ስለሚቆጥረውና ስለሚያፍርበት፣ እያየውም
አውቆ አይኑን ይጨፍናል። ስለዚህ ያስመስላል፤ ያስመስላል፡
ያስመስላል። አቤት ስንት ማስመሰል አለ!
«እዚህ ላይ ነው አንተን ከልቤ የማደንቅህ፡፡ እቺን
ያህል አትፈራም። ወደነብስህ ውስጥ አትኩረህ ትመለከታለህ፡፡ እዚያ ውስጥ ምንም ቀፋፊ ነገር ብታይ አይንህን አትጨፍንም፡፡ ስለዚህ ያለማስመሰል ትኖራለህ ውስጣዊውን ኑሮ ማለቴ ነው። እንግዲህ ወደ ውስጥህ ተመለከትክ፣ ውስጥህ እኔን ሌሎች ቢተኙኝ ከነሱ
ቀምተህ ስትተኛኝ ደስ እንደሚለው ነገረህ። ስለዚህ እኔን 'ሂጂ ወንዶችሽ ጋ አልከኝ። ሄድኩ፡፡ ተመለስኩ። ተደሰትክብኝ፡፡ ወንድ
ነህ። አንተ እውነተኛ ወንድ የሆንከውን ያህል እኔ እውነተኛ ሴት ሆኜ እንደሆነ እጅግ ኩራት ይሰማኛል።»
«አንቺ እንደምትይኝ ከሆንኩ፣ አንቺም እንደኔ አይነት ነሽ።
ልክ እንደኔ አይነት! አብዛኛዎቹ ሴቶች፣ ፍቅር ከያዘኝ ወንድ ጋር
ብቻ ነው ግብረ ስጋ ደስ የሚለኝ ይላሉ። ይህም ማስመሰል፣
ማስመሰል፣ ማስመሰል ነው። አንቺ ግን ለራስሽ አትዋሺም። ቆንጆ ወጣት ሆኖ ቆንጆ ወንድ እያቀያየሩ መደሰት እንዴት ያለ ገነት ነው!' ትያለሽ። እኔኮ አልችልም፣ ቆንጆ ወንድ ሳይ አያስችለኝም፣ቁንጅናውን መንካት መዳሰስ አለብኝ፣ በወጣትነቱ መደሰት አለብኝ ትያለሽ
“አንድ ቀን አንድ ነገር አልሽኝ። አስከመቼም አልረሳውም፡፡»
«ምን አልኩህ?»
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...ስለነሱ ስትነግሪኝ ለምን ልቤ እንደሚጠፋ ልንገርሽ»
«ለምንድነው?»
«ከነገርሽኝ ነገሩን አወቅኩት ማለት ነው። ካወቅኩት ደሞ
አያስፈራኝም፡፡ ጭለማ ሲሆን፣ ምን ይመጣብኝ ይሆን? በማለት
እፈራለሁ እንጂ፡ በብርሀን ካየሁት ማንም ሰው ቢሆን አያስፈራኝም፡፡ ማለቴ ሳላውቀው አንድ ሰው ይተኛሽ ይሆን? ብዬ እፈራለሁ እንጂ፣ እያወቅኩ ከሆነ፣ አስር ሰው ቢተኛሽም አልፈራም፡፡
እያወቅኩት ከተደረገ ድርጊቱ የኔ ሆነ ማለት ነው፡፡ የኔ ከሆነ
ሊጎዳኝ አይችልም .. እንዴት እንደተኙሽ ስትነግሪኝ፣ እኔ እነሱን
ሆኜ ተኛሁሽ፣ ተወስዶብኝ የነበረውን ገላሽን፣ ቃላትን መለሱልኝ ማለት ነው። ... ስለዚህ ነው የተኙሽ ወንዶች ቁጥር እንደመብዛቱ መጠን የኔ ደስታ የሚበዛው፡፡»
«አልገባኝም»
«አየሽ፣ ማንም አልተኛሽም ማለት ያስፈራኛል፡፡ ጭለማ ውስጥ
ነኝ ማለት ነው። .. አንድ ሰው ተኝቶኛል ብትይ፡ ትንሽ ይሻለኛል። ግን አሁንም አንድ ሰው ደብቀሽኝ ሊሆን ይችላል። አራት ወንድ ተኛኝ ብትይ የበለጠ ይሻላል። ምክንያቱም የደበቅሽኝ ነገር
የለም ማለት ነው። ስለዚህ መፍራት አያስፈልገኝም፤ ምክንያቱም የተወሰደብኝ ሁሉ ተመልሶልኝ አቅፌዋለሁ ማለት ነው፡፡»
«ገባኝ። አንድ ጥያቄ፡፡»
«ምን?»
«እኔም እነሱም ያው ነን ካልክ፣ ምን እንዳረጉኝ ባታውቅስ ምን
ልዩነት ያመጣል?»
«ይህን አትጠይቂኝ። ላስረዳሽ አልችልም፡፡ እኔም ራሴ
አይገባኝም፡፡ ምናልባት እኔም እነሱም ያው ለመሆን የምንችለው፣ እነሱ ያረጉትን ካወቅኩ ብቻ ይሆናል፡፡»
ዝም ዝም ሆነ፡፡ ታችኛ ከንፈሯን እየነከለች ስታስብ ቆየች
«ልንገርህ?» አለች
«ምን?»
«እኔ በበኩሌ ሌላ ሆኖ ነው የሚታየኝ»
እንዴት ሆኖ ነው ሚታይሽ?»
“በጭራሽ በሽታ አልያዘህም፡፡ እንደሌላ ወንድ ነህ»
ሌሎች ወንዶች ከሌላ ጋር ተኝተሽ ነይልኝ ይሉሻል?»
« አይሉኝም
እኔም የሚሉሽ አልመሰለኝም
«ስማኝ እንግዲህ:: ክርክሩን ተውና አድምጠኝ። በግብረ ስጋ
በኩል ስለሴቶች ታውቃለህ እንጂ፣ በጥቅሉ ስለ ሴቶች ምን
ታውቃለህ? እነሱ ካልነገሩሀ ስለነሱ ለማወቅ አትችልም፡፡ እነሱ ደሞ የውስጡን አይነግሩህም። ለምሳሌ፣ አንተ እኔን ከሌሎች እየተቀበልክ እንደምትደሰትብኝ ለሰው ትነግራለህ ይመስልሀል? ለማንም አትናገርም። ሌሎችም ወንዶች ውስጣዊውን ምስጢር አይነግሩህም፡፡
ስለዚህ ሴት ካልሆንክ ወንዶችን በዚህ በኩል ልታውቃቸው
አትችልም። እኔ ልንገርህ
“ብዙ ጋብቻዎች መቀዝቀዝ ሲጀምሩ፣ ሴትዮዋ ተስፋ
ትቆርጥና ውሽማ ትይዛለች። ባልየው ሲያውቅ ምን እንደሚያደርግ ታውቃለህ? ለጊዜው ይናደዳል፣ ይደበድባታል፣ እንፋታ ይላል።
በኋላ ግን ታርቀው ይቅርታ ያደርግላትና፣ በጣም ሊወዳት
ይጀምራል። ቀዝቅዞ የነበረው ጋብቻ ይሞቃል፣ ይታደሳል። ለምን? ሴትዮዋ ሌላ ወንድ ጋ ስለሄደች ነው
መንገድ ዳር ውጣና ጎረምሶቹን ሴት ሲያድኑ እያቸው።
ሴትዮዋ በጣም ጨዋ ከመሰለቻቸው፣ ምንም ቆንጆ ብትሆን አይከተሏትም፡፡ ትንሽ በመጠኑ ስድ ብጤ ከሆነች ግን
አስተያየቷ፣ አረማመዷ፣ ወይም አለባበሷ በቂ ልቅነት ካሳየ
ጎረምሶቹ ይሻሟታል። በቀላሉ ሊያገኙዋት ስለሚችሉ ብቻ
እንዳይመስልህ፡፡ ዋናው ምክንያት ሌላ ነው። ባለጌ ከመሰለች፣
እንግዲያው ብዙ ወንድ ኣውቃለች ማለት ነው:: ለዚህ ነው
የሚሻሟት
«እየው፣ የሰው ልጅ ፍጥረቱ እንደዚህ ነው:: አንድ የለመድከው ሰው ሊለይህ የሆነ እንደሆነ ልትወደው ትጀምራለህ።
ለህይወትህ የሚያስፈራ በሽታ የያዘህ የመሰለህ እንደሆነ፣ በፊት
ከምንም የማትቆጥራትን ህይወትህን በሀይል ልትወዳት ትጀምራለህ
ሀኪም ጨው እንዳትበላ ያዘዘህ : እንደሆነ፣ ጨው ምንኛ ግሩም
ቅመም እንደሆነ ትገነዘባለህ ሴትህ ወደሌላ የሄደችብህ
እንደሆነ፣ እንዴት ቆንጆ እንደሆነች እንደ አዲስ ሊታይህ ይጀምራል
በራሲ የሚያጋጥመኝን ለምን አልነግርህም? በዚህ ሰሞን
ከማያቸው ወንዶች ሁለቱ እንዴት እንደሚሆኑ ላጫውትህ፡፡ ሁለቱም
ያው ናቸው። ስለዚህ ስለአንዱ ልንገርህ፡፡ ማርሴል ይባላል። በጣም ቆንጆ ነው። ብዙ ሴት ያወቀ ወጣት ነው። ማታ ከእራት በኋላ ካንተ እንደተለየሁ፣ በቀጥታ ወደሱ የሄድኩ እንደሆነ፣ ንፁህ ነኝ፣ የማንም ላብ አልነካኝም፣ ጠረኔ የራሴ ነው፡፡ ልብሴን አስወልቆ ያቅፈኛል! በደምብ ያስደስተኛል፡፡ አንዳንዴ ታድያ፣ ካንተ እንደትለየሁ በቀጥታ ወደሱ እልሄድም፡፡ በፊት ሌላጋ እደርሳለሁ። እና እሱጋ ስሄድ የሌላ ወንድ ላብ ነክቶኛል፣ ጠረኔ የብቻዬ ሳይሆን ከጎረምሳ ጠረን ጋር ተቀላቅሏል። አሁንም ልብሴን ያስወልቀኝና ያቅፈኛል፤ ግን እንደነብር ይሆናል፣ ይጨፈልቀኛል፣ ይነክሰኛል።
ስለሌላ ወንድ አንነጋገርም ግን ሌላጋ እንደነበርኩ በማወቁ የበለጠ እንደሚጣፍጠው ግልፅ ነው፡፡ ይታይሀል?"
«በሚገባ! እና እኔ እንዲህ የምሆንበት ምክንያቱ ምን
ይመስልሻል?» ቀላል ነው። አንደኛ፣ ሌላ ወንድ ከተኛኝ ቆንጆ ነኝ ማለት ነው። ብዙዎች ከተኙኝ እጅግ በጣም ቆንጆ ነኝ፡፡ ስለዚህ የቀለጠ ትፈልገኛለህ፡፡ ሁለተኛ፣ ሌላው ተኝቶኝ አንተ ቀጥለህ ከተኛኸኝ፣ ከሱ ቀምተህ ወሰድከኝ ማለት ነው:: እኔ በሀይል ቆንጆ ሆኜ ከሌሎቹ ሁሉ ቀምተህ ከወሰድከኝ፣ ከሌሎቹ ሁሉ የበለጠ ወንድ ነህ።በወንድነት ከሁሉ በላይ ሆንክ፣ ስለዚህ ደስ ይልሀል፡፡ በጣም ደስ ይልሀል። ወንዶች ሁላችሁም እንደሱ ናችሁ። ግን አየችኝ..
«ግን ምን?» አልኳት
አብዛኛዎቹ ወንዶች ውጪውን ጎበዝ ቢመስሉም ውስጡን ፈሪ
ናቸው፡፡ የውስጥ ስሜታቸውን አይተው መቀበል ይፈራሉ። ስለዚህ ከራሳቸው ይደብቁታል። ሁሉም ወንድ አብዛኛው ወንድ ልበል የራሱን ሴት ሌሎች ሲቀምሱበትና እሱ ነጥቋቸው መልሶ የራሱ ሲያረጋት፣ የበለጠ ወንድነት ይሰማዋል። በሀይል ደስ ይለዋል። ግን ይህን እንደ ጉድ አርጎ ስለሚቆጥረውና ስለሚያፍርበት፣ እያየውም
አውቆ አይኑን ይጨፍናል። ስለዚህ ያስመስላል፤ ያስመስላል፡
ያስመስላል። አቤት ስንት ማስመሰል አለ!
«እዚህ ላይ ነው አንተን ከልቤ የማደንቅህ፡፡ እቺን
ያህል አትፈራም። ወደነብስህ ውስጥ አትኩረህ ትመለከታለህ፡፡ እዚያ ውስጥ ምንም ቀፋፊ ነገር ብታይ አይንህን አትጨፍንም፡፡ ስለዚህ ያለማስመሰል ትኖራለህ ውስጣዊውን ኑሮ ማለቴ ነው። እንግዲህ ወደ ውስጥህ ተመለከትክ፣ ውስጥህ እኔን ሌሎች ቢተኙኝ ከነሱ
ቀምተህ ስትተኛኝ ደስ እንደሚለው ነገረህ። ስለዚህ እኔን 'ሂጂ ወንዶችሽ ጋ አልከኝ። ሄድኩ፡፡ ተመለስኩ። ተደሰትክብኝ፡፡ ወንድ
ነህ። አንተ እውነተኛ ወንድ የሆንከውን ያህል እኔ እውነተኛ ሴት ሆኜ እንደሆነ እጅግ ኩራት ይሰማኛል።»
«አንቺ እንደምትይኝ ከሆንኩ፣ አንቺም እንደኔ አይነት ነሽ።
ልክ እንደኔ አይነት! አብዛኛዎቹ ሴቶች፣ ፍቅር ከያዘኝ ወንድ ጋር
ብቻ ነው ግብረ ስጋ ደስ የሚለኝ ይላሉ። ይህም ማስመሰል፣
ማስመሰል፣ ማስመሰል ነው። አንቺ ግን ለራስሽ አትዋሺም። ቆንጆ ወጣት ሆኖ ቆንጆ ወንድ እያቀያየሩ መደሰት እንዴት ያለ ገነት ነው!' ትያለሽ። እኔኮ አልችልም፣ ቆንጆ ወንድ ሳይ አያስችለኝም፣ቁንጅናውን መንካት መዳሰስ አለብኝ፣ በወጣትነቱ መደሰት አለብኝ ትያለሽ
“አንድ ቀን አንድ ነገር አልሽኝ። አስከመቼም አልረሳውም፡፡»
«ምን አልኩህ?»
👍23👎1