#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
....“ ምናገባህ ? ሞዛዛ ?" ስትለው ድምጿ የብሽቀት ቅላጺ ነበረው ።
“እውነት ብርቄ ፥ ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ?” አላት ሳምሶን?
"አራት ዓመት!”
"የአራት ዓመት የሥራ ልምድ ! ከሌሎቹ አንጻር ሲታይ ትንሽ ነው ” እላት ሳምሶን "
“ መላጣ ! ” አለችው ፡ ጭንቅላቱን በዐይኗ ቂጥ እያየችው ።
“ በአራት ዓመት ውስጥ ስምሽን ለመለወጥ አልሞክርሽም ? ”አላት እስክንድር ሲቀልድባት ፡ “ እዲስ የከተማ
ስም እንደ ራሄል ኤደን ማርታ ፡ ዓለም ከተሜ ለመሆን እ ? ”
“ሒድ'ደረቅ ! ”
ሒድ፡ደረቅ !ሒድ፡ደረቅ!ደረቅ ማርታ በቅናት ቅንድቧን እያርገበገበች ከፊቱ ድቅን አለችበት ። በሐሳቡ ቁመናዋን ቃኘ በሞቅታ መንፈስ እንደገና አለማት ፡ ኪሱ ባዶ ማለም ብቻ ! ማነጣጠር ብቻ !
"ሒድ ፡ ደረቅ የሴቶች የጋራ ፈሊጽ ” አለ በልቡ ።
የብርቅነሽ ጥሬነት አስገረመው ፡ ስትጫወት የባላገር ለዛ አላት ። ንቅሳቷ ባላገርነቷን ይመሰክራል የባላገር ስሟን
አልለወጠችም " እምብዛም የከተሜ ጭምብል አላጠለቀችም ግን ከሀገርሽ ለምን ወጣሽ ? ” አላት በድንገት ።
“ ሆሆይ !ጋዜጠኛ ነህ እንዴ ?”
ባልሆን ፥ ይህን ሥራ ምን አስመረጠሽ ፡ ማለቴ ነው ። ””
“ ዋ ! ወድጄን መሰለህ ? ግድ ሆኖብኝ እንጂ ” ከማለቷ ፊቷ የኀዘን ጭጋግ ለበሰ
“ ምነው ?እንዴ? ” አላት እስክንድር ስሜቷን ተከትሎ ስሜቱ እየዳመነ።
“ ባልተቤቴ ነው ለነዚ ያበቃኝ ! በሱ ምክንያት ነው ሀገሬን ለቅቄ የወጣሁት እያለች የታሪኳ ዳር ዳር ጨረፈችው
በፍቅር ለቀረባት ሁሉ ታሪኳን ታወራለች
ልስ ልስ ሆኖ ለቀረባት የአንጀቷን ትዘከዝካለች የተማረ መስሎ ለታያት ችግሯን አፍረጥርጣ ትናገራለች ። መፍትሔ ይገኝልኛል ብላ አይደለም :: የውስጧን ተንፍሳ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን የመንፈስ እረፍት ታገኛለች።
«« እባክሽ አታጓጊን ፣ በደንብ አጫውቺን" አላት እስክንድር ታሪኳን ለመስማት ተጣድፎ።
“ አያችሁ እናንተ ዕድለኞች ናችሁ : ከደኅና ቤተሰብ በመወለዳችሁ ወይም ከተማ በማደጋችሁ ለመማር በቅታችሆል እኔ የቀለም ትምህርት የለኝም ማንበብና መፃፍ እንኳ የቻልኩት አሁን የመሰረተ ትምህርት ዘመቻ ከተጀመረ ወዲህ ነው።
የድሀ ገበሬ ልጅ ነኝ ። ያውም በእንጀራ
እናት ያደግኩ !ህም እቴ! ታድያ በአሥራ አራት ዓመቴ ተዳርኩ ። ባሌ ገበሬ ነበር ። እኔ ሁለተኛ ሚስቱ ነኝ ።የመጀመሪያ ሚስቱ ከተጋቡ መንፈቅ እንኳ ሳይሞላቸው ሞታበት ነበር ። ወላጆቼም ሲድሩኝ ይህን ያቃሉ በእድሜ በሰል ያለ ነው ። ጸባዩም ጥሩ ነው ለትዳሩ ታታሪ ነው ” ተባለና ተሰጠሁ ።
“ ጎጆአችንን እያሞቅን ፡ የባላባቶችን ግልምጫና ዱላ በጋራ እየተቀበልን መኖር ጀመርን ፡ ምን ይሆናል ። እግዜር ለትንኮሉ ማሕፀኔን ድፍን እደረገው። ዓመት ጠበቅን ሁለት ዓመት ጠበቅን ልጅ የለም ። በእኔና በባልተቤቴ መሐል ቅሬታ መጣ ያም ሆኖ አልተቃቃርንም ። ድህነት ያስተሳስረን ነበር ። እሱ ከገበሬዎቹ ጋር ውጭ ደክሞ ውሎ ሲመጣ ከቤት ያለሁ
ረዳቱ እኔው ነበርኩ በባላባት ጅራፍ ጀርባው ቆስሎ ሲመጣ አንጀቴ እየተንሰፈሰፈ የማለቅስላት እኔ ነበርኩ ዋ! እቴ ምን ያደርጋል!
እንዲህ እንዲህ እያልን አምስት ዓመት ያህል እንደኖርን አብዮቱ ፈነዳ ። ለውጥ መጣ ። ደክመን ለባላበት መገበሩ ቀረ። እፎይ አለን ። ቤታችን ሙሉ ሆነ እውነቴን ነው ደህና ነገር መብላት መልበስም ጀመርን ። ምን ይሆናል ። ከድህና
ኑሮ ጋር ተያይዞ ነገር መጣ ባልተቤቴ ሌላ ሴት ጋር በስርቆት መሔድ ጀምሯል የሚል ወሬ ሰማሁ ። ስውል ሳድር እኔም
ነገሩን ደረስኩበት። እንዲያውም አንድ ልጅ እንደ ወለደችለት አረጋገጥኩ ። ቀናሁ ! ቅናት አንገበገበኝ ። በሐሳብ
ተብከነከንኩ። ጨስኩ ።ቤት ውስጥ !
መቀመጥ አቃተኝ ብዙም ሳልቆይ ጓዝ ምንጓዝ ሳልል በርሬ ወጥቼ አዲስ አበባ ገበኋት !
“ እዚህ ስደርስ ደግሞ ያዘጋጀሁት ማረፊያ የለኝ ፥ እንደሁ ሜዳ ቀረሁ ። ትንሽ ቀን ሰንብቼ በደላላ አማካይነት
ግርድና ተቀጠርኩ። ስድስት ወር እንደ ሰራሁ ግርድናን እርም ብዬ ተውኩት። አባስኩ እቴ ! የሰው ቤት ሹሮ ሲያልቅ
እኔ ላይ ማፍጠጥ ። ዕቃ ሲጠፉ እኔን መወንጀል ። ምነው ከዚህ ሁሉ ሥጋዬን ሸጨ ባድር አልኩና ሽርሙጥና ጀመርኩ
እላችኋለሁ ።
ብርቅነሽ ስትናገር ታላቅ ማዕበል ተነሥቶ ባሕር ውስጥ የከታቸውን ያኸል ሥስቱም ጸጥ ብለው ነበር ። አሳዘነቻቸው። ምስኪን ጥሬ ፍጥረት ! በመጠጥ ሞቅታ ኃይል ለሁሉ ነገር ግዴለሽ ሆኖ የቆየው አቤል እንኳ፥ ከብርቅነሽ አፍ የድህነት ድምፅ ሲሰማ ቸል ማለት አልቻለም ። ሕዋሳቱ በኀዘን ስሜት ተወራጩ ::
ግን ዝዎም ብለሽ ከምትኮበልይ ፥ ሰላምን በአካባቢሽ በሚገኘው የሴቶች ወይም የገበሬ ማኅበር አመልክተሽ መፍ
ትሔ ኣትፈልጊም ነበር ? ” እላት እስክንድር ፡ ከማዘኑ የተነሣ የሚናገረው ጠፍቶት ።
ዋ እቴ ! ቤት ከፈረሰ ወዲያ ሁሉስ ምን ሊበጅ ? አየህ ፡ ቅናት ከመጣ ቤት ፈረሰ ማለት ነው። ለሁሉም እኔ ለማንም አላማከርኩ ። የሚያለቅሱ ልጆች የሉኝ ' ነጠላ ሰው ምናለበት አልኩና ብር ብዬ አዲስ አበባ ፣ ”
ታዲያ ባልሽ ሊፈልግሽ አልመጣም ” አላትአቤል በሁኔታዋ ስሜቱ ተነክቶ ።
“ ውእእይ • ሥራ አጥቶ ! እንዲያውም ከዚያ ሀገር ለንፀግድ የሚመላለሱ ሰዎች እዚሁ ቡና ቤት አግኝቼ ሲነግሩኝ' ውሽማውን ጠቅልሎ ይዟል አሉኝ • እዩዬ ! ” ብላ ሳትጨርስ ጥሬ ሰማች «
“ ብርቅነሽ ? ! አንቺን'ኮ ነው ? ” የቡና ቤት ባለቢቷ ድምፅ ነበር
“ እመት ! ወይ ጕዱ ዛሬ ! ” እያለች ብርቅነሽ ከተቀመጠችበት ተነሣች
“ እንድዩ ! ሰው ሲገባ አትታዘዥም እንዴ! ምን ይጎልትሻል ? ”
ብርቅነሽ የውስጧን ተንፍሳ ቃጠሎዎን አብርዳ ተነሣች ፡ እስክንድር ተከዘ ቃጠሉዋ ወደ እሱ ተላለፈበት ኀዘኗ ጠልቆ ወጋው ። ቅናት ተፈጥሮአዊ ነው ሀብታምና ድሀ አይልም ። የወደደ ሁሌ ለወደደው ነገር ይቀናል ። ለቀናበት ነገር ይሠዋል ። ብርቅነሽ የቅናትን እሳት ሸሽታ ኮበለለች ። ከቅናት ሸሽታ ሴትኛ አዳሪ ሆነች "
እስክንድር ሐሳቡ ከግላዊነት ወደነማኅበራዊነት መጠቀ ለእሱ ሲጋራ መግዣ መስጠት ያቃታቸው ደሀ እናቱ ላይ ሆኑ፡ሕዝቧን በሰፊው ማስተማር ' በቂ ኢንዱስትሪ ከፍታ እነብርቅነሽን ማሠማራት ያልቻለች ረሀብን ለማጥፋት
ማይምነትን ለማጥፋት ርካሽ ልምዶችን ለማስወገድ በባህል ለማደግና የቴክኖሎጂ ውጤት ተጠቃሚ ለመሆን የልጆቿን እጅ የምትማጠን እናት ሀገር፡እጆቿን ዘርግታ በሐሳቡ ታየችው
ከሐሳቡ ፋታ አግኝቶ እሱነቱን ወዳለበት ሲመልስ ምሶን ዐይኑን አፍጥጦ ተመለከተ ።አስተያየቱ አላማረውም ። በልቡ ምርምርህን እዚያው ዩኒቨርስቲው ውስጥ አድርገው ፥ ይሄ መጠጥ ቤት ነው የሚለው መሰለው "
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
....“ ምናገባህ ? ሞዛዛ ?" ስትለው ድምጿ የብሽቀት ቅላጺ ነበረው ።
“እውነት ብርቄ ፥ ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ?” አላት ሳምሶን?
"አራት ዓመት!”
"የአራት ዓመት የሥራ ልምድ ! ከሌሎቹ አንጻር ሲታይ ትንሽ ነው ” እላት ሳምሶን "
“ መላጣ ! ” አለችው ፡ ጭንቅላቱን በዐይኗ ቂጥ እያየችው ።
“ በአራት ዓመት ውስጥ ስምሽን ለመለወጥ አልሞክርሽም ? ”አላት እስክንድር ሲቀልድባት ፡ “ እዲስ የከተማ
ስም እንደ ራሄል ኤደን ማርታ ፡ ዓለም ከተሜ ለመሆን እ ? ”
“ሒድ'ደረቅ ! ”
ሒድ፡ደረቅ !ሒድ፡ደረቅ!ደረቅ ማርታ በቅናት ቅንድቧን እያርገበገበች ከፊቱ ድቅን አለችበት ። በሐሳቡ ቁመናዋን ቃኘ በሞቅታ መንፈስ እንደገና አለማት ፡ ኪሱ ባዶ ማለም ብቻ ! ማነጣጠር ብቻ !
"ሒድ ፡ ደረቅ የሴቶች የጋራ ፈሊጽ ” አለ በልቡ ።
የብርቅነሽ ጥሬነት አስገረመው ፡ ስትጫወት የባላገር ለዛ አላት ። ንቅሳቷ ባላገርነቷን ይመሰክራል የባላገር ስሟን
አልለወጠችም " እምብዛም የከተሜ ጭምብል አላጠለቀችም ግን ከሀገርሽ ለምን ወጣሽ ? ” አላት በድንገት ።
“ ሆሆይ !ጋዜጠኛ ነህ እንዴ ?”
ባልሆን ፥ ይህን ሥራ ምን አስመረጠሽ ፡ ማለቴ ነው ። ””
“ ዋ ! ወድጄን መሰለህ ? ግድ ሆኖብኝ እንጂ ” ከማለቷ ፊቷ የኀዘን ጭጋግ ለበሰ
“ ምነው ?እንዴ? ” አላት እስክንድር ስሜቷን ተከትሎ ስሜቱ እየዳመነ።
“ ባልተቤቴ ነው ለነዚ ያበቃኝ ! በሱ ምክንያት ነው ሀገሬን ለቅቄ የወጣሁት እያለች የታሪኳ ዳር ዳር ጨረፈችው
በፍቅር ለቀረባት ሁሉ ታሪኳን ታወራለች
ልስ ልስ ሆኖ ለቀረባት የአንጀቷን ትዘከዝካለች የተማረ መስሎ ለታያት ችግሯን አፍረጥርጣ ትናገራለች ። መፍትሔ ይገኝልኛል ብላ አይደለም :: የውስጧን ተንፍሳ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን የመንፈስ እረፍት ታገኛለች።
«« እባክሽ አታጓጊን ፣ በደንብ አጫውቺን" አላት እስክንድር ታሪኳን ለመስማት ተጣድፎ።
“ አያችሁ እናንተ ዕድለኞች ናችሁ : ከደኅና ቤተሰብ በመወለዳችሁ ወይም ከተማ በማደጋችሁ ለመማር በቅታችሆል እኔ የቀለም ትምህርት የለኝም ማንበብና መፃፍ እንኳ የቻልኩት አሁን የመሰረተ ትምህርት ዘመቻ ከተጀመረ ወዲህ ነው።
የድሀ ገበሬ ልጅ ነኝ ። ያውም በእንጀራ
እናት ያደግኩ !ህም እቴ! ታድያ በአሥራ አራት ዓመቴ ተዳርኩ ። ባሌ ገበሬ ነበር ። እኔ ሁለተኛ ሚስቱ ነኝ ።የመጀመሪያ ሚስቱ ከተጋቡ መንፈቅ እንኳ ሳይሞላቸው ሞታበት ነበር ። ወላጆቼም ሲድሩኝ ይህን ያቃሉ በእድሜ በሰል ያለ ነው ። ጸባዩም ጥሩ ነው ለትዳሩ ታታሪ ነው ” ተባለና ተሰጠሁ ።
“ ጎጆአችንን እያሞቅን ፡ የባላባቶችን ግልምጫና ዱላ በጋራ እየተቀበልን መኖር ጀመርን ፡ ምን ይሆናል ። እግዜር ለትንኮሉ ማሕፀኔን ድፍን እደረገው። ዓመት ጠበቅን ሁለት ዓመት ጠበቅን ልጅ የለም ። በእኔና በባልተቤቴ መሐል ቅሬታ መጣ ያም ሆኖ አልተቃቃርንም ። ድህነት ያስተሳስረን ነበር ። እሱ ከገበሬዎቹ ጋር ውጭ ደክሞ ውሎ ሲመጣ ከቤት ያለሁ
ረዳቱ እኔው ነበርኩ በባላባት ጅራፍ ጀርባው ቆስሎ ሲመጣ አንጀቴ እየተንሰፈሰፈ የማለቅስላት እኔ ነበርኩ ዋ! እቴ ምን ያደርጋል!
እንዲህ እንዲህ እያልን አምስት ዓመት ያህል እንደኖርን አብዮቱ ፈነዳ ። ለውጥ መጣ ። ደክመን ለባላበት መገበሩ ቀረ። እፎይ አለን ። ቤታችን ሙሉ ሆነ እውነቴን ነው ደህና ነገር መብላት መልበስም ጀመርን ። ምን ይሆናል ። ከድህና
ኑሮ ጋር ተያይዞ ነገር መጣ ባልተቤቴ ሌላ ሴት ጋር በስርቆት መሔድ ጀምሯል የሚል ወሬ ሰማሁ ። ስውል ሳድር እኔም
ነገሩን ደረስኩበት። እንዲያውም አንድ ልጅ እንደ ወለደችለት አረጋገጥኩ ። ቀናሁ ! ቅናት አንገበገበኝ ። በሐሳብ
ተብከነከንኩ። ጨስኩ ።ቤት ውስጥ !
መቀመጥ አቃተኝ ብዙም ሳልቆይ ጓዝ ምንጓዝ ሳልል በርሬ ወጥቼ አዲስ አበባ ገበኋት !
“ እዚህ ስደርስ ደግሞ ያዘጋጀሁት ማረፊያ የለኝ ፥ እንደሁ ሜዳ ቀረሁ ። ትንሽ ቀን ሰንብቼ በደላላ አማካይነት
ግርድና ተቀጠርኩ። ስድስት ወር እንደ ሰራሁ ግርድናን እርም ብዬ ተውኩት። አባስኩ እቴ ! የሰው ቤት ሹሮ ሲያልቅ
እኔ ላይ ማፍጠጥ ። ዕቃ ሲጠፉ እኔን መወንጀል ። ምነው ከዚህ ሁሉ ሥጋዬን ሸጨ ባድር አልኩና ሽርሙጥና ጀመርኩ
እላችኋለሁ ።
ብርቅነሽ ስትናገር ታላቅ ማዕበል ተነሥቶ ባሕር ውስጥ የከታቸውን ያኸል ሥስቱም ጸጥ ብለው ነበር ። አሳዘነቻቸው። ምስኪን ጥሬ ፍጥረት ! በመጠጥ ሞቅታ ኃይል ለሁሉ ነገር ግዴለሽ ሆኖ የቆየው አቤል እንኳ፥ ከብርቅነሽ አፍ የድህነት ድምፅ ሲሰማ ቸል ማለት አልቻለም ። ሕዋሳቱ በኀዘን ስሜት ተወራጩ ::
ግን ዝዎም ብለሽ ከምትኮበልይ ፥ ሰላምን በአካባቢሽ በሚገኘው የሴቶች ወይም የገበሬ ማኅበር አመልክተሽ መፍ
ትሔ ኣትፈልጊም ነበር ? ” እላት እስክንድር ፡ ከማዘኑ የተነሣ የሚናገረው ጠፍቶት ።
ዋ እቴ ! ቤት ከፈረሰ ወዲያ ሁሉስ ምን ሊበጅ ? አየህ ፡ ቅናት ከመጣ ቤት ፈረሰ ማለት ነው። ለሁሉም እኔ ለማንም አላማከርኩ ። የሚያለቅሱ ልጆች የሉኝ ' ነጠላ ሰው ምናለበት አልኩና ብር ብዬ አዲስ አበባ ፣ ”
ታዲያ ባልሽ ሊፈልግሽ አልመጣም ” አላትአቤል በሁኔታዋ ስሜቱ ተነክቶ ።
“ ውእእይ • ሥራ አጥቶ ! እንዲያውም ከዚያ ሀገር ለንፀግድ የሚመላለሱ ሰዎች እዚሁ ቡና ቤት አግኝቼ ሲነግሩኝ' ውሽማውን ጠቅልሎ ይዟል አሉኝ • እዩዬ ! ” ብላ ሳትጨርስ ጥሬ ሰማች «
“ ብርቅነሽ ? ! አንቺን'ኮ ነው ? ” የቡና ቤት ባለቢቷ ድምፅ ነበር
“ እመት ! ወይ ጕዱ ዛሬ ! ” እያለች ብርቅነሽ ከተቀመጠችበት ተነሣች
“ እንድዩ ! ሰው ሲገባ አትታዘዥም እንዴ! ምን ይጎልትሻል ? ”
ብርቅነሽ የውስጧን ተንፍሳ ቃጠሎዎን አብርዳ ተነሣች ፡ እስክንድር ተከዘ ቃጠሉዋ ወደ እሱ ተላለፈበት ኀዘኗ ጠልቆ ወጋው ። ቅናት ተፈጥሮአዊ ነው ሀብታምና ድሀ አይልም ። የወደደ ሁሌ ለወደደው ነገር ይቀናል ። ለቀናበት ነገር ይሠዋል ። ብርቅነሽ የቅናትን እሳት ሸሽታ ኮበለለች ። ከቅናት ሸሽታ ሴትኛ አዳሪ ሆነች "
እስክንድር ሐሳቡ ከግላዊነት ወደነማኅበራዊነት መጠቀ ለእሱ ሲጋራ መግዣ መስጠት ያቃታቸው ደሀ እናቱ ላይ ሆኑ፡ሕዝቧን በሰፊው ማስተማር ' በቂ ኢንዱስትሪ ከፍታ እነብርቅነሽን ማሠማራት ያልቻለች ረሀብን ለማጥፋት
ማይምነትን ለማጥፋት ርካሽ ልምዶችን ለማስወገድ በባህል ለማደግና የቴክኖሎጂ ውጤት ተጠቃሚ ለመሆን የልጆቿን እጅ የምትማጠን እናት ሀገር፡እጆቿን ዘርግታ በሐሳቡ ታየችው
ከሐሳቡ ፋታ አግኝቶ እሱነቱን ወዳለበት ሲመልስ ምሶን ዐይኑን አፍጥጦ ተመለከተ ።አስተያየቱ አላማረውም ። በልቡ ምርምርህን እዚያው ዩኒቨርስቲው ውስጥ አድርገው ፥ ይሄ መጠጥ ቤት ነው የሚለው መሰለው "
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
እነሱ ለትህትና ሕይወት እንደዚያ ሲሯሯጡ ደግሞ የእንደሻው ወላጆች ደግሞ የልጃቸውን ህይወት ለማትረፍ ከላይ ከተች እየተሯሯጡም ብቻ ሳይሆን እየተራወጡ ናቸው። የእንደሻው ጉዳት ከባድ ነበር። በተለይ አንዷ ጥይት የራስ ቅሉን በስታው ስላለፈች፤ የአእምሮ ቀውስ
እንዳያስከትልበት፤ ከፍተኛ ስጋት አለ፡፡
በተፈጠረው አደጋ ምክንያት የእንደሻው ወላጆችና የአዜብ ወላጆችም ግንኙነት አቋርጠዋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ...
"ያቺን የተረገመች ልጅ አምጥታ ልጃችንን ልታስገድለው የነበረችው አዜብ ነች በሚል ሲሆን፤ ፀቡን ከአዜብ ጋር ብቻ ሳይሆን ከቤተሰቦቿ ጭምር አድርገውታል :: እነሱ እንደዚያ ብለው ይናገሩ እንጂ ፤ የአዜብ ወላጆች ሁኔታው ሊፈጠር የቻለው አለሌው ልጃቸው
በፈፀመው ተደጋጋሚ አስነዋሪ ድርጊት ሳቢያ መሆኑን ሲያውቁ የክርስትና ልጃችን ነው በሚል ምክንያት ብቻ ፤ በትህትና ላይ ሊፈርዱባት
አልደፈሩም....
"ሁሉንም ስራው ያውጣው በማለት መጨረሻውን ለማየት እየተጠባበቁ ናቸው፡፡ ትህትና ጤናዋ በከፍተኛ ፍጥነት እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም፤ ጐን ለጐን በነፍስ ማጥፋት ሙከራ ወንጀል በአቃቤ ህግ ክስ ተመሰረተባት፡፡ አዜብና ብሩክ ይህንን እንዳወቁ ቀጣዩ ትኩረታቸው
በምን ላይ መሆን እንዳለበት በስፋት ተመካከሩ፡፡ ከዚያም አንዳንድ
በመከላከያነት ይጠቅማሉ ያሏቸውን ማስረጃዎች ለማሰባሰብ ፤ ሁለቱም
በየፊናቸው ሩጫ ጀመሩ፡፡ ለዚህ ጉዳይ አበራ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገመቱ :: ምክንያቱም አበራ በእንደሻው ክህደት የደረሰበትና፤ በትህትና ላይ ስለተፈፀመው ወንጀል በሚገባ የሚያውቅ የአይን ምስክር ስለነበረ ነው፡፡ አበራ በእንደሻው ስለተፈፀመበት ክህደት ለአገሩ ሁሉ ሲያወራ ለአዜብም አጫውቷት ነበር ፡፡
ከዝምድና ይልቅ ገንዘብን አስበልጦ አስር
አመት ሙሉ ያጠራቀምኩትን ገንዘቤን ወስዶ ከከበረበት በኋላ ከዳኝ፡፡ በጋራ
እናድግበታለን ብሎ የገባውን ቃሉን አፍርሶ አባረረኝ " በማለት በምሬት ነበር የገለፀላት፡፡ ታዲያ ያ ሁሉ በደል የተፈፀመበት ሰው ፍርድ ቤት ቀርቦ እውነቱንና የሚያውቀውን ከመናገር ወደኋላ ሊል ይችላል? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ በፍፁም ወደኋላ አይልም ስትል ተማመነች፡፡ምክንያቱም እሱ እንደዚያ በንዴት እየተንቀጠቀጠ
ሲነግራት...
“አይዞህ አበራ ተወው፡፡ አንተ ጤና ሁን እንጂ ፤ገንዘብ አላፊ ጠፊ ነው፡፡ በክህደት የተገኘ ገንዘብ ደግሞ የትም አያደርስም፡፡
ከሰራህ ከካደህ ሰው በላይ መሆን ትችላለህ :: አይዞህ! እግዚአብሄር ላንተ ያለውን ምንግዜም አታጣውም " በማለት ትልቅ የማፅነኛ ቃል ለግሳው ነበር፡፡ ያንን
የሰጠችውን የተስፋ ቃል እንኳ አስታውሶ እሺ ይላት ይሆን? ወይንስ እሱም እንደወላጆቹ ተደርቦ ከእውነት ጀርባ ይቆም ይሆን? ልቧ ተጠራጠረ፡፡ ለማንኛውም አለችና ስልክ ደወለችለት :: ስልኩን አነሳና እሷ መሆንዋን ሲያውቅ የሞቀ ሰላምታ አቀረበላት፡፡ ትንሽ እፎይ አለች በልቧ፡፡ለጉዳይ እንደምትፈልገው
ስትገልፅለት፤ በደስታ ተቀብሎ የሚገናኙበትን ቦታ ተቀጣጥረው
ተሰነባበቱ፡፡ በማግስቱ በቀጠሮው ቦታ ቀድሞ የደረሰው እሱ ነበር።
የተፈለገበትን ጉዳይ ስትነግረው...
"ተይ እንጂ አዜብ እቤት ድረስ የወሰድኳት እኮ እኔ ነኝ፡፡በወንጀለኛነት አያስጠይቅህም ነው የምትይኝ?" ሲል በጥርጣሬ ጠየቃት።
"ስለሱ ከሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል፡፡ አንተን በወንጀል
ተባባሪነት እንዳያስጠይቅህ በቂ ምክንያት ማቅረብ ይቻላል፡፡”
"ለምሳሌ ምን?"
"አበራ ሙት ምንም አትፍራ! በዚህ ጉዳይ አንተ በጥፋተኛነት እንድትጠየቅ የሚፈልግ ሰው የለም፡፡ አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር ፧ አንተ ይዘሃት የሄድከው ወደ ቀጣሪዋ ቤት እንጂ፤ ወንጀል
ወደሚፈጸምበት ጫካ ውስጥ አይደለም፡ቀጣሪዋ ቤት አደረስካት ማለት፤ እንደሻው ደብድቦና፤ አስገድዶ፧ ክብረ ንፅህናዋን እንዲደፍራት አደረክ ማለት አይደለም :: የቀጣሪዋን ቤት የወንጀል መፈፀሚያ ዋሻ ያደረገው ወንጀለኛ ብቻ ነው ለዚህ ተጠያቂ የሚሆነው፡፡ አይዞህ ምንም የሚያስፈራ ነገር የለውም፡ አበራን ለማሳመን ብሎ ብሩክ ያስጠናትን ደሰኮረችለት፡፡ አበራ ልቡ ትንሽ ተለሳለሰ፡፡
"በሌላ በኩል ብታየው ደግሞ የቀጣሪዋ ባለቤት ልጅ የቅጥር ውል እንድትፈርም ይዘሃት ና ብሎ አዘዘህ :: አንተም ይህን ነገርካት። እሷም እሺ ብላ ሳታስገድዳት በፈቃደኝነት አብራህ ሄደች። ከዚያም አንተ በሌለህበት እንደሻው ወንጀል ፈፅሞባት ደረስክ፡፡ በቃ፡፡ ይህ አይደለም
ታሪኩ? አንተን የሚያስጠይቅህ ምኑ ነው ታዲያ?" ስትል የማደፋፈሪያ
ሀሳብ አዥጐደጐደችለት፡፡
በልቡ ያሳደረው ጥርጣሬ ሙሉ ለሙሉ ባይጠፋለትም፤ በአዜብ አቀራረብ ተስማማ፡፡ እንዳለችውም እሱን በቀጥታ ተጠያቂ ሊያደርገው የሚችል ጭብጥ እንደሌለ ተሰማው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ
ያቺ ምስኪን እንጀራ ፈላጊ ልጅ ፤ በደም ተጨማልቃ ወድቃ ያያት እለት የተሰማው ስሜት ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡ በተፈፀመባት ወንጀል ከልቡ አዝኖ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ያ ግፈኛ ከሃዲ ከሱቁ ካባረረው በኋላ አሁን አሁን በርካታ ካፒታል በማንቀሳቀስ በቅናት እያቃጠለው
ነው፡፡ በጥይት መቃጠሉን የሰማ እለት " እሰይ የእጁን ነው ያገኘው"ነበር ያለው፡፡ አሁን ደግሞ እሱ ተጠያቂ በማይሆንበት ሁኔታ ለምን ያየውን ከመመስከር ወደ ኋላ ማለት እንደሌለበት ተገነዘበ ፡፡ያየኽውን እውነት መሰከርክ ብሎ የሚፈርድበት ዘመድ እንደማይኖርና፤ ቢኖርም መፅሀፍ ቅዱስ ይዞ በሚፈፅመው መሃላ በውሸት መስክሮ ነፍሱን ማስኮነን እንደሌለበት ተሰማው። እንደሻውን ሊበቀል
የሚችልበትን ይህንን መልካም አጋጣሚ ሊጠቀምበት ወሰነ : እንቢ ቢልስ የት ሊደርስ ? በተለይ አዜብ እየነገረችው
ያለው ፣ ባለስልጣን ፖሊስ ከአዜብ በስተጀርባ መኖሩን ነው፡፡ በተለይ "ሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል"
ስትለው ምን እያለች እንደሆነ
ገብቶታል፡፡አልመሰክርም ቢል በተባባሪ ወንጀለኛነት ተፈርጆ፣ ለፍርድ እንደሚቀርብ እየነገረችው ነው፡፡ ይሄንን ጭምር አስቦ፤ ልቡ ስለፈራ፤ ያየውን ሁሉ በዝርዝር ሊያስረዳና፤ ለትህትና ድንበሩ የመከላከያ ምስክር ሊሆን ቃል ገባላት፡፡ ቃል መግባት ብቻም ሳይሆን ተጨማሪ ማስረጃ ጠቆማት..
"እኔ ብቻ ሳልሆን በዚያን እለት ሁኔታውን የተመለከተችው የቤት ሰራተኛዋ ወርቅ ያንጥፉም ያየችውን ሁሉ እውነቱን ሳትደብቅ እንድትመሰክር እናደርጋለን :: ደግሞም ትመሰክራለች፡፡ አትጠራጠሪ!
በትህትና ሁኔታ በጣም ነው ያዘነችው፡፡እሷም ስመ እግዚአብሄርን ጠርታ
ያየችውን ሁሉ ትመሰክራለች፡፡ አይዞሽ ! " አላት፡፡ አዜብ ከጠበቀችው በላይ ተባባሪ ሆኖ ስለኣገኘችው፤ በደስታ እቅፍ አደረገችው፡፡ በዚሁ መሰረት አበራና ወርቅ ያንጥፉ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው፤ የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ተደረገ፡፡ ቀኑን፡ ሰአቱን፡ የድርጊቱን አፈፃፀም፡ ዝርዝር ሁኔታውን፤ በሙሉ በአንድ አይነትና ፤ ተመሳሳይ በሆነ ቃል
መሰከሩ። ያም ብቻ ሳይሆን አንዱአለምን ጋርጠው በሚል ቅፅል ስሙ በሚታወቀው ወሮበላ እንዳይሞት፤ እንዳይድን፤ አደርጐ ያስደበደበው
መሆኑን፤ ራሱ እንደሻው በኩራት ሲናገር መስማቱን፧ ጭምር ገለፀ፡፡
በእርግጥም እንደሻው ያንን ለአበራ የተናገረው፤ ይሄ ይመጣብኛል ብሎ ሳይሆን፤ አንተም አርፈህ የማትቀመጥና ወሬ አበዛለሁ የምትል ከሆነ፤ አስወቅጥሀለሁ፤ የሚል ማስጠንቀቂያ ለመስጠት ነበር፡፡ ሆኖም በዚህ አጋጣሚ እንደሻውን የደበደበው ጉልበተኛ
ስለታወቀ፤ ወዲያውኑ ታድኖ እንዲያዝ ሲደረግ ፤ አበራ ማንነቱን በማሳየትና የሚገኝበትን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
እነሱ ለትህትና ሕይወት እንደዚያ ሲሯሯጡ ደግሞ የእንደሻው ወላጆች ደግሞ የልጃቸውን ህይወት ለማትረፍ ከላይ ከተች እየተሯሯጡም ብቻ ሳይሆን እየተራወጡ ናቸው። የእንደሻው ጉዳት ከባድ ነበር። በተለይ አንዷ ጥይት የራስ ቅሉን በስታው ስላለፈች፤ የአእምሮ ቀውስ
እንዳያስከትልበት፤ ከፍተኛ ስጋት አለ፡፡
በተፈጠረው አደጋ ምክንያት የእንደሻው ወላጆችና የአዜብ ወላጆችም ግንኙነት አቋርጠዋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ...
"ያቺን የተረገመች ልጅ አምጥታ ልጃችንን ልታስገድለው የነበረችው አዜብ ነች በሚል ሲሆን፤ ፀቡን ከአዜብ ጋር ብቻ ሳይሆን ከቤተሰቦቿ ጭምር አድርገውታል :: እነሱ እንደዚያ ብለው ይናገሩ እንጂ ፤ የአዜብ ወላጆች ሁኔታው ሊፈጠር የቻለው አለሌው ልጃቸው
በፈፀመው ተደጋጋሚ አስነዋሪ ድርጊት ሳቢያ መሆኑን ሲያውቁ የክርስትና ልጃችን ነው በሚል ምክንያት ብቻ ፤ በትህትና ላይ ሊፈርዱባት
አልደፈሩም....
"ሁሉንም ስራው ያውጣው በማለት መጨረሻውን ለማየት እየተጠባበቁ ናቸው፡፡ ትህትና ጤናዋ በከፍተኛ ፍጥነት እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም፤ ጐን ለጐን በነፍስ ማጥፋት ሙከራ ወንጀል በአቃቤ ህግ ክስ ተመሰረተባት፡፡ አዜብና ብሩክ ይህንን እንዳወቁ ቀጣዩ ትኩረታቸው
በምን ላይ መሆን እንዳለበት በስፋት ተመካከሩ፡፡ ከዚያም አንዳንድ
በመከላከያነት ይጠቅማሉ ያሏቸውን ማስረጃዎች ለማሰባሰብ ፤ ሁለቱም
በየፊናቸው ሩጫ ጀመሩ፡፡ ለዚህ ጉዳይ አበራ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገመቱ :: ምክንያቱም አበራ በእንደሻው ክህደት የደረሰበትና፤ በትህትና ላይ ስለተፈፀመው ወንጀል በሚገባ የሚያውቅ የአይን ምስክር ስለነበረ ነው፡፡ አበራ በእንደሻው ስለተፈፀመበት ክህደት ለአገሩ ሁሉ ሲያወራ ለአዜብም አጫውቷት ነበር ፡፡
ከዝምድና ይልቅ ገንዘብን አስበልጦ አስር
አመት ሙሉ ያጠራቀምኩትን ገንዘቤን ወስዶ ከከበረበት በኋላ ከዳኝ፡፡ በጋራ
እናድግበታለን ብሎ የገባውን ቃሉን አፍርሶ አባረረኝ " በማለት በምሬት ነበር የገለፀላት፡፡ ታዲያ ያ ሁሉ በደል የተፈፀመበት ሰው ፍርድ ቤት ቀርቦ እውነቱንና የሚያውቀውን ከመናገር ወደኋላ ሊል ይችላል? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ በፍፁም ወደኋላ አይልም ስትል ተማመነች፡፡ምክንያቱም እሱ እንደዚያ በንዴት እየተንቀጠቀጠ
ሲነግራት...
“አይዞህ አበራ ተወው፡፡ አንተ ጤና ሁን እንጂ ፤ገንዘብ አላፊ ጠፊ ነው፡፡ በክህደት የተገኘ ገንዘብ ደግሞ የትም አያደርስም፡፡
ከሰራህ ከካደህ ሰው በላይ መሆን ትችላለህ :: አይዞህ! እግዚአብሄር ላንተ ያለውን ምንግዜም አታጣውም " በማለት ትልቅ የማፅነኛ ቃል ለግሳው ነበር፡፡ ያንን
የሰጠችውን የተስፋ ቃል እንኳ አስታውሶ እሺ ይላት ይሆን? ወይንስ እሱም እንደወላጆቹ ተደርቦ ከእውነት ጀርባ ይቆም ይሆን? ልቧ ተጠራጠረ፡፡ ለማንኛውም አለችና ስልክ ደወለችለት :: ስልኩን አነሳና እሷ መሆንዋን ሲያውቅ የሞቀ ሰላምታ አቀረበላት፡፡ ትንሽ እፎይ አለች በልቧ፡፡ለጉዳይ እንደምትፈልገው
ስትገልፅለት፤ በደስታ ተቀብሎ የሚገናኙበትን ቦታ ተቀጣጥረው
ተሰነባበቱ፡፡ በማግስቱ በቀጠሮው ቦታ ቀድሞ የደረሰው እሱ ነበር።
የተፈለገበትን ጉዳይ ስትነግረው...
"ተይ እንጂ አዜብ እቤት ድረስ የወሰድኳት እኮ እኔ ነኝ፡፡በወንጀለኛነት አያስጠይቅህም ነው የምትይኝ?" ሲል በጥርጣሬ ጠየቃት።
"ስለሱ ከሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል፡፡ አንተን በወንጀል
ተባባሪነት እንዳያስጠይቅህ በቂ ምክንያት ማቅረብ ይቻላል፡፡”
"ለምሳሌ ምን?"
"አበራ ሙት ምንም አትፍራ! በዚህ ጉዳይ አንተ በጥፋተኛነት እንድትጠየቅ የሚፈልግ ሰው የለም፡፡ አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር ፧ አንተ ይዘሃት የሄድከው ወደ ቀጣሪዋ ቤት እንጂ፤ ወንጀል
ወደሚፈጸምበት ጫካ ውስጥ አይደለም፡ቀጣሪዋ ቤት አደረስካት ማለት፤ እንደሻው ደብድቦና፤ አስገድዶ፧ ክብረ ንፅህናዋን እንዲደፍራት አደረክ ማለት አይደለም :: የቀጣሪዋን ቤት የወንጀል መፈፀሚያ ዋሻ ያደረገው ወንጀለኛ ብቻ ነው ለዚህ ተጠያቂ የሚሆነው፡፡ አይዞህ ምንም የሚያስፈራ ነገር የለውም፡ አበራን ለማሳመን ብሎ ብሩክ ያስጠናትን ደሰኮረችለት፡፡ አበራ ልቡ ትንሽ ተለሳለሰ፡፡
"በሌላ በኩል ብታየው ደግሞ የቀጣሪዋ ባለቤት ልጅ የቅጥር ውል እንድትፈርም ይዘሃት ና ብሎ አዘዘህ :: አንተም ይህን ነገርካት። እሷም እሺ ብላ ሳታስገድዳት በፈቃደኝነት አብራህ ሄደች። ከዚያም አንተ በሌለህበት እንደሻው ወንጀል ፈፅሞባት ደረስክ፡፡ በቃ፡፡ ይህ አይደለም
ታሪኩ? አንተን የሚያስጠይቅህ ምኑ ነው ታዲያ?" ስትል የማደፋፈሪያ
ሀሳብ አዥጐደጐደችለት፡፡
በልቡ ያሳደረው ጥርጣሬ ሙሉ ለሙሉ ባይጠፋለትም፤ በአዜብ አቀራረብ ተስማማ፡፡ እንዳለችውም እሱን በቀጥታ ተጠያቂ ሊያደርገው የሚችል ጭብጥ እንደሌለ ተሰማው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ
ያቺ ምስኪን እንጀራ ፈላጊ ልጅ ፤ በደም ተጨማልቃ ወድቃ ያያት እለት የተሰማው ስሜት ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡ በተፈፀመባት ወንጀል ከልቡ አዝኖ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ያ ግፈኛ ከሃዲ ከሱቁ ካባረረው በኋላ አሁን አሁን በርካታ ካፒታል በማንቀሳቀስ በቅናት እያቃጠለው
ነው፡፡ በጥይት መቃጠሉን የሰማ እለት " እሰይ የእጁን ነው ያገኘው"ነበር ያለው፡፡ አሁን ደግሞ እሱ ተጠያቂ በማይሆንበት ሁኔታ ለምን ያየውን ከመመስከር ወደ ኋላ ማለት እንደሌለበት ተገነዘበ ፡፡ያየኽውን እውነት መሰከርክ ብሎ የሚፈርድበት ዘመድ እንደማይኖርና፤ ቢኖርም መፅሀፍ ቅዱስ ይዞ በሚፈፅመው መሃላ በውሸት መስክሮ ነፍሱን ማስኮነን እንደሌለበት ተሰማው። እንደሻውን ሊበቀል
የሚችልበትን ይህንን መልካም አጋጣሚ ሊጠቀምበት ወሰነ : እንቢ ቢልስ የት ሊደርስ ? በተለይ አዜብ እየነገረችው
ያለው ፣ ባለስልጣን ፖሊስ ከአዜብ በስተጀርባ መኖሩን ነው፡፡ በተለይ "ሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል"
ስትለው ምን እያለች እንደሆነ
ገብቶታል፡፡አልመሰክርም ቢል በተባባሪ ወንጀለኛነት ተፈርጆ፣ ለፍርድ እንደሚቀርብ እየነገረችው ነው፡፡ ይሄንን ጭምር አስቦ፤ ልቡ ስለፈራ፤ ያየውን ሁሉ በዝርዝር ሊያስረዳና፤ ለትህትና ድንበሩ የመከላከያ ምስክር ሊሆን ቃል ገባላት፡፡ ቃል መግባት ብቻም ሳይሆን ተጨማሪ ማስረጃ ጠቆማት..
"እኔ ብቻ ሳልሆን በዚያን እለት ሁኔታውን የተመለከተችው የቤት ሰራተኛዋ ወርቅ ያንጥፉም ያየችውን ሁሉ እውነቱን ሳትደብቅ እንድትመሰክር እናደርጋለን :: ደግሞም ትመሰክራለች፡፡ አትጠራጠሪ!
በትህትና ሁኔታ በጣም ነው ያዘነችው፡፡እሷም ስመ እግዚአብሄርን ጠርታ
ያየችውን ሁሉ ትመሰክራለች፡፡ አይዞሽ ! " አላት፡፡ አዜብ ከጠበቀችው በላይ ተባባሪ ሆኖ ስለኣገኘችው፤ በደስታ እቅፍ አደረገችው፡፡ በዚሁ መሰረት አበራና ወርቅ ያንጥፉ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው፤ የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ተደረገ፡፡ ቀኑን፡ ሰአቱን፡ የድርጊቱን አፈፃፀም፡ ዝርዝር ሁኔታውን፤ በሙሉ በአንድ አይነትና ፤ ተመሳሳይ በሆነ ቃል
መሰከሩ። ያም ብቻ ሳይሆን አንዱአለምን ጋርጠው በሚል ቅፅል ስሙ በሚታወቀው ወሮበላ እንዳይሞት፤ እንዳይድን፤ አደርጐ ያስደበደበው
መሆኑን፤ ራሱ እንደሻው በኩራት ሲናገር መስማቱን፧ ጭምር ገለፀ፡፡
በእርግጥም እንደሻው ያንን ለአበራ የተናገረው፤ ይሄ ይመጣብኛል ብሎ ሳይሆን፤ አንተም አርፈህ የማትቀመጥና ወሬ አበዛለሁ የምትል ከሆነ፤ አስወቅጥሀለሁ፤ የሚል ማስጠንቀቂያ ለመስጠት ነበር፡፡ ሆኖም በዚህ አጋጣሚ እንደሻውን የደበደበው ጉልበተኛ
ስለታወቀ፤ ወዲያውኑ ታድኖ እንዲያዝ ሲደረግ ፤ አበራ ማንነቱን በማሳየትና የሚገኝበትን
👍2❤1
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
..... የረር ጎታ ሲቃረቡ ነበር ሲቲና ከእንቅልፏ የተነሳችው፡፡
“ለምን አትተኛም ነበር? ቀንኮ ይደክምሃል» አለችው:: እንቅልፍ
ያሳቀጣቸውን ጉንጮቿን እያሻሸች::
“ተመችቶሽ ተኛሽ? ” አላት ፈገግ ብሎ፡፡
“አመሰግናለህ፡፡ የሚመች ትከሻ አላህ፡፡” አለች እየሳቀች፡፡ ጎንበስ ብላ ከሻንጣዋ ውስጥ ሎሚ አወጣችና አንድ ለእሱ አንድ ለራሷ ወሰደች::
“ሎማ ያነቃቃል፤ ታውቃለሁ? " አለች የያዘችውን ሎሚ እየመጠጠች፡፡
ድሬዳዋ ለገሃሬ ደርሰው ከባቡሩ ሲወርዱ ናትናኤል ተደነጋገረው:: የባቡር ጣቢያው በሰው ተጨናንቋል፡፡ አንድ እርምጃ ለመራመድ ሁለት ሦስት ሰዎች መገፍተር አለባቸው:: ሰው የት ወደየት እንደሚሄድ መለየት ያስቸግራል፡፡ ብቻ ባለበት ይተራመሳል፧ ይገፋፋል ፧ ይታሻሽል። ከኋላው ተቀምጣ የነበረችው ሴት አብሯት ከተቀመጠው ተሳፋሪ ጋር እያወራች ስትወርድ ዞሮ ተመሰክታት:: አብሯትት ካለው ሰው ጋር ታውራ እንጂ
አይኖቿ ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡ እርግጠኛ ነው... ከዚህ ቀደም አያቷታል፡፡
“የት ነው የምታርፈው አለችው
ሲቲና ቀደማ ከባበሩ እየወረደች::
“እ… አልወሰንኩም።” አላት ከጀርባው ተቀምጣ የነበረችውን ሴት ማንነት ለማስታወስ እየጣረ:: እርግጠኛ ነው.. መልኳን ያውቀዋል ግን ራቀበት፡፡
“ማለቴ ዘመድ ጋ ነው... ወይስ ሆቴል?” አለችው ሲቲና::ድንገት ብልጭ ሲልለት ድጋሚ ፊቱን ወደ ሴትየዋ አዙሮ ተመለከታት፡፡ የአብርሃም ሠራተኛ! ዞሮ ተመስከታት:: ሳያውቀው ዓይን ለዓይን ተጋጩ፡፡ ቀድማው ፊቷን መለሰች:: ሴትየዋ ቀድሞ ካላያቸው ሁለት ሰዎች ጋር ስታወራ ተመለከተ፡፡
“እ..ምን አልሺኝ? አይ…. ሆቴል ነው የማርፈው ለጊዜው፡፡” አለ ፊቱን ወደ ስቲና መልሶ፡፡
“ከፈለግህ እኔጋ ማረፍ ትችላለህ፡ባዶ ቤት ነው ያለሁት፡፡”
“እ... አለ አሁንም ፊቱን መልሶ የአብርሃምን ሠራተኛ ባየበት አቅጣጫ ተመለከተ፡፡ ዓይኑን የምትሸሽ መሰለው፡፡ አብረዋት የነበሩት ሦስት ሰዎች በአጠገቧ የሉም፡፡ ሴትየዋ ብቻዋን ጥግ ይዛ ቆማለች፡፡
«ማለቴ ለሁለት ለሦስት ቀን ችግር የለም ማለቴ ነው፡» ከጎኑ ከጎኑ እየሄደች አንገቷን አቀርቅራ ተናገረችው ሲቲና፡፡
ከሰው ግፊያ ወጣ ብለው ወደዳር ላይ የያዟቸውን ሻንጣዎች ከመሬት ላይ አሳርፎ ቀና ሲል ባሻገር ተመለከታት፡፡ ሴትየዋ አሁንም ታየዋለች:: ምናልባት የት እንያምታውቀኝ ጠፍቷት ይሆናል።" ብሎ አሰበ፡፡
“አስቸግርሽ እንደሆነ…” አለ ፊቱን ወደ ሲቲና መልሶ፡፡
“በፍጹም፡፡” አለች ፊቷ በሃፍረት እየቀላ፡፡
“እ... ” ናትናኤል አመነታ፡፡ ሆቴል አለመያዙ ከዓይን የሚያድነው ብቻ ሳይሆን ገንዘብም የሚቆጥብለት ነው፡፡ ግን ይቺን ልጅ ተከትሎ ከቤቷ ሄዶ ምን እንደሚከተል ለማወቅ አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ መቼም ምሳና እራት ሊያባላት ወይ ለነፍሷ ብላ እንዳላስጠጋችው ግልጽ ነው፡፡ ግን ቢሆንስ እንዴት ድንገት ልታቀርበው ፈለገች? “ምን መሰለሽ…” አለ ግብዣዋን
እምቢ የሚልበት ዘዴ ጠፍቶት ኣቧራ ያበላሸውን ነጭ ጀለቢያውን
እያራገፈ፡፡
“አስቸግራታለሁ ብለህ አስበህ ከሆነ ምንም ችግር የለም፡፡ ባዶ ቤት ነው ከፍቼ የምገባው:: ወላሂ አልኩህ፡፡”
“እስቲ እየሄድን እናውራ፡፡” አለ ናትናኤል - የሰው ትፍግፍግ ማለትና የአየሩ ሙቀት ትንፋሽ ቢያሳጥረው።
ጎንበስ ብሎ ሻንጣውን ሲያነሳ ከጎኑ ቆማ የነበረችው ሲቲና ገፍትራ ከመሬት ደባለቀችው፡፡ መሬት ላይ ሁለቴ ተንኮበሉ ቀና ሲል ነበር ነገሩ ጭንቅላቱን የመታው ከጀርባወ ቆመው የነበሩ አንድ አዛውንት በደም የተጨማለቀ ሆዳቸውን ይዘው ወደ ሠሬት ሲያዘቅጡ አያኖቹን አፍጥጦ
ተመለከታቸው!” እሪ አለች ከጎናቸው የነበረች ወጣት ሴት፡፡ ከወደቀበት
ለመነሳት ሲጣደፍ ሲቲና ሸብረክ ብላ ከተከናነበችው ድሪያ ስር ሽጉጥ
መዥረጥ ስታደርግ አያት:: ተቀደመች:: የያዘችው ሽጉጥ እጇ ወስጥ ተፈናጥሮ ሲወረወር እሷ ደረቷን አፍና ወደ ኋላዋ ወደቀች.. ዙሪያውን ረብሻ ሆነ... ጩኸት... ሩጫ.. ኡኡታ... ቶክስ እሪታ ዙሪያወን አደባለቀው..ናትናኤል ከአንገቷ ቀና አደረጋት...
«ሩ...ጥ! ተክትለውሃል... ሩጥ!» አለችው በግራ እጇ በደም የተዘፈቀውን ደረቷን አፍና እንደያዘች ሲር ሲር ከሚለው ትንፋሿ እየቆነጠበች ‹‹ ሩጥ!»
ቀና ሲል አየው:: የጨበጠውን ሽጉጥ ከትከሻው በላይ ይዞ ከፊቱ የሚጋረጡትን ሰዎች አንዴ ወዲህ አንዴ ወዲያ እየገፋ እየገፈታተረ ወደ እሱ እየቀረበ ሲመጣ በሚተራመሰው ሕዝብ መሃል በሩቁ አየሁ
ከአብርሃም ሠራተኛ ጋር የነበረውን አንድ ሰውዬ! እንደ ጥንቸል ተፈናጥሮ ከሚደነባበረው ከሚራበሸው ሕዝብ መሃል እየተሹለከለከ በትርምሱ ውስጥ
ሰመጠ... የአብርሃም ሠራተኛ! የፈጣሪ ያለህ! የአብርሃም ሠራተኛ! ከራሱ ጋር እያነበነበ ሮጠ፡፡ ከጀርባው የተኩስ እሩምታ አጀበው::
ወዴት እንደሚሮጥ.. የት እንደሚደርስ ግድ አልነበረውም:: ብቻ ሮጠ፡፡ እራቅ እንዳለ በሩቁ እንዳይለዩት ጭንቅላቱ ላይ የጠመጠመውን ሽርጡን አውልቆ በእጁ ያዘው:: ትንሽ ከራቀ በኋላ ደግሞ ወደ ጥግ ዞር አለና ጀለቢያውን አውልቆ ወርውሮ ከወገቡ በታች ሽርጡን አጥልቆ ከላይ ነጭ ሸሚዙን እንዳደረገ ከራሱ ጋር እያጉተመተመ ሮጠ፡፡ የአብርሃም
ሠሪተኛ! እንዴት ሊከተሉት ቻሉ? ወደ ድሬዳዋ መምጣቱንስ እንደት አወቁ? ሲቲና ባትገፈትረው'ኮ ወደፊቱ ሲወድቅ ባይስቱት'ኮ.. ' በደም የተጨማለቀ ሆዳቸውን ይዘው ያዘቀጡት ሽማግሌ ታዩት:: የፈጣሪ ያለህ! ገለውት ነበር'ኮ የአብርሃም ሠራተኛ! ወያኔ አብርሃም! ለካ ሳያውቀው!
ሲቲና ማነች? ሩጥ…ተከትለውሃል ሩጥ የምስራችን የገደለቻት ሴት ምንድን ነበር ያለችው? ሩጥ!' ሲቲና ማነች? የፈጣሪ ያለህ! ሁሉ ነገር ተወሳሰበበት:: ማሰቡን አቁሞ ሩጫውን ቀጠለ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ያለበት ቦታ የት እንደሆነ ለመረዳት አልቻለም፡፡ በስተግራው መደዳ የተሰሩ ቤቶች ማስታወቂያዎቻቸውን በየቢሮዎቻቸው ላይ እንዳንጠለጠሉ ተደርድረዋል:: ፈቶግራፍ ቤት..የልብስ ሰፊ...ስዓት ማደሻ..በስተቀኙ ደግሞ በረንዳው ላይ የሳጠራ ወንበሮች የተደረደሩበት በሐረግ የተሸፈነ በረንዳ ያለው ቤት ይታያል ድሪዳዋ፡፡
ወደ ቡና ቤቱ፡ ተጠጋና አካባቢያን ለማጥናት ሞክረ፡፡ የፊተኛው ክፍል ሰፊ ቢሆንም ጨለምለም ያለ ነው፡፡ ፈጠን አለና ወደ ውስጥ ገባ፡፡በትናንሽ ጠረጴዛዎች ዙሪያ የተኮለኮሉ ትናንሽ የብረት ወንበሮች ፈንጠር ፈንጠር ብለው ክብ ክብ ሰርተዋል፡፡ በጋዝ የተወለወለው የሲሚንቶ ወለል ቢያብለጨልጭም ሽታው ይከብዳል:: ቁርስ የሚያቂርጉ የቡና ቤቱ ደንበኞች በየወንበሮቻቸው ተቀምጠሁ ያዘዙትን ይስተናግዳሉ፡፡
ባዶ ወረጴዛ ፈለገና ወንበር ስቦ ተቀመጠ፡፡
“ምን ልታዘዝም ! በስተቀኝ የተንዘላዘለ ፀጉሯን ጣቷ ላይ እየጠመጠመች እየፈታች ጠየቀችው::
ሻይ አላት ቶሎ ለመገላገል፡፡ ፊቷን መልሳ ሄደች፡፡ ናትናኤል ከራሱ ጋር ምክክር ቀጠለ።
ጊዜ የለውም:: መፍጠን አለበት:: አለበለዚያ ያገኙታል በማያውቀው ከተማ ውስጥ ተደብቆ መቆየት ዘበት ነው ግን እንዴት ተከተሉት? ከርብቃ ቤት አምልጦ ሲሮጥ ተከትለውት ነበር ማለት ነው?
መሆን አለበት፡፡ የአብርሃምስ የቤት ሰራተኛ እዚህ ምን አመጣት? ወይኔ!
አብርሃምን ትከታተለው ነበር ማለት ነው! አሁን ደግሞ
የቡና ቤቱ አስተናጋጅ ያዘዘውን ሻይ አምጥታ ፊቱ አስቀመጠችለት::
እባክሽ የእኔ እመቤት የስልክ ቁጥር ማውጫ ደብተር ይኖራችኋል? “ አላት
“ይቅርታ የለንም ለምን ማዞሪያ አይጠይቁም
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
..... የረር ጎታ ሲቃረቡ ነበር ሲቲና ከእንቅልፏ የተነሳችው፡፡
“ለምን አትተኛም ነበር? ቀንኮ ይደክምሃል» አለችው:: እንቅልፍ
ያሳቀጣቸውን ጉንጮቿን እያሻሸች::
“ተመችቶሽ ተኛሽ? ” አላት ፈገግ ብሎ፡፡
“አመሰግናለህ፡፡ የሚመች ትከሻ አላህ፡፡” አለች እየሳቀች፡፡ ጎንበስ ብላ ከሻንጣዋ ውስጥ ሎሚ አወጣችና አንድ ለእሱ አንድ ለራሷ ወሰደች::
“ሎማ ያነቃቃል፤ ታውቃለሁ? " አለች የያዘችውን ሎሚ እየመጠጠች፡፡
ድሬዳዋ ለገሃሬ ደርሰው ከባቡሩ ሲወርዱ ናትናኤል ተደነጋገረው:: የባቡር ጣቢያው በሰው ተጨናንቋል፡፡ አንድ እርምጃ ለመራመድ ሁለት ሦስት ሰዎች መገፍተር አለባቸው:: ሰው የት ወደየት እንደሚሄድ መለየት ያስቸግራል፡፡ ብቻ ባለበት ይተራመሳል፧ ይገፋፋል ፧ ይታሻሽል። ከኋላው ተቀምጣ የነበረችው ሴት አብሯት ከተቀመጠው ተሳፋሪ ጋር እያወራች ስትወርድ ዞሮ ተመሰክታት:: አብሯትት ካለው ሰው ጋር ታውራ እንጂ
አይኖቿ ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡ እርግጠኛ ነው... ከዚህ ቀደም አያቷታል፡፡
“የት ነው የምታርፈው አለችው
ሲቲና ቀደማ ከባበሩ እየወረደች::
“እ… አልወሰንኩም።” አላት ከጀርባው ተቀምጣ የነበረችውን ሴት ማንነት ለማስታወስ እየጣረ:: እርግጠኛ ነው.. መልኳን ያውቀዋል ግን ራቀበት፡፡
“ማለቴ ዘመድ ጋ ነው... ወይስ ሆቴል?” አለችው ሲቲና::ድንገት ብልጭ ሲልለት ድጋሚ ፊቱን ወደ ሴትየዋ አዙሮ ተመለከታት፡፡ የአብርሃም ሠራተኛ! ዞሮ ተመስከታት:: ሳያውቀው ዓይን ለዓይን ተጋጩ፡፡ ቀድማው ፊቷን መለሰች:: ሴትየዋ ቀድሞ ካላያቸው ሁለት ሰዎች ጋር ስታወራ ተመለከተ፡፡
“እ..ምን አልሺኝ? አይ…. ሆቴል ነው የማርፈው ለጊዜው፡፡” አለ ፊቱን ወደ ስቲና መልሶ፡፡
“ከፈለግህ እኔጋ ማረፍ ትችላለህ፡ባዶ ቤት ነው ያለሁት፡፡”
“እ... አለ አሁንም ፊቱን መልሶ የአብርሃምን ሠራተኛ ባየበት አቅጣጫ ተመለከተ፡፡ ዓይኑን የምትሸሽ መሰለው፡፡ አብረዋት የነበሩት ሦስት ሰዎች በአጠገቧ የሉም፡፡ ሴትየዋ ብቻዋን ጥግ ይዛ ቆማለች፡፡
«ማለቴ ለሁለት ለሦስት ቀን ችግር የለም ማለቴ ነው፡» ከጎኑ ከጎኑ እየሄደች አንገቷን አቀርቅራ ተናገረችው ሲቲና፡፡
ከሰው ግፊያ ወጣ ብለው ወደዳር ላይ የያዟቸውን ሻንጣዎች ከመሬት ላይ አሳርፎ ቀና ሲል ባሻገር ተመለከታት፡፡ ሴትየዋ አሁንም ታየዋለች:: ምናልባት የት እንያምታውቀኝ ጠፍቷት ይሆናል።" ብሎ አሰበ፡፡
“አስቸግርሽ እንደሆነ…” አለ ፊቱን ወደ ሲቲና መልሶ፡፡
“በፍጹም፡፡” አለች ፊቷ በሃፍረት እየቀላ፡፡
“እ... ” ናትናኤል አመነታ፡፡ ሆቴል አለመያዙ ከዓይን የሚያድነው ብቻ ሳይሆን ገንዘብም የሚቆጥብለት ነው፡፡ ግን ይቺን ልጅ ተከትሎ ከቤቷ ሄዶ ምን እንደሚከተል ለማወቅ አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ መቼም ምሳና እራት ሊያባላት ወይ ለነፍሷ ብላ እንዳላስጠጋችው ግልጽ ነው፡፡ ግን ቢሆንስ እንዴት ድንገት ልታቀርበው ፈለገች? “ምን መሰለሽ…” አለ ግብዣዋን
እምቢ የሚልበት ዘዴ ጠፍቶት ኣቧራ ያበላሸውን ነጭ ጀለቢያውን
እያራገፈ፡፡
“አስቸግራታለሁ ብለህ አስበህ ከሆነ ምንም ችግር የለም፡፡ ባዶ ቤት ነው ከፍቼ የምገባው:: ወላሂ አልኩህ፡፡”
“እስቲ እየሄድን እናውራ፡፡” አለ ናትናኤል - የሰው ትፍግፍግ ማለትና የአየሩ ሙቀት ትንፋሽ ቢያሳጥረው።
ጎንበስ ብሎ ሻንጣውን ሲያነሳ ከጎኑ ቆማ የነበረችው ሲቲና ገፍትራ ከመሬት ደባለቀችው፡፡ መሬት ላይ ሁለቴ ተንኮበሉ ቀና ሲል ነበር ነገሩ ጭንቅላቱን የመታው ከጀርባወ ቆመው የነበሩ አንድ አዛውንት በደም የተጨማለቀ ሆዳቸውን ይዘው ወደ ሠሬት ሲያዘቅጡ አያኖቹን አፍጥጦ
ተመለከታቸው!” እሪ አለች ከጎናቸው የነበረች ወጣት ሴት፡፡ ከወደቀበት
ለመነሳት ሲጣደፍ ሲቲና ሸብረክ ብላ ከተከናነበችው ድሪያ ስር ሽጉጥ
መዥረጥ ስታደርግ አያት:: ተቀደመች:: የያዘችው ሽጉጥ እጇ ወስጥ ተፈናጥሮ ሲወረወር እሷ ደረቷን አፍና ወደ ኋላዋ ወደቀች.. ዙሪያውን ረብሻ ሆነ... ጩኸት... ሩጫ.. ኡኡታ... ቶክስ እሪታ ዙሪያወን አደባለቀው..ናትናኤል ከአንገቷ ቀና አደረጋት...
«ሩ...ጥ! ተክትለውሃል... ሩጥ!» አለችው በግራ እጇ በደም የተዘፈቀውን ደረቷን አፍና እንደያዘች ሲር ሲር ከሚለው ትንፋሿ እየቆነጠበች ‹‹ ሩጥ!»
ቀና ሲል አየው:: የጨበጠውን ሽጉጥ ከትከሻው በላይ ይዞ ከፊቱ የሚጋረጡትን ሰዎች አንዴ ወዲህ አንዴ ወዲያ እየገፋ እየገፈታተረ ወደ እሱ እየቀረበ ሲመጣ በሚተራመሰው ሕዝብ መሃል በሩቁ አየሁ
ከአብርሃም ሠራተኛ ጋር የነበረውን አንድ ሰውዬ! እንደ ጥንቸል ተፈናጥሮ ከሚደነባበረው ከሚራበሸው ሕዝብ መሃል እየተሹለከለከ በትርምሱ ውስጥ
ሰመጠ... የአብርሃም ሠራተኛ! የፈጣሪ ያለህ! የአብርሃም ሠራተኛ! ከራሱ ጋር እያነበነበ ሮጠ፡፡ ከጀርባው የተኩስ እሩምታ አጀበው::
ወዴት እንደሚሮጥ.. የት እንደሚደርስ ግድ አልነበረውም:: ብቻ ሮጠ፡፡ እራቅ እንዳለ በሩቁ እንዳይለዩት ጭንቅላቱ ላይ የጠመጠመውን ሽርጡን አውልቆ በእጁ ያዘው:: ትንሽ ከራቀ በኋላ ደግሞ ወደ ጥግ ዞር አለና ጀለቢያውን አውልቆ ወርውሮ ከወገቡ በታች ሽርጡን አጥልቆ ከላይ ነጭ ሸሚዙን እንዳደረገ ከራሱ ጋር እያጉተመተመ ሮጠ፡፡ የአብርሃም
ሠሪተኛ! እንዴት ሊከተሉት ቻሉ? ወደ ድሬዳዋ መምጣቱንስ እንደት አወቁ? ሲቲና ባትገፈትረው'ኮ ወደፊቱ ሲወድቅ ባይስቱት'ኮ.. ' በደም የተጨማለቀ ሆዳቸውን ይዘው ያዘቀጡት ሽማግሌ ታዩት:: የፈጣሪ ያለህ! ገለውት ነበር'ኮ የአብርሃም ሠራተኛ! ወያኔ አብርሃም! ለካ ሳያውቀው!
ሲቲና ማነች? ሩጥ…ተከትለውሃል ሩጥ የምስራችን የገደለቻት ሴት ምንድን ነበር ያለችው? ሩጥ!' ሲቲና ማነች? የፈጣሪ ያለህ! ሁሉ ነገር ተወሳሰበበት:: ማሰቡን አቁሞ ሩጫውን ቀጠለ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ያለበት ቦታ የት እንደሆነ ለመረዳት አልቻለም፡፡ በስተግራው መደዳ የተሰሩ ቤቶች ማስታወቂያዎቻቸውን በየቢሮዎቻቸው ላይ እንዳንጠለጠሉ ተደርድረዋል:: ፈቶግራፍ ቤት..የልብስ ሰፊ...ስዓት ማደሻ..በስተቀኙ ደግሞ በረንዳው ላይ የሳጠራ ወንበሮች የተደረደሩበት በሐረግ የተሸፈነ በረንዳ ያለው ቤት ይታያል ድሪዳዋ፡፡
ወደ ቡና ቤቱ፡ ተጠጋና አካባቢያን ለማጥናት ሞክረ፡፡ የፊተኛው ክፍል ሰፊ ቢሆንም ጨለምለም ያለ ነው፡፡ ፈጠን አለና ወደ ውስጥ ገባ፡፡በትናንሽ ጠረጴዛዎች ዙሪያ የተኮለኮሉ ትናንሽ የብረት ወንበሮች ፈንጠር ፈንጠር ብለው ክብ ክብ ሰርተዋል፡፡ በጋዝ የተወለወለው የሲሚንቶ ወለል ቢያብለጨልጭም ሽታው ይከብዳል:: ቁርስ የሚያቂርጉ የቡና ቤቱ ደንበኞች በየወንበሮቻቸው ተቀምጠሁ ያዘዙትን ይስተናግዳሉ፡፡
ባዶ ወረጴዛ ፈለገና ወንበር ስቦ ተቀመጠ፡፡
“ምን ልታዘዝም ! በስተቀኝ የተንዘላዘለ ፀጉሯን ጣቷ ላይ እየጠመጠመች እየፈታች ጠየቀችው::
ሻይ አላት ቶሎ ለመገላገል፡፡ ፊቷን መልሳ ሄደች፡፡ ናትናኤል ከራሱ ጋር ምክክር ቀጠለ።
ጊዜ የለውም:: መፍጠን አለበት:: አለበለዚያ ያገኙታል በማያውቀው ከተማ ውስጥ ተደብቆ መቆየት ዘበት ነው ግን እንዴት ተከተሉት? ከርብቃ ቤት አምልጦ ሲሮጥ ተከትለውት ነበር ማለት ነው?
መሆን አለበት፡፡ የአብርሃምስ የቤት ሰራተኛ እዚህ ምን አመጣት? ወይኔ!
አብርሃምን ትከታተለው ነበር ማለት ነው! አሁን ደግሞ
የቡና ቤቱ አስተናጋጅ ያዘዘውን ሻይ አምጥታ ፊቱ አስቀመጠችለት::
እባክሽ የእኔ እመቤት የስልክ ቁጥር ማውጫ ደብተር ይኖራችኋል? “ አላት
“ይቅርታ የለንም ለምን ማዞሪያ አይጠይቁም
👍1
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
ድርጅት የእገታ ማስለቀቂያውን የገንዘብ ክፍያ ከታጋች ቤተሰብ ተቀብለው እና ድርሻቸውን ቆርጠው ለአጋቾች እንደሚሰጡ ነው፡፡ ይሄ ደግሞ አንደኛው የቢዝነስ አካሄድ ነው፡፡ ሌላኛው ነገር ደግሞ ራሳቸው የወሮበላ ቡድኖቹ አብረዋቸው የሚሰሩ ሰዎቻቸውን ወደ አሜሪካ ከገቡ በኋላ በአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪዎች ላይ የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተው ጥበቃ ከሚደረግላቸው ሰዎች መዝገብ ውስጥ እንዲገቡ ታስደርግላቸዋለች፡፡ ይሄ ደግሞ የሚያሳየው እሷን የሚያግዝ የመንግስት አካል ከውስጥ እንዳላት ነው።
“ከፖሊሶች ውስጥ ማለት ነው?” ብላ ኒኪ ጠየቀች፡፡ ዊሊያምስም ትንሽ ፈገግ አለና “አትገረሚ፡፡ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ ከባድ ልብስ ሲሰቀልበት እንደሚረግብ አሮጌ የልብስ መስቀያ ሆኗል፡፡ ሌላው ደግሞ የጠፉ ልጆችን በህገወጥ መንገድ ከሚያዘዋውሩ ሰዎች እጅ ውስጥ እንደሚገቡ ነው፤ እነዚህ በአየር
መንገዱ የተጠለፉ ህፃናት እና ወጣት ሴቶችም ለሩሲያ የወሲብ ንግድ
አስማሪ የወርበሎች ቡድን ይሸጣሉ የሚል መረጃ አለኝ፡፡ ይህንንም
ላረጋግጥልሽ አልችልም ግን ያው ውስጥ ለውስጥ የሚወራ ነገር ነው፡፡” ኒኪም አይኗን ገርጥጣ “እና ቻርሎቴ ክላንሲ...?” ዊሊያምም ራሱን በአሉታ
ነቅንቆ “አይመስለኝም፤ የወሲብ ንግድ የሚሰሩ ሰዎችን በህገ ወጥ መንገድ
በየሀገሩ የሚያዘዋውሩ ቢዝነሶች አነስተኛ ገቢ ነው ያላቸው፡፡ ቤተሰቦቻቸው
አጥብቀው የማይፈልጓቸውን ህፃናት ወንዶችና ሴቶችን ነው በዚህ ሥራ ላይ
የሚያሰማሩት፡፡ ስለዚህ አንዲት የ18 ዓመት ዕድሜ ሴትን በዚህ ቢዝነስ
ውስጥ ማሰራታቸው ይጎዳቸዋል እንጂ አይጠቅማቸውም፡፡ ብቻ በአንድም
ሆነ በሌላ መልኩ ይህ የቫላንቲና ቡድን ድርጅት ከፊት ለፊቱ የጠፉ ሰዎችን
የሚያፈላልግ መስሎ ከጀርባ ግን የሚፈልጉትን ሥራ ይሰራሉ። በቫላንቲና
ባደን የበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥም ሌሎች የበጎ አድራጎት ድርጅቶች
ከሚያገኙት (ከሚያስጭኑት) ገንዘብ እጅግ በጣም የላቀ ገንዘብን ያስገባል።”
አላት፡፡
ኒኪ በዝምታ ውስጥ ሆና ዊሊያምስ በወሬ ሰማሁ ያላትን ጓደኛዋ ግሬንቸን እና ገና በወጣትነቷ እህቷን ያጣችውን ቫላንቲና ባደንን ከዚህ ቡድን ጋር ማጣመር አቃታት፡፡ እርግጥ ነው ሁሉም በዙሪያዋ የሚገኙ ሰዎች በመንፈስና በምግባር ጥንካሬ እየለሰለሱ መሆናቸውን እያየች ቢሆንም ዊሊያምን ተሳስተሃል ለማለት ተቸገረች፡፡
“በማንኛውም መልኩ” ብሎ ዊልያምስ በመሀከላቸው ያለውን ዝምታ ሰበረ እና “ሚስ ባደን እዚህ ነገር ተግባር ላይ እንድትገኝ የሚያደርገው የምትገኘው ዋነኛው ስው ሉዊስ ሮድሪጌዝ ነው፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት ደግሞ ትኩረቱን ከኮኬይን ላይ አንስቶ ክሮክ ላይ አድርጓል። በዚህም
የኤል.ኤን የዕፅ ገበያን ከሩሲያኖቹ ለመንጠቅ አጥብቀው እየሰሩ ይገኛሉ።
እዚህ ከተማ ውስጥ በጣም ብዙ ሰዎች አሉት። በቃ እነርሱ ልክ እንደ ወረርሽኝ ሁሉም ቦታ ላይ ይገኛሉ።” አላት፡፡
ዊልያምስ እነርሱ እንደ ወረርሽኝ ሁሉም ቦታ ላይ ይገኛሉ ብሎ የተናገረውን ነገር ስትሰማ ካርተርን አስታወሰች፡፡ ምክንያቱም ቀን ላይ ካርተር ይገድሉኛል ብሎ ስለሚፈራቸው ሜክሲካውያን ሲነግራት የገለፀላት በዚሁ መንገድ ነበር። ስለዚህ የካርተርን ሀሳብ ማመን ይኖርብኝ ይሆን?”
“ሌላ ግንኙነት። ሌላ የጭለማ ውስጥ የሸረሪት ድር”
ከዚህ የጥልፍልፎሽ ሀሳብ ውስጥ በጠራ አዕምሮ ማሰብ ፈልጋም “እሺ ሉዊስ ያደንዥ ዕፅ ቢዝነስ ውስጥ አለበት እንበል። ግን አኔ ስለዚህ ነገር
ታውቃለች?” ብላ ዊልያምስን ጠየቀችው፡፡
“ሉዊስ የአደንዛዥ ዕፅ ቢዝነስ እንደሚሰራ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ይህቺ ሚስቱ ይሄን ሁሉ ገንዘብ ከየት እንደሚያመጣው ትወቅ አትወቅ ግን እርግጠኛ አይደለሁም። አንቺ ስለእሷ ከነገርሺኝ ነገር በመነሳት ግን እሷ ይህንን ነገር የምታውቅ አይመስለኝም:: ምክንያቱም ሮድሪጌዝ ሁለት ስብእና ያለው ሰው ነው፡፡ ቢዝነሱን ከግላዊ ኑሮው ለይቶ ማስኬድ ይችላል።”
ይህንንማ ለአኔ መንገር አለብኝ ብላ አሰበች በውስጧ፡፡ ኒኪ የእሷ ባል
ማን እንደሆነ የማወቅ መብት አላት። እያንዳንዷ ሚስት ይህ መብት ሊኖራት ይገባል። እየተዋሸች መኖር የለባትም። ብላ አሰበች፡፡
“እሺ ይህንን የእሱን ሥራ ፖሊሶች ያውቁታል ብለኸኛል? እዚህ
የኤል.ኤ. ፖሊስ እና የኤፍ.ቢ.አይ ሰዎችም ስለ ጉዳዩ ያውቃሉ?”
“በደንብ ነዋ” ብሎ ዊሊያምስ ፈገግ አለ እና ባይገርምሽ የኤሌ.ኤ.ፒ.ዲ የፀረ አደንዛዥ ዕፅ የምርመራ ቡድን ስለ ዴላ ሮዛ እና ስለ ሮድሪጌዝ ክምር ዶሴዎች ሁሉ ሳይኖራቸው ይቀራል ብለሽ ነው?”
“ይሄ ንፁህ የተባለው ክሮክ ከየት እንደሚመጣ በደንብ ያውቁታል።
ምናልባትም ሩሲያውያን ይህንን ሥራ ከሚሰሩት ሜክሲካውያን እንዲሰሩት
ፈልገውም ይሆናል ዝም የሚሉት፡፡ አልያም ደግሞ አንድ ትልቅ የፖሊስ
አለቃ ከእያንዳንዱ የአደንዛዥ ዕፁ ሽያጭ ላይ የሚቆረጥለት ነገር አለ ማለት
ነው።”
ኒክም የሰማችውን ነገር ለጥቂት ሰኮንዶች ያህል ስታመነዥክ ቆየች እና
“አንተ የምትለው ፖሊሶቹ እዚህ ድርድር ውስጥ አሉበት ነው? ማለቴ ልክ
የጠፉ ሰዎችን አፈላላጊ የበጎ አድራጎት ድርጅቱ እንደሚያደርገው ማለት
ነው?”
“አዎን እንደዚያ ነው ብዬ አምናለሁ” አላት እና ዊሊያምስ በመቀጠልም ፖሊሶቹ እናም ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች እዚህ የአደንዛዥ ዕፅ ሽያጭ ላይ ይኖሩበታል፡፡ ሮድሪጌዝ ደግሞ ልክ ሜክሲኮ ውስጥ ሲያደርግ የነበረውን
ነገር እዚህም በማድረግ ላይ ይገኛል። ወንዶችን ማፍራት፣ በእጅ መሄድን
ያውቅበታል። በዚያ ላይ ደግሞ በአደንዛዥ ዕፅ ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ለድሆችም የልገሳ እጁን በስፋት በመዘርጋት ላይ ይገኛል።”
ሃሳቡን እየተናገረ እያለ ኒኪ በትኩረት ስትከታተለው ስላየ ከተጣላችኝም
ይለይለት አለና “የሜክሲኮ አደንዛዥ ዕፅ አምራቾች ከትሬይ እና ከሊዛ ፍላንገን ግድያዎች በስተጀርባ እንደሚገኝ አልጠራጠርም፡፡ ከዚህ በላይ ደግሞ
ምናልባትም በባለቤትሽም ግድያ ላይ እጃቸው ሊኖርበት ስለሚችል ለዚህም
ራስሽን አዘጋጂ” አላት፡፡
ኒኪ ይህን ስትሰማ አይኗ በራ። ምናልባት የባለቤትሽ ግድያ ውስጥ የሊዊስ እጃቸው ሊኖርበት ይችላል ማለቱን አልወደደችለትም፡፡ ምክንያቱም
ከባሏ እና ከውሽማው ግድያ ጋር በተያያዘ የእሷ ታካሚ የሆነችው ከአኔ
ባለቤት ሉዊስ ሮድሪጌዝ ጋር እንዲገናኝ አትፈልግም፡፡ ይህ እንዴት ሊሆን
ይችላል? ብላ አሰበች፡፡
“ለማንኛውም ማጠቃለያ ይህንን ይመስላል” ብሎ ባወራት ነገር የረካው
ዊሊያምስ ወደ ኋላ ወንበሩ ላይ እየተለጠጠ “በሚቀጥለው ምን ላይ አተኩሬ ሥራዬን እንድሠራ ትፈልጊያለሽ?” ብሎ ጠየቃት፡፡ ኒኪ ዝም ብላ ስታየው
ዊሊያምስ ነገሩን ማብራራት ጀመረ “በዚህ ሳምንት ትኩረቴን ትሬድ ላይ
አድርጌ ነው ምርመራዬን ላካሂድ የፈለግኩት።” አላት እና ዊሊያምስ
በመቀጠልም ከነገ ጀምሮ ሊና ፍላንገን ላይ ትኩረቴን ለማድረግ አስቤያለሁ፡፡ ማለትም ስለ በፊቱ የአደንዛዥ ዕፅ አጠቃቀሟ ምናልባትም ከሆነ ትልቅ የዕፅ አዘዋዋሪ ጋር ስላላት ግንኙነት ወይም ደግሞ ከዊሊ ቡድን ጋር ስላላት ግንኙነት ምናልባትም ደግሞ እኔ ካሰብኩት በላይ የዊሊ እና ቫለንቲና ቡድን እዚህ የአደንዛዥ ዕፅ ቢዝነስ ውስጥ ሊኖሩበት ይችሉ ይሆናል፡፡ አሊያም ደግሞ ፖሊሶች የአንቺ የቀድሞ ታካሚ ከሆነው ብራንዶን ግሮልሽ ላይ አትኩሮታቸውን አድርገው በመንቀሳቀስ ላይ እንዳሉ
በማወቅ ላይ አትኩሮቴን ማድረግ እፈልጋለሁ። ደግሞም መርማሪ ፖሊስ
ጆንሰን ይሄ ዘረኛ እጁ እዚህ ነገር ውስጥ በሙስና
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
ድርጅት የእገታ ማስለቀቂያውን የገንዘብ ክፍያ ከታጋች ቤተሰብ ተቀብለው እና ድርሻቸውን ቆርጠው ለአጋቾች እንደሚሰጡ ነው፡፡ ይሄ ደግሞ አንደኛው የቢዝነስ አካሄድ ነው፡፡ ሌላኛው ነገር ደግሞ ራሳቸው የወሮበላ ቡድኖቹ አብረዋቸው የሚሰሩ ሰዎቻቸውን ወደ አሜሪካ ከገቡ በኋላ በአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪዎች ላይ የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተው ጥበቃ ከሚደረግላቸው ሰዎች መዝገብ ውስጥ እንዲገቡ ታስደርግላቸዋለች፡፡ ይሄ ደግሞ የሚያሳየው እሷን የሚያግዝ የመንግስት አካል ከውስጥ እንዳላት ነው።
“ከፖሊሶች ውስጥ ማለት ነው?” ብላ ኒኪ ጠየቀች፡፡ ዊሊያምስም ትንሽ ፈገግ አለና “አትገረሚ፡፡ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ ከባድ ልብስ ሲሰቀልበት እንደሚረግብ አሮጌ የልብስ መስቀያ ሆኗል፡፡ ሌላው ደግሞ የጠፉ ልጆችን በህገወጥ መንገድ ከሚያዘዋውሩ ሰዎች እጅ ውስጥ እንደሚገቡ ነው፤ እነዚህ በአየር
መንገዱ የተጠለፉ ህፃናት እና ወጣት ሴቶችም ለሩሲያ የወሲብ ንግድ
አስማሪ የወርበሎች ቡድን ይሸጣሉ የሚል መረጃ አለኝ፡፡ ይህንንም
ላረጋግጥልሽ አልችልም ግን ያው ውስጥ ለውስጥ የሚወራ ነገር ነው፡፡” ኒኪም አይኗን ገርጥጣ “እና ቻርሎቴ ክላንሲ...?” ዊሊያምም ራሱን በአሉታ
ነቅንቆ “አይመስለኝም፤ የወሲብ ንግድ የሚሰሩ ሰዎችን በህገ ወጥ መንገድ
በየሀገሩ የሚያዘዋውሩ ቢዝነሶች አነስተኛ ገቢ ነው ያላቸው፡፡ ቤተሰቦቻቸው
አጥብቀው የማይፈልጓቸውን ህፃናት ወንዶችና ሴቶችን ነው በዚህ ሥራ ላይ
የሚያሰማሩት፡፡ ስለዚህ አንዲት የ18 ዓመት ዕድሜ ሴትን በዚህ ቢዝነስ
ውስጥ ማሰራታቸው ይጎዳቸዋል እንጂ አይጠቅማቸውም፡፡ ብቻ በአንድም
ሆነ በሌላ መልኩ ይህ የቫላንቲና ቡድን ድርጅት ከፊት ለፊቱ የጠፉ ሰዎችን
የሚያፈላልግ መስሎ ከጀርባ ግን የሚፈልጉትን ሥራ ይሰራሉ። በቫላንቲና
ባደን የበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥም ሌሎች የበጎ አድራጎት ድርጅቶች
ከሚያገኙት (ከሚያስጭኑት) ገንዘብ እጅግ በጣም የላቀ ገንዘብን ያስገባል።”
አላት፡፡
ኒኪ በዝምታ ውስጥ ሆና ዊሊያምስ በወሬ ሰማሁ ያላትን ጓደኛዋ ግሬንቸን እና ገና በወጣትነቷ እህቷን ያጣችውን ቫላንቲና ባደንን ከዚህ ቡድን ጋር ማጣመር አቃታት፡፡ እርግጥ ነው ሁሉም በዙሪያዋ የሚገኙ ሰዎች በመንፈስና በምግባር ጥንካሬ እየለሰለሱ መሆናቸውን እያየች ቢሆንም ዊሊያምን ተሳስተሃል ለማለት ተቸገረች፡፡
“በማንኛውም መልኩ” ብሎ ዊልያምስ በመሀከላቸው ያለውን ዝምታ ሰበረ እና “ሚስ ባደን እዚህ ነገር ተግባር ላይ እንድትገኝ የሚያደርገው የምትገኘው ዋነኛው ስው ሉዊስ ሮድሪጌዝ ነው፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት ደግሞ ትኩረቱን ከኮኬይን ላይ አንስቶ ክሮክ ላይ አድርጓል። በዚህም
የኤል.ኤን የዕፅ ገበያን ከሩሲያኖቹ ለመንጠቅ አጥብቀው እየሰሩ ይገኛሉ።
እዚህ ከተማ ውስጥ በጣም ብዙ ሰዎች አሉት። በቃ እነርሱ ልክ እንደ ወረርሽኝ ሁሉም ቦታ ላይ ይገኛሉ።” አላት፡፡
ዊልያምስ እነርሱ እንደ ወረርሽኝ ሁሉም ቦታ ላይ ይገኛሉ ብሎ የተናገረውን ነገር ስትሰማ ካርተርን አስታወሰች፡፡ ምክንያቱም ቀን ላይ ካርተር ይገድሉኛል ብሎ ስለሚፈራቸው ሜክሲካውያን ሲነግራት የገለፀላት በዚሁ መንገድ ነበር። ስለዚህ የካርተርን ሀሳብ ማመን ይኖርብኝ ይሆን?”
“ሌላ ግንኙነት። ሌላ የጭለማ ውስጥ የሸረሪት ድር”
ከዚህ የጥልፍልፎሽ ሀሳብ ውስጥ በጠራ አዕምሮ ማሰብ ፈልጋም “እሺ ሉዊስ ያደንዥ ዕፅ ቢዝነስ ውስጥ አለበት እንበል። ግን አኔ ስለዚህ ነገር
ታውቃለች?” ብላ ዊልያምስን ጠየቀችው፡፡
“ሉዊስ የአደንዛዥ ዕፅ ቢዝነስ እንደሚሰራ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ይህቺ ሚስቱ ይሄን ሁሉ ገንዘብ ከየት እንደሚያመጣው ትወቅ አትወቅ ግን እርግጠኛ አይደለሁም። አንቺ ስለእሷ ከነገርሺኝ ነገር በመነሳት ግን እሷ ይህንን ነገር የምታውቅ አይመስለኝም:: ምክንያቱም ሮድሪጌዝ ሁለት ስብእና ያለው ሰው ነው፡፡ ቢዝነሱን ከግላዊ ኑሮው ለይቶ ማስኬድ ይችላል።”
ይህንንማ ለአኔ መንገር አለብኝ ብላ አሰበች በውስጧ፡፡ ኒኪ የእሷ ባል
ማን እንደሆነ የማወቅ መብት አላት። እያንዳንዷ ሚስት ይህ መብት ሊኖራት ይገባል። እየተዋሸች መኖር የለባትም። ብላ አሰበች፡፡
“እሺ ይህንን የእሱን ሥራ ፖሊሶች ያውቁታል ብለኸኛል? እዚህ
የኤል.ኤ. ፖሊስ እና የኤፍ.ቢ.አይ ሰዎችም ስለ ጉዳዩ ያውቃሉ?”
“በደንብ ነዋ” ብሎ ዊሊያምስ ፈገግ አለ እና ባይገርምሽ የኤሌ.ኤ.ፒ.ዲ የፀረ አደንዛዥ ዕፅ የምርመራ ቡድን ስለ ዴላ ሮዛ እና ስለ ሮድሪጌዝ ክምር ዶሴዎች ሁሉ ሳይኖራቸው ይቀራል ብለሽ ነው?”
“ይሄ ንፁህ የተባለው ክሮክ ከየት እንደሚመጣ በደንብ ያውቁታል።
ምናልባትም ሩሲያውያን ይህንን ሥራ ከሚሰሩት ሜክሲካውያን እንዲሰሩት
ፈልገውም ይሆናል ዝም የሚሉት፡፡ አልያም ደግሞ አንድ ትልቅ የፖሊስ
አለቃ ከእያንዳንዱ የአደንዛዥ ዕፁ ሽያጭ ላይ የሚቆረጥለት ነገር አለ ማለት
ነው።”
ኒክም የሰማችውን ነገር ለጥቂት ሰኮንዶች ያህል ስታመነዥክ ቆየች እና
“አንተ የምትለው ፖሊሶቹ እዚህ ድርድር ውስጥ አሉበት ነው? ማለቴ ልክ
የጠፉ ሰዎችን አፈላላጊ የበጎ አድራጎት ድርጅቱ እንደሚያደርገው ማለት
ነው?”
“አዎን እንደዚያ ነው ብዬ አምናለሁ” አላት እና ዊሊያምስ በመቀጠልም ፖሊሶቹ እናም ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች እዚህ የአደንዛዥ ዕፅ ሽያጭ ላይ ይኖሩበታል፡፡ ሮድሪጌዝ ደግሞ ልክ ሜክሲኮ ውስጥ ሲያደርግ የነበረውን
ነገር እዚህም በማድረግ ላይ ይገኛል። ወንዶችን ማፍራት፣ በእጅ መሄድን
ያውቅበታል። በዚያ ላይ ደግሞ በአደንዛዥ ዕፅ ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ለድሆችም የልገሳ እጁን በስፋት በመዘርጋት ላይ ይገኛል።”
ሃሳቡን እየተናገረ እያለ ኒኪ በትኩረት ስትከታተለው ስላየ ከተጣላችኝም
ይለይለት አለና “የሜክሲኮ አደንዛዥ ዕፅ አምራቾች ከትሬይ እና ከሊዛ ፍላንገን ግድያዎች በስተጀርባ እንደሚገኝ አልጠራጠርም፡፡ ከዚህ በላይ ደግሞ
ምናልባትም በባለቤትሽም ግድያ ላይ እጃቸው ሊኖርበት ስለሚችል ለዚህም
ራስሽን አዘጋጂ” አላት፡፡
ኒኪ ይህን ስትሰማ አይኗ በራ። ምናልባት የባለቤትሽ ግድያ ውስጥ የሊዊስ እጃቸው ሊኖርበት ይችላል ማለቱን አልወደደችለትም፡፡ ምክንያቱም
ከባሏ እና ከውሽማው ግድያ ጋር በተያያዘ የእሷ ታካሚ የሆነችው ከአኔ
ባለቤት ሉዊስ ሮድሪጌዝ ጋር እንዲገናኝ አትፈልግም፡፡ ይህ እንዴት ሊሆን
ይችላል? ብላ አሰበች፡፡
“ለማንኛውም ማጠቃለያ ይህንን ይመስላል” ብሎ ባወራት ነገር የረካው
ዊሊያምስ ወደ ኋላ ወንበሩ ላይ እየተለጠጠ “በሚቀጥለው ምን ላይ አተኩሬ ሥራዬን እንድሠራ ትፈልጊያለሽ?” ብሎ ጠየቃት፡፡ ኒኪ ዝም ብላ ስታየው
ዊሊያምስ ነገሩን ማብራራት ጀመረ “በዚህ ሳምንት ትኩረቴን ትሬድ ላይ
አድርጌ ነው ምርመራዬን ላካሂድ የፈለግኩት።” አላት እና ዊሊያምስ
በመቀጠልም ከነገ ጀምሮ ሊና ፍላንገን ላይ ትኩረቴን ለማድረግ አስቤያለሁ፡፡ ማለትም ስለ በፊቱ የአደንዛዥ ዕፅ አጠቃቀሟ ምናልባትም ከሆነ ትልቅ የዕፅ አዘዋዋሪ ጋር ስላላት ግንኙነት ወይም ደግሞ ከዊሊ ቡድን ጋር ስላላት ግንኙነት ምናልባትም ደግሞ እኔ ካሰብኩት በላይ የዊሊ እና ቫለንቲና ቡድን እዚህ የአደንዛዥ ዕፅ ቢዝነስ ውስጥ ሊኖሩበት ይችሉ ይሆናል፡፡ አሊያም ደግሞ ፖሊሶች የአንቺ የቀድሞ ታካሚ ከሆነው ብራንዶን ግሮልሽ ላይ አትኩሮታቸውን አድርገው በመንቀሳቀስ ላይ እንዳሉ
በማወቅ ላይ አትኩሮቴን ማድረግ እፈልጋለሁ። ደግሞም መርማሪ ፖሊስ
ጆንሰን ይሄ ዘረኛ እጁ እዚህ ነገር ውስጥ በሙስና
👍3
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....ጋሻዬነህ ከእናቴ ጋር ውሉ አደረ፡፡ የየወዲያነሽ የእናትነት አንጀት በናፍቆት ተላወሰ፡፡ ሮብ ጧት ለቁርስ እንደ ተቀመጥን «ምነው ዝም አልክ ጌታነህ? ረሳኸው እንዴ? ከጋሼ ጉልላት ጋር ምን ምን ነበር የተባባላችሁት?
ሂድና አምጣው እንጂ» አለችኝ፡፡
“ምናልባት ዛሬ የውብነሽ ታመጣው ይሆናል» አልኩና እንደገና ደግሞ
«ምናለባት ጋሻዬነህን ለእነርሱ ብንሰጣቸውና እኔና አንቺ ደግሞ….ሌላ» ብዬ ንግግሬን ሳልጨርስ ደረቷን ሁለት ጊዜ በጥፊ ደቃችና «ህ! እንዴት ያለህው ዓለመኛ ነህ! ምነው ምን በወጣኝ! ዕድሜ ላንተ እያልኩ ዐይን ዐይኑን እንዳላይ ነው!» ብላ ከነጥርጣሬዋ ዝም አለች።
ሐሳብን ማሻሻልና ፈጽሞም መለወጥ አንድ ዐይነት ዕድገት በሆኑ የሐሳቧ መለወጥና ተቃውሞዋ ደስ አለኝ፡፡ ለጥያቄዋ መልስ ሳልሰጥ ወደ ሥራ ሄድኩ፡፡
የውብነሽ ቀንም ሆነ ማታ ብቅ ሳትል ቀረች፡፡ የሮብ ጀንበር ጠልቃ የሐሙሷ ተወለደች፡፡ አዲሱ የፍርሃት ሸክም ከየወዲያነሽ ይልቅ እኔን ከበደኝ፡፡ ከማታ
ትምህርት መልስ ሻይ እየጠጣን ስናወራ አንዱን ተረስቶ የቀረ የጋሻዬነህን የሒሳብ ደብተር እያገላበጠች «እሷ መች ሥራ አጣችና ነው ይዛው ትመጣለች
የምትለው? እኔ እኮ ነገሩ የገባኝ የመማሪያ ደብተሩን ይዛ ስትሒድ ነው» ብላ ወደ ራሷ ደብተሮች መለስ አለች፡፡
«እኔን ያሠጋኝ ሌላው አይደለም.....አባባ ይመለሳል ከተባለበት ቀን ቀደም ብሎ ቢመለስና ይኸ ልጅ የማን ነው ልጅ? ብሎ ቢጠየቅ ምን ይላሉ?
እናቴ ገና እንማከራለን ነው ያለችኝ እንጂ ሌላ የተነጋገርነው ነገር የለም ከማለቴ፣ የማን ልጅ እንዲባልልህ ትፈልጋለህ? የጌታነህ ልጅ ነው ብለው
ይነግሩልሃላ» ብላ ኩታ አጣፍቶ የመልበስ ያህል ጉዳዩን አቃልላ መለሰችልኝ።
«እንዴት አንቺ? እኔ እኮ ገና ብዙ ግብግብና ትግል ይጠብቀኛል።
የሙሉ ድሌ ቀኔ ገና ነው:: ምኑ ተያዘና!ምኑ ተነካና! እንዴት አድርጌ እንደምገጥመውና ድል እንደማደርገው ዕቅድና ብልሃቴ አልተጠናቀቀም፡፡ወደፊት የሚቀረኝ የትግል ጉራንጉር ያለፉትን የመከራና የትግል ገድሎች ሁሉ ሊያጠቃልል ይችላል፡፡ ቀሪው ትግል በዕድልና በአጋጣሚ የማምንበት ነገር
የለም፡፡ የሚጠብቀኝ ውጣ ውረድ ሁሉ በበቂ ምክንያትና በተግባር የሚመራ ነው። «የዘልማድ ዝላይና ባወጣ ያውጣኝ በቃው! በቂ ምክንያት ጥሩ የተግባር
ዋስትና» ብዬ በመጀመር ለወደፊት ከሚያጋጠሙኝ አንደንድ ችግሮች መኻል አንዳንዶቹን በከፊል አዋየኋት፡፡
ዓርብ ከጧቱ ሁለት ሰዓት ላይ የውብነሽ ጋሻዬነህን ይዛ መጣች።
የሚያምር አዲስ ልብስ ለብሶ
ከፈገግታው ጋር ሲታይ የመስከረም ዝናብ ያጠባት
የለጋ ዘንባባ ተክል መስሏል። የወዲያነሽ ግልገሏን አስከትላ ጢሻ ውስጥ እንደምትገባ ሰስ ልጅዋን አስከትላ ወደ ጓዳ ገባች። እኔና የውብነሽ ወጣ ብለን ሰበሰቡ ላይ እንደቆምን «አባባ የነገ ሳምንት ከሰዓት በኋላ ይገባል፡፡ ባለቢትህን እንዴት አድርገን እሱ ፊት እንደምናቀርባት፡ አንተም ምንና ምን እያልክ መናገርና ማስረዳት እንዳለብህ አንድ ባንድ አውጥተን አውርደን ጨርሰናል» ብላ ስለ እኛ ሕይወት እኔና ባለቤቴ ያልተካፈልንበትን የአፈጻጸም ዕቅድ አረዳችኝ፡፡
የችግሬን ዐይነትና ዓላማዬን የማውቀው እኔ ሆኜ ሳለሁ መወከልና ማስፈጸም
የማይገባቸው እኅቴና እናቴ አፈ ቀላጤ ሆነን እንገኝ ሲሉ በመስማቴ ተናደድኩ፡፡
አልተዋጠልኝም፡፡
የአባቴ ግብዝነትና ቁጣዉ፣ ግትርነቱንና የመጣ ይምጣ ባይነቱ፣ እንደ ጨካኝ አገረ ገዢ ፊት ለፊት ቆሞ እንደ እሳት ፈጀኝ፡፡ «ማታ ከትምህርት ቤት
መልስ ከየወዲያነሽ ጋር እንድትመጡ፣ ነገሩን አብራራልሃለሁ። አሁን ግን
ቸኩያለሁ ደኀና ዋል» ብላኝ ቶሉ ብለህ ና እንደ ተባለ መልእክተኛ ጥላኝ ሄደች። አእምሮዬ በሐሳብ ተወቃ፡፡ ሁለመናዬ ብው ብሎ ጋመ፡፡ አዳዲስ ጭንቀቶች በውስጤ ተራወጡ፡፡ የሐሳቤ አድማስ ለመጥበብም ሆነ ለመስፋት ባለመቻሉ መረጋጊያ አጣሁ፡፡
ጎርፍ እንደ ገረሰሰው ዛፍ ግድግዳውን ተደግፌ ቆምኩ፡፡ የወዲያነሽ ከወደ ውስጥ መጥታ «ከምን ጊዜው ሄደች? ያንተ ነገር እኮ...አናደድካት እንዴ?» ብላ
በሥጋት አዘል ሁኔታ ጠየቀችኝ፡፡ «ቸኩላ ነበር፡ ታናድደኛለች እንጂ ምን አናድዳታለሁ፡፡ የማይጠቅሙሽ እጠቅምሻለሁ፣ የሚያጠፉሽ አለማሻለሁ፣
የሚገድሉሽ አድንሻለሁ ሲሉሽ አትናደጂም? አሁን የነገረችኝን ማታ ስትነግረኝ ትሰሚያታለሽ፡፡ አሁን ወደ ሥራሽ ሂጂ» ብያት ዝም አልኩ፡፡ የእርሷ ከአጠገቤ
ገለል ማለት የሚረዳኝ ስለ መሰላት ተመልሳ ገባች፡፡ በአካባቢዬ የሚገኙት ነገሮች
ሁሉ ለችግሮች ማቃለያ የሚሆን ብልሃት ያቀርቡልኝ ይመስል ትክ ብዬ አየኋቸው:: ሆኖም ከበድን መልስ የለምና አፍጥጨ ቀረሁ። ሳላስበው ከቤት ወጣ ብዬ ቆምኩ፡፡ የማለዳዋ ፀሐይ ደጋናማ ጉዞዋን ጀምራለች፡፡ ደመና የማይታይበትን ሰማይ ትኩር ብሎ ላየው ኣስፈሪነቱ አይጣል! ዘልዓለም የሚሉት ይህን ርቀትና
ጥልቀት ይሆን? አንጋጥጬ ስመለከት ሐሳብ አሽቆልቁሎ አየኝ፡፡ አካባቢዬን ፈራሁት፡፡ ጥቂት ርምጃ ተራምጄ ግቢው መኻል ተገተርኩ፡፡ ከመሬት ውስጥ
መልስ ይፈልቅልኝ ይመስል ደቃቁን አፈርና ኮረት ባይኔ ሰለልኩት። ቀዝቃዛና ለስላሳ ትንሽ እጅ የቀኝ እጄን ከበስተኋላዬ ስትነካው ከፍዘቴ ነቃሁ። ጋሻዬነህን እጁን ስቤ ወደፊት አዞርኩት፡፡ ከፍ ብለው የሚበርሩ አዕዋፋትን እንደሚከታተል
ወፍ ጠባቂ ዐይኖቼን አሻቅቦ ከፈለገ በኋላ ና ቶሎ! አሁኑኑ ና ቶሎ ብላሃለች እማማዬ» ብሎ መልሴን ለመስማት ኣፉን እንደ ከፈተ ዝም አለ፡፡ ከቁመቱ ጋር ለማስተካከል ጉልበቴን አጥፈ ቁጢጥ አልኩና፣ እኔን ነው እማማዬህን ነው የምትወደው ጋሻዬነህ?» አልኩት።ፊቱ በፈገግታ ፈክቶ የደብር ጉልላት የሚመስሉት ዐይኖቹ በሰፊው ተከፈቱ። «አንተንም እማማዬንም እወዳችኋለሁ...ያንን ቀይ ሽጉጥ እገዛልሃለሁ አላልከኝም ነበር፡ መቼ ትገዛልኛለህ?» ብሎ ዐይን ዐይኔን ሲያይ ዐይኖቹ በዐይኖቼ ውስጥ ሠረጉ፡፡ ትልቋ እማማስ እዚያ ትልቁ ቤት ውስጥ ያየሃቸው
የእኔ እናት አያትህ ጥሩ ናቸው? በል እስኪ ንገረኝ፡ ያንን ሽጉጥ እንድገዛልህ?»አልኩት። ከንፈሩን ትንሽ ሾል ካደረገ በኋላ «እሳቸው ደግሞ በጣም ደስ ሊሉኝ፡
ጥሩ ናቸው፡፡ ያንተ እማማ ናቸው እንዴ? እወዳቸዋለሁ» ካለ በኋላ ትልቅ በመሆኔ ከእናት ያልተወለድኩ ይመስል አወጣጧ የምታምር ሞንሟና ሣቅ ሣቀ።
«እስኪ ትወደኝ እንደሆነ ሳመኝ?» አልኩት፡፡ ጉንጩን ተራ በተራ ሳመ። «ኧረ እባካችሁ ኑ ግቡ! እባትና ልጅ ምን ትማከራላችሁ? እኔ እንዳልሰማችሁ ነው?» የሚል ድምፅ ከወደ ቤት ተሰማ፡፡ የወዲያነሽ ፍቅራዊ ትእዛዝ ስለሆነብኝ ጋሻዬነህን ይዤ ገባሁ፡፡ ቁርስ ይዛ ከተፍ አለች፡፡ የጀመረችውን ሥራ ለመዉረስ
መለስ ስትል «በይ አንሺና ይዘሽው ሂጂ!» ብዩ የካንገት በላይ ቁጣን በሚገልጽ
ስሜት ተናገርኩ፡፡ ደንገጥ ብላ ተመለሰችና «ምነው? ምን አጠፋሁ? የት ልሄድ
ነው? እደርሳለሁ ብዬ ነው ! » በማለት በፍርሃት ሳይሆን በፍቅራዊ ስሜት ትኩር
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....ጋሻዬነህ ከእናቴ ጋር ውሉ አደረ፡፡ የየወዲያነሽ የእናትነት አንጀት በናፍቆት ተላወሰ፡፡ ሮብ ጧት ለቁርስ እንደ ተቀመጥን «ምነው ዝም አልክ ጌታነህ? ረሳኸው እንዴ? ከጋሼ ጉልላት ጋር ምን ምን ነበር የተባባላችሁት?
ሂድና አምጣው እንጂ» አለችኝ፡፡
“ምናልባት ዛሬ የውብነሽ ታመጣው ይሆናል» አልኩና እንደገና ደግሞ
«ምናለባት ጋሻዬነህን ለእነርሱ ብንሰጣቸውና እኔና አንቺ ደግሞ….ሌላ» ብዬ ንግግሬን ሳልጨርስ ደረቷን ሁለት ጊዜ በጥፊ ደቃችና «ህ! እንዴት ያለህው ዓለመኛ ነህ! ምነው ምን በወጣኝ! ዕድሜ ላንተ እያልኩ ዐይን ዐይኑን እንዳላይ ነው!» ብላ ከነጥርጣሬዋ ዝም አለች።
ሐሳብን ማሻሻልና ፈጽሞም መለወጥ አንድ ዐይነት ዕድገት በሆኑ የሐሳቧ መለወጥና ተቃውሞዋ ደስ አለኝ፡፡ ለጥያቄዋ መልስ ሳልሰጥ ወደ ሥራ ሄድኩ፡፡
የውብነሽ ቀንም ሆነ ማታ ብቅ ሳትል ቀረች፡፡ የሮብ ጀንበር ጠልቃ የሐሙሷ ተወለደች፡፡ አዲሱ የፍርሃት ሸክም ከየወዲያነሽ ይልቅ እኔን ከበደኝ፡፡ ከማታ
ትምህርት መልስ ሻይ እየጠጣን ስናወራ አንዱን ተረስቶ የቀረ የጋሻዬነህን የሒሳብ ደብተር እያገላበጠች «እሷ መች ሥራ አጣችና ነው ይዛው ትመጣለች
የምትለው? እኔ እኮ ነገሩ የገባኝ የመማሪያ ደብተሩን ይዛ ስትሒድ ነው» ብላ ወደ ራሷ ደብተሮች መለስ አለች፡፡
«እኔን ያሠጋኝ ሌላው አይደለም.....አባባ ይመለሳል ከተባለበት ቀን ቀደም ብሎ ቢመለስና ይኸ ልጅ የማን ነው ልጅ? ብሎ ቢጠየቅ ምን ይላሉ?
እናቴ ገና እንማከራለን ነው ያለችኝ እንጂ ሌላ የተነጋገርነው ነገር የለም ከማለቴ፣ የማን ልጅ እንዲባልልህ ትፈልጋለህ? የጌታነህ ልጅ ነው ብለው
ይነግሩልሃላ» ብላ ኩታ አጣፍቶ የመልበስ ያህል ጉዳዩን አቃልላ መለሰችልኝ።
«እንዴት አንቺ? እኔ እኮ ገና ብዙ ግብግብና ትግል ይጠብቀኛል።
የሙሉ ድሌ ቀኔ ገና ነው:: ምኑ ተያዘና!ምኑ ተነካና! እንዴት አድርጌ እንደምገጥመውና ድል እንደማደርገው ዕቅድና ብልሃቴ አልተጠናቀቀም፡፡ወደፊት የሚቀረኝ የትግል ጉራንጉር ያለፉትን የመከራና የትግል ገድሎች ሁሉ ሊያጠቃልል ይችላል፡፡ ቀሪው ትግል በዕድልና በአጋጣሚ የማምንበት ነገር
የለም፡፡ የሚጠብቀኝ ውጣ ውረድ ሁሉ በበቂ ምክንያትና በተግባር የሚመራ ነው። «የዘልማድ ዝላይና ባወጣ ያውጣኝ በቃው! በቂ ምክንያት ጥሩ የተግባር
ዋስትና» ብዬ በመጀመር ለወደፊት ከሚያጋጠሙኝ አንደንድ ችግሮች መኻል አንዳንዶቹን በከፊል አዋየኋት፡፡
ዓርብ ከጧቱ ሁለት ሰዓት ላይ የውብነሽ ጋሻዬነህን ይዛ መጣች።
የሚያምር አዲስ ልብስ ለብሶ
ከፈገግታው ጋር ሲታይ የመስከረም ዝናብ ያጠባት
የለጋ ዘንባባ ተክል መስሏል። የወዲያነሽ ግልገሏን አስከትላ ጢሻ ውስጥ እንደምትገባ ሰስ ልጅዋን አስከትላ ወደ ጓዳ ገባች። እኔና የውብነሽ ወጣ ብለን ሰበሰቡ ላይ እንደቆምን «አባባ የነገ ሳምንት ከሰዓት በኋላ ይገባል፡፡ ባለቢትህን እንዴት አድርገን እሱ ፊት እንደምናቀርባት፡ አንተም ምንና ምን እያልክ መናገርና ማስረዳት እንዳለብህ አንድ ባንድ አውጥተን አውርደን ጨርሰናል» ብላ ስለ እኛ ሕይወት እኔና ባለቤቴ ያልተካፈልንበትን የአፈጻጸም ዕቅድ አረዳችኝ፡፡
የችግሬን ዐይነትና ዓላማዬን የማውቀው እኔ ሆኜ ሳለሁ መወከልና ማስፈጸም
የማይገባቸው እኅቴና እናቴ አፈ ቀላጤ ሆነን እንገኝ ሲሉ በመስማቴ ተናደድኩ፡፡
አልተዋጠልኝም፡፡
የአባቴ ግብዝነትና ቁጣዉ፣ ግትርነቱንና የመጣ ይምጣ ባይነቱ፣ እንደ ጨካኝ አገረ ገዢ ፊት ለፊት ቆሞ እንደ እሳት ፈጀኝ፡፡ «ማታ ከትምህርት ቤት
መልስ ከየወዲያነሽ ጋር እንድትመጡ፣ ነገሩን አብራራልሃለሁ። አሁን ግን
ቸኩያለሁ ደኀና ዋል» ብላኝ ቶሉ ብለህ ና እንደ ተባለ መልእክተኛ ጥላኝ ሄደች። አእምሮዬ በሐሳብ ተወቃ፡፡ ሁለመናዬ ብው ብሎ ጋመ፡፡ አዳዲስ ጭንቀቶች በውስጤ ተራወጡ፡፡ የሐሳቤ አድማስ ለመጥበብም ሆነ ለመስፋት ባለመቻሉ መረጋጊያ አጣሁ፡፡
ጎርፍ እንደ ገረሰሰው ዛፍ ግድግዳውን ተደግፌ ቆምኩ፡፡ የወዲያነሽ ከወደ ውስጥ መጥታ «ከምን ጊዜው ሄደች? ያንተ ነገር እኮ...አናደድካት እንዴ?» ብላ
በሥጋት አዘል ሁኔታ ጠየቀችኝ፡፡ «ቸኩላ ነበር፡ ታናድደኛለች እንጂ ምን አናድዳታለሁ፡፡ የማይጠቅሙሽ እጠቅምሻለሁ፣ የሚያጠፉሽ አለማሻለሁ፣
የሚገድሉሽ አድንሻለሁ ሲሉሽ አትናደጂም? አሁን የነገረችኝን ማታ ስትነግረኝ ትሰሚያታለሽ፡፡ አሁን ወደ ሥራሽ ሂጂ» ብያት ዝም አልኩ፡፡ የእርሷ ከአጠገቤ
ገለል ማለት የሚረዳኝ ስለ መሰላት ተመልሳ ገባች፡፡ በአካባቢዬ የሚገኙት ነገሮች
ሁሉ ለችግሮች ማቃለያ የሚሆን ብልሃት ያቀርቡልኝ ይመስል ትክ ብዬ አየኋቸው:: ሆኖም ከበድን መልስ የለምና አፍጥጨ ቀረሁ። ሳላስበው ከቤት ወጣ ብዬ ቆምኩ፡፡ የማለዳዋ ፀሐይ ደጋናማ ጉዞዋን ጀምራለች፡፡ ደመና የማይታይበትን ሰማይ ትኩር ብሎ ላየው ኣስፈሪነቱ አይጣል! ዘልዓለም የሚሉት ይህን ርቀትና
ጥልቀት ይሆን? አንጋጥጬ ስመለከት ሐሳብ አሽቆልቁሎ አየኝ፡፡ አካባቢዬን ፈራሁት፡፡ ጥቂት ርምጃ ተራምጄ ግቢው መኻል ተገተርኩ፡፡ ከመሬት ውስጥ
መልስ ይፈልቅልኝ ይመስል ደቃቁን አፈርና ኮረት ባይኔ ሰለልኩት። ቀዝቃዛና ለስላሳ ትንሽ እጅ የቀኝ እጄን ከበስተኋላዬ ስትነካው ከፍዘቴ ነቃሁ። ጋሻዬነህን እጁን ስቤ ወደፊት አዞርኩት፡፡ ከፍ ብለው የሚበርሩ አዕዋፋትን እንደሚከታተል
ወፍ ጠባቂ ዐይኖቼን አሻቅቦ ከፈለገ በኋላ ና ቶሎ! አሁኑኑ ና ቶሎ ብላሃለች እማማዬ» ብሎ መልሴን ለመስማት ኣፉን እንደ ከፈተ ዝም አለ፡፡ ከቁመቱ ጋር ለማስተካከል ጉልበቴን አጥፈ ቁጢጥ አልኩና፣ እኔን ነው እማማዬህን ነው የምትወደው ጋሻዬነህ?» አልኩት።ፊቱ በፈገግታ ፈክቶ የደብር ጉልላት የሚመስሉት ዐይኖቹ በሰፊው ተከፈቱ። «አንተንም እማማዬንም እወዳችኋለሁ...ያንን ቀይ ሽጉጥ እገዛልሃለሁ አላልከኝም ነበር፡ መቼ ትገዛልኛለህ?» ብሎ ዐይን ዐይኔን ሲያይ ዐይኖቹ በዐይኖቼ ውስጥ ሠረጉ፡፡ ትልቋ እማማስ እዚያ ትልቁ ቤት ውስጥ ያየሃቸው
የእኔ እናት አያትህ ጥሩ ናቸው? በል እስኪ ንገረኝ፡ ያንን ሽጉጥ እንድገዛልህ?»አልኩት። ከንፈሩን ትንሽ ሾል ካደረገ በኋላ «እሳቸው ደግሞ በጣም ደስ ሊሉኝ፡
ጥሩ ናቸው፡፡ ያንተ እማማ ናቸው እንዴ? እወዳቸዋለሁ» ካለ በኋላ ትልቅ በመሆኔ ከእናት ያልተወለድኩ ይመስል አወጣጧ የምታምር ሞንሟና ሣቅ ሣቀ።
«እስኪ ትወደኝ እንደሆነ ሳመኝ?» አልኩት፡፡ ጉንጩን ተራ በተራ ሳመ። «ኧረ እባካችሁ ኑ ግቡ! እባትና ልጅ ምን ትማከራላችሁ? እኔ እንዳልሰማችሁ ነው?» የሚል ድምፅ ከወደ ቤት ተሰማ፡፡ የወዲያነሽ ፍቅራዊ ትእዛዝ ስለሆነብኝ ጋሻዬነህን ይዤ ገባሁ፡፡ ቁርስ ይዛ ከተፍ አለች፡፡ የጀመረችውን ሥራ ለመዉረስ
መለስ ስትል «በይ አንሺና ይዘሽው ሂጂ!» ብዩ የካንገት በላይ ቁጣን በሚገልጽ
ስሜት ተናገርኩ፡፡ ደንገጥ ብላ ተመለሰችና «ምነው? ምን አጠፋሁ? የት ልሄድ
ነው? እደርሳለሁ ብዬ ነው ! » በማለት በፍርሃት ሳይሆን በፍቅራዊ ስሜት ትኩር
👍6