#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
.....“እህ • ውጤት እንዴት ነው ?” አለ ገና ሲያያት "
“ ኮንግራጁሌሽን ! አልፌአለሁ” አለችው በተቀመጠበት ልታቅፈው እየተንደረደረች
“ ወዳጅ ዘመድ ይኑር በይ ” አላት እርዳታውን ለመጠቀምም ።
“ ይኑር ! ” ብላ አንገቱ ላይ ተጠመጠመችና ጉንጬን ሳመችው
"ምን ምን ደኅና አገኘሽ ? ” ሲል ጠየቃት
“ ሒሳብ “ 203 ” ጎጆ ሠርቻለሁ
በዩኒቨርስቲ ውስጥ “F ያገኙበትን ትምህርት ባንዲራ ሰቅያለሁ” ሲባል “ A ? ያገኙበትን ትምህርት ደግሞ ፡ “ ጎጆ ሠርቻለሁ” ማለት የተለመደ ቋንቋ ሆኖአል
“ እሱማ የኔው ነው ” አላት እንደገና ባለውለታነቱን ለመጠቆም
“ እኮ ! ” አለችው እየቦረቀች ።
ታዲያ ጎጆውን የሰራው ማነው ? እኔ ነኝ ወይስ አንቺ ? ”
“ አንተ!” ብላው እንደገና ልትስመው ከንፈሯን ስታስጠጋው በሩ በድንገት ብርግድ አለ ። ሁለቱም እንደ ተቃቀፉ
ክው ብለው ቀሩ የገባው ሳምሶን ጉልቤው ነበር ። አውሬ መስሎ
ታያቸው
ሁኔታቸው የፊልም ትርኢት መሰለ ። እነሱ ዱብ ዕዳ እንደ ወረደባቸው ፍቅረኞቹ በጭንቀት ተቃቅፈው ሳምሶን ቆሞ በፍቅረኞቹ ላይ ሽጉጡን የደገነ ፥ " ቴክስ” ይመስል ነበር።
“ ምን ፈለግክ ? ” አለው ለማ ድንጋጤው ከበረደለት በኋላ በትዕቢት ድምፅ ። ሳምሶን ለእሱ አልመለሰለትም ።
“ አንቺ ሸርሙጣ!” አላት ቤተልሔም ላይ አፍጥጦ። እናንተ አስተማሪ እያወረዳችሁ ትኖራላችሁ ፤ እኛ ግን እንባረራለን ! ”
“ ወይኔ ! ” ብላ ቤተልሔም ለማ ሥር ሽጉጥ አለች። ሊውጣት የመጣ ነው የመሰላት ። ዐይኖቹ ውስጥ የሚንቀ
ለቀለው የንዴት እሳት አስፈራት። ሽንቷ አምልጧት ጭርር ሲል ተሰማትና ጭንና ጭኗን አጋጠመች ።
ለማና ሳምሶን ተፋጠጡ ። የአንበሳና የነብር ፍጥጫ መሰለ ። በጉልበቱ የሚተማመነው ሳምሶን ለማ ፊት እንደ
ቆመ ጡንቻውን ለመሰንዘር ምን እንዳገደው ለማሰብ ሞከረ፡ ሕግ ! የሰዎችን የስሜት ፈረስ ለጉሞ ሲይዝ ታየው ።
“ እንዴዬ ! አሁን ምንድነው የፈለግከው ? ” አለው "ከተቀመጠበት ለመነሣት እያሰላ
“ ምን አገባህ ! ” ብሎ ሳምሶን ሌላ መናገር ፈርቶ እንዳፈጠጠ'ያላየው ሰው ከኋላ መጥቶ በድንገት ትከሻውን
ጨመደደው ።
“ምን ማድረግህ ነው ሳምሶን ? ” አለው እስክንድር ትከሻውን እንደ ጨመደደ ከቢሮው ሊያስወጣው እየታገለ ።
ከእሱና ከአቤል ተለይቶአቸው መምጣቱ ከንክኖት ነበር እስክንድር እየሮጠ የደረሰበት ።
“ ልቀቀኝ ! ” አለው ሳምሶን መጋበዙ እልሁን አግሎበት ።
እስክንድር በግድ እየጎተት ከቢሮው ካወጣው በኋላ
“ ዕረፍ ሳምሶን ” አለው ፡ “ ነገሮችን ለማመዛዘን ሞክር ።ለማ ቤተልሔምን ይጠቅማት ይሆናል እንጂ አንተን አይ
ጎዳህም ። ምክንያቱም ቀድሞ የምትዋደዱበት ወይም የምትጣሉበት ምንም ግንኙነት አልነበራችሁም
“ እንጃልህ ! ” አለና እሱም ላይ አፈጠጠበት ። “ ወቼ ጉድ ! ዛሬስ ለእኔም አይመለስ ” አለና ቀስ ብሎ እያባበለሀው ይዞት ሔደ ።
እስክንድርና አቤል ፥ ሳምሶንን እያባበሉ ወደ መኝታ ክፍሉ ከወሰዱት በኋላ ስለ ራሳቸው ለማሰብ ተገደዱ። የሌላውን የፈተና ውጤት የሰማው ጆሮአቸው የራሳቸውን ለመስማት ተጣደፈ ። መውደቅና ማለፍ ሁለቱ ተቃራኒ ነገሮች
እስካሉ ድረስ ፥ መከሠታቸው የግድ ቢሆንም ፡ የማንም አእምሮ በቀላሉ አይቀበላቸውም ። ከሰዓት በኋላው ለእነአቤል በጣም ራቀባቸው ። በተለይ አቤል የትዕግሥትን ማለፍ ከሰማ በኋላ የራሱን ውጤት ለማወቅ ለምን እንደሚጓጓ ሊገባው አልቻለም ። ምናልባት ተአምር ይወርድ ይሆን ?
ሁለቱም፥ ውጤት ከሰማው ተማሪ ጋር መቀላቀል አልፈለጉም ። ግን ጆሮአቸውን በጥጥ አይደፍነት ነገር! ባለፉ ባገደሙበት ቦታ ተማሪው በቡድን ቆሞ አንዱን ሲያነሣ አንዱን ሲጥል መስማት እሰለቻቸው ። አንዱ በአንዱ ሲቀና ወይም ደግሞ መምህሩን ሲወነጅል ነው የሚሰማው ።
በዚህ ዓለም ላይ ማን ይሆን ለኅሊናው ሐቀኛ የሆነ ፍጡር ! ሁሌም የራሱን ማንነት ደብቆ ሌላውን ሲወነጅል
ነው የሚገኘው ሁሉም ። ተማሪው አስተማሪውን በማርክ አሰጣጥ ይወነጅላል።ሠራተኛ አለቃውን ይወነጅላል።አለቃም ድክመቱን በበታች ሠራተኛ ላይ ይለጥፋል ። ለዚህ ምንጩ
ምን ይሆን ? የአስተዳደጋችንና የአኗኗራችን ኋላቀርነት የፈጠረብን ችግር ይሆን እንዴ ? ምናለበት አንዱ ሌላውን ከመወንጀሉ በፊት ፡ « ለመሆኑ እኔ ማን ነኝ ? ” ብሎ ራሱን መጠየቅ ቢችል ? አንዱ ከሌላዉ ጋር የሚኖረው የግንኙነት መሠረት ሥራና የሀገር ፅድት ሆኖ ሳለ ፥ እርስ በርስ መቦጫጨቅ ቢቀር ምናለበት ? ማንም ከምድር በላይ ወይም
ከምድር በታች ላይኖር ለመበላለጥ በምናደርገው ቅናት የበዛበት ፉክቻና ግላዊ ርኩቻ የጋራችን የሆነችውን ምድር
ባንጎዳት ምናለበት ? እስክንድር በሸቀ ።
ከቀትር በኋላ፥ከነእስክንድርና ከአቤል ቀድሞ ውጤቱን የተመለከተው "ድብርት ” ነበር ።
“ ውጤት ወጥቷል ” አላቸው ፡ የራሱን አይቶ ወደ መኝታ ክፍሉ ከተመለሰ በኋላ ደስታ አፍኖት ሲያልጎመጉም ጥርሱን አሳይቶ አልሣቀም ።
"ያንተ እንዴት ነው ? ” አሉት ።
"ግሩም ነው !
“ ስንት ጎጆ ሠራህ ? ” አለው እስክንድር
ሦስቱን ጣቶቹን አሳያቸው ።
“ የጉልበት ዋጋ ነው !” አለ እስክንድር በልቡ የድብርት ” አጠናን ምንጊዜም የጉልበት ሥራ ያህል በመታገልና
ብዙ ሰዓት በማጥናት ስለሆነ፡በጉልበቱ ዩኒቨርስቲ መቆየቱን ሁሉም ያውቅለታል "
ወዲያው እስክንድርና አቤል ተያይዘው ወደ ሰሌዳው ሔዱ። የሦስተኛና የአራተኛ ዓመት ተማሪዎች ቁጥር ያን ያህል ብዛት ስለ ሌለው በቀላሉ ወደ ሰሌዳው ተጠግተው ተመለከቱ ። እስክንድር በጥሩ ውጤት ዐልፏል ። የአቤል
ውጤት ግን አልወጣም ። አቤል ራሱን ማመን አቅቶት የመታወቂያ ወረቀቱን
ከኪሱ አውጥቶ የመለያ ቁጥሩን ተመለከተ ። ያ ቁጥር ሰሌዳው ላይ የለም ማለፍም ሆነ መውደቅ የግድ ሰሌዳ ላይ
መውጣት አለበት ። እና የአቤል ከዚህ ከሁለቱ ውጭ ምን ሊሆን ይችላል ?
የእስክንድር ማለፍ ሲያስደስታቸው፡ በሌላ በኩል ደግሞ የአቤል ጉዳይ ሁለቱንም ግራ አጋባቸው ። እስክንድር
ልቡ ፈራ ። ስሜቱ መጥፎ ነገር ጠረጠረ ። ለማንኛውም ተያይዘው ውጤቱ ወደ ተዘጋጀበት ቢሮ ሒዱ ።
“ አቤት ! ምን ነበር ? " አለቻቸው ጸሐፊዋ ፡ የምታንቀጭቅጨውን ታይፕ አቋርጣ ። “ የእሱ ውጤት አልወጣም ። እና ... ብሎ እስክንድር ወደ አቤል እያመለከተ
ንግግሩን ሳይጨርስ አቋረጠችው ።
« ስሙ ማን ነው ? ”
“ አቤል ። የፍልስፍና ትምህርት ክፍል
“አሃ ! አቤል ሙሉዬ ፡ ያንተ ውጤት አልደረሰንም እስኪ ዮናታንን ሒደህ አነጋግራቸው አለችና ሥራዎን
ቀጠለች ።
“ውጤቱ ዮናታን ጋር ምን ያደርጋል?” አለ አቤል በልቡ።ዮናታንን ማየት አልፈለገም ነበር ። በዝጉ ውስጥ ሲሸሻቸው ነው የከረመው። ምክራቸውን አለመስማቱና ሕክምናውን ያለ መቀጠሉ እያሳፈሩት ከእሳቸው ለመራቅ ምክሮ ነበር።
የግዱን ከእስክንድር ጋር ሆኖ ወደ ዮናታን ቢሮ ሔደ።ዮናታን የሉም ። ቢሮኣቸው ተቆልፎአል ።
“ ምን ይሻላል ? ” አለ የእስክንድርን ዐይን ዐይን እያየ
“ ምን ይሻላል ? ” ብሎ እስክንድርም ቃሉን በትካዜ ድምፅ ከደገመ በኋላ ፥ “ እንግዲህ ነገ መጥተን እንጠይቃቸዋለን " መቼም ከአሁን በኋላ አይገቡም ” አለው እያስተዛዘነ።
ነገ እንዴት ይነጋ ይሆን ? የጭንቅ ምሽት ፤የመከራ ሕልም ሌሊት ።
በማግሥቱ ጠዋት አቤልና እስክንድር ዮናታንን ቀድመው ነበር፡ ከቢሮአቸው የደረሱት ።አቤል ዐይናቸውን ማየት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
.....“እህ • ውጤት እንዴት ነው ?” አለ ገና ሲያያት "
“ ኮንግራጁሌሽን ! አልፌአለሁ” አለችው በተቀመጠበት ልታቅፈው እየተንደረደረች
“ ወዳጅ ዘመድ ይኑር በይ ” አላት እርዳታውን ለመጠቀምም ።
“ ይኑር ! ” ብላ አንገቱ ላይ ተጠመጠመችና ጉንጬን ሳመችው
"ምን ምን ደኅና አገኘሽ ? ” ሲል ጠየቃት
“ ሒሳብ “ 203 ” ጎጆ ሠርቻለሁ
በዩኒቨርስቲ ውስጥ “F ያገኙበትን ትምህርት ባንዲራ ሰቅያለሁ” ሲባል “ A ? ያገኙበትን ትምህርት ደግሞ ፡ “ ጎጆ ሠርቻለሁ” ማለት የተለመደ ቋንቋ ሆኖአል
“ እሱማ የኔው ነው ” አላት እንደገና ባለውለታነቱን ለመጠቆም
“ እኮ ! ” አለችው እየቦረቀች ።
ታዲያ ጎጆውን የሰራው ማነው ? እኔ ነኝ ወይስ አንቺ ? ”
“ አንተ!” ብላው እንደገና ልትስመው ከንፈሯን ስታስጠጋው በሩ በድንገት ብርግድ አለ ። ሁለቱም እንደ ተቃቀፉ
ክው ብለው ቀሩ የገባው ሳምሶን ጉልቤው ነበር ። አውሬ መስሎ
ታያቸው
ሁኔታቸው የፊልም ትርኢት መሰለ ። እነሱ ዱብ ዕዳ እንደ ወረደባቸው ፍቅረኞቹ በጭንቀት ተቃቅፈው ሳምሶን ቆሞ በፍቅረኞቹ ላይ ሽጉጡን የደገነ ፥ " ቴክስ” ይመስል ነበር።
“ ምን ፈለግክ ? ” አለው ለማ ድንጋጤው ከበረደለት በኋላ በትዕቢት ድምፅ ። ሳምሶን ለእሱ አልመለሰለትም ።
“ አንቺ ሸርሙጣ!” አላት ቤተልሔም ላይ አፍጥጦ። እናንተ አስተማሪ እያወረዳችሁ ትኖራላችሁ ፤ እኛ ግን እንባረራለን ! ”
“ ወይኔ ! ” ብላ ቤተልሔም ለማ ሥር ሽጉጥ አለች። ሊውጣት የመጣ ነው የመሰላት ። ዐይኖቹ ውስጥ የሚንቀ
ለቀለው የንዴት እሳት አስፈራት። ሽንቷ አምልጧት ጭርር ሲል ተሰማትና ጭንና ጭኗን አጋጠመች ።
ለማና ሳምሶን ተፋጠጡ ። የአንበሳና የነብር ፍጥጫ መሰለ ። በጉልበቱ የሚተማመነው ሳምሶን ለማ ፊት እንደ
ቆመ ጡንቻውን ለመሰንዘር ምን እንዳገደው ለማሰብ ሞከረ፡ ሕግ ! የሰዎችን የስሜት ፈረስ ለጉሞ ሲይዝ ታየው ።
“ እንዴዬ ! አሁን ምንድነው የፈለግከው ? ” አለው "ከተቀመጠበት ለመነሣት እያሰላ
“ ምን አገባህ ! ” ብሎ ሳምሶን ሌላ መናገር ፈርቶ እንዳፈጠጠ'ያላየው ሰው ከኋላ መጥቶ በድንገት ትከሻውን
ጨመደደው ።
“ምን ማድረግህ ነው ሳምሶን ? ” አለው እስክንድር ትከሻውን እንደ ጨመደደ ከቢሮው ሊያስወጣው እየታገለ ።
ከእሱና ከአቤል ተለይቶአቸው መምጣቱ ከንክኖት ነበር እስክንድር እየሮጠ የደረሰበት ።
“ ልቀቀኝ ! ” አለው ሳምሶን መጋበዙ እልሁን አግሎበት ።
እስክንድር በግድ እየጎተት ከቢሮው ካወጣው በኋላ
“ ዕረፍ ሳምሶን ” አለው ፡ “ ነገሮችን ለማመዛዘን ሞክር ።ለማ ቤተልሔምን ይጠቅማት ይሆናል እንጂ አንተን አይ
ጎዳህም ። ምክንያቱም ቀድሞ የምትዋደዱበት ወይም የምትጣሉበት ምንም ግንኙነት አልነበራችሁም
“ እንጃልህ ! ” አለና እሱም ላይ አፈጠጠበት ። “ ወቼ ጉድ ! ዛሬስ ለእኔም አይመለስ ” አለና ቀስ ብሎ እያባበለሀው ይዞት ሔደ ።
እስክንድርና አቤል ፥ ሳምሶንን እያባበሉ ወደ መኝታ ክፍሉ ከወሰዱት በኋላ ስለ ራሳቸው ለማሰብ ተገደዱ። የሌላውን የፈተና ውጤት የሰማው ጆሮአቸው የራሳቸውን ለመስማት ተጣደፈ ። መውደቅና ማለፍ ሁለቱ ተቃራኒ ነገሮች
እስካሉ ድረስ ፥ መከሠታቸው የግድ ቢሆንም ፡ የማንም አእምሮ በቀላሉ አይቀበላቸውም ። ከሰዓት በኋላው ለእነአቤል በጣም ራቀባቸው ። በተለይ አቤል የትዕግሥትን ማለፍ ከሰማ በኋላ የራሱን ውጤት ለማወቅ ለምን እንደሚጓጓ ሊገባው አልቻለም ። ምናልባት ተአምር ይወርድ ይሆን ?
ሁለቱም፥ ውጤት ከሰማው ተማሪ ጋር መቀላቀል አልፈለጉም ። ግን ጆሮአቸውን በጥጥ አይደፍነት ነገር! ባለፉ ባገደሙበት ቦታ ተማሪው በቡድን ቆሞ አንዱን ሲያነሣ አንዱን ሲጥል መስማት እሰለቻቸው ። አንዱ በአንዱ ሲቀና ወይም ደግሞ መምህሩን ሲወነጅል ነው የሚሰማው ።
በዚህ ዓለም ላይ ማን ይሆን ለኅሊናው ሐቀኛ የሆነ ፍጡር ! ሁሌም የራሱን ማንነት ደብቆ ሌላውን ሲወነጅል
ነው የሚገኘው ሁሉም ። ተማሪው አስተማሪውን በማርክ አሰጣጥ ይወነጅላል።ሠራተኛ አለቃውን ይወነጅላል።አለቃም ድክመቱን በበታች ሠራተኛ ላይ ይለጥፋል ። ለዚህ ምንጩ
ምን ይሆን ? የአስተዳደጋችንና የአኗኗራችን ኋላቀርነት የፈጠረብን ችግር ይሆን እንዴ ? ምናለበት አንዱ ሌላውን ከመወንጀሉ በፊት ፡ « ለመሆኑ እኔ ማን ነኝ ? ” ብሎ ራሱን መጠየቅ ቢችል ? አንዱ ከሌላዉ ጋር የሚኖረው የግንኙነት መሠረት ሥራና የሀገር ፅድት ሆኖ ሳለ ፥ እርስ በርስ መቦጫጨቅ ቢቀር ምናለበት ? ማንም ከምድር በላይ ወይም
ከምድር በታች ላይኖር ለመበላለጥ በምናደርገው ቅናት የበዛበት ፉክቻና ግላዊ ርኩቻ የጋራችን የሆነችውን ምድር
ባንጎዳት ምናለበት ? እስክንድር በሸቀ ።
ከቀትር በኋላ፥ከነእስክንድርና ከአቤል ቀድሞ ውጤቱን የተመለከተው "ድብርት ” ነበር ።
“ ውጤት ወጥቷል ” አላቸው ፡ የራሱን አይቶ ወደ መኝታ ክፍሉ ከተመለሰ በኋላ ደስታ አፍኖት ሲያልጎመጉም ጥርሱን አሳይቶ አልሣቀም ።
"ያንተ እንዴት ነው ? ” አሉት ።
"ግሩም ነው !
“ ስንት ጎጆ ሠራህ ? ” አለው እስክንድር
ሦስቱን ጣቶቹን አሳያቸው ።
“ የጉልበት ዋጋ ነው !” አለ እስክንድር በልቡ የድብርት ” አጠናን ምንጊዜም የጉልበት ሥራ ያህል በመታገልና
ብዙ ሰዓት በማጥናት ስለሆነ፡በጉልበቱ ዩኒቨርስቲ መቆየቱን ሁሉም ያውቅለታል "
ወዲያው እስክንድርና አቤል ተያይዘው ወደ ሰሌዳው ሔዱ። የሦስተኛና የአራተኛ ዓመት ተማሪዎች ቁጥር ያን ያህል ብዛት ስለ ሌለው በቀላሉ ወደ ሰሌዳው ተጠግተው ተመለከቱ ። እስክንድር በጥሩ ውጤት ዐልፏል ። የአቤል
ውጤት ግን አልወጣም ። አቤል ራሱን ማመን አቅቶት የመታወቂያ ወረቀቱን
ከኪሱ አውጥቶ የመለያ ቁጥሩን ተመለከተ ። ያ ቁጥር ሰሌዳው ላይ የለም ማለፍም ሆነ መውደቅ የግድ ሰሌዳ ላይ
መውጣት አለበት ። እና የአቤል ከዚህ ከሁለቱ ውጭ ምን ሊሆን ይችላል ?
የእስክንድር ማለፍ ሲያስደስታቸው፡ በሌላ በኩል ደግሞ የአቤል ጉዳይ ሁለቱንም ግራ አጋባቸው ። እስክንድር
ልቡ ፈራ ። ስሜቱ መጥፎ ነገር ጠረጠረ ። ለማንኛውም ተያይዘው ውጤቱ ወደ ተዘጋጀበት ቢሮ ሒዱ ።
“ አቤት ! ምን ነበር ? " አለቻቸው ጸሐፊዋ ፡ የምታንቀጭቅጨውን ታይፕ አቋርጣ ። “ የእሱ ውጤት አልወጣም ። እና ... ብሎ እስክንድር ወደ አቤል እያመለከተ
ንግግሩን ሳይጨርስ አቋረጠችው ።
« ስሙ ማን ነው ? ”
“ አቤል ። የፍልስፍና ትምህርት ክፍል
“አሃ ! አቤል ሙሉዬ ፡ ያንተ ውጤት አልደረሰንም እስኪ ዮናታንን ሒደህ አነጋግራቸው አለችና ሥራዎን
ቀጠለች ።
“ውጤቱ ዮናታን ጋር ምን ያደርጋል?” አለ አቤል በልቡ።ዮናታንን ማየት አልፈለገም ነበር ። በዝጉ ውስጥ ሲሸሻቸው ነው የከረመው። ምክራቸውን አለመስማቱና ሕክምናውን ያለ መቀጠሉ እያሳፈሩት ከእሳቸው ለመራቅ ምክሮ ነበር።
የግዱን ከእስክንድር ጋር ሆኖ ወደ ዮናታን ቢሮ ሔደ።ዮናታን የሉም ። ቢሮኣቸው ተቆልፎአል ።
“ ምን ይሻላል ? ” አለ የእስክንድርን ዐይን ዐይን እያየ
“ ምን ይሻላል ? ” ብሎ እስክንድርም ቃሉን በትካዜ ድምፅ ከደገመ በኋላ ፥ “ እንግዲህ ነገ መጥተን እንጠይቃቸዋለን " መቼም ከአሁን በኋላ አይገቡም ” አለው እያስተዛዘነ።
ነገ እንዴት ይነጋ ይሆን ? የጭንቅ ምሽት ፤የመከራ ሕልም ሌሊት ።
በማግሥቱ ጠዋት አቤልና እስክንድር ዮናታንን ቀድመው ነበር፡ ከቢሮአቸው የደረሱት ።አቤል ዐይናቸውን ማየት
👍2❤1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#ክፍል_ሶስት
#ትንሣኤ
በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሠረት የምርኮኞች ልውውጥ የሚጀመርበት የመጀመሪያው ምዕራፍ......
የድሬዳዋ ከተማ አሸብርቃለች፡፡ ገንደቆሬ፣ ገንደገራዳ፣ መጋላ፣ ከዚራ፣ ለገሀሬ፣ ..... መንደሮች በሙሉ በደስታ ስቀዋል፡፡
በየመንገዱ ግራና ቀኝ ተተክለው ቀዝቃዛና፤ ነፋሻማ አየርን የሚረጩት ዛፎች በደስታ ተውጠው የሚደንሱ ይመስላሉ፡፡ በዚያች ምድር ላይ የተካሄደው ቀውጢ ጦርነት አልፎ፤ ያንን የመሰለ የሰላም አየር መተንፈስ መቻል ዳግማዊ ልደት ነው፡፡
በሐረርጌ ምድር፡፡ በደገሀቡር፣ ቀብሪደሀር፣ መራራሌ፣ በሺላቦ፣
ደቦይን፣ በቆራሄ አሸዋማ ሜዳ፣ በኦጋዴን በረሃ፣ በካራማራ ተራሮችና በሌሎችም ሺህ ሌሊት ሺህ መአልት የፈሰሰው ደም፣ የተከሰከሰው አጥንት፣ያስገኘው ውጤት፡፡
በዚያን ቀውጢ ሰዓት ላይ ለዳር ድንበር ሲሉ ከጠላት ጋር እየተናነቁ አኩሪ ገድል የፈጸሙት፤ በደማቸው ማህተም፤ በአጥንታቸው ክስካሽ፤ ምድሪቱን ያቀሉት...የመስዋዕትነት ፈርጦች! የሚጠበቁበት ዕለት......
ሰማዩ በዚያን ቀውጢ የጦርነት ወቅት በኢትዮጵያ አየር ሃይል የተሠራውን አስደናቂ ትርኢትና ተአምር አፍ አውጥቶ ሊናገር፣ የታሪክ ምስክርነቱን ሊሰጥ፣ የተዘጋጀ ይመስል አጉረመረመ፡፡ ለሚወዷት እናት አገራቸው ዳር ድንበር ሲሉ የተፋለሙና ልዩ ልዩ ጀብድ ከፈጸሙ በኋላ በጠላት እጅ ወድቀው በባእድ ሀገር በምርኮኝነትና፤ በእስረኝነት ለበርካታ
አመታት ከቆዩ በኋላ በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሰረት ዛሬ ወደሚያፈቅሯትና፤ ወደሚወዷት፤ እናት አገራቸው የሚመለሱበት እለት ስለሆነ፤ እነዚህን ውድ የሀገር አለኝታዎችና፤ ጀግኖች፤በልዩና፤ በደማቅ አቀባበል ፤ ሊቀበል ህዝቡ የአውሮፕላን
ማረፊያውን አካባቢ አጥለቅልቆታል....
ማርሽ የሚያሰማው ሠራዊት በተጠንቀቅ ቆሞ ይጠባበቃል።ባንዲራዎች ይውለበለባሉ፡፡ ህዝቡ ይሯሯጣል፡፡ ይራወጣል። ሰማይ ሰማዩን እያንጋጠጠ ይመለከታል፡፡
አንዳንድ ጊዜ ትላልቅ አሞራዎች ያሳስታሉ፡፡ የሁሉም ልብ ተንጠልጥሏል፡፡ እነማን ይሆኑ?! ሞቱ ተብለው ደረት
የተመታላቸው፣ ተዝካር የተበላላቸው፣ ማን ያውቃል? በህይወት ሊገኙ
ይችሉ ይሆናል፡፡ ይህ ጦርነት በተካሄደባቸው ብዙ አገሮች በተደጋጋሚ
የታየ ክስተት ነው፡፡
ሰዓቱ ደረሰ፡፡ ሰማዩ እንደገና በከፍተኛ ድምፅ አጉረመረመ፡፡አውሮፕላኗ በርቀት ታየች፡፡ ከዚያም እየጐላች ፤እየጐላች፤ መጣችና፤በማረፊያው ላይ እየዞረች፤ ማንዣባብ ጀመረች።
የሰው ጩኸት ሁካታ... ግርግር... ትርምሱ...ሌላ ሆኗል፡፡ማርሽ በረጅሙ ይሰማል፡፡ አውሮፕላኗ አዘቀዘቀች..... ከዚያም አኮበኮበችና አረፈች፡፡
ጀግኖች የታደሙባት አውሮፕላን! ለዳር ድንበሯ ሱሉ ደማቸውን ያፈሰሱላትን፣ በእስር የማቀቁላትን፣ ጥለው የወደቁላትን፣ ታስረው የተገረፉላትን፣ የጦር ምርኮኞችን ይዛ ይሄውና አውሮፕላኗ መሬት ላይ አረፈች....
የአውሮፕላኗ በር ተከፍቶ አንድ ረጅም፧ ቀጭን፤ መነጽር ያደረገና በአየር ኃይሉ ውስጥ በጦር ጄት የጠላትን ሃይል ድባቅ
በመምታት በደማቅ ቀለም ታሪክ ያስመዘገበ ምርኮኛ ብቅ አለ፡፡ማርሹ ይሰማል፡፡ እልልታው ቀለጠ!! ግማሹ በሲቃ ያለቅሳል፣ይፈነድቃል፡፡ ምርኮኞቹን ለማየት ሰው በሰው ላይ ይንጠላጠላል፣
ትዕይንቱ ብዙ ነው፡፡ ከዚያም የተዘጋጀውን እቅፍ አበባ ምርኮኛው ተቀበለ፡፡
ምርኮኞቹ ከአውሮፕላኗ እንደወረዱ መሬቷን ይስማሉ። አፈሯን ይልሳሉ፡፡ ያለቅሳሉ፣ ይንከባለላሉ፡፡ የደስታ እንባ... የናፍቆት እንባ... የትዝታ እንባ...
ላለፉት አስራ አንድ ዓመታት ከአገር፤ ከወገን፣ ከቤተሰብ ጋር ተለያይተው ፤ የብቸኝነትንና የመከራ ኑሮን ሲገፉ ከቆዩ በኋላ፤የሚወዱትንና፤ የሚያፈቅሩትን፤ ህዝብና አገር መቀላቀል ዳግም መወለድ
ነውና፤ ምርኮኞች ዳግም የተወለዱ ያህል በደስታ ሰከሩ። እንደዚያ ዳር ድንበርዋን ሊያስከብሩላት፤ ከጠላት ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀው፡ ሳንጃ ለሳንጃ ተሞዣልቀው፡ ጥለው የወደቁላት፡ የውድ ሀገራቸውን ለም አፈር ለማሽተት በመቻላቸው በደስታ የሚሆኑትን አጡ ...ህዝቡም በእልልታና በሆታ የጀግና አቀባበል አደረገላቸው፡፡ ደስ የሚል ከህሊና የማይጠፋ የአቀባበል ሥነ ሥርዓት......
ለተወሰኑ ቀናቶች በድሬዳዋ ከተማ እረፍት አድርገው ከቆዩና መንፈሳቸው ከተረጋጋ በኋላ፣ በየክፍለ ሀገሩ የሚገኙ ዘመዶቻቸውን ሊቀላቀሉ የቸኮሉት ቀድመው ተንቀሳቀሱ፡፡
እለተ ቅዳሜ! አዲስ አበባ!! የኢትዮጵያ ዋና ከተማ! ቀዝቃዛ ንፋስ ይነፍስባታል ። በተለይ የባህር ማዶው ዛፍ ለቅዝቃዜው የራሱን ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል፡፡
ባቡሩ መንገደኞቹን ጣቢያው አራገፈ፡፡ ግፊያው ለጉድ ነው፡፡ግማሹ ሲመጣ ግማሹ ሲሄድ... የገቢና ወጪ መንገደኞች ምልልስ የማያቋርጥበት አምባ......
ጊዜው ለዐይን ያዝ ማድረግ የጀመረበት ሰዓት ነው፡፡
አንድ ቁመቱ ረዘም ያለ፣ ሰውነቱ በበረሃ ግርፋትና በእስር ስቃይ ምክንያት የተለበለበ ግንድ ቢመስልም፤ በሰላሙ ጊዜ ማራኪ መልክና ቁመና እንደነበረው አሁንም በግልጽ የሚታየው ትክለ ሰውነቱ
ዐቢይ ምስክርነቱን የሚሰጥለት፤ ከሲታ ሰው ከባቡሩ ወረደ፡፡
ደረቱ ሰፋ ያለ፣ ፀጉረ ዞማና ዐይኖቹ ጐላ ጐላ ብለው የሚታዩ ረጅም ሰው ነው፡፡ ሻንጣ አንጠልጥሏል፡፡ ከተሰጠው የኪስ ገንዘብ ውስጥ አብዛኛውን ያዋለው ለሁለት ሴቶችና፤ ለአንድ ወንድ የሚሆኑ ልብሶችን በመግዛት ነው፡፡ ከባቡሩ ወርዶ፤ በአምባሳደር ቲያትር በኩል መጥቶ ፤ ወደ ኦርማ ጋራዥ አቀና፡፡ የሚራመደው በደመነፍስ ዐይነት ነው፡፡
በህልም ዓለም የሚራመድ ይመስላል፡፡
እሱ እራሱ የሚያየው ነገር እውነት መሆኑን ተጠራጥሯል።ግራና ቀኙን በዓይኑ ያማትራል፡፡ ሰዎችን ይቃኛል፡፡ ምናልባት የማውቀው ሰው ካገኘሁ በሚል ግምት ነው፡፡ ግን ማንም የሚያውቀው ሰው አላገኘም፡፡ ድሮ የሚያውቁት ሲያዩት እንኳን፤ በቀላሉ ሊለዩት አይችሉም፡፡ ተለውጧል፡፡ ተጉሳቁሏል፡፡
መንገዶቹ የጠበቡ፣ ቤቶቹም ከምዕተ ዓመት በፊት የነበሩ መስለው ታዩት፡፡ በየመንገዱ ላይ ከሚያያቸው ሰዎች ውስጥ ሶስት ሰዎችን ለማግኘት በናፍቆትና በጉጉት ደጋግሞ ይቃኛል፡፡
የሱ ብርቅዬ፤ ድንቅዬዎች፡፡ ልዩ የህይወቱ ቅመሞች፡፡ የተዳፈነ የናፍቆቱ እምቅ ሊፈነዳ ተቃረበ፡፡ ልቡ ተሸበረ... እየተቃረበ ሲመጣ ልቡ ድው ድው የሚል ድምጽ ሰጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው፡፡
እጅግ አስገራሚ ነው! አስደናቂ
የማይጠበቀው ሰው ፤ እንደዚህ ባልተጠበቀ ሰዓት ከች! ሲል፤ እነሱ
ከአንጀቱ የሚያፈቅራቸው፣ የሚወዳቸው፣ የሚሞትላቸው ቤተሰቦቹ እንዴት ሆነው ይሆን? የሚወዳት ሚስቱ፣ የሚወዳቸው ልጆቹ እንዴት ሆነው ይሆን? ሲለያቸው በነበራቸው ዕድሜ ላይ አስራ አንድ ዓመት ሲጨመርበት የትየለሌ ነው፡፡ ምን መስለው ይሆን?
አቤቱ ፈጣሪ ያንተ ተአምር እንዴት ተወርቶ ያልቅ ይሆን? አደራህን ሁሉንም ለአንድ ቀን እንኳን ቢሆን ዐይናቸውን አይቼው
እንድሞት እርዳኝ፡፡ አንተ ታውቃለህ፡፡
ወባ እንደያዘው ሰው እየተቃረበ መጣ፡፡ ቤቱ ጋ ሲደርስ ሰውነቱ ተንዘፈዘፈበት :: ልቡ በፍጥነት ይመታ ጀመር፡፡
ግቢው ...ያ ...ግቢ የሚወደው ግቢ...እዚያ ውስጥ ያሉት እነ.. መራመድ አልቻለም፡፡ ቆመ፡፡ እንደሀውልት ተገትሮ ቀረ፡፡ ከዚያም ለዘመናት በወስጡ ሲንተከተክ የነበረው እንባ በድንገት ገንፍሉ ወጣ፡፡
ከደስታ ብዛት ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ ቤቱን አየው፡፡ ልጆቹን አቅፎ የሳመበትን፣ ከሚያፈቅራት ባለቤቱ ጋር ደስታን ያሳለፈበትን፣ በመጨረሻም ወደ ጦርነት ሲሄድ ከቤተሰቦቹ ጋር ተላቅሶ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#ክፍል_ሶስት
#ትንሣኤ
በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሠረት የምርኮኞች ልውውጥ የሚጀመርበት የመጀመሪያው ምዕራፍ......
የድሬዳዋ ከተማ አሸብርቃለች፡፡ ገንደቆሬ፣ ገንደገራዳ፣ መጋላ፣ ከዚራ፣ ለገሀሬ፣ ..... መንደሮች በሙሉ በደስታ ስቀዋል፡፡
በየመንገዱ ግራና ቀኝ ተተክለው ቀዝቃዛና፤ ነፋሻማ አየርን የሚረጩት ዛፎች በደስታ ተውጠው የሚደንሱ ይመስላሉ፡፡ በዚያች ምድር ላይ የተካሄደው ቀውጢ ጦርነት አልፎ፤ ያንን የመሰለ የሰላም አየር መተንፈስ መቻል ዳግማዊ ልደት ነው፡፡
በሐረርጌ ምድር፡፡ በደገሀቡር፣ ቀብሪደሀር፣ መራራሌ፣ በሺላቦ፣
ደቦይን፣ በቆራሄ አሸዋማ ሜዳ፣ በኦጋዴን በረሃ፣ በካራማራ ተራሮችና በሌሎችም ሺህ ሌሊት ሺህ መአልት የፈሰሰው ደም፣ የተከሰከሰው አጥንት፣ያስገኘው ውጤት፡፡
በዚያን ቀውጢ ሰዓት ላይ ለዳር ድንበር ሲሉ ከጠላት ጋር እየተናነቁ አኩሪ ገድል የፈጸሙት፤ በደማቸው ማህተም፤ በአጥንታቸው ክስካሽ፤ ምድሪቱን ያቀሉት...የመስዋዕትነት ፈርጦች! የሚጠበቁበት ዕለት......
ሰማዩ በዚያን ቀውጢ የጦርነት ወቅት በኢትዮጵያ አየር ሃይል የተሠራውን አስደናቂ ትርኢትና ተአምር አፍ አውጥቶ ሊናገር፣ የታሪክ ምስክርነቱን ሊሰጥ፣ የተዘጋጀ ይመስል አጉረመረመ፡፡ ለሚወዷት እናት አገራቸው ዳር ድንበር ሲሉ የተፋለሙና ልዩ ልዩ ጀብድ ከፈጸሙ በኋላ በጠላት እጅ ወድቀው በባእድ ሀገር በምርኮኝነትና፤ በእስረኝነት ለበርካታ
አመታት ከቆዩ በኋላ በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሰረት ዛሬ ወደሚያፈቅሯትና፤ ወደሚወዷት፤ እናት አገራቸው የሚመለሱበት እለት ስለሆነ፤ እነዚህን ውድ የሀገር አለኝታዎችና፤ ጀግኖች፤በልዩና፤ በደማቅ አቀባበል ፤ ሊቀበል ህዝቡ የአውሮፕላን
ማረፊያውን አካባቢ አጥለቅልቆታል....
ማርሽ የሚያሰማው ሠራዊት በተጠንቀቅ ቆሞ ይጠባበቃል።ባንዲራዎች ይውለበለባሉ፡፡ ህዝቡ ይሯሯጣል፡፡ ይራወጣል። ሰማይ ሰማዩን እያንጋጠጠ ይመለከታል፡፡
አንዳንድ ጊዜ ትላልቅ አሞራዎች ያሳስታሉ፡፡ የሁሉም ልብ ተንጠልጥሏል፡፡ እነማን ይሆኑ?! ሞቱ ተብለው ደረት
የተመታላቸው፣ ተዝካር የተበላላቸው፣ ማን ያውቃል? በህይወት ሊገኙ
ይችሉ ይሆናል፡፡ ይህ ጦርነት በተካሄደባቸው ብዙ አገሮች በተደጋጋሚ
የታየ ክስተት ነው፡፡
ሰዓቱ ደረሰ፡፡ ሰማዩ እንደገና በከፍተኛ ድምፅ አጉረመረመ፡፡አውሮፕላኗ በርቀት ታየች፡፡ ከዚያም እየጐላች ፤እየጐላች፤ መጣችና፤በማረፊያው ላይ እየዞረች፤ ማንዣባብ ጀመረች።
የሰው ጩኸት ሁካታ... ግርግር... ትርምሱ...ሌላ ሆኗል፡፡ማርሽ በረጅሙ ይሰማል፡፡ አውሮፕላኗ አዘቀዘቀች..... ከዚያም አኮበኮበችና አረፈች፡፡
ጀግኖች የታደሙባት አውሮፕላን! ለዳር ድንበሯ ሱሉ ደማቸውን ያፈሰሱላትን፣ በእስር የማቀቁላትን፣ ጥለው የወደቁላትን፣ ታስረው የተገረፉላትን፣ የጦር ምርኮኞችን ይዛ ይሄውና አውሮፕላኗ መሬት ላይ አረፈች....
የአውሮፕላኗ በር ተከፍቶ አንድ ረጅም፧ ቀጭን፤ መነጽር ያደረገና በአየር ኃይሉ ውስጥ በጦር ጄት የጠላትን ሃይል ድባቅ
በመምታት በደማቅ ቀለም ታሪክ ያስመዘገበ ምርኮኛ ብቅ አለ፡፡ማርሹ ይሰማል፡፡ እልልታው ቀለጠ!! ግማሹ በሲቃ ያለቅሳል፣ይፈነድቃል፡፡ ምርኮኞቹን ለማየት ሰው በሰው ላይ ይንጠላጠላል፣
ትዕይንቱ ብዙ ነው፡፡ ከዚያም የተዘጋጀውን እቅፍ አበባ ምርኮኛው ተቀበለ፡፡
ምርኮኞቹ ከአውሮፕላኗ እንደወረዱ መሬቷን ይስማሉ። አፈሯን ይልሳሉ፡፡ ያለቅሳሉ፣ ይንከባለላሉ፡፡ የደስታ እንባ... የናፍቆት እንባ... የትዝታ እንባ...
ላለፉት አስራ አንድ ዓመታት ከአገር፤ ከወገን፣ ከቤተሰብ ጋር ተለያይተው ፤ የብቸኝነትንና የመከራ ኑሮን ሲገፉ ከቆዩ በኋላ፤የሚወዱትንና፤ የሚያፈቅሩትን፤ ህዝብና አገር መቀላቀል ዳግም መወለድ
ነውና፤ ምርኮኞች ዳግም የተወለዱ ያህል በደስታ ሰከሩ። እንደዚያ ዳር ድንበርዋን ሊያስከብሩላት፤ ከጠላት ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀው፡ ሳንጃ ለሳንጃ ተሞዣልቀው፡ ጥለው የወደቁላት፡ የውድ ሀገራቸውን ለም አፈር ለማሽተት በመቻላቸው በደስታ የሚሆኑትን አጡ ...ህዝቡም በእልልታና በሆታ የጀግና አቀባበል አደረገላቸው፡፡ ደስ የሚል ከህሊና የማይጠፋ የአቀባበል ሥነ ሥርዓት......
ለተወሰኑ ቀናቶች በድሬዳዋ ከተማ እረፍት አድርገው ከቆዩና መንፈሳቸው ከተረጋጋ በኋላ፣ በየክፍለ ሀገሩ የሚገኙ ዘመዶቻቸውን ሊቀላቀሉ የቸኮሉት ቀድመው ተንቀሳቀሱ፡፡
እለተ ቅዳሜ! አዲስ አበባ!! የኢትዮጵያ ዋና ከተማ! ቀዝቃዛ ንፋስ ይነፍስባታል ። በተለይ የባህር ማዶው ዛፍ ለቅዝቃዜው የራሱን ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል፡፡
ባቡሩ መንገደኞቹን ጣቢያው አራገፈ፡፡ ግፊያው ለጉድ ነው፡፡ግማሹ ሲመጣ ግማሹ ሲሄድ... የገቢና ወጪ መንገደኞች ምልልስ የማያቋርጥበት አምባ......
ጊዜው ለዐይን ያዝ ማድረግ የጀመረበት ሰዓት ነው፡፡
አንድ ቁመቱ ረዘም ያለ፣ ሰውነቱ በበረሃ ግርፋትና በእስር ስቃይ ምክንያት የተለበለበ ግንድ ቢመስልም፤ በሰላሙ ጊዜ ማራኪ መልክና ቁመና እንደነበረው አሁንም በግልጽ የሚታየው ትክለ ሰውነቱ
ዐቢይ ምስክርነቱን የሚሰጥለት፤ ከሲታ ሰው ከባቡሩ ወረደ፡፡
ደረቱ ሰፋ ያለ፣ ፀጉረ ዞማና ዐይኖቹ ጐላ ጐላ ብለው የሚታዩ ረጅም ሰው ነው፡፡ ሻንጣ አንጠልጥሏል፡፡ ከተሰጠው የኪስ ገንዘብ ውስጥ አብዛኛውን ያዋለው ለሁለት ሴቶችና፤ ለአንድ ወንድ የሚሆኑ ልብሶችን በመግዛት ነው፡፡ ከባቡሩ ወርዶ፤ በአምባሳደር ቲያትር በኩል መጥቶ ፤ ወደ ኦርማ ጋራዥ አቀና፡፡ የሚራመደው በደመነፍስ ዐይነት ነው፡፡
በህልም ዓለም የሚራመድ ይመስላል፡፡
እሱ እራሱ የሚያየው ነገር እውነት መሆኑን ተጠራጥሯል።ግራና ቀኙን በዓይኑ ያማትራል፡፡ ሰዎችን ይቃኛል፡፡ ምናልባት የማውቀው ሰው ካገኘሁ በሚል ግምት ነው፡፡ ግን ማንም የሚያውቀው ሰው አላገኘም፡፡ ድሮ የሚያውቁት ሲያዩት እንኳን፤ በቀላሉ ሊለዩት አይችሉም፡፡ ተለውጧል፡፡ ተጉሳቁሏል፡፡
መንገዶቹ የጠበቡ፣ ቤቶቹም ከምዕተ ዓመት በፊት የነበሩ መስለው ታዩት፡፡ በየመንገዱ ላይ ከሚያያቸው ሰዎች ውስጥ ሶስት ሰዎችን ለማግኘት በናፍቆትና በጉጉት ደጋግሞ ይቃኛል፡፡
የሱ ብርቅዬ፤ ድንቅዬዎች፡፡ ልዩ የህይወቱ ቅመሞች፡፡ የተዳፈነ የናፍቆቱ እምቅ ሊፈነዳ ተቃረበ፡፡ ልቡ ተሸበረ... እየተቃረበ ሲመጣ ልቡ ድው ድው የሚል ድምጽ ሰጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው፡፡
እጅግ አስገራሚ ነው! አስደናቂ
የማይጠበቀው ሰው ፤ እንደዚህ ባልተጠበቀ ሰዓት ከች! ሲል፤ እነሱ
ከአንጀቱ የሚያፈቅራቸው፣ የሚወዳቸው፣ የሚሞትላቸው ቤተሰቦቹ እንዴት ሆነው ይሆን? የሚወዳት ሚስቱ፣ የሚወዳቸው ልጆቹ እንዴት ሆነው ይሆን? ሲለያቸው በነበራቸው ዕድሜ ላይ አስራ አንድ ዓመት ሲጨመርበት የትየለሌ ነው፡፡ ምን መስለው ይሆን?
አቤቱ ፈጣሪ ያንተ ተአምር እንዴት ተወርቶ ያልቅ ይሆን? አደራህን ሁሉንም ለአንድ ቀን እንኳን ቢሆን ዐይናቸውን አይቼው
እንድሞት እርዳኝ፡፡ አንተ ታውቃለህ፡፡
ወባ እንደያዘው ሰው እየተቃረበ መጣ፡፡ ቤቱ ጋ ሲደርስ ሰውነቱ ተንዘፈዘፈበት :: ልቡ በፍጥነት ይመታ ጀመር፡፡
ግቢው ...ያ ...ግቢ የሚወደው ግቢ...እዚያ ውስጥ ያሉት እነ.. መራመድ አልቻለም፡፡ ቆመ፡፡ እንደሀውልት ተገትሮ ቀረ፡፡ ከዚያም ለዘመናት በወስጡ ሲንተከተክ የነበረው እንባ በድንገት ገንፍሉ ወጣ፡፡
ከደስታ ብዛት ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ ቤቱን አየው፡፡ ልጆቹን አቅፎ የሳመበትን፣ ከሚያፈቅራት ባለቤቱ ጋር ደስታን ያሳለፈበትን፣ በመጨረሻም ወደ ጦርነት ሲሄድ ከቤተሰቦቹ ጋር ተላቅሶ
👍2🔥1
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
...የሠራሁትን ጥፋት ለአገሬ መንግሥት እንደሚያሳውቁ እስጠነቀቁኝ፡፡ በዚህ
ላይ እንዳለን የጊኒና የሞሮኮ አታሼዎች ተገደሉ፡፡
“አየህ... እኔ ምስጢሩን ላወጣ አልፈለግሁም:: እርግጥ በአንድ
ወቅት በገዛ አገሬ ላይ ሰልያለሁ፡፡ በመላው አፍሪካ ላይ ይህን በደል
ልፈጽም አልቻልኩም፡፡ የምከዳው አንዲትን አገር ሳይሆን መላውን አፍሪካ
ነበር፡፡ እንዳስፈራሩኝ ከዚህ ቀደም የሰራሁትን ወንጀል ቢያወጡ: ደግሞ
ያለጥርጥር እንደጊኒና ሞሮኮ ወታደራዊ አታሼዎች መሰበሬ ሆነ:: ተሰወርኩ፡፡” ካልቨርት የያዘውን ግማሽ መለኪያ አረቄ ጨልጠው::
“የጊኒና የሞሮኮ አታሼዎች ምስጢር አውጥተው ነው ማለት ነው ለሞት የበቁት?” አለ ናትናኤል ፊቱን አኮማትሮ።
“በእርግጥ አላውቅም.… ግን ሊሆን ይችላል፡፡ አየህ.. ይኸው አካል
የተጠናከረ የመረጃ መረብ አለው:: ከፍተኛ ቁጥጥርም ያደርግብናል፡፡
ምንም እንኳን ቀደም ብሎ ስለ እያንዳንዳችን ጥልቅ ጥናት የተደረገ ቢሆንም አንዳንድ ያልታሰቡ ሁኔታዎች ለመቋቋም ሲባል ይከታተሉናል፡፡ አስፈላጊ ሲሆን ደግሞ በሁለቱ ኣታሼዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ከፍተኛ የአፍሪካ ባላሥልጣናት ላይም የተፈጸመውን ግድያ ከመፈጸም ወደኋላ የሚል ኃይል አይደለም፡፡ብቻ ሁለቱ አታሼዎች ምሲጥር፡ አውጥተዋል ብዬ ስመናገር ያዳግተኛል አውጥተውት ቢሆን እስካሁን ብዙ መፍረክረኮች ይከተሉ ነበር፡፡ቢሆንም አመኔታ እስከታጣብን ድረስና የአንተ መኖር ለአፍሪካ ስጋት
እስከሆነ ድረስ ያለማመንታት ትወገዳለህ፡፡ ብዙዎቹ ተወግደዋል፡፡ ለዚህ ነው ከሁሉ የተሰርኩ፤ ከምደግፋቸውም ከምፀየፋቸውም የተሰወርኩ፡፡እኔም እንደሌላው አፍሪካዊ አፍሪካ አንድ ሆና ማየት እፈልጋለሁ፡፡”
"በመጀመሪያ ለሌላ ባዕድ ድርጅት መስራትህን እንዴት ሳይደርሱበት ቀሩ?”
“ስህተት ነው፡፡ ስህተት ነው የፈፀሙት፡፡ እርግጥ ጠንቃቃ ነበርኩ፤ ቢሆንም መሳሳታቸው በጊዜው እኔንም ያስደነገጠኝ ጉዳይ ነበር።”
“ከጠፋህስ ሰኋላ እንዴት ሊያገኙ አልቻሉም? ማለቴ መንግሥት የሚደግፋቸው እስከሆነ ድረስ አንተን ማደን ያን ያህል አስቸጋሪ አይሆንም...
ሌላውን ብንተወው እንኳን አድራሻህን እንድትነግራቸው የምሥራችን
ሊያስገድዷት ይችሉ ነበር፡፡ እኔ'ኮ ግራ የሆነብኝ ይህን ያህል በመላው አፍሪካ
እየተርመሰመስ ያለ ኃይል አድኖ ሊያገኘው ያልቻለውን ሰው እንዴት እኔ
ላገኝህ ቻልኩ?”
“ሊያገኙኝ ያልቻሉት ስላልሞከሩ ብቻ ነው፡፡ለመሰወር እንደቆረጥኩ
ከዚህ በፊት ያጠፋሁትን ጥፋት በገዛ አገሬ ላይ የሰራሁትን ወንጀል በሙሉ
ዘርዝሬ በጽሁፍ አስተላዕፍኩላቸው፡፡ይህንንም ያለፈ ጥፋቴን እንደማስፈ
ራሪያ በመጠቀም የባዕድ የስለላ ድርጅቶች ምስጢሩን ከእኔ ለማግኘት
በመጣር ላይ መሆናቸውንና ምስጢሩን አውጥቼ ከዳተኛ ከመሆን አለበለዚያም ነጮቹ ያለፈ ስራዬን ይፋ አውጥተው ለጥፋት ሳይዱርጉኝ በፊት ለመጥፋት መወሰኔን ገለጽኩላቸው፡፡ ሆኖም እኔን አድነው ለማግኘት ቢጥሩ ወይም የምሥራችን ለማስገደድ ቢሞክሩ ደብቄ የያዝኩት ምሥጢር የጋዜጦች ቆሎ እንደሚሆኝ እስፈራራኋቸው፡፡” ካልቨርት በቀኙ የጨበጠ ውን ባዶ መለኪያ አተኩሮ ተመለከተው፡፡ “ለዚህ ነው ሳይተናኮሉኝ ባለሁበት ሊተውኝ የመረጡት። ድምጼን አጥፍቼ ጭንቅላቴን ቀብሬ ሰዓቷ እስክትደርስ ከታገለኩ ከዚያ ወዲያ ሊበቀሉኝ እንደማይሞክሩ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ምክንያት አይኖራቸውማ፡፡ ለምስጢራቸው ደህንነት ስል ነዋ የተሰወርኩት፡፡”
“ታዲያ የምሥራችን ለምን ገደሏት?”
“እመነኝ እነሱ አይደሉም የገደሏት… ነጮቹ ናቸው፡፡”
“እነማን ናቸው ነጮቹ?”
“እንግሊዞቹ አስራኤላውያኑ… አላውቅም”
“እንዴት ለምን?”
“አየህ እንዳልኩህ ከመጥፋቱ በፊት በምሥራች ላይ አደጋ ሲደርስ
ምሥጢሩን እንደማመጣ ዝቼ ስለነበር ጥበቃ ይደረግላት ነበር በስውር፡፡”
“በማን?”
“በቆንጆዎቹ።”
“ማን እንዳይጎዳት?”
“በብስጭት ምሥጢሩን ይፋ እንዳደርገው ሲሉ ነኞቹ የምሥራችን
ሊያፍኗት ወይ ሊገሏት ይችላሉ ብለው በመፍራት ይመስለኛል። አንተም
ከሆቴሏ ድረስ ሄደህ አንድ ክፍል ውስጥ አስገብተሃት ስትዘጋ የነጮቹ
ቅጥረኛ መስለሃቸው አንድ ነገር እንዳታደርጋት በመፍራት ይሆናል
ቆንጆዎቹ ሊያቆሙህ የሞከሩት፡፡”
“ግን እንዴት ነው ነገሩ?” ናትናኤል ግራ ተጋባ፡፡ “ያ የባዕድ የሆነ የስለላ ድርጅት ኢትዮያውያንን መልምሎ አሰማርቷል ማለት ነው? የገደለቻት ሴት'ኮ ያለ ጥርጥር ኢትዮጵያዊት ነች::” አለ ናትናኤል ሲቲና ፊቱ ላይ ግጥም ስትልበት::
“አይደለም አይደለም::” አለ ካልቨርት የናትናኤል ውሱን እውቀት ነገሩን ሁሉእንዳዘበራረቀበት ሲረዳ፡፡ “ለነጮቹ የስለላ ድርጅት በአዲስ አበባ
ውስጥ የመስክ ስራ እየሠራላት ያለ ሞሳድ ነው፡፡ እሥራኤል ቀደም ሲል
ከዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ የኢትዮጵያ አይሁዳውያንን
መልሳ ወደ አዲስ አበባ በብዛት አስገብታ የመረጃ ስራ እያሰራቻቸው ነው::”
“ለምን?” ናትናኤል አቋረጠው፡፡ “እሥራኤል ለምን ብላ ለነጮቹ
ትሠራለች? ከኢትጵያ ጋር ያላት ግንኙነት መጥፎ አይደለም!እንደውም ግንኙነታችን ከመቼውም ጊዜ የተሻለ ነው::”
“የስለላ መረብ የምትዘረጋው በጠላትህ ላይ ብቻ አይደለም። ስለላ በአጭሩ መረጃዎችን መሰብሰቢያ መንገድ እንጂ የግድ አንዱ አንዱ ካለው
ጥላቻ የሚመነጭ አይደለም፡፡
አስታውስ እሥራኤል በ1980ዎቹ መጨረሻ በዋንኛ ደጋፊዋ በዩናይትድ ስቴትስ ላይ ሳይቅር ስለላ ስታካሂድ ተደርሶባታል፡፡ አይደለም፡፡ እሥራኤል ከኢትዮጵያ ጋር ካላት ግንኙነት ጋር የተያያዘ አይደለም::”
“ታዲያ ለምን?” ናትናኤል አፈጠጠ፡፡
“በመጀመሪያ ነገሩ የተለመደ ነው::የተለያዩ የመረጃ ቤቶች አንዱ
ለአንዱ ውለታ መፈጻጸሙና መረጃ መለዋለጠ የተለመደ ነው፡፡ ግን
እሥራኤል እዚህ ውስጥ አጇን የከተተችው ለራሷ ስትል ነው፡፡ አየህ
አፍሪካ ተባብራ ለመንቀሳቀስ ከቻለች ምናልባት በግብጽና በጥቂት የሰሜን
አፍሪካ አገሮች ገፋፊነት አጥፊ እርምጃ በእርሷ ላይ እንዳይፈጸም የሰጋች
ይመስለኛል ለዚህ ነው ሁኔታውን ከወዲሁ ለመከታተል የመረጠችው::”
“እና…. የምሥራችን የገደሏት…”
“ቆንጆዎቹ አይደሉም፡፡ የነጭ ጠላቶቻችን ናቸው::” አለ ካልቨርት አቋርጦ::
“ታዲያ እሁን ምን ልታደርግ ነው? ምሥጢሩን ልታወጣ ነው
ወይስ…?”
ካልቨርት ጭንቅላቱን ነቀነቀ፡፡
“ስታየኝ ጅል እመስላለሁ? በፍጹም! ሊያታልሉኝ ሲሞክሩ...
እንዳችንን በአንዳችን ላይ ሊያነሳሱ ሲሞክሩ እያየሁ እንዴት እጃጃላለሁ?”
“ጥሩ፡፡ አሁን ምንድነው ማድረግ ያለብን?” ናትናኤል ዙሪያው
ድቅድቅ ጨለማ ሆነበት፡፡
“መጠበቅ፡፡”
“ምኑን?”
“ቀኑን፡፡”
“የቱን ቀን?”
“የስብሰባውን ቀን፤ አፍሪካ አንድ የምትሆንበትን.…”
“አንችልም!” ናትናኤል ከተቀመጠበት ተፈናጥሮ ተነሳ።
“ለምንድነው የማንችለው.…የቀሩን ሦስት ቀናት ብቻ ናቸው፡፡ ከዚያ በኋላ ነፃ ነን፡፡”
“ይይዙናል!” አለ ናትናኤል በጭንቀት ተወጥሮ፡፡
“አያገኙንም፡፡”
“ያገኙናል፡፡ ባቡር ጣቢያው ድረስ ተከታትለውኛል ! አይቼዋለሁ፡፡
ሽጉጡኝ ከትከሻው በላይ ይዞ ሊቀጥፈኝ ሲንደረደር እነዛን አይኖቹን አይቻቸዋለሁ! ትሰማኛለህ? ! ድጋሚ ካገኘኝ ስሜን እንኳን አይጠራም፡፡ በጆሮ ግንዴ ነው የሚለቅብኝ! ትሰማኛለህ? ! መሞት አልፈልግም፡፡ በጤና ከቤቴ መመለስ ነው የምፈልገው!” ናትናኤል ሰውነቱ ሳይታወቀው ከቁጥጥሩ ውጭ ሲሆንበት ጭንቅላቱን በሁለት እጆቹ ግጥም አድርጎ ይዞ መሃል ወለሉ ላይ ቆመ፡፡
“ቁጭ በል…” አለ ካልቨርት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
...የሠራሁትን ጥፋት ለአገሬ መንግሥት እንደሚያሳውቁ እስጠነቀቁኝ፡፡ በዚህ
ላይ እንዳለን የጊኒና የሞሮኮ አታሼዎች ተገደሉ፡፡
“አየህ... እኔ ምስጢሩን ላወጣ አልፈለግሁም:: እርግጥ በአንድ
ወቅት በገዛ አገሬ ላይ ሰልያለሁ፡፡ በመላው አፍሪካ ላይ ይህን በደል
ልፈጽም አልቻልኩም፡፡ የምከዳው አንዲትን አገር ሳይሆን መላውን አፍሪካ
ነበር፡፡ እንዳስፈራሩኝ ከዚህ ቀደም የሰራሁትን ወንጀል ቢያወጡ: ደግሞ
ያለጥርጥር እንደጊኒና ሞሮኮ ወታደራዊ አታሼዎች መሰበሬ ሆነ:: ተሰወርኩ፡፡” ካልቨርት የያዘውን ግማሽ መለኪያ አረቄ ጨልጠው::
“የጊኒና የሞሮኮ አታሼዎች ምስጢር አውጥተው ነው ማለት ነው ለሞት የበቁት?” አለ ናትናኤል ፊቱን አኮማትሮ።
“በእርግጥ አላውቅም.… ግን ሊሆን ይችላል፡፡ አየህ.. ይኸው አካል
የተጠናከረ የመረጃ መረብ አለው:: ከፍተኛ ቁጥጥርም ያደርግብናል፡፡
ምንም እንኳን ቀደም ብሎ ስለ እያንዳንዳችን ጥልቅ ጥናት የተደረገ ቢሆንም አንዳንድ ያልታሰቡ ሁኔታዎች ለመቋቋም ሲባል ይከታተሉናል፡፡ አስፈላጊ ሲሆን ደግሞ በሁለቱ ኣታሼዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ከፍተኛ የአፍሪካ ባላሥልጣናት ላይም የተፈጸመውን ግድያ ከመፈጸም ወደኋላ የሚል ኃይል አይደለም፡፡ብቻ ሁለቱ አታሼዎች ምሲጥር፡ አውጥተዋል ብዬ ስመናገር ያዳግተኛል አውጥተውት ቢሆን እስካሁን ብዙ መፍረክረኮች ይከተሉ ነበር፡፡ቢሆንም አመኔታ እስከታጣብን ድረስና የአንተ መኖር ለአፍሪካ ስጋት
እስከሆነ ድረስ ያለማመንታት ትወገዳለህ፡፡ ብዙዎቹ ተወግደዋል፡፡ ለዚህ ነው ከሁሉ የተሰርኩ፤ ከምደግፋቸውም ከምፀየፋቸውም የተሰወርኩ፡፡እኔም እንደሌላው አፍሪካዊ አፍሪካ አንድ ሆና ማየት እፈልጋለሁ፡፡”
"በመጀመሪያ ለሌላ ባዕድ ድርጅት መስራትህን እንዴት ሳይደርሱበት ቀሩ?”
“ስህተት ነው፡፡ ስህተት ነው የፈፀሙት፡፡ እርግጥ ጠንቃቃ ነበርኩ፤ ቢሆንም መሳሳታቸው በጊዜው እኔንም ያስደነገጠኝ ጉዳይ ነበር።”
“ከጠፋህስ ሰኋላ እንዴት ሊያገኙ አልቻሉም? ማለቴ መንግሥት የሚደግፋቸው እስከሆነ ድረስ አንተን ማደን ያን ያህል አስቸጋሪ አይሆንም...
ሌላውን ብንተወው እንኳን አድራሻህን እንድትነግራቸው የምሥራችን
ሊያስገድዷት ይችሉ ነበር፡፡ እኔ'ኮ ግራ የሆነብኝ ይህን ያህል በመላው አፍሪካ
እየተርመሰመስ ያለ ኃይል አድኖ ሊያገኘው ያልቻለውን ሰው እንዴት እኔ
ላገኝህ ቻልኩ?”
“ሊያገኙኝ ያልቻሉት ስላልሞከሩ ብቻ ነው፡፡ለመሰወር እንደቆረጥኩ
ከዚህ በፊት ያጠፋሁትን ጥፋት በገዛ አገሬ ላይ የሰራሁትን ወንጀል በሙሉ
ዘርዝሬ በጽሁፍ አስተላዕፍኩላቸው፡፡ይህንንም ያለፈ ጥፋቴን እንደማስፈ
ራሪያ በመጠቀም የባዕድ የስለላ ድርጅቶች ምስጢሩን ከእኔ ለማግኘት
በመጣር ላይ መሆናቸውንና ምስጢሩን አውጥቼ ከዳተኛ ከመሆን አለበለዚያም ነጮቹ ያለፈ ስራዬን ይፋ አውጥተው ለጥፋት ሳይዱርጉኝ በፊት ለመጥፋት መወሰኔን ገለጽኩላቸው፡፡ ሆኖም እኔን አድነው ለማግኘት ቢጥሩ ወይም የምሥራችን ለማስገደድ ቢሞክሩ ደብቄ የያዝኩት ምሥጢር የጋዜጦች ቆሎ እንደሚሆኝ እስፈራራኋቸው፡፡” ካልቨርት በቀኙ የጨበጠ ውን ባዶ መለኪያ አተኩሮ ተመለከተው፡፡ “ለዚህ ነው ሳይተናኮሉኝ ባለሁበት ሊተውኝ የመረጡት። ድምጼን አጥፍቼ ጭንቅላቴን ቀብሬ ሰዓቷ እስክትደርስ ከታገለኩ ከዚያ ወዲያ ሊበቀሉኝ እንደማይሞክሩ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ምክንያት አይኖራቸውማ፡፡ ለምስጢራቸው ደህንነት ስል ነዋ የተሰወርኩት፡፡”
“ታዲያ የምሥራችን ለምን ገደሏት?”
“እመነኝ እነሱ አይደሉም የገደሏት… ነጮቹ ናቸው፡፡”
“እነማን ናቸው ነጮቹ?”
“እንግሊዞቹ አስራኤላውያኑ… አላውቅም”
“እንዴት ለምን?”
“አየህ እንዳልኩህ ከመጥፋቱ በፊት በምሥራች ላይ አደጋ ሲደርስ
ምሥጢሩን እንደማመጣ ዝቼ ስለነበር ጥበቃ ይደረግላት ነበር በስውር፡፡”
“በማን?”
“በቆንጆዎቹ።”
“ማን እንዳይጎዳት?”
“በብስጭት ምሥጢሩን ይፋ እንዳደርገው ሲሉ ነኞቹ የምሥራችን
ሊያፍኗት ወይ ሊገሏት ይችላሉ ብለው በመፍራት ይመስለኛል። አንተም
ከሆቴሏ ድረስ ሄደህ አንድ ክፍል ውስጥ አስገብተሃት ስትዘጋ የነጮቹ
ቅጥረኛ መስለሃቸው አንድ ነገር እንዳታደርጋት በመፍራት ይሆናል
ቆንጆዎቹ ሊያቆሙህ የሞከሩት፡፡”
“ግን እንዴት ነው ነገሩ?” ናትናኤል ግራ ተጋባ፡፡ “ያ የባዕድ የሆነ የስለላ ድርጅት ኢትዮያውያንን መልምሎ አሰማርቷል ማለት ነው? የገደለቻት ሴት'ኮ ያለ ጥርጥር ኢትዮጵያዊት ነች::” አለ ናትናኤል ሲቲና ፊቱ ላይ ግጥም ስትልበት::
“አይደለም አይደለም::” አለ ካልቨርት የናትናኤል ውሱን እውቀት ነገሩን ሁሉእንዳዘበራረቀበት ሲረዳ፡፡ “ለነጮቹ የስለላ ድርጅት በአዲስ አበባ
ውስጥ የመስክ ስራ እየሠራላት ያለ ሞሳድ ነው፡፡ እሥራኤል ቀደም ሲል
ከዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ የኢትዮጵያ አይሁዳውያንን
መልሳ ወደ አዲስ አበባ በብዛት አስገብታ የመረጃ ስራ እያሰራቻቸው ነው::”
“ለምን?” ናትናኤል አቋረጠው፡፡ “እሥራኤል ለምን ብላ ለነጮቹ
ትሠራለች? ከኢትጵያ ጋር ያላት ግንኙነት መጥፎ አይደለም!እንደውም ግንኙነታችን ከመቼውም ጊዜ የተሻለ ነው::”
“የስለላ መረብ የምትዘረጋው በጠላትህ ላይ ብቻ አይደለም። ስለላ በአጭሩ መረጃዎችን መሰብሰቢያ መንገድ እንጂ የግድ አንዱ አንዱ ካለው
ጥላቻ የሚመነጭ አይደለም፡፡
አስታውስ እሥራኤል በ1980ዎቹ መጨረሻ በዋንኛ ደጋፊዋ በዩናይትድ ስቴትስ ላይ ሳይቅር ስለላ ስታካሂድ ተደርሶባታል፡፡ አይደለም፡፡ እሥራኤል ከኢትዮጵያ ጋር ካላት ግንኙነት ጋር የተያያዘ አይደለም::”
“ታዲያ ለምን?” ናትናኤል አፈጠጠ፡፡
“በመጀመሪያ ነገሩ የተለመደ ነው::የተለያዩ የመረጃ ቤቶች አንዱ
ለአንዱ ውለታ መፈጻጸሙና መረጃ መለዋለጠ የተለመደ ነው፡፡ ግን
እሥራኤል እዚህ ውስጥ አጇን የከተተችው ለራሷ ስትል ነው፡፡ አየህ
አፍሪካ ተባብራ ለመንቀሳቀስ ከቻለች ምናልባት በግብጽና በጥቂት የሰሜን
አፍሪካ አገሮች ገፋፊነት አጥፊ እርምጃ በእርሷ ላይ እንዳይፈጸም የሰጋች
ይመስለኛል ለዚህ ነው ሁኔታውን ከወዲሁ ለመከታተል የመረጠችው::”
“እና…. የምሥራችን የገደሏት…”
“ቆንጆዎቹ አይደሉም፡፡ የነጭ ጠላቶቻችን ናቸው::” አለ ካልቨርት አቋርጦ::
“ታዲያ እሁን ምን ልታደርግ ነው? ምሥጢሩን ልታወጣ ነው
ወይስ…?”
ካልቨርት ጭንቅላቱን ነቀነቀ፡፡
“ስታየኝ ጅል እመስላለሁ? በፍጹም! ሊያታልሉኝ ሲሞክሩ...
እንዳችንን በአንዳችን ላይ ሊያነሳሱ ሲሞክሩ እያየሁ እንዴት እጃጃላለሁ?”
“ጥሩ፡፡ አሁን ምንድነው ማድረግ ያለብን?” ናትናኤል ዙሪያው
ድቅድቅ ጨለማ ሆነበት፡፡
“መጠበቅ፡፡”
“ምኑን?”
“ቀኑን፡፡”
“የቱን ቀን?”
“የስብሰባውን ቀን፤ አፍሪካ አንድ የምትሆንበትን.…”
“አንችልም!” ናትናኤል ከተቀመጠበት ተፈናጥሮ ተነሳ።
“ለምንድነው የማንችለው.…የቀሩን ሦስት ቀናት ብቻ ናቸው፡፡ ከዚያ በኋላ ነፃ ነን፡፡”
“ይይዙናል!” አለ ናትናኤል በጭንቀት ተወጥሮ፡፡
“አያገኙንም፡፡”
“ያገኙናል፡፡ ባቡር ጣቢያው ድረስ ተከታትለውኛል ! አይቼዋለሁ፡፡
ሽጉጡኝ ከትከሻው በላይ ይዞ ሊቀጥፈኝ ሲንደረደር እነዛን አይኖቹን አይቻቸዋለሁ! ትሰማኛለህ? ! ድጋሚ ካገኘኝ ስሜን እንኳን አይጠራም፡፡ በጆሮ ግንዴ ነው የሚለቅብኝ! ትሰማኛለህ? ! መሞት አልፈልግም፡፡ በጤና ከቤቴ መመለስ ነው የምፈልገው!” ናትናኤል ሰውነቱ ሳይታወቀው ከቁጥጥሩ ውጭ ሲሆንበት ጭንቅላቱን በሁለት እጆቹ ግጥም አድርጎ ይዞ መሃል ወለሉ ላይ ቆመ፡፡
“ቁጭ በል…” አለ ካልቨርት
👍1