#በኔ_የደረሰ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በጥላሁን
የኔም የጓደኛዬም ፍቅረኞች ሁለቱም ሀብታም የሚለው ምን አይነት ሀብታም? የሚለን ጥያቄ የማያብራራ ጥቅል መጠሪያ ከማይገልፃቸው ከበቃቸው ሀብታም ቤተሰቦች የተወለዱ ናቸው።
የኔና የጋደኛዬ ቤተሰቦች ለመኖር የማይቸገሩ መካከለኛ የኑሮ ደረጃ በመባል የሚጠራውን አይነት ኑሮ የሚኖሩ ናቸው ። የኔ ፍቅር ሊሊ ስትባል የጋደኛዬ ፍቅረኛ ኪሪያ ትባላለች ትርጉሙስ ካላችሁ እኔን ሳይሆን እራሷን ጠይቋት ።
ገና በአዳማ ዩኒቨርስቲ የአንደኛ አመት የአካውንቲንግ ተማሪ ነኝ ፍቅር የጀመርኩት አስረኛ ክፍል ሆኜ ነው ታድያ ለፍቅር ምን አጣደፈህ አትበሉኝ የደረሰበት እንኳን እንደማይለኝ አውቃለሁ ያልደረሰባችሁ ካላችሁ
" አርፎ ትምህርቱን አይማርም ለፍቅሩ ይደርስበታል!" ምናምን እያለችሁ ብትሞልጩኝም እችለዋለሁ።
መጀመሪያ በጥፊ ተመቶ ቀጥሎ በኮብል የተፈነከተ ሰው የመጀመሪያውን ጥፊ ወድያው ረሳው ቢሉት ባይረሳው ገረመውን ይገርመው ነበር አለ ገረመው
የራሴ አባባል ነች ስለዚህ አሁን በተቆለለብኝ ዱብዳ የተነሳ ጭንቅላቴ ስድብም ብጨቃም ዝልዘላም አይሰማውም አቅማችሁ የቻለውን ያህል ተሳደቡ አጋጣሚውን ተጠቀሙበት።
እናላችሁ ••• ከዚቹ ከኔ ፍቅር ከሊሊ ጋር ፍቅር የጀመርነው ከሁለት አመት በፊት አስረኛ ክፍል እያለሁ ነው ። አንድ ክፍል ነበርን ቀድሜ የወደድኳት እኔ ነበርኩ እንደወደድኳት ግን ነግሪያት አላውቅም እንኳን ለሷ ልነግራት እኔ እራሴ የያዘኝ ፍቅር መሆኑን መች ቶሎ ገባኝና ብቻ እኔ የማውቀው
ስተኛ ትዝ እንደምትለኝ ።
ስበላ እንደማስታውሳት።
ሴት ልጅ ከሩቁ ባየሁ ቁጥር እሷ እንደምትመስለኝ።
ሳትጠራኝ የጠራችኝ እየመሰለኝ ብንን እንደምል።
ጥዋት ገብቼ ለመማር ሳይሆን እሷን ለማየት ከክፍሉ ተማሪ በሙሉ ቀድሜ እንደምገኝ።
ሌሎች ወንዶች ሲያናግራት የሆነ የሚያቃጥል ነገር እንደሚሰማኝ በለው በለው ንከሰው ቦጭቀው እንደሚለኝ።
አጠገቤ ስትቀመጥ ላብ እንደሚያሰምጠኝ ።
ስታወራኝ ምላሴ ወደውስጥ ገብቶ እማወራው ነገር እንደሚጠፋብኝ ።
ቅዳሜና እሁድ የሚባል ነገር እንደሚያስጠላኝ ።
ሰኞ እንደምፅአት ቀን እንደምትርቅብኝ ብቻ ነበር።
ለእንደኔ አይነቱ ጭምት እንኳን ፍቅር ሊጀምር የፍቅር ፊልም እንዲያይ አባቱ የማይፈቅድለት
ከደብተሩና ከቤተሰቦቹ ውጪ ከሌላው አለም ጋር ሳይተዋወቅ ያደገ ልጅ ከላይ የታዩበት ምልክቶች የፍቅር ምልክት መሆናቸውን መለየት ከባድ ነበር አይ ፍቅር ዶክተር አልባ ህመም ።
እናማ በአንድ አጋጣሚ የቤተሰብ ፕሮግራም ላይ ለአንድ የአክስቴ ልጅ የፍቅር ህመም ምልክቶቼን አውራሁለት
በቃ ሳያት ደስ ይለኛል ተለይቻት ፊቷ ከፊቴ ላይ አይጠፋም ለምን እንደሆነ እኔ እንጃ ከሌላ ወንድ ጋር ስታወራ እናደዳለሁ ስለው
ረጅም ሳቅ ሳቀብኝ በትግስት ጠበኩት የትግስቴን ፍሬ ነገረኝ ። "ፍቅር ይዞሀል ሶልዬ " አለኝ። ብትችል ትምህርትህን እስክትጨርስ እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ባትገባ ይሻል ነበር
አሁን ግን ከነገርከኝ አንፃር ላትመለስ ተዘፍቀህበታል እና ንገራት" የሚለውን አስከትሎ ተለየኝ ። ንገራት! ንገራት! ንገራት! የሚለው ቃሉ ጭንቃላቴ ላይ ሲያቃጭልብኝ አምሽቶ አነጋ ። እነግራታለሁ ወሰንኩ ሰኞ ለሊት አስራ አንድ ሰአት ተነስቼ ገላዬን ታጠብኩ ። ጥዋት ሶስት ፔሬድ ሙሉ የተማርኩትም የፃፍኩትም ትዝ አይለኝም ።
ምን እንደምላት ስፅፍ ስለማመድ ቆየሁ•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በጥላሁን
የኔም የጓደኛዬም ፍቅረኞች ሁለቱም ሀብታም የሚለው ምን አይነት ሀብታም? የሚለን ጥያቄ የማያብራራ ጥቅል መጠሪያ ከማይገልፃቸው ከበቃቸው ሀብታም ቤተሰቦች የተወለዱ ናቸው።
የኔና የጋደኛዬ ቤተሰቦች ለመኖር የማይቸገሩ መካከለኛ የኑሮ ደረጃ በመባል የሚጠራውን አይነት ኑሮ የሚኖሩ ናቸው ። የኔ ፍቅር ሊሊ ስትባል የጋደኛዬ ፍቅረኛ ኪሪያ ትባላለች ትርጉሙስ ካላችሁ እኔን ሳይሆን እራሷን ጠይቋት ።
ገና በአዳማ ዩኒቨርስቲ የአንደኛ አመት የአካውንቲንግ ተማሪ ነኝ ፍቅር የጀመርኩት አስረኛ ክፍል ሆኜ ነው ታድያ ለፍቅር ምን አጣደፈህ አትበሉኝ የደረሰበት እንኳን እንደማይለኝ አውቃለሁ ያልደረሰባችሁ ካላችሁ
" አርፎ ትምህርቱን አይማርም ለፍቅሩ ይደርስበታል!" ምናምን እያለችሁ ብትሞልጩኝም እችለዋለሁ።
መጀመሪያ በጥፊ ተመቶ ቀጥሎ በኮብል የተፈነከተ ሰው የመጀመሪያውን ጥፊ ወድያው ረሳው ቢሉት ባይረሳው ገረመውን ይገርመው ነበር አለ ገረመው
የራሴ አባባል ነች ስለዚህ አሁን በተቆለለብኝ ዱብዳ የተነሳ ጭንቅላቴ ስድብም ብጨቃም ዝልዘላም አይሰማውም አቅማችሁ የቻለውን ያህል ተሳደቡ አጋጣሚውን ተጠቀሙበት።
እናላችሁ ••• ከዚቹ ከኔ ፍቅር ከሊሊ ጋር ፍቅር የጀመርነው ከሁለት አመት በፊት አስረኛ ክፍል እያለሁ ነው ። አንድ ክፍል ነበርን ቀድሜ የወደድኳት እኔ ነበርኩ እንደወደድኳት ግን ነግሪያት አላውቅም እንኳን ለሷ ልነግራት እኔ እራሴ የያዘኝ ፍቅር መሆኑን መች ቶሎ ገባኝና ብቻ እኔ የማውቀው
ስተኛ ትዝ እንደምትለኝ ።
ስበላ እንደማስታውሳት።
ሴት ልጅ ከሩቁ ባየሁ ቁጥር እሷ እንደምትመስለኝ።
ሳትጠራኝ የጠራችኝ እየመሰለኝ ብንን እንደምል።
ጥዋት ገብቼ ለመማር ሳይሆን እሷን ለማየት ከክፍሉ ተማሪ በሙሉ ቀድሜ እንደምገኝ።
ሌሎች ወንዶች ሲያናግራት የሆነ የሚያቃጥል ነገር እንደሚሰማኝ በለው በለው ንከሰው ቦጭቀው እንደሚለኝ።
አጠገቤ ስትቀመጥ ላብ እንደሚያሰምጠኝ ።
ስታወራኝ ምላሴ ወደውስጥ ገብቶ እማወራው ነገር እንደሚጠፋብኝ ።
ቅዳሜና እሁድ የሚባል ነገር እንደሚያስጠላኝ ።
ሰኞ እንደምፅአት ቀን እንደምትርቅብኝ ብቻ ነበር።
ለእንደኔ አይነቱ ጭምት እንኳን ፍቅር ሊጀምር የፍቅር ፊልም እንዲያይ አባቱ የማይፈቅድለት
ከደብተሩና ከቤተሰቦቹ ውጪ ከሌላው አለም ጋር ሳይተዋወቅ ያደገ ልጅ ከላይ የታዩበት ምልክቶች የፍቅር ምልክት መሆናቸውን መለየት ከባድ ነበር አይ ፍቅር ዶክተር አልባ ህመም ።
እናማ በአንድ አጋጣሚ የቤተሰብ ፕሮግራም ላይ ለአንድ የአክስቴ ልጅ የፍቅር ህመም ምልክቶቼን አውራሁለት
በቃ ሳያት ደስ ይለኛል ተለይቻት ፊቷ ከፊቴ ላይ አይጠፋም ለምን እንደሆነ እኔ እንጃ ከሌላ ወንድ ጋር ስታወራ እናደዳለሁ ስለው
ረጅም ሳቅ ሳቀብኝ በትግስት ጠበኩት የትግስቴን ፍሬ ነገረኝ ። "ፍቅር ይዞሀል ሶልዬ " አለኝ። ብትችል ትምህርትህን እስክትጨርስ እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ባትገባ ይሻል ነበር
አሁን ግን ከነገርከኝ አንፃር ላትመለስ ተዘፍቀህበታል እና ንገራት" የሚለውን አስከትሎ ተለየኝ ። ንገራት! ንገራት! ንገራት! የሚለው ቃሉ ጭንቃላቴ ላይ ሲያቃጭልብኝ አምሽቶ አነጋ ። እነግራታለሁ ወሰንኩ ሰኞ ለሊት አስራ አንድ ሰአት ተነስቼ ገላዬን ታጠብኩ ። ጥዋት ሶስት ፔሬድ ሙሉ የተማርኩትም የፃፍኩትም ትዝ አይለኝም ።
ምን እንደምላት ስፅፍ ስለማመድ ቆየሁ•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
❤1
#በኔ_የደረሰ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በጥላሁን
ንገራት ንገራት ንገራት የሚለው ቃሉ ጭንቃላቴ ላይ ሲያቃጭልብኝ አምሽቶ. አነጋ ። እነግራታለሁ ወሰንኩ ሰኛ ለሊት አስራ አንድ ሰአት ተነስቼ ገላዬን ታጠብኩ
ጥዋት ሶስት ፔሬድ ሙሉ የተማርኩትም የፃፍኩትም ትዝ አይለኝም ።
ምን እንደምላት ስፅፍ ስለማመድ ቆየሁ•••
ምን ብዬ እንደምጀምር ምን ብዬ እንደምቀጥል እና ምን ብዬ እንደምደመድም የትኛው ሀሳብ መቅደም የትኛው መከተል እንዳለበት መግቢያ ማጠናከሪያ መደምደሚያ ብዬ ከፋፍዬ ላስቀምጥ ብሞክርም ውስጤ ያለውን የፍቅር ንዳድ በደንብ ሊገልፁላት የሚችሉ ቃላቶች ማግኘት ፈተና ሆነብኝ።
መግቢያ:- ሊሊዬ ለብቻሽ ላናግርሽ የፈለኩት አንድ ጉዳይ ነበረኝ ለዛ ነው ለብቻሽን ላናግርሽ የፈለኩት....
ወይ ጣጣ እሄ ደሞ የፍቅር ጥያቄ ሳይሆን ብድር የሚጠይቅ ሰው የሚጠቀምበት የመግቢያ ንግግር ይመስላ አቦ አልኩና እላዩ ላይ ትልቅ የኤክስ ምልክት አጋድሜ ግድግዳውን ተደግፌ ከክፍሉ ሴት ተማሪዎች በሙሉ እንኳን የትምህርትቤቱን ይንፎርም የተቀዳደደ ጆንያ ለብሳ ብትመጣ ውበቷ የማይጎድልብኝን የለበሰችው የሳቀችው የተናገረችው ሁሉ ልዩ እና ውብ መስሎ የሚታየኝን እኔ ከተቀመጥኩበት በስተግራ እክፍሉ መሀል ላይ ከሁለት ሴት ጓደኛቿ መሀል ላይ ያለችውን ሊሊዬን ከጀርባ እያየሁ የምላትን ማሰብ ጀመርኩ።
የመጣልኝን ሁለተኛውን ሀሳብ መፃፍ ጀመርኩ•••
ፅሁፉ እየመራኝ ይሁን እኔ እየመራሁት ባይገባኝም ፊደሎቹ እየተፈላለጉ መመሳሰል ጀመሩ ። ሳላስበው እንደመግጠምም አደረገኝ•••
ምን መሰለሽ ? እሄውልሽ ሊሊዬ
እኔ ባንቺ ፍቅር ሁሉን ነገር ጥዬ
ሳይሽ ደስ ይለኛል
ካጠገብሽ ስርቅ ጭንቀት ይወረኛል
ሲለው ፍርሀት ፍርሀት ብርድ ብርድ ይለኛል
በቤተሰብ መሀል እቤቴ ቁጭ ብዬ
ብቻዬን የሆንኩኝ ያህል ይሰማኛል
ሳቅሽ ይርበኛል
አንቺ ሳትኖሪ ድምፅሽ ይጠራኛል
በውድቅት ለሊት ሰው ሁሉ ተኝቶ
እኔ አስብሻለሁ
አንቺ ሳትመጪ ኮቴሽ ይሰማኛል
የቱንስ ልንገርሽ የቱኛውን ትቼ
በፍቅርሽ ሳስቼ እራሴን ረስቼ
ምግብ መብላት ትቼ
መኖር እንደጀመርኩ እኔን ላንቺ ትቼ
ስትስቂ ካየሁ ባንቺ ደስታ ስስቅ
የከፋሽ ሲመስለኝ ሲልብኝ ድብልቅልቅ
በጣም የሚገርመው ይህ ሁሉ በኔ ላይ ሲሆን የነበረው በፍቅርሽ መያዜን ከቶም ሳልረዳው ጭራሽ ሳይገባኝ ነው
እናም የኔ ፍቅር
ፍቃድሽ ከሆነ ወድሻለሁና
ያንቺ ልሁንና ላንቺው ፍቅር ልኑር።
አሁን ይሄን ባነብላት ከዚህ በፊት ሁለት ስንኝ ያላት ግጥም ስፅፍ አይታኝ አታውቅ ላንቺ የውስጤን ይገልፅልኛል ብዬ የፃፍኩት ግጥም ነው ብላት ያንን ደስ የሚል ሳቋን ስቃ። አይ ሶልዬ በዳዲ ሞት ሙድ መያዝህን ተውና ግጥሙን ወድጄዋለሁ ይልቅ ኬትኛው መፅሀፍ ላይ ነው ያገኘከው ብትለኝ ምን ይውጠኛል ከዛ ቡሀላ ቁምነገር ነው ብላትም አላግጣብኝ ነው እምትሄደው ይቅርብኝ።
ባይሆን እሄን ግጥም ምናልባት ከሊሊ በላይ ማፍቀሬን ባልነግረውም የሚረዳኝ እና ውስጤን የሚያውቀው የፍቅር አምላክ አሳክቶልኝ እሺ ብላኝ አብራኝ ከሆነች ቡሀላ ባነብላት ይሻላል ።
ይሄም ተሰረዘ ። ግጥሙን የፃፍኩባትን ወረቀት በጥንቃቄ አጣጥፌ ኪሴ ውስጥ ከተትኩና ሌላ ባዶ ወረቀት ፊቴ አስቀመጥኩ።
ይልቅ እንድታምነኝ ንግግሬን በሀይለ ቃል አጅቤ ማዥጎድጎድ እንዳለብኝ ውስጤ ሹክ አለኝ።
በቃ በፍቅርሽ ጨርቄን ጥዬ ማበዴ ነው አልቻልኩም እኔስ አፍቅሬሽ ልበድ ላንቺ ማበዴ አይበዛብሽም ግን ደግሞ የኔ ማበድ ለቤቴሰቦቼ ከባድ ነው የማይቋቋሙት ትልቅ ሀዘን ውስጥ እንደሚገቡ አውቃለሁ ያንን ሳስበው ደሞ እንደዛ የሚንሰፈሰፉልኝ ቤተሰቦቼ በኔ ምክንያት ተጎድተው ከማይ ሞቴን እመርጣለሁ ። እውነቴን ነው ሊሊዬ እኔ አብጄ ሁሌ እያዩኝ የስቃይ ሂወት ከሚገፉ ዛሬውኑ ብሞት ይሻለኛል።
እሄን የፍቅር ጥያቄ ሳይሆን ከፊሉ ዛቻ ከፊሉ ኑዛዜ የመሰለ ፅሁፍ ወረቀት ላይ አስፍሬ የራሴ ሀሳብ ሳይሆን ሰው ፅፎ የሰጠኝ ይመስል መልሼ ሳነበው ተናደድኩ። ወረቀቱን በጫጭቄ ጣልኩት።
ሁለተኛው የትምህርት ክፍለ ግዜ ተጠናቆ ሶስተኛው ተጋመሰ።ሲደወል እረፍት ነው። ሊሊን አዋራታለሁ። እስካሁን ግን ምን እንደምላት አልወሰንኩም ።
ደቂቃዎቹ እያለቁ በሄዱ ቁጥር ንዴቴ እየጨመረ መጣ። የእረፍት ሰአት ሲደወል ።መፃፉን አቃረጥኩና ብእሩን ዴክሱ ላይ አስቀምጬ እጄን አጣጥፌ ከራሴ ጋር ማውራት ጀመርኩ•••
ቆይ ግን ፍቅር እኔን የያዘኝ አለማምዶ ነው እንዴ? ፍቅር ማለት ምን ማለት እንደሆነና እንዴት እንደሚያደርግ እንደማላውቅ እያወቀ አደል እንዴ ዘሎ የተከመረብኝ ታድያ ምን እንደምል እንዴት እንደማስረዳት እንዴት እንደማሳምናት እያሰብኩ ምን አጨናነቀኝ።
ልክ ሳገኛት ለስንት ወራት ውስጤ ተቀምጦ የነበረው ፍቅር እራሱን ይግለጥላት።
ሰው ምን ብዬ ባስረዳት ታምነኛለች እያለ መጨነቅ ያለበት ፍቅሩ የውሸት ከሆነ ብቻ ነው። እኔ እሷን ማፍቀሬ ግን እውነት ነው። እውነት ደሞ እራሱን የሚገልጥበት መንገድ አያጣም። የቃላት ቀመር የንግግር ልምምድ አያስፈልገውም። ምክንያቱም ምን ልበል ብዬ አላስብም የምለው ነገር በሙሉ የሆንኩትን ነው።
የሆነውን ነገር መናገር ቢያቅተኝ እንኳን እሷ ፊት ቆሜ የልቤን ህመም መግለጥ አለመቻሌ በራሱ ፍቅር ነው አልኩና።
ያሰብኩትን ደግሜ ሳስበው ይገርማል ፍቅር ፈላስፋም፣ ዘፋኝም፣ ገጣሚም፣ እብድም፣ ፀሀፊም፣ አልቃሽ ደስተኛም ተካዥም፣ ብቸኛም ያረጋል ሲባል አይገባኝም ነበር ዛሬ ግን ያሰብኩት ምን ማለት እንደሆነ ለራሴም ግራ እስኪገባኝ ፈላስፋ አድርጎኝ አረፈው።
ግን ይሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትምሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር
ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ
እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••
💫የቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በጥላሁን
ንገራት ንገራት ንገራት የሚለው ቃሉ ጭንቃላቴ ላይ ሲያቃጭልብኝ አምሽቶ. አነጋ ። እነግራታለሁ ወሰንኩ ሰኛ ለሊት አስራ አንድ ሰአት ተነስቼ ገላዬን ታጠብኩ
ጥዋት ሶስት ፔሬድ ሙሉ የተማርኩትም የፃፍኩትም ትዝ አይለኝም ።
ምን እንደምላት ስፅፍ ስለማመድ ቆየሁ•••
ምን ብዬ እንደምጀምር ምን ብዬ እንደምቀጥል እና ምን ብዬ እንደምደመድም የትኛው ሀሳብ መቅደም የትኛው መከተል እንዳለበት መግቢያ ማጠናከሪያ መደምደሚያ ብዬ ከፋፍዬ ላስቀምጥ ብሞክርም ውስጤ ያለውን የፍቅር ንዳድ በደንብ ሊገልፁላት የሚችሉ ቃላቶች ማግኘት ፈተና ሆነብኝ።
መግቢያ:- ሊሊዬ ለብቻሽ ላናግርሽ የፈለኩት አንድ ጉዳይ ነበረኝ ለዛ ነው ለብቻሽን ላናግርሽ የፈለኩት....
ወይ ጣጣ እሄ ደሞ የፍቅር ጥያቄ ሳይሆን ብድር የሚጠይቅ ሰው የሚጠቀምበት የመግቢያ ንግግር ይመስላ አቦ አልኩና እላዩ ላይ ትልቅ የኤክስ ምልክት አጋድሜ ግድግዳውን ተደግፌ ከክፍሉ ሴት ተማሪዎች በሙሉ እንኳን የትምህርትቤቱን ይንፎርም የተቀዳደደ ጆንያ ለብሳ ብትመጣ ውበቷ የማይጎድልብኝን የለበሰችው የሳቀችው የተናገረችው ሁሉ ልዩ እና ውብ መስሎ የሚታየኝን እኔ ከተቀመጥኩበት በስተግራ እክፍሉ መሀል ላይ ከሁለት ሴት ጓደኛቿ መሀል ላይ ያለችውን ሊሊዬን ከጀርባ እያየሁ የምላትን ማሰብ ጀመርኩ።
የመጣልኝን ሁለተኛውን ሀሳብ መፃፍ ጀመርኩ•••
ፅሁፉ እየመራኝ ይሁን እኔ እየመራሁት ባይገባኝም ፊደሎቹ እየተፈላለጉ መመሳሰል ጀመሩ ። ሳላስበው እንደመግጠምም አደረገኝ•••
ምን መሰለሽ ? እሄውልሽ ሊሊዬ
እኔ ባንቺ ፍቅር ሁሉን ነገር ጥዬ
ሳይሽ ደስ ይለኛል
ካጠገብሽ ስርቅ ጭንቀት ይወረኛል
ሲለው ፍርሀት ፍርሀት ብርድ ብርድ ይለኛል
በቤተሰብ መሀል እቤቴ ቁጭ ብዬ
ብቻዬን የሆንኩኝ ያህል ይሰማኛል
ሳቅሽ ይርበኛል
አንቺ ሳትኖሪ ድምፅሽ ይጠራኛል
በውድቅት ለሊት ሰው ሁሉ ተኝቶ
እኔ አስብሻለሁ
አንቺ ሳትመጪ ኮቴሽ ይሰማኛል
የቱንስ ልንገርሽ የቱኛውን ትቼ
በፍቅርሽ ሳስቼ እራሴን ረስቼ
ምግብ መብላት ትቼ
መኖር እንደጀመርኩ እኔን ላንቺ ትቼ
ስትስቂ ካየሁ ባንቺ ደስታ ስስቅ
የከፋሽ ሲመስለኝ ሲልብኝ ድብልቅልቅ
በጣም የሚገርመው ይህ ሁሉ በኔ ላይ ሲሆን የነበረው በፍቅርሽ መያዜን ከቶም ሳልረዳው ጭራሽ ሳይገባኝ ነው
እናም የኔ ፍቅር
ፍቃድሽ ከሆነ ወድሻለሁና
ያንቺ ልሁንና ላንቺው ፍቅር ልኑር።
አሁን ይሄን ባነብላት ከዚህ በፊት ሁለት ስንኝ ያላት ግጥም ስፅፍ አይታኝ አታውቅ ላንቺ የውስጤን ይገልፅልኛል ብዬ የፃፍኩት ግጥም ነው ብላት ያንን ደስ የሚል ሳቋን ስቃ። አይ ሶልዬ በዳዲ ሞት ሙድ መያዝህን ተውና ግጥሙን ወድጄዋለሁ ይልቅ ኬትኛው መፅሀፍ ላይ ነው ያገኘከው ብትለኝ ምን ይውጠኛል ከዛ ቡሀላ ቁምነገር ነው ብላትም አላግጣብኝ ነው እምትሄደው ይቅርብኝ።
ባይሆን እሄን ግጥም ምናልባት ከሊሊ በላይ ማፍቀሬን ባልነግረውም የሚረዳኝ እና ውስጤን የሚያውቀው የፍቅር አምላክ አሳክቶልኝ እሺ ብላኝ አብራኝ ከሆነች ቡሀላ ባነብላት ይሻላል ።
ይሄም ተሰረዘ ። ግጥሙን የፃፍኩባትን ወረቀት በጥንቃቄ አጣጥፌ ኪሴ ውስጥ ከተትኩና ሌላ ባዶ ወረቀት ፊቴ አስቀመጥኩ።
ይልቅ እንድታምነኝ ንግግሬን በሀይለ ቃል አጅቤ ማዥጎድጎድ እንዳለብኝ ውስጤ ሹክ አለኝ።
በቃ በፍቅርሽ ጨርቄን ጥዬ ማበዴ ነው አልቻልኩም እኔስ አፍቅሬሽ ልበድ ላንቺ ማበዴ አይበዛብሽም ግን ደግሞ የኔ ማበድ ለቤቴሰቦቼ ከባድ ነው የማይቋቋሙት ትልቅ ሀዘን ውስጥ እንደሚገቡ አውቃለሁ ያንን ሳስበው ደሞ እንደዛ የሚንሰፈሰፉልኝ ቤተሰቦቼ በኔ ምክንያት ተጎድተው ከማይ ሞቴን እመርጣለሁ ። እውነቴን ነው ሊሊዬ እኔ አብጄ ሁሌ እያዩኝ የስቃይ ሂወት ከሚገፉ ዛሬውኑ ብሞት ይሻለኛል።
እሄን የፍቅር ጥያቄ ሳይሆን ከፊሉ ዛቻ ከፊሉ ኑዛዜ የመሰለ ፅሁፍ ወረቀት ላይ አስፍሬ የራሴ ሀሳብ ሳይሆን ሰው ፅፎ የሰጠኝ ይመስል መልሼ ሳነበው ተናደድኩ። ወረቀቱን በጫጭቄ ጣልኩት።
ሁለተኛው የትምህርት ክፍለ ግዜ ተጠናቆ ሶስተኛው ተጋመሰ።ሲደወል እረፍት ነው። ሊሊን አዋራታለሁ። እስካሁን ግን ምን እንደምላት አልወሰንኩም ።
ደቂቃዎቹ እያለቁ በሄዱ ቁጥር ንዴቴ እየጨመረ መጣ። የእረፍት ሰአት ሲደወል ።መፃፉን አቃረጥኩና ብእሩን ዴክሱ ላይ አስቀምጬ እጄን አጣጥፌ ከራሴ ጋር ማውራት ጀመርኩ•••
ቆይ ግን ፍቅር እኔን የያዘኝ አለማምዶ ነው እንዴ? ፍቅር ማለት ምን ማለት እንደሆነና እንዴት እንደሚያደርግ እንደማላውቅ እያወቀ አደል እንዴ ዘሎ የተከመረብኝ ታድያ ምን እንደምል እንዴት እንደማስረዳት እንዴት እንደማሳምናት እያሰብኩ ምን አጨናነቀኝ።
ልክ ሳገኛት ለስንት ወራት ውስጤ ተቀምጦ የነበረው ፍቅር እራሱን ይግለጥላት።
ሰው ምን ብዬ ባስረዳት ታምነኛለች እያለ መጨነቅ ያለበት ፍቅሩ የውሸት ከሆነ ብቻ ነው። እኔ እሷን ማፍቀሬ ግን እውነት ነው። እውነት ደሞ እራሱን የሚገልጥበት መንገድ አያጣም። የቃላት ቀመር የንግግር ልምምድ አያስፈልገውም። ምክንያቱም ምን ልበል ብዬ አላስብም የምለው ነገር በሙሉ የሆንኩትን ነው።
የሆነውን ነገር መናገር ቢያቅተኝ እንኳን እሷ ፊት ቆሜ የልቤን ህመም መግለጥ አለመቻሌ በራሱ ፍቅር ነው አልኩና።
ያሰብኩትን ደግሜ ሳስበው ይገርማል ፍቅር ፈላስፋም፣ ዘፋኝም፣ ገጣሚም፣ እብድም፣ ፀሀፊም፣ አልቃሽ ደስተኛም ተካዥም፣ ብቸኛም ያረጋል ሲባል አይገባኝም ነበር ዛሬ ግን ያሰብኩት ምን ማለት እንደሆነ ለራሴም ግራ እስኪገባኝ ፈላስፋ አድርጎኝ አረፈው።
ግን ይሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትምሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር
ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ
እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••
💫የቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1🔥1
#በኔ_የደረሰ•
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
፡
#በጥላሁን
...እሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትንሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••
መጨነቄን በማስተዋል ስታይ የነበረችው ሊሊ
"ሶልዬ አትጨነቅ በቃ እንደምትወደኝ እንኳን እኔ ጓደኛቼም ያውቃሉ!
ታፈቅረኛለህ አደል?
እሱን ልትነግረኝ ፈልገህ ነው አደል እንዲህ ፈንጅ እንደረገጠ ሰው በቆምክበት ደርቀህ ምላስህም ሰውነትህም አልንቀሳቀስ ያለው ?ስትለኝ ጆሮዬን ማመን ተሳነኝ ።
ንግግሯ ምላሴ የታሰረበትን ገመድ በጣጠሰው መሰለኝ
" ሊሊዬ አዎ አፈቅርሻለሁ ግን እንደማፈቅርሽ በምን አውቅሽ ?
ጓደኛችሽ እንዴት አወቁ ? ስላት ሳቋን ለቀቅችው
"አንተስ እንዳፈቀርከኝ በምን አወክ? ብላ ግራ የገባው ጥያቄ በመጠየቅ ግራ አጋባችኝ ቢሆንም ምላሴ ተፈቷልና ለመመለስ አልቦዘንኩም•••
እኔማ እንዴት አላውቅም ሊሊዬ
ለሰከንድ ስላንቺና አንቺን ከማሰብ ተዘናግቼ አላውቅም ።
የሚዘፈነው የፍቅር ዘፈን በሙሉ ላንቺ የተዘፈነ ይመስለኛል ።
በፍቅሯ የሆንኩትን በሙሉ ለመዘርዘር ሲዳዳኝ •••
አንገቴ ላይ ድንገት ተጠምጥማ " እኔም እወድሀለሁኮ ሶልዬ!" ስትለኝ ከደረቴ በታች የሆነ ብቻ ለመግለፅም የሚከብድ እስከዛሬ ተሰምቶኝ የማያውቅ ስሜት ተሰማኝ።
ምን አልሽኝ ሊሊዬ አልኩ እንድትደግምልኝ ፈልጌ ዝም አለች። ደግሜ ለመስማት ፈልጌ በዝምታ ጠብኳት ። ደገመችው ።ደጋገመችው። አብረን ሆንን።
እኔ ከሊሊ ጋር በፍቅር ብን ማለቴ ጨርሶ ያልተዋጠለትና ያልተመቸው ሰው ቢኖር ጓደኛዬ ነው
እሄ ጓደኛዬ ኪሩቤል ይባላል ከወንድ ጓደኛቼ በጣም የምወደውና እንደወንድሜ የማየው ከልጅነት ጀምሮ ለብዙ አመታት ተለይቼው የማላውቅ ጓደኛዬ ነው
ታድያ እንደጓደኛ የማፈቅራት ልጅ እሺ ስላለችኝ እና አብራኝ ስለሆነች መደሰት ሲገባው ወረደብኝ ወረደብኝ አይገልፀውም በተግፃፅ እና በምፀት ደበደበኝ ብል ይቀለኛል
"አንተ ግን ምንድን ነው ወንድ አደለህ እንዴ ቆፍጠን በል እንጂ ምን ያዝረከርክሀል ኧረ በናትህ ለሴት ልጅ እሄን ያህል መሸነፍ መዋረድ ነው ለኔ ፍቅር ምናምን ትላለህ እንዴ ፍቅር አንተ ካልደረስክበት አይደርስብህም አንተ ፊት ካልሰጠከው ድርሽ አይልም ለሴት ልጅ የሚያለቅስ ጓደኛ ስላለኝ በጣም ነው ያፈርህምኩት ጓደኛቿ ሁሉ እኮ በፍቅሯ እግሯ ስር እንደጣለችህ ነው የሚያወሩት ኧረ እኔ ለሴት መቼም ቢሆን እንዳንተ ከምሆን ብሞት ይሻለኛል!"
አለኝ ይህን ፀባዩን እና አመለካከቱን በሌሎች ጓደኛቻችን ላይም ሲያንፀባርቀው ስላየሁ በውስጤ "ደርሶብህ እየው ያኔ ብናወራ ይሻላል ፍቅርን የሚያውቀው ያጣጣመው አልያም አልያም አናቱ ላይ ወጥቶ ያብከነከነው ብቻ ነው" እያልኩ ካጠገቡ ከመሄድ በቀር መልስ አልሰጠሁትም።
እንደው ሰው አማህ አትበሉኝና ጓደኛዬ ከምጣላበት የምወድለት ባህሪው በልጦብኝ ዘለቅን እንጂ የሚያናድድ ጢባር አለበት።
ደፋር ነኝ አደል ሰው አማህ አትበሉኝና ማለቴ ?
ቆይ እንዲህ በሀሜት አንስቼ እያፈረጥኩት
ሰው አማህ ካላላችሁኝ ምን ልትሉኝ ነው ?
ምን ላርግ ሲሉ ሰምቼ ነው።
ሲሉ ሰምቼ ያልኩትም ሲሉ ሰምተው ሲሉ ሰምቼ ነው።
አንዳንድ ሰዎች አንድን ሰው በሀሜት ስጋውን ቦጫጭቀው ባጥንቱ ሊያስቀሩት መንደርደር እንደጀመሩ መግቢያ አድርገው የሚጠቀሙት
"ሰው አማህ(አማሽ) አትበሉኝና!"
የሚለውን ፈንጅ አምካኝ ንግግር ነው ሰው ላይ የሀሜት ፈንጅ እየወረወሩ እነሱ ላይ የሚወረወረውን የትዝብት ፈንጅ የሚያመክኑት "ሰው አማህ /ሰው አማሽ አትበሉኝና" በሚለው ቅድመ ሀሜት ንግግራቸው ነው።
እናም ሁሌም እንደዚህ የሚሉ ሰዎች ሲያጋጥሟችሁ ሰው እያሙ ሰው አማህ ወይም ሰው አማሽ ካላላቹሀቸው ምን ምን እንደምትሏቸው ማሰብ ጀምሩ።
መልሱን ለናንተ ልተወውና ወደ ጉዳዬ ልመለስ
ሰው አማህ አትበሉኝና ጋደኛዬ ክሩቤል በተለይ በተለይ በፍቅር ዙርያ ያለው አመለካከትና በፍቅር መሀል ጣልቃ ለመግባት ያለው ድፍረት ያናድደኛል።
ፍቅርም አይዘኝም ፍቅር የምታስይዘኝም ሴት የለችም መፈክሩ ነው።
አንድ ቀን የኔዋ ሊሊ •••
"ጋደኛዬ ጓደኛህን ክሩቤልን ወዳዋለች ልጁ ግን እሚገባው ነገር አደለም እባክህን አናግረው እስቲ ሶልዬ!" ስትለኝ በጣም ደነገጥኩ ሄጄ ሳናግረው ምን እንደሚለኝ! እንዴት እንደሚላላጥብኝ! አንተን አረከኝ እንዴ ብሎ እንደሚዘልፈኝም አውቀዋለሁ ቢሆንም የማይቻል ወይም ጭራሽ የማይሞከር ካልሆነ በስተቀር ሊሊዬ ምንም አድርግልኝ ብትለኝ የትም ሂድልኝ ብትለኝ እምቢ ለማለት አቅም የለኝምና ኩሩቤልን አናግሬው ምላሹን እንደምነግራት ቃል ገብቼ ተለያየን።
ሄጄ ሳናግረው እንደፈራሁት ተላላጠብኝ ብዙ ነገር አውርቶ በመጨረሻ ጥየው ስሄድ ጮክ ብሎ "ቢጤሽን ፈልጊ በላት "አለኝ ።
ለሊዬ በቃ ልጁ አይሆናትም ይቅርባት ምላሹ ጥሩ አደለም አልኳት። ልጅታ ከሊሊ መልሱን ስትሰማ "ያፈቀረ ሲቆርጥም የመረረ!" እንዲሉ እርግፍ አድርጋ ተወችው ። ከተወሰነ ግዜ ቡሀላ ልጅቷ ከአንድ ልጅ ጋር ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ አዘውትራ መታየት ጀመረች።
ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነበር
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
፡
#በጥላሁን
...እሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትንሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••
መጨነቄን በማስተዋል ስታይ የነበረችው ሊሊ
"ሶልዬ አትጨነቅ በቃ እንደምትወደኝ እንኳን እኔ ጓደኛቼም ያውቃሉ!
ታፈቅረኛለህ አደል?
እሱን ልትነግረኝ ፈልገህ ነው አደል እንዲህ ፈንጅ እንደረገጠ ሰው በቆምክበት ደርቀህ ምላስህም ሰውነትህም አልንቀሳቀስ ያለው ?ስትለኝ ጆሮዬን ማመን ተሳነኝ ።
ንግግሯ ምላሴ የታሰረበትን ገመድ በጣጠሰው መሰለኝ
" ሊሊዬ አዎ አፈቅርሻለሁ ግን እንደማፈቅርሽ በምን አውቅሽ ?
ጓደኛችሽ እንዴት አወቁ ? ስላት ሳቋን ለቀቅችው
"አንተስ እንዳፈቀርከኝ በምን አወክ? ብላ ግራ የገባው ጥያቄ በመጠየቅ ግራ አጋባችኝ ቢሆንም ምላሴ ተፈቷልና ለመመለስ አልቦዘንኩም•••
እኔማ እንዴት አላውቅም ሊሊዬ
ለሰከንድ ስላንቺና አንቺን ከማሰብ ተዘናግቼ አላውቅም ።
የሚዘፈነው የፍቅር ዘፈን በሙሉ ላንቺ የተዘፈነ ይመስለኛል ።
በፍቅሯ የሆንኩትን በሙሉ ለመዘርዘር ሲዳዳኝ •••
አንገቴ ላይ ድንገት ተጠምጥማ " እኔም እወድሀለሁኮ ሶልዬ!" ስትለኝ ከደረቴ በታች የሆነ ብቻ ለመግለፅም የሚከብድ እስከዛሬ ተሰምቶኝ የማያውቅ ስሜት ተሰማኝ።
ምን አልሽኝ ሊሊዬ አልኩ እንድትደግምልኝ ፈልጌ ዝም አለች። ደግሜ ለመስማት ፈልጌ በዝምታ ጠብኳት ። ደገመችው ።ደጋገመችው። አብረን ሆንን።
እኔ ከሊሊ ጋር በፍቅር ብን ማለቴ ጨርሶ ያልተዋጠለትና ያልተመቸው ሰው ቢኖር ጓደኛዬ ነው
እሄ ጓደኛዬ ኪሩቤል ይባላል ከወንድ ጓደኛቼ በጣም የምወደውና እንደወንድሜ የማየው ከልጅነት ጀምሮ ለብዙ አመታት ተለይቼው የማላውቅ ጓደኛዬ ነው
ታድያ እንደጓደኛ የማፈቅራት ልጅ እሺ ስላለችኝ እና አብራኝ ስለሆነች መደሰት ሲገባው ወረደብኝ ወረደብኝ አይገልፀውም በተግፃፅ እና በምፀት ደበደበኝ ብል ይቀለኛል
"አንተ ግን ምንድን ነው ወንድ አደለህ እንዴ ቆፍጠን በል እንጂ ምን ያዝረከርክሀል ኧረ በናትህ ለሴት ልጅ እሄን ያህል መሸነፍ መዋረድ ነው ለኔ ፍቅር ምናምን ትላለህ እንዴ ፍቅር አንተ ካልደረስክበት አይደርስብህም አንተ ፊት ካልሰጠከው ድርሽ አይልም ለሴት ልጅ የሚያለቅስ ጓደኛ ስላለኝ በጣም ነው ያፈርህምኩት ጓደኛቿ ሁሉ እኮ በፍቅሯ እግሯ ስር እንደጣለችህ ነው የሚያወሩት ኧረ እኔ ለሴት መቼም ቢሆን እንዳንተ ከምሆን ብሞት ይሻለኛል!"
አለኝ ይህን ፀባዩን እና አመለካከቱን በሌሎች ጓደኛቻችን ላይም ሲያንፀባርቀው ስላየሁ በውስጤ "ደርሶብህ እየው ያኔ ብናወራ ይሻላል ፍቅርን የሚያውቀው ያጣጣመው አልያም አልያም አናቱ ላይ ወጥቶ ያብከነከነው ብቻ ነው" እያልኩ ካጠገቡ ከመሄድ በቀር መልስ አልሰጠሁትም።
እንደው ሰው አማህ አትበሉኝና ጓደኛዬ ከምጣላበት የምወድለት ባህሪው በልጦብኝ ዘለቅን እንጂ የሚያናድድ ጢባር አለበት።
ደፋር ነኝ አደል ሰው አማህ አትበሉኝና ማለቴ ?
ቆይ እንዲህ በሀሜት አንስቼ እያፈረጥኩት
ሰው አማህ ካላላችሁኝ ምን ልትሉኝ ነው ?
ምን ላርግ ሲሉ ሰምቼ ነው።
ሲሉ ሰምቼ ያልኩትም ሲሉ ሰምተው ሲሉ ሰምቼ ነው።
አንዳንድ ሰዎች አንድን ሰው በሀሜት ስጋውን ቦጫጭቀው ባጥንቱ ሊያስቀሩት መንደርደር እንደጀመሩ መግቢያ አድርገው የሚጠቀሙት
"ሰው አማህ(አማሽ) አትበሉኝና!"
የሚለውን ፈንጅ አምካኝ ንግግር ነው ሰው ላይ የሀሜት ፈንጅ እየወረወሩ እነሱ ላይ የሚወረወረውን የትዝብት ፈንጅ የሚያመክኑት "ሰው አማህ /ሰው አማሽ አትበሉኝና" በሚለው ቅድመ ሀሜት ንግግራቸው ነው።
እናም ሁሌም እንደዚህ የሚሉ ሰዎች ሲያጋጥሟችሁ ሰው እያሙ ሰው አማህ ወይም ሰው አማሽ ካላላቹሀቸው ምን ምን እንደምትሏቸው ማሰብ ጀምሩ።
መልሱን ለናንተ ልተወውና ወደ ጉዳዬ ልመለስ
ሰው አማህ አትበሉኝና ጋደኛዬ ክሩቤል በተለይ በተለይ በፍቅር ዙርያ ያለው አመለካከትና በፍቅር መሀል ጣልቃ ለመግባት ያለው ድፍረት ያናድደኛል።
ፍቅርም አይዘኝም ፍቅር የምታስይዘኝም ሴት የለችም መፈክሩ ነው።
አንድ ቀን የኔዋ ሊሊ •••
"ጋደኛዬ ጓደኛህን ክሩቤልን ወዳዋለች ልጁ ግን እሚገባው ነገር አደለም እባክህን አናግረው እስቲ ሶልዬ!" ስትለኝ በጣም ደነገጥኩ ሄጄ ሳናግረው ምን እንደሚለኝ! እንዴት እንደሚላላጥብኝ! አንተን አረከኝ እንዴ ብሎ እንደሚዘልፈኝም አውቀዋለሁ ቢሆንም የማይቻል ወይም ጭራሽ የማይሞከር ካልሆነ በስተቀር ሊሊዬ ምንም አድርግልኝ ብትለኝ የትም ሂድልኝ ብትለኝ እምቢ ለማለት አቅም የለኝምና ኩሩቤልን አናግሬው ምላሹን እንደምነግራት ቃል ገብቼ ተለያየን።
ሄጄ ሳናግረው እንደፈራሁት ተላላጠብኝ ብዙ ነገር አውርቶ በመጨረሻ ጥየው ስሄድ ጮክ ብሎ "ቢጤሽን ፈልጊ በላት "አለኝ ።
ለሊዬ በቃ ልጁ አይሆናትም ይቅርባት ምላሹ ጥሩ አደለም አልኳት። ልጅታ ከሊሊ መልሱን ስትሰማ "ያፈቀረ ሲቆርጥም የመረረ!" እንዲሉ እርግፍ አድርጋ ተወችው ። ከተወሰነ ግዜ ቡሀላ ልጅቷ ከአንድ ልጅ ጋር ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ አዘውትራ መታየት ጀመረች።
ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነበር
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#በኔ_የደረሰ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በጥላሁን
...ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት
ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነው •••
ስገባ ቀና አለ ። ሁኔታውን ሳየው እንኳን እሱ እኔም ሲለኝ የነበረውን ነገር ሁሉ ረሳሁት። አንጀቴን በላኝ ትናንት እንደዛ ስትል እንዳልነበር ዛሬ እያልኩ በፍቅር በወደቀው ዛፍ ላይ መጥረቢያ ማብዛቱን በጭራሽ አልፈለኩም።
እንኳን እንደዛ ልለው የሆነውን ከሁኔታው ተረድቼ ሳለሁ ምን ሆነሀል? ብዬ ላስጨንቀው አልፈለኩም።
እራሴ ወደጉዳዩ ቀጥታ ብገባ ሁለቴ ቀጥሮኝ ለመናገር የከበደውን ነገር እንደማቀልለት አሰብኩና •••
ትናንት ያጣጣልካትን ልጁ መልሰህ ስላፈቀርካት አይሰማህ ጋደኛዬ ይህ ፍቅር ጉልበቱን የሚያሳይበት አንዱ ባህሪው ነውና "ትናንት እሷ አፍቅራኝ ቢጤሽን ፈልጊ ያልኳትን ልጅ እንዴት እንዲህ በፍቅሯ ልንበረከክ ቻልኩ " እያልክ ከራስህ ጋር አትጣላ የደካማነት ስሜትም እንዳይሰማህ።
ማፍቀር መታደል እንጂ መሸነፍ ወይም መዋረድ አይደለም።ስለፍቅር ሊያውም ጥቂቱ የሚያውቀው ያፈቀረ ብቻ ነው ። ትናንት ስለማታውቀው ፍቅር ምንም ብትል አይገርምም።
አሁን ማፍቀር ዝቅ ማለት መሸነፍ መዝረክረክ ሳይሆን መታደል መሆኑን የተረዳህ ይመስለኛል? ይህን ተናግሬ ቀና መልሱን ስጠብቅ ጭንቄቱን በማወዛወዝ አዎንታውን ከገለፀልኝ ቡሀላ
"እና ያኔ ባልኩህ ነገር አልተቀየምከኝም ማለት ነው ጓደኛዬ? ከተቀየምከኝ ግን ይቅርታ!" አለኝ። አነጋገሩ እና አስተያየቱ በጣም ያሳዝን ነበር።
በጭራሽ አልተቀየምኩህም ጓደኛዬ በጣም የምወድህ ጓደኛዬ እኮ ነህ ከልጅነታችን ጀምሮ ብዙ ነገር አብረን ያሳለፍን ወንድማማቾች ነን ።
እኔ እናት እና አባቴ እህት እንጂ ወንድም አልሰጡኝም አንተ ነህ ከፈጣሪ የተሰጠከኝ ወንድሜም ጋደኛዬም ።
ጋደኛማቾች ነን ማለት ግን አንድ አይነት አስተሳሰብና አመለካከት አለን ማለት አይደለም የአመለካከት ወይም የሀሳብ ልዩነት ደግሞ አያቀያይምም። በርግጥ ጣልቃ ገብተህ ስትገስፀኝ እናደድብህ ይሆናል ቢሆንም በፍቅር ዙርያ የነበረን የአመለካከት ልዩነት ጓደኝነታችንን የማሻከር አቅም የለውም። ስለው ተነስቶ አቀፈኝ። ተቃቀፍን።
"እሺ ምንድን ነው የማናደርገው ሶልዬ እኔ የማብድ የማብድ እየመሰለኝ ነው ከልጁ ጋር ፍቅር የጀመሩ ይመስልሀል?" ሲለኝ•••
አይመስለኝም ለሁሉም ነገር መጀመሪያ የኔዋ ሊሊን ያለውን ነገር በግልፅ እንድትነግረኝ እጠይቃታለሁ ከዛ የሷን መልስ ከሰማሁ ቡሀላ ያለህበትን ሁኔታ መንገር ይኑርብኝ አይኑርብኝ ወስናለሁ።
ጋደኛዬ አንድ ነገር ግን ልነግርህ እፈልጋለሁ ልጅቷን በጣም እንዳፈቀርካት ተረድቻለሁ ከተሳካ እሰየው ባይሳካም ግን ሂወት እንደምትቀጥልና ያንተ ብትሆን ኖሮ እንደሚሳካ ያልተሳካው ፈጣሪ እሷን ላንተ ስላላላት መሆኑን አምነህ ለመቀበል ተዠጋጅ።
ካልሆነ ግን ከዚህኛው ጉዳት ያኛው ይከብዳል ። የሰው እንደሆነች እና እንደማታገኛት እያወክ ማፍቀርን የመሰለ ከባድ ህመም የለም።
ህመሙ ባይቀርልህም እንዳይጠናብህና እራስህን እንዳትጥል ቅድም እንዳልኩህ ሌላ ሂወት እንዳለና ያንተ የሆነችውን ለማግኘት ያንተ ያልሆነችውን ረስተህ እራስህን ሳትጥል መጠበቅ እንዳለብህ ማመን አለብህ ያለበለዝያ ያንተ ያልሆነችውን በማይሳካው የፍቅር አለም ውስጥ ስታሳድድ ያንተ የሆነውን ሁሉ ታጣለህ።
በቅድሚያ ከራስህ ትጣላለህ ። በመቀጠል በዙርያህ ያሉ ሰዎች ሁሉ ያስጠሉህና ከነሱም ትጣላለህ ።
ከዛ በየመንገዱ ከድንጋዩም ከግድግዳውም ከአየሩም ከንፋሱም መጣላት ብቻህን ማውራት ትጀምራለህ ። በመጨረሻ አብደህ ከፈጠርህ ጋም ትጣላና የሰይጣን ትሆናለህ።
ስለዚህ በማፍቀርህ ልክ ባይሳካ ለመርሳትም ተዘጋጅ።
እሺ ሶልዬ በጣም አመሰግናለሁ ግን ልጁን የምታፈቅረው ይመስልሀል?"
እኔ በምን አውቃለሁ ጓደኛዬ እኔም እንዳንተው አብረው አየኋቸው እንጂ ሌላ ምንም የማውቀው ነገር የለም ።
ስንቱ ተቃቅፎ እየሄደ በሆዱ በሚሰዳደብባት አለም አብረው ስለተቀመጡና አብረው ስለሄዱ ብቻ ይፋቀራሉ ብሎ መደምደም መጃጃል ነው
"እሺ አሁን ሊሊን መቼ ልታናግራት ወሰንክ ሶልዬ!"
"ነገ እንገናኛለን ነገ አናግራታለሁ "
"ኧረ ሶልዬ እስከነገ ለምን አሁን ብትደውልላት አይሻልም ቢያንስ ከልጁ ጋር ያላትን ጉኑኝነት ሰምቼ ቁርጤን እንዳውቅ!" ከስልክ ይልቅ ሳገኛት ባወራት እንደሚሻል ውስጤ ቢያምን በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኖ አልደውልም ብለው ምን ያህል እንደሚከፋው በማሰብ ስልኬን አውጥቼ ደወልኩ።
ሊሊዬ ስልኬን አንስታው የራሳችንን ወሬ ከጨረስን ቡሀላ በጎደኛዋና ሰሞኑን አብራት በሚታየው ልጅ መካከል ያለው ግኑኝነት ምን እንደሆነ ስጠይቃት ገብቷት ነው መሰለኝ ረጅም ሳቅ ሳቀች።
ሳቋን ስትጨርስ ለምን እንደሳቀች ስጠይቃት
"ለምን እንደሳኩ እንድነግርህ አንተ በቅድሚያ ለምን እንደጠየከኝ ንገረኝ?" አለችኝ አሁንም ሙሉ በሙሉ ከሳቋ ሳታባራ።
ምን እንደምላት ጨነቀኝ ፍንጭ ካልሰጠኋት ልትነግረኝ እንደማትችል ስረዳ ከጓደኛዬ ክፍል እየወጣው
" ማንነቱን ሳልነግራት አንድ ጓደኛዬ በፍቅሯ እየትንገላታ መሆኑን ልነግራት ገና በቃ አንድ ጋደኛዬ አፍቅሯት•••
ስል በድጋሚ ሳቋ አቃረጠኝ ከሳቋ ከጠል አድርጋ
"ዋው ቀመራችን ሰርቷል ማለት ነዋ "
አለች የምን ቀመር ሊሊዬ?
ቀመሩ ወንዶች ስትባሉ የጣላችሁትን እንኳን ሲያነስባችሁ እንደምትወዱ አውቀን የቀመርነው ነዋ!"
"ልጁ ዘመዷ ነው አብራ መታየት የጀመረችው ሆን ብለን ተማክረን ነበር ጓደኛህ ወጥመዳችን ውስጥ ዘሎ መግባቱ እንደማይቀር ገምቼ ነበር ስትለኝ ደነገጥኩም ደስ አለኝም።
ስልኩን ዘግቼ የጓደኛዬን ክፍል በር በርግጄ ገባሁ
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በጥላሁን
...ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት
ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነው •••
ስገባ ቀና አለ ። ሁኔታውን ሳየው እንኳን እሱ እኔም ሲለኝ የነበረውን ነገር ሁሉ ረሳሁት። አንጀቴን በላኝ ትናንት እንደዛ ስትል እንዳልነበር ዛሬ እያልኩ በፍቅር በወደቀው ዛፍ ላይ መጥረቢያ ማብዛቱን በጭራሽ አልፈለኩም።
እንኳን እንደዛ ልለው የሆነውን ከሁኔታው ተረድቼ ሳለሁ ምን ሆነሀል? ብዬ ላስጨንቀው አልፈለኩም።
እራሴ ወደጉዳዩ ቀጥታ ብገባ ሁለቴ ቀጥሮኝ ለመናገር የከበደውን ነገር እንደማቀልለት አሰብኩና •••
ትናንት ያጣጣልካትን ልጁ መልሰህ ስላፈቀርካት አይሰማህ ጋደኛዬ ይህ ፍቅር ጉልበቱን የሚያሳይበት አንዱ ባህሪው ነውና "ትናንት እሷ አፍቅራኝ ቢጤሽን ፈልጊ ያልኳትን ልጅ እንዴት እንዲህ በፍቅሯ ልንበረከክ ቻልኩ " እያልክ ከራስህ ጋር አትጣላ የደካማነት ስሜትም እንዳይሰማህ።
ማፍቀር መታደል እንጂ መሸነፍ ወይም መዋረድ አይደለም።ስለፍቅር ሊያውም ጥቂቱ የሚያውቀው ያፈቀረ ብቻ ነው ። ትናንት ስለማታውቀው ፍቅር ምንም ብትል አይገርምም።
አሁን ማፍቀር ዝቅ ማለት መሸነፍ መዝረክረክ ሳይሆን መታደል መሆኑን የተረዳህ ይመስለኛል? ይህን ተናግሬ ቀና መልሱን ስጠብቅ ጭንቄቱን በማወዛወዝ አዎንታውን ከገለፀልኝ ቡሀላ
"እና ያኔ ባልኩህ ነገር አልተቀየምከኝም ማለት ነው ጓደኛዬ? ከተቀየምከኝ ግን ይቅርታ!" አለኝ። አነጋገሩ እና አስተያየቱ በጣም ያሳዝን ነበር።
በጭራሽ አልተቀየምኩህም ጓደኛዬ በጣም የምወድህ ጓደኛዬ እኮ ነህ ከልጅነታችን ጀምሮ ብዙ ነገር አብረን ያሳለፍን ወንድማማቾች ነን ።
እኔ እናት እና አባቴ እህት እንጂ ወንድም አልሰጡኝም አንተ ነህ ከፈጣሪ የተሰጠከኝ ወንድሜም ጋደኛዬም ።
ጋደኛማቾች ነን ማለት ግን አንድ አይነት አስተሳሰብና አመለካከት አለን ማለት አይደለም የአመለካከት ወይም የሀሳብ ልዩነት ደግሞ አያቀያይምም። በርግጥ ጣልቃ ገብተህ ስትገስፀኝ እናደድብህ ይሆናል ቢሆንም በፍቅር ዙርያ የነበረን የአመለካከት ልዩነት ጓደኝነታችንን የማሻከር አቅም የለውም። ስለው ተነስቶ አቀፈኝ። ተቃቀፍን።
"እሺ ምንድን ነው የማናደርገው ሶልዬ እኔ የማብድ የማብድ እየመሰለኝ ነው ከልጁ ጋር ፍቅር የጀመሩ ይመስልሀል?" ሲለኝ•••
አይመስለኝም ለሁሉም ነገር መጀመሪያ የኔዋ ሊሊን ያለውን ነገር በግልፅ እንድትነግረኝ እጠይቃታለሁ ከዛ የሷን መልስ ከሰማሁ ቡሀላ ያለህበትን ሁኔታ መንገር ይኑርብኝ አይኑርብኝ ወስናለሁ።
ጋደኛዬ አንድ ነገር ግን ልነግርህ እፈልጋለሁ ልጅቷን በጣም እንዳፈቀርካት ተረድቻለሁ ከተሳካ እሰየው ባይሳካም ግን ሂወት እንደምትቀጥልና ያንተ ብትሆን ኖሮ እንደሚሳካ ያልተሳካው ፈጣሪ እሷን ላንተ ስላላላት መሆኑን አምነህ ለመቀበል ተዠጋጅ።
ካልሆነ ግን ከዚህኛው ጉዳት ያኛው ይከብዳል ። የሰው እንደሆነች እና እንደማታገኛት እያወክ ማፍቀርን የመሰለ ከባድ ህመም የለም።
ህመሙ ባይቀርልህም እንዳይጠናብህና እራስህን እንዳትጥል ቅድም እንዳልኩህ ሌላ ሂወት እንዳለና ያንተ የሆነችውን ለማግኘት ያንተ ያልሆነችውን ረስተህ እራስህን ሳትጥል መጠበቅ እንዳለብህ ማመን አለብህ ያለበለዝያ ያንተ ያልሆነችውን በማይሳካው የፍቅር አለም ውስጥ ስታሳድድ ያንተ የሆነውን ሁሉ ታጣለህ።
በቅድሚያ ከራስህ ትጣላለህ ። በመቀጠል በዙርያህ ያሉ ሰዎች ሁሉ ያስጠሉህና ከነሱም ትጣላለህ ።
ከዛ በየመንገዱ ከድንጋዩም ከግድግዳውም ከአየሩም ከንፋሱም መጣላት ብቻህን ማውራት ትጀምራለህ ። በመጨረሻ አብደህ ከፈጠርህ ጋም ትጣላና የሰይጣን ትሆናለህ።
ስለዚህ በማፍቀርህ ልክ ባይሳካ ለመርሳትም ተዘጋጅ።
እሺ ሶልዬ በጣም አመሰግናለሁ ግን ልጁን የምታፈቅረው ይመስልሀል?"
እኔ በምን አውቃለሁ ጓደኛዬ እኔም እንዳንተው አብረው አየኋቸው እንጂ ሌላ ምንም የማውቀው ነገር የለም ።
ስንቱ ተቃቅፎ እየሄደ በሆዱ በሚሰዳደብባት አለም አብረው ስለተቀመጡና አብረው ስለሄዱ ብቻ ይፋቀራሉ ብሎ መደምደም መጃጃል ነው
"እሺ አሁን ሊሊን መቼ ልታናግራት ወሰንክ ሶልዬ!"
"ነገ እንገናኛለን ነገ አናግራታለሁ "
"ኧረ ሶልዬ እስከነገ ለምን አሁን ብትደውልላት አይሻልም ቢያንስ ከልጁ ጋር ያላትን ጉኑኝነት ሰምቼ ቁርጤን እንዳውቅ!" ከስልክ ይልቅ ሳገኛት ባወራት እንደሚሻል ውስጤ ቢያምን በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኖ አልደውልም ብለው ምን ያህል እንደሚከፋው በማሰብ ስልኬን አውጥቼ ደወልኩ።
ሊሊዬ ስልኬን አንስታው የራሳችንን ወሬ ከጨረስን ቡሀላ በጎደኛዋና ሰሞኑን አብራት በሚታየው ልጅ መካከል ያለው ግኑኝነት ምን እንደሆነ ስጠይቃት ገብቷት ነው መሰለኝ ረጅም ሳቅ ሳቀች።
ሳቋን ስትጨርስ ለምን እንደሳቀች ስጠይቃት
"ለምን እንደሳኩ እንድነግርህ አንተ በቅድሚያ ለምን እንደጠየከኝ ንገረኝ?" አለችኝ አሁንም ሙሉ በሙሉ ከሳቋ ሳታባራ።
ምን እንደምላት ጨነቀኝ ፍንጭ ካልሰጠኋት ልትነግረኝ እንደማትችል ስረዳ ከጓደኛዬ ክፍል እየወጣው
" ማንነቱን ሳልነግራት አንድ ጓደኛዬ በፍቅሯ እየትንገላታ መሆኑን ልነግራት ገና በቃ አንድ ጋደኛዬ አፍቅሯት•••
ስል በድጋሚ ሳቋ አቃረጠኝ ከሳቋ ከጠል አድርጋ
"ዋው ቀመራችን ሰርቷል ማለት ነዋ "
አለች የምን ቀመር ሊሊዬ?
ቀመሩ ወንዶች ስትባሉ የጣላችሁትን እንኳን ሲያነስባችሁ እንደምትወዱ አውቀን የቀመርነው ነዋ!"
"ልጁ ዘመዷ ነው አብራ መታየት የጀመረችው ሆን ብለን ተማክረን ነበር ጓደኛህ ወጥመዳችን ውስጥ ዘሎ መግባቱ እንደማይቀር ገምቼ ነበር ስትለኝ ደነገጥኩም ደስ አለኝም።
ስልኩን ዘግቼ የጓደኛዬን ክፍል በር በርግጄ ገባሁ
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
❤1👍1