😘 #ቃል 😘
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ ሶስት (33)
‹‹እንግዲያውስ…. አንቺና ጆርጅ ተጋብታችሁ… ሥራውን ለቀሽ ማለት ነው፡፡ ለምን እየተደጋገፋችሁ ፤ ደስ እየተሰኛችሁ አትኖሩም ?! እግረ መንገዱን አዲስ አይነት ኑሮም ይሆንላችኋል » አለ ማይክ ። ማይክል ስለጆርጅ እና ስለ ማሪዮን ሂልያርድ ግንኙነት በግልፅ ሲናገር ይህ የመጀመሪያው ነበር ። ስለዚህ ጆርጅ ይህን ሲሰማ አፈረ ። ፊቱ ቀላ ። ሆኖም የመከፋት ስሜት አልታየበትም።
«ማይክል!» አለች ማሪዮን ። ያ ይህን አድርግ ፤ ይህን አታድርግ የሚለው ድምጽዋ እየተመለሰ «ማይክል እስበህ ተናገር። ሌላው ቢቀር ጆርጅን እስበው ። እንዴት እንዳስደነገጥከው ይታይሀል ? ያም ተባለ ይህ ሥራ ለመተው አልደረስኩም ። አመመኝም ቀረም ለመሥራት ጉልበት አላነሰኝም»
«እሱ እንዳልሽው ይሁን ፤እሺ ልበል። ምንም ማድረግ ልችልም። ግን ሥራ ቀንሺ። ማለት ለምሳሌ በሚቀጥለው ሳምንት ሳንፍራንሲስኮ መሄድሽ አስፈላጊ አይደለም ። እኔ ልሄድና ጉዳዩን ልፈፅም እችላለሁ ። እዚህ እዋናው መሥሪያ ቤት ቁጭ ብለሽ ይህን ያን አድርጉ ብትይን ልንረዳሽ እንችላለን ። በቃ፣ይህን ያህል እሺ በይኝ» ሳቀች እንጂ ሌላ መልስ አልሰጠችውም ። ከዚያም ብድግ ብላ ወደ መደበኛ የቢሮ መቀመጫዋ ሄደችና ተቀመጠች ። ስጋዋ እንደደከመ ይታያል ። መንፈሷ ግን ወደ ዱሮ ቦታው ተመልሷል ። ሁሉንም ካየች በኋላ ፡፡ «አሁን በከንፈር መጠጣና በአዘንልሽ አትጫኑኝ ። ሁላችሁም ማለቴ ነው ። ሂዱልኝ ። እናንተ ሥራ ከሌላችሁ… እንዲያ ይመስለኛል ሳያችሁ… እኔ ሥራ አለብኝ ፤ ልሥራበት»
«እማዬ ፤ ቤት አድርሼሽ ልምጣ።እስኪ አንዳንድ ቀን ሰው የሚልሽን እሺ በይ !» አለ ማይክል ቆጣና ኮረፍ ብሎ። «ማይክል የማይቻል ነገር አታውራ ። አሁን ቀጥ ብለህ ወደ ሥራህ ሂድ። ያለዚያ ጆርጅን እየገፈተርክ አስወጣልኝ እንዳልለው» ጆርጅ ፈገግ አለ… የነገሩ መታሰብ አስገርሞት ። «ባይሆን ሰዓት ደረሰ አልደረሰ ሳልል ለመሄድ እሞክራለሁ እንጄ አሁን አይሆንም ። በተረፈ ስለመልካም አስተሳሰብህና ስለሌላው እመሰግናለሁ ። በቃ ። ሩት ያን በር ክፈች» ጸሐፊዋ በሩን ከፍታ እንዲወጡ መጠባበቅ ጀመረች ። ማይክልና ቤን ወጡ ። ጆርጅ እደረጃው ላይ ቆሞ ፤
«ማሪዮን» አለ።
«እሀ»
«ወደ ቤት መሄድ አለብሽኮ »
«ትንሽ ቆየት ብዬ»
«ደግ። ከግማሽ ሰዓት በኋላ እመለሳለሁ» ወጣ። ፈገግ አለች ። ሆኖም ወደራሷ ሀሳብ ስትመለስ ገና በሩ አልተዘጋም ።
የዛሬው ህመሟ የተነሳበት ምክንያት በሚገባ ታውቋታል ። ስለዚህ አንድ ነገር ማድረግ አለባት ። በሌላው ሌላ ምክንያት እየተነሳ እረፍት አሳጥቷታል ህመሙ። ሌላ መነሻ ሲጨመር ዝም ብላ ማየት አትችልም ። ለምን እንደሆነ አይግባት እንጂ ቤን አቭሪ ስለሜሪ አዳምሰን ሲናገር ሜሪ ማን እንደሆነች አውቃለች ። በርግጥ ናንሲ ማክአሊስተር ናት ብላለች ። ቅድም እስብሰባው ላይ በግልጥ እንደተናገረችው ወደ ሳንፍራንሲስኮ ስትሄድ ሜሪን ለማየትም ፤ ለማነጋገርም ወስናለች ። ግን ታውቃት ይሆን? ምናልባት የተደረገላት የቀዶ ጥገና ህክምና (ፕላስቲክ ሰርጀሪ) ፈጽሞ ለውጧት ሊሆን ይችላል ። ያስ ባይሆን ናንሲን በሚገባ ታስታውሳታለች እንዴ ? አይታወቅም ። ቤን አቭሪ የሰጣትን የሜሪ አዳምሰን አድራሻ አውጥታ ስልክ ደወለች። ስልኩ ሶስቴ ይሁን አራቴ ሲጮህ ተሰማት ። ተነሳ። ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት አቅሏን ስታ ወድቃ የነበረችው ማሪዮን ሂልያርድ መሆኗን ማንም ሊያምን በማይችልበት ደረጃ ረጋ ባለና ስልጣን በተሞላበት ድምጽ፤ «ሚስ አዳምሰን ። ማሪዮን ሂልያርድ ነኝ ፤ ከኒወዮርክ » ስትል ተናገረች ።
ንግግራቸው በጣም አጭር ፤ ተዝቃዛና በመደነጋገር የተሞላ ነበር። ማሪዮን ሂልያርድ ስለሜሪ አዳምሰን በተጨማሪ ያገኘችው እውቀትም አልነበረም ። ይሁን ። ልክ የዛሬ ሶስት ሳምንት ማወቅ የሚገባትን ሁሉ ታውታለች ። ሊገናኙ ተቀጣጥረዋል ። ማሪዮን ቀጠሮውን አጀንዳዋ ላይ ካሰፈረች በኋላ የወንበሯን መከዳ ደገፍ ብላ ወደ ኋላዋ ተለጠጠች ። አይኖቿን ዘጋች ።
ከሜሪ አዳምሰን ጋር ከተገናኙም በኋላ ምንም ጠቃሚ ነገር ላታገኝ ትችላለች ። ሁሉም እንዳሰበችው ላይሆን ይችላል ። ወይም ሜሪ ምንም ነገር ላለመናገር ትወስን ይሆናል... ሆናም ያን ቀን ትፈልገዋለች ። ልትናገራቸው ያውጠነጠነቻቸው ጥቂት ነገሮች አሉ ። ብቻ. . . ብቻ ከዚያ ወዲህ ክፉ ነገር እንዳያጋጥማት። ትልቁ ምኞቷ ይህ ብቻ ነው።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ሶስት ሣምንት ሲደርስ አጭር ጊዜ ነው፡፡ ሲያስቡት ይርዘም እንጂ፤ የማሪዮን ሂልያርድና የሜሪ አዳምሰን ቀጠሮ ደረሰ ከሶስት ሣምንት በኋላ እለተ ሰሉስ ።
ማሪዮን ሂልያርድ ፌይርሞንት በተባለው ሆቴል በተከራየችው የልዩ ማዕረግ ማረፊያዋ ሳሎን ውስጥ ተቀምጣለች ። እዚያ ክፍል ውስጥ አረፍ ብሎ ወደ ውጭ ለተመለከተ ሰው ደንቅ የሆነው ወደብና ከዚያ አልፎ የሚገኘው የማሪን ካውንቲ ውበት በእጅጉ ያስደምመዋል ። ከሌላ ሀሳብም ያወጣዋል ። ማሪዮን ሂልያርድ ግን ይህን ትእይንት ለማየት ፍላጐት አልነበራትም ። ስለዚያች ልጅ በማሰብ ላይ ነበረች ። ምን ሆና ይሆን? ምን ትመስል ይሆን? ግሬግሰን (ፒተር) ከሁለት ዓመት በፊት ታምር አሳይሻለሁ ብሎ አንደፎከረ ተሳክቶለት ታምር በርቶ ይሆን? ቤን አቭሪ ሜሪ አዳምሰንን ሲያያት የሚያውቃት ሴት እንዳልሆነችበት ግልፅ ነው… ማይክልም ቢያያት አያስታውሳትም ይሆን? እሷስ እንዴት ነው ይሆን የምትኖረው ? ከሌላ ወንድ ጋር ፍቅር ይዞአት ይሆን ወይስ እንደማይክል ሁሉን ነገር ትታ አንገቷን ደፍታ ውስጧ እየበገነ መኖር ቀጥላ ይሆን ? ማሪዮን ሂልያርድ የቀጠሮው ሰዓት እስኪደርስ ስለ ናንሲ ማክአሊስተር ስታስብ ልጅዋ በመሀል ገባ። እሱም ፍቅር ያውቅ ነበር ። አፍቅሮ ነበር ። እንዲያውም አሁን እምትጠብቀው ማይክል ሂልያርድ በጣም ይወዳት የነበረችዋን ልጅ ነው። ግን…. እሷ ባትሆንስ ? ካልሆነች . . . ካልሆነች ምንም ለውጥ አያመጣም። እሷ ካልሆነች አንዲት የዚሁ አካባቢ ተወላጅ የሆነች ፎቶ አንሺ ናት ማለት ነው ቤን አቭሪ አይኑን የጣለባት ፎቶግራፍ አንሺ። በቃ። ሊሆን ይችላል ። ያወጣሁት ያወረድኩት ፤ አስቤ የቀመርኩት ፤እውነት ብዬ ያሰብኩት ነገር ሁሉ መሰረተ ቢስ ፤ አጉል ሀሳብ ሊሆን ይችላል አለች በሀሳቧ።
ምናልባት. . . ምናልባት
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ ሶስት (33)
‹‹እንግዲያውስ…. አንቺና ጆርጅ ተጋብታችሁ… ሥራውን ለቀሽ ማለት ነው፡፡ ለምን እየተደጋገፋችሁ ፤ ደስ እየተሰኛችሁ አትኖሩም ?! እግረ መንገዱን አዲስ አይነት ኑሮም ይሆንላችኋል » አለ ማይክ ። ማይክል ስለጆርጅ እና ስለ ማሪዮን ሂልያርድ ግንኙነት በግልፅ ሲናገር ይህ የመጀመሪያው ነበር ። ስለዚህ ጆርጅ ይህን ሲሰማ አፈረ ። ፊቱ ቀላ ። ሆኖም የመከፋት ስሜት አልታየበትም።
«ማይክል!» አለች ማሪዮን ። ያ ይህን አድርግ ፤ ይህን አታድርግ የሚለው ድምጽዋ እየተመለሰ «ማይክል እስበህ ተናገር። ሌላው ቢቀር ጆርጅን እስበው ። እንዴት እንዳስደነገጥከው ይታይሀል ? ያም ተባለ ይህ ሥራ ለመተው አልደረስኩም ። አመመኝም ቀረም ለመሥራት ጉልበት አላነሰኝም»
«እሱ እንዳልሽው ይሁን ፤እሺ ልበል። ምንም ማድረግ ልችልም። ግን ሥራ ቀንሺ። ማለት ለምሳሌ በሚቀጥለው ሳምንት ሳንፍራንሲስኮ መሄድሽ አስፈላጊ አይደለም ። እኔ ልሄድና ጉዳዩን ልፈፅም እችላለሁ ። እዚህ እዋናው መሥሪያ ቤት ቁጭ ብለሽ ይህን ያን አድርጉ ብትይን ልንረዳሽ እንችላለን ። በቃ፣ይህን ያህል እሺ በይኝ» ሳቀች እንጂ ሌላ መልስ አልሰጠችውም ። ከዚያም ብድግ ብላ ወደ መደበኛ የቢሮ መቀመጫዋ ሄደችና ተቀመጠች ። ስጋዋ እንደደከመ ይታያል ። መንፈሷ ግን ወደ ዱሮ ቦታው ተመልሷል ። ሁሉንም ካየች በኋላ ፡፡ «አሁን በከንፈር መጠጣና በአዘንልሽ አትጫኑኝ ። ሁላችሁም ማለቴ ነው ። ሂዱልኝ ። እናንተ ሥራ ከሌላችሁ… እንዲያ ይመስለኛል ሳያችሁ… እኔ ሥራ አለብኝ ፤ ልሥራበት»
«እማዬ ፤ ቤት አድርሼሽ ልምጣ።እስኪ አንዳንድ ቀን ሰው የሚልሽን እሺ በይ !» አለ ማይክል ቆጣና ኮረፍ ብሎ። «ማይክል የማይቻል ነገር አታውራ ። አሁን ቀጥ ብለህ ወደ ሥራህ ሂድ። ያለዚያ ጆርጅን እየገፈተርክ አስወጣልኝ እንዳልለው» ጆርጅ ፈገግ አለ… የነገሩ መታሰብ አስገርሞት ። «ባይሆን ሰዓት ደረሰ አልደረሰ ሳልል ለመሄድ እሞክራለሁ እንጄ አሁን አይሆንም ። በተረፈ ስለመልካም አስተሳሰብህና ስለሌላው እመሰግናለሁ ። በቃ ። ሩት ያን በር ክፈች» ጸሐፊዋ በሩን ከፍታ እንዲወጡ መጠባበቅ ጀመረች ። ማይክልና ቤን ወጡ ። ጆርጅ እደረጃው ላይ ቆሞ ፤
«ማሪዮን» አለ።
«እሀ»
«ወደ ቤት መሄድ አለብሽኮ »
«ትንሽ ቆየት ብዬ»
«ደግ። ከግማሽ ሰዓት በኋላ እመለሳለሁ» ወጣ። ፈገግ አለች ። ሆኖም ወደራሷ ሀሳብ ስትመለስ ገና በሩ አልተዘጋም ።
የዛሬው ህመሟ የተነሳበት ምክንያት በሚገባ ታውቋታል ። ስለዚህ አንድ ነገር ማድረግ አለባት ። በሌላው ሌላ ምክንያት እየተነሳ እረፍት አሳጥቷታል ህመሙ። ሌላ መነሻ ሲጨመር ዝም ብላ ማየት አትችልም ። ለምን እንደሆነ አይግባት እንጂ ቤን አቭሪ ስለሜሪ አዳምሰን ሲናገር ሜሪ ማን እንደሆነች አውቃለች ። በርግጥ ናንሲ ማክአሊስተር ናት ብላለች ። ቅድም እስብሰባው ላይ በግልጥ እንደተናገረችው ወደ ሳንፍራንሲስኮ ስትሄድ ሜሪን ለማየትም ፤ ለማነጋገርም ወስናለች ። ግን ታውቃት ይሆን? ምናልባት የተደረገላት የቀዶ ጥገና ህክምና (ፕላስቲክ ሰርጀሪ) ፈጽሞ ለውጧት ሊሆን ይችላል ። ያስ ባይሆን ናንሲን በሚገባ ታስታውሳታለች እንዴ ? አይታወቅም ። ቤን አቭሪ የሰጣትን የሜሪ አዳምሰን አድራሻ አውጥታ ስልክ ደወለች። ስልኩ ሶስቴ ይሁን አራቴ ሲጮህ ተሰማት ። ተነሳ። ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት አቅሏን ስታ ወድቃ የነበረችው ማሪዮን ሂልያርድ መሆኗን ማንም ሊያምን በማይችልበት ደረጃ ረጋ ባለና ስልጣን በተሞላበት ድምጽ፤ «ሚስ አዳምሰን ። ማሪዮን ሂልያርድ ነኝ ፤ ከኒወዮርክ » ስትል ተናገረች ።
ንግግራቸው በጣም አጭር ፤ ተዝቃዛና በመደነጋገር የተሞላ ነበር። ማሪዮን ሂልያርድ ስለሜሪ አዳምሰን በተጨማሪ ያገኘችው እውቀትም አልነበረም ። ይሁን ። ልክ የዛሬ ሶስት ሳምንት ማወቅ የሚገባትን ሁሉ ታውታለች ። ሊገናኙ ተቀጣጥረዋል ። ማሪዮን ቀጠሮውን አጀንዳዋ ላይ ካሰፈረች በኋላ የወንበሯን መከዳ ደገፍ ብላ ወደ ኋላዋ ተለጠጠች ። አይኖቿን ዘጋች ።
ከሜሪ አዳምሰን ጋር ከተገናኙም በኋላ ምንም ጠቃሚ ነገር ላታገኝ ትችላለች ። ሁሉም እንዳሰበችው ላይሆን ይችላል ። ወይም ሜሪ ምንም ነገር ላለመናገር ትወስን ይሆናል... ሆናም ያን ቀን ትፈልገዋለች ። ልትናገራቸው ያውጠነጠነቻቸው ጥቂት ነገሮች አሉ ። ብቻ. . . ብቻ ከዚያ ወዲህ ክፉ ነገር እንዳያጋጥማት። ትልቁ ምኞቷ ይህ ብቻ ነው።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ሶስት ሣምንት ሲደርስ አጭር ጊዜ ነው፡፡ ሲያስቡት ይርዘም እንጂ፤ የማሪዮን ሂልያርድና የሜሪ አዳምሰን ቀጠሮ ደረሰ ከሶስት ሣምንት በኋላ እለተ ሰሉስ ።
ማሪዮን ሂልያርድ ፌይርሞንት በተባለው ሆቴል በተከራየችው የልዩ ማዕረግ ማረፊያዋ ሳሎን ውስጥ ተቀምጣለች ። እዚያ ክፍል ውስጥ አረፍ ብሎ ወደ ውጭ ለተመለከተ ሰው ደንቅ የሆነው ወደብና ከዚያ አልፎ የሚገኘው የማሪን ካውንቲ ውበት በእጅጉ ያስደምመዋል ። ከሌላ ሀሳብም ያወጣዋል ። ማሪዮን ሂልያርድ ግን ይህን ትእይንት ለማየት ፍላጐት አልነበራትም ። ስለዚያች ልጅ በማሰብ ላይ ነበረች ። ምን ሆና ይሆን? ምን ትመስል ይሆን? ግሬግሰን (ፒተር) ከሁለት ዓመት በፊት ታምር አሳይሻለሁ ብሎ አንደፎከረ ተሳክቶለት ታምር በርቶ ይሆን? ቤን አቭሪ ሜሪ አዳምሰንን ሲያያት የሚያውቃት ሴት እንዳልሆነችበት ግልፅ ነው… ማይክልም ቢያያት አያስታውሳትም ይሆን? እሷስ እንዴት ነው ይሆን የምትኖረው ? ከሌላ ወንድ ጋር ፍቅር ይዞአት ይሆን ወይስ እንደማይክል ሁሉን ነገር ትታ አንገቷን ደፍታ ውስጧ እየበገነ መኖር ቀጥላ ይሆን ? ማሪዮን ሂልያርድ የቀጠሮው ሰዓት እስኪደርስ ስለ ናንሲ ማክአሊስተር ስታስብ ልጅዋ በመሀል ገባ። እሱም ፍቅር ያውቅ ነበር ። አፍቅሮ ነበር ። እንዲያውም አሁን እምትጠብቀው ማይክል ሂልያርድ በጣም ይወዳት የነበረችዋን ልጅ ነው። ግን…. እሷ ባትሆንስ ? ካልሆነች . . . ካልሆነች ምንም ለውጥ አያመጣም። እሷ ካልሆነች አንዲት የዚሁ አካባቢ ተወላጅ የሆነች ፎቶ አንሺ ናት ማለት ነው ቤን አቭሪ አይኑን የጣለባት ፎቶግራፍ አንሺ። በቃ። ሊሆን ይችላል ። ያወጣሁት ያወረድኩት ፤ አስቤ የቀመርኩት ፤እውነት ብዬ ያሰብኩት ነገር ሁሉ መሰረተ ቢስ ፤ አጉል ሀሳብ ሊሆን ይችላል አለች በሀሳቧ።
ምናልባት. . . ምናልባት
👍17
ሲጋራ ለኮሰችና ቀና ብላ በግድግዳው ላይ የተሰቀለውን ሰዓት ተመለከተች ። አስር ከሩብ ፣ ከቀኑ ። ይህም ማለት ኒውዮርክ ውስጥ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ይሆናል ማለት ነው። ማይክል ገና ከሥራ አይወጣም ። ቤን አቭሪ ግን ከሥራ ወጥቶ ከዚያች እዲዛይን ክፍል ከምትሰራ ሴት ጋር ይላላስ ይሆናል ። ኮስታራ አደለም ባህሪው ፤እንደማይክል ። ግን. . . ግን እንደማይክል ትካዜ አያበዛም ። ማይክ ግን . . . በረጅሙ ተነፈሰች ። ምናልባት ያችን የወደዳትን ልጅ ስታርቅበት ሕይወቱን እስከ ዘለቄታ የሚያስረሣ ስህተት ፈፅማ ይሆን ፤ ማሪዮን ? የለም ፤ የለም ልጅነቱ ነው እንጂ ቢበስል እሱ ራሱ ያለአቻው ማግባትን አይሞክረውም ነበር ። አዎ እንደዚያ ነው ። ሆኖም የለም አልተሳሳተችም ። ምናልባትም አልትሳሳተች ይሆናል ። ምንአልባት። ሁሉም ነገር ጥቂት ማስቸገሩ አይቀርም ። ያ እስኪያልፍ ነው። ነገ ተነስቶ ምን የመሰለች ሚስት ሊያገኝ ይችላል፤ ያገኛል ። በባህሪዋ በመልኳ ፤ በዘሯ ፤ በአስተዳደጓ የምታኮራ። ምን ጎድሎበት ሚስት ያጣል ? ሀብት… ሞልቶ ተርፎ። ችሎታ ከሱ የተረፈ ነው። መልክ ይህ ጎደለህ አይባልም ። ጠባይ! ሲስቅ ሲጫወት ያምርበታል ። ቁም ነገር ሲያወራ ትርፍ ነገር አይጨምር!. ስለ ማይክል ስታስብ ፊቷ እየተፈታ ልቧ እየለሰለሰ ሄደ። ማይክል ምን አይነቱ ደግ ፤ ጠንካራና . .. ብቸኛ ሰው ነው! አዎ ብቸኛ ነው ። አደጋው ከደረሰበትና… አዎ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ከማንም ጋር መቀላቀል አልቻለም ። ምናልባትም እልቡ ውስቅያኖ የተሰበረ አንድ ነገር ቢኖር ይሆናል ። ያ ነገር ደግሞ እስከ ዛሬ ሊቀጥል ሊለመልም አልቻለም ማለት ነው ። ነፍስ አልዘራም ማለት ነው። አሁን አሁን ግን እየተሻለው ይመስላል ። በግልፅ መቆዘሙንና በየእለቱ ጠጥቶ መስከሩን አቁሟል ። ግን ምን ዋጋ አለው ደስታ የለውም ። ሁሉ ነገር አለው። ሲደሰት ፤ ሊጨፍር ይችላል ። ግን ደስታ ወደሚገኝበት ቦታ ፊቱን እንኳ አያዞርም ። በፊቱ ላይ የሚታየው ሌላ ነገር ነው፡፡ ስለመኖር የሚያስብ አይመስልም ። ወይም ይህን ጨርሼ እዚህ እደርሳለሁ ብሎ ወስኖ በድንገት እኮ ለምን ፤ ምን ለማግኘት እንዳለ ፤ ጭልጥ ባለ በረሀ ላይ እንደሚጓዝ መንገደኛ ተስፋው ባዶና አላማ የለሽ ይመስላል ። አይኑ ላይ ተስሎ እምታየው ይህን ነው ። ለምንም ነገር ፍቅር የለውም ። ለሥራው እንኳ ፍቅር የለውም። በሥራው ላይ ተደፍቶ ይውላል ። ብዙ ይሰራል ። እንከን የለበትም ።ግን ማይክል ሥራውን የሚወደው ማሪዮን ሥራዋን በምትወድበት መንገድ አይደለም ። አባቱ አያቱ ያን ሥራ በሚወዱበት መንገድም አይደለም ።
የማይክል አባት ትዝ ሲላት በፍቅር አስታወሰችው ። እንዴት አይነት ግሩም ሰው ነበር ። ሃሳቧ ወደ ጆርጅ ተሻገረ። ጆርጅን ባይጥልላት ምን ይውጣት፡፡ ሃላፊነት ሲከብዳት የሃላፊነቱን እንዛዝላ የሚሸከምላት ፤ ስታዝን የሚያፅናናት ፤ ሲከፋት የሚያስደስታት. . . ጆርጅ ለሷ ሁሱ ነገር ነው ። ያም ሆኖ ይህን ያሀል መሆኑን አታውቅም ነበር ። አሥራ ሁለት አመት ያህል ጆርጅ ያገልግላት ፤ ይታዘዛት ፤ በትህትናው ይደግፋት እንጂ ማሪዮን ጆርጅን አስባው እንኳ አታውቅም ነበር ። ምን ነክቷት ይሆን? ምክንያቱም ግልጽ ነው። ያን ያሀል ጊዜ ልቧ ለማንም ወንድ ቦታ አልነበረውም ። ያለ ማይክል አባት ለሷ ወንድ አልነበረም ፤ አለፈ።
የበሩ ደወል ተንጫረረ ። ከሀሳቧ ቀሰቀሳት ። ሰዓቱ አስር ሰዓት ከሃያ አምስት ደቂቃ ይላል ። ልጅቷ መሆን አለባት ። ሃያ አምስት ደቂቃ አሳልፋ ነው ማለት ነው የመጣችው ግን ማሪዮን አልተናደደችም ። ቶሎ ብትመጣባት ኖሮ ይህን ሁሉ ለማሰብ ትችል ነበርን ?
«ሚስ እዳምሰን ? » ስትል ። ያየቻት ልጅ ከዚያችኛዋ ፈፅማ የተለየች ሆና አገኘቻች ። ድንገት ደስ ሲላት ተሰማት ። «ሚስዝ ሂልያርድ?» አለች ሜሪ ። ትጠይቃት እንጂ በሚገባ አውቃታለች ። በርግጥ በአይኗ አይታት አታውቅም ። እሆስፒታሉ ውስጥ ስታነጋግራትም አይኗ በፋሻ ተጠቅልሎ ነበር፤ አላየቻትም ። ግን ፎቶግራፉዋን አይታለች… እማይክል ቤት ። ከዚያ ወዲህም ሺ ጊዜ በህልሟ እየመጣች አስፈራርታታለች ። ማሪዮን ሂልያርድ ለሜሪ አዳምሰን ቅዠት ነች ። አለም ዳርቻ ብታገኛትም አታጣትም ። «እንደምን አለሽ?» አለች ማሪዮን ፤ እጅዋን ለሰላምታ እየዘረጋች ። እንደሚሆን እንደሚሆነው ሰላምታ ተለዋወጡ ። «ወደ ውስጥ እንግባ» አለች ማሪዮን ። «እሺ አመሰግናለሁ» አለች ሜሪ ።
ሜሪ በሕይወቷ ብዙ ለውጥ ያመጣችውንና በአይነ ስጋ አይታት የማታውቀውን አዲስ ሰው ያደረገቻትን ሴትዮ ሁኔታ ለመገንዘብ ፤ ሁለቱም በየመንገዳቸው ፤ አንዳቸው የሌላውን ልብ ዘልቆ ለመመልከት ይጠናኑ ጀመር። ማሪዮን ይህች የምታያት ሴት ከዚያች በፎቶግራፍ ከምታውቃት ናንሲ ጋር ምንም አይነት የመልክ መመሳሰል እንደሌላት ተገነዘበች ። ለስላሳ መጠጦችንና ሻይ ልትጋብዛት ስትዘጋጅ ሁሉ ያን ያህል ገንዘብ ላወጣችላት ሰው ተጨማሪ ግብዣ ማድረጉ አስፈላጊ እንዳልሆነ ለልቧ ነገረችው ። ቢሆንም መነጋገር ያስፈልጋል ። መልኳ ቢለወጥ ድምጽዋ ቶኑ አይለወጥም ። ያንን የመጨረሻውን እለት ስቃይ የተሞላ የናንሲ ማክአሊስተር ድምፅ እንዲህ በቀላሉ አትረሳውም ።
«ምን ትጠጫያለሽ» አለች ማሪዮን ። «ስለግብዣው እግዜር ይስጥልኝ ። ግን ደግሞ... ምንም ነገር» አለችና አቋረጠች ። ሴትየዋ ትኩር ብላ ስታያት ፤ ሜሪም ሴትዮዋን ትኩር ብላ ስታይያት የተፈጠረው የአይን ግጭት ንግግሯን እንድታቋርጥ አስገደዳት ። ማሪዮን የልጅቷን ውበት ፤ የለበሰችውን ልብስ ውድነት እየተመለከተች ለሕይወቷ ያሰፈልጋል ተብሎ የቆረጥኩላትን ገንዘብ በልብስ ብቻ እያባከነችው ይሆን ? ስትል አሰበች ። የልብሶችዋን ዉድ መሆን ፤ ለሳንፍራንሲስኮ የአየር ጠባይ የለበሰችው ካፖርት በጣም ሞቃት ሊሆን እንደሚችልና ኒውዮርክን ታውቅ እንደሆነ ደራርባ ጠየቀቻት ። ጥያቄው ቢበዛባትም ፤ ሜሪ የመጨረሻውን ጥያቄ ለመመለስ አሰበች ። እውነተኛውን ነገር ብትነግራት በወደደች ። ሆኖም አያስፈልግም ። ስለዚህም ፤ «ኒውዮርክን ብዙም አላውቀው። እንዲያውም ትልቅ ከተማ ኗሪ አይደለሁም » አለች ሜሪ። «እኔ ሳይሽ ደሞ ትልቅ ከተማ ያንች ግዛት ሆኖ ነው የተሰማኝ» አለች ማሪዮን ።
የማይክል አባት ትዝ ሲላት በፍቅር አስታወሰችው ። እንዴት አይነት ግሩም ሰው ነበር ። ሃሳቧ ወደ ጆርጅ ተሻገረ። ጆርጅን ባይጥልላት ምን ይውጣት፡፡ ሃላፊነት ሲከብዳት የሃላፊነቱን እንዛዝላ የሚሸከምላት ፤ ስታዝን የሚያፅናናት ፤ ሲከፋት የሚያስደስታት. . . ጆርጅ ለሷ ሁሱ ነገር ነው ። ያም ሆኖ ይህን ያሀል መሆኑን አታውቅም ነበር ። አሥራ ሁለት አመት ያህል ጆርጅ ያገልግላት ፤ ይታዘዛት ፤ በትህትናው ይደግፋት እንጂ ማሪዮን ጆርጅን አስባው እንኳ አታውቅም ነበር ። ምን ነክቷት ይሆን? ምክንያቱም ግልጽ ነው። ያን ያሀል ጊዜ ልቧ ለማንም ወንድ ቦታ አልነበረውም ። ያለ ማይክል አባት ለሷ ወንድ አልነበረም ፤ አለፈ።
የበሩ ደወል ተንጫረረ ። ከሀሳቧ ቀሰቀሳት ። ሰዓቱ አስር ሰዓት ከሃያ አምስት ደቂቃ ይላል ። ልጅቷ መሆን አለባት ። ሃያ አምስት ደቂቃ አሳልፋ ነው ማለት ነው የመጣችው ግን ማሪዮን አልተናደደችም ። ቶሎ ብትመጣባት ኖሮ ይህን ሁሉ ለማሰብ ትችል ነበርን ?
«ሚስ እዳምሰን ? » ስትል ። ያየቻት ልጅ ከዚያችኛዋ ፈፅማ የተለየች ሆና አገኘቻች ። ድንገት ደስ ሲላት ተሰማት ። «ሚስዝ ሂልያርድ?» አለች ሜሪ ። ትጠይቃት እንጂ በሚገባ አውቃታለች ። በርግጥ በአይኗ አይታት አታውቅም ። እሆስፒታሉ ውስጥ ስታነጋግራትም አይኗ በፋሻ ተጠቅልሎ ነበር፤ አላየቻትም ። ግን ፎቶግራፉዋን አይታለች… እማይክል ቤት ። ከዚያ ወዲህም ሺ ጊዜ በህልሟ እየመጣች አስፈራርታታለች ። ማሪዮን ሂልያርድ ለሜሪ አዳምሰን ቅዠት ነች ። አለም ዳርቻ ብታገኛትም አታጣትም ። «እንደምን አለሽ?» አለች ማሪዮን ፤ እጅዋን ለሰላምታ እየዘረጋች ። እንደሚሆን እንደሚሆነው ሰላምታ ተለዋወጡ ። «ወደ ውስጥ እንግባ» አለች ማሪዮን ። «እሺ አመሰግናለሁ» አለች ሜሪ ።
ሜሪ በሕይወቷ ብዙ ለውጥ ያመጣችውንና በአይነ ስጋ አይታት የማታውቀውን አዲስ ሰው ያደረገቻትን ሴትዮ ሁኔታ ለመገንዘብ ፤ ሁለቱም በየመንገዳቸው ፤ አንዳቸው የሌላውን ልብ ዘልቆ ለመመልከት ይጠናኑ ጀመር። ማሪዮን ይህች የምታያት ሴት ከዚያች በፎቶግራፍ ከምታውቃት ናንሲ ጋር ምንም አይነት የመልክ መመሳሰል እንደሌላት ተገነዘበች ። ለስላሳ መጠጦችንና ሻይ ልትጋብዛት ስትዘጋጅ ሁሉ ያን ያህል ገንዘብ ላወጣችላት ሰው ተጨማሪ ግብዣ ማድረጉ አስፈላጊ እንዳልሆነ ለልቧ ነገረችው ። ቢሆንም መነጋገር ያስፈልጋል ። መልኳ ቢለወጥ ድምጽዋ ቶኑ አይለወጥም ። ያንን የመጨረሻውን እለት ስቃይ የተሞላ የናንሲ ማክአሊስተር ድምፅ እንዲህ በቀላሉ አትረሳውም ።
«ምን ትጠጫያለሽ» አለች ማሪዮን ። «ስለግብዣው እግዜር ይስጥልኝ ። ግን ደግሞ... ምንም ነገር» አለችና አቋረጠች ። ሴትየዋ ትኩር ብላ ስታያት ፤ ሜሪም ሴትዮዋን ትኩር ብላ ስታይያት የተፈጠረው የአይን ግጭት ንግግሯን እንድታቋርጥ አስገደዳት ። ማሪዮን የልጅቷን ውበት ፤ የለበሰችውን ልብስ ውድነት እየተመለከተች ለሕይወቷ ያሰፈልጋል ተብሎ የቆረጥኩላትን ገንዘብ በልብስ ብቻ እያባከነችው ይሆን ? ስትል አሰበች ። የልብሶችዋን ዉድ መሆን ፤ ለሳንፍራንሲስኮ የአየር ጠባይ የለበሰችው ካፖርት በጣም ሞቃት ሊሆን እንደሚችልና ኒውዮርክን ታውቅ እንደሆነ ደራርባ ጠየቀቻት ። ጥያቄው ቢበዛባትም ፤ ሜሪ የመጨረሻውን ጥያቄ ለመመለስ አሰበች ። እውነተኛውን ነገር ብትነግራት በወደደች ። ሆኖም አያስፈልግም ። ስለዚህም ፤ «ኒውዮርክን ብዙም አላውቀው። እንዲያውም ትልቅ ከተማ ኗሪ አይደለሁም » አለች ሜሪ። «እኔ ሳይሽ ደሞ ትልቅ ከተማ ያንች ግዛት ሆኖ ነው የተሰማኝ» አለች ማሪዮን ።
👍11
በዚህ ሁኔታ ብዙ ተነጋገሩ ። ቀስ እያሉ ፤ እያዘገሙ ። ከብዙ ማዝገም በኋላ ማሪዮን ንግግራቸውን ወደፈሩ መምራት ጀመረች ። «ቤን አቫሪ ኮንትራት ሊሰጥሽ የፈለገው በከንቱ እንዳልሆነ ገባኝ። ይህ እጅግ ውብ የሆነ የጥበብ ሥራ ነው። በዚህ ሥራ ላይ ብዙ ቆይተሽበታል!?» አለች ማሪዮን ፤ አስቀድመው በተነጋገሩት መሰረት ናንሲ መርጣ ያመጣቻቸውን ፎቶግራፎች እየተመለከተች ። «የፎቶ ግራፍ ሥራ ለኔ እንግዳ ነው ። ከዚሀ በፊት ሰአሊ ነበርኩ »
«አዎ፤ አሁን ትዝ አለኝ። ቤን አቭሪ ነግሮኝ ነበር ። ›› ማሪዮን ይህን ብላ ፎቶግራፎቹን ትመለከት ጀመር ። ለረጂም ጊዜ በፎቶግራፎቹ ውበት ተውጣ ቆየች ። ከዚያም አይኗን ሳትነቅል «ስዕል ስትስይም ይህን ያህል ይዋጣልሻል.› ስትል ጠየቀች። «ይዋጣልኝ ነበር ይመስለኛል ። » ማሪዮንና እሷ ድብብቆሽ የሚጫወቱ መስሎ ተሰማት ። «ዛሬ ዛሬ የፎቶግራፍን ሥራ ፤ ያኔ የስዕልን ሥራ የምወደውን ያህል እየወደድኩት ነው»
«ሙያሽን ለምን ቀየርሽ?»
«ምክንያቱም ተለወጥኩ። ሁሉ ነገሬ አዲስ ሆነ ። የስዕል ሥራ የዚያ ያለፈው ህይወቴ አካል ነበር ። ብቀጥለው ሁሌ ያን ሕይወት ያስታውሰኛል ። ስቃይ እንጂ ሌላ ትርፍ እንደሌለው ተገነዘብኩ ። ተውኩትና የፎቶግራፍ ሥራ ጀመርኩ ። አዲስ ሕይወት አዲስ ሰው አዲስ ሙያ... እንደዚያ ነው»
« እህ ?እንዲያ ነው? ... የሆነው ሆኖ አለም ያችን የመሰለች ሰዓሊ አሕሁ ልትል አይገባትም ። ፎቶ ግራፎችሽን እንደማያቸው ክሆነ በሷ በኩል እያገስገልሻት ነው። ማነው ይህን ሥራ እንድትጀምሪ ያበረታታሽ። ይኸኔ አንዱ ታላቅ ጠቢብ ይሆናል! መቼም ሳንፍራንሲስኮ ብዙ የጥበብ ሰው አለባት»
ሜሪ ራሷን ነቀነቀች ፤ ፈገግ ብላ ። ሁሉም ነገር አስገራሚ ነው። ማሪዮን ሂልያርድን እጅግ ለመጥላት ተዘጋጅታ ፤ ታጥቃ ነበር ከቤቷ የወጣችው ። ግን አልቻለችም ። አልወደደቻትም ግን አልጠላቻትም ። አዘነችላት? እንጂ ሴትዮዋ ምንም ልትኩራራ ብትፈልግ ረጋ ማለት ብትሻ ፤ ዘመናይ ለመምሰል ብትሞክር ውስጧ ተመርዞአል ። ሞት ሲያንዣብባት ይታያል ። ይህን ሁሉ ስሜት የለበሰውን ፊት በደንብ ሲመለከቱት ፤የእርጅና መዳረስን ለመረዳት ከሱ በሚመነጨው ኀዘን ሲሰቃይ ይታያል ። ሁሉን ዘልቆ መመልከት ለቻለ ። ምንድን ነበር ጥያቄው፤ ፎቶግራፍ ማንሳት እንድትጀምሪ ያበረታታሽ ማነው ? በሳንፍራንሲስኮ ከሚገኙት ባለሙያዎች አንዱ!?... አዎ ፤ ይህን ነበር የጠየቀችኝ ። ‹‹ባለሙያ ንኳ አይደለም ። ማለት የፎቶግራፍ ሥራ አይደለም ። አንድ ወዳጄ ነው። የግል ሀኪሜ ነው ማለቱ ይበልጥ ግልፅ ያደርገዋል ነገሩን ። እሱ ነው ያስተዋወቀኝ። በዚች ከተማ ውስጥ የማያውቀው ሰው የለም »
«ፒተር ግሬሰን» አለች ማሪዮን በለሆሳስ ። ማሪዮን የራሷን ድምፅ የሰማችው እንደ ህልም ነበር ። ልትናገር አላስበችም እንዲያ ብላ ። ሜሪ ይህን ስትለማ ደነገጠች።. . . ማን ነገራት ? እንዴት ልታውቅ ቻለች ? ምናልባት ፒተር?.... የለም እሱ አያደርገውም
«ትተዋወቃላችሁ ? » አለች ሜሪ ።
«ምን… ከኔ ጋር ? አዎ» አለች ማሪዮን ። ሁለቱም ፀጥ አሉ፣ ረጂም ለመሰለ ጊዜ ። በመጨረሻ «እንተዋወቃለን ናንሲ ። ፒተርን አውቀዋለሁ ። ላንች ያደረገልሽ ህክምናም እጅግ የሚደነቅ ነው» አለች ማሪዮን ።
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
«አዎ፤ አሁን ትዝ አለኝ። ቤን አቭሪ ነግሮኝ ነበር ። ›› ማሪዮን ይህን ብላ ፎቶግራፎቹን ትመለከት ጀመር ። ለረጂም ጊዜ በፎቶግራፎቹ ውበት ተውጣ ቆየች ። ከዚያም አይኗን ሳትነቅል «ስዕል ስትስይም ይህን ያህል ይዋጣልሻል.› ስትል ጠየቀች። «ይዋጣልኝ ነበር ይመስለኛል ። » ማሪዮንና እሷ ድብብቆሽ የሚጫወቱ መስሎ ተሰማት ። «ዛሬ ዛሬ የፎቶግራፍን ሥራ ፤ ያኔ የስዕልን ሥራ የምወደውን ያህል እየወደድኩት ነው»
«ሙያሽን ለምን ቀየርሽ?»
«ምክንያቱም ተለወጥኩ። ሁሉ ነገሬ አዲስ ሆነ ። የስዕል ሥራ የዚያ ያለፈው ህይወቴ አካል ነበር ። ብቀጥለው ሁሌ ያን ሕይወት ያስታውሰኛል ። ስቃይ እንጂ ሌላ ትርፍ እንደሌለው ተገነዘብኩ ። ተውኩትና የፎቶግራፍ ሥራ ጀመርኩ ። አዲስ ሕይወት አዲስ ሰው አዲስ ሙያ... እንደዚያ ነው»
« እህ ?እንዲያ ነው? ... የሆነው ሆኖ አለም ያችን የመሰለች ሰዓሊ አሕሁ ልትል አይገባትም ። ፎቶ ግራፎችሽን እንደማያቸው ክሆነ በሷ በኩል እያገስገልሻት ነው። ማነው ይህን ሥራ እንድትጀምሪ ያበረታታሽ። ይኸኔ አንዱ ታላቅ ጠቢብ ይሆናል! መቼም ሳንፍራንሲስኮ ብዙ የጥበብ ሰው አለባት»
ሜሪ ራሷን ነቀነቀች ፤ ፈገግ ብላ ። ሁሉም ነገር አስገራሚ ነው። ማሪዮን ሂልያርድን እጅግ ለመጥላት ተዘጋጅታ ፤ ታጥቃ ነበር ከቤቷ የወጣችው ። ግን አልቻለችም ። አልወደደቻትም ግን አልጠላቻትም ። አዘነችላት? እንጂ ሴትዮዋ ምንም ልትኩራራ ብትፈልግ ረጋ ማለት ብትሻ ፤ ዘመናይ ለመምሰል ብትሞክር ውስጧ ተመርዞአል ። ሞት ሲያንዣብባት ይታያል ። ይህን ሁሉ ስሜት የለበሰውን ፊት በደንብ ሲመለከቱት ፤የእርጅና መዳረስን ለመረዳት ከሱ በሚመነጨው ኀዘን ሲሰቃይ ይታያል ። ሁሉን ዘልቆ መመልከት ለቻለ ። ምንድን ነበር ጥያቄው፤ ፎቶግራፍ ማንሳት እንድትጀምሪ ያበረታታሽ ማነው ? በሳንፍራንሲስኮ ከሚገኙት ባለሙያዎች አንዱ!?... አዎ ፤ ይህን ነበር የጠየቀችኝ ። ‹‹ባለሙያ ንኳ አይደለም ። ማለት የፎቶግራፍ ሥራ አይደለም ። አንድ ወዳጄ ነው። የግል ሀኪሜ ነው ማለቱ ይበልጥ ግልፅ ያደርገዋል ነገሩን ። እሱ ነው ያስተዋወቀኝ። በዚች ከተማ ውስጥ የማያውቀው ሰው የለም »
«ፒተር ግሬሰን» አለች ማሪዮን በለሆሳስ ። ማሪዮን የራሷን ድምፅ የሰማችው እንደ ህልም ነበር ። ልትናገር አላስበችም እንዲያ ብላ ። ሜሪ ይህን ስትለማ ደነገጠች።. . . ማን ነገራት ? እንዴት ልታውቅ ቻለች ? ምናልባት ፒተር?.... የለም እሱ አያደርገውም
«ትተዋወቃላችሁ ? » አለች ሜሪ ።
«ምን… ከኔ ጋር ? አዎ» አለች ማሪዮን ። ሁለቱም ፀጥ አሉ፣ ረጂም ለመሰለ ጊዜ ። በመጨረሻ «እንተዋወቃለን ናንሲ ። ፒተርን አውቀዋለሁ ። ላንች ያደረገልሽ ህክምናም እጅግ የሚደነቅ ነው» አለች ማሪዮን ።
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍23❤4🔥1👏1
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ናንሲ ሌኔሃን ከማታውቀው ሰው ጋር አንድ ክፍል ውስጥ መተኛቷ
ሰላም ሳይነሳት አልቀረም:
ምንም እንኳን ክፍሉ የሙሽሮች ክፍል ቢሆንም አልጋዎቹ ተደራራቢ ናቸው፡፡ በሩ ክፍት እንዲሆን ቢፈልጉም በወጀቡ ምክንያት በሩ እየተወረወረ
ይዘጋል፡፡ ስለዚህ አስሬ ሲዘጋ እየተነሱ ከመክፈት ይልቅ አንድ ጊዜ ዘግቶ
መተዉ የሰውን ትኩረት አይስብም:፡
ናንሲ በጊዜ ላለመተኛት ብዙ ጥራለች። በዋናው ሳሎን ሄዳ ለመቀመጥ
ብትፈልግም ወንዶች ብቻ ናቸው የተሰባሰቡት፡፡ ቦታው በሲጋራ ጭስ ታፍኗል፧ በዊስኪ ሽታ ታውዷል፡ በተጨማሪም የካርታ ተጫዋቾች ስድብና
ጫጫታ ጆሮ ይሰነጥቃል፤ ቦታው ለሴት ልጅ የሚሆን አይደለም፤ ስለዚህ
‹መተኛት ሳይሻል አይቀርም› ብላ ወደ መኝታ ክፍሏ ሄደች።
ስለዚህ መርቪንና ናንሲ መብራቱን አጠፉና በየአልጋቸው ላይ ሰፈሩ።
ናንሲ ዓይኖቿን ብትጨፍንም እንቅልፍ በአይኗ hልዞር አለ፡፡ ወጣቱ ሄሪ ማርክስ ያመጣላት አንድ መለኪያ ዊስኪ እንኳን ለመተኛት የረዳት ነገር
የለም፡ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ቢሆንም በዓይኗ እንቅልፍ አልኳል ብሏል፡
መርቪንም እንቅልፍ እንዳልያዘው አውቃለች፡ የላይኛው ቆጥ ላይ
ሰፍሮ ይገላበጣል፡፡ እንደ ሌሎች መኝታዎች የሙሽሮቹ አልጋዎች በመጋረጃ የተሸፈኑ ባለመሆናቸው ላለመታየት ያላት ምርጫ መብራቱን ማጥፋት ነው፡፡
እንቅልፍ አልመጣላት ሲል ማርጋሬት ኦክሰንፎርድ በሀሳቧ መጣች ማርጋሬት በጣም ወጣት፣ የኑሮ ውጣ ውረድ የማይገባትና ወደፊት
ስለሚገጥማት ነገር ቅንጣት ታህል የማታውቅ ልጅ ናት። ከማርጋሬት
በጥርጣሬ የተሞላ ፊት ላይ ያነበበችው ግን ከፍተኛ ነፃ የመሆን ስሜት ነው፡፡ ይህ ደግሞ እሷ ወጣት በነበረችበት ጊዜ የገጠማት አይነት ችግር ነው፡፡ ናንሲም በዚያ ወቅት ከወላጆቿ ጋር አተካራ ውስጥ ገብታ ነበር፧
በተለይ ከእናቷ ጋር፡ እናቷ የተከበረ የቦስተን ቤተሰብ ልጅ እንድታገባ
ብትፈልግም እሷ ግን ገና አስራ ስድስት አመት ሲሞላት ሾን ሌኔሃን
ከሚባል የህክምና ትምህርት ከተማረ ከአባቷ ፋብሪካ ውስጥ ከሚሰራ ካቦ ልጅ ጋር ፍቅር ጀመረች፡፡ እናትዬው ናንሲ ይህን ልጅ እንዳታገባው ልጁ ከሌሎች ሴቶች ጋር እንደሚማግጥ፣ እናት አባቱን ከፍ ዝቅ እያደረገ
እንደሚሳደብና በየጊዜው እንደሚያመው ሀሜት ብታስወራም ናንሲ ግን
የሚነዛውን ሀሜት እንዳልሰማች በማሳለፍ ሾንን አግብታ እስከ ዕለተ ሞቷ ድረስ አብራው ኖራለች፡፡
ማርጋሬት የእሷን ያህል ጥንካሬ ያላት ልጅ አትመስልም፡፡ ከአባቷ ጋር
ካልተስማማች ከቤታቸው መውጣት ትችላለች፡፡ ይቺ ልጅ በየጊዜው ችግር
እያነሳች እንዳታላዝንና ራሷን ለመቻል እንድትጥር የሚመክራት ሰው ያስፈልጋታል፡ እኔ በእሷ እድሜ የሁለት ህጻናት እናት ነበርኩ› አለች በሃሳቧ፡
ስለዚህ ማርጋሬት ራሷን እንድትችል ጠበቅ ያለ ምክር ለግሳታለች እሷም ቃሏን በመጠበቅ ስራ ልትሰጣት ተስፋ አድርጋለች፡፡
ይሄ ሁሉ ደግሞ የሚወሰነው ከወንድሟ ጋር ባላት ጠብ የሀይል
ሚዛኑን በጨበጠው በአጭበርባሪው ሽማግሌ በዳኒ ሪሌይ ነው፡፡ ናንሲ
እንደገና ወደ ጭንቀቷ ተመለሰች፡፡ ጠበቃዋ ማክ ዳኒ ሪሌይን ይኸኔ
አግኝቶት ይሆን? ከአገኘውስ ስለቀድሞው ወንጀሉ ሲነግረው ምን አለ? ይህ ሁሉ ሴራ እሱ ላይ ግፊት ለማድረግ የተጠነሰሰ መሆኑን ጠርጥሮ ይሆን?›
እነዚህን ገና ምላሽ ያላገኙ ጥያቄዎች ስታወጣ ስታወርድ እንቅልፍ አጥታ
አልጋዋ ላይ ትገላበጣለች፡፡
የሚቀጥለው የአይሮፕላኑ ማረፊያ ቦትውድ ከተማ ነው፡፡ ኒውፋውንድ ስትደርስ ማክጋ ስልክ ደውላ ታረጋግጣለች፡፡በዚያ ጊዜ ሁሉ ነገር ይለይለታል፡
አይሮፕላኑ ሲንዘፈዘፍና ሲንገጫገጭ ናንሲ መላ አካልዋ ተረበሸ፡፡አሁን ደግሞ ብሶበታል፡ በአይሮፕላን በተደጋጋሚ ብትሄድም ከዚህ ቀደም
እንዲህ አይነት ሁኔታ ገጥሟት አያውቅም፡፡ ግዙፉ አይሮፕላን በንፋሱና
በወጀቡ ሲወዛወዝ ስጋት ገብቷት ተወርውራ እንዳትወድቅ የአልጋውን ብረት አጥብቃ ያዘች፡፡ ባሏ ከሞተ ወዲህ ብዙ ችግር ገጥሟታል፤ ‹አሁን ጉልበቴ
በርታ በርታ› ማለት አለበት፤ ነገር ግን የአይሮፕላኑ መንዘፍዘፍ ክንፎቹን
ይገነጥል፣ ሞተሩን ሰብሮ ይጥለው ይሆን?› እያለች መፍራቷ አልቀረም፡፡
ፍርሃቷን ይቋቋምላት ይመስል ትራሷን በጥርሷ ነክሳ ያዘች፡፡ ድንገት
አይሮፕላኑ ቁልቁል ወረደ፡፡ ቁልቁል መውረዱ እንዲቆም በእጅጉ ብትመኝም
መውረዱን ቀጥሏል፡ ይህ ሁኔታ ክፉኛ አስደነገጣት፡፡ ከዚያም ዘጭ አለና
ቀጥ ብሎ መብረር ጀመረ፡
መርቪን እጁን ሰዶ ትከሻዋን ያዝ አደረገና ‹‹ንፋሱ የፈጠረው ወጀብ ነው አይሮፕላኑን እንዲህ የሚያደርገው›› አለ ‹‹ከዚህ የባሰ ሁኔታ እኔ ብዙ
ገጥሞኛል፤ አይዞሽ አትፍሪ›› ሲል አጽናናት፡፡
እጁን በእጇ ፈልጋ አጥብቃ ያዝ አደረገችው፡፡ ከአልጋው ወረደና እሷ አልጋ ጫፍ ላይ ቁጭ ብሎ ፀጉሯን ይደባብስ ገባ፡፡ አሁንም ፍርሃቷ ሙሉ በሙሉ ባይለቃትም አይሮፕላኑ ሲወዛወዝ መርቪን ያዝ ስላደረጋት በመጠኑ
ቀለል አላት፡፡
ምን ያህል ጊዜ እንደተያያዙ አላወቀችም:: ትንሽ ቆይቶ ወጀቡ ተነሳ፡፡በደምብ ስትረጋጋ የመርቪንን እጅ
ለቀቅ አደረገችው፡፡ ምን ማለት እንዳለባት አላወቀችም።
ናንሲ መብራቱን አበራችና ከአልጋዋ ውስጥ ወጣች፡፡ ከላይ የሆነ ልብስ ደረብ አደረገችና መስታወቱ ፊት ቁጭ አለች፡፡ ሁልጊዜም
ጭንቀት ሲይዛት እንደምታደርገው ፀጉሯን አበጠረች፡፡ በጭንቀቷ ጊዜ የመርቪንን እጅ መያዟ አሳፈራት፡ በዚያ ጊዜ ክብሯን ሸጣ እጁን ለጥቂት ጊዜ በመያዟ በሆዷ
ብታመሰግነውም አሁን ፍርሃቷ ሲለቃት ግን ነገሩ አስፈራት፡፡ እሱም ስሜቷን በመረዳት እፍረቷ እንዲለቃት ብሎ ለጊዜው ክፍሉን ለቆላት ወጣ፡፡
መርቪን ትንሽ ቆይቶ ጠርሙስ ብራንዲ ከሁለት መለኪያ ጋር አመጣና
መጠጡን ቀድቶ አንዱን ሰጣት፡፡ አይሮፕላኑ ትንሽ ይወዛወዝ ስለነበር
በአንድ እጇ መለኪያውን በሌላ እጇ ደግሞ የአልጋውን ብረት ይዛለች:
የለበሰው አስቂኝ ልብስ ባያስቃት ኖሮ ድንጋጤው ቶሎ አይለቃትም አስቂኝ ቢሆንም ልክ ሱፍ ለብሶ
እንደሚንጎራደድ ሁሉ ምንም አልመሰለውም፡፡ ሰው ሞኝ ነው ቢለው ግድ
የለውም፡፡ ልበ ሙሉነቱ አስደስቷታል፡፡
ብራንዲዋን ስትጨልጥ በሰራ አካላቷ ሙቀት ስለፈጠረላት ደጋግማ
ተጎነጨች፡፡
መርቪን ወሬ ለመጀመር ብሎ ‹‹እዚያ መታጠቢያ ክፍል ውስጥ የሆነ
እንግዳ ነገር አየሁ›› አለ ‹‹እኔ ወደ መታጠቢያ ክፍል ስገባ አንድ በድንጋጤ
ቀልቡ የተገፈፈ ተሳፋሪ ሲወጣ አየሁ፡፡ የመታጠቢያ ክፍሉ መስኮት ተሰብሯል የበረራ መሀንዲሱ ደግሞ ጥፋት ሲፈጸም የተያዘ ሰው መስሎ እዚያ ቆሟል፡፡ መስኮቱ የተሰበረው ከአይሮፕላኑ ውጭ ተወርውሮ በገባ
የበረዶ ቋጥኝ መሆኑን ሊታመን የማይችል ታሪክ ነገረኝ፡፡ እኔ ግን ሁለ±
ሲደባደቡ እንደነበር መገመት አላቃተኝም፡፡››
ናንሲ እዚያ እጅ ለእጅ ተያይዘው ከሚቀመጡ ታሪክ ስለነገራት በሆዷ
መርቪንን አመሰገነችው፡፡ ‹‹የትኛው የበረራ መሀንዲስ?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹እንደ እኔ ቁመቱ ሎጋ የሆነና ፀጉሩ ቃጫ የመሰለ መልከ መልካም ወጣት››
‹‹መሀንዲሱን አወቅሁት፤ ተሳፋሪውስ ማን ነው?››
‹‹ስሙን አላውቀውም፤ ነጋዴ ይመስላል፤ አመድማ ሱፍ ልብስ የለበሰው ሰውዬ ነው›› አለና መርቪን ተነስቶ ብራንዲ ብርጭቆዋ ውስጥ
ጨመረላት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ናንሲ ሌኔሃን ከማታውቀው ሰው ጋር አንድ ክፍል ውስጥ መተኛቷ
ሰላም ሳይነሳት አልቀረም:
ምንም እንኳን ክፍሉ የሙሽሮች ክፍል ቢሆንም አልጋዎቹ ተደራራቢ ናቸው፡፡ በሩ ክፍት እንዲሆን ቢፈልጉም በወጀቡ ምክንያት በሩ እየተወረወረ
ይዘጋል፡፡ ስለዚህ አስሬ ሲዘጋ እየተነሱ ከመክፈት ይልቅ አንድ ጊዜ ዘግቶ
መተዉ የሰውን ትኩረት አይስብም:፡
ናንሲ በጊዜ ላለመተኛት ብዙ ጥራለች። በዋናው ሳሎን ሄዳ ለመቀመጥ
ብትፈልግም ወንዶች ብቻ ናቸው የተሰባሰቡት፡፡ ቦታው በሲጋራ ጭስ ታፍኗል፧ በዊስኪ ሽታ ታውዷል፡ በተጨማሪም የካርታ ተጫዋቾች ስድብና
ጫጫታ ጆሮ ይሰነጥቃል፤ ቦታው ለሴት ልጅ የሚሆን አይደለም፤ ስለዚህ
‹መተኛት ሳይሻል አይቀርም› ብላ ወደ መኝታ ክፍሏ ሄደች።
ስለዚህ መርቪንና ናንሲ መብራቱን አጠፉና በየአልጋቸው ላይ ሰፈሩ።
ናንሲ ዓይኖቿን ብትጨፍንም እንቅልፍ በአይኗ hልዞር አለ፡፡ ወጣቱ ሄሪ ማርክስ ያመጣላት አንድ መለኪያ ዊስኪ እንኳን ለመተኛት የረዳት ነገር
የለም፡ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ቢሆንም በዓይኗ እንቅልፍ አልኳል ብሏል፡
መርቪንም እንቅልፍ እንዳልያዘው አውቃለች፡ የላይኛው ቆጥ ላይ
ሰፍሮ ይገላበጣል፡፡ እንደ ሌሎች መኝታዎች የሙሽሮቹ አልጋዎች በመጋረጃ የተሸፈኑ ባለመሆናቸው ላለመታየት ያላት ምርጫ መብራቱን ማጥፋት ነው፡፡
እንቅልፍ አልመጣላት ሲል ማርጋሬት ኦክሰንፎርድ በሀሳቧ መጣች ማርጋሬት በጣም ወጣት፣ የኑሮ ውጣ ውረድ የማይገባትና ወደፊት
ስለሚገጥማት ነገር ቅንጣት ታህል የማታውቅ ልጅ ናት። ከማርጋሬት
በጥርጣሬ የተሞላ ፊት ላይ ያነበበችው ግን ከፍተኛ ነፃ የመሆን ስሜት ነው፡፡ ይህ ደግሞ እሷ ወጣት በነበረችበት ጊዜ የገጠማት አይነት ችግር ነው፡፡ ናንሲም በዚያ ወቅት ከወላጆቿ ጋር አተካራ ውስጥ ገብታ ነበር፧
በተለይ ከእናቷ ጋር፡ እናቷ የተከበረ የቦስተን ቤተሰብ ልጅ እንድታገባ
ብትፈልግም እሷ ግን ገና አስራ ስድስት አመት ሲሞላት ሾን ሌኔሃን
ከሚባል የህክምና ትምህርት ከተማረ ከአባቷ ፋብሪካ ውስጥ ከሚሰራ ካቦ ልጅ ጋር ፍቅር ጀመረች፡፡ እናትዬው ናንሲ ይህን ልጅ እንዳታገባው ልጁ ከሌሎች ሴቶች ጋር እንደሚማግጥ፣ እናት አባቱን ከፍ ዝቅ እያደረገ
እንደሚሳደብና በየጊዜው እንደሚያመው ሀሜት ብታስወራም ናንሲ ግን
የሚነዛውን ሀሜት እንዳልሰማች በማሳለፍ ሾንን አግብታ እስከ ዕለተ ሞቷ ድረስ አብራው ኖራለች፡፡
ማርጋሬት የእሷን ያህል ጥንካሬ ያላት ልጅ አትመስልም፡፡ ከአባቷ ጋር
ካልተስማማች ከቤታቸው መውጣት ትችላለች፡፡ ይቺ ልጅ በየጊዜው ችግር
እያነሳች እንዳታላዝንና ራሷን ለመቻል እንድትጥር የሚመክራት ሰው ያስፈልጋታል፡ እኔ በእሷ እድሜ የሁለት ህጻናት እናት ነበርኩ› አለች በሃሳቧ፡
ስለዚህ ማርጋሬት ራሷን እንድትችል ጠበቅ ያለ ምክር ለግሳታለች እሷም ቃሏን በመጠበቅ ስራ ልትሰጣት ተስፋ አድርጋለች፡፡
ይሄ ሁሉ ደግሞ የሚወሰነው ከወንድሟ ጋር ባላት ጠብ የሀይል
ሚዛኑን በጨበጠው በአጭበርባሪው ሽማግሌ በዳኒ ሪሌይ ነው፡፡ ናንሲ
እንደገና ወደ ጭንቀቷ ተመለሰች፡፡ ጠበቃዋ ማክ ዳኒ ሪሌይን ይኸኔ
አግኝቶት ይሆን? ከአገኘውስ ስለቀድሞው ወንጀሉ ሲነግረው ምን አለ? ይህ ሁሉ ሴራ እሱ ላይ ግፊት ለማድረግ የተጠነሰሰ መሆኑን ጠርጥሮ ይሆን?›
እነዚህን ገና ምላሽ ያላገኙ ጥያቄዎች ስታወጣ ስታወርድ እንቅልፍ አጥታ
አልጋዋ ላይ ትገላበጣለች፡፡
የሚቀጥለው የአይሮፕላኑ ማረፊያ ቦትውድ ከተማ ነው፡፡ ኒውፋውንድ ስትደርስ ማክጋ ስልክ ደውላ ታረጋግጣለች፡፡በዚያ ጊዜ ሁሉ ነገር ይለይለታል፡
አይሮፕላኑ ሲንዘፈዘፍና ሲንገጫገጭ ናንሲ መላ አካልዋ ተረበሸ፡፡አሁን ደግሞ ብሶበታል፡ በአይሮፕላን በተደጋጋሚ ብትሄድም ከዚህ ቀደም
እንዲህ አይነት ሁኔታ ገጥሟት አያውቅም፡፡ ግዙፉ አይሮፕላን በንፋሱና
በወጀቡ ሲወዛወዝ ስጋት ገብቷት ተወርውራ እንዳትወድቅ የአልጋውን ብረት አጥብቃ ያዘች፡፡ ባሏ ከሞተ ወዲህ ብዙ ችግር ገጥሟታል፤ ‹አሁን ጉልበቴ
በርታ በርታ› ማለት አለበት፤ ነገር ግን የአይሮፕላኑ መንዘፍዘፍ ክንፎቹን
ይገነጥል፣ ሞተሩን ሰብሮ ይጥለው ይሆን?› እያለች መፍራቷ አልቀረም፡፡
ፍርሃቷን ይቋቋምላት ይመስል ትራሷን በጥርሷ ነክሳ ያዘች፡፡ ድንገት
አይሮፕላኑ ቁልቁል ወረደ፡፡ ቁልቁል መውረዱ እንዲቆም በእጅጉ ብትመኝም
መውረዱን ቀጥሏል፡ ይህ ሁኔታ ክፉኛ አስደነገጣት፡፡ ከዚያም ዘጭ አለና
ቀጥ ብሎ መብረር ጀመረ፡
መርቪን እጁን ሰዶ ትከሻዋን ያዝ አደረገና ‹‹ንፋሱ የፈጠረው ወጀብ ነው አይሮፕላኑን እንዲህ የሚያደርገው›› አለ ‹‹ከዚህ የባሰ ሁኔታ እኔ ብዙ
ገጥሞኛል፤ አይዞሽ አትፍሪ›› ሲል አጽናናት፡፡
እጁን በእጇ ፈልጋ አጥብቃ ያዝ አደረገችው፡፡ ከአልጋው ወረደና እሷ አልጋ ጫፍ ላይ ቁጭ ብሎ ፀጉሯን ይደባብስ ገባ፡፡ አሁንም ፍርሃቷ ሙሉ በሙሉ ባይለቃትም አይሮፕላኑ ሲወዛወዝ መርቪን ያዝ ስላደረጋት በመጠኑ
ቀለል አላት፡፡
ምን ያህል ጊዜ እንደተያያዙ አላወቀችም:: ትንሽ ቆይቶ ወጀቡ ተነሳ፡፡በደምብ ስትረጋጋ የመርቪንን እጅ
ለቀቅ አደረገችው፡፡ ምን ማለት እንዳለባት አላወቀችም።
ናንሲ መብራቱን አበራችና ከአልጋዋ ውስጥ ወጣች፡፡ ከላይ የሆነ ልብስ ደረብ አደረገችና መስታወቱ ፊት ቁጭ አለች፡፡ ሁልጊዜም
ጭንቀት ሲይዛት እንደምታደርገው ፀጉሯን አበጠረች፡፡ በጭንቀቷ ጊዜ የመርቪንን እጅ መያዟ አሳፈራት፡ በዚያ ጊዜ ክብሯን ሸጣ እጁን ለጥቂት ጊዜ በመያዟ በሆዷ
ብታመሰግነውም አሁን ፍርሃቷ ሲለቃት ግን ነገሩ አስፈራት፡፡ እሱም ስሜቷን በመረዳት እፍረቷ እንዲለቃት ብሎ ለጊዜው ክፍሉን ለቆላት ወጣ፡፡
መርቪን ትንሽ ቆይቶ ጠርሙስ ብራንዲ ከሁለት መለኪያ ጋር አመጣና
መጠጡን ቀድቶ አንዱን ሰጣት፡፡ አይሮፕላኑ ትንሽ ይወዛወዝ ስለነበር
በአንድ እጇ መለኪያውን በሌላ እጇ ደግሞ የአልጋውን ብረት ይዛለች:
የለበሰው አስቂኝ ልብስ ባያስቃት ኖሮ ድንጋጤው ቶሎ አይለቃትም አስቂኝ ቢሆንም ልክ ሱፍ ለብሶ
እንደሚንጎራደድ ሁሉ ምንም አልመሰለውም፡፡ ሰው ሞኝ ነው ቢለው ግድ
የለውም፡፡ ልበ ሙሉነቱ አስደስቷታል፡፡
ብራንዲዋን ስትጨልጥ በሰራ አካላቷ ሙቀት ስለፈጠረላት ደጋግማ
ተጎነጨች፡፡
መርቪን ወሬ ለመጀመር ብሎ ‹‹እዚያ መታጠቢያ ክፍል ውስጥ የሆነ
እንግዳ ነገር አየሁ›› አለ ‹‹እኔ ወደ መታጠቢያ ክፍል ስገባ አንድ በድንጋጤ
ቀልቡ የተገፈፈ ተሳፋሪ ሲወጣ አየሁ፡፡ የመታጠቢያ ክፍሉ መስኮት ተሰብሯል የበረራ መሀንዲሱ ደግሞ ጥፋት ሲፈጸም የተያዘ ሰው መስሎ እዚያ ቆሟል፡፡ መስኮቱ የተሰበረው ከአይሮፕላኑ ውጭ ተወርውሮ በገባ
የበረዶ ቋጥኝ መሆኑን ሊታመን የማይችል ታሪክ ነገረኝ፡፡ እኔ ግን ሁለ±
ሲደባደቡ እንደነበር መገመት አላቃተኝም፡፡››
ናንሲ እዚያ እጅ ለእጅ ተያይዘው ከሚቀመጡ ታሪክ ስለነገራት በሆዷ
መርቪንን አመሰገነችው፡፡ ‹‹የትኛው የበረራ መሀንዲስ?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹እንደ እኔ ቁመቱ ሎጋ የሆነና ፀጉሩ ቃጫ የመሰለ መልከ መልካም ወጣት››
‹‹መሀንዲሱን አወቅሁት፤ ተሳፋሪውስ ማን ነው?››
‹‹ስሙን አላውቀውም፤ ነጋዴ ይመስላል፤ አመድማ ሱፍ ልብስ የለበሰው ሰውዬ ነው›› አለና መርቪን ተነስቶ ብራንዲ ብርጭቆዋ ውስጥ
ጨመረላት፡፡
👍20🥰1
ናንሲ ከላይ የለበሰችው የመኝታ ልብስ ከላይዋ ላይ ሲወድቅ ባቷና እግሯ ቢጋለጥም ልቡን የወሰደችበትን ሚስቱን ዱካ እግር እግር በፅናት
የሚከተል በመሆኑ እሷ ዓይኑ ውስጥ እንደማትገባ አውቃለች፡፡ ኧረ እንደውም እርቃኗን ብትሆን እንኳን ማስተዋሉን እንጃ፡፡ የእሱ የእሷን እጅ መያዝ አንድ የሰው ልጅ ለሌላው የሚያደርገው ንፁህ የሀዘኔታ ምልክት
ነው፡፡
ውይይታቸው እንዲቀጥል ፈልጋ ‹‹ባለቤትህ አሁንም ተናዳብሃለች?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹ንዴቷ አልበረደላትም›› አለ መርቪን፡፡
ናንሲ ልብሷን ለመለወጥ ከሄደችበት መታጠቢያ ቤት ስትመለስ ያየችው በመርቪን፣ በዳያናና በማርክ መካከል ሲካሄድ የነበረው ትዕይንት ትዝ ብሏት ፈገግ አለች፡፡ የመርቪን ሚስት በባሏ ላይ ትጮሃለች፣ ወዳጇ ደግሞ በሷ ላይ ይጮሀል እሷ ስትደርስ ማርክና ዳያና ንዴታቸውን ዋጥ አድርገው በመሀከላቸው የተፈጠረውን ንትርክ ሌላ ቦታ ሄዶ ለመቀጠል ወዲያው ነው ወጥተው የሄዱት፡ ናንሲ መርቪን እንዳያፍር ብላ በወቅቱ ስለተፈጠረው ነገር ከዚያ በኋላ አላነሳችም፤ ሆኖም ይህ ሁኔታ አንዳንድ
ግላዊ ሁኔታዎችን መርቪንን እንዳትጠይቀው አላገዳትም፡፡ ሆነም ቀረ
ያሉበት ሁኔታ የግድ ስላቀራረባቸው የሆድ ሆዳቸውን መነጋገር ጀምረዋል፡፡
‹‹ታዲያ ወዳንተ ተመልሳ ትመጣ ይሆን?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹ማወቅ አስቸጋሪ ነው፡፡ አብሯት ያለው ሰው ደካማ ይመስላል፡፡ምናልባትም የፈለገችው ይህን ይሆናል›› አለ፡፡
ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡፡ ማርክና መርቪን በእጅጉ የተለያዩ ሰዎች ናቸው፡ መርቪን ዘንካታ፣ መልከ መልካም ሲሆን ሰው ከመጤፍ የማይቆጥር እና ቀጥተኛ ተናጋሪ ነው፡፡ ማርክ ደግሞ ባህሪው ለስለስ ያለ እና ፈገግታ የማይለየው ሰው ነው፡፡ እኔ ልጅ የሚመስል ሰው አልወድም፧ ነገሩ ለእሷ ይሄ ባህሪው ስቧት ሊሆን ይችላል፧ እኔ ብሆን ኖሮ መርቪንን በማርክ አልለውጠውም ነገር ግን የሰው ፍላጎት የተለያየ ነው አለች በሆዷ።
"አንቺስ እንዴት ልታደርጊ ነው፡፡ ወንድምሽን ለመግጠም ተዘጋጅተሻል?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አሁን ድክመቱን አግኝቼዋለሁ›› አለች ናንሲ፡፡
‹‹ዳኒ ሪሌይ እግሯ
ስር ሊወድቅ ደርሷል፡፡ አንድ መርቺያ መንገድ ለማግኘት ተቃርቤያለሁ›› አለች፡፡
መርቪን ፈገግ አለና ‹‹አንቺን ጓደኛ ማድረግ እንጂ ጠላት አድርጎ ማየት ተገቢ እንዳልሆነ ነው አሁን የገቧኝ›› አለ፡፡
‹‹እኔ ለአባቴ ብዬ ነው›› አለች ‹‹በጣም እወደው ነበር፧ ሁሉ ነገሬ ደግሞ እሱ ትቶልኝ ያለፈው ፋብሪካ ነው፤ ፋብሪካው የእሱ መታሰቢያ ነው፤ የእሱ አሻራ ታትሞበታል፡››
‹‹እስቲ ስለአባትሽ ንገሪኝ›› አለ መርቪን፡፡
‹‹እሱን አንድ ጊዜ የተዋወቀው ሰው ሊረሳው አይችልም፡፡ እንዳንተ
ቁመተ ሎጋ ሲሆን ጠጉሩ ጠቆር፣ ድምጹ ጎርነን ያለ ሰው ነው፡፡ ገና ስታየው መንፈሰ ጠንካራነቱን ትረዳለህ፡፡ በፋብሪካው ተቀጥረው የሚሰሩ
ሰዎችን ስም፣ የሚስቶቻቸውን ጤንነትና የልጆቻቸውን የትምህርት ሁኔታ ይጠይቃል፡፡ በርካታ የፋብሪካው ሰራተኞች ልጆች ከፍሎ በማስተማር ለወግ ማዕረግ አብቅቷቸዋል፡፡ እሱ ሰዎች ለእሱ ታማኝ እንዴት ሊሆኑ እንደ ሚችሉ ነው ዘወትር የሚጥረው፡፡ በዚህ ባህሪው ዘመነኛ አይመስልም፧ አባታዊ ባህሪ ነው ያለው፡፡ እሱ ለንግድ ስራ የተፈጠረ ጭንቅላት ነበረው፡
የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በወደቀበት በዚያ ጨለማ ዘመን በኒው ኢንግላንድ ስቴት በርካታ ፋብሪካዎች ሲዘጉ የእኛ ፋብሪካ ሽያጭ ያድግ ስለነበር ብዙ ሰራተኞች ይቀጥር ነበር፡፡ እሱ የሰዎችን ስነ ልቦና ማሸነፍ ላይ ነው ዋናው ትኩረቱ፡ አንድ ነገር ይዘህ ብትመጣ ለችግሩ ፍንትው ያለ መፍትሄ ይሰጥሃል
ሳልጠግበው ነው ያለፈው፡፡ ሞቱ በጣም ነው የጎዳኝ፡፡ የባሌም እንዲሁ፡››
ድንገት ንድድ ብላ ‹‹አባቴ ህይወቱን ሙሉ የለፋበትን ፋብሪካውን በማይረባው ወንድሜ እንዳልነበር እንዲሆን አልፈቅድም›› አለችና ተቁነጠነጠች፡፡
‹‹አንዱ ቁልፍ የአክሲዮን ባለቤት እኔን እንዲደግፍ ግፊት እያደረኩበት
ነው፡፡ ነገር ግን እስካሁን ምን ያህል እንደተሳካልኝ አላውቅም›› አለች::
ታሪኳን ነግራው ሳትጨርስ አይሮፕላኑ ከባድ ነውጥ ውስጥ በመግባቱ
እንዳልተገራ ፈረስ ይጋልብ ጀመር፡፡ በዚህ ጊዜ ናንሲ መለኪያዋን ጣለችና
የመዋቢያ ዕቃ መደርደሪያ ጠረጴዛውን በሁለት እጇ ጥርቅም አድርጋ ያዘች መርቪን ቀጥ ብሎ ለመቆም ቢጥርም አይሮፕላኑ ወደ ጎን
በማዘምበሉ ወለሉ ላይ ተፈጠፈጠ፡፡
አይሮፕላኑ እንደገና ተረጋጋ ናንሲ መርቪንን እንዲነሳ ለማገዝ እጇን ሰደደችና ‹‹ተረፍክ?›› ብላ ጠየቀችው: በዚህ ጊዜ አይሮፕላኑ እንደገና
ሲወዛወዝ ሚዛኗን ሳተችና የያዘችውን ስትለቀው በቀጥታ መርቪን ላይ
ወደቀች::
መርቪን ሁኔታው በሳቅ አፈነዳው፡፡
ናንሲ መርቪን ላይ ስትወድቅ የጎዳችው መስሏት ነበር፡
እሷ ቀጭን እሱ ደግሞ ግዙፍ መሆኑን ስታውቅ ድንጋጤዋ ለቀቃት።ሁለቱ ሰዎች ወለሉ ላይ ጎን ለጎን ተጋድመዋል፡ ተረጋግቶ ሲሄድ ከወደቀችበት ቀና ብላ በቂጧ ተቀመጠች፡፡
አይሮፕላኑ እንደገና
‹‹እንዲህ ሆነን ሰው ቢያይ ጅል ሳንመስለው አንቀርም›› አለና ሳቀ፡
ሳቁ ተጋባባትና እሷም
ሳቀች፡፡ለአፍታ ከሃያ ሰዓት በፊት የተፈጠረውን ውጥረት የረሳች መሰለች፡፡ በመርቪን አይሮፕላን ከገደል ጋር ልትጋጭ የነበረውና በሙሽሮች ክፍል ውስጥ ያለችበት ሁኔታ፧ በመብል ቤት ከይሁዳውያኑ ጋር የተነሳው ጠብ፣ የመርቪን ሚስት ቅናት የፈጠረው ጭቅጭቅ፣ የአይሮፕላኑ በወጀቡ ምክንያት ከቁጥጥር ውጭ
መሆን የፈጠረው ድንጋጤና ፍርሃት፣ እንግዳ ከሆነ ሰው ጋር በመኝታ ልብስ ሆኖ
እንደ ፈረስ በሚጋልብ አይሮፕላን ወለል ላይ ቁጭ ብላ ያለችበት ሁኔታ
ሁሉ ተደማምሮ በእጅጉ ስላስፈነደቃት የወንድሟን ሽር ለጊዜውም ቢሆን
ረስታ ነበር፡፡
ቀጥሎ የተፈጠረው የአይሮፕላኑ መዋዠቅ
እርስ በእርስ
አስተቃቀፋቸው:፡ ከዚያማ ግጥም አድርጋ ሳመችው ይህ አድራጎቷ
አስደንቋታል፡ እሱን እስመዋለሁ ብላ አስባም አልማም አታውቅም፡
እንዲያው ድንገት የተፈጠረ ስሜት ነው፡፡
መርቪን የተፈጠረው ሁኔታ ያልጠበቀው በመሆኑ ቢያስደነግጠውም
ቶሎ ከድንጋጤው መለስ አለናእሱም ግጥም አድርጎ ሳማት፡፡ ምጥጥ አድርጎ ሲስማት ከባድ ሙቀት በሰራ አካላቷ ለቀቀባት፡፡
ትንሽ ተሳስመው እንደቆዩ ገፋ አደረገችውና ጫን ጫን እየተነፈሰች
‹‹ምንድን ነው ያደረግነው?›› ስትል የጅል ጥያቄ ጠየቀችው፡
‹‹ሳምሽኝ ሳምኩሽ›› አለ በተደሰተ መንፈስ፡፡
‹‹ልስምህ ፈልጌ አይደለም›› አለች፡
ሆነ ሆኖ ስለሳምሽኝ ደስ ብሎኛል›› አለና በድጋሚ ሳማት፡፡
ከእቅፉ መውጣት ያለባት ቢሆንም አያያዙ ጠንከር ያለና እሷም እንዲለቃት ስላልፈለገች ዝም አለችው፡ እጁን በመኝታ ልብሷ ውስጥ ሲሰደው ሰውነቷ ሽምቅቅ አለ፡፡ ጡቶቿ ትንሽ መሆናቸው ስላሳፈራት
መርቪን ይጠላኛል ብላ ገምታ ነበር፡፡ እሱ ግን በግዙፍ እጁ ትንንሽና ክብ
ጡቶቿን ያዝ አድርጎ ሲያሻሻቸው በጉሮሮው ምራቁ ሲወርድ ተሰማ፡፡ የጣቱ ጫፍ የጡቷን ጫፍ ሲነካው አሁንም እፍረት ቢጤ ጠቅ አደረጋት፡ የጡቷ
ጫፍ ከጡቷ ጋር ሲወዳደር ትልቅ ነው፤ ትንሽ ጡት ትልቅ የጡት ጫፍ፡
መርቪን ግን የጡቷ ማነስ ይበልጥ ፍላጎት አጫረበት፡፡ ጡቶቿን እያቀያየረ
ለስለስ አድርጎ ደባበሳቸው፡፡ ናንሲም ቀስ በቀስ እየጨመረ የመጣው ማሻሸቱ የወሲብ ስሜት ስለቀሰቀሰባት እጇን ልትሰጥ ትንሽ ነበር የቀራት፡ እንዲህ አይነት የወሲብ ስሜት ከተሰማት ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡
የሚከተል በመሆኑ እሷ ዓይኑ ውስጥ እንደማትገባ አውቃለች፡፡ ኧረ እንደውም እርቃኗን ብትሆን እንኳን ማስተዋሉን እንጃ፡፡ የእሱ የእሷን እጅ መያዝ አንድ የሰው ልጅ ለሌላው የሚያደርገው ንፁህ የሀዘኔታ ምልክት
ነው፡፡
ውይይታቸው እንዲቀጥል ፈልጋ ‹‹ባለቤትህ አሁንም ተናዳብሃለች?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹ንዴቷ አልበረደላትም›› አለ መርቪን፡፡
ናንሲ ልብሷን ለመለወጥ ከሄደችበት መታጠቢያ ቤት ስትመለስ ያየችው በመርቪን፣ በዳያናና በማርክ መካከል ሲካሄድ የነበረው ትዕይንት ትዝ ብሏት ፈገግ አለች፡፡ የመርቪን ሚስት በባሏ ላይ ትጮሃለች፣ ወዳጇ ደግሞ በሷ ላይ ይጮሀል እሷ ስትደርስ ማርክና ዳያና ንዴታቸውን ዋጥ አድርገው በመሀከላቸው የተፈጠረውን ንትርክ ሌላ ቦታ ሄዶ ለመቀጠል ወዲያው ነው ወጥተው የሄዱት፡ ናንሲ መርቪን እንዳያፍር ብላ በወቅቱ ስለተፈጠረው ነገር ከዚያ በኋላ አላነሳችም፤ ሆኖም ይህ ሁኔታ አንዳንድ
ግላዊ ሁኔታዎችን መርቪንን እንዳትጠይቀው አላገዳትም፡፡ ሆነም ቀረ
ያሉበት ሁኔታ የግድ ስላቀራረባቸው የሆድ ሆዳቸውን መነጋገር ጀምረዋል፡፡
‹‹ታዲያ ወዳንተ ተመልሳ ትመጣ ይሆን?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹ማወቅ አስቸጋሪ ነው፡፡ አብሯት ያለው ሰው ደካማ ይመስላል፡፡ምናልባትም የፈለገችው ይህን ይሆናል›› አለ፡፡
ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡፡ ማርክና መርቪን በእጅጉ የተለያዩ ሰዎች ናቸው፡ መርቪን ዘንካታ፣ መልከ መልካም ሲሆን ሰው ከመጤፍ የማይቆጥር እና ቀጥተኛ ተናጋሪ ነው፡፡ ማርክ ደግሞ ባህሪው ለስለስ ያለ እና ፈገግታ የማይለየው ሰው ነው፡፡ እኔ ልጅ የሚመስል ሰው አልወድም፧ ነገሩ ለእሷ ይሄ ባህሪው ስቧት ሊሆን ይችላል፧ እኔ ብሆን ኖሮ መርቪንን በማርክ አልለውጠውም ነገር ግን የሰው ፍላጎት የተለያየ ነው አለች በሆዷ።
"አንቺስ እንዴት ልታደርጊ ነው፡፡ ወንድምሽን ለመግጠም ተዘጋጅተሻል?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አሁን ድክመቱን አግኝቼዋለሁ›› አለች ናንሲ፡፡
‹‹ዳኒ ሪሌይ እግሯ
ስር ሊወድቅ ደርሷል፡፡ አንድ መርቺያ መንገድ ለማግኘት ተቃርቤያለሁ›› አለች፡፡
መርቪን ፈገግ አለና ‹‹አንቺን ጓደኛ ማድረግ እንጂ ጠላት አድርጎ ማየት ተገቢ እንዳልሆነ ነው አሁን የገቧኝ›› አለ፡፡
‹‹እኔ ለአባቴ ብዬ ነው›› አለች ‹‹በጣም እወደው ነበር፧ ሁሉ ነገሬ ደግሞ እሱ ትቶልኝ ያለፈው ፋብሪካ ነው፤ ፋብሪካው የእሱ መታሰቢያ ነው፤ የእሱ አሻራ ታትሞበታል፡››
‹‹እስቲ ስለአባትሽ ንገሪኝ›› አለ መርቪን፡፡
‹‹እሱን አንድ ጊዜ የተዋወቀው ሰው ሊረሳው አይችልም፡፡ እንዳንተ
ቁመተ ሎጋ ሲሆን ጠጉሩ ጠቆር፣ ድምጹ ጎርነን ያለ ሰው ነው፡፡ ገና ስታየው መንፈሰ ጠንካራነቱን ትረዳለህ፡፡ በፋብሪካው ተቀጥረው የሚሰሩ
ሰዎችን ስም፣ የሚስቶቻቸውን ጤንነትና የልጆቻቸውን የትምህርት ሁኔታ ይጠይቃል፡፡ በርካታ የፋብሪካው ሰራተኞች ልጆች ከፍሎ በማስተማር ለወግ ማዕረግ አብቅቷቸዋል፡፡ እሱ ሰዎች ለእሱ ታማኝ እንዴት ሊሆኑ እንደ ሚችሉ ነው ዘወትር የሚጥረው፡፡ በዚህ ባህሪው ዘመነኛ አይመስልም፧ አባታዊ ባህሪ ነው ያለው፡፡ እሱ ለንግድ ስራ የተፈጠረ ጭንቅላት ነበረው፡
የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በወደቀበት በዚያ ጨለማ ዘመን በኒው ኢንግላንድ ስቴት በርካታ ፋብሪካዎች ሲዘጉ የእኛ ፋብሪካ ሽያጭ ያድግ ስለነበር ብዙ ሰራተኞች ይቀጥር ነበር፡፡ እሱ የሰዎችን ስነ ልቦና ማሸነፍ ላይ ነው ዋናው ትኩረቱ፡ አንድ ነገር ይዘህ ብትመጣ ለችግሩ ፍንትው ያለ መፍትሄ ይሰጥሃል
ሳልጠግበው ነው ያለፈው፡፡ ሞቱ በጣም ነው የጎዳኝ፡፡ የባሌም እንዲሁ፡››
ድንገት ንድድ ብላ ‹‹አባቴ ህይወቱን ሙሉ የለፋበትን ፋብሪካውን በማይረባው ወንድሜ እንዳልነበር እንዲሆን አልፈቅድም›› አለችና ተቁነጠነጠች፡፡
‹‹አንዱ ቁልፍ የአክሲዮን ባለቤት እኔን እንዲደግፍ ግፊት እያደረኩበት
ነው፡፡ ነገር ግን እስካሁን ምን ያህል እንደተሳካልኝ አላውቅም›› አለች::
ታሪኳን ነግራው ሳትጨርስ አይሮፕላኑ ከባድ ነውጥ ውስጥ በመግባቱ
እንዳልተገራ ፈረስ ይጋልብ ጀመር፡፡ በዚህ ጊዜ ናንሲ መለኪያዋን ጣለችና
የመዋቢያ ዕቃ መደርደሪያ ጠረጴዛውን በሁለት እጇ ጥርቅም አድርጋ ያዘች መርቪን ቀጥ ብሎ ለመቆም ቢጥርም አይሮፕላኑ ወደ ጎን
በማዘምበሉ ወለሉ ላይ ተፈጠፈጠ፡፡
አይሮፕላኑ እንደገና ተረጋጋ ናንሲ መርቪንን እንዲነሳ ለማገዝ እጇን ሰደደችና ‹‹ተረፍክ?›› ብላ ጠየቀችው: በዚህ ጊዜ አይሮፕላኑ እንደገና
ሲወዛወዝ ሚዛኗን ሳተችና የያዘችውን ስትለቀው በቀጥታ መርቪን ላይ
ወደቀች::
መርቪን ሁኔታው በሳቅ አፈነዳው፡፡
ናንሲ መርቪን ላይ ስትወድቅ የጎዳችው መስሏት ነበር፡
እሷ ቀጭን እሱ ደግሞ ግዙፍ መሆኑን ስታውቅ ድንጋጤዋ ለቀቃት።ሁለቱ ሰዎች ወለሉ ላይ ጎን ለጎን ተጋድመዋል፡ ተረጋግቶ ሲሄድ ከወደቀችበት ቀና ብላ በቂጧ ተቀመጠች፡፡
አይሮፕላኑ እንደገና
‹‹እንዲህ ሆነን ሰው ቢያይ ጅል ሳንመስለው አንቀርም›› አለና ሳቀ፡
ሳቁ ተጋባባትና እሷም
ሳቀች፡፡ለአፍታ ከሃያ ሰዓት በፊት የተፈጠረውን ውጥረት የረሳች መሰለች፡፡ በመርቪን አይሮፕላን ከገደል ጋር ልትጋጭ የነበረውና በሙሽሮች ክፍል ውስጥ ያለችበት ሁኔታ፧ በመብል ቤት ከይሁዳውያኑ ጋር የተነሳው ጠብ፣ የመርቪን ሚስት ቅናት የፈጠረው ጭቅጭቅ፣ የአይሮፕላኑ በወጀቡ ምክንያት ከቁጥጥር ውጭ
መሆን የፈጠረው ድንጋጤና ፍርሃት፣ እንግዳ ከሆነ ሰው ጋር በመኝታ ልብስ ሆኖ
እንደ ፈረስ በሚጋልብ አይሮፕላን ወለል ላይ ቁጭ ብላ ያለችበት ሁኔታ
ሁሉ ተደማምሮ በእጅጉ ስላስፈነደቃት የወንድሟን ሽር ለጊዜውም ቢሆን
ረስታ ነበር፡፡
ቀጥሎ የተፈጠረው የአይሮፕላኑ መዋዠቅ
እርስ በእርስ
አስተቃቀፋቸው:፡ ከዚያማ ግጥም አድርጋ ሳመችው ይህ አድራጎቷ
አስደንቋታል፡ እሱን እስመዋለሁ ብላ አስባም አልማም አታውቅም፡
እንዲያው ድንገት የተፈጠረ ስሜት ነው፡፡
መርቪን የተፈጠረው ሁኔታ ያልጠበቀው በመሆኑ ቢያስደነግጠውም
ቶሎ ከድንጋጤው መለስ አለናእሱም ግጥም አድርጎ ሳማት፡፡ ምጥጥ አድርጎ ሲስማት ከባድ ሙቀት በሰራ አካላቷ ለቀቀባት፡፡
ትንሽ ተሳስመው እንደቆዩ ገፋ አደረገችውና ጫን ጫን እየተነፈሰች
‹‹ምንድን ነው ያደረግነው?›› ስትል የጅል ጥያቄ ጠየቀችው፡
‹‹ሳምሽኝ ሳምኩሽ›› አለ በተደሰተ መንፈስ፡፡
‹‹ልስምህ ፈልጌ አይደለም›› አለች፡
ሆነ ሆኖ ስለሳምሽኝ ደስ ብሎኛል›› አለና በድጋሚ ሳማት፡፡
ከእቅፉ መውጣት ያለባት ቢሆንም አያያዙ ጠንከር ያለና እሷም እንዲለቃት ስላልፈለገች ዝም አለችው፡ እጁን በመኝታ ልብሷ ውስጥ ሲሰደው ሰውነቷ ሽምቅቅ አለ፡፡ ጡቶቿ ትንሽ መሆናቸው ስላሳፈራት
መርቪን ይጠላኛል ብላ ገምታ ነበር፡፡ እሱ ግን በግዙፍ እጁ ትንንሽና ክብ
ጡቶቿን ያዝ አድርጎ ሲያሻሻቸው በጉሮሮው ምራቁ ሲወርድ ተሰማ፡፡ የጣቱ ጫፍ የጡቷን ጫፍ ሲነካው አሁንም እፍረት ቢጤ ጠቅ አደረጋት፡ የጡቷ
ጫፍ ከጡቷ ጋር ሲወዳደር ትልቅ ነው፤ ትንሽ ጡት ትልቅ የጡት ጫፍ፡
መርቪን ግን የጡቷ ማነስ ይበልጥ ፍላጎት አጫረበት፡፡ ጡቶቿን እያቀያየረ
ለስለስ አድርጎ ደባበሳቸው፡፡ ናንሲም ቀስ በቀስ እየጨመረ የመጣው ማሻሸቱ የወሲብ ስሜት ስለቀሰቀሰባት እጇን ልትሰጥ ትንሽ ነበር የቀራት፡ እንዲህ አይነት የወሲብ ስሜት ከተሰማት ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡
👍18🥰2
‹ምን እያደረኩ ነው? አለች በሆዷ ‹እኔ የተከበርኩ ሴት ነኝ፤ አሁን ግን ገና ትናንት ከተዋወቅሁት ሰው ጋር አይሮፕላን ወለል ላይ
እየተንከባለልኩ ነው፤ ምን ነካኝ? አቁሚ አላት አዕምሮዋ፡፡ ከመርቪን ራሷን አላቀቀችና በቂጧ ቁጭ አለች፡ ስስ የመኝታ ልብሷ ተገልቦ ጭኖቿ ይታያሉ፡ መርቪን የተራቆቱ እግሮቿን ይደባብሳል፡፡ ‹‹ተው በቃ›› አለችው።
‹‹እንዳልሽ›› አለ መርቪን ድንገት ተው› መባሉ ቅሬታ ቢፈጥርበትም፡፡
‹‹ሃሳብሽን ከለወጥሽ ግን አለሁልሽ›› አላት፡፡
ወደ ሱሪው ስታማትር ብልቱ ተገትሮ ሊፈነዳ ደርሷል፡፡ ናንሲ ፊቷን አዞረችና ‹‹እኔ ነኝ ጥፋተኛዋ›› አለች ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ እያለ፡፡
‹ቢሆንም ስህተት ነው የሰራነው፤ እኔ ለቀልድ እንደሳምኩህ አውቃለሁ ይቅርታ›› አለች፡፡
‹‹ምንም ይቅርታ የሚያስጠይቅ ነገር የለም አለ መርቪን ‹‹እኔ
እንዲህ አይነት ስሜት ከተሰማኝ ቆይቷል››
‹‹ነገር ግን ሚስትህን ትወዳታለህ አይደል አትወዳትም?››
‹‹ይመስለኝ ነበር፤ አሁን ግን ግራ ገብቶኛል፡›› እውነቱን ለመናገር ናንሲም የተሰማት ተመሳሳይ ስሜት ነው፡፡ ድንግርግር ብሏታል፡፡ ባሏ ከሞተ ወዲህ ለአስር ዓመት ከወሲብ ተለይታ አሁን በቅጡ የማታውቀውን ሰው አቅፋለች፡፡
ምንድነው ታዲያ ችግሩ? ይሄን ሰው አሁን አውቄዋለሁ አለች
በሃሳቧ፡፡ ‹ኧረ በሚገባ አውቄዋለሁ፤ ከእሱ ጋር ብዙ ርቀት አብሬ መጥቻለሁ፡ ችግሮቻችንን በጋራ ፈተናል፡፡ በችግራችን ጊዜ ተረዳድተናል፡፡ባህሪው ጋጠ ወጥ እና ኩሩ የመሆኑን ያህል አፍቃሪ፣ ታማኝና ብርቱ ነው፡፡ ይህን ሰው ከነችግሩ ወድጄዋለሁ አክብሬዋለሁ የለበሰው ሽሚዝ ለእሱ የሚስማማ ባይሆንም ሴትን ልጅ እንደ ቅቤ የሚያቀልጥ የደስ ደስ
አለው፡ አይሮፕላኑ ሲዋዥቅ ፍርሃት ውስጥ ሆኜ እያለሁ እጄን ያዝ አድርጎ አይዞሽ ብሎኛል፡ ሁል ጊዜ እንደዚህ የሚያስፈራ ነገር ሲገጥመኝ ምን አለ የሚያደፋፍረኝ ወገን ቢኖረኝ፡፡
ልክ በአዕምሮዋ የምታስበውን ያወቀ ይመስል እጇን ለቀም አድርጎ ያዘው፡፡ እጇን ገልበጥ አደረገና መዳፏን ሳመው፡ ከዚያም ደረቱ ላይ
ለጠፋትና አፏን መጠጠው፡፡
‹‹ተው እንደዚህ አታድርግ›› አለች እያለከለከች ‹‹አንዴ ከጀመርን ማቆም አንችልም››
‹‹አሁን ካቆምን እንደገና መጀመር የምንችል አይመስለኝም›› ሲል
በተቃውሞ አጉረመረመ
ናንሲ በመርቪን ውስጥ ያየችው የተገደበ ነገር ግን ጠንከር ያለ ስሜት የራሷን የወሲብ ፍላጎት አቀጣጠለባት፡፡ ባሏ ከሞተ ወዲህ የእሷን ድጋፍና ጥበቃው የሚፈልጉ ደካማ ሰዎች የወሲብ ጥያቄ አቅርበውላት እምቢ ስትላቸው በቀላሉ ይተዋሉ፡፡ መርቪን ግን ፈርጠም ብሎ እየጠየቃት ነው፡፡በጣም ፈልጓታል፡፡ የፈለጋትም አሁኑኑ ነው፡፡ ለዚህ ሰው ገላዋን ልትሰጠው ፈለገች፡፡
እጁን በመኝታ ልብሷ ስር ሰዶ ጭኖቿን በጣቶቹ አፍተለተላቸው
እሷም ዓይኗን ጨፍና እየተግደረደረች ትንሽ ጭኖቿን ከፈት አደረገቻቸው፡እሱም ከዚህ በላይ አልጠየቀም፡፡ ትንሽ ቆየና ብልቷን በጣቶቹ ሲጠነቁለው አቃሰተች፡፡ ከባሏ ሾን ሌላ እንዲህ አድርጎላት የሚያውቅ ሰው የለም፡፡ ይህም ሃሳብ ደስታዋን ወደ ሀዘን ለወጠው፡ ‹ኦው ሾንዬ ና! የት ነው የማገኝህ?
ያንተ ሞት ምን እንዳጎደለብኝ ታውቃለህ? አለች በሆዷ፡ አሁን የተሰማት ሀዘን የባሏ ቀብር ላይ ከተሰማት አልተናነሰም፡፡ እምባዋ በተዘጉት ዓይኖቿ
እየተንቆረዘዘ ጉንጮቿን አራሱት፡፡ መርቪን ሲስማት እምባዋን ቀመሰና
‹‹ምን ሆንሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡ ዓይኖቿን ስትከፍት በእንባ የተጋረዱት ዓይኖቿ የመርቪን የሚያምር ነገር ግን ሀዘኔታ የተሞላው ፊት ተመለከተች፡፡ በሌላ በኩል ግን ቀሚሷ ወገቧ ድረስ ተገልቧል የመርቪን
እጅ ደግሞ ጭኖቿን ይዟል፡፡ ከዚያም እጁን ገፋ አደረገችውና ‹‹ ባክህ አትናደድብኝ›› አለችው::
‹‹ባልሽ ነው ሾን?››
ራሷን በአዎንታ ነቀነቀች፡:
‹‹ምን ያህል ጊዜ ሆኖሻል?››
‹‹አስር ዓመት››
‹‹ረጅም ጊዜ ነው››
እኔ ታማኝ ሴት ነኝ እንዳንተ›› አለች ፊቷ እንባ በእንባ ቢሆንም
ፈገግ ብላ
‹‹ልክ ነሽ፤ እኔ ሁለትጊዜአግብቻለሁ ሁለተኛ ሚስቴን ካገባሁ
ወዲህ ለሚስቴ ታማኝነቴን ያጎደልኩት አሁን ነው፡፡ እኔም ሚስቴንና ያንን
ሰው ከአዕምሮዬ ማውጣት አልቻልኩም፡››
‹‹እኛም ጅሎች ሆንን ልበል?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹ምናልባት ስላለፈው ማሰብ ማቆም አለብን፤ በእጃችን ያለውን አሁን ማጥበቅ ይኖርብናል፡››
አይሮፕላኑ ልክ የሆነ ነገር የገጨ ይመስል ወደ ላይ ሲዘል መርቪን እና ናንሲ ተላተሙ፡ መብራቱም ብልጭ ድርግም አለ፡፡ አይሮፕላኑ በሃይል ሲናወጥ ናንሲ ሳትወድ በግድ መርቪን ደረት ላይ ተጣበቀች፡፡
የአይሮፕላኑ መናወጥ ሲቆም መርቪንን ለቀቅ አድርጋ ስታየው ከንፈሩ ደምቷል፡ ‹‹ነከሺኝ›› አላት መርቪን ፈገግታ ሳይለየው፡፡
‹‹ይቅርታ››
‹‹ስለነከሺኝ ደስ ብሎኛል ጠባሳ ይፈጥራል››
ናንሲ በፍቅር ደረቱ ላይ ተለጥፋ ቀረች፡፡ወጀቡ እስኪጠፋ ወለሉ ላይ ተቃቅፈው ቆዩና ‹‹መርቪን አልጋው ላይ እንውጣ ከወለሉ ይልቅ እዚያ ይመቸናል›› አለ ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡፡ ከዚያም በጉልበቷ እየዳኸች አልጋው ላይ ወጣች፡፡ መርቪንም ተከተላትና አልጋው ላይ አብሯት ወጣ፡፡
እሱም እቅፍ አድርጎ ያዛት፡፡
በወጀቡ ምክንያት አይሮፕላኑ በተናወጠ ቁጥር ልክ መርከበኛ የጀልባውን ምሰሶ እንደሚይዝ ሁሉ ናንሲ መርቪንን ጭምቅ አድርጋ ትይዛለች፡፡
ወጀቡ ሲቀንስና ዘና ስትል እሱም ሰውነቷን በፍቅር ይነካካቸዋል፡
ከዚያ ትንሽ ቆየችና እንቅልፍ ይዟት ሄደ፡፡....
✨ይቀጥላል✨
እየተንከባለልኩ ነው፤ ምን ነካኝ? አቁሚ አላት አዕምሮዋ፡፡ ከመርቪን ራሷን አላቀቀችና በቂጧ ቁጭ አለች፡ ስስ የመኝታ ልብሷ ተገልቦ ጭኖቿ ይታያሉ፡ መርቪን የተራቆቱ እግሮቿን ይደባብሳል፡፡ ‹‹ተው በቃ›› አለችው።
‹‹እንዳልሽ›› አለ መርቪን ድንገት ተው› መባሉ ቅሬታ ቢፈጥርበትም፡፡
‹‹ሃሳብሽን ከለወጥሽ ግን አለሁልሽ›› አላት፡፡
ወደ ሱሪው ስታማትር ብልቱ ተገትሮ ሊፈነዳ ደርሷል፡፡ ናንሲ ፊቷን አዞረችና ‹‹እኔ ነኝ ጥፋተኛዋ›› አለች ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ እያለ፡፡
‹ቢሆንም ስህተት ነው የሰራነው፤ እኔ ለቀልድ እንደሳምኩህ አውቃለሁ ይቅርታ›› አለች፡፡
‹‹ምንም ይቅርታ የሚያስጠይቅ ነገር የለም አለ መርቪን ‹‹እኔ
እንዲህ አይነት ስሜት ከተሰማኝ ቆይቷል››
‹‹ነገር ግን ሚስትህን ትወዳታለህ አይደል አትወዳትም?››
‹‹ይመስለኝ ነበር፤ አሁን ግን ግራ ገብቶኛል፡›› እውነቱን ለመናገር ናንሲም የተሰማት ተመሳሳይ ስሜት ነው፡፡ ድንግርግር ብሏታል፡፡ ባሏ ከሞተ ወዲህ ለአስር ዓመት ከወሲብ ተለይታ አሁን በቅጡ የማታውቀውን ሰው አቅፋለች፡፡
ምንድነው ታዲያ ችግሩ? ይሄን ሰው አሁን አውቄዋለሁ አለች
በሃሳቧ፡፡ ‹ኧረ በሚገባ አውቄዋለሁ፤ ከእሱ ጋር ብዙ ርቀት አብሬ መጥቻለሁ፡ ችግሮቻችንን በጋራ ፈተናል፡፡ በችግራችን ጊዜ ተረዳድተናል፡፡ባህሪው ጋጠ ወጥ እና ኩሩ የመሆኑን ያህል አፍቃሪ፣ ታማኝና ብርቱ ነው፡፡ ይህን ሰው ከነችግሩ ወድጄዋለሁ አክብሬዋለሁ የለበሰው ሽሚዝ ለእሱ የሚስማማ ባይሆንም ሴትን ልጅ እንደ ቅቤ የሚያቀልጥ የደስ ደስ
አለው፡ አይሮፕላኑ ሲዋዥቅ ፍርሃት ውስጥ ሆኜ እያለሁ እጄን ያዝ አድርጎ አይዞሽ ብሎኛል፡ ሁል ጊዜ እንደዚህ የሚያስፈራ ነገር ሲገጥመኝ ምን አለ የሚያደፋፍረኝ ወገን ቢኖረኝ፡፡
ልክ በአዕምሮዋ የምታስበውን ያወቀ ይመስል እጇን ለቀም አድርጎ ያዘው፡፡ እጇን ገልበጥ አደረገና መዳፏን ሳመው፡ ከዚያም ደረቱ ላይ
ለጠፋትና አፏን መጠጠው፡፡
‹‹ተው እንደዚህ አታድርግ›› አለች እያለከለከች ‹‹አንዴ ከጀመርን ማቆም አንችልም››
‹‹አሁን ካቆምን እንደገና መጀመር የምንችል አይመስለኝም›› ሲል
በተቃውሞ አጉረመረመ
ናንሲ በመርቪን ውስጥ ያየችው የተገደበ ነገር ግን ጠንከር ያለ ስሜት የራሷን የወሲብ ፍላጎት አቀጣጠለባት፡፡ ባሏ ከሞተ ወዲህ የእሷን ድጋፍና ጥበቃው የሚፈልጉ ደካማ ሰዎች የወሲብ ጥያቄ አቅርበውላት እምቢ ስትላቸው በቀላሉ ይተዋሉ፡፡ መርቪን ግን ፈርጠም ብሎ እየጠየቃት ነው፡፡በጣም ፈልጓታል፡፡ የፈለጋትም አሁኑኑ ነው፡፡ ለዚህ ሰው ገላዋን ልትሰጠው ፈለገች፡፡
እጁን በመኝታ ልብሷ ስር ሰዶ ጭኖቿን በጣቶቹ አፍተለተላቸው
እሷም ዓይኗን ጨፍና እየተግደረደረች ትንሽ ጭኖቿን ከፈት አደረገቻቸው፡እሱም ከዚህ በላይ አልጠየቀም፡፡ ትንሽ ቆየና ብልቷን በጣቶቹ ሲጠነቁለው አቃሰተች፡፡ ከባሏ ሾን ሌላ እንዲህ አድርጎላት የሚያውቅ ሰው የለም፡፡ ይህም ሃሳብ ደስታዋን ወደ ሀዘን ለወጠው፡ ‹ኦው ሾንዬ ና! የት ነው የማገኝህ?
ያንተ ሞት ምን እንዳጎደለብኝ ታውቃለህ? አለች በሆዷ፡ አሁን የተሰማት ሀዘን የባሏ ቀብር ላይ ከተሰማት አልተናነሰም፡፡ እምባዋ በተዘጉት ዓይኖቿ
እየተንቆረዘዘ ጉንጮቿን አራሱት፡፡ መርቪን ሲስማት እምባዋን ቀመሰና
‹‹ምን ሆንሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡ ዓይኖቿን ስትከፍት በእንባ የተጋረዱት ዓይኖቿ የመርቪን የሚያምር ነገር ግን ሀዘኔታ የተሞላው ፊት ተመለከተች፡፡ በሌላ በኩል ግን ቀሚሷ ወገቧ ድረስ ተገልቧል የመርቪን
እጅ ደግሞ ጭኖቿን ይዟል፡፡ ከዚያም እጁን ገፋ አደረገችውና ‹‹ ባክህ አትናደድብኝ›› አለችው::
‹‹ባልሽ ነው ሾን?››
ራሷን በአዎንታ ነቀነቀች፡:
‹‹ምን ያህል ጊዜ ሆኖሻል?››
‹‹አስር ዓመት››
‹‹ረጅም ጊዜ ነው››
እኔ ታማኝ ሴት ነኝ እንዳንተ›› አለች ፊቷ እንባ በእንባ ቢሆንም
ፈገግ ብላ
‹‹ልክ ነሽ፤ እኔ ሁለትጊዜአግብቻለሁ ሁለተኛ ሚስቴን ካገባሁ
ወዲህ ለሚስቴ ታማኝነቴን ያጎደልኩት አሁን ነው፡፡ እኔም ሚስቴንና ያንን
ሰው ከአዕምሮዬ ማውጣት አልቻልኩም፡››
‹‹እኛም ጅሎች ሆንን ልበል?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹ምናልባት ስላለፈው ማሰብ ማቆም አለብን፤ በእጃችን ያለውን አሁን ማጥበቅ ይኖርብናል፡››
አይሮፕላኑ ልክ የሆነ ነገር የገጨ ይመስል ወደ ላይ ሲዘል መርቪን እና ናንሲ ተላተሙ፡ መብራቱም ብልጭ ድርግም አለ፡፡ አይሮፕላኑ በሃይል ሲናወጥ ናንሲ ሳትወድ በግድ መርቪን ደረት ላይ ተጣበቀች፡፡
የአይሮፕላኑ መናወጥ ሲቆም መርቪንን ለቀቅ አድርጋ ስታየው ከንፈሩ ደምቷል፡ ‹‹ነከሺኝ›› አላት መርቪን ፈገግታ ሳይለየው፡፡
‹‹ይቅርታ››
‹‹ስለነከሺኝ ደስ ብሎኛል ጠባሳ ይፈጥራል››
ናንሲ በፍቅር ደረቱ ላይ ተለጥፋ ቀረች፡፡ወጀቡ እስኪጠፋ ወለሉ ላይ ተቃቅፈው ቆዩና ‹‹መርቪን አልጋው ላይ እንውጣ ከወለሉ ይልቅ እዚያ ይመቸናል›› አለ ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡፡ ከዚያም በጉልበቷ እየዳኸች አልጋው ላይ ወጣች፡፡ መርቪንም ተከተላትና አልጋው ላይ አብሯት ወጣ፡፡
እሱም እቅፍ አድርጎ ያዛት፡፡
በወጀቡ ምክንያት አይሮፕላኑ በተናወጠ ቁጥር ልክ መርከበኛ የጀልባውን ምሰሶ እንደሚይዝ ሁሉ ናንሲ መርቪንን ጭምቅ አድርጋ ትይዛለች፡፡
ወጀቡ ሲቀንስና ዘና ስትል እሱም ሰውነቷን በፍቅር ይነካካቸዋል፡
ከዚያ ትንሽ ቆየችና እንቅልፍ ይዟት ሄደ፡፡....
✨ይቀጥላል✨
👍21❤1
😘 #ቃል 😘
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ አራት (34)
«ምን… ከኔ ጋር ? አዎ» አለች ማሪዮን ። ሁለቱም ፀጥ አሉ፣ ረጂም ለመሰለ ጊዜ ። በመጨረሻ «እንተዋወቃለን ናንሲ ። ፒተርን አውቀዋለሁ ። ላንች ያደረገልሽ ህክምናም እጅግ የሚደነቅ ነው» አለች ማሪዮን ።
«ትንሽ ስህተት ሳይፈጠር አልቀረም መሰለኝ ። እኔ ናንሲ ሳልሆን ሜሪ…» ንግግሯን አልጨረሰችም ። ጉልበቷ ተሟጦ ሲወጣ ተሰማት፡፡ ባዶ ሆነች። አጥንት አልባ የሆነች ይመስል ተልፈሰፈሰች ። እንባ አነቃት ። እንደምንም ብላ ተነሳች ። ወደ መስኮቱ ሄዳ ጀርባዋን ለማሪዮን ሰጥታ ቆመች ። እና «ማን . . . እንዴት ልታውቂኝ ቻልሽ ?» አለች ። የተሰበረ ድምፅ ነበር ። ማሪዮን ርግጠኛ ሆነች ። የዛሬ ሁለት አመት የሰማችው የናንሲ ማክአሊስተር ድምፅ ብቅ አለ። «ማን ነገረሽ ? » አለች ሜሪ ደግማ በሚያስገድድ ድምፅ ። «ማንም አልነገረኝም ። ገመትኩ ። ግምቱ ለምን እንደመጣብኝም አላውቅም ። ሆኖም ገመትኩ ። ገና ቤን ስለሁኔታሽ መግለፅ ሲጀምር እሷ ናት? የሚል ጥያቄ መጣብኝ ። የነገረን ነገር ሁሉ ስለአንቺ ከማውቀው ጋር ሙሉ በሙሉ ሲመሳሰል ጊዜ ነው መሰል »
«እንዲያ ከሆነ ... » አለችና ዝም አለች፡፡ ማይክልም ያውቃል ማለት ነዋ! ልትል ነበር ። የተረገመ ልብ መቼ ነው ተስፋ እሚቆርጠው! መቼ ነው መጥላት የሚገባውን የሚጠላው ? «አሁንስ ለምን እዚህ ድረስ መጣሽ ? መኖሬን ስታውቂ ጊዜ ፈራሽ? ውል እማፈርስ መሰለሽ ? እና ውሉ ያልፈረሰ መሆኑን ልታስታውሺኝ ፈለግሽ ? »
«አይደለም ። በዚያ በኩል አልጠረጥርሽም ። ቃልሽን ማክበር እንደምትችይ አረጋግጫለሁ» አለች ማሪዮን ፤ እጅግ ያረጀሰው በመሰለ ድክም ባለና ደግነት በተሞላ ድምፅ «ላይሽ ነው የመጣሁ ። ላነጋግርሽ ምን እንደመሰልሽ ፤ ይመችሽ ፤ይክፋሽ ... ላይሽ ነው የመጣሁ። ላያት የመጣኋት ልጅ አንች ነሽ ማለት ከደፈርኩ ። ሌላውን ምክንያት እኔም በቅጡ አላውቀው»
«ለምን ? ይህን ያህል አመት ትዝ ሳልልሽ ቆይቼ ድንገት ምን አዲስ ስሜት ተፈጠረ ?» የሜሪ ድምፅ የሚናደፍ መርዛም ነበር ። ማሪዮን ምንም አልመለሰችም ።
«ድንገት ምን ነገር ተፈጠረ ሚስ ሂልያርድ? ወይስ የግሬግሰንን ሥራ ተመልክቶ ማድነቅ ስላማረሽ ይሆን ? እንዲያ ከሆነ ... እንዴት ነው በአራት መቶ ሺ ዶላር ክፍያ ያሰራሻት አሻንጉሊት እምታምር አትመስልሽም? አራት መቶ ሺ ዶላር ቢወጣም አይቆጭ! የሚያሰኝ ነው?. . . የሚያሰኝ ነው ወይ ? ምነው ጭጭ አልሽ ? ጥያቄየን መልሺልኝ እንጂ… ደስ አለሽ ወይስ ከፋሽ?» ደስ ቢለኝ ኖሮ እንዴት ደስ ይለኝ ነበር ! አለች ማሪዮን በሀሳቧ ። ድንገት ደስ ቢለኝ የሚል ምኞት አደረባት ። ግን የሰራችው ነገር ውጤት መጥፎ ፤ ያደረገችው ነገር አስቀያሚ እንደሆነ ወለል ብሎ ታያት። ለዚህ ገጽታ ሁሉም ብዙ እንደከፈሉ ግን ያ ሁሉ ከንቱ እንደነበረ ተገነዘበች ። ይህ ፀፀት ነው። ፀፀት ግን ዋጋ የለውም ። ሁሉም ነገር ካለፈ ፤ ምንጩ ከነጠፈ በኋላ ቢፀፀቱት ምን ፋይዳ አለው? ማይክልን አሰበች ። ናንሲን ተመለከተች ። እሷን ራሷንም ። አንዳቸውም እንደነበሩ አይደሉም። ሁሉም ሌላ ሆነዋል ። ማይክልና ናንሲ። ሁሉም ነገር ሩቅ ከሩቅ ፤ የራቀ ሩቅ ሆኗል ። ለነሱም ። አንዳቸው ላንዳቸው ይሆኑ ዘንድ የማይቻል ነው ። ህልማቸውን በግል ሲያባርሩ ፤ ሊያገኙት ከቻሉ ሌላ ቦታ ቢፈልጉት ይሻላል ። «ናንሲ በጣም ቆንጆ ልጅ ሆነሻል ኮ» አለች ማሪዮን ፤ ወንድ አይጠፋም ለማለት ያህል ። «ቆንጆ ስላልሺኝ አመሰግናለሁ ይገባኛል ። ፒተር ውብ የእጅ ሥራ ቀርጾአል ። ግን ይህን ለማድረግ የገባሁበት ውል…. ከሰይጣን ጋር እንደመዋዋል የሚቆጠር ነው ። ቆንጆ ፊት ለማግኘት ሕይወትን መሰዋእት ማቅረብ ። ሌላ ትርጉም የለውም»
«ሰይጣኒቷም እኔ እንደሆንኩ አውቃለሁ» አለች ማሪዮን በሀዘን በተሰበረ ድምፅ «ምንም እንኳ ዛሬ ይህን ላንች መንገር ርኩስ ተግባር እንደሆነ ቢገባኝም ፡ ያኔ ናንሲ ፣ያኔ ቃል እንድ ትገቢልኝ ሳግባባሽ ፤ ሊሆን የሚገባውን ነገር ያደረግኩ መስሎኝ ነበር»
«አሁንስ ? አሁንስ ምን ይመስልሻል ? » አለች ፊት ለፊት በድፍረት እየተፋጠጠቻት «አሁንስ ምን ይሰማሻል ፤ሚስ ሂልያርድ ? ለመሆኑ ማይክል ደስተኛ ነው? እኔን እንደ አሮጌ ዕቃ ወርውረሸ ከጣልሽለት በኋላ ደስ ብሎት መኖር ጀመረ? ተልእኮሽ ሰመረልሽ ? » ስሜት ተናነቃት ። በጥፊ ልታልሳት ፈለገች ። ይህን የወይዛዝርት ልብሷን እንደተጎናፀፈች ገፍትሬ ጥዬ መሬት ለመሬች ብጎትታት ! ስትል ተመኘች ። «የለም የለም አንዱም ነገር አልተሳካልኝም ። ማይክል ደስተኛ አይደለም ። ከጊዜ ጊዜ ሁሉን ነገር ይረሳል ፤ ሀዘኑ ይሽራል በሚል ተስፋ ስጽናና ቆየሁ ። ግን አልሆነም ። አንችም እንዲያ እንደምትሆኝ ተስፋ ነበረኝ ።ግን ሳይሽ ነሽ ሀዘንሽ አልሻረም ምንም ነገር አልተረሳሽም ። ወይስ የተሻለ መንገድ መርጠሻል? ብዬ እጠይቅሽ ነበር ። ሆኖም መብት ያለኝ አይመስለኝም »
«ልክ ነሽ። ያን ጥያቄ ለማቅረብ ምንም መብት የለሽም ማይክል ሚስት አገባ ወይስ ?»
«አግብቷል» አለች ማሪዮን ። ሜሪ ክው ብላ ደነገጠች ። ኡኡ ! ብላ ለመጮህ ፈለገች ። ድምጹን አፍና አስቀረችው ። ያ ድምፅ ከጉሮሮዋ ሳይወጣ ሟሟ። «አዎን ፤ ሜሪ ። አግብቷል ። ሥራውን አግብቶ ትዳር መስርቷል ። የሚበላው የሚጠጣው የሚተኛው እሥራው ላይ ሆኗል። ትንፋሹ ሳይቀር ሥራው ሆኗል ።» ሜሪ ትንፋሽዋ መለስ አለ። «ከሥራው ላይ ንቅንቅ አይልም ። በሥራው ውስጥ ሰምጦ ዘለአለም አለሙን ሊያሳልፍ የፈለገ እስኪመስል ። አብረን እንኖራለን ይባላል እንጂ መልኩን የማየው ከዝንተ አለም አንድ ጊዜ ነው»
የት አባሽ አንች ውሻ !እንኳን ! አለች ሜሪ በሀሳቧ «እንዲያ ካልሽ ፤ ስህተት መስራትሽን ተገንዝበሻል ማለት ነው። ማለት በአለም ላይ ካለው ሀብትና ማንኛውም ድንቅ ነገር አብልጨ እወደው እንደነበር ታውቂያለሽ ? » ይህን ብላ ስታበቃ በኃሳቧ ከዚህ ፊቴ በስተቀር…. ከፊቴ በስተቀር ! አምላኬ ምናልኩህ «በስተቀር» እንድል አደረግከኝ! «አውቃለሁ ። አውቅ ነበር ። ግን ፍቅር ነውና ያልፋል ብዬ ገመትኩ»
«ሆነ ? ግምቱ ትክክል ነበር ? ረሳኝ ? »
«እንጃ ። ምናልባት አልፎለት ይሆናል ። ስምሽን አንስቶ አያውቅም መቼም»
«በመጀመሪያ ወይም መቼም ቢሆን የት እንዳለሁ ለማወቅ ሙከራ አድርጎ ነበር ?» ማሪዮን በአሉታ ራሷን እየነቀነቀች «እልሞከረም» አለች ። ይህን ትበላት እንጂ ለማይክል ናንሲ ሞታለች እንዳለችው አልነገረቻትም ። «ያ ከሆነ ታዲያ ለምን ጠራሽኝ? እኔን የማየት ጉጉትሽ እንዲረካ ? ….. ፎቶግራፎች እንዳሳይሽ?. . . ለምን ?»
«እኔም ለምን እንደፈለግኩሽ አላውቅም ፤ ናንሲ ። ይቅርታ... ሜሪ ። ቅድም እንደነገርኩሽ ነው ። አላውቀውም።... በግድ እዘኑልኝ ማለት ፤ ወይም ሆደባሻነት ይመስላል እንጂ ደኅና አይደለሁም ። መሞቻዬ ሩቅ አይደለም ። እመቃብሬ አፋፍ ላይ የቆምኩ ይመስለኛል»
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ አራት (34)
«ምን… ከኔ ጋር ? አዎ» አለች ማሪዮን ። ሁለቱም ፀጥ አሉ፣ ረጂም ለመሰለ ጊዜ ። በመጨረሻ «እንተዋወቃለን ናንሲ ። ፒተርን አውቀዋለሁ ። ላንች ያደረገልሽ ህክምናም እጅግ የሚደነቅ ነው» አለች ማሪዮን ።
«ትንሽ ስህተት ሳይፈጠር አልቀረም መሰለኝ ። እኔ ናንሲ ሳልሆን ሜሪ…» ንግግሯን አልጨረሰችም ። ጉልበቷ ተሟጦ ሲወጣ ተሰማት፡፡ ባዶ ሆነች። አጥንት አልባ የሆነች ይመስል ተልፈሰፈሰች ። እንባ አነቃት ። እንደምንም ብላ ተነሳች ። ወደ መስኮቱ ሄዳ ጀርባዋን ለማሪዮን ሰጥታ ቆመች ። እና «ማን . . . እንዴት ልታውቂኝ ቻልሽ ?» አለች ። የተሰበረ ድምፅ ነበር ። ማሪዮን ርግጠኛ ሆነች ። የዛሬ ሁለት አመት የሰማችው የናንሲ ማክአሊስተር ድምፅ ብቅ አለ። «ማን ነገረሽ ? » አለች ሜሪ ደግማ በሚያስገድድ ድምፅ ። «ማንም አልነገረኝም ። ገመትኩ ። ግምቱ ለምን እንደመጣብኝም አላውቅም ። ሆኖም ገመትኩ ። ገና ቤን ስለሁኔታሽ መግለፅ ሲጀምር እሷ ናት? የሚል ጥያቄ መጣብኝ ። የነገረን ነገር ሁሉ ስለአንቺ ከማውቀው ጋር ሙሉ በሙሉ ሲመሳሰል ጊዜ ነው መሰል »
«እንዲያ ከሆነ ... » አለችና ዝም አለች፡፡ ማይክልም ያውቃል ማለት ነዋ! ልትል ነበር ። የተረገመ ልብ መቼ ነው ተስፋ እሚቆርጠው! መቼ ነው መጥላት የሚገባውን የሚጠላው ? «አሁንስ ለምን እዚህ ድረስ መጣሽ ? መኖሬን ስታውቂ ጊዜ ፈራሽ? ውል እማፈርስ መሰለሽ ? እና ውሉ ያልፈረሰ መሆኑን ልታስታውሺኝ ፈለግሽ ? »
«አይደለም ። በዚያ በኩል አልጠረጥርሽም ። ቃልሽን ማክበር እንደምትችይ አረጋግጫለሁ» አለች ማሪዮን ፤ እጅግ ያረጀሰው በመሰለ ድክም ባለና ደግነት በተሞላ ድምፅ «ላይሽ ነው የመጣሁ ። ላነጋግርሽ ምን እንደመሰልሽ ፤ ይመችሽ ፤ይክፋሽ ... ላይሽ ነው የመጣሁ። ላያት የመጣኋት ልጅ አንች ነሽ ማለት ከደፈርኩ ። ሌላውን ምክንያት እኔም በቅጡ አላውቀው»
«ለምን ? ይህን ያህል አመት ትዝ ሳልልሽ ቆይቼ ድንገት ምን አዲስ ስሜት ተፈጠረ ?» የሜሪ ድምፅ የሚናደፍ መርዛም ነበር ። ማሪዮን ምንም አልመለሰችም ።
«ድንገት ምን ነገር ተፈጠረ ሚስ ሂልያርድ? ወይስ የግሬግሰንን ሥራ ተመልክቶ ማድነቅ ስላማረሽ ይሆን ? እንዲያ ከሆነ ... እንዴት ነው በአራት መቶ ሺ ዶላር ክፍያ ያሰራሻት አሻንጉሊት እምታምር አትመስልሽም? አራት መቶ ሺ ዶላር ቢወጣም አይቆጭ! የሚያሰኝ ነው?. . . የሚያሰኝ ነው ወይ ? ምነው ጭጭ አልሽ ? ጥያቄየን መልሺልኝ እንጂ… ደስ አለሽ ወይስ ከፋሽ?» ደስ ቢለኝ ኖሮ እንዴት ደስ ይለኝ ነበር ! አለች ማሪዮን በሀሳቧ ። ድንገት ደስ ቢለኝ የሚል ምኞት አደረባት ። ግን የሰራችው ነገር ውጤት መጥፎ ፤ ያደረገችው ነገር አስቀያሚ እንደሆነ ወለል ብሎ ታያት። ለዚህ ገጽታ ሁሉም ብዙ እንደከፈሉ ግን ያ ሁሉ ከንቱ እንደነበረ ተገነዘበች ። ይህ ፀፀት ነው። ፀፀት ግን ዋጋ የለውም ። ሁሉም ነገር ካለፈ ፤ ምንጩ ከነጠፈ በኋላ ቢፀፀቱት ምን ፋይዳ አለው? ማይክልን አሰበች ። ናንሲን ተመለከተች ። እሷን ራሷንም ። አንዳቸውም እንደነበሩ አይደሉም። ሁሉም ሌላ ሆነዋል ። ማይክልና ናንሲ። ሁሉም ነገር ሩቅ ከሩቅ ፤ የራቀ ሩቅ ሆኗል ። ለነሱም ። አንዳቸው ላንዳቸው ይሆኑ ዘንድ የማይቻል ነው ። ህልማቸውን በግል ሲያባርሩ ፤ ሊያገኙት ከቻሉ ሌላ ቦታ ቢፈልጉት ይሻላል ። «ናንሲ በጣም ቆንጆ ልጅ ሆነሻል ኮ» አለች ማሪዮን ፤ ወንድ አይጠፋም ለማለት ያህል ። «ቆንጆ ስላልሺኝ አመሰግናለሁ ይገባኛል ። ፒተር ውብ የእጅ ሥራ ቀርጾአል ። ግን ይህን ለማድረግ የገባሁበት ውል…. ከሰይጣን ጋር እንደመዋዋል የሚቆጠር ነው ። ቆንጆ ፊት ለማግኘት ሕይወትን መሰዋእት ማቅረብ ። ሌላ ትርጉም የለውም»
«ሰይጣኒቷም እኔ እንደሆንኩ አውቃለሁ» አለች ማሪዮን በሀዘን በተሰበረ ድምፅ «ምንም እንኳ ዛሬ ይህን ላንች መንገር ርኩስ ተግባር እንደሆነ ቢገባኝም ፡ ያኔ ናንሲ ፣ያኔ ቃል እንድ ትገቢልኝ ሳግባባሽ ፤ ሊሆን የሚገባውን ነገር ያደረግኩ መስሎኝ ነበር»
«አሁንስ ? አሁንስ ምን ይመስልሻል ? » አለች ፊት ለፊት በድፍረት እየተፋጠጠቻት «አሁንስ ምን ይሰማሻል ፤ሚስ ሂልያርድ ? ለመሆኑ ማይክል ደስተኛ ነው? እኔን እንደ አሮጌ ዕቃ ወርውረሸ ከጣልሽለት በኋላ ደስ ብሎት መኖር ጀመረ? ተልእኮሽ ሰመረልሽ ? » ስሜት ተናነቃት ። በጥፊ ልታልሳት ፈለገች ። ይህን የወይዛዝርት ልብሷን እንደተጎናፀፈች ገፍትሬ ጥዬ መሬት ለመሬች ብጎትታት ! ስትል ተመኘች ። «የለም የለም አንዱም ነገር አልተሳካልኝም ። ማይክል ደስተኛ አይደለም ። ከጊዜ ጊዜ ሁሉን ነገር ይረሳል ፤ ሀዘኑ ይሽራል በሚል ተስፋ ስጽናና ቆየሁ ። ግን አልሆነም ። አንችም እንዲያ እንደምትሆኝ ተስፋ ነበረኝ ።ግን ሳይሽ ነሽ ሀዘንሽ አልሻረም ምንም ነገር አልተረሳሽም ። ወይስ የተሻለ መንገድ መርጠሻል? ብዬ እጠይቅሽ ነበር ። ሆኖም መብት ያለኝ አይመስለኝም »
«ልክ ነሽ። ያን ጥያቄ ለማቅረብ ምንም መብት የለሽም ማይክል ሚስት አገባ ወይስ ?»
«አግብቷል» አለች ማሪዮን ። ሜሪ ክው ብላ ደነገጠች ። ኡኡ ! ብላ ለመጮህ ፈለገች ። ድምጹን አፍና አስቀረችው ። ያ ድምፅ ከጉሮሮዋ ሳይወጣ ሟሟ። «አዎን ፤ ሜሪ ። አግብቷል ። ሥራውን አግብቶ ትዳር መስርቷል ። የሚበላው የሚጠጣው የሚተኛው እሥራው ላይ ሆኗል። ትንፋሹ ሳይቀር ሥራው ሆኗል ።» ሜሪ ትንፋሽዋ መለስ አለ። «ከሥራው ላይ ንቅንቅ አይልም ። በሥራው ውስጥ ሰምጦ ዘለአለም አለሙን ሊያሳልፍ የፈለገ እስኪመስል ። አብረን እንኖራለን ይባላል እንጂ መልኩን የማየው ከዝንተ አለም አንድ ጊዜ ነው»
የት አባሽ አንች ውሻ !እንኳን ! አለች ሜሪ በሀሳቧ «እንዲያ ካልሽ ፤ ስህተት መስራትሽን ተገንዝበሻል ማለት ነው። ማለት በአለም ላይ ካለው ሀብትና ማንኛውም ድንቅ ነገር አብልጨ እወደው እንደነበር ታውቂያለሽ ? » ይህን ብላ ስታበቃ በኃሳቧ ከዚህ ፊቴ በስተቀር…. ከፊቴ በስተቀር ! አምላኬ ምናልኩህ «በስተቀር» እንድል አደረግከኝ! «አውቃለሁ ። አውቅ ነበር ። ግን ፍቅር ነውና ያልፋል ብዬ ገመትኩ»
«ሆነ ? ግምቱ ትክክል ነበር ? ረሳኝ ? »
«እንጃ ። ምናልባት አልፎለት ይሆናል ። ስምሽን አንስቶ አያውቅም መቼም»
«በመጀመሪያ ወይም መቼም ቢሆን የት እንዳለሁ ለማወቅ ሙከራ አድርጎ ነበር ?» ማሪዮን በአሉታ ራሷን እየነቀነቀች «እልሞከረም» አለች ። ይህን ትበላት እንጂ ለማይክል ናንሲ ሞታለች እንዳለችው አልነገረቻትም ። «ያ ከሆነ ታዲያ ለምን ጠራሽኝ? እኔን የማየት ጉጉትሽ እንዲረካ ? ….. ፎቶግራፎች እንዳሳይሽ?. . . ለምን ?»
«እኔም ለምን እንደፈለግኩሽ አላውቅም ፤ ናንሲ ። ይቅርታ... ሜሪ ። ቅድም እንደነገርኩሽ ነው ። አላውቀውም።... በግድ እዘኑልኝ ማለት ፤ ወይም ሆደባሻነት ይመስላል እንጂ ደኅና አይደለሁም ። መሞቻዬ ሩቅ አይደለም ። እመቃብሬ አፋፍ ላይ የቆምኩ ይመስለኛል»
👍15
ማሪዮን ይህን ብላ ወደ ሜሪ አዳምሰን ዞረች ። ያኔም ሜሪን ማሪዮን ሞቷ ስለቀረበ ምን ያህል እንዳዘነች አየች ። ሜሪን ስትመለከት ማሪዮን ለምን ነገርኳት? የሚል ብስጭት ገባት ። በዚያም አለ በዚህ ሜሪ ለማሪዮን ቅንጣት ያህል ሀዘን አልተሰማትም ። ማሪዮንን ለረጅም ጊዜ ትኩር ብላ ስትመለከት ከቆየች በኋላ ፤ «እንዲህ ያለውን ነገር በመስማቴ አዝናለሁ ፤ ሚስዝ ሂልያርድ ። ግን ደግሞ እኔም ሙት ነኝ። ከሞትኩ ሁለት አመት ሞላኝ ። እንደሰማሁት ከሆነ አንድ ልጅሺም ሞቷል ። ሁለት ነፍስ አጥፍተሻል ማለት ነው ። የሁለት ሰው ደም አለብሽ ። እና እውነቱን መናገር ካለብኝ የሆነው ነገር ቢደርስብሽ ፤ እኔ ሳልሆን ልቤ ሀዘን ሊፀንስ አይችልም። መቼም በመንገድ ላይ ስሄድ ወንዶች አየት አድርገውኝ ፊቴ መበላሸቱን ብቻ ሳይሆን ጣረሞት መምሰሌን አይተው እንዳይሸሹኝ አድርገሽልኛል ። በዚህ ላመሰግንሽ ፤ይህን ውለታ ልቆጥርልሽ ይገባኝ ነበር ግን አልችልም ። ብዙ ብዙ ነገር ሊሰማኝ ይገባ ነበር ብዬ አምናለሁ ። ግን ምንም አይሰማኝም ። ብቻ ልጅሽን እንዲያ እንዳደረግሽው በመገንዘብሽ በዚያ ብቻ ትንሽ ሀዘን ቢጤ ይሰማኝ ይሆናል ። ሌላ የለም»
ማሪዮን ፀጥ ብላ ራሷን በአወንታ እየነቀነቀች የሜሪን ወቀሳ በፀጋ ተቀበለች። ለምን? ሜሪ ያለችው ሁሉ እውነት እንደሆነ ራሷ ደርሳበታለች ! ዛሬ አይደለም ። ከሆነ በኋላ ለራሷ አትመነው ፡ አትቀበለው እንጂ ልቧ የሰራችውን ጥፋት አውቆታል። ቢያንስ በማይክል ላይ የፈፀመችው በደል ያለ ጥርጥር ግብቷታል። ከገባትም ቆይቷል ። ምናልባት ሜሪ ለማየት የፈለገችውም ፤ በሷ (ሜሪ) በኩል የተሻለ ሕይወት አይ ይሆን) ስትል ተስፋ በማድረግ ሊሆን ይችላል ። «ልክ ነሽ የኔ ልጅ። ልክ ነሽ። ምን ብ....ምን ብዬ ልንገርሽ….. የምናገረውም የለኝ»
«ደህና ሁኝ ብትይኝ ደግ ነው» አለች ሜሪ።
ይህን ብላ ካፖርቷንና ፎቶግራፍ መያዣዋን አነሳችና ወደ በሩ አመራች ። በሩን ለመክፈት እጄታውን እንደያዘች አንገቷን ደፍታ ፣፤ እንባዋ ተንቆርዝዞ ለጥቂት ጊዜ ቆማ ቆዘመች ። ቀስ ብላ ወደ ክፍሉ ውስጥ ዞረች ። ያኔም የማሪዮን ሂልያርድ ፊት እንባ በእንባ ሆኖ ተመለከተች ። ማሪዮን በራሷ ስቃይ ተለጉማ ነበርና አንዲት ቃል ልትተነፍስ አልቻለችም ። ወጣቷ ሜሪ ግን እንደምንም ሳጓንና ከላይ ከላይ ሲላት የጀመረ ትንፋሽዋን ተቆጣጥራ «ሚስዝ ሂልያርድ ደህና ሁኝ ። ለማይክል...ፍ...ፍቅ የፍቅር ሰላምታዬን አቅርቢልኝ» አለች ። ይህን ተናግራ በሩን ከፍታ ወጣች ።
ማሪዮን ሂልያርድ ግን ካለችበት ንቅንቅ ማለት አልተቻላትም ። ልቧ እየዘለለ ሳንባዋን ሲደበድበው ከፍተኛ የሀመም ስቃይ ለቀቀባት ። ከላይ ከላይ እየተነፈሰች ፤ መጥሪያ ደወሉ ወዳለበት እየተንቦራቸች ሄደች ። ያን መጥሪያ ብትነካው አንድ ሰው አንዲት ሠራተኛ እንደምትደርስላት ታውቃለች ። እንደምንም ደረሰች ። እንደምንም መጥሪያውን አንዴ ብቻ ተጫነችው። ከዚያ በኋላ ሁሉም ነገር ጨለማ ሆነ «
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
ማሪዮን ፀጥ ብላ ራሷን በአወንታ እየነቀነቀች የሜሪን ወቀሳ በፀጋ ተቀበለች። ለምን? ሜሪ ያለችው ሁሉ እውነት እንደሆነ ራሷ ደርሳበታለች ! ዛሬ አይደለም ። ከሆነ በኋላ ለራሷ አትመነው ፡ አትቀበለው እንጂ ልቧ የሰራችውን ጥፋት አውቆታል። ቢያንስ በማይክል ላይ የፈፀመችው በደል ያለ ጥርጥር ግብቷታል። ከገባትም ቆይቷል ። ምናልባት ሜሪ ለማየት የፈለገችውም ፤ በሷ (ሜሪ) በኩል የተሻለ ሕይወት አይ ይሆን) ስትል ተስፋ በማድረግ ሊሆን ይችላል ። «ልክ ነሽ የኔ ልጅ። ልክ ነሽ። ምን ብ....ምን ብዬ ልንገርሽ….. የምናገረውም የለኝ»
«ደህና ሁኝ ብትይኝ ደግ ነው» አለች ሜሪ።
ይህን ብላ ካፖርቷንና ፎቶግራፍ መያዣዋን አነሳችና ወደ በሩ አመራች ። በሩን ለመክፈት እጄታውን እንደያዘች አንገቷን ደፍታ ፣፤ እንባዋ ተንቆርዝዞ ለጥቂት ጊዜ ቆማ ቆዘመች ። ቀስ ብላ ወደ ክፍሉ ውስጥ ዞረች ። ያኔም የማሪዮን ሂልያርድ ፊት እንባ በእንባ ሆኖ ተመለከተች ። ማሪዮን በራሷ ስቃይ ተለጉማ ነበርና አንዲት ቃል ልትተነፍስ አልቻለችም ። ወጣቷ ሜሪ ግን እንደምንም ሳጓንና ከላይ ከላይ ሲላት የጀመረ ትንፋሽዋን ተቆጣጥራ «ሚስዝ ሂልያርድ ደህና ሁኝ ። ለማይክል...ፍ...ፍቅ የፍቅር ሰላምታዬን አቅርቢልኝ» አለች ። ይህን ተናግራ በሩን ከፍታ ወጣች ።
ማሪዮን ሂልያርድ ግን ካለችበት ንቅንቅ ማለት አልተቻላትም ። ልቧ እየዘለለ ሳንባዋን ሲደበድበው ከፍተኛ የሀመም ስቃይ ለቀቀባት ። ከላይ ከላይ እየተነፈሰች ፤ መጥሪያ ደወሉ ወዳለበት እየተንቦራቸች ሄደች ። ያን መጥሪያ ብትነካው አንድ ሰው አንዲት ሠራተኛ እንደምትደርስላት ታውቃለች ። እንደምንም ደረሰች ። እንደምንም መጥሪያውን አንዴ ብቻ ተጫነችው። ከዚያ በኋላ ሁሉም ነገር ጨለማ ሆነ «
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍14❤1
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሦስት ወራት አለፈ" ካርለት በሐመር ቆይታዋ ብዙ ልምድ አካበተች ያልጠበቀችውንም እርካታ አገኘች ካርለት ከሎን ወደ ዲመካ፣ ቱርሚና ጂንካ ከተማ ሲሄዱ እግረ መንገዷን መኪና ማሽከርከር ስላስለመደችው መረዳዳት
ጀምረዋል" ካርለት በሐመር ኑሮዋ ዕቃዋን፣ ገንዘቧን ለማስቀመጥ የምትተማመነው በመኪናዋ ውስጥ ነው፤ በተለይም ሙዚቃ ለማዳመጥ መኪናዋ ከፍተኛ ጥቅም ትሰጣታለች" በነዳጅ በኩል እስከዚያ ወቅት ድረስ ችግር አላጋጠማትም፤ ካስፈለጋት ግን ጂንካ ከተማ ናፍታ ማግኘት እንደምትችል ተረድታለች።
የሐመር ሰማይ ጥርት ያለና አልፎ አልፎ ብን ያለ የጥጥ ባዘቶ መሳይ ዳመና ይታይበታል” የዝናቡ ወቅት፣ እምብዛም የሚያስተማምን ባይሆንም፣ ድንገት እያጓራ የሚያጋሽብ ጥልመት ዳመና ከታየ «አህያ» የማይችለው ዝናብ፣ መዓቱን ያወርደዋል" በዚህ
ወቅት የዕጽዋት ቅጠሎች እንደ በረዶ ብን ብን እያሉ ሲወድቁ ከብቶች ጅራታቸውን ሸጒጠው፣ ጆሮአቸውን ይጥላሉ።
በዚህ ወቅት፣ የከሰኬ ወንዝ ከአሸዋ በላይ ዛፍ ቅጠሉን እያተራመሰ፣ ባሕርይውን ይቀይርና በመደንፋት፣ እየተነሣ ይፈርጣል"
በዚያን ጊዜ ከሰኬ ወንዝና የሐመር ማኅበረሰብ፣ ከብቱ፣ ፍየሉ፣ ይኰራረፋሉ «አትድረስብኝ» አንመጣብህም ይባባላሉ"
አንድ ጊዜ፣ ካርለትና ከሎ መዝነቡን ሳያውቁ ከጂንካ ወደ ሻንቆ ሲሄዱ፣ ከሰኬ ወንዝን በመኪና ገብተው ሊሻገሩ ሲሉ መኪናዋ
በአሸዋው ተያዘች እነሱም ከመኪናቸው ወርደው በዶማና አካፋ
ለማውጣት ሲሞክሩ «ፉ..ፉ..ፉ.» የሚል ድምፅ ሰሙ። ቀና ሲሉ ደረቱን ገልብጦ፣ የሚጣደፍ ደራሽ ውኃ ተመለከቱ። ካርለትና ከሎ ብርክ ይዟቸው እንደ ሕፃን ልጅ ተንቦራቹ። ውኃው ግን ገሰገሰ ካርለትና ከሎ ዳር ላይ ሊደርሱ ሲሉ ውኃው ሲያጠናግራቸው
ተንገዳገዱ፤ ሳያስቡት እጅ ለእጅ መያያዛቸው ግን በጃቸውና ለትንሽ
አመለጡ። ደራሽ ውኃው መጀመሪያ መኪናዋን እያነቃነቀ ፈተሻት፣
ቀጥሎ በጎኗ፣ ከዚያም በጭንቅላቷ አቆማት።
«አምላኬ!» አለች፣ ካርለት መኪና የሚያገለባብጠው ውኃ እነሱን ቢያገኝ እንዴት ብትንትናቸውን እንደሚያወጣቸው እያሰበች።
ዛፉ «ቋ..ቀሽ.."ቀሽቀሽ...» ይላል፤ ግንድና ቅጠሉ ብቅ–ጥልቅ ይጫወታሉ፤ ውኃው፣ ሣር ቅጠሉን ያግበሰብሳል" መኪናዋ ጎማዋ ሲታይ ቆይታ በጎኗ ተጋደመች። ደራሽ የውኃ ሙላቱ ግን ለማንም
በሚያስገርም ሁኔታ እየቀነሰ፣ እየቀነሰ መጣና ጸጥ አለ። ካርለትና
ከሎ መኪናዋን ማውጣት ባለመቻላቸው፣ በየቦታው የተገነደሰውንም
ግንድ ለብቻቸው ማነቃነቅ የማይሞከር በመሆኑ፣ የሻንቆን መንደር
ኗሪ በእግር ሄደው ጠርተው፣ በስንት ችግር መኪናዋን ሊያወጡ
ቻሉ" ስለዚህ፣ ሐመር ላይ ዝናብ ሲዘንብ ከስኬ ሰው፣ ከብት፣ መኪና ሳይቀር ስለሚወስድና ስለሚያሰምጥ ምሱን አያጣም፤ ከብቱን፣ አራዊቱን፣ ሰውን...ድንገት ጠልፎ በመዋጥ የቆየ ልምድ አለው። ካርለትና ከሎ በቆይታቸው የተለያዩ ዕጽዋትንና ጥቅማቸውንም ተረድተዋል። ወንዴና ሴቴ ቃጫ ለገመድና ቤት ሥራ፣
ጠዬ ለዱላ፣ ሌልሜ ለቤት ሥራ፣ ፌጦ ለመፋቂያ፣፣ ኩንኩሮ ለተለያየ ጥቅም፣ ፊላና ሰንበሌጥ ለቤት ሥራ እንደሚውሉ ተረድተዋል።
በተረፈ ጨው ሊንባ፣ እንኮይ፣ ዘምባባ፣ አጋም፣ ጨዋንዛ፣ ግራር
ወዘተ የሐመርንና የአጐራባቾችን መሬቶች አስውበው ሲመለከቱ፣
ከመንፈስ እርካታው በተጨማሪ አንዳንዶቹን መጠቀም ችለዋል።
ካርለትና ከሎ ሻንቆ፣ ላላ፣ ወሮ፣ ዴንባይቴ፣ ዲመካ፣ ቱርሚ፣ ሚኖ፣ ሚርሻ፣ ሜን፣ አንጉዴ...መንደሮች ሲዘዋወሩ ከማኅበረሰቡ
አባላት ጋር ከሚገናኙበት አንዱ ሸፈሮ ቡና (የቡና ገለባ) የሚፈላበት
ወቅት ነው። የሐመር ቡና የሚፈላው በጀበና ሳይሆን በትልቅ እንስራ ነው ቡናው የሚጠጣው ንጋት ላይ ጀምሮ እስከ ረፋዱ ድረስ
ሲሆን፣ ያደረሰው ሁሉ መጠጣት ይችላል። አንድ ጊዜ ታዲያ፣ ካርለትና ከሎ ሻንቆ መንደር ለመጀመሪያ
ጊዜ ቡና ሊጠጡ ሄደው፣ ኦይጊ የተባለችው የመንደሩ ኗሪ ቤቷ ለመጡት እንግዶች በሾርቃ ከትልቅ ቅል ላይ በተከፈለ መጠጫ
ለሁሉም እንግዳ ስታድል፣ ለሁለቱም ሰጠቻቸው" ካርለት አንዱን
ሾርቃ እንደምንም ጨርሳ ‹ተገላገልኩ› ብላ፣ ሾርቃውን ለአይጊ አቀበለቻት በሐመር ባህል ሾርቃውን ቡናውን ለምትቀዳው ካቀበሉ
ድገሚኝ እንደማለት በመሆኑ፣ ኦይጊ ቡናውን በሾርቃ ሞልታ ለካርለት ሰጠቻት፤ «አምላኬ!» አለች ካርለት የመጀመሪያው ቋቅ
ሊላት ደርሶ፣ ሁለተኛውን ስታስታቅፋት።
ካርለት፣ ቡናውን መጠጣት ከበዳት። ቁጭ አድርጋ ትታ
እንዳትሄድ፣ ባህሉን መናቅ እንዳይሆንባት ሠግታ ስትጨነቅ ቡናውን
በያዘው ሾርቃ ላይ ዝንቦች እየገቡ ተንሳፈፉ። ካርለት፣ «ጥሩ አጋጣሚ» ብላ፣ እየሣቀች፣ «ዝንብ ገባበት» በላቸው አለችው ከሎን!
«ድፊው» ይሉኛል ብላ። እነሱ ግን፣ «ጠጭው ምንም አይልሽም፣
ይሄ የወተት እንጂ፣ የቆሻሻ ዝንብ አይደለም» አሏት። ካርለት፣ ሌላ አማራጭ ስላልነበራት የሚንሳፈፉትን ዝንቦች «እፍ» እያለች
ቡናውን ጠጥታ ጨረሰች።
ካርለት በሐመር ኑሮዋ በጣም የከበዳት ችግሯ ግን የሐመሮች የጊዜ ዕውቀት አለመኖር ነው። ካለፕሮግራሟ በተለይ በገበያ ቀን ዲመካ፣ ቱርሚ፣ ቀይአፈርና ጂንካ በመኪናዋ እንድትወስዳቸው
ይጠይቋትና መኪናዋ ውስጥ ዱቄት፣ ፍየል፣ በግ፣አረቄ፣ ማርና ቅቤ
ሰለሚጭኑ ሁሌ ትሳቀቃለች" አንዳንዴም አፍ አውጥታ! «አልሄድም» ትላለች።
ካርለት ምግብ፣ ደብዳቤ፣ መጽሔት፣ ከቤተሰብ ጋር የስልክ ግንኙነት ለማድረግ አዲሳባ ስትሄድም በጕዞው ከሎ ሆራ መኪና
ማሽከርከር ቢረዳትም ወንዝ እየሞላ፣ ጭቃ ሲይዛቸው ትማረራለች።
ካርለትና ከሎ ወደ አዲሳባ ሲሄዱ አልፎ አልፎ የሚላኩት መልእክት የተወሰነ ሲሆን አቡጀዲ፣ የላስቲክ ጫማ፣ ሸፈሮ ቡና
ሽጉጥ መሳይ መድኃኒት «ቴትራሳይክሊን ወይም ክሎሮፌኒኮል”ዋነኞቹ ናቸው"
ካርለት ሐመር ሦስት ወር ቆይታ አዲሳባ እንደሄደች፣ ከስቲቭ ጋር ተገናኙ። ስለ ሐመር ሕይወቷ፣ ስላየቻቸው ነገሮች፣ ስላጋጠማት ችግርና ስለ ወሰደችው የመፍትሔ እርምጃ አጫወተችው
ስቲቭ ከነገረችው ሌላ፣ ካርለት አንገቷና እጇ ላይ ያለውን ነገር ከማየቱም ባሻገር፣ ሳታቋርጥ ስታክ ተመለከታት» ከዚያም፣ «የኔ
ፍቅር፣ ይህን ያህል ለምን ራስሽን ለችግር ታጋልጫለሽ?» አላት
ስቲቭ"
«ችግር ስትል ምን ማለትህ ነው?»
«ይህ ደረሰብኝ እያልሽ ያወራሽኝ ሁሉኮ ጋሪ ላይ የተጫነ ጭነት ሳይሆን፣ አንች የተሸከምሽው ችግር ነው?» አላት"
«ስቲቭ፣ አንድ ሰው የምኖረው ትርጕም ያለው ሥራ ለመሥራት ነው ካለ፣ ሕይወቱም ትርጕም ያለው ይሆናል" ሌላው ደግሞ
(ምኖረው ለመሞት ነው› ካለ በውስጡ እውነትነት አለው” ሕይወቱ ግን፣ ትርጕም አልባ ይሆንበታል"
«ማንኛውም አጋጣሚ በየግላችን አእምሮ አመዛዝነን፣ መክረን፣
እናወጣ እናወርደዋለን፣ ቀጥሎ ጥሩ ወይም መጥፎ ትርጕም እንሰጥና ተግባሩ ላይ ያን አጋጣሚ እንጠላዋለን ወይም እንወደዋለን።
«አንዱ መኖርን ጥሩ ሥራ ለመሥራት እንደሆነ ተረድቶ ሲጥርI ሌላው ደግሞ መኖሩ ለመሞት መሆኑን አውቆ ተስፋው ይኰሰምናል"
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሦስት ወራት አለፈ" ካርለት በሐመር ቆይታዋ ብዙ ልምድ አካበተች ያልጠበቀችውንም እርካታ አገኘች ካርለት ከሎን ወደ ዲመካ፣ ቱርሚና ጂንካ ከተማ ሲሄዱ እግረ መንገዷን መኪና ማሽከርከር ስላስለመደችው መረዳዳት
ጀምረዋል" ካርለት በሐመር ኑሮዋ ዕቃዋን፣ ገንዘቧን ለማስቀመጥ የምትተማመነው በመኪናዋ ውስጥ ነው፤ በተለይም ሙዚቃ ለማዳመጥ መኪናዋ ከፍተኛ ጥቅም ትሰጣታለች" በነዳጅ በኩል እስከዚያ ወቅት ድረስ ችግር አላጋጠማትም፤ ካስፈለጋት ግን ጂንካ ከተማ ናፍታ ማግኘት እንደምትችል ተረድታለች።
የሐመር ሰማይ ጥርት ያለና አልፎ አልፎ ብን ያለ የጥጥ ባዘቶ መሳይ ዳመና ይታይበታል” የዝናቡ ወቅት፣ እምብዛም የሚያስተማምን ባይሆንም፣ ድንገት እያጓራ የሚያጋሽብ ጥልመት ዳመና ከታየ «አህያ» የማይችለው ዝናብ፣ መዓቱን ያወርደዋል" በዚህ
ወቅት የዕጽዋት ቅጠሎች እንደ በረዶ ብን ብን እያሉ ሲወድቁ ከብቶች ጅራታቸውን ሸጒጠው፣ ጆሮአቸውን ይጥላሉ።
በዚህ ወቅት፣ የከሰኬ ወንዝ ከአሸዋ በላይ ዛፍ ቅጠሉን እያተራመሰ፣ ባሕርይውን ይቀይርና በመደንፋት፣ እየተነሣ ይፈርጣል"
በዚያን ጊዜ ከሰኬ ወንዝና የሐመር ማኅበረሰብ፣ ከብቱ፣ ፍየሉ፣ ይኰራረፋሉ «አትድረስብኝ» አንመጣብህም ይባባላሉ"
አንድ ጊዜ፣ ካርለትና ከሎ መዝነቡን ሳያውቁ ከጂንካ ወደ ሻንቆ ሲሄዱ፣ ከሰኬ ወንዝን በመኪና ገብተው ሊሻገሩ ሲሉ መኪናዋ
በአሸዋው ተያዘች እነሱም ከመኪናቸው ወርደው በዶማና አካፋ
ለማውጣት ሲሞክሩ «ፉ..ፉ..ፉ.» የሚል ድምፅ ሰሙ። ቀና ሲሉ ደረቱን ገልብጦ፣ የሚጣደፍ ደራሽ ውኃ ተመለከቱ። ካርለትና ከሎ ብርክ ይዟቸው እንደ ሕፃን ልጅ ተንቦራቹ። ውኃው ግን ገሰገሰ ካርለትና ከሎ ዳር ላይ ሊደርሱ ሲሉ ውኃው ሲያጠናግራቸው
ተንገዳገዱ፤ ሳያስቡት እጅ ለእጅ መያያዛቸው ግን በጃቸውና ለትንሽ
አመለጡ። ደራሽ ውኃው መጀመሪያ መኪናዋን እያነቃነቀ ፈተሻት፣
ቀጥሎ በጎኗ፣ ከዚያም በጭንቅላቷ አቆማት።
«አምላኬ!» አለች፣ ካርለት መኪና የሚያገለባብጠው ውኃ እነሱን ቢያገኝ እንዴት ብትንትናቸውን እንደሚያወጣቸው እያሰበች።
ዛፉ «ቋ..ቀሽ.."ቀሽቀሽ...» ይላል፤ ግንድና ቅጠሉ ብቅ–ጥልቅ ይጫወታሉ፤ ውኃው፣ ሣር ቅጠሉን ያግበሰብሳል" መኪናዋ ጎማዋ ሲታይ ቆይታ በጎኗ ተጋደመች። ደራሽ የውኃ ሙላቱ ግን ለማንም
በሚያስገርም ሁኔታ እየቀነሰ፣ እየቀነሰ መጣና ጸጥ አለ። ካርለትና
ከሎ መኪናዋን ማውጣት ባለመቻላቸው፣ በየቦታው የተገነደሰውንም
ግንድ ለብቻቸው ማነቃነቅ የማይሞከር በመሆኑ፣ የሻንቆን መንደር
ኗሪ በእግር ሄደው ጠርተው፣ በስንት ችግር መኪናዋን ሊያወጡ
ቻሉ" ስለዚህ፣ ሐመር ላይ ዝናብ ሲዘንብ ከስኬ ሰው፣ ከብት፣ መኪና ሳይቀር ስለሚወስድና ስለሚያሰምጥ ምሱን አያጣም፤ ከብቱን፣ አራዊቱን፣ ሰውን...ድንገት ጠልፎ በመዋጥ የቆየ ልምድ አለው። ካርለትና ከሎ በቆይታቸው የተለያዩ ዕጽዋትንና ጥቅማቸውንም ተረድተዋል። ወንዴና ሴቴ ቃጫ ለገመድና ቤት ሥራ፣
ጠዬ ለዱላ፣ ሌልሜ ለቤት ሥራ፣ ፌጦ ለመፋቂያ፣፣ ኩንኩሮ ለተለያየ ጥቅም፣ ፊላና ሰንበሌጥ ለቤት ሥራ እንደሚውሉ ተረድተዋል።
በተረፈ ጨው ሊንባ፣ እንኮይ፣ ዘምባባ፣ አጋም፣ ጨዋንዛ፣ ግራር
ወዘተ የሐመርንና የአጐራባቾችን መሬቶች አስውበው ሲመለከቱ፣
ከመንፈስ እርካታው በተጨማሪ አንዳንዶቹን መጠቀም ችለዋል።
ካርለትና ከሎ ሻንቆ፣ ላላ፣ ወሮ፣ ዴንባይቴ፣ ዲመካ፣ ቱርሚ፣ ሚኖ፣ ሚርሻ፣ ሜን፣ አንጉዴ...መንደሮች ሲዘዋወሩ ከማኅበረሰቡ
አባላት ጋር ከሚገናኙበት አንዱ ሸፈሮ ቡና (የቡና ገለባ) የሚፈላበት
ወቅት ነው። የሐመር ቡና የሚፈላው በጀበና ሳይሆን በትልቅ እንስራ ነው ቡናው የሚጠጣው ንጋት ላይ ጀምሮ እስከ ረፋዱ ድረስ
ሲሆን፣ ያደረሰው ሁሉ መጠጣት ይችላል። አንድ ጊዜ ታዲያ፣ ካርለትና ከሎ ሻንቆ መንደር ለመጀመሪያ
ጊዜ ቡና ሊጠጡ ሄደው፣ ኦይጊ የተባለችው የመንደሩ ኗሪ ቤቷ ለመጡት እንግዶች በሾርቃ ከትልቅ ቅል ላይ በተከፈለ መጠጫ
ለሁሉም እንግዳ ስታድል፣ ለሁለቱም ሰጠቻቸው" ካርለት አንዱን
ሾርቃ እንደምንም ጨርሳ ‹ተገላገልኩ› ብላ፣ ሾርቃውን ለአይጊ አቀበለቻት በሐመር ባህል ሾርቃውን ቡናውን ለምትቀዳው ካቀበሉ
ድገሚኝ እንደማለት በመሆኑ፣ ኦይጊ ቡናውን በሾርቃ ሞልታ ለካርለት ሰጠቻት፤ «አምላኬ!» አለች ካርለት የመጀመሪያው ቋቅ
ሊላት ደርሶ፣ ሁለተኛውን ስታስታቅፋት።
ካርለት፣ ቡናውን መጠጣት ከበዳት። ቁጭ አድርጋ ትታ
እንዳትሄድ፣ ባህሉን መናቅ እንዳይሆንባት ሠግታ ስትጨነቅ ቡናውን
በያዘው ሾርቃ ላይ ዝንቦች እየገቡ ተንሳፈፉ። ካርለት፣ «ጥሩ አጋጣሚ» ብላ፣ እየሣቀች፣ «ዝንብ ገባበት» በላቸው አለችው ከሎን!
«ድፊው» ይሉኛል ብላ። እነሱ ግን፣ «ጠጭው ምንም አይልሽም፣
ይሄ የወተት እንጂ፣ የቆሻሻ ዝንብ አይደለም» አሏት። ካርለት፣ ሌላ አማራጭ ስላልነበራት የሚንሳፈፉትን ዝንቦች «እፍ» እያለች
ቡናውን ጠጥታ ጨረሰች።
ካርለት በሐመር ኑሮዋ በጣም የከበዳት ችግሯ ግን የሐመሮች የጊዜ ዕውቀት አለመኖር ነው። ካለፕሮግራሟ በተለይ በገበያ ቀን ዲመካ፣ ቱርሚ፣ ቀይአፈርና ጂንካ በመኪናዋ እንድትወስዳቸው
ይጠይቋትና መኪናዋ ውስጥ ዱቄት፣ ፍየል፣ በግ፣አረቄ፣ ማርና ቅቤ
ሰለሚጭኑ ሁሌ ትሳቀቃለች" አንዳንዴም አፍ አውጥታ! «አልሄድም» ትላለች።
ካርለት ምግብ፣ ደብዳቤ፣ መጽሔት፣ ከቤተሰብ ጋር የስልክ ግንኙነት ለማድረግ አዲሳባ ስትሄድም በጕዞው ከሎ ሆራ መኪና
ማሽከርከር ቢረዳትም ወንዝ እየሞላ፣ ጭቃ ሲይዛቸው ትማረራለች።
ካርለትና ከሎ ወደ አዲሳባ ሲሄዱ አልፎ አልፎ የሚላኩት መልእክት የተወሰነ ሲሆን አቡጀዲ፣ የላስቲክ ጫማ፣ ሸፈሮ ቡና
ሽጉጥ መሳይ መድኃኒት «ቴትራሳይክሊን ወይም ክሎሮፌኒኮል”ዋነኞቹ ናቸው"
ካርለት ሐመር ሦስት ወር ቆይታ አዲሳባ እንደሄደች፣ ከስቲቭ ጋር ተገናኙ። ስለ ሐመር ሕይወቷ፣ ስላየቻቸው ነገሮች፣ ስላጋጠማት ችግርና ስለ ወሰደችው የመፍትሔ እርምጃ አጫወተችው
ስቲቭ ከነገረችው ሌላ፣ ካርለት አንገቷና እጇ ላይ ያለውን ነገር ከማየቱም ባሻገር፣ ሳታቋርጥ ስታክ ተመለከታት» ከዚያም፣ «የኔ
ፍቅር፣ ይህን ያህል ለምን ራስሽን ለችግር ታጋልጫለሽ?» አላት
ስቲቭ"
«ችግር ስትል ምን ማለትህ ነው?»
«ይህ ደረሰብኝ እያልሽ ያወራሽኝ ሁሉኮ ጋሪ ላይ የተጫነ ጭነት ሳይሆን፣ አንች የተሸከምሽው ችግር ነው?» አላት"
«ስቲቭ፣ አንድ ሰው የምኖረው ትርጕም ያለው ሥራ ለመሥራት ነው ካለ፣ ሕይወቱም ትርጕም ያለው ይሆናል" ሌላው ደግሞ
(ምኖረው ለመሞት ነው› ካለ በውስጡ እውነትነት አለው” ሕይወቱ ግን፣ ትርጕም አልባ ይሆንበታል"
«ማንኛውም አጋጣሚ በየግላችን አእምሮ አመዛዝነን፣ መክረን፣
እናወጣ እናወርደዋለን፣ ቀጥሎ ጥሩ ወይም መጥፎ ትርጕም እንሰጥና ተግባሩ ላይ ያን አጋጣሚ እንጠላዋለን ወይም እንወደዋለን።
«አንዱ መኖርን ጥሩ ሥራ ለመሥራት እንደሆነ ተረድቶ ሲጥርI ሌላው ደግሞ መኖሩ ለመሞት መሆኑን አውቆ ተስፋው ይኰሰምናል"
👍25🥰2
«እኔም፣ ገጠመኜን ማውራቴ ለአንተ ፍርሃትን ሲፈጥርብህ፣ለእኔ ግን ፍቅር ስላሳደረብኝ፣ አብሬያቸው መኖሩን እመርጣለሁ»አለችውና ዝም ብላ ቆይታ፣ «አየህ ስቲቭ፣ ከርቀት ጠቦ የሚታይህ ድልድይ፣ ስትደርስበት ግን ሰፊ ነው» ብላ ጉንጩን ቆንጠጥ
አድርጋ፣ ከከሎ ጋር ጕዞዋን ቀጠለች"...
«በአባቴ ቆዳ ላይ ተኝተህ፣ ኩርኩፋህን እየበላህ፣ ሸፈሮ ቡናህ እየጠጣህ፣ ቀና ብለህ የቦርጆን (የአምላክን) ከዋክብት ተመልከት
አሸጋግረህ የሐመር ተራራዎችን ቃኝ በእበትና አፈር እያጌጥክ
የባንኪሞሮን ንቦች እየተንከባከብክ፣ ማሩን ብላ የአበቦችን መዓዛ
አሽትት"
«ጠላቶቻችን ከተራራው ግርጌ ናቸው" የአባቴ አጥንት ስለ ወጋቸው፣ ጠረኑ ስለሚያስበረግጋቸው፣ አይመጡብህም ሾልከው
ከገቡ ግን እበቴን ተቀብቼ፣ ንቤን በብብቴ ይዤ፣ ሁለት አፍ ጦሬ በመያዝ፣ አንተን አስከትዬ እሄድላቸዋለሁ የሀገሬ አዕዋፍ አውሬ፣ ያኔ ይጠግባሉ"
«ፀሐይ ከወደቀችበት ነገ ትነሣለች ጨረቃን ገፍትራ ጥላ ቦታዋን እስክትይዝ ግን ታጋሽ ሁን ጨለማን ተገን አድርገህ ተንኮል
አትሥራ» ከስኬ ከአሸዋ በላይ እስኪሞላ፣ የሰማይ ውኃን እየጠበቅህ
ጓሮህን እንድትቆፍር ልጃገረድህን እዘዝ"
«እጅህንና እግርህን በምላስህ እሠር የአባቴን ደንብና ባህል አክብር የታላላቆችህን ትእዛዝ ተቀበል ለጠላቶችህ የማትፈራ ወፍ በጥይት የምታስቀር፣ ጀግና ሁን። ካለበለዚያ፣ የአባቴን ደንብ
ሽረሃልና ደረቴን አስጌጥብሃለሁ (እገድልሃለሁ)።
«ተጫወት፣ በአባትህ ሜዳና ተራራ ተዘዋወር ከልጃገረዶ ጋር ዝለል ወተትና ደም ጠጣ ውለድ ከብትህን በበረት ሙላ
...የኔ ልጅ ጨርሻለሁ» ብለው የሚጠጡትን ሸፈሮ ቡና «ፕስስ...» እያሉ፣ በአራቱም ማዕዘን ያማትቡና የልጃቸውን ራስ
ዝቅ አድርገው የሸፈሮ ቡናውን ውኃ፣ «ፕስስ…» እያሉ ያርhፈክፉበታል።
ደልቲ ገልዲ፣ አባቱ ገና ከመሞታቸው በፊት ምርቃታቸውንና
አደራቸውን በገሐድ አሳያቸው ለምሳሌ ደልቲ ገልዲ ማጎ በረሃ
ከጓደኞቹ ጋር ወርዶ ካለምንም ስንቅ ለተወሰነ ጊዜ በረሃብ ቢሠቃይም፣ ከዚያ በኋላ ግን ሚዳቋም፣ ውድንቢትም፣ ድኩላም፣
እየገደሉ፤ ቋንጣውን በፀሐይ በማድረቅ እየተመገቡ ታላላቅ አራዊት
ሊገኝበት ከሚችልበት አካባቢ በመዘዋወር ሰንብተው፣ አንድ ቀን
ከማጎ ወንዝ ውስጥ ተነከረው እንዳሉ የአራዊት ዳና ሰሙ እየሮጡ በመውጣት ድምፁን ከሰሙበት አቅጣጫ በተቃራኒ ካለው ጫካ ውስጥ አደፈጡ" ሆኖም ግን፣ መሣሪያቸው ወዲያ ማዶ በመሆኑ ሲመኙት የነበረው ዕድል አመለጣቸው" የመጣው የጎሽ መንጋ ካለብዙ ችግር፣ እርስ በርስ እየተጠባበቀ በመጣበት አቅጣጫ
ሄዶ ተሠወረባቸው"
ደልቲም ሆነ ሌሎች ጓደኞቹ ወደ አደን ከመምጣታቸው በፊት ብዙ የአራዊት ጠባይ ተነግሯቸዋል" ጎሽ ከቈሰለ፣ የአቈሰለውን ሰው
እንደማይለቅ ያንን ሰው ባያገኘው እንኳን ዝንብ ቈስሉን እየበላ እንዳያስቸግረው ከወንዝ ውስጥ እየገባ እንደሚያደፍጥና ሌላ ሰው
ካገኘ ብጥስጥሱን በእልክ እንደሚያወጣው ሰምተዋል" ስለሆነም፣
ጎሽን ለመግደል ብልቱን ለይቶ መምታት እንደሚያስፈልግ፣ በመንጋው ላይ ከመተኰስም፣ ከመንጋው የተለየውን መግደል እንደ
ሚሻል፣ ተመከረዋል"
ግታ ማታ አንበሳና ነብር እንዳይተናኰላቸውም እሳት ማቀጣጠል እንደሚገባና እሳቱ ብዙ ጭስ እንዳይኖረውና ጫካውንና
ኣውሬዎችን የሚጠብቁት ዘበኞች አደጋ እንዳያደርሱባቸው
እንዲጠነቀቁ እባብ በተለይም የጠገበ ዘንዶ፣ አንዳንዴ ግንድ መስሎ እንደሚጠቀለልና ድንገት ቁጭ ካሉበት ለአደጋ
እንዳይጋለጡም ተመክረዋል።
አቅጣጫ ጠፍቶባቸው በተለይ በውኃ ጥም እንዳይጠቁም ልምምድና ውኃ የማያስጠማ መፋቂያ
እንዲይዙና በጨረቃና በከዋክብት አቅጣጫ እንዲንቀሳቀሱ፣
ተነግሯቸዋል" በተለይ ደግሞ፣ ሲጓዙ በጋራና በዘዴ እንዲሆንና፥ በተናጠል እንዳይጓዙ፣ ችግር ሆኖ ከተጠፋፉም እንቅልፍ ለመተኛት ሲፈልጉ ከመጋደም ይልቅ ቁጭ ብለው አንገትን ወደ ታች በመቅበር እንዲተኙ ከብትም ሆነ ሰው ላይ ጥላው ሲያርፍ ወገብ የሚያጣምመው አሞሯ ሲበር ሲታይ መደበቅና ከጥላው መራቅ ማስፈለጉን የግድ የሚቀርብ ከሆነም ተኵሶ ማባረር የሚሻል መሆኑን ተመክረዋል" በተረፈ አራዊት ከጠፉ የጀግንነታቸው ማረጋገጫ
ስለማይኖር ሴትና ወንዱን መለየት ስለማይቻል ዕድል ቀናኝ ብለው በብዛት መግደልና ማስደንበርም እንዳይፈጽሙ አደራ ተብለዋል።
ስለዚህ፣ የጎሹ መንጋ ተመልሶ ሄዶ ከአካባቢያቸው መራቁን
አረጋግጠው ከተደበቁበት ብቅ ሊሉ ሲሉ፣ ሴትና ወንድ አንበሳ ወደ ውኃው ሲመጡ አዩ ወዲያው ደንግጠው ተመልሰው ተደበቁ
በቁጥቋጦው ውስጥ ከርቀት ሲመለከቱ ደግሞ፣ ግንድና ቅጠሉ ሲርመሰመስ ተመለከቱ" ከዚያ አንበሶቹ እነሱ ወደ ተደበቁበት አቅጣጫ ሲመጡ፣ ሁሉም ወሽመጣቸው ተበጠሰ። ባዶ እጅ ከአንበሳ
ጋር መግጠም መቼም አይቻልም" ያውም ከሁለት አንበሳ" አንበሶቹ
ከኋላ ግንድና ቅጠሉን እያተረማመሱ የሚመጣውን አውሬ በጥርጣሬ እያዩ ስለሚሸሹ ደግነቱ እነሱን ፈርተው የሚንቀጠቀጡት
አላስተዋሉም። ስለዚህ፣ መንገዳቸውን ቀጠሉ።
ግንድና ቅጠሉ በሚሰባበርበትና በሚንሿሿበት አቅጣጫ
ሲመለከቱም፣ ለቍጥር የሚታክት ዝሆን ተመለከቱ" ስለ ዝሆን ደግሞ የሰሙት አለ" ዝሆን ከፍተኛ የማሽተት ችሎታ አለው" እስከ ብዙ ርቀት ጠረን ማሽተት ይችላል" ምናልባት ደግነቱ ነፋሱ ወደነሱ
አቅጣ ስለሆነ ጠረናቸው ላይደርሰው ይችላል" እንሽሽም ተባብለው ነበር" ግን፣ ከዚህ የዝሆን ረገጣና ወገራ ቢያልፉ፣ ከዚያ
ደግሞ የአንበሳ ክንድና የጎሽ ቀንድ ይጠብቃቸዋል" ሁሉም ያው እንዳቅሙ ሰባብሮ፣ መጨረሻው ሞት ነው" ስለዚህ መሸሹ
እንደማያዋጣ አመኑ።
የዝሆን መንጋው በኩንቢው ውኃውን ሰውነቱ ላይ እየረጨ! ውኃው ውስጥ ለብዙ ሰዓት ቆየ" አንድ ዝሆን እንዲያውም፣ ድንጋይ
ተደግፎ የተቀመጠውን ምንሽር ጠመንጃ ወደ ላይ በኩንቢው አንሥቶ አይቶ መልሶ አስቀመጠው የሱ ማደኛ መሆኑን ቢያውቅ
ኖሮ ወደ አመድነት ይለውጠው ነበርI ነገር ግን አላወቀም። ስለዚህ
ጠላቱን አንሥቶ መልሶ አስቀመጠው"
ደልቲና ጓደኞቹ ይህንና ይህን የመሳሰለውን ችግርና አደጋ በማኅበረሰባቸው የሚያገኙት የጀግንነት ክብርና ሙገሳ፣ ልብን
ያማልላል" ከወንድነት ማረጋገጫውም ውስጥ ዋናው በጠላትነት
የሚያዩትን የማኅበረሰብ አባል መግደል ሲሆን ከዚያ የሚቀጥለው ደግሞ አውራሪስ፣ ዝሆን፣ አንበሳ፣ ጎሽ፣ ቀጭኔ መግደሉ ነው።
በሌላ ቀን ደልቲ ገልዲና ጓደኞቹ አደናቸውን እንደ ጀመሩ፣ከመንጋ የተለዩ ጎሾችን ተመለከቱ" ሁሉም በየተራ እያነጣጠሩ ተኮሱ የቀሩት ጎሾች ሲሸሹ፣ ሦስት ጓደኞቹ ብቻ ሦስት ጎሽ ገደሉ።ከነዚያ ውስጥ ደግሞ የመጀመሪያው ገዳይ ደልቲ ገልዲ ሆነ።
የገደሉት፣ ባልገደሉት ላይ ጀግንነት ተሰማቸው አቅራሩ ፎከሩ።
ለአደን በሄዱ በሦስተኛው ሳምንታቸው ደግሞ ከርቀት የቀጭኔ መንጋ ተመለከቱ፣ ቀጭኔ ከርቀት ማየት ስለሚችል እንዲህ በዋዛ
ማደን ስለማይቻል እምብዛም ተስፋ አጡ" ገልዲ ግን፣ በየት እንደሄደ ጓደኞቹ እንኳ ሳያዩት ከቀጭኔዎቹ እይታ ውጭ በመሆን ሥራቸው ድረስ መጠጋት በመቻሉ፣ በምንሽር ጠመንጃው አንዱን ቀጭኔ በሁለት ጥይት ወርቹን በጥሶ አንበረከከው። ጓደኞቹ ሲመጡ ከቀጭኔው ጀርባ ላይ ወጥቶ ጠበቃቸው።
አድርጋ፣ ከከሎ ጋር ጕዞዋን ቀጠለች"...
«በአባቴ ቆዳ ላይ ተኝተህ፣ ኩርኩፋህን እየበላህ፣ ሸፈሮ ቡናህ እየጠጣህ፣ ቀና ብለህ የቦርጆን (የአምላክን) ከዋክብት ተመልከት
አሸጋግረህ የሐመር ተራራዎችን ቃኝ በእበትና አፈር እያጌጥክ
የባንኪሞሮን ንቦች እየተንከባከብክ፣ ማሩን ብላ የአበቦችን መዓዛ
አሽትት"
«ጠላቶቻችን ከተራራው ግርጌ ናቸው" የአባቴ አጥንት ስለ ወጋቸው፣ ጠረኑ ስለሚያስበረግጋቸው፣ አይመጡብህም ሾልከው
ከገቡ ግን እበቴን ተቀብቼ፣ ንቤን በብብቴ ይዤ፣ ሁለት አፍ ጦሬ በመያዝ፣ አንተን አስከትዬ እሄድላቸዋለሁ የሀገሬ አዕዋፍ አውሬ፣ ያኔ ይጠግባሉ"
«ፀሐይ ከወደቀችበት ነገ ትነሣለች ጨረቃን ገፍትራ ጥላ ቦታዋን እስክትይዝ ግን ታጋሽ ሁን ጨለማን ተገን አድርገህ ተንኮል
አትሥራ» ከስኬ ከአሸዋ በላይ እስኪሞላ፣ የሰማይ ውኃን እየጠበቅህ
ጓሮህን እንድትቆፍር ልጃገረድህን እዘዝ"
«እጅህንና እግርህን በምላስህ እሠር የአባቴን ደንብና ባህል አክብር የታላላቆችህን ትእዛዝ ተቀበል ለጠላቶችህ የማትፈራ ወፍ በጥይት የምታስቀር፣ ጀግና ሁን። ካለበለዚያ፣ የአባቴን ደንብ
ሽረሃልና ደረቴን አስጌጥብሃለሁ (እገድልሃለሁ)።
«ተጫወት፣ በአባትህ ሜዳና ተራራ ተዘዋወር ከልጃገረዶ ጋር ዝለል ወተትና ደም ጠጣ ውለድ ከብትህን በበረት ሙላ
...የኔ ልጅ ጨርሻለሁ» ብለው የሚጠጡትን ሸፈሮ ቡና «ፕስስ...» እያሉ፣ በአራቱም ማዕዘን ያማትቡና የልጃቸውን ራስ
ዝቅ አድርገው የሸፈሮ ቡናውን ውኃ፣ «ፕስስ…» እያሉ ያርhፈክፉበታል።
ደልቲ ገልዲ፣ አባቱ ገና ከመሞታቸው በፊት ምርቃታቸውንና
አደራቸውን በገሐድ አሳያቸው ለምሳሌ ደልቲ ገልዲ ማጎ በረሃ
ከጓደኞቹ ጋር ወርዶ ካለምንም ስንቅ ለተወሰነ ጊዜ በረሃብ ቢሠቃይም፣ ከዚያ በኋላ ግን ሚዳቋም፣ ውድንቢትም፣ ድኩላም፣
እየገደሉ፤ ቋንጣውን በፀሐይ በማድረቅ እየተመገቡ ታላላቅ አራዊት
ሊገኝበት ከሚችልበት አካባቢ በመዘዋወር ሰንብተው፣ አንድ ቀን
ከማጎ ወንዝ ውስጥ ተነከረው እንዳሉ የአራዊት ዳና ሰሙ እየሮጡ በመውጣት ድምፁን ከሰሙበት አቅጣጫ በተቃራኒ ካለው ጫካ ውስጥ አደፈጡ" ሆኖም ግን፣ መሣሪያቸው ወዲያ ማዶ በመሆኑ ሲመኙት የነበረው ዕድል አመለጣቸው" የመጣው የጎሽ መንጋ ካለብዙ ችግር፣ እርስ በርስ እየተጠባበቀ በመጣበት አቅጣጫ
ሄዶ ተሠወረባቸው"
ደልቲም ሆነ ሌሎች ጓደኞቹ ወደ አደን ከመምጣታቸው በፊት ብዙ የአራዊት ጠባይ ተነግሯቸዋል" ጎሽ ከቈሰለ፣ የአቈሰለውን ሰው
እንደማይለቅ ያንን ሰው ባያገኘው እንኳን ዝንብ ቈስሉን እየበላ እንዳያስቸግረው ከወንዝ ውስጥ እየገባ እንደሚያደፍጥና ሌላ ሰው
ካገኘ ብጥስጥሱን በእልክ እንደሚያወጣው ሰምተዋል" ስለሆነም፣
ጎሽን ለመግደል ብልቱን ለይቶ መምታት እንደሚያስፈልግ፣ በመንጋው ላይ ከመተኰስም፣ ከመንጋው የተለየውን መግደል እንደ
ሚሻል፣ ተመከረዋል"
ግታ ማታ አንበሳና ነብር እንዳይተናኰላቸውም እሳት ማቀጣጠል እንደሚገባና እሳቱ ብዙ ጭስ እንዳይኖረውና ጫካውንና
ኣውሬዎችን የሚጠብቁት ዘበኞች አደጋ እንዳያደርሱባቸው
እንዲጠነቀቁ እባብ በተለይም የጠገበ ዘንዶ፣ አንዳንዴ ግንድ መስሎ እንደሚጠቀለልና ድንገት ቁጭ ካሉበት ለአደጋ
እንዳይጋለጡም ተመክረዋል።
አቅጣጫ ጠፍቶባቸው በተለይ በውኃ ጥም እንዳይጠቁም ልምምድና ውኃ የማያስጠማ መፋቂያ
እንዲይዙና በጨረቃና በከዋክብት አቅጣጫ እንዲንቀሳቀሱ፣
ተነግሯቸዋል" በተለይ ደግሞ፣ ሲጓዙ በጋራና በዘዴ እንዲሆንና፥ በተናጠል እንዳይጓዙ፣ ችግር ሆኖ ከተጠፋፉም እንቅልፍ ለመተኛት ሲፈልጉ ከመጋደም ይልቅ ቁጭ ብለው አንገትን ወደ ታች በመቅበር እንዲተኙ ከብትም ሆነ ሰው ላይ ጥላው ሲያርፍ ወገብ የሚያጣምመው አሞሯ ሲበር ሲታይ መደበቅና ከጥላው መራቅ ማስፈለጉን የግድ የሚቀርብ ከሆነም ተኵሶ ማባረር የሚሻል መሆኑን ተመክረዋል" በተረፈ አራዊት ከጠፉ የጀግንነታቸው ማረጋገጫ
ስለማይኖር ሴትና ወንዱን መለየት ስለማይቻል ዕድል ቀናኝ ብለው በብዛት መግደልና ማስደንበርም እንዳይፈጽሙ አደራ ተብለዋል።
ስለዚህ፣ የጎሹ መንጋ ተመልሶ ሄዶ ከአካባቢያቸው መራቁን
አረጋግጠው ከተደበቁበት ብቅ ሊሉ ሲሉ፣ ሴትና ወንድ አንበሳ ወደ ውኃው ሲመጡ አዩ ወዲያው ደንግጠው ተመልሰው ተደበቁ
በቁጥቋጦው ውስጥ ከርቀት ሲመለከቱ ደግሞ፣ ግንድና ቅጠሉ ሲርመሰመስ ተመለከቱ" ከዚያ አንበሶቹ እነሱ ወደ ተደበቁበት አቅጣጫ ሲመጡ፣ ሁሉም ወሽመጣቸው ተበጠሰ። ባዶ እጅ ከአንበሳ
ጋር መግጠም መቼም አይቻልም" ያውም ከሁለት አንበሳ" አንበሶቹ
ከኋላ ግንድና ቅጠሉን እያተረማመሱ የሚመጣውን አውሬ በጥርጣሬ እያዩ ስለሚሸሹ ደግነቱ እነሱን ፈርተው የሚንቀጠቀጡት
አላስተዋሉም። ስለዚህ፣ መንገዳቸውን ቀጠሉ።
ግንድና ቅጠሉ በሚሰባበርበትና በሚንሿሿበት አቅጣጫ
ሲመለከቱም፣ ለቍጥር የሚታክት ዝሆን ተመለከቱ" ስለ ዝሆን ደግሞ የሰሙት አለ" ዝሆን ከፍተኛ የማሽተት ችሎታ አለው" እስከ ብዙ ርቀት ጠረን ማሽተት ይችላል" ምናልባት ደግነቱ ነፋሱ ወደነሱ
አቅጣ ስለሆነ ጠረናቸው ላይደርሰው ይችላል" እንሽሽም ተባብለው ነበር" ግን፣ ከዚህ የዝሆን ረገጣና ወገራ ቢያልፉ፣ ከዚያ
ደግሞ የአንበሳ ክንድና የጎሽ ቀንድ ይጠብቃቸዋል" ሁሉም ያው እንዳቅሙ ሰባብሮ፣ መጨረሻው ሞት ነው" ስለዚህ መሸሹ
እንደማያዋጣ አመኑ።
የዝሆን መንጋው በኩንቢው ውኃውን ሰውነቱ ላይ እየረጨ! ውኃው ውስጥ ለብዙ ሰዓት ቆየ" አንድ ዝሆን እንዲያውም፣ ድንጋይ
ተደግፎ የተቀመጠውን ምንሽር ጠመንጃ ወደ ላይ በኩንቢው አንሥቶ አይቶ መልሶ አስቀመጠው የሱ ማደኛ መሆኑን ቢያውቅ
ኖሮ ወደ አመድነት ይለውጠው ነበርI ነገር ግን አላወቀም። ስለዚህ
ጠላቱን አንሥቶ መልሶ አስቀመጠው"
ደልቲና ጓደኞቹ ይህንና ይህን የመሳሰለውን ችግርና አደጋ በማኅበረሰባቸው የሚያገኙት የጀግንነት ክብርና ሙገሳ፣ ልብን
ያማልላል" ከወንድነት ማረጋገጫውም ውስጥ ዋናው በጠላትነት
የሚያዩትን የማኅበረሰብ አባል መግደል ሲሆን ከዚያ የሚቀጥለው ደግሞ አውራሪስ፣ ዝሆን፣ አንበሳ፣ ጎሽ፣ ቀጭኔ መግደሉ ነው።
በሌላ ቀን ደልቲ ገልዲና ጓደኞቹ አደናቸውን እንደ ጀመሩ፣ከመንጋ የተለዩ ጎሾችን ተመለከቱ" ሁሉም በየተራ እያነጣጠሩ ተኮሱ የቀሩት ጎሾች ሲሸሹ፣ ሦስት ጓደኞቹ ብቻ ሦስት ጎሽ ገደሉ።ከነዚያ ውስጥ ደግሞ የመጀመሪያው ገዳይ ደልቲ ገልዲ ሆነ።
የገደሉት፣ ባልገደሉት ላይ ጀግንነት ተሰማቸው አቅራሩ ፎከሩ።
ለአደን በሄዱ በሦስተኛው ሳምንታቸው ደግሞ ከርቀት የቀጭኔ መንጋ ተመለከቱ፣ ቀጭኔ ከርቀት ማየት ስለሚችል እንዲህ በዋዛ
ማደን ስለማይቻል እምብዛም ተስፋ አጡ" ገልዲ ግን፣ በየት እንደሄደ ጓደኞቹ እንኳ ሳያዩት ከቀጭኔዎቹ እይታ ውጭ በመሆን ሥራቸው ድረስ መጠጋት በመቻሉ፣ በምንሽር ጠመንጃው አንዱን ቀጭኔ በሁለት ጥይት ወርቹን በጥሶ አንበረከከው። ጓደኞቹ ሲመጡ ከቀጭኔው ጀርባ ላይ ወጥቶ ጠበቃቸው።
👍19❤3🥰1
ደልቲ ገልዲ፣ አንድ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የጎሽና የቀጭኔ ገዳይ ሆነ። ወደ መንደራቸው ሲመለሱም የመንደሩ ልጃገረዶች
ለገዳዮቹ፣ በተለይም ለጎሽና ቀጭኔ ገዳዩ፣ ጨሌያቸውን በአንገቱ አጠለቁለት" በየዘመዶቹም እያቅራራና እየፎከረ ሲሄድ በግና
ፍየላቸውን እያረዱ፣ ጀርባው ላይ ደሙን አፈሰሱለት" ለወራት ያህል ምግቡ ደምና ወተት፣ ሥጋና ማር ሆነ" በዚህ ደግሞ፣ አባቱ
ልጃቸው እሳቸው እንኳን ያልቀናቸውን የጎሽና ቀጭኔ ገዳይ በመሆኑ ኮሩበት"
ብዙም ሳይቆይ ደልቲ ገልዲ በሐመርና በሙርሲ ማኅበረሰቦች መካከል በተፈጠረው ግጭትና ጦርነት እንደ ጉርኑክ እየዘለለ በመዋጋት፣ሁለት ሙርሲ ገድሎ መሣሪያቸውን በመማረኩ፣
ደረቱን በመተልተል፣ ራሱን በቀይና በነጭ አኖ አፈር በማስጌጥ፣በአንገቱ ከደረደረው ጨሌና በእጆቹ ካጠለቃቸው አንባሮች ሌላ
በወገቡ በታጠቀው ዝናርና መያዣዋ በሚያንጸባርቀው ቤልጅግ ጠመንጃ ከአካባቢው ኗሪ ልዩ ክብር ተጎናፀፈ የመንደሩ ልጃገረዶ ቀርቶ ከመንደሩ ራቅ ያሉትም ልጃገረዶች ሳይቀሩ በዝናው በቁመናው በመመሰጥ፣ የመጀመሪያውን እፍታ በየጫካው አጐረፉለት። ከሙርሲ ማኅበረሰብ በዘረፋቸው ከብቶችም መሣሪያ ገዛና በረቱን በከብት ሞላ። ሁለት ሚስት አግብቶ፣ የአባቱን ምኞትም
አሟላ። አባቱም ምንም እንኳን ከዳሰነች ማኅበረሰብ ጋር በተደረገው ጦርነት ቢሞቱም፣ የአባቱ ደም መላሽ ለመሆን ቻለ።
ደልቲ ገልዲ ስሙ እየገነነ ሲሄድ፣ የእሱም ልብ እያበጠ ሄደ።መቼም ሲመጣ በላይ በላይ ነውና፣ የላላና ሻንቆን መንደር ሰዎች ከብት እየሰበረ ያስቸገረ አንበሳ ለማደን ሁሉም በቡድን በቡድን ጫካ ሲገባ፣ እሱ ግን፣ «በእኔ በኩል ብቻዬን እበቃለሁ» ብሎ፣ ከነመሣሪ
ያው ለአደን ተሰማራ" ሁሉም ቦርጆን (አምላክን) እየተማፀነ፣ የአንበሳው ገዳይ ሆኖ እንደ አባያ በሬ ለመንጐማለል ሲመኝ
ፍለጋው ሲጧጧፍ ውሎ የጥይት ተኲስ ተሰማ፤ ወዲያው አንበሳው
ተገደለ ተባለና ገዳዩ ማን እንደሆነ አንዱ ሌላውን ሲጠይቅ፣ «ደልቲ
ገልዲ፣ የተኛ አንበሳ አልገድልም ብሎ ‹ጎፈር) ብሎ ቀስቅሶ አስነሥቶ፣ አጓርቶ ወደ እሱ ሲዘልበት በሚያስደንቅ ፍጥነት
መሣሪያውን አቀባብሎ፣ በሁለት ጥይት፣ ልሳኑን ዘጋው» ተባለ"
ልጃገረዶች፣ «ይኸዋ አላልኩሽም!» ሲባባሉ፣ «ኧረ እሱ ምኑ ነው ይሄን ያህል!» እያሉ ያናንቁ የነበሩት ጐረምሶች እንኳን
ሳይቀሩ፣ አንገታቸውን ደፉለት እረኞች፣ ልጃገረዶች በስሙ ዘፈኑለት፣ ሌላው ቀርቶ የመፎከሪያ በሬው ከሌሎች ከብቶች በልጦ
ተንጐማለለ" ደልቲ ገልዲ፣ ከግዙፉ የቡስካ ተራራ ይበልጥ ገዝፎ መታየት ጀመረ" በዚህ ሰሞን ነበር ሁለት እንግዶች ወደ
መንደራቸው የዘለቁት።....
💫ይቀጥላል💫
ለገዳዮቹ፣ በተለይም ለጎሽና ቀጭኔ ገዳዩ፣ ጨሌያቸውን በአንገቱ አጠለቁለት" በየዘመዶቹም እያቅራራና እየፎከረ ሲሄድ በግና
ፍየላቸውን እያረዱ፣ ጀርባው ላይ ደሙን አፈሰሱለት" ለወራት ያህል ምግቡ ደምና ወተት፣ ሥጋና ማር ሆነ" በዚህ ደግሞ፣ አባቱ
ልጃቸው እሳቸው እንኳን ያልቀናቸውን የጎሽና ቀጭኔ ገዳይ በመሆኑ ኮሩበት"
ብዙም ሳይቆይ ደልቲ ገልዲ በሐመርና በሙርሲ ማኅበረሰቦች መካከል በተፈጠረው ግጭትና ጦርነት እንደ ጉርኑክ እየዘለለ በመዋጋት፣ሁለት ሙርሲ ገድሎ መሣሪያቸውን በመማረኩ፣
ደረቱን በመተልተል፣ ራሱን በቀይና በነጭ አኖ አፈር በማስጌጥ፣በአንገቱ ከደረደረው ጨሌና በእጆቹ ካጠለቃቸው አንባሮች ሌላ
በወገቡ በታጠቀው ዝናርና መያዣዋ በሚያንጸባርቀው ቤልጅግ ጠመንጃ ከአካባቢው ኗሪ ልዩ ክብር ተጎናፀፈ የመንደሩ ልጃገረዶ ቀርቶ ከመንደሩ ራቅ ያሉትም ልጃገረዶች ሳይቀሩ በዝናው በቁመናው በመመሰጥ፣ የመጀመሪያውን እፍታ በየጫካው አጐረፉለት። ከሙርሲ ማኅበረሰብ በዘረፋቸው ከብቶችም መሣሪያ ገዛና በረቱን በከብት ሞላ። ሁለት ሚስት አግብቶ፣ የአባቱን ምኞትም
አሟላ። አባቱም ምንም እንኳን ከዳሰነች ማኅበረሰብ ጋር በተደረገው ጦርነት ቢሞቱም፣ የአባቱ ደም መላሽ ለመሆን ቻለ።
ደልቲ ገልዲ ስሙ እየገነነ ሲሄድ፣ የእሱም ልብ እያበጠ ሄደ።መቼም ሲመጣ በላይ በላይ ነውና፣ የላላና ሻንቆን መንደር ሰዎች ከብት እየሰበረ ያስቸገረ አንበሳ ለማደን ሁሉም በቡድን በቡድን ጫካ ሲገባ፣ እሱ ግን፣ «በእኔ በኩል ብቻዬን እበቃለሁ» ብሎ፣ ከነመሣሪ
ያው ለአደን ተሰማራ" ሁሉም ቦርጆን (አምላክን) እየተማፀነ፣ የአንበሳው ገዳይ ሆኖ እንደ አባያ በሬ ለመንጐማለል ሲመኝ
ፍለጋው ሲጧጧፍ ውሎ የጥይት ተኲስ ተሰማ፤ ወዲያው አንበሳው
ተገደለ ተባለና ገዳዩ ማን እንደሆነ አንዱ ሌላውን ሲጠይቅ፣ «ደልቲ
ገልዲ፣ የተኛ አንበሳ አልገድልም ብሎ ‹ጎፈር) ብሎ ቀስቅሶ አስነሥቶ፣ አጓርቶ ወደ እሱ ሲዘልበት በሚያስደንቅ ፍጥነት
መሣሪያውን አቀባብሎ፣ በሁለት ጥይት፣ ልሳኑን ዘጋው» ተባለ"
ልጃገረዶች፣ «ይኸዋ አላልኩሽም!» ሲባባሉ፣ «ኧረ እሱ ምኑ ነው ይሄን ያህል!» እያሉ ያናንቁ የነበሩት ጐረምሶች እንኳን
ሳይቀሩ፣ አንገታቸውን ደፉለት እረኞች፣ ልጃገረዶች በስሙ ዘፈኑለት፣ ሌላው ቀርቶ የመፎከሪያ በሬው ከሌሎች ከብቶች በልጦ
ተንጐማለለ" ደልቲ ገልዲ፣ ከግዙፉ የቡስካ ተራራ ይበልጥ ገዝፎ መታየት ጀመረ" በዚህ ሰሞን ነበር ሁለት እንግዶች ወደ
መንደራቸው የዘለቁት።....
💫ይቀጥላል💫
👍23
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ወጀቡ እስኪጠፋ ወለሉ ላይ ተቃቅፈው ቆዩና ‹‹መርቪን አልጋው ላይ
እንውጣ ከወለሉ ይልቅ እዚያ ይመቸናል›› አለ፡
ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡፡ ከዚያም በጉልበቷ እየዳኸች
አልጋው ላይ ወጣች፡፡ መርቪንም ተከተላትና አልጋው ላይ አብሯት ወጣ፡፡
እሱም እቅፍ አድርጎ ያዛት፡፡
በወጀቡ ምክንያት አይሮፕላኑ በተናወጠ ቁጥር ልክ መርከበኛ የጀልባ
ውን ምሰሶ እንደሚይዝ ሁሉ ናንሲ መርቪንን ጭምቅ አድርጋ ትይዛለች፡፡
ወጀቡ ሲቀንስና ዘና ስትል እሱም ሰውነቷን በፍቅር ይነካካቸዋል ከዚያ ትንሽ ቆየችና እንቅልፍ ይዟት ሄደ፡፡.
በሩ ተቆርቁሮ «አስተናጋጅ መቷል» የሚል ድምፅ ስትሰማ ከእንቅልፏ ነቃች።
ዓይኖቿን ስትከፍታቸው መርቪን ደረት ላይ መተኛቷን አወቀች
‹ወይ አምላኬ! አለች እየተርበተበተች፡
መርቪን ከተኛችበት እንድትነሳ በእጁ ገፋ አደረጋትና ‹‹ትንሽ ጠብቀን
አስተናጋጅ›› አለ፡፡
ከበሩ ውጭ የቆመው አስተናጋጅ በተደናገጠ ድምፅ እሺ ጌታዬ
እጠብቃለሁ›› አለ፡፡
መርቪን ከአልጋው ወረደና በአልጋ ልብስ ናንሲን ሸፈናት::
በዚህ አድራጎቱ በሆዷ አመሰገነችው፡፡ አስተናጋጁ እንዳያያት ፊቷን ወደ ግድግዳው አዞረች፡፡
መርቪን በሩን ሲከፍት አስተናጋጁ ገባና ‹‹እንዴት አደራችሁ›› አለ በፈገግታ፡፡
የትኩስ ቡና መዓዛ ናንሲን አወዳት፡፡ ‹‹በእንግሊዝ የሰዓት አቆጣጠር
የሶስት ሰዓት ተኩል ወደ ኋላ ነው ማለት ነው?›› አለ አስተናጋጁን
‹‹ልክ ነው ጌታዬ የኒውፋውንድ ላንድ የሰዓት አቆጣጠር ከግሪንዊች
የሰዓት አቆጣጠር ሶስት ሰዓት ተኩል ወደ ኋላ ይዘገያል፡››
‹‹መቼም የአየር መንገዶችን የጉዞ መርሃ ግብር ለሚያዘጋጁ ሰዎች ይህ የሰዓት አቆጣጠር ችግር
ሳይፈጥርባቸው አይቀርም፡፡ ባህር ላይ ለማረፍ ምን
ያህል ሰዓት ይቀረናል?›› ሲል ጠየቀ መርቪን
‹‹ከግማሽ ሰዓት በኋላ እናርፋለን፡ ከመርሃ ግብሩ አንድ ሰዓት ጉዟችን
የዘገየው በወጀቡ ምክንያት ነው›› አለና አስተናጋጁ በሩን ዘግቶ ወጣ፡
ናንሲ በሩ ከተዘጋ በኋላ ‹የመስኮቱን መጋረጃ ክፈተው፡ ነግቷል››
አለችው:፡ መርቪን ቡና ሲቀዳ የትናንት ምሽት አዳራቸው ፊቱ ላይ መጥቶ
ድቅን አለ፡፡ ወጀቡ በተነሳ ቁጥር መርቪን እጇን የሚይዛት፣ ወለሉ ላይ
የሚወድቁት፣ የመርቪን እጆች ጡቶቿን ሲጨብጥ፣ አይሮፕላኑ ሲናወጥ፣
እሱ ደረት ላይ ልጥፍ የምትለውና እየደባበሰ የሚያስተኛት ትዝ አላት:
ይህን ሰው በጣም ወድጄዋለሁ› አለች በሆዷ።
‹‹ቡና እንደወረደ ወይስ ከወተት ጋር ነው የምትፈልጊው?›› ሲል
ጠየቃት፡፡
‹‹ጥቁር ቡና ይሁንልኝ፡ ስኳር አልፈልግም››
‹‹እንደ እኔ›› አለና ቡናዋን አቀበላት ናንሲ አመስግና ቡናዋን ጠጣች፡፡
ናንሲ ስለ መርቪን በደንብ ማወቅ ፈለገች፡፡ ቡናውን እየጠጣ ስለእሱ ልማዶች ግምቷን አስቀመጠች፡፡ ቴኒስ ይጫወታል፣ ልብ ወለድ ብዙ ማንበብ አይወድም፣ ገበያ መሄድም እንደዚሁ፣ ቁማር ጨዋታ የሚሳካለት ይመስላል፣ ዳንስ ግን የሚችል አይመስልም፡፡›
‹‹ምንድን ነው የምታውጠነጥኚው?›› ሲል
ጠየቀ ለሕይወት ኢንሹራንስ አደገኛ እንደሆንኩ አድርገሽ የምታይኝ መሰለኝ፡፡››
ናንሲ ቀልዱ አሳቃት፡፡ ‹‹ምን አይነት ሙዚቃ ነው የምትወደው?›› ለሙዚቃ ጆሮ አልሰጥም›› አለ ‹‹መደነስ ባልጠላም ጥሩ ደናሽ ግን አይደለሁም፡፡ አንቺስ?››
እኔ ድሮ ደንሼያለሁ፡መደነስም ነበረብኝ፡፡ እሁድ እሁድ ሱፍ ከሚለብሱ ወንዶች ልጆች ጋር በዳንስ ትምህርት ቤት ዳንስ እማር ነበር፡፡ከላይኛው መደብ የቦስተን ማህበረሰቦች ጋር ለመግባባት ብቸኛው መንገድ ይህ ብቻ እንደሆነ እናቴ ትነግረኝ ነበር፡ እኔ ግን ከዛ ማህበረሰብ ውስጥ
ብገባ ባልገባ ግድ አልነበረኝም፡: የኔ ቀልብ ያለው ከአባቴ ፋብሪካ ጋር ነው፡፡ እናቴ ደግሞ ይሄን ባህሪዬን አትወደውም ነበር፡››
ሁለቱ አዲስ ፍቅረኛሞች ተያዩ፡፡ መርቪንም ትናንት ማታ እንዴት ሲላፉና ሲላላሱ እንዳመሹ እንደሚያስብ ነቃችበት፡፡ ይህም ሀሳብ እፍረት
ውስጥ ከተታትና ፊቷን ወደ መስኮቱ ስታዞር መሬት ታያት፡፡ አይሮፕላኑ
ቦትውድ ሲያርፍ ህይወቷን የሚለውጠውን የስልክ ጥሪ ማድረግ እንዳለባት ትዝ አላት፡ ‹‹ደርሰናል›› አለችና ከመኝታዋ ዘላ ተነሳች ‹‹ልብሴን ልልበስ›› አለች፡፡
‹‹እኔ ቀድሜ ልውጣ›› አለ መርቪን ‹‹ለአንቺ ጥሩ ነው››
እሺ፧ አሁንስ ምን ቀልብ አለኝ አለች በሀሳቧ። ይህን ለእሱ አልነገረችውም፡፡ መርቪን ልብሱን ስበሰበ፡፡ በሩን ከፍቶ ሊወጣ ሲል
ተጠራጠረና ቆመ፡፡ እሷም እንደገና ሊስማት እንደፈለገ አውቃ ወደ እሱ ሄደችና ከንፈሯን ሰጠችው፡፡ ‹‹ሌሊቱን በሙሉ እቅፍ አድርገህ ስላስተኛኸኝ
አመሰግንሃለሁ›› አለችው:
መርቪን ከአንገቱ ዝቅ አለና ሳማት፡፡ አሳሳሙ ልስልስ ያለ ነበር፡ አፏን በአፉ ግጥም አድርጎ ነው የሳማት፡፡ እየተሳሳሙ ትንሽ ቆዩና ተላቀቁ፡፡
ናንሲ በሩን ከፍታ ያዘችለትና ወጥቶ ሄደ፡፡
በሩን እንደዘጋች የደስታ ሲቃ ተናነቃት፡ ከዚህ ሰው ፍቅር ሊይዘኝ ነው አለች፡ በመስኮቱ ስታማትር አይሮፕላኑ ቀስ በቀስ እየወረደ ነው፡፡
መፍጠን አለባት፡፡
መስታወቱ ፊት ቆማ ፀጉሯን ቶሎ አሰረችና የመዋቢያ ዕቃዎቿን ይዛ የሙሽሮቹ ክፍል አጠገብ ወደሚገኘው ወደ ሴቶች መታጠቢያ ቤት ሄደች፡፡እዚያ ሉሉ ቤልንና አንድ ሌላ ሴት አገኘች፡፡ የመርቪን ሚስት ግን የለችም:
ናንሲ ፊቷን እየታጠበች ጧት ከመርቪን ጋር ያደረገችውን ውይይት
አስታወሰች፡፡ እሱን ስታስብ ደስታ ቢሰማትም ደስታው የተሟላ ባለመሆኑ
ከጭንቀት ሊገላግላት አልቻለም፡፡ ስለሚስቱ ምንም አላለም፡፡ ትናንት ማታ ስለእሷ ስትጠይቀው ድንግርግር እንዳለው ነው የነገራት፡፡ ከዚያ በኋላ ግን
ይወዳት ይሆን? ትናንት ማታ ሌሊቱን ሙሉ ደረቱ ላይ ለጥፎ ነው ያሳደራት ይህ ብቻውን ጋብቻን ይፍቃል ማለት ግን አይደለም፡
እኔ የምፈልገው ምንድን ነው? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ ‹መርቪንን እንደገና ማግኘት እፈልጋለሁ ከእሱ ጋር ድብቅ ወዳጅነት ልመስርት?ታዲያ ለኔ ብሎ ጋብቻውን እንዲያፈርስ እፈልጋለሁ? ከአንድ ሌሊት
ወሲባዊ ልፊያና መሳሳም በኋላ ይህን እንዴት ማወቅ እችላለሁ?
ሊፕስቲክ ለመቀባት መስታወቱ ላይ አፈጠጠች ናንሲ መጠራጠርሽን አቁሚ
ስትል ለራሷ አሳሰበች እውነታውን ታውቂዋለሽ፤ ይሄን ሰው በጣም ፈልገሽዋል፧ ከአስር ዓመት ወዲህ እጅሽን የሰጠሸው ለዚህ ሰው ነው፡:
አሁን አርባ አመትሽን ደፍነሻል፡ አሁን ተገቢውን ሰው አግኝተሻል፡ እዚህ
እዚያ መርገጥሽን ትተሽ ይህን ሰው በእጅሽ አድርጊ፡፡›
ሰውነቷ ላይ ሽቶ አርከፈከፈችና ወጣች፡
ስትወጣ ከመታጠቢያ ቤቱ አጠገብ የተቀመጡትን ናት ሪጅዌይና ወንድሟን ፒተርን አገኘቻቸው ናት ‹‹ደህና አደርሽ ናንሲ›› አላት::
ይህን ስትሰማ ከአምስት ዓመት በፊት በዚህ ሰው የነበራትን ስሜት
አስታወሳት፡፡ እኔ ከእሱ ፍቅር ይዞኝ ነበር፡፡ እሱ ግን ከእኔ ይልቅ የፈለገው
ብላክ ቡትስ ኩባንያን ነበር፡፡ አሁንም ኩባንያውን በእጁ ለማስገባት
የሚፈልገውን ያህል እኔን አይፈልገኝም፡፡ ለሰላምታው በራስ ንቅናቄ ብቻ
አፀፋዊ ሰላምታ ሰጥታው ወደ ክፍሏ ሄደች፡፡
አስተናጋጆቹ መኝታዎቹን ወደ ሶፋነት ለውጠዋቸዋል። መርቪን ጢሙን ተላጭቶና በነጭ ሽሚዝ ላይ ሱፍ ልብሱን ለብሶ ሶፋ ላይ ቁጭ ብሏል፡፡ ‹‹በመስኮት ተመልከች ደርሰናል›› አላት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ወጀቡ እስኪጠፋ ወለሉ ላይ ተቃቅፈው ቆዩና ‹‹መርቪን አልጋው ላይ
እንውጣ ከወለሉ ይልቅ እዚያ ይመቸናል›› አለ፡
ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡፡ ከዚያም በጉልበቷ እየዳኸች
አልጋው ላይ ወጣች፡፡ መርቪንም ተከተላትና አልጋው ላይ አብሯት ወጣ፡፡
እሱም እቅፍ አድርጎ ያዛት፡፡
በወጀቡ ምክንያት አይሮፕላኑ በተናወጠ ቁጥር ልክ መርከበኛ የጀልባ
ውን ምሰሶ እንደሚይዝ ሁሉ ናንሲ መርቪንን ጭምቅ አድርጋ ትይዛለች፡፡
ወጀቡ ሲቀንስና ዘና ስትል እሱም ሰውነቷን በፍቅር ይነካካቸዋል ከዚያ ትንሽ ቆየችና እንቅልፍ ይዟት ሄደ፡፡.
በሩ ተቆርቁሮ «አስተናጋጅ መቷል» የሚል ድምፅ ስትሰማ ከእንቅልፏ ነቃች።
ዓይኖቿን ስትከፍታቸው መርቪን ደረት ላይ መተኛቷን አወቀች
‹ወይ አምላኬ! አለች እየተርበተበተች፡
መርቪን ከተኛችበት እንድትነሳ በእጁ ገፋ አደረጋትና ‹‹ትንሽ ጠብቀን
አስተናጋጅ›› አለ፡፡
ከበሩ ውጭ የቆመው አስተናጋጅ በተደናገጠ ድምፅ እሺ ጌታዬ
እጠብቃለሁ›› አለ፡፡
መርቪን ከአልጋው ወረደና በአልጋ ልብስ ናንሲን ሸፈናት::
በዚህ አድራጎቱ በሆዷ አመሰገነችው፡፡ አስተናጋጁ እንዳያያት ፊቷን ወደ ግድግዳው አዞረች፡፡
መርቪን በሩን ሲከፍት አስተናጋጁ ገባና ‹‹እንዴት አደራችሁ›› አለ በፈገግታ፡፡
የትኩስ ቡና መዓዛ ናንሲን አወዳት፡፡ ‹‹በእንግሊዝ የሰዓት አቆጣጠር
የሶስት ሰዓት ተኩል ወደ ኋላ ነው ማለት ነው?›› አለ አስተናጋጁን
‹‹ልክ ነው ጌታዬ የኒውፋውንድ ላንድ የሰዓት አቆጣጠር ከግሪንዊች
የሰዓት አቆጣጠር ሶስት ሰዓት ተኩል ወደ ኋላ ይዘገያል፡››
‹‹መቼም የአየር መንገዶችን የጉዞ መርሃ ግብር ለሚያዘጋጁ ሰዎች ይህ የሰዓት አቆጣጠር ችግር
ሳይፈጥርባቸው አይቀርም፡፡ ባህር ላይ ለማረፍ ምን
ያህል ሰዓት ይቀረናል?›› ሲል ጠየቀ መርቪን
‹‹ከግማሽ ሰዓት በኋላ እናርፋለን፡ ከመርሃ ግብሩ አንድ ሰዓት ጉዟችን
የዘገየው በወጀቡ ምክንያት ነው›› አለና አስተናጋጁ በሩን ዘግቶ ወጣ፡
ናንሲ በሩ ከተዘጋ በኋላ ‹የመስኮቱን መጋረጃ ክፈተው፡ ነግቷል››
አለችው:፡ መርቪን ቡና ሲቀዳ የትናንት ምሽት አዳራቸው ፊቱ ላይ መጥቶ
ድቅን አለ፡፡ ወጀቡ በተነሳ ቁጥር መርቪን እጇን የሚይዛት፣ ወለሉ ላይ
የሚወድቁት፣ የመርቪን እጆች ጡቶቿን ሲጨብጥ፣ አይሮፕላኑ ሲናወጥ፣
እሱ ደረት ላይ ልጥፍ የምትለውና እየደባበሰ የሚያስተኛት ትዝ አላት:
ይህን ሰው በጣም ወድጄዋለሁ› አለች በሆዷ።
‹‹ቡና እንደወረደ ወይስ ከወተት ጋር ነው የምትፈልጊው?›› ሲል
ጠየቃት፡፡
‹‹ጥቁር ቡና ይሁንልኝ፡ ስኳር አልፈልግም››
‹‹እንደ እኔ›› አለና ቡናዋን አቀበላት ናንሲ አመስግና ቡናዋን ጠጣች፡፡
ናንሲ ስለ መርቪን በደንብ ማወቅ ፈለገች፡፡ ቡናውን እየጠጣ ስለእሱ ልማዶች ግምቷን አስቀመጠች፡፡ ቴኒስ ይጫወታል፣ ልብ ወለድ ብዙ ማንበብ አይወድም፣ ገበያ መሄድም እንደዚሁ፣ ቁማር ጨዋታ የሚሳካለት ይመስላል፣ ዳንስ ግን የሚችል አይመስልም፡፡›
‹‹ምንድን ነው የምታውጠነጥኚው?›› ሲል
ጠየቀ ለሕይወት ኢንሹራንስ አደገኛ እንደሆንኩ አድርገሽ የምታይኝ መሰለኝ፡፡››
ናንሲ ቀልዱ አሳቃት፡፡ ‹‹ምን አይነት ሙዚቃ ነው የምትወደው?›› ለሙዚቃ ጆሮ አልሰጥም›› አለ ‹‹መደነስ ባልጠላም ጥሩ ደናሽ ግን አይደለሁም፡፡ አንቺስ?››
እኔ ድሮ ደንሼያለሁ፡መደነስም ነበረብኝ፡፡ እሁድ እሁድ ሱፍ ከሚለብሱ ወንዶች ልጆች ጋር በዳንስ ትምህርት ቤት ዳንስ እማር ነበር፡፡ከላይኛው መደብ የቦስተን ማህበረሰቦች ጋር ለመግባባት ብቸኛው መንገድ ይህ ብቻ እንደሆነ እናቴ ትነግረኝ ነበር፡ እኔ ግን ከዛ ማህበረሰብ ውስጥ
ብገባ ባልገባ ግድ አልነበረኝም፡: የኔ ቀልብ ያለው ከአባቴ ፋብሪካ ጋር ነው፡፡ እናቴ ደግሞ ይሄን ባህሪዬን አትወደውም ነበር፡››
ሁለቱ አዲስ ፍቅረኛሞች ተያዩ፡፡ መርቪንም ትናንት ማታ እንዴት ሲላፉና ሲላላሱ እንዳመሹ እንደሚያስብ ነቃችበት፡፡ ይህም ሀሳብ እፍረት
ውስጥ ከተታትና ፊቷን ወደ መስኮቱ ስታዞር መሬት ታያት፡፡ አይሮፕላኑ
ቦትውድ ሲያርፍ ህይወቷን የሚለውጠውን የስልክ ጥሪ ማድረግ እንዳለባት ትዝ አላት፡ ‹‹ደርሰናል›› አለችና ከመኝታዋ ዘላ ተነሳች ‹‹ልብሴን ልልበስ›› አለች፡፡
‹‹እኔ ቀድሜ ልውጣ›› አለ መርቪን ‹‹ለአንቺ ጥሩ ነው››
እሺ፧ አሁንስ ምን ቀልብ አለኝ አለች በሀሳቧ። ይህን ለእሱ አልነገረችውም፡፡ መርቪን ልብሱን ስበሰበ፡፡ በሩን ከፍቶ ሊወጣ ሲል
ተጠራጠረና ቆመ፡፡ እሷም እንደገና ሊስማት እንደፈለገ አውቃ ወደ እሱ ሄደችና ከንፈሯን ሰጠችው፡፡ ‹‹ሌሊቱን በሙሉ እቅፍ አድርገህ ስላስተኛኸኝ
አመሰግንሃለሁ›› አለችው:
መርቪን ከአንገቱ ዝቅ አለና ሳማት፡፡ አሳሳሙ ልስልስ ያለ ነበር፡ አፏን በአፉ ግጥም አድርጎ ነው የሳማት፡፡ እየተሳሳሙ ትንሽ ቆዩና ተላቀቁ፡፡
ናንሲ በሩን ከፍታ ያዘችለትና ወጥቶ ሄደ፡፡
በሩን እንደዘጋች የደስታ ሲቃ ተናነቃት፡ ከዚህ ሰው ፍቅር ሊይዘኝ ነው አለች፡ በመስኮቱ ስታማትር አይሮፕላኑ ቀስ በቀስ እየወረደ ነው፡፡
መፍጠን አለባት፡፡
መስታወቱ ፊት ቆማ ፀጉሯን ቶሎ አሰረችና የመዋቢያ ዕቃዎቿን ይዛ የሙሽሮቹ ክፍል አጠገብ ወደሚገኘው ወደ ሴቶች መታጠቢያ ቤት ሄደች፡፡እዚያ ሉሉ ቤልንና አንድ ሌላ ሴት አገኘች፡፡ የመርቪን ሚስት ግን የለችም:
ናንሲ ፊቷን እየታጠበች ጧት ከመርቪን ጋር ያደረገችውን ውይይት
አስታወሰች፡፡ እሱን ስታስብ ደስታ ቢሰማትም ደስታው የተሟላ ባለመሆኑ
ከጭንቀት ሊገላግላት አልቻለም፡፡ ስለሚስቱ ምንም አላለም፡፡ ትናንት ማታ ስለእሷ ስትጠይቀው ድንግርግር እንዳለው ነው የነገራት፡፡ ከዚያ በኋላ ግን
ይወዳት ይሆን? ትናንት ማታ ሌሊቱን ሙሉ ደረቱ ላይ ለጥፎ ነው ያሳደራት ይህ ብቻውን ጋብቻን ይፍቃል ማለት ግን አይደለም፡
እኔ የምፈልገው ምንድን ነው? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ ‹መርቪንን እንደገና ማግኘት እፈልጋለሁ ከእሱ ጋር ድብቅ ወዳጅነት ልመስርት?ታዲያ ለኔ ብሎ ጋብቻውን እንዲያፈርስ እፈልጋለሁ? ከአንድ ሌሊት
ወሲባዊ ልፊያና መሳሳም በኋላ ይህን እንዴት ማወቅ እችላለሁ?
ሊፕስቲክ ለመቀባት መስታወቱ ላይ አፈጠጠች ናንሲ መጠራጠርሽን አቁሚ
ስትል ለራሷ አሳሰበች እውነታውን ታውቂዋለሽ፤ ይሄን ሰው በጣም ፈልገሽዋል፧ ከአስር ዓመት ወዲህ እጅሽን የሰጠሸው ለዚህ ሰው ነው፡:
አሁን አርባ አመትሽን ደፍነሻል፡ አሁን ተገቢውን ሰው አግኝተሻል፡ እዚህ
እዚያ መርገጥሽን ትተሽ ይህን ሰው በእጅሽ አድርጊ፡፡›
ሰውነቷ ላይ ሽቶ አርከፈከፈችና ወጣች፡
ስትወጣ ከመታጠቢያ ቤቱ አጠገብ የተቀመጡትን ናት ሪጅዌይና ወንድሟን ፒተርን አገኘቻቸው ናት ‹‹ደህና አደርሽ ናንሲ›› አላት::
ይህን ስትሰማ ከአምስት ዓመት በፊት በዚህ ሰው የነበራትን ስሜት
አስታወሳት፡፡ እኔ ከእሱ ፍቅር ይዞኝ ነበር፡፡ እሱ ግን ከእኔ ይልቅ የፈለገው
ብላክ ቡትስ ኩባንያን ነበር፡፡ አሁንም ኩባንያውን በእጁ ለማስገባት
የሚፈልገውን ያህል እኔን አይፈልገኝም፡፡ ለሰላምታው በራስ ንቅናቄ ብቻ
አፀፋዊ ሰላምታ ሰጥታው ወደ ክፍሏ ሄደች፡፡
አስተናጋጆቹ መኝታዎቹን ወደ ሶፋነት ለውጠዋቸዋል። መርቪን ጢሙን ተላጭቶና በነጭ ሽሚዝ ላይ ሱፍ ልብሱን ለብሶ ሶፋ ላይ ቁጭ ብሏል፡፡ ‹‹በመስኮት ተመልከች ደርሰናል›› አላት፡፡
👍19
ናንሲ ወደ ውጭ ስትመለከት መሬት አየች፡፡ እታች ደን የለበሰ መሬትና ወንዝ ይታያል፡፡ ትንሽ ራቅ ብሎ ወደቡና ከእንጨት የተሰሩ ቤቶችና ቤተክርሰቲያን አየች፡፡
አይሮፕላኑ በፍጥነት ወደ መሬት ወረደ፡ ናንሲና መርቪን ሶፋው ላይ
እጃቸውን አቆላልፈውና የመቀመጫ ቀበቷቸውን አስረው ተቀምጠዋል
የሰማይ በራሪው ጀልባ ባህሩ ላይ ሲያርፍ መስታወቶቹ ላይ የውሃ
ፍንጥቅጣቂ ሲረጭ አዩ፡፡
‹‹አትላንቲክን አቋርጠናል›› አለች፡፡
ግማሹን ጉዞ ያሳለፈችው ስለ ፋብሪካው ስታስብ ሲሆን ቀሪው ግማሽ
ደግሞ ያለፈው የሰው ባል እጅ ይዛ ነው፡፡ የአየር ጠባዩ መጥፎ ስለነበር ያሳለፈችው ጉዞ አስፈሪ እንደነበር አስታወሰች፡፡ ለልጆቿ ምን ልትላቸው ነው? ሁሉንም ነገር ንገሪኝ ሊሏት ይችላሉ፡ አይሮፕላኑ በሰዓት ስንት
ማይል መብረር እንደሚችል እንኳን አታውቅም እንዲህ አይነቱን መረጃ ኒውዮርክ ከመድረሳቸው በፊት ታጣራለች፡፡
የሰማይ በራሪው ጀልባ ወደቡ ላይ ደርሶ ሲቆም አንድ ወደ መሬት
የሚወስዳቸው ጀልባ ወደ እነሱ መጣ፡፡ ናንሲ ኮቷን ስትይዝ መርቪን ደግሞ
ከቆዳ የተሰራውን
የአብራሪዎች ጃኬት ለበሰ፡፡ ገሚሱ ተሳፋሪዎች
ከአይሮፕላኑ ወጥተው እግራቸውን ለማፍታታት ሲወስኑ ገሚሶቹ ግን
አልጋቸው ላይ እንቅልፋቸውን እየለጠጡ ነው፡፡
hአይሮፕላኑ ወጡና ጀልባ ላይ ተሳፈሩ፡ አየሩ በባህርና በግንድ ሽታ ታውዷል አጠገባቸው የእንጨት
መሰንጠቂያ ሳይኖር አይቀርም፡፡አይሮፕላኑ ከቆመበት ወደብ ቀጥሎ ነዳጅ የሚሞሉ ሰራተኞች ቱታቸውን ለብሰው በተጠንቀቅ ቆመዋል፡፡ ራቅ ብሎ ደግሞ ሁለት መርከቦች ይታያሉ፡፡
የመርቪን ሚስትና ፍቅረኛዋ ከአይሮፕላኑ ወጥተው ለመንሸራሸር ወስነዋል፡ ዳያና ናንሲ ላይ ብታፈጥም ናንሲ በዓይኗ ሙሉ ዳያናን ማየት አልተቻላትም ምንም እንኳን ከዳያና የበለጠ የጥፋተኝነት ስሜት ሊሰማት ባይችልም፡፡ በባሏ ላይ የሄደች ዳያና ራሷ እንጂ ናንሲ አይደለችም፡፡
ገና ማለዳ በመሆኑ ጥቂት ጎብኚዎች ናቸው የሚታዩት፡፡
ተሳፋሪዎች ከአይሮፕላኑ ወርደው ወደ አየር መንገዱ ህንጻ ሄዱና እንቅልፉን ላልጨረሰ ሰራተኛ ፓስፖርታቸውን አሳዩት
የተሳፋሪዎች መቆያ ክፍል ቢኖርም ተሳፋሪዎች መንደሪቷን በእግር
ለማካለል ፈለጉ፡
ናንሲ ቦስተን ካለው ጠበቃዋ ፓትሪክ ማክብራይድ ጋር ለመነጋገር በእጅጉ ጓጉታለች፡፡ ስልክ እንዳለ ለመጠየቅ ስትዘጋጅ የፓን አሜሪካን ዩኒፎርም የለበሰ ሰው ‹‹ስልክ ይፈልግዎታል የኔ እመቤት›› አላት።
የናንሲ ልብ ዘለለ ‹‹የት ነው ስልኩ?›› ስትል ጠየቀች፡
‹‹ከዚህ አንድ ኪሎ ሜትር ያህል ያስኬዳል››
‹‹አንድ ማይል!›› ንዴቷን መቆጣጠር አቃታት፡ ‹‹እንፍጠና ግንኙነት
ከመቋረጡ በፊት፡፡ መኪና አላችሁ?›› ስትል ጠየቀች፡፡
ሰውዬው ልክ የጠፈር መንኮራኩር የተጠየቀ ይመስል ድንግርግር
ሲለው ታዬ፡፡ ‹‹የለም የኔ እመቤት›
‹‹ስለዚህ በእግራችን እንሂድ በል መንገዱን ምራኝ›› አለች።
ናንሲና መርቪን መልእክተኛውን ተከትለው ነጎዱ፡፡ የእግረኛ መንገድ
የሌለው ጥርጊያ መንገድ ተከትለው በመሄድ ወደ ጋራው ወጡ፡፡ በየመንገዱ
በጎች ሳር ሲግጡ ይታያሉ፡ ናንሲ የብላክ ኩባንያ ያመረተው ጫማ ምስጋና
ይግባውና ተፍ ተፍ እያለች ትሄዳለች ነገ ማታ የብላክ ኩባንያ በእሷ ቁጥጥር ስር ይሆን? ይህን ማክብራይድ አሁን ያረጋግጥላታል፡ ከዚህ በላይ ከዘገየች በውጥረት መሞቷ ነው፡፡
ለአስር ደቂቃ ያህል ከተጓዙ በኋላ አንድ ከእንጨት የተሰራ ቤት አገኙና ጥልቅ አሉ፡፡ ናንሲ ስልኩ አጠገብ ያለ ወንበር ላይ ተቀምጣ እጇ እየተንቀጠቀጠ የስልኩን እጀታ አነሳችና ‹‹ናንሲ ሌኔሃን ነኝ›› አለች፡፡
✨ይቀጥላል✨
አይሮፕላኑ በፍጥነት ወደ መሬት ወረደ፡ ናንሲና መርቪን ሶፋው ላይ
እጃቸውን አቆላልፈውና የመቀመጫ ቀበቷቸውን አስረው ተቀምጠዋል
የሰማይ በራሪው ጀልባ ባህሩ ላይ ሲያርፍ መስታወቶቹ ላይ የውሃ
ፍንጥቅጣቂ ሲረጭ አዩ፡፡
‹‹አትላንቲክን አቋርጠናል›› አለች፡፡
ግማሹን ጉዞ ያሳለፈችው ስለ ፋብሪካው ስታስብ ሲሆን ቀሪው ግማሽ
ደግሞ ያለፈው የሰው ባል እጅ ይዛ ነው፡፡ የአየር ጠባዩ መጥፎ ስለነበር ያሳለፈችው ጉዞ አስፈሪ እንደነበር አስታወሰች፡፡ ለልጆቿ ምን ልትላቸው ነው? ሁሉንም ነገር ንገሪኝ ሊሏት ይችላሉ፡ አይሮፕላኑ በሰዓት ስንት
ማይል መብረር እንደሚችል እንኳን አታውቅም እንዲህ አይነቱን መረጃ ኒውዮርክ ከመድረሳቸው በፊት ታጣራለች፡፡
የሰማይ በራሪው ጀልባ ወደቡ ላይ ደርሶ ሲቆም አንድ ወደ መሬት
የሚወስዳቸው ጀልባ ወደ እነሱ መጣ፡፡ ናንሲ ኮቷን ስትይዝ መርቪን ደግሞ
ከቆዳ የተሰራውን
የአብራሪዎች ጃኬት ለበሰ፡፡ ገሚሱ ተሳፋሪዎች
ከአይሮፕላኑ ወጥተው እግራቸውን ለማፍታታት ሲወስኑ ገሚሶቹ ግን
አልጋቸው ላይ እንቅልፋቸውን እየለጠጡ ነው፡፡
hአይሮፕላኑ ወጡና ጀልባ ላይ ተሳፈሩ፡ አየሩ በባህርና በግንድ ሽታ ታውዷል አጠገባቸው የእንጨት
መሰንጠቂያ ሳይኖር አይቀርም፡፡አይሮፕላኑ ከቆመበት ወደብ ቀጥሎ ነዳጅ የሚሞሉ ሰራተኞች ቱታቸውን ለብሰው በተጠንቀቅ ቆመዋል፡፡ ራቅ ብሎ ደግሞ ሁለት መርከቦች ይታያሉ፡፡
የመርቪን ሚስትና ፍቅረኛዋ ከአይሮፕላኑ ወጥተው ለመንሸራሸር ወስነዋል፡ ዳያና ናንሲ ላይ ብታፈጥም ናንሲ በዓይኗ ሙሉ ዳያናን ማየት አልተቻላትም ምንም እንኳን ከዳያና የበለጠ የጥፋተኝነት ስሜት ሊሰማት ባይችልም፡፡ በባሏ ላይ የሄደች ዳያና ራሷ እንጂ ናንሲ አይደለችም፡፡
ገና ማለዳ በመሆኑ ጥቂት ጎብኚዎች ናቸው የሚታዩት፡፡
ተሳፋሪዎች ከአይሮፕላኑ ወርደው ወደ አየር መንገዱ ህንጻ ሄዱና እንቅልፉን ላልጨረሰ ሰራተኛ ፓስፖርታቸውን አሳዩት
የተሳፋሪዎች መቆያ ክፍል ቢኖርም ተሳፋሪዎች መንደሪቷን በእግር
ለማካለል ፈለጉ፡
ናንሲ ቦስተን ካለው ጠበቃዋ ፓትሪክ ማክብራይድ ጋር ለመነጋገር በእጅጉ ጓጉታለች፡፡ ስልክ እንዳለ ለመጠየቅ ስትዘጋጅ የፓን አሜሪካን ዩኒፎርም የለበሰ ሰው ‹‹ስልክ ይፈልግዎታል የኔ እመቤት›› አላት።
የናንሲ ልብ ዘለለ ‹‹የት ነው ስልኩ?›› ስትል ጠየቀች፡
‹‹ከዚህ አንድ ኪሎ ሜትር ያህል ያስኬዳል››
‹‹አንድ ማይል!›› ንዴቷን መቆጣጠር አቃታት፡ ‹‹እንፍጠና ግንኙነት
ከመቋረጡ በፊት፡፡ መኪና አላችሁ?›› ስትል ጠየቀች፡፡
ሰውዬው ልክ የጠፈር መንኮራኩር የተጠየቀ ይመስል ድንግርግር
ሲለው ታዬ፡፡ ‹‹የለም የኔ እመቤት›
‹‹ስለዚህ በእግራችን እንሂድ በል መንገዱን ምራኝ›› አለች።
ናንሲና መርቪን መልእክተኛውን ተከትለው ነጎዱ፡፡ የእግረኛ መንገድ
የሌለው ጥርጊያ መንገድ ተከትለው በመሄድ ወደ ጋራው ወጡ፡፡ በየመንገዱ
በጎች ሳር ሲግጡ ይታያሉ፡ ናንሲ የብላክ ኩባንያ ያመረተው ጫማ ምስጋና
ይግባውና ተፍ ተፍ እያለች ትሄዳለች ነገ ማታ የብላክ ኩባንያ በእሷ ቁጥጥር ስር ይሆን? ይህን ማክብራይድ አሁን ያረጋግጥላታል፡ ከዚህ በላይ ከዘገየች በውጥረት መሞቷ ነው፡፡
ለአስር ደቂቃ ያህል ከተጓዙ በኋላ አንድ ከእንጨት የተሰራ ቤት አገኙና ጥልቅ አሉ፡፡ ናንሲ ስልኩ አጠገብ ያለ ወንበር ላይ ተቀምጣ እጇ እየተንቀጠቀጠ የስልኩን እጀታ አነሳችና ‹‹ናንሲ ሌኔሃን ነኝ›› አለች፡፡
✨ይቀጥላል✨
👍16
😘 #ቃል 😘
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ አምስት (35) በሆስፒታሉ ኮሪደር ውስጥ እየተጣደፈ ሲሄድ የጫማው ድምፅ ጎልቶ ይሰማ ነበር። ምን ብታስብ ነው ወደ ሳንፍራንሲስኮ ስትመጣ ብቻየን ነው የምሄድ ብላ ድርቅ ያለችው ? ይህን ያህል አመት ስትኖር ረዳት አያስፈልገኝም ፤ሁሉንም ነገር ብቻየን ልወጣው እፈልጋለሁ የምትለው ለምንድነው ? ይህን እያሰበ በሩን አንኳኳ ። አንዲት በገጺ ላይ ምን ይፈልጋሉ ? የሚል ጥያቄ የተሳለባት ነርስ በሩን ከፈተችለት ። «ማሪዮን ሂልያርድ የተኛችው እዚህ ክፍል ነው ?» ሲል ጠየቃት ። በነርሷ ገፅታ ላይ የተሳለው ጥያቄ አልተነሳም ነበረና «ጆርጅ ኮሎዌ እባላለሁ» ሲል ጨመረ ። ድካም ፡ እርጅናና ያለመረጋጋት ስሜት በፊቱ ላይ ጎልተው ይታያሉ ። እነዚህ ስሜቶች በሠራ አካላቱ ተሰራጭተው ይሰሙትም ነበር ። የለም እንዲህ አይነቱ ርባና ቢስ ነገር አሁንስ ስልችት አለኝ ። ማሪዮን በዚሀ ሁኔታ ልትቀጥል አትችልም። ዛሬ ሁሉንም ግልጥልጥ አድርጌ መንገር አለብኝ ሲል አሰበ ። እንዳገኛት ይነግራታል ። ገና ከኒውዮርክ ከመነሳቱ በፊት ይህን ውሳኔ ለማይክል ሂልያርድም ነግሮታል ።
«ሚስተር ኮሎዌ ?» አለች ነርሷ ስሙን ስትሰማ በገዝፅዋ ላይ የተሳለው ጥያቄ ወደ ፈገግታ እየተለወጠ «ስንጠባበቅ ነበር » ማሪዮን እዚህ ሆስፒታል የገባችው ምሽቱ ላይ ፤አሥራ ሁለት ሰዓት አካባቢ ሲሆን ጆርጅ ከኒውዮርክ ተነስቶ እዚያ የደረሰው ከምሽቱ ስድስት ሰዓት አካባቢ ነበር ።ይሀ ደግሞ ከኒውዮርክ ሳንፍራንሲስኮ ለመድረስ የመጨረሻው ፈጣን ጉዞ ሳይሆን አይቀርም ። ነርሷን አልፎ ገባ። ማሪዮን የጆርጅን መምጣት አይታ ፈገግ ስትል ነርሷ ከክፍሉ ውስጥ ወጥታ ወደ ሠራተኞች ማረፊያ አዳራሽ ሄደች ።
«ሄሎ ጆርጅ »
«ሄሎ ማሪዮን ፤ ተሻለሽ ?»
«ከድካሙ በስተቀር አደጋውን አልፌዋለሁ ። ማለት ሀኪሞቹ የነገሩኝ እንዲያ ብለው ነው ። ኃይለኛ አልነበረም አያያዙ»
«ዛሬስ እንዲያ ሆነ ግን ለወደፊቱስ? ወደፊት›› ጀርጅ ይህን ተናግሮ በክፍሉ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ሲንጎራደድ እርምጃው ሁሉ የአንበሳ ይመስል ነበር። ቁጣውም ለማሪዮን ግፅል ሆኖ ታያት ። ይህን ያየችው ማሪዮን ሁኔታው አስገረማት። እንደሁልጊዜው አልሰማትም ።። ብዙ ነገር ሲነግራት አስቧል ማለት ነው ። «ለወደፊቱ ፣ ወደፊት ሲሆን ይታሰብበታል ። ላሁኑ አረፍ በልና ሰውነትህን ዘና አድርገው ። እኔን ጭምር እየረበሽከኝኮ ነው። የሚበላ ነገር ይቅረብልህ ? አንድ ሣንዱች እንዲያስቀምጡልህ ለነርሶቹ ነግሬአቸዋለሁ »
«መብላት አልችልም»
«አይ አሁን አበዛኸው ። ደሞ የምን አዲስ ጠባይ ነው? ይህን ያህል ዘመን ስንኖር እንዲህ ስትሆን አይቼህ አላውቅም። በሽታው ያን ያህል ከባድ መስሎህ ነው? አልነበረም ። እና በስላሴ ይዣሀለሁ እኔን ጨምረህ አትረብሸኝ››
«የለም የለም ፤ አትምከሪኝ ። አልፈልግም ፤ አትምከሪኝ ማሪዮን ሂልያርድ። እንደፈለኩት ልሁን ስትይ እሽ ስል ምን መጣ ይኸዋ በሽታ ላይ ወድቀሽ አረፍሽው ። አሁን በዛብኝ በቃኝ። አልቻልኩም »
«በቃ ተስፋ ቆረጥክ?» አለች የፌዝ ፈገግታ ፈግጋ ተስፉ ከቆረጥክ ፤ ከሰለቸህ ለምን ሥራውን ለቀህ አረፍ አትልም›› የጆርጅ ሁኔታ የቀልድ ያህል አስደነቃት ሆኖም ፊቱን ወደሷ ሲመልስና ከጀመረው ሀሳብ ወደኋላ እንደማይል የሚገልፅ ገፅታውን ስታይ የቀልድ እድናቆቷ ወደ እውነተኛ አድናቆትና ድንጋጤ ተለወጠ ።
«ሥራ ልቀቅ አልሺኝ ፣ ማሪዮን ? እኔም አስቤ እሰላስዬ የወሰንኩት እሱን ነበር ። እኔም አንችም ሥራውን ለቀን በጡረታችን መኖር አለብን» ይቀልዳል ?... የለም ከልቡ ነው ፤ አለች በሀሳቧ ። «አትቀልድ» አለች ። ሆኖም ድምጺ የተለመደው ጥንካሬ ይጎድለው ነበር ። «ቀልድ ? ቀልድ የለም ። እንዲያውም በዚህ አብረን በኖርንበት ሃያ አመት ውስጥ እንዲሀ አይነት ጠንካራ ውሣኔ ወስኘ አላውቅም ። ሁለታችንም ከሥራ እንሰናበታለን ። ለማይክልም ይህንኑ ነግሬዋለሁ ። እግዜር ይስጠው አውሮፕላን ማረፊያ ያደረሰኝ እሱ ነበር ። ልመጣ ስላልቻልኩ በጣም አዝናለሁ ። በሥራ ተወጥሬ ነው ብሏል ። እና ተስማምተናል ። አንች ይህን አልሽ ያን አሁን ዋጋ የለውም ። ተወስኖአል ፤ያበቃ ነገር ነው»
«አበድክ ልበል ?» አለችና ከተጋደመችበት ተነስታ ቁጭ አለች ። አፈጠጠችበት ፤ በደብዛዛው ብርሃን «ልስማህና ሥራውን ትቼ ልቀመጥ እንበል ግን ምን ሳደርግ ልዋል ? ሹራብ ስሠራ ወይስ መጽሐፍ ሳነብ ?»
«ሹራብ ሥሪ ወይም መፅሐፍ አንብቢ ። የፈለገሽውን ብታደርጊ ከተስማማሽ ጥሩ ነው። ሥራውን ከተውን በኋላ ግን ወዲያውኑ የምናደርገው ነገር አለ ። እኔና አንቺ እንጋባለን ። ከዚያ በኋላ እንዳፈቀደሽ መሆን ትችያለሽ ። ግልፅ ነው?››
«እንዴት ያለ ነገር ነው ባካችሁ? ቢያንስ ቢያንስ እንድንጋባ ፈቃደኛ ነሽ ወይስ አይደለሽም ተብዬ አልጠየቅም ? ወይሰ ይኸም ከዋናው ሥራ አስኪያጅ ከማይክል የመጣ ትዕዛዝ ነው» ኣለች ማሪዮን ። ሆኖም ድምጺ የቃላቱን ያህል መከፋትም ቁጣም አልነበረበትም። ስላሰቡላት ልቧ ተነካ ። ሸክሙ ቀለል አላት ። እውነትም ይበቃታል ። ብዙ ነገር አድርጋለች መጥፎም ጥሩም ፣ እኩል በኩል ። ይህን ደግሞ ተገንዝባዋለች ። አውቃዋለች ።
ከሜሪ ኣዳምሰን (ናንሲ ማክአሊስተር ) ጋር ያንለት ያደረገችው ንግግር ይህን ጉዳይ ግልፅ አድርጎላታል ፣የዕድሜ ልክ ተግባሯን ተመልሳ እንድታይ አድርጓታል ። ደግም ከፋትም ሠርታለች ። «የማይክልን ምርቃትም አግኝተናል» አለ ጆርጅ ። ይህን ብሎ ወደ አልጋው ሄደና እጅዋን ጨብጦ «ታገቢኛለሽ፤ማሪዮን !?» ሲል እየፈራ ጠየቀ ። ይህን ያሀል ዘመን አብረው ኖረው ሲያፍራት ገረመው ። እንዲያውም ማይክል «ይገባል ። ፍቅራችሁን ልታከብሩት ይገባል» አይነት ነገር ባይለውና ምንም ትርጉሙ ግልፅ ሆኖ ለጊዜው ባይታየው «ለጋብቻው አበረታታት» ባይለው ኖሮ ላይጠይቃትም ይችል ነበር ። «ንገሪኝ እንጂ» ይህን ብሎ እጅዋን ጠበቅ አደረጋት ።
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ አምስት (35) በሆስፒታሉ ኮሪደር ውስጥ እየተጣደፈ ሲሄድ የጫማው ድምፅ ጎልቶ ይሰማ ነበር። ምን ብታስብ ነው ወደ ሳንፍራንሲስኮ ስትመጣ ብቻየን ነው የምሄድ ብላ ድርቅ ያለችው ? ይህን ያህል አመት ስትኖር ረዳት አያስፈልገኝም ፤ሁሉንም ነገር ብቻየን ልወጣው እፈልጋለሁ የምትለው ለምንድነው ? ይህን እያሰበ በሩን አንኳኳ ። አንዲት በገጺ ላይ ምን ይፈልጋሉ ? የሚል ጥያቄ የተሳለባት ነርስ በሩን ከፈተችለት ። «ማሪዮን ሂልያርድ የተኛችው እዚህ ክፍል ነው ?» ሲል ጠየቃት ። በነርሷ ገፅታ ላይ የተሳለው ጥያቄ አልተነሳም ነበረና «ጆርጅ ኮሎዌ እባላለሁ» ሲል ጨመረ ። ድካም ፡ እርጅናና ያለመረጋጋት ስሜት በፊቱ ላይ ጎልተው ይታያሉ ። እነዚህ ስሜቶች በሠራ አካላቱ ተሰራጭተው ይሰሙትም ነበር ። የለም እንዲህ አይነቱ ርባና ቢስ ነገር አሁንስ ስልችት አለኝ ። ማሪዮን በዚሀ ሁኔታ ልትቀጥል አትችልም። ዛሬ ሁሉንም ግልጥልጥ አድርጌ መንገር አለብኝ ሲል አሰበ ። እንዳገኛት ይነግራታል ። ገና ከኒውዮርክ ከመነሳቱ በፊት ይህን ውሳኔ ለማይክል ሂልያርድም ነግሮታል ።
«ሚስተር ኮሎዌ ?» አለች ነርሷ ስሙን ስትሰማ በገዝፅዋ ላይ የተሳለው ጥያቄ ወደ ፈገግታ እየተለወጠ «ስንጠባበቅ ነበር » ማሪዮን እዚህ ሆስፒታል የገባችው ምሽቱ ላይ ፤አሥራ ሁለት ሰዓት አካባቢ ሲሆን ጆርጅ ከኒውዮርክ ተነስቶ እዚያ የደረሰው ከምሽቱ ስድስት ሰዓት አካባቢ ነበር ።ይሀ ደግሞ ከኒውዮርክ ሳንፍራንሲስኮ ለመድረስ የመጨረሻው ፈጣን ጉዞ ሳይሆን አይቀርም ። ነርሷን አልፎ ገባ። ማሪዮን የጆርጅን መምጣት አይታ ፈገግ ስትል ነርሷ ከክፍሉ ውስጥ ወጥታ ወደ ሠራተኞች ማረፊያ አዳራሽ ሄደች ።
«ሄሎ ጆርጅ »
«ሄሎ ማሪዮን ፤ ተሻለሽ ?»
«ከድካሙ በስተቀር አደጋውን አልፌዋለሁ ። ማለት ሀኪሞቹ የነገሩኝ እንዲያ ብለው ነው ። ኃይለኛ አልነበረም አያያዙ»
«ዛሬስ እንዲያ ሆነ ግን ለወደፊቱስ? ወደፊት›› ጀርጅ ይህን ተናግሮ በክፍሉ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ሲንጎራደድ እርምጃው ሁሉ የአንበሳ ይመስል ነበር። ቁጣውም ለማሪዮን ግፅል ሆኖ ታያት ። ይህን ያየችው ማሪዮን ሁኔታው አስገረማት። እንደሁልጊዜው አልሰማትም ።። ብዙ ነገር ሲነግራት አስቧል ማለት ነው ። «ለወደፊቱ ፣ ወደፊት ሲሆን ይታሰብበታል ። ላሁኑ አረፍ በልና ሰውነትህን ዘና አድርገው ። እኔን ጭምር እየረበሽከኝኮ ነው። የሚበላ ነገር ይቅረብልህ ? አንድ ሣንዱች እንዲያስቀምጡልህ ለነርሶቹ ነግሬአቸዋለሁ »
«መብላት አልችልም»
«አይ አሁን አበዛኸው ። ደሞ የምን አዲስ ጠባይ ነው? ይህን ያህል ዘመን ስንኖር እንዲህ ስትሆን አይቼህ አላውቅም። በሽታው ያን ያህል ከባድ መስሎህ ነው? አልነበረም ። እና በስላሴ ይዣሀለሁ እኔን ጨምረህ አትረብሸኝ››
«የለም የለም ፤ አትምከሪኝ ። አልፈልግም ፤ አትምከሪኝ ማሪዮን ሂልያርድ። እንደፈለኩት ልሁን ስትይ እሽ ስል ምን መጣ ይኸዋ በሽታ ላይ ወድቀሽ አረፍሽው ። አሁን በዛብኝ በቃኝ። አልቻልኩም »
«በቃ ተስፋ ቆረጥክ?» አለች የፌዝ ፈገግታ ፈግጋ ተስፉ ከቆረጥክ ፤ ከሰለቸህ ለምን ሥራውን ለቀህ አረፍ አትልም›› የጆርጅ ሁኔታ የቀልድ ያህል አስደነቃት ሆኖም ፊቱን ወደሷ ሲመልስና ከጀመረው ሀሳብ ወደኋላ እንደማይል የሚገልፅ ገፅታውን ስታይ የቀልድ እድናቆቷ ወደ እውነተኛ አድናቆትና ድንጋጤ ተለወጠ ።
«ሥራ ልቀቅ አልሺኝ ፣ ማሪዮን ? እኔም አስቤ እሰላስዬ የወሰንኩት እሱን ነበር ። እኔም አንችም ሥራውን ለቀን በጡረታችን መኖር አለብን» ይቀልዳል ?... የለም ከልቡ ነው ፤ አለች በሀሳቧ ። «አትቀልድ» አለች ። ሆኖም ድምጺ የተለመደው ጥንካሬ ይጎድለው ነበር ። «ቀልድ ? ቀልድ የለም ። እንዲያውም በዚህ አብረን በኖርንበት ሃያ አመት ውስጥ እንዲሀ አይነት ጠንካራ ውሣኔ ወስኘ አላውቅም ። ሁለታችንም ከሥራ እንሰናበታለን ። ለማይክልም ይህንኑ ነግሬዋለሁ ። እግዜር ይስጠው አውሮፕላን ማረፊያ ያደረሰኝ እሱ ነበር ። ልመጣ ስላልቻልኩ በጣም አዝናለሁ ። በሥራ ተወጥሬ ነው ብሏል ። እና ተስማምተናል ። አንች ይህን አልሽ ያን አሁን ዋጋ የለውም ። ተወስኖአል ፤ያበቃ ነገር ነው»
«አበድክ ልበል ?» አለችና ከተጋደመችበት ተነስታ ቁጭ አለች ። አፈጠጠችበት ፤ በደብዛዛው ብርሃን «ልስማህና ሥራውን ትቼ ልቀመጥ እንበል ግን ምን ሳደርግ ልዋል ? ሹራብ ስሠራ ወይስ መጽሐፍ ሳነብ ?»
«ሹራብ ሥሪ ወይም መፅሐፍ አንብቢ ። የፈለገሽውን ብታደርጊ ከተስማማሽ ጥሩ ነው። ሥራውን ከተውን በኋላ ግን ወዲያውኑ የምናደርገው ነገር አለ ። እኔና አንቺ እንጋባለን ። ከዚያ በኋላ እንዳፈቀደሽ መሆን ትችያለሽ ። ግልፅ ነው?››
«እንዴት ያለ ነገር ነው ባካችሁ? ቢያንስ ቢያንስ እንድንጋባ ፈቃደኛ ነሽ ወይስ አይደለሽም ተብዬ አልጠየቅም ? ወይሰ ይኸም ከዋናው ሥራ አስኪያጅ ከማይክል የመጣ ትዕዛዝ ነው» ኣለች ማሪዮን ። ሆኖም ድምጺ የቃላቱን ያህል መከፋትም ቁጣም አልነበረበትም። ስላሰቡላት ልቧ ተነካ ። ሸክሙ ቀለል አላት ። እውነትም ይበቃታል ። ብዙ ነገር አድርጋለች መጥፎም ጥሩም ፣ እኩል በኩል ። ይህን ደግሞ ተገንዝባዋለች ። አውቃዋለች ።
ከሜሪ ኣዳምሰን (ናንሲ ማክአሊስተር ) ጋር ያንለት ያደረገችው ንግግር ይህን ጉዳይ ግልፅ አድርጎላታል ፣የዕድሜ ልክ ተግባሯን ተመልሳ እንድታይ አድርጓታል ። ደግም ከፋትም ሠርታለች ። «የማይክልን ምርቃትም አግኝተናል» አለ ጆርጅ ። ይህን ብሎ ወደ አልጋው ሄደና እጅዋን ጨብጦ «ታገቢኛለሽ፤ማሪዮን !?» ሲል እየፈራ ጠየቀ ። ይህን ያሀል ዘመን አብረው ኖረው ሲያፍራት ገረመው ። እንዲያውም ማይክል «ይገባል ። ፍቅራችሁን ልታከብሩት ይገባል» አይነት ነገር ባይለውና ምንም ትርጉሙ ግልፅ ሆኖ ለጊዜው ባይታየው «ለጋብቻው አበረታታት» ባይለው ኖሮ ላይጠይቃትም ይችል ነበር ። «ንገሪኝ እንጂ» ይህን ብሎ እጅዋን ጠበቅ አደረጋት ።
👍27🥰2
ማሪዮን ሂልያርድ ቀስ ብላ ከልብ የሆነ ግን ደከም ያለ ፈገግታ እያሳየችውና እራሷን በአወንታ እየነቀነቀች… «ቀደም ብለን ልናስበው ይገባ ነበር ፤ ጆርጅ» አለችው ። «እኔ ገና ዱሮ ነው ያሰብኩት ። ግን በጅ አትልም ስል ተውኩት» አለ ጆርጅ። «ደሞ ልክ ሳትሆን አትቀርም ። ያኔ ብትነግረኝ ሳይገርመኝ አይቀርም ነበር ። በጄ ማለቱን ተወው ። ጅልኮ ነኝ» አለች ። ይህን ብላ በረጂሙ ተንፍሳ ተጋደመችና ትራሱን ደገፍ ብ… «እንዴት አድርጌ በሕይወቴ ተጫወትኩባት» ስትል ተፀፀተች። «አረ እንደሱ አይባልም ተይ» አለ ጆርጅ «እኔ ሳውቅሽ ሕይወትሽን በሙሉ በትጋት ፤ በአዋቂነት ፤ ቁም ነገር በመሥራት ነው ያሳለፍሺው» እጅዋን ይዞ በፍቅር ያሻሻት ጀመር ። ለረጂም ጊዜ ሲመኘው የነበረ ነገር ነው ። «ደሞም ያለፈ ነገር አልፏል ። ባለፈ ፋይዳ ቢስ ስህተት እየተፀፀቱ ራስን መጉዳት ጥቅም የለውም» ሲል ጨመረ። ይህን ስትሰማ ማሪዮን ከተጋደመችበት ተነስታ ተቀመጠችና ትኩር ብላ እያየችውና እጅዋ ድንገት ቅዝቅዝና ጥንክር እያለ «ግን...ግን ይኸ ፋይዳ ቢስ ያልከው ስህተት የሌሎችን ሕይወት አበላሽቶ ቢሆንስ?... ልርሳህ ብለውስ የሚረሳልኝ ይመስልሃል ጆርጅ ?» አለች ። «ምነው ማሪዮን እያወቅሽው? የሌላ ሰው ህይወት ለማበላሸት ምን ጊዜ ኖሮሽ ?» ሲል ጠየቃት ።
በአእምሮው ውስጥ ዶክተሩ የእንቅልፍ ክኒን ወይም ህመም እንዳይሰማት የሚያደርግ መድኃኒት ሰጥቷት ይሆን ? ሲል ጠየቀ ። ያለዚያ እንዲህ አይነት ቅብጥርጥር ከማሪዮን የሚጠበቅ እንዳይደለ እየገመተ ። «አንተ እማታውቀው ብዙ ነገር አለ ጆርጅ ። አይገባህም ነገሩ»
«ሁሉንም ማወቅ አለብኝ ?»
«ምናልባት ። ምናልባት ማወቅ ይኖርብህ ይሆናል ። ብታውቅ ደግሞ ልታገባኝ አትፈልግም ነበር ። ምናልባት »
«ፍሬ ከርስኪ !ይህን ሀሳብ ከልብሽ አስወጭው ። ይልቅ እንዲያ ካልሽ ነገሩን የማወቅ መብት አለኝኮ። ስለዚሀ ያስጨነቀሽን ነገር ንገሪኝ» ማሪዮን በሀሳብ ተውጣ አትኩራ እያየችው ለረጂም ጊዜ ዝም ካለች በኋላ…. «እንጃ ፤መናገር መቻሌንም እንጃ» አለች ። «ለምን ? ለኔ ፈርተሽልኝ ፣ ይከፋዋል ይቀፈዋል ብለሽ ፈርተሽልኝ ከሆነ እርሺው ። በዚች ዓለም ላይ ይኸ አእምሮዬን ይበጠብጠዋል የምለው ነገር የለኝም ። ደሞም ላንቺ መስሎሽ እንጂ እኔ ሳስበው የምትነግሪኝ ነገር ይኸኔ የማውቀው ነው ። ስላንቺ ማላውቅው ነገር አለ ብዬ አላስብም» አለና በስጋት እየተመለክታት «የለም ። የልብ በሽታው ሲነሳብሽ ጊዜ ትንሽ ሳያስደነ ግጥሽና ሳያናውጥሽ አልቀረም መሰለኝ»
«በሽታው ሳይሆን ስሸሸው የነበረ ዛሬ ፊት ለፊት የተጋ ፈጥኩት እውነት ነው እንዲህ ያናወፀኝ»
«ምን?.... አንድ የተለዬ ነገር አጋጥሞሽ ነበር ?» አለ ከብዙ ፀጥታና ሀሳብ በኋላ ። ቶሎ አልመለሰችለትም ። ጠበቀ ቆይታ
«አዎ» ስትል ተናገረች ። «እንዲያ ነው?» አለ…. ጥያቄ ሳይሆን ገባኝ እንደማለት ። «የሆነውም ቢሆን አሁን እንርሳው ። አረፍ ማለት ያስፈልግሻል። ጉዳዩን አንስቶ መድገም አያሻም ። ይቆይልን ይህን ሲል ስጋቱ ይታወቅ ነበር ። ከድምጹ፣፤ ከገፅታው ልብ ድካሟ እንደገና ቢነሳስ ? የሚለው ጥያቄ ይነበብ ነበር ። ስለዚህ ያጋጠማትንም ነገር አልጠየቃትም ። «ከልጅቷ ጋር ተገናኘን» አለች ማሪዮን ። «የምን ልጅ ?» አለ ጆርጅ ፤ ሴትዮ ምንድነው እምታወሪው በሚል ድምፅ።
እንባዋ መውረድ ጀምሯል ።
«ስለየትኛዋ ልጅ ማለትሽ ነው?» አለ ጆርጅ እየተጨነቀ። ዝም ብላ ስታየው ቆይታ እንባዋን ገትታ… «ማይክል የወደዳት ፤ አፍቅሮ ሊያገባት የነበረችው ልጅ» አለች ማሪዮን ተስተካክላ እየተቀመጠች ። «ታስታውሳለህ ጆርጅ ? ማይክ አደጋ የደረሰበት ቀን… ማታ ትዝ ይልሀል ? ሊያነጋግረኝ እንኳ መጥቶ ። ትዝ ካለህ ያንለት ልክ እንተ ስትገባ እሱ ወጥቶ አልሄደም ? እየተቆጣ ? ያንለት የመጣው ልጅቷን እንደሚያገባት ሊነግረኝ ነበር ። እኔ ደግሞ ስለቤተሰቧ ያሠራሁትን ሪፖርት ሰጠሁት »
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
በአእምሮው ውስጥ ዶክተሩ የእንቅልፍ ክኒን ወይም ህመም እንዳይሰማት የሚያደርግ መድኃኒት ሰጥቷት ይሆን ? ሲል ጠየቀ ። ያለዚያ እንዲህ አይነት ቅብጥርጥር ከማሪዮን የሚጠበቅ እንዳይደለ እየገመተ ። «አንተ እማታውቀው ብዙ ነገር አለ ጆርጅ ። አይገባህም ነገሩ»
«ሁሉንም ማወቅ አለብኝ ?»
«ምናልባት ። ምናልባት ማወቅ ይኖርብህ ይሆናል ። ብታውቅ ደግሞ ልታገባኝ አትፈልግም ነበር ። ምናልባት »
«ፍሬ ከርስኪ !ይህን ሀሳብ ከልብሽ አስወጭው ። ይልቅ እንዲያ ካልሽ ነገሩን የማወቅ መብት አለኝኮ። ስለዚሀ ያስጨነቀሽን ነገር ንገሪኝ» ማሪዮን በሀሳብ ተውጣ አትኩራ እያየችው ለረጂም ጊዜ ዝም ካለች በኋላ…. «እንጃ ፤መናገር መቻሌንም እንጃ» አለች ። «ለምን ? ለኔ ፈርተሽልኝ ፣ ይከፋዋል ይቀፈዋል ብለሽ ፈርተሽልኝ ከሆነ እርሺው ። በዚች ዓለም ላይ ይኸ አእምሮዬን ይበጠብጠዋል የምለው ነገር የለኝም ። ደሞም ላንቺ መስሎሽ እንጂ እኔ ሳስበው የምትነግሪኝ ነገር ይኸኔ የማውቀው ነው ። ስላንቺ ማላውቅው ነገር አለ ብዬ አላስብም» አለና በስጋት እየተመለክታት «የለም ። የልብ በሽታው ሲነሳብሽ ጊዜ ትንሽ ሳያስደነ ግጥሽና ሳያናውጥሽ አልቀረም መሰለኝ»
«በሽታው ሳይሆን ስሸሸው የነበረ ዛሬ ፊት ለፊት የተጋ ፈጥኩት እውነት ነው እንዲህ ያናወፀኝ»
«ምን?.... አንድ የተለዬ ነገር አጋጥሞሽ ነበር ?» አለ ከብዙ ፀጥታና ሀሳብ በኋላ ። ቶሎ አልመለሰችለትም ። ጠበቀ ቆይታ
«አዎ» ስትል ተናገረች ። «እንዲያ ነው?» አለ…. ጥያቄ ሳይሆን ገባኝ እንደማለት ። «የሆነውም ቢሆን አሁን እንርሳው ። አረፍ ማለት ያስፈልግሻል። ጉዳዩን አንስቶ መድገም አያሻም ። ይቆይልን ይህን ሲል ስጋቱ ይታወቅ ነበር ። ከድምጹ፣፤ ከገፅታው ልብ ድካሟ እንደገና ቢነሳስ ? የሚለው ጥያቄ ይነበብ ነበር ። ስለዚህ ያጋጠማትንም ነገር አልጠየቃትም ። «ከልጅቷ ጋር ተገናኘን» አለች ማሪዮን ። «የምን ልጅ ?» አለ ጆርጅ ፤ ሴትዮ ምንድነው እምታወሪው በሚል ድምፅ።
እንባዋ መውረድ ጀምሯል ።
«ስለየትኛዋ ልጅ ማለትሽ ነው?» አለ ጆርጅ እየተጨነቀ። ዝም ብላ ስታየው ቆይታ እንባዋን ገትታ… «ማይክል የወደዳት ፤ አፍቅሮ ሊያገባት የነበረችው ልጅ» አለች ማሪዮን ተስተካክላ እየተቀመጠች ። «ታስታውሳለህ ጆርጅ ? ማይክ አደጋ የደረሰበት ቀን… ማታ ትዝ ይልሀል ? ሊያነጋግረኝ እንኳ መጥቶ ። ትዝ ካለህ ያንለት ልክ እንተ ስትገባ እሱ ወጥቶ አልሄደም ? እየተቆጣ ? ያንለት የመጣው ልጅቷን እንደሚያገባት ሊነግረኝ ነበር ። እኔ ደግሞ ስለቤተሰቧ ያሠራሁትን ሪፖርት ሰጠሁት »
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍23
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
..ደልቲ ገልዲ በራሱ የሚተማመን ጀግና በመሆኑ በዚህ ዓለም ላይ
ከእሱ በላይ ሰው ያለ አይመስለውም" ስለሆነም፥ የሚፈልገውን አጣለሁ የሚል ቅንጣት ታህል ጥርጣሬ የለውም" በስሙ ሲዘፈንና ሲዘመር ጥርሱን እየፋቀ በርኳታው (መቀመጫው) ላይ ቁጭ ብሎ ወይንም ጋደም ብሎ መዝናናት ነው;
ጀግንነት ከሀብት ጋር ገና ዕድሜው ሳይገፋ፥ «ቤት ለእንቦሳ» ሲል «እንቦሳ እሠር» ብሎ፥ ተቀብሎታል" በእርግጥ እያንዳንዱ
የሐመር ጓዳ ላጠቃላይ ማኅበረሰቡ ግልጽ ነው። ተካፍሎ መመገብ፥
ተሰባስቦ መጨፈር፥ ተከባብሮ መኖር፥ ጠላትን በጋራ ማጥቃትና
መደናነቅ የማኅበረሰቡ ወግና ልማድ ነው። ደልቲ ገልዲም የዚህ ባህላዊ ኑሮ ተሳታፊና ተገዥ በመሆኑ ኃይሉን ተማምኖ ሌላውን የሐመር አባል ማጥቃትም ሆነ ንብረት መቀማት ክብሩን ለውርደት፥ ሀብቱን
ለጥፋት ስለሚያበቃ ከልጅነቱ ጀምሮ ክብርንና መብትን በጥንቃቄ
መያዙንና ተከባብሮና ተመካክሮ መኖርን ሊዘነጋ አልቻለም።
ደልቲ ገልዲ፥ በዚያን ሰሞን ወደ መንደራቸው የመጣችውን እንግዳ የተመለከታት በኲራት ነበር" የለበሰችውን ጨርቅና
የምትሸተው ቃና ከአካባቢው ልጃገረዶች ጠረን የተለየ በመሆኑ ራቅ
ብሎ ነው ያስተዋላት።
«እንደ ሐመር ሴቶች ቆዳ የማትለብሰውና ጭኖቿን የማታሳየው ምናልባት የሚያሳፍር ነገር ቢኖርባት ይሆናል» ብሎ፥ከመገመቱም
በላይ የሴትነት ጠረኗን የዋጠው ሽታ አስጠልቶት ነበር በተደጋጋሚ
ቀናት እንዳያትም በሚኰርፍ ነገር መተጣጠቧ ብልግናዋን ከማረጋገጡም በላይ መጥፎ ጠረኗን ለማጥፋት መሆኑን አምኖበታል"
የሐመር ልጃገረዶች በውኃ አይታጠቡም። «ብልታቸውን ውኃ ከነካው መካን ይሆናሉ» ስለሚባል፣ በጣም ነውር ነው" ይህችኛዋ እንግዳ ግን አልፎ አልፎ ብቻ ሳይሆን ዘወትር ስትተጣጠብ ያያታል" «መካንነቷ መቼም የማይቀር ነው" ግን ሴት ሆና ስትተጣጠብ
የማታፍር ምኒቱ ባለጌ ናት?» እያለ ኮንኗታል። ሌላውም እንደሱ
በድርጊቷ ጠልቷታል"
ሆኖም እሱ የጀግኖች ጀግና ነው፤ እንዲህ ዓይነቷን ባለጌ ልክ የማግባቱ ኃላፊነት ከሱ ትከሻ ላይ የወደቀ ነው" ስለዚህ፣ እንግዳይቱን በግርፋትም ቢሆን ሥነ ሥርዓትን ሊያስተምራት ይችላል"
ይህን ለማድረግ ደግሞ፣ እሷን ማግባት አለበት" ካለበለዚያ ዝንቧንም እሽ ማለት ላይችል ነው ደግሞኮ የሱ ሚስቶች በመልካቸው ጥቋቁሮች ናቸውI ስለዚህ ነጭ ሚስት ያስፈልገዋል" ሀብቱ
እንደሆነ የትየለሌ ነውI ሦስት በረት ከብት፣ በየጋጡ ብዛት ያለው ፍየል፣ በየጫካው ለቍጥር የሚታክት ቀፎ አለው" በዚያ ላይ የቀጭኔ፣ የጎሽ፣ የአንበሳና የሰው ገዳይ ነው።
ስለዚህ፣ ይህችን ባለጌ ለማረቅ እንዲችል እሷን የራሱ የሚያደርግበት በቂ ሀብት አለው። እና፣ የሚጠየቀውን ጥሎሽ ከፍሎ የሱ ንብረት ካደረጋት በኋላ ቢቀጣት ጠያቂ የለበትም። ለዚህ ሁሉ
ግን፣ ሚስቱ እንድትሆን ማድረግ እንዳለበት አመነ። አብሯት የመጣው ከሎ ሆራ እንደሆነ ምኗም እንዳልሆነ አረጋግጧል"
አንድ ቀን ካርለትና ከሎ ሆራ ሲጨዋወቱ ደልቲ ገልዲ
«ነጋያ» ብሎ አጠገባቸው ለመቀመጥ ይዞት በሚዞረው በርኮታ ላይ
መሣሪያውን ጭኖቹ መሃል አድርጎ ተቀመጠ" ከዚያም፣ «ባል አለሽ?» ብሎ በቋንቋው ጠየቃት" ይሉኝታና ፍርሃት የሐመርን
ተወላጅ ሲያልፍም አይነካካውም" ደግሞስ ሰው ሰው ነው" ያውም
እሱ ጀግናው። ከሎ ሆራ ያለውን ለካርለት ተረጐመላት።
«የለኝም» አለችው" ካርለት በቀኝ እጇ ግንባሯ ላይ
የተበታተነውን ጸጕር ወደ ኋላዋ እየመለሰች።
«አባትሽ ስንት ከብት አለው?» አላት፣ ደልቲ።
«ከብት የለውም፣ ፕሮፌሰር ነበር" ስለዚህ ደመወዙ…»
ፕሮፌሰር፣ ደመወዝ ያለችው ሊገባው አይችልም። ከባለጌ የሚጠበቅ
ተራ የተራ ነገር ይሆናልና ስለሱ ማሰብ አያስፈልግም።
«ቀፎና ፍየልስ?» ጠየቀ ደልቲ።
«የለውም» አለች" አባቷ ደሃ ቢሆን ነው ማለት ነው ወደዚህ የላካት ብሎ አዘነላት" በሐመር ማኅበረሰብ ሀብት ማለት ከብት፣ ፍየል፣ ቀፎ ነው። ከዚህ ውጭ ደመወዝ፣ ቪላ፣ መኪና ብሎ ሐተታ፣
የሚገባው የለም። ደልቲ ገልዲ በክልሉ የሀብት ሁሉ ባለቤት አባወራው እንደሆነ
አሳምሮ ያውቃል" ስለዚህ፣ እንግዳዋን ስለ እናቷ
አያስፈልግም" ደግሞ ሴትን፣ «ሀብት አላት ወይ?» ብሎ መጠየቅ ነውር ነው። የእንግዳዋን አባት ሁኔታ እንደሆነ ጠይቆ፣ ድህነቱን
ተረድቷል
ደልቲ ገልዲ በእሱና በእንግዳዋ አባት ሀብት መካከል ያለው ልዩነት የሰማይና የምድር ያህል ሰፍቶ ታየው" ለምግብ ማቅረቢያ፣ ለመኝታ የምትጠቀምበት፣ በተለይም ማታ ማታ «ፋ» የምታደርገው መብራትና ብልጭልጭ ቅራቅንቦዋ፣ ከሱ ንብረት አንፃር ሲታይ
ጠጠርና ተራራን ማወዳደር ቢሆንም፣ አባቷ ሀብቱን ለምን ለእሷ እንደተወላት ግራ ገብቶታል። የሱ ወገን የሆኑት የሐመር ሴቶች የግሌ የሚሉት ሀብታቸው የሚለብሱት ቆዳ፣ ጨሌና አንባራቸውን ብቻ
እንደሆነ ጥርት አድርጎ ያውቃል።
ያም ሆነ ይህ ግን፣ እንግዳዋን አግብቶ በግርፋት መግራት እንዲችል ሊያገባት መፈለጉን ለሽማግሎች ማማከር አለበት ሽማግሎች የሚሉት ባይታወቅም ብልግናዋን ገልጾ ሊገራት እንደሚፈልግ
ሲነግራቸው እነሱም ይህን ስለሚረዱ ተቃውሞ እንደማይኖራቸው
ተማምኗል" አንድ ግን ግራ የገባው ጉዳይ አለ" ጋብቻውን ሽማግሎች ቢቀበሉት «ልጅቱን ለማግባት፣ አባቷ የት ተገኝቶ በሽማግሎች
ይጠየቃል? ጥሎሹንስ እንዴት ወስዶ ከችግሩ ይላቀቃል?» ብሎ
አሰበ።
ይህ ከሆነ በኋላ ግን፣ ብዙም ሳይቆይ ደልቲ ገልዲና ካርለት በምሽት ጭፈራ ተገናኙ ካርለት ያ አስደናቂ ጥያቄ ሲጠይቃት
የነበረው ወላንሳ እየዘለለና እያሸበሸበ ሲደንስና ሲሥቅ፣ ደጋግማ
ስታየው ሁሉን ነገር በተለይም ስለሱ የሚባለውን ሁሉ አስታወሰች። ስለዚህ፣ ዛሬ ይህን ስሙ በሐመር ሰማይ ላይ የሚንሳፈፍ ሰው ማንነት ማወቅ አለባት"
ያም ሆኖ ግን ካርለት ስሜቷ ለሁለት ተከፈለባት" በአገሯ ምን ዓይነት ውበትና ጠባይ ያላቸው ወንዶች በሴቶች እንደሚፈቀሩ፣ ከሞላ ጎደል ታውቃለች። እሷም ብትሆን በአፍላው የወጣትነት ጊዜዋ የነበራት የስሜት ቅብጥብጥነትና በምታፈቅረው ወንድ ላይ
ታጠምደው የነበረውን መረብ አስታወሰች" ሆኖም ይህ ሰው እዚ
ከምታውቃቸው ሰዎች በብዙ መልኩ ይለያል ለነገሩ የደልቲ ውበት
ጭጋግ ለብሶ ይታያልI ያውም ይኖራል ብላ ያልገመተችው ውበ
የሐመር ልጃገረዶችን ሕሊና ያማልላል ተብሎ የሚደነቀውን ልበ ሙሉ ወንድ ጭጋጉን በታትና ሥነ ውበቱን በትክhል መቁጠር አለባት" የለንደኑ፣ የቦኑ፣ የማንቸስተሩ..ወጥመዷ ያለውን የመያዝ ችሎታም መፈተን ይኖርባታል"
እንደ ባልጩት ድንጋይ የለሰለሰውን ገላውንና በጨረቃ የሚያንፀባርቁት ጥርሶቹን ባሰበች ቍጥር ጥርት ጎላ እያሉ ታይዋት
ስለዚህ፣ ማራኪውና የመጨረሻ ዓይነት የጭፈራ ምት መጀመሪያው ጊዜ መቃረቡን ስታውቅ፣ ሐሳቧን ተግባራዊ ለማድረግ ለሩጫ
እንደሚዘጋጅ ሯጭ አደፈጠች።
ያን የወቅቱን ወላንሳና ቀብራራ ሐመር ጠብቃ ለዳንስ ስትጋብዘውና እያኮበኮበ፣ አየሩን በመቅዘፍ ቀርቦ ጥቁሩ ጭኑ ከነጩ ጭኗ ሲተሻሽ፣ ሸካራና ጠንካራ እጆቹ ትከሻዋን ሲይዙ፣ ስሜቱ
በስሜቷ ውስጥ ሲሟሟ፣ ያለችበትን ቦታና ሰዎችን በመዘንጋት የሚያቃጥል፣ የሚነዝርና በሰመመን የሚያሰጥም ስሜት እንደ
ተሰማት፣ ከራሷ ቍጥጥር ውጭ ሆነች" ስለዚህ፣ ሁሉን ነገር ዘንግታ
ተንጠራርታ አንገቱን በማቀፍ ከንፈሯን ከከንፈሩ ጋር ለማላተም
ተጣጣረች ደልቲ ግን፣ በጠንካራ እጆቹ እጇን ያዝ አድርጎ፣ የዳንሱን ቦታ ጥሎ፣ ወደ ጫካ ይዟት ገባ፤ ጥቁሩና ነጭ አባይ ጫካ መሃል ተገናኙ።
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
..ደልቲ ገልዲ በራሱ የሚተማመን ጀግና በመሆኑ በዚህ ዓለም ላይ
ከእሱ በላይ ሰው ያለ አይመስለውም" ስለሆነም፥ የሚፈልገውን አጣለሁ የሚል ቅንጣት ታህል ጥርጣሬ የለውም" በስሙ ሲዘፈንና ሲዘመር ጥርሱን እየፋቀ በርኳታው (መቀመጫው) ላይ ቁጭ ብሎ ወይንም ጋደም ብሎ መዝናናት ነው;
ጀግንነት ከሀብት ጋር ገና ዕድሜው ሳይገፋ፥ «ቤት ለእንቦሳ» ሲል «እንቦሳ እሠር» ብሎ፥ ተቀብሎታል" በእርግጥ እያንዳንዱ
የሐመር ጓዳ ላጠቃላይ ማኅበረሰቡ ግልጽ ነው። ተካፍሎ መመገብ፥
ተሰባስቦ መጨፈር፥ ተከባብሮ መኖር፥ ጠላትን በጋራ ማጥቃትና
መደናነቅ የማኅበረሰቡ ወግና ልማድ ነው። ደልቲ ገልዲም የዚህ ባህላዊ ኑሮ ተሳታፊና ተገዥ በመሆኑ ኃይሉን ተማምኖ ሌላውን የሐመር አባል ማጥቃትም ሆነ ንብረት መቀማት ክብሩን ለውርደት፥ ሀብቱን
ለጥፋት ስለሚያበቃ ከልጅነቱ ጀምሮ ክብርንና መብትን በጥንቃቄ
መያዙንና ተከባብሮና ተመካክሮ መኖርን ሊዘነጋ አልቻለም።
ደልቲ ገልዲ፥ በዚያን ሰሞን ወደ መንደራቸው የመጣችውን እንግዳ የተመለከታት በኲራት ነበር" የለበሰችውን ጨርቅና
የምትሸተው ቃና ከአካባቢው ልጃገረዶች ጠረን የተለየ በመሆኑ ራቅ
ብሎ ነው ያስተዋላት።
«እንደ ሐመር ሴቶች ቆዳ የማትለብሰውና ጭኖቿን የማታሳየው ምናልባት የሚያሳፍር ነገር ቢኖርባት ይሆናል» ብሎ፥ከመገመቱም
በላይ የሴትነት ጠረኗን የዋጠው ሽታ አስጠልቶት ነበር በተደጋጋሚ
ቀናት እንዳያትም በሚኰርፍ ነገር መተጣጠቧ ብልግናዋን ከማረጋገጡም በላይ መጥፎ ጠረኗን ለማጥፋት መሆኑን አምኖበታል"
የሐመር ልጃገረዶች በውኃ አይታጠቡም። «ብልታቸውን ውኃ ከነካው መካን ይሆናሉ» ስለሚባል፣ በጣም ነውር ነው" ይህችኛዋ እንግዳ ግን አልፎ አልፎ ብቻ ሳይሆን ዘወትር ስትተጣጠብ ያያታል" «መካንነቷ መቼም የማይቀር ነው" ግን ሴት ሆና ስትተጣጠብ
የማታፍር ምኒቱ ባለጌ ናት?» እያለ ኮንኗታል። ሌላውም እንደሱ
በድርጊቷ ጠልቷታል"
ሆኖም እሱ የጀግኖች ጀግና ነው፤ እንዲህ ዓይነቷን ባለጌ ልክ የማግባቱ ኃላፊነት ከሱ ትከሻ ላይ የወደቀ ነው" ስለዚህ፣ እንግዳይቱን በግርፋትም ቢሆን ሥነ ሥርዓትን ሊያስተምራት ይችላል"
ይህን ለማድረግ ደግሞ፣ እሷን ማግባት አለበት" ካለበለዚያ ዝንቧንም እሽ ማለት ላይችል ነው ደግሞኮ የሱ ሚስቶች በመልካቸው ጥቋቁሮች ናቸውI ስለዚህ ነጭ ሚስት ያስፈልገዋል" ሀብቱ
እንደሆነ የትየለሌ ነውI ሦስት በረት ከብት፣ በየጋጡ ብዛት ያለው ፍየል፣ በየጫካው ለቍጥር የሚታክት ቀፎ አለው" በዚያ ላይ የቀጭኔ፣ የጎሽ፣ የአንበሳና የሰው ገዳይ ነው።
ስለዚህ፣ ይህችን ባለጌ ለማረቅ እንዲችል እሷን የራሱ የሚያደርግበት በቂ ሀብት አለው። እና፣ የሚጠየቀውን ጥሎሽ ከፍሎ የሱ ንብረት ካደረጋት በኋላ ቢቀጣት ጠያቂ የለበትም። ለዚህ ሁሉ
ግን፣ ሚስቱ እንድትሆን ማድረግ እንዳለበት አመነ። አብሯት የመጣው ከሎ ሆራ እንደሆነ ምኗም እንዳልሆነ አረጋግጧል"
አንድ ቀን ካርለትና ከሎ ሆራ ሲጨዋወቱ ደልቲ ገልዲ
«ነጋያ» ብሎ አጠገባቸው ለመቀመጥ ይዞት በሚዞረው በርኮታ ላይ
መሣሪያውን ጭኖቹ መሃል አድርጎ ተቀመጠ" ከዚያም፣ «ባል አለሽ?» ብሎ በቋንቋው ጠየቃት" ይሉኝታና ፍርሃት የሐመርን
ተወላጅ ሲያልፍም አይነካካውም" ደግሞስ ሰው ሰው ነው" ያውም
እሱ ጀግናው። ከሎ ሆራ ያለውን ለካርለት ተረጐመላት።
«የለኝም» አለችው" ካርለት በቀኝ እጇ ግንባሯ ላይ
የተበታተነውን ጸጕር ወደ ኋላዋ እየመለሰች።
«አባትሽ ስንት ከብት አለው?» አላት፣ ደልቲ።
«ከብት የለውም፣ ፕሮፌሰር ነበር" ስለዚህ ደመወዙ…»
ፕሮፌሰር፣ ደመወዝ ያለችው ሊገባው አይችልም። ከባለጌ የሚጠበቅ
ተራ የተራ ነገር ይሆናልና ስለሱ ማሰብ አያስፈልግም።
«ቀፎና ፍየልስ?» ጠየቀ ደልቲ።
«የለውም» አለች" አባቷ ደሃ ቢሆን ነው ማለት ነው ወደዚህ የላካት ብሎ አዘነላት" በሐመር ማኅበረሰብ ሀብት ማለት ከብት፣ ፍየል፣ ቀፎ ነው። ከዚህ ውጭ ደመወዝ፣ ቪላ፣ መኪና ብሎ ሐተታ፣
የሚገባው የለም። ደልቲ ገልዲ በክልሉ የሀብት ሁሉ ባለቤት አባወራው እንደሆነ
አሳምሮ ያውቃል" ስለዚህ፣ እንግዳዋን ስለ እናቷ
አያስፈልግም" ደግሞ ሴትን፣ «ሀብት አላት ወይ?» ብሎ መጠየቅ ነውር ነው። የእንግዳዋን አባት ሁኔታ እንደሆነ ጠይቆ፣ ድህነቱን
ተረድቷል
ደልቲ ገልዲ በእሱና በእንግዳዋ አባት ሀብት መካከል ያለው ልዩነት የሰማይና የምድር ያህል ሰፍቶ ታየው" ለምግብ ማቅረቢያ፣ ለመኝታ የምትጠቀምበት፣ በተለይም ማታ ማታ «ፋ» የምታደርገው መብራትና ብልጭልጭ ቅራቅንቦዋ፣ ከሱ ንብረት አንፃር ሲታይ
ጠጠርና ተራራን ማወዳደር ቢሆንም፣ አባቷ ሀብቱን ለምን ለእሷ እንደተወላት ግራ ገብቶታል። የሱ ወገን የሆኑት የሐመር ሴቶች የግሌ የሚሉት ሀብታቸው የሚለብሱት ቆዳ፣ ጨሌና አንባራቸውን ብቻ
እንደሆነ ጥርት አድርጎ ያውቃል።
ያም ሆነ ይህ ግን፣ እንግዳዋን አግብቶ በግርፋት መግራት እንዲችል ሊያገባት መፈለጉን ለሽማግሎች ማማከር አለበት ሽማግሎች የሚሉት ባይታወቅም ብልግናዋን ገልጾ ሊገራት እንደሚፈልግ
ሲነግራቸው እነሱም ይህን ስለሚረዱ ተቃውሞ እንደማይኖራቸው
ተማምኗል" አንድ ግን ግራ የገባው ጉዳይ አለ" ጋብቻውን ሽማግሎች ቢቀበሉት «ልጅቱን ለማግባት፣ አባቷ የት ተገኝቶ በሽማግሎች
ይጠየቃል? ጥሎሹንስ እንዴት ወስዶ ከችግሩ ይላቀቃል?» ብሎ
አሰበ።
ይህ ከሆነ በኋላ ግን፣ ብዙም ሳይቆይ ደልቲ ገልዲና ካርለት በምሽት ጭፈራ ተገናኙ ካርለት ያ አስደናቂ ጥያቄ ሲጠይቃት
የነበረው ወላንሳ እየዘለለና እያሸበሸበ ሲደንስና ሲሥቅ፣ ደጋግማ
ስታየው ሁሉን ነገር በተለይም ስለሱ የሚባለውን ሁሉ አስታወሰች። ስለዚህ፣ ዛሬ ይህን ስሙ በሐመር ሰማይ ላይ የሚንሳፈፍ ሰው ማንነት ማወቅ አለባት"
ያም ሆኖ ግን ካርለት ስሜቷ ለሁለት ተከፈለባት" በአገሯ ምን ዓይነት ውበትና ጠባይ ያላቸው ወንዶች በሴቶች እንደሚፈቀሩ፣ ከሞላ ጎደል ታውቃለች። እሷም ብትሆን በአፍላው የወጣትነት ጊዜዋ የነበራት የስሜት ቅብጥብጥነትና በምታፈቅረው ወንድ ላይ
ታጠምደው የነበረውን መረብ አስታወሰች" ሆኖም ይህ ሰው እዚ
ከምታውቃቸው ሰዎች በብዙ መልኩ ይለያል ለነገሩ የደልቲ ውበት
ጭጋግ ለብሶ ይታያልI ያውም ይኖራል ብላ ያልገመተችው ውበ
የሐመር ልጃገረዶችን ሕሊና ያማልላል ተብሎ የሚደነቀውን ልበ ሙሉ ወንድ ጭጋጉን በታትና ሥነ ውበቱን በትክhል መቁጠር አለባት" የለንደኑ፣ የቦኑ፣ የማንቸስተሩ..ወጥመዷ ያለውን የመያዝ ችሎታም መፈተን ይኖርባታል"
እንደ ባልጩት ድንጋይ የለሰለሰውን ገላውንና በጨረቃ የሚያንፀባርቁት ጥርሶቹን ባሰበች ቍጥር ጥርት ጎላ እያሉ ታይዋት
ስለዚህ፣ ማራኪውና የመጨረሻ ዓይነት የጭፈራ ምት መጀመሪያው ጊዜ መቃረቡን ስታውቅ፣ ሐሳቧን ተግባራዊ ለማድረግ ለሩጫ
እንደሚዘጋጅ ሯጭ አደፈጠች።
ያን የወቅቱን ወላንሳና ቀብራራ ሐመር ጠብቃ ለዳንስ ስትጋብዘውና እያኮበኮበ፣ አየሩን በመቅዘፍ ቀርቦ ጥቁሩ ጭኑ ከነጩ ጭኗ ሲተሻሽ፣ ሸካራና ጠንካራ እጆቹ ትከሻዋን ሲይዙ፣ ስሜቱ
በስሜቷ ውስጥ ሲሟሟ፣ ያለችበትን ቦታና ሰዎችን በመዘንጋት የሚያቃጥል፣ የሚነዝርና በሰመመን የሚያሰጥም ስሜት እንደ
ተሰማት፣ ከራሷ ቍጥጥር ውጭ ሆነች" ስለዚህ፣ ሁሉን ነገር ዘንግታ
ተንጠራርታ አንገቱን በማቀፍ ከንፈሯን ከከንፈሩ ጋር ለማላተም
ተጣጣረች ደልቲ ግን፣ በጠንካራ እጆቹ እጇን ያዝ አድርጎ፣ የዳንሱን ቦታ ጥሎ፣ ወደ ጫካ ይዟት ገባ፤ ጥቁሩና ነጭ አባይ ጫካ መሃል ተገናኙ።
👍24👎1
ደልቲ ገልዲ ከእንግዳዋ ጋር ግንኙነት ከፈጠረ ጊዜ ጀምሮ፣ በተለይም በጭፈራ ቦታ፣ በሁለቱም መፈቃቀድ ግንኙነት ማድረጋቸው ቢቀጥልም በእንግዳዋ ላይ የሚያየው ባሕርይ ይበል
ግራ እያጋባው መምጣቱ አልቀረም። የእንግዳዋ ሰውነት እጅግ ለስላሳ ከመሆኑ የተነሣ እንኳን ተገርፋ ሲነኩት የሚላጥ ይመስላል" እጅና እግሯ በአጠቃላይ ሁለመናዋ መለስለሱ አስገርሞታል
«እንዴት ነው ይህች ሰው ሳታርስ፣ ሳትፈጭ፣ የከብቶችን እበት
ሳትጠርግና እንጨት ሳትለቅም ነው የኖረችው » በማለት ተደንቋል"
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አንድ ወቅት ሐመሮች ግብር አንከፍልም ብለው አመፁ ቢቻል በስምምነት ካልተቻለ በኃይል እንዲያስገብሩ አፄ ኃይለ ሥላሴ የሠለጠነ ወታደር ወደ ሐመር ይልካሉ" በዚያ ወቀት፣ ሐመሮች ባላሰቡት ጊዜ ጥያቄውን በወታደር መልእክተኛ ይጠየቃሉ። ሆኖም ግን ፈቃደኛ አለመሆናቸውን በመግለጻቸው ውጊያ ተጀመረና የሐመሮች ሕይወት የሆነው የከስኬ ወንዝ ከሞላ ጎደል በወታደሮች ተያዘ። ሐመሮች በለመዱት ክልል ከቋጥኝ ቋጥኝ እየዘለሉ ኋላ ቀር በሆነው መሣሪያ ጠንክረው ቢዋጉም በመትረየስና በተሻለ መሣሪያና ስንቅ በመምጣት በከስኬ ወንዝ አሸዋ ጉድባ ሠርቶ ጥይት የሚያዘንብባቸውን ኃይል መቋቋም ተሳናቸው
በዚህ መልክ ጥቂት ቀን እንደ ቆዩ በውኃ ጥምና ስንቅ ማጣት ሐመሮች እየተጠቁ የመላ ያለህ ሲባል ለአውሬ አደን የመጣ
መንገደኛ በጦርነት ለእነሱ በመርዳት ሲታኰስ ሰነበተ። ልብ ያላሉት እንግዳ ወታደሩ የመሸገበትን ሲያስተውል በወንዙ ጠርዝና ጠርዝ
ባሉት ዛፎች ብዙ ቀፎዎች ተሰቅለው በማየቱ ዒላማውን እዚያ ላይ
በማድረጉ ከቀፎው ተረብሸው የሚወጡት ንቦች ወታደሩን ጒድጓዱ
ድረስ በመግባት ቁም ስቅሉን ስላሳዩት ከምሽጉ እየዘለለ ለመውጣት
ተገደደ» ሐመሮች ከምሽጉ የሚወጣውን ወታደር ከላይ እየቀለቡ ሲያስቀሩ እንደ ቆዩ የእሩምታ ተኵስ ቀልጦ፣ በተኵሱ ሽፋን
ወታደሮች በመሸሻቸው ከስኬ ወንዝን ማስመለስ ተቻለ" ግጭቱም
ሳይደገም በእርቅ አለቀ።
ሐመሮች ያን ጸጕረ ልውጥ መንገደኛ ከሞት አትርፈውታል። እሱም በተራው ይከፍለዋል ብለው ከጠበቁት በላቀ ሁኔታ ውለታውን መለሰላቸው። ስለዚህ መንገደኛውን ከብት በመስጠት እንደ
አባት የሚመርጠው ሽማግሌ፣ ዘመዶች የሆኑ ልጃገረዶች እንደሚገርፉለትና ሚስት እንደሚያገባ፣ እንደ አንድ የሐመር አባልም እንደሚቈጠር በመግለጽ ስለ ለመኑት መንገደኛው ትንሽ ካቅማማ በኋላ ሆድ የባሰውና ተስፋ የቈረጠ ስለነበር ተስማማ።
መንገደኛው፣ አመጣጡ ከወደ መንዝ ነው። ለስሙ ዘሩ የባላባት ይሁን እንጂ እሱም ሆነ ቤተሰቦቹ የነጡ ድሆች ነበሩ" ስለዚህ ቋት
ለማይሞላው ሕይወቱ ደፋ ቀና እያለ፣ በእርሻ ቀንና ምሽት ሲባዝን ኖረ። ከልጅነቱ ጀምሮ ሠርቶ ከሚከበረው፣ ገሎ የሚደነቀውና ከበሬታን የሚያገኘው ሲልቅ ሲያይ ኖሯልና ጀግና ተብሎ መከበሩና ወገኖቹንም ማስከበሩ ሕሊናውን እያሸፈተበትና ልቡን እያቆመበት መጣ። በተለይ ወደ ደቡብ ተጕዘው የአንበሳ፣ የጎሽ፣ የዝሆን…ገዳይ እየተባሉ የሚመለሱት፣ በአካባቢው ያላቸውን ከበሬታ ሲመለከት
አንዳንዴም ከብት ውኃ ለማጠጣት ወይም ልብሱን ለማጠብ ወደ ምንጭ ውኃው ወረድ ባለ ቍጥር፣ የገዳይ ሚስት ተራ ሳትጠብቅ ገብታ ውኃውን ቀድታ እንስራዋን በመሸከም፣ ቀሚሷን ሳብ ሳብ አድርጋ እያንጐራጐረች ሞንደል ሞንደል እያለች ስትሄድ፣ ተራ ጠባቂ ሴቶች፣ «.ኧረ ኤዲያልኝ…አኮራታ…ወይ ነዶ.የኛዎቹማ
ወንዶች ምድጃ ለምድጃ፣ ሽሮው ቀጠነ› ይበሉ…አይ ሱሪ እቴ…ኧረ እንዲያው ወይ ነዶ! አንሶ አሳናሽ...ሙቅ ሁላ» ሲሉ
አንገቱን ደፍቶ ሲሰማ አንጀቱ እየተኰማተረ፣ ልቡ የገበታ ውኃ እየሆነ፣ ቤቱም ቤት አልመስለው እያለ ከርሞ.ቆይ ከመንፈቅ
ወዲያ…..እሄዳለሁ» ሲል ኖሮ፣ እንደሱ ልባቸው ከኮበለለው ጋር
ዘጠኝ ሆነው ስንቃቸውን ቋጥረው በድብቅ ጕዞ ጀመሩ፤ ወደ ደቡብ
ኢትዮጵያ።
ከጕዞው ሦስት ዓመታት በፊት መሆኑ ነው፤ ጥር ላይ ይሄው መንገደኛ በአጎቱ ልጅ ሠርግ ጊዜ ነጠላውን አጣጥፎ ሲያስተናግድ
የደም ገንቦ የሆነች ዓይን አፋር ወጣት ለዘፈን እንድትገባ ስትለመን
ማስተናገዱን ትቶ ትኵር ብሎ ተመለከታት" ልጅቱ አንገቷን ሰበር አድርጋ፣ ነጠላዋን ከትከሻዋ አውርዳ ወገቧ ላይ ስታደርግ፣ እሱ
ደግሞ አንገቱን ሰገግ አድርጎ፣ እሷን ለማየት ተንጠራራ" ከበሮው
ድልድልድል እያለ ሲመታና ጭብጨባው ቀልጦ፣
«...እንዴነሽ ገዳዎ...» ሲባል፣ ወጣቷ እግሯንና እጇን በስልት እያንቀሳቀሰች፣ ስታሸበሽብ ቆየችና፣ «ኦሆ…ዎ» ብሎ፣
አቀንቃኙ፣ «ደርብ፣ ምታ.» ሲል፣ ልጅቷ እንደ ባሕር ቀጤማ ትውረገረግ ጀመር።
ይህ መንገደኛ በልጅቷ ውበትና እንቅስቃሴ ተደንቆ፣ በመፍዘዝ
ሲመለከታት እንደ ቆየ፣ አንዳች ነገር ልቡን ነሸጠውና ዘሎ ዘፈኑ
ውስጥ ሲገባ፣ ጭብጨባው ቀለጠ" ልጅቷም ልቧ ሞላ" ሁለቱም
ገጠሙ መንገደኛው እስክስታውን እየወረደ ያያታል፣ እሷ ግን
ዓይኗን እያስለመለመች ትውረገረጋለች" እሱ ቀስ በቀስ እየፈዘዘ መጣ መወዛወዙን አቆመና ባለበት ቆመ ልጅቷ እስከስታ
የገጠማትን ሰው ምት ዓይኗን ገልጣ ለማየት ስትሞክር ቆሟል"
ትኵር ብላ ትመለከተችው።
ከዘፈኑ ከወጡ በኋላ ያጎቱን ሠርግ ረሳ ማስተናገዱንም ተወው ልጅቷ በሄደችበት ሁሉ የሚከተል ያሳደገችው ውሻ ሆነ" ሲነካት
ትሸሸው፣ ሲቆነጥጣት ስታመናጭቀው ቆዩ እሱ ግን በማመናጨቋ
የሚበረግግ አልሆነም። ይባስ ብሎ ሌሎችን ጐረምሶች እየገላመጠ
ሲከታተላት እንደ ቆየ፣ ለሽንት ወጣ ስትል አብሮ ተከትሏት ወጣና ስትመለስ አድፍጦ ያዛት፤ ወዲያው ወደ ታዛው ይዟት ወደቀ።
አንገራገረች በኋላ ግን...
ከዚች ወጣት ጋር ግንኙነታቸው በስርቆሽ ቀጥሎ እንደ ሰነባበቱ
ወላጆቿ ለሁለተኛ ባል ዳሯት" ሲፈልግ፣ ሲያስፈላልግ ከርሞ፣
አንድ ቀን ድንገት ከቅዳሜ ገበያ ሲመለስ ተገናኙ" ያለፈውን ፍቅሯን ያውቃልና ገና ሲያያት ልቡ ሞላ፤ ናፍቆቱ አገረሸበት
ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ፤
«...እህሳ» ሲላት"
«አሁንማ የጀግና ሚስት ነኝ የገዳይ ባለቤት» ብላ፣ በኵራት መንፈስ ፊት ነስታው ከሄደች ወዲህ እሱም፣ «ገዳይ መባል አለብኝ» ብሎ፣ ውሳኔውን አጠናከረ።
ረጅሙን ጕዟቸውን የጀመሩት በእግር ሲሆን፣ በመጀመሪያዎቹ
የጕዞ ቀናት መንገዱ ተገፍቶላቸው ነበር። በኋላ ግን፣ ቀስ በቀስ ጕዟቸው የኤሊ ጕዞ ሆነ" ውኃ ጥሙ፣ ረሃቡ፣ ድካሙ ጥንዝል ቢያደርጋቸውም፣ በተለይም ወይጦና ተልተሌ በረሃ ላይ ሲጓዙ
አቅጣጫቸውን በመሳት በአዙሪት ኃይል ወደ መጡበት ሲመለሱ
ከቆዩ በኋላ በአጋጣሚ በቅሎ ከጫኑ መንገደኞች ጋር ተገናኙ ያጋጣሚ ጉዳይ ሆኖ የሚሄዱበት አካባቢም አንድ በመሆኑ አንድ ላይ
መጓዝ ጀመሩ"
ነጋዴዎች አቅጣጫ እንዳይጠፋባቸው በመኝታ ጊዜ እግራቸውን
ወደ መጡበት፣ እራሳቸውን ወደሚሄዱበት አቅጣጫ ከማድረጋቸው ሌላ፣ አቅጣጫቸውንም ለማወቅ ባላ እየተከሉ ምልክት በማድረግ፣ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ባኮ hተባለው ከተማ በሦስተኛ ወራቸው
ደረሱ።
ባኮ ከደረሱ በኋላ፣ ለአውሬ አደን መምጣታቸውን በመግለጽ ከባህላዊ አሳዳኞች ጋ ተገናኙ" አሳዳኞች ሁለት ምንሽርና አንድ ቤልጅግ ጠመንጃ ያላቸው ሲሆን፣ መንገደኞቹም የተለያየ ቍጥር ያለው የምንሽርና የቤልጅግ ጥይቶችን ከመያዛቸው ባሻገር
የማርትሬዛ ብር ይዘው ስለመጡ፣ ከአሳዳኞች ጋር በቀላሉ ተግባብተው ወደ በረሃ ወረዱ።
ግራ እያጋባው መምጣቱ አልቀረም። የእንግዳዋ ሰውነት እጅግ ለስላሳ ከመሆኑ የተነሣ እንኳን ተገርፋ ሲነኩት የሚላጥ ይመስላል" እጅና እግሯ በአጠቃላይ ሁለመናዋ መለስለሱ አስገርሞታል
«እንዴት ነው ይህች ሰው ሳታርስ፣ ሳትፈጭ፣ የከብቶችን እበት
ሳትጠርግና እንጨት ሳትለቅም ነው የኖረችው » በማለት ተደንቋል"
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አንድ ወቅት ሐመሮች ግብር አንከፍልም ብለው አመፁ ቢቻል በስምምነት ካልተቻለ በኃይል እንዲያስገብሩ አፄ ኃይለ ሥላሴ የሠለጠነ ወታደር ወደ ሐመር ይልካሉ" በዚያ ወቀት፣ ሐመሮች ባላሰቡት ጊዜ ጥያቄውን በወታደር መልእክተኛ ይጠየቃሉ። ሆኖም ግን ፈቃደኛ አለመሆናቸውን በመግለጻቸው ውጊያ ተጀመረና የሐመሮች ሕይወት የሆነው የከስኬ ወንዝ ከሞላ ጎደል በወታደሮች ተያዘ። ሐመሮች በለመዱት ክልል ከቋጥኝ ቋጥኝ እየዘለሉ ኋላ ቀር በሆነው መሣሪያ ጠንክረው ቢዋጉም በመትረየስና በተሻለ መሣሪያና ስንቅ በመምጣት በከስኬ ወንዝ አሸዋ ጉድባ ሠርቶ ጥይት የሚያዘንብባቸውን ኃይል መቋቋም ተሳናቸው
በዚህ መልክ ጥቂት ቀን እንደ ቆዩ በውኃ ጥምና ስንቅ ማጣት ሐመሮች እየተጠቁ የመላ ያለህ ሲባል ለአውሬ አደን የመጣ
መንገደኛ በጦርነት ለእነሱ በመርዳት ሲታኰስ ሰነበተ። ልብ ያላሉት እንግዳ ወታደሩ የመሸገበትን ሲያስተውል በወንዙ ጠርዝና ጠርዝ
ባሉት ዛፎች ብዙ ቀፎዎች ተሰቅለው በማየቱ ዒላማውን እዚያ ላይ
በማድረጉ ከቀፎው ተረብሸው የሚወጡት ንቦች ወታደሩን ጒድጓዱ
ድረስ በመግባት ቁም ስቅሉን ስላሳዩት ከምሽጉ እየዘለለ ለመውጣት
ተገደደ» ሐመሮች ከምሽጉ የሚወጣውን ወታደር ከላይ እየቀለቡ ሲያስቀሩ እንደ ቆዩ የእሩምታ ተኵስ ቀልጦ፣ በተኵሱ ሽፋን
ወታደሮች በመሸሻቸው ከስኬ ወንዝን ማስመለስ ተቻለ" ግጭቱም
ሳይደገም በእርቅ አለቀ።
ሐመሮች ያን ጸጕረ ልውጥ መንገደኛ ከሞት አትርፈውታል። እሱም በተራው ይከፍለዋል ብለው ከጠበቁት በላቀ ሁኔታ ውለታውን መለሰላቸው። ስለዚህ መንገደኛውን ከብት በመስጠት እንደ
አባት የሚመርጠው ሽማግሌ፣ ዘመዶች የሆኑ ልጃገረዶች እንደሚገርፉለትና ሚስት እንደሚያገባ፣ እንደ አንድ የሐመር አባልም እንደሚቈጠር በመግለጽ ስለ ለመኑት መንገደኛው ትንሽ ካቅማማ በኋላ ሆድ የባሰውና ተስፋ የቈረጠ ስለነበር ተስማማ።
መንገደኛው፣ አመጣጡ ከወደ መንዝ ነው። ለስሙ ዘሩ የባላባት ይሁን እንጂ እሱም ሆነ ቤተሰቦቹ የነጡ ድሆች ነበሩ" ስለዚህ ቋት
ለማይሞላው ሕይወቱ ደፋ ቀና እያለ፣ በእርሻ ቀንና ምሽት ሲባዝን ኖረ። ከልጅነቱ ጀምሮ ሠርቶ ከሚከበረው፣ ገሎ የሚደነቀውና ከበሬታን የሚያገኘው ሲልቅ ሲያይ ኖሯልና ጀግና ተብሎ መከበሩና ወገኖቹንም ማስከበሩ ሕሊናውን እያሸፈተበትና ልቡን እያቆመበት መጣ። በተለይ ወደ ደቡብ ተጕዘው የአንበሳ፣ የጎሽ፣ የዝሆን…ገዳይ እየተባሉ የሚመለሱት፣ በአካባቢው ያላቸውን ከበሬታ ሲመለከት
አንዳንዴም ከብት ውኃ ለማጠጣት ወይም ልብሱን ለማጠብ ወደ ምንጭ ውኃው ወረድ ባለ ቍጥር፣ የገዳይ ሚስት ተራ ሳትጠብቅ ገብታ ውኃውን ቀድታ እንስራዋን በመሸከም፣ ቀሚሷን ሳብ ሳብ አድርጋ እያንጐራጐረች ሞንደል ሞንደል እያለች ስትሄድ፣ ተራ ጠባቂ ሴቶች፣ «.ኧረ ኤዲያልኝ…አኮራታ…ወይ ነዶ.የኛዎቹማ
ወንዶች ምድጃ ለምድጃ፣ ሽሮው ቀጠነ› ይበሉ…አይ ሱሪ እቴ…ኧረ እንዲያው ወይ ነዶ! አንሶ አሳናሽ...ሙቅ ሁላ» ሲሉ
አንገቱን ደፍቶ ሲሰማ አንጀቱ እየተኰማተረ፣ ልቡ የገበታ ውኃ እየሆነ፣ ቤቱም ቤት አልመስለው እያለ ከርሞ.ቆይ ከመንፈቅ
ወዲያ…..እሄዳለሁ» ሲል ኖሮ፣ እንደሱ ልባቸው ከኮበለለው ጋር
ዘጠኝ ሆነው ስንቃቸውን ቋጥረው በድብቅ ጕዞ ጀመሩ፤ ወደ ደቡብ
ኢትዮጵያ።
ከጕዞው ሦስት ዓመታት በፊት መሆኑ ነው፤ ጥር ላይ ይሄው መንገደኛ በአጎቱ ልጅ ሠርግ ጊዜ ነጠላውን አጣጥፎ ሲያስተናግድ
የደም ገንቦ የሆነች ዓይን አፋር ወጣት ለዘፈን እንድትገባ ስትለመን
ማስተናገዱን ትቶ ትኵር ብሎ ተመለከታት" ልጅቱ አንገቷን ሰበር አድርጋ፣ ነጠላዋን ከትከሻዋ አውርዳ ወገቧ ላይ ስታደርግ፣ እሱ
ደግሞ አንገቱን ሰገግ አድርጎ፣ እሷን ለማየት ተንጠራራ" ከበሮው
ድልድልድል እያለ ሲመታና ጭብጨባው ቀልጦ፣
«...እንዴነሽ ገዳዎ...» ሲባል፣ ወጣቷ እግሯንና እጇን በስልት እያንቀሳቀሰች፣ ስታሸበሽብ ቆየችና፣ «ኦሆ…ዎ» ብሎ፣
አቀንቃኙ፣ «ደርብ፣ ምታ.» ሲል፣ ልጅቷ እንደ ባሕር ቀጤማ ትውረገረግ ጀመር።
ይህ መንገደኛ በልጅቷ ውበትና እንቅስቃሴ ተደንቆ፣ በመፍዘዝ
ሲመለከታት እንደ ቆየ፣ አንዳች ነገር ልቡን ነሸጠውና ዘሎ ዘፈኑ
ውስጥ ሲገባ፣ ጭብጨባው ቀለጠ" ልጅቷም ልቧ ሞላ" ሁለቱም
ገጠሙ መንገደኛው እስክስታውን እየወረደ ያያታል፣ እሷ ግን
ዓይኗን እያስለመለመች ትውረገረጋለች" እሱ ቀስ በቀስ እየፈዘዘ መጣ መወዛወዙን አቆመና ባለበት ቆመ ልጅቷ እስከስታ
የገጠማትን ሰው ምት ዓይኗን ገልጣ ለማየት ስትሞክር ቆሟል"
ትኵር ብላ ትመለከተችው።
ከዘፈኑ ከወጡ በኋላ ያጎቱን ሠርግ ረሳ ማስተናገዱንም ተወው ልጅቷ በሄደችበት ሁሉ የሚከተል ያሳደገችው ውሻ ሆነ" ሲነካት
ትሸሸው፣ ሲቆነጥጣት ስታመናጭቀው ቆዩ እሱ ግን በማመናጨቋ
የሚበረግግ አልሆነም። ይባስ ብሎ ሌሎችን ጐረምሶች እየገላመጠ
ሲከታተላት እንደ ቆየ፣ ለሽንት ወጣ ስትል አብሮ ተከትሏት ወጣና ስትመለስ አድፍጦ ያዛት፤ ወዲያው ወደ ታዛው ይዟት ወደቀ።
አንገራገረች በኋላ ግን...
ከዚች ወጣት ጋር ግንኙነታቸው በስርቆሽ ቀጥሎ እንደ ሰነባበቱ
ወላጆቿ ለሁለተኛ ባል ዳሯት" ሲፈልግ፣ ሲያስፈላልግ ከርሞ፣
አንድ ቀን ድንገት ከቅዳሜ ገበያ ሲመለስ ተገናኙ" ያለፈውን ፍቅሯን ያውቃልና ገና ሲያያት ልቡ ሞላ፤ ናፍቆቱ አገረሸበት
ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ፤
«...እህሳ» ሲላት"
«አሁንማ የጀግና ሚስት ነኝ የገዳይ ባለቤት» ብላ፣ በኵራት መንፈስ ፊት ነስታው ከሄደች ወዲህ እሱም፣ «ገዳይ መባል አለብኝ» ብሎ፣ ውሳኔውን አጠናከረ።
ረጅሙን ጕዟቸውን የጀመሩት በእግር ሲሆን፣ በመጀመሪያዎቹ
የጕዞ ቀናት መንገዱ ተገፍቶላቸው ነበር። በኋላ ግን፣ ቀስ በቀስ ጕዟቸው የኤሊ ጕዞ ሆነ" ውኃ ጥሙ፣ ረሃቡ፣ ድካሙ ጥንዝል ቢያደርጋቸውም፣ በተለይም ወይጦና ተልተሌ በረሃ ላይ ሲጓዙ
አቅጣጫቸውን በመሳት በአዙሪት ኃይል ወደ መጡበት ሲመለሱ
ከቆዩ በኋላ በአጋጣሚ በቅሎ ከጫኑ መንገደኞች ጋር ተገናኙ ያጋጣሚ ጉዳይ ሆኖ የሚሄዱበት አካባቢም አንድ በመሆኑ አንድ ላይ
መጓዝ ጀመሩ"
ነጋዴዎች አቅጣጫ እንዳይጠፋባቸው በመኝታ ጊዜ እግራቸውን
ወደ መጡበት፣ እራሳቸውን ወደሚሄዱበት አቅጣጫ ከማድረጋቸው ሌላ፣ አቅጣጫቸውንም ለማወቅ ባላ እየተከሉ ምልክት በማድረግ፣ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ባኮ hተባለው ከተማ በሦስተኛ ወራቸው
ደረሱ።
ባኮ ከደረሱ በኋላ፣ ለአውሬ አደን መምጣታቸውን በመግለጽ ከባህላዊ አሳዳኞች ጋ ተገናኙ" አሳዳኞች ሁለት ምንሽርና አንድ ቤልጅግ ጠመንጃ ያላቸው ሲሆን፣ መንገደኞቹም የተለያየ ቍጥር ያለው የምንሽርና የቤልጅግ ጥይቶችን ከመያዛቸው ባሻገር
የማርትሬዛ ብር ይዘው ስለመጡ፣ ከአሳዳኞች ጋር በቀላሉ ተግባብተው ወደ በረሃ ወረዱ።
👍12
ምንም እንኳ ከማጎ ወንዝ ሲርቁ በውኃ እጦት ቢቸገሩም፣ አውሬ
እያደኑ ጥብሱንም፣ ጥሬውንም፣ ቋንጣውንም፣ አልፎ አልፎም በሶውንም እየተመገቡ ችግሩን እየተቋቋሙ ቆዩ"
በመጨረሻም ባመጡት ጥይትና በተውሶ መሣሪያ እንደ ዕድላቸው ጎሽም፣ አንበሳም፣ አውራሪስም በመግደል ተጠባብቀው
ለሁለት ወር ከሳምንት በረሃ ቆዩ።
ሁሉም ቀንቷቸው አውሬውን ከገደሉ በኋላ፣ የነገው የጀግንነት ገድል ታሪክ በየቀያቸው ሲያስተጋባ ወንዱ አንገቱን ሲደፋ፣ ሴቷ
አይታቸው ስትሽኮረመም፣ ሽማግሎች (ጀግና ነው! ወንድ እያሉ ሲያወድሷቸው፣ ሚስቶቻቸው ከአካባቢው ሴቶች ልዕልና አግኝተው ሲያንጐራጕሩላቸው እየታያቸው፣ በደስታ እየሸለሉና እያቅራሩ የመልስ ጕዞ አደረጉ" ከዚያም፣ ካሳዳኞች ጋር የመለያያ ግብዣ አልጋ ከተባለው መንደር አቅራቢያ አደረጉ"
በመጨረሻም፣ መንገደኞት ከያዙት ጥይትና ማርትሬዛ ብር ከውላቸው ተጨማሪ ለአሳዳኞች ሸልመው፣ ተቃቅፈው በመሳሳም
መራርቀው ተለያዩ
አሳዳኞት ግን፣ የባኮን አቀበት ጕዞ እንደ ተያያዙ የጠጡት ሰዎች የያዙትን ጥይትና ብር እንዲያስታውሱና እንዲጐመዡ አደረጋቸው" መንገደኞቹ ከአልጋ መንደር
ያስመጡትን የአበሻ አረቄ እየጠጡ ሲያቅራሩ ቆይተው በያሉበት በመጠጥ ኃይል ተዳክመው ሲተኙ፣ ሁለቱ አሳዳኞች ተኩስ ከፍተው
ስምንቱን ገደሏቸው" አንዱ ግን እንደ ነብር አጓርቶ፣ አንዱን አሳዳኝ
ከነጠመንጃው በማነቅ ከመሬት ደባልቆ ጥይቱን በጆሮግንዱ ለቀቀበት" ከዚያም ከሁለተኛው ጋር እየተታኰሰ አባረረው"
ይሁን እንጂ፣ ከትንሽ ጊዜ በፊት አብረውት የነበሩት ሁሉ አልቀው፣ በዘጠኝ አስከሬን መከበቡን ሲያውቅ ፍርሃት አናወጠው"
ሰማይ ምድሩ ዞረበት «እየዬም ሲዳላ ነውና» እንባው ነጠፈ። ተስፋው ጨለመ፤ ጀግንነቱን ረሳው። የቀረው አማራጭ ምን እንደሆነ አያውቅም" ሙት መሃል ቢሆንም እሱም ከእንግዲህ ሙት ነው
ስለዚህ ዝም ብሎ ወደ ጫካው ሸሸ። ብርሃን ወዳላየው ጨለማ ገባ"
ብቸኛው መንገደኛ፣ የት እንደሚሄድ ቀርቶ የት እንዳለ እንኳ አያውቅም" ብቻ መጓዝ ሆነ፣ «ወደ መንዝስ እንግዲህ በምን አባቴ እሄዳለሁ? እንዴትስ ብዬ የዘመዶቼን ዓይን አያለሁ? ምንስ ዋጣቸው እላለሁ? ኧረ እኔንም ጅቡ ይብላኝ፤ ካለ ምስክር የቀረሁ ከንቱ ነኝ» እያለ፣ አቅሙ እስከቻለ ተጓዘ
መንገደኛው በመጨረሻ ሲደክመው፣ «አይ ሞኝነቴ አሁን እንግዲህ መልፋቴ ማን እንዲገለኝ ፈልጌ ይሆን? አውሬው በላኝ፣ ረሃብ ገደለኝ ሰው ገደለኝ ላልተርፍ ምን አስፈራኝ? እንዲያው እኮ ይገርማል ያለሁበትንና የምሄድበትን አላውቅ እና መሞቴን
እረስቼ ለመኖር ምን አቃዥኝ፣ ያሻው ይገላግለኝ» ብሎ፣ መተኛቱን
ያስታውሳል" ሲነቃ ግን፣ ጥቋቁር ጠብደሎች ከበውታል። መሣሪያ
አንግተዋል" ጦር፣ ጩቤ፣ መጥረቢያ የያዙም ይታዩታል“ አማትቦ
መልሶ ዓይኑን ከደነ። ሰዎቹ ግን ጠቆም ጠቆም እያደረጉ እንዲነሣ አደረጉት። ሁሉንም በየተራ አያቸው፤ እንኳን የሚያውቀው ሊኖር
የሚሉትም አልገባውም በሐሳቡ፣ «እንግዲህ መሞቴ ላይቀር በምን
እንግደልህ በመሣሪያ ነው፣ በጦር እያሉ እስኪጠይቁኝ ነው የምጠብቀው? ስታገላቸው እሞታለሁ» ብሎ ግብግብ ገጠመ" ትንሽ ታግሎ ቢያስቸግራቸውም፣ ከመሬት ደባልቀው ጕሮሮው ላይ መሣሪያ ደገኑበት። መንገደኛው፣ «ለካ የመጨረሻው ዕድሌ በጥይት መሞት ኖሯል!» ብሉ ዓይኖቹን ጨፈነ"
ሐመሮች መሣሪያና ጥይት ከምንም ነገር በላይ ይወዳሉ። ተኳሾችም ናቸው" በማንም ላይ ግን ቃታ በድንገት አይስቡም" የሚገድሉትን ሰው ማንነት ለይተው ማረጋገጥ አለባቸው።
የሚገድሉት «ቢታው» እንዲገድሉ የፈቀደላቸውን ነው። ቢታ ማለት ጥንት የነበረ ሲሆን፣ ሲወለድ በግራ ብብቱ ንብ፣ በቀኝ ብብቱ እበት ይዞ የተወለደና ከቦርጆ (አምላከ) ጋር ማኅበረሰቡን የሚያገናኝ
ቅዱስ ሰው ነው፣ ብለው ስለሚያምኑ ቢታው ካወጣላቸው ደንብ
ዝንፍ ሳይሉ ለዓመታት የኖሩ ናቸው።
እንግዳው የሙርሲ፣ የማሌ…ማኅበረሰብ አባል ቢሆን ኖሮ ቢታው እንዲገድሉ የፈቀደላቸው ስለሆነ ይገሉት ነበር። እንግዳው ግን የተለየ ነው። ስለዚህ ሳይገሉት ቀሩ። እንዲያውም የደከመ
ሰውነቱን የከብት ደምና ወተት በማጠጣትና ፍየልና በግ በማረድ ያን እየሰበቁ መረቁን እንዲጠጣና ሥጋውንም እንዲበላ በማድረጋቸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያገግም አደረጉት" ከዚህ በኋላ ግን፣ ሐመሮች ከመንግሥት ወታደሮች ጋር ባደረጉት ጦርነት ለእነሱ አብሮ ተዋጋ። መዋጋትም ብቻ ሳይሆን፣ በሱ ስልት ከእልቂት አዳናቸው። ለዚህም ለፈጸመው ትብብር ከብት ዘሎ፣ ልጃገረዶች ተገርፈውለት ሚስት አገባ።
የዚህ እንግዳ ሰው ስም አንተነህ ይመር ይባል እንጂ ከብት ሲዘል መጀመሪያ እግሩ የረገጠበት ትንሽ ጥጃ ቀለሟን በማየት ጋልታምቤ ተባለ።
ጋልታምቤ ከሐመር ማኅበረሰብ አባል ከሆነችው ሚስቱ አንዲት
ሴት ልጅ ወልዶ፣ ቋንቋውን፣ አለባበሱን፣ አመጋገቡን ተለማምዶ ደስ ብሎት የሚኖር ሰው ሆነ።
ጋልታምቤ ሃያ ዓመት ሙሉ ሐመር ውስጥ ሲኖር የተቸገረበት፣ የተለየበት አንዳችም ሁኔታ የለም ከቋቋው ልዩነት በስተቀር
ይህ ነው የሚባል የጎሳ ልዩነት እሱ ከሚያውቀው የተለየ የለም"
በሐመር ማኅበረሰብ ችግርን በሽማግሎች ምክክርና በማኅበረሰቡ
ነፃ ውይይት መፍታት እንጂ፣ ችግርን በተናጠልና በኃይል መፍታት በኗሪዎች በሙሉ የተወገዘ ነው።
ተመካከሮ፣ ተከባብሮ፣ ተፈቃቅሮ፣ደካማና ጠንካራው ካለሥጋት የሚኖርበት ማኅበረሰብ በመሆኑ እንግዳው ጋልታምቤ እንኳን እሱ ለልጅ ልጆቹም ከዚያ የተሻለ ዓለም አይመርጥላቸውም"
💫ይቀጥላል💫
እያደኑ ጥብሱንም፣ ጥሬውንም፣ ቋንጣውንም፣ አልፎ አልፎም በሶውንም እየተመገቡ ችግሩን እየተቋቋሙ ቆዩ"
በመጨረሻም ባመጡት ጥይትና በተውሶ መሣሪያ እንደ ዕድላቸው ጎሽም፣ አንበሳም፣ አውራሪስም በመግደል ተጠባብቀው
ለሁለት ወር ከሳምንት በረሃ ቆዩ።
ሁሉም ቀንቷቸው አውሬውን ከገደሉ በኋላ፣ የነገው የጀግንነት ገድል ታሪክ በየቀያቸው ሲያስተጋባ ወንዱ አንገቱን ሲደፋ፣ ሴቷ
አይታቸው ስትሽኮረመም፣ ሽማግሎች (ጀግና ነው! ወንድ እያሉ ሲያወድሷቸው፣ ሚስቶቻቸው ከአካባቢው ሴቶች ልዕልና አግኝተው ሲያንጐራጕሩላቸው እየታያቸው፣ በደስታ እየሸለሉና እያቅራሩ የመልስ ጕዞ አደረጉ" ከዚያም፣ ካሳዳኞች ጋር የመለያያ ግብዣ አልጋ ከተባለው መንደር አቅራቢያ አደረጉ"
በመጨረሻም፣ መንገደኞት ከያዙት ጥይትና ማርትሬዛ ብር ከውላቸው ተጨማሪ ለአሳዳኞች ሸልመው፣ ተቃቅፈው በመሳሳም
መራርቀው ተለያዩ
አሳዳኞት ግን፣ የባኮን አቀበት ጕዞ እንደ ተያያዙ የጠጡት ሰዎች የያዙትን ጥይትና ብር እንዲያስታውሱና እንዲጐመዡ አደረጋቸው" መንገደኞቹ ከአልጋ መንደር
ያስመጡትን የአበሻ አረቄ እየጠጡ ሲያቅራሩ ቆይተው በያሉበት በመጠጥ ኃይል ተዳክመው ሲተኙ፣ ሁለቱ አሳዳኞች ተኩስ ከፍተው
ስምንቱን ገደሏቸው" አንዱ ግን እንደ ነብር አጓርቶ፣ አንዱን አሳዳኝ
ከነጠመንጃው በማነቅ ከመሬት ደባልቆ ጥይቱን በጆሮግንዱ ለቀቀበት" ከዚያም ከሁለተኛው ጋር እየተታኰሰ አባረረው"
ይሁን እንጂ፣ ከትንሽ ጊዜ በፊት አብረውት የነበሩት ሁሉ አልቀው፣ በዘጠኝ አስከሬን መከበቡን ሲያውቅ ፍርሃት አናወጠው"
ሰማይ ምድሩ ዞረበት «እየዬም ሲዳላ ነውና» እንባው ነጠፈ። ተስፋው ጨለመ፤ ጀግንነቱን ረሳው። የቀረው አማራጭ ምን እንደሆነ አያውቅም" ሙት መሃል ቢሆንም እሱም ከእንግዲህ ሙት ነው
ስለዚህ ዝም ብሎ ወደ ጫካው ሸሸ። ብርሃን ወዳላየው ጨለማ ገባ"
ብቸኛው መንገደኛ፣ የት እንደሚሄድ ቀርቶ የት እንዳለ እንኳ አያውቅም" ብቻ መጓዝ ሆነ፣ «ወደ መንዝስ እንግዲህ በምን አባቴ እሄዳለሁ? እንዴትስ ብዬ የዘመዶቼን ዓይን አያለሁ? ምንስ ዋጣቸው እላለሁ? ኧረ እኔንም ጅቡ ይብላኝ፤ ካለ ምስክር የቀረሁ ከንቱ ነኝ» እያለ፣ አቅሙ እስከቻለ ተጓዘ
መንገደኛው በመጨረሻ ሲደክመው፣ «አይ ሞኝነቴ አሁን እንግዲህ መልፋቴ ማን እንዲገለኝ ፈልጌ ይሆን? አውሬው በላኝ፣ ረሃብ ገደለኝ ሰው ገደለኝ ላልተርፍ ምን አስፈራኝ? እንዲያው እኮ ይገርማል ያለሁበትንና የምሄድበትን አላውቅ እና መሞቴን
እረስቼ ለመኖር ምን አቃዥኝ፣ ያሻው ይገላግለኝ» ብሎ፣ መተኛቱን
ያስታውሳል" ሲነቃ ግን፣ ጥቋቁር ጠብደሎች ከበውታል። መሣሪያ
አንግተዋል" ጦር፣ ጩቤ፣ መጥረቢያ የያዙም ይታዩታል“ አማትቦ
መልሶ ዓይኑን ከደነ። ሰዎቹ ግን ጠቆም ጠቆም እያደረጉ እንዲነሣ አደረጉት። ሁሉንም በየተራ አያቸው፤ እንኳን የሚያውቀው ሊኖር
የሚሉትም አልገባውም በሐሳቡ፣ «እንግዲህ መሞቴ ላይቀር በምን
እንግደልህ በመሣሪያ ነው፣ በጦር እያሉ እስኪጠይቁኝ ነው የምጠብቀው? ስታገላቸው እሞታለሁ» ብሎ ግብግብ ገጠመ" ትንሽ ታግሎ ቢያስቸግራቸውም፣ ከመሬት ደባልቀው ጕሮሮው ላይ መሣሪያ ደገኑበት። መንገደኛው፣ «ለካ የመጨረሻው ዕድሌ በጥይት መሞት ኖሯል!» ብሉ ዓይኖቹን ጨፈነ"
ሐመሮች መሣሪያና ጥይት ከምንም ነገር በላይ ይወዳሉ። ተኳሾችም ናቸው" በማንም ላይ ግን ቃታ በድንገት አይስቡም" የሚገድሉትን ሰው ማንነት ለይተው ማረጋገጥ አለባቸው።
የሚገድሉት «ቢታው» እንዲገድሉ የፈቀደላቸውን ነው። ቢታ ማለት ጥንት የነበረ ሲሆን፣ ሲወለድ በግራ ብብቱ ንብ፣ በቀኝ ብብቱ እበት ይዞ የተወለደና ከቦርጆ (አምላከ) ጋር ማኅበረሰቡን የሚያገናኝ
ቅዱስ ሰው ነው፣ ብለው ስለሚያምኑ ቢታው ካወጣላቸው ደንብ
ዝንፍ ሳይሉ ለዓመታት የኖሩ ናቸው።
እንግዳው የሙርሲ፣ የማሌ…ማኅበረሰብ አባል ቢሆን ኖሮ ቢታው እንዲገድሉ የፈቀደላቸው ስለሆነ ይገሉት ነበር። እንግዳው ግን የተለየ ነው። ስለዚህ ሳይገሉት ቀሩ። እንዲያውም የደከመ
ሰውነቱን የከብት ደምና ወተት በማጠጣትና ፍየልና በግ በማረድ ያን እየሰበቁ መረቁን እንዲጠጣና ሥጋውንም እንዲበላ በማድረጋቸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያገግም አደረጉት" ከዚህ በኋላ ግን፣ ሐመሮች ከመንግሥት ወታደሮች ጋር ባደረጉት ጦርነት ለእነሱ አብሮ ተዋጋ። መዋጋትም ብቻ ሳይሆን፣ በሱ ስልት ከእልቂት አዳናቸው። ለዚህም ለፈጸመው ትብብር ከብት ዘሎ፣ ልጃገረዶች ተገርፈውለት ሚስት አገባ።
የዚህ እንግዳ ሰው ስም አንተነህ ይመር ይባል እንጂ ከብት ሲዘል መጀመሪያ እግሩ የረገጠበት ትንሽ ጥጃ ቀለሟን በማየት ጋልታምቤ ተባለ።
ጋልታምቤ ከሐመር ማኅበረሰብ አባል ከሆነችው ሚስቱ አንዲት
ሴት ልጅ ወልዶ፣ ቋንቋውን፣ አለባበሱን፣ አመጋገቡን ተለማምዶ ደስ ብሎት የሚኖር ሰው ሆነ።
ጋልታምቤ ሃያ ዓመት ሙሉ ሐመር ውስጥ ሲኖር የተቸገረበት፣ የተለየበት አንዳችም ሁኔታ የለም ከቋቋው ልዩነት በስተቀር
ይህ ነው የሚባል የጎሳ ልዩነት እሱ ከሚያውቀው የተለየ የለም"
በሐመር ማኅበረሰብ ችግርን በሽማግሎች ምክክርና በማኅበረሰቡ
ነፃ ውይይት መፍታት እንጂ፣ ችግርን በተናጠልና በኃይል መፍታት በኗሪዎች በሙሉ የተወገዘ ነው።
ተመካከሮ፣ ተከባብሮ፣ ተፈቃቅሮ፣ደካማና ጠንካራው ካለሥጋት የሚኖርበት ማኅበረሰብ በመሆኑ እንግዳው ጋልታምቤ እንኳን እሱ ለልጅ ልጆቹም ከዚያ የተሻለ ዓለም አይመርጥላቸውም"
💫ይቀጥላል💫
👍33👎2❤1🥰1