አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ

“ደህና እደሪ ካተሪን፡ በጣም ጥሩ እህትና ለመንትዮቹም እናት ነሽ. ግን በጣም ቀሽምና ጥሩ ያልሆንሽ ሌባ ነሽ" አለኝ።.

እያንዳንዱ የክሪስ የእናታችንን ክፍል መጎብኘት የተደበቀውን ገንዘባችንን መጠን አሳደገው ነገር ግን ግባችን የሆነው አምስት መቶ ዶላር ላይ ለመድረስ ረጅም ጊዜ ይወስዳል አሁን እንደገና በጋ መጣ: አሁን አስራ አምስት አመት ሆኖኛል። መንትዮቹ በቅርቡ ስምንት አመት ይሆናቸዋል። በቅርቡ ነሀሴ ሲመጣ የታሰርንበት ሶስተኛ አመት ይሆናል። ሌላ ክረምት ከመግባቱ በፊት ማምለጥ አለብን፡ ኬሪን ስመለከተው ፍዝዝ ብሎ አደንጓሬዎች ይለቅማል። ምክንያቱም የመልካም ዕድል ጥራጥሬ ስለሆኑ ነበር በአዲሱ አመት መጀመሪያ ትንንሾቹ ቡናማ አይኖች ውስጡን እንዳያዩት ብሎ አይበላቸውም ነበር አሁን ግን እኔና ክሪስ እያንዳንዱ አደንጓሬ የአንድ ቀን ሙሉ ደስታ ይሰጣል ብለን ስለነገርነው ይበላል እኔና ክሪስ እንደዚህ አይነት ተረቶች እየፈጠርን እንዲበሉ እናደርጋለን፡ ወለሉ ላይ ይቀመጥና ጊታሩን አንስቶ
አይኖቹን የካርቱን ፊልም ላይ ይተክላል። ኬሪ በቻለችው መጠን ወደሱ
ተጠግታ ቲቪውን ሳይሆን የሱን ፊት እየተመለከተች ትቀመጣለች።

"ካቲ" አለች በዚያች እንደ ወፍ በመሰለች ድምፅዋ

“ኮሪ ደህና አይደለም፡”

“እንዴት አወቅሽ?”

“በቃ አወቅኩ”

“አመመኝ ብሎ ነግሮሻል?”

“ማለት የለበትም”

“እና ምን ተሰማሽ?”

“እንደ ሁልጊዜው”

“እንደ ሁልጊዜው እንዴት ነው?”

“አላውቅም”

"አዎ! መውጣት አለብን፣ በፍጥነት!

በኋላ ላይ መንትዮቹን አንድ አልጋ ላይ አደረግኳቸው: ሁለቱም እንቅልፍ
ሲወስዳቸው ኬሪን አንስቼ ወደ አልጋችን እወስዳታለሁ ለአሁን ግን ለኮሪ
እህቱ አጠገቡ ሆና መተኛት በጣም የሚመች ነው: “ሮዝ አንሶላ አልወድም።”
አለች ኬሪ ተኮሳትራ “ሁላችንም ነጭ አንሶላ ነው የምንወደው: ነጩ አንሶላ
የታለ?”

እኔና ክሪስ ነጭ ከሁሉም ቀለማት ይልቅ ተስማሚ ነው ብለን የተናገርንበት
ቀን ፀፀተኝ። ካቲ እናታችን በአብዛኛው ጥቁር ቀለም ያላቸውን ቀሚሶች
የምትወደው ለምንድነው? ጠየቀች ኬሪ ሮዙን አንሶላ አንስቼ በነጭ እስክቀይረው እየጠበቀች።

“እናታችን ፀጉሯ ቢጫና የፊቷ ቀለም ነጣ ያለ ነው፡ እና ጥቁር ቀለም ደግሞ
የበለጠ ቆንጆ ያደርጋታል።

“ጥቁር አትፈራም?”

“ጥቁር ቀለም በትልልቅ ጥርሶቹ የማይባላ መሆኑን ለማወቅ ስንት አመት
መሆን ነው ያለብሽ?”

“እንደዚህ አይነት የሞኝ ጥያቄዎችን ማወቅ የምችልበት በቂ እድሜ ሲኖረኝ::

“ግን ጣራው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ያሉት ጥቁር ጥላዎች ሁሉ የሚያበራ፣
ሹል ጥርሶች አሏቸው::” አለ ኮሪ ሮዙ አንሶላ እንዳይነካው እየሸሸ።

“አሁን ተመልከቱ” አልኩ የሆነ ዘዴ እየፈጠርኩ እንደሆነ ጠርጥሮ ክሪስ
በሚስቁ አይኖቹ እያየኝ ነው: “እናንተ ቆዳችሁ አረንጓዴ፣ አይናችሁ
ወይንጠጅ፣ ፀጉራችሁ ቀይ እንዲሁም በሁለት ጆሮዎች ፋንታ ሶስት ጆሮዎች
ከሌሏችሁ በስተቀር ጥቋቁሮቹ ጥላዎች የሚያበራ ሹል ጥርስ አያወጡም::እንደዛ ከሆነ ብቻ ነው ጥቁር የሚያስፈራው:”

ዘና አሉ‥ ከዚያ ነጭ አንሶላቸውንና ነጭ ብርድ ልብሳቸው ውስጥ ገቡና
ወዲያው እንቅልፍ ወሰዳቸው ከዚያ ገላዬንና ፀጉሬን ለመታጠብና ልብሴን ለመቀየር ጊዜ አገኘሁ: ጣራው ስር ወዳለው ክፍል ሮጥኩና መስኮቶቹን ከፋፈትኳቸው፡ ቀዝቃዛ አየር ገብቶ ክፍሉን እንዲያቀዘቅዘውና ጠውልጌ
ከምቀመጥ የመደነስ ፍላጎት እንዲሰማኝ ፈልጌያለሁ ንፋሱ ወደ ክፍሉ መግቢያ የሚያገኘው በክረምት ብቻ የሆነው ለምንድነው? ለምን አሁን በጣም በምንፈልገው ጊዜ አይመጣም?

እኔና ክሪስ ሀሳቦቻችንን፣ ተስፋዎቻችንን፣ ጥርጣሬዎቻችንንና ፍርሀቶቻችንን
አንንነጋገራለን ችግር ሲያጋጥመኝ ዶክተሬ ነው: እንደመታደል ሆኖ
የሚያጋጥሙኝ ችግሮች ከባድ አይደሉም ወር ሲመጣ የሚያጋጥመኝ
ቁርጠትና የወር አበባዬ በፕሮግራሙ መሰረት አለመምጣቱ ብቻ ነበር።
ለዚህም ዶክተሬ የሚጠበቅ እንደሆነ ይነግረኛል። እኔ በረባው ባልረባው ጥንቃቄ የማደርግ አይነት ስለሆንኩ ውስጣዊው ማሽኔም ይህንኑ ይከተላል።

ስለዚህ አሁን በመስከረም አንድ ምሽት እኔ ጣራው ስር ያለው ክፍል ውስጥ
ሆኜ ክሪስ ሊሰርቅ ሄዶ የሆነውን ነገር ልክ ክሪስ የነበረበት ቦታ እንደሆንኩ
አድርጌ መፃፍ እችላለሁ: ስለዚህ የተለየ ወደ እናታችን ክፍል የተደረገ ጉዞ
በዝርዝር ነግሮኝ ነበር።
እንደነገረኝ መሳቢው ውስጥ ያለው መፅሀፍ ሁልጊዜ ይስበው ነበር ማረከው፣በኋላ ግን አስጥሞታል። ልክ እንደኔ ለምሽቱ የፈለገውን በቂ ገንዘብ ካገኘ በኋላ ልክ በማግኔት እንደተሳበ አይነት ወደዛ ጠረጴዛ ሄደ።

እሱ እያወራልኝ እኔ ግን በአንድ እይታ እያንዳንዱ ፎቶግራፍ ለዘለአለም
ጭንቅላቴ ውስጥ ተቀርፆ እያለ ለምን እሱ ደጋግሞ ይመለከተዋል? እያልኩ
ከራሴ ጋር እያወራሁ ነበር:

“እዚያ ቆሜ በየጊዜው የተወሰኑ ገፆች ላይ የተፃፈውን እያነበብኩ ነበር” አለኝ እና ስለ ትክክልና ስህተት ስለሚባሉ ነገሮች እያሰብኩና ስለ ተፈጥሮ፣ ደስ ስለሚያሰኘው እንግዳ ጥሪዎቹ እየተገረምኩና ስለእኛ ህይወት ሁኔታዎች
እያሰላሰልኩ ነበር ስላንቺና ስለኔ እያሰብኩ ነበር፡ እነዚህ ለእኛ የማበቢያችን
አመታት መሆን ይገባቸው ነበር። በማደጌና በእኔ እድሜ ላይ ያሉ ወንዶች
ፈቃደኛ ከሆኑ ሴቶች ሊያገኟቸው የሚችሉ ነገሮችን ስለማሰብ ጥፋተኝነትና እፍረት ይሰማኛል። እና እዚያው ቆሜ ባላገኝሽ እያልኩ ስመኝ አዳራሹ ውስጥ ወደ ክፍሉ እየቀረበ የሚመጣ ድምፅ ሰማሁ። ማን እንደሆነ ታውቂያለሽ እናታችንና ባሏ እየተመለሱ ነበር። በፍጥነት መጽሀፉን ቦታው ላይ መለስኩና ቀጥሎ ትልቁ አልጋው አጠገብ ያለው የእናታችን ልብስ ማስቀመጫ ሳጥን ውስጥ ተደበቅኩ: ከገባች አታየኝም ብዬ አሰብኩ። ግን ልታየኝ እንደምትችልም ተጠራጥሬያለሁ። ነገር ግን ይህንን እያሰላሰልኩ
ድንገት በሩን ሳልዘጋ መርሳቴን አስታወስኩ።

የዚያን ጊዜ ነው የእናታችንን ድምፅ የሰማሁት። “የእውነት ባርት? አለች
ወደ ክፍሉ ገብታ መብራት እያበራች። “ብዙ ጊዜ የኪስ ቦርሳህን መርሳትህ
ግዴለሽነትህን ያሳያል”

“ተመሳሳይ ቦታ ስለማላስቀምጠው ነው የምረሳው:” ሲል መለሰላት።እቃዎችን ሲያንቀሳቅስ መሳቢያዎችን ሲከፍትና ሲዘጋ ይሰማኛል። ከዚያ “እዚህኛው ሱሪ ኪስ ውስጥ እንደተውኩት እርግጠኛ ነኝ ... ካለ መንጃ ፈቃዴ የትም መሄድ አልችልም::” አለ

“በአነዳድህ ላይ ቅሬታ የለኝም፧ ግን በዚህ ምክንያት እንደገና ልንዘገይ ነው ምንም ያህል በፍጥነት ብትነዳ የመጀመሪያው ክፍል ያመልጠናል” አለች
እናታችን

“ሄይ!” አለ ባሏ ድምፁ ውስጥ መደነቅ ይሰማኛል። ምን እንዳደረግኩ አስታውሼ በውስጥ አቃሰትኩ ቦርሳዬ ይኸው ኮመዲኖው ላይ: እዛ ላይ ማስቀመጤን አላስታውስም ሱሪው ውስጥ እንደነበረ መማል እችላለሁ” አለ

“መሳቢያው ውስጥ ደብቆት ነበር” ክሪስ አብራራልኝ፡ “ሸሚዞቹ ስር ተቀምጦ ጰነው ያገኘሁት: የተወሰኑ ገንዘቦች ወስጄ ከዚያ አስቀምጬው ያንን መፅሀፍ እሱ እያወራልኝ እኔ ግን በአንድ እይታ እያንዳንዱ ፎቶግራፍ ለዘለአለም ጭንቅላቴ ውስጥ ተቀርፆ እያለ ለምን እሱ ደጋግሞ ይመለከተዋል? እያልኩ
👍511
#ጠላፊዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#በኬንፎሌት


#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


ወሮበሎቹ የሚፈልጉትን ማግኘታቸው አያስደስተውም የሉተር ዕቅድ ቢጨናገፍ ደስታው ነበር፡፡ ነገር ግን ሉተር ጎርዲኖን ካላስለቀቀ ኤዲ ካሮል አንን ማግኘት አይችልም፡፡

ካሮል አንን በእጄ ካስገባሁ በኋላ ጎርዲኖ መያዙ አይቀርም  ሲል አሰበ፡ ይህ ግን የሚሆን አልመሰለውም፡፡ ጎርዲኖ በዚህ ጊዜ ውስጥ ርቆ
ሊሄድ ይችላል፡ ሌላው አማራጭ ሉተር ካሮል አንን በመጀመሪያ በእጁ
እንዲያስገባለት መደራደር ቢሆንም ሉተርን ለማስገደድ ምንም ማስፈራሪያ የለውም፡ ሉተር በአንፃሩ ካሮል አንን ይዟል፡

ወዲያው አንድ ሃሳብ ብልጭ አለበት፡፡ ጎርዲኖ በእኔ እጅ እኮ ነው ያለው፤ እሱን እንደማስፈራሪያ መጠቀም እችላለሁ› አለ፡፡ እነሱ ካሮል አንን ይዘዋል፧ እሷን ለማግኘት ከእነሱ ጋር መተባበር አለብኝ፤ ነገር ግን ጎርዲኖ በዚህ አይሮፕላን ላይ ነው ያለው፡፡ እሱን ማግኘት ከፈለጉ ከእኔ ጋር
መተባበር ይኖርባቸዋል
ሁሉም ነገር በእነሱ እጅ አይደለም ሲል በአዕምሮው አውጠነጠነ።

ስለዚህ የድርድሩን መዘውር በእጁ ማስገባት የሚችልበት መንገድ
ይኖር እንደሆን ማሰብ ጀመረ፡፡

አንድ መንገድ ይኖራል።

ለምንድን ነው እነሱ በመጀመሪያ ጎርዲኖን የሚወስዱት? ልውውጡ
መሳ ለመሳ ነው መከናወን ያለበት፡፡›

ከዚያም ንዴቱን ውጦ በጥልቅ ማሰብ ጀመረ፡

‹እንዴት ነው ልውውጡ ሊከናወን የሚችለው?

ጎርዲኖን ሊወስዱ በሚመጡበት ጀልባ ካሮል አንን ይዘው መምጣት
አለባቸው።
ለምን አይሆንም?  ሲል ከራሱ ጋር ተሟገተ፡፡ እሷን ያገቷት ከቤታቸው ብዙም ባልራቀ ቦታ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ይህም  ቦታ አይሮፕላኑ ከሚያርፍበት ቦታ ብዙም እንደማይርቅ ገምቷል፡፡ ምናልባትም ከአይሮፕላኑ ማረፊያ ቦታ እሷ እስከታሰረችበት ቦታ ድረስ የአንድ ሰዓት የመኪና ጉዞ ሊሆን ይችላል፡ ይሄ ደግሞ ሩቅ አይደለም፡፡

ኤዲ ባሰበው እቅድ ሉተር የሚስማማ ከሆነ ጓደኞቹን በስልክ ሊያናግር
የሚችለው አይሮፕላኑ ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት ቦትውድ (ካናዳ) ላይ ሲደርስ ይሆናል፡፡ ከቦትውድ ቀጥሎ አይሮፕላኑ የሚያርፈው ከሰባት ሰዓት ጉዞ በኋላ ማለትም ከቀኑ አስር ሰዓት ላይ ሼዲያክ ላይ ነው: ወሮበሎቹ ደግሞ
በሁለት ሰዓት ጊዜ ውስጥ እዚያ ቦታ ላይ ካሮል አንን ይዘው መምጣት
አለባቸው::

ኤዲ ካሮል አንን አስቀድሞ በእጁ ሊያስገባ እንደሚችል ሲያስበው ደስታውን መቆጣጠር አቃተው፡ የሉተርንም ጎርዲኖን የማስለቀቅ ጥረት
ሊያመክን እንደሚችል ትንሽ እድል እንዳለ ሲያስበው ደግሞ ተጨማሪ
ደስታ ፈጠረለት፡፡ ይሄ ደግሞ በስራ ባልደረቦቹ በኩል ጀግና ያስብለዋል፡
እነዚህን ነፍሰ ገዳይ ወሮበሎች መያዝ ከቻለ ጓደኞቹ ቀደም ብሎ ለፈጸመው ክህደት ምህረት ያደርጉለታል፡፡
መለስ ብሎ ሲያስበው ደግሞ ብዙ ተስፋ ማድረግ እንደሌለበት ገባው፡፡
ይሄ ሁሉ ገና ሀሳብ ነው፡፡ ሉተርም ባሰበው እቅድ አልስማማም ሊል ይችላል ኤዲ ያቀረበውን እቅድ ወሮበሎቹ የማይቀበሉ ከሆነ አይሮፕላኑን
የተባለው ቦታ እንደማያሳርፍ ያስጠነቅቃል፡ ነገር ግን ወሮበሎቹ የኤዲን
ማስፈራሪያ ከባዶ ዛቻ እንደማይዘል መገመት አያቅታቸውም፡፡ ኤዲ ሚስቱን ለማዳን ሲል የተባለውን ሁሉ እንደሚፈፅም ያውቃሉ፡፡ እነሱ የሚፈልጉትን
ሰው በእጃቸው ከማስገባት ውጭ ምንም ፍላጎት የላቸውም፡፡ እኔ ከነሱ
በላይ የተቸገርኩ ስለሆንኩ አቅመ ቢስ ነኝ ሲል አሰበ፡፡ ይህም ወደ ቀድሞው መከፋት ወሰደው፡፡

ሆኖም ኤዲ ያሰበውን ለሉተር ለመንገር ሰውዬውን ለመፈተን አሰበ፡፡
ቢያንስ ሰውዬውን ጥርጥርና ጭንቀት ውስጥ መክተት ይችላል፡፡ ምናልባት ሉተር የኤዲን ማስፈራራት አምኖ ላይቀበል ይችላል፡ ግን እንዴት እርግጠኛ ሊሆን ይችላል፡፡ ‹ኤዲ ውሸቱን ነው› ለማለት ወኔ ይጠይቃል፡፡ ሉተር ደግሞ ፈሪ እንደሆነ ታይቷል፤ በተለይ አሁን፡፡

ኤዲ ያሰበውን ለመሞከር ቆረጠ፡፡ ከሉተር በኩል ሊመጣ የሚችለውን
ተቃውሞ ለመመከት የሚያስችል ምላሽ አስቀድሞ መቀመር አለበት፡፡

ሉተር እንቅልፍ ካጡት ተሳፋሪዎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ በእንግዳ መቀበያው አንድ ጥግ ቁጭ ብሎ ብቻውን ዊስኪውን ይጨልጣል፡፡አይሮፕላኑ የፈጠረበት የሆድ መታወክ አሁን ስለቀነሰለት ፊቱ ፈካ ብሏል መጽሔት እያነበበ ነው፡፡ ኤዲ አጠገቡ ሄደና ጀርባውን ነካ አደረገው፡፡ ሉተር ኤዲን ሲያይ ደንገርገር አለው፤ ፍርሃት ብጤም ስለተሰማው ጠብ ጠብ ሸተተው፧ ኤዲም ‹‹ሚስተር ሉተር ካፒቴኑ ሊያናግርህ ይፈልጋል›› አለው፡፡

ሉተር ስጋት ገባው፡፡ ከተቀመጠበት አልነሳ ሲል ኤዲ ተነስቶ የጭንቅላት ምልክት አሳየው፡፡ከዚያም ሉተር መጽሔቱን አስቀመጠና የመቀመጫ ቀበቶውን አላቆ ተነሳ፡፡

ኤዲ ሉተርን ወደ ማብረሪያው ክፍል ሳይሆን ወደ መጸዳጃ ቤት ወሰደው፡፡፤

መጸዳጃ ቤቱ በትውከት ሽታ ታውኳል፡፡ እንደ እድል ሆኖ አንድ ሰው እጁን እየታጠበ ስላገኘ ኤዲ መጸዳጃ ክፍሉ ውስጥ እንዲቆይ ለሉተር የእጅ ምልክት ሰጠውና እሱ ማበጠሪያ አውጥቶ እያበጠረ ጠበቀው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ እጁን የሚታጠበው ተሳፋሪ ከመጸዳጃ ክፍሉ ወጥቶ ሄደ፡፡ ኤዲም የሰውየውን መውጣት ተከትሎ ሉተር ያለበትን መጸዳጃ በር ቆረቀረ ሉተርም ‹‹ምን ፈለግህ?›› ሲል አምባረቀ፡፡
‹‹አፍህን ዝጋና አዳምጥ›› አለው፡፡ ኤዲ ከሉተር ጋር ጠብ ለመፍጠር አላሰበም፡፡ ሉተር ግን ጠብ ጠብ ብሎታል፡፡ ‹‹እዚህ አይሮፕላን ላይ ምን
እንደምትፈልጉ ደርሼበታለሁ ዕቅዳችሁን አውቄዋለሁ አሁን  የእቅድ
ለውጥ አድርጌያለሁ፤ እኔ አይሮፕላኑን የማወርድበት ቦታ ላይ ካሮል አንን
በጀልባ ይዛችሁ መምጣት አለባችሁ›› አለው፡፡ሉተር አፉን በንቀት ሸረመመና ‹‹አንተ ጥያቄ ማቅረብ እኮ አትችልም የተባልከውን ማድረግ እንጂ›› አለው፡፡

ሉተር እንዲህ አይነት መልስ ይሰጣል ብሎ ኤዲ አልገመተም፡
‹‹እንግዲያውስ ስምምነታችን እዚህ ላይ አብቅቷል›› አለው ኤዲ፡
ሉተር መጨነቁን ፊቱ እያሳበቀበት ነው፡፡ ‹‹አንተ እኮ ምርጫ የለህም፧
ስለዚህ አፍንጫህን ተይዘህ አይሮፕላኑን የተባልክበት ቦታ ላይ ማውረድ
ያቺን ከአፍ የወደቀች ጥሬ የምታክል ሚስትህን ማስመለስ ትፈልጋለህ፧
ስለዙህ አፍንጫህን ተይዘክ
አውሮፕላኑን የተባልክበት ቦታ ላይ ማውረድ አለብህ››

‹‹እውነት ነው፡፡ ነገር ግን…›› ኤዲ ራሱን እየነቀነቀ ‹‹አላምናችሁም›› አለው ሉተርን «እንዴት አምናቹሀለው እኔ እናንተን አምኜ ሁሉን ነገር አድርጌ ብትከዱኝ እድሌን ማበላሸት የለብኝም።አዲስ ድርድር
እንድናደርግ እፈልጋለሁ፡፡››

የሉተር የመንፈስ ብርታት አሁንም ፍንክች አላለም፡:
አዲስ ስምምነት የለም›› አለ ፈርጠም ብሎ፡፡

አሁን ኤዲ ሉተርን የሚያንበረክክበትን ነገር መዘዘ ‹‹እሺ እንግዲያው
ወህኒ ትወርዳለህ›› አለው፡፡

ሉተር የንዴት ሳቅ ሳቀና ‹‹ምንድን ነው የምታወራው?›› ሲል ጠየቀ
ኤዲ አሁን ጥንካሬ ገባው፡፡ በአንጻሩ ሉተር ደግሞ ደካማ ሆኗል፡ለካፒቴኑ ሁሉን ነገር እነግረውና በሚቀጥለው የአይሮፕላን ማረፊያ ከተማ ላይ ለፖሊስ እንሰጥሃለን፡፡ ፖሊስ እዚያ ቦታ ላይ እንዲጠብቅህ በመገናኛ ሬዲዮ እንነግራለን፡፡ ካናዳ ውስጥ እስር ቤት ትወረወራለህ ጓደኞችህ ሊያድኑህ አይችሉም፡፡ ሰው በማገት፣ በባህር ላይ ውንብድናና በመሳሰሉት ወንጀሎች ትከሰሳለህ፡፡ እስር ቤት ውስጥ ትበሰብሳለህ›› አለው።

በመጨረሻ ሉተር መርበድበድ ጀመረ ‹‹ሁሉም ነገር በዕቅዱ መሰረት
እየተፈጸመ ነው›› ሲል የኤዲን ሀሳብ ተቃወመ ‹‹አሁን እቅዱን መለወጥ
አይቻልም፤ ጊዜ የለም፡፡››
👍17
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት 


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ካርለት ከዳንሱ ቦታ ራቅ ብላ ጀግናዋን በአይኖቿ
ስትፈልገው በጆሮዋ ስልምልም የሚያደርግ የሙዚቃ ቃና ሰማች።
እንግዳ ነው ያ ሙዚቃ ለጆሮዋ! ሳባት ሙዚቃው
ተጎተተችለት: ቃናው ጆሮዋን እየላሳት ወደ ውስጧ ዘለቀ የህሊናዋን ጓዳ! የስርቆሽ በሯን ከፍታ አስገባችው። አሻት፤ ዳሰሳት…..እሷም
አንኳኳ የሆሊናዋን ጓዳ የስርቆሽ በሯን ከፍታ አስገባችው አሻት፤ ዳሰሳት
ሁለመናዋን ነካካው
አንሸራተታት ደመቅ
ደመቅመቅ... የሚለው ዜማ ፍል ውኃ ውስጥ እንደገባች ሁሉ ቁልቁል እየፈሰሰ ሰውነቷን አጋላት ደስ አላት ሰውነቷ ሲግል‥. ጡቶችዋ ግን ተቆጥተው ቆሙ፤ ዳሌዋ አኩሩፎ አበጠ ፤ ጭኗ አዝኖ ለሰለሰ… ሙዚቃና ልብ ወለድ ጽሑፍ ካለ እሳት ሰውነቷን ሲያጋግሉት ደስ ይላታል... የረሳችው ስሜት
ፈረሰኛው አረፋ እንደሚያስደፍቀው ወራጅ ወንዝ ሞተሯን አሽከረከረው፤ አቃሰተች ያኔም ስርቅርቁ ዜማ በጆሮዋ መግባቱን
አላቆመም:

እየቀረበች ስትሄድ በርኮታው ላይ ቁጭ ብሎ ወይሳውን እየነፋ ጥዑም ዜማ የሚያወጣውን ጀግና አየችው። የሙዚቃው
ቅላፄ እንደ “ቤቶሆቨን ሞዛርት ሲንፎኒ" ቃናው እየቆዬ ጣማት።እሰይ እሱ ነው ብላ አጉተመተመች..

ከዚያ ዱካዋን አጥፍታ በሙዚቃው ስልት እርምጃዋን አስተካክላ ተጠጋችው፡
ባለወይሳው አይኖቹ ከጨረቃና ከዋክብቱ ጋር ይጫወታሉ ቅላፄው
ወዲያና ወዲህ ይመላለሳል። ሙዚቃው እንኳን ሌላውን ራሱንም
መስጦታል። እውነተኛ የኪነ ጥበብ ሥራ ውጤት ስቃይና ደስታዋ፤ሐዘንና ትካዜዋ. እፍታውን ቀማሹ ጣዕሙን አስተካካዩና ፈጣሪው
ያኔው ነውና ወይሳው ደልቲን መስጦታል! ወጥሮታል...

ካርለት ደልቲን በሚጫወተው የሙዚቃ ቃና ተመስጦ በማየቷ ይበልጥ ወደደችው፡ ደልቲ
ለስሜቱ ታማኝ ነው አይቀጥፍም አያስመስልም...
ስርቅርቁ የሙዚቃ ቃና
የሚንቆረቆረው ለህሊናው እርካታ ነው::

ካርለትን የሙዚቃው ስልት አቅም አሳነሳት: ሁለመናዋ
እንቅስቃሴ ፍጥነቱን ስለጨመረ ደካከመች: ስሜቷን አፋጭቶ
ሃይሏን መልሶ ለመሳል አጋዥ ያስፈልጋታል
ባለወይሳው ያን ሰው አጥታው ከርማለች! አሁን ግን አጠገቧ ነው።

እጆችዋ ትከሻው ላይ አረፉ። ባለወይሳው ስርቅርቅ ዜማውን አቁሞ ቀና ብሎ አያት። ቆዳዋ ተገልቧል፣ ከርቀት ጠቆር
ብለ የታየው አካሏ ቁልቁል ወደሱ ሲመጣ እየጎላ ታየው። የራቀው
ሽለቆ ቀረበው።

ንጥት ያለው ገላዋ  በተለይም ጭኗን ትክ ብሎ እያዬ፡ “ካርለትት አላትና አይኖቹ ሳቁ። ሃይል ያጣችው ካርለት
የተሸበሸበ ርጥብ ከንፈሯን ለጠጥ አርጋ ደካማ ፈግታዋን አሳየችው።

ባለወይሳው አስተውሎ አያት ውስጧንም አየው
የተቀጣጠለውን ስሜቷን ነካው፡

ጭኖቹ ላይ ያለውን ወይሳ አንስቶ ለጨረቃ ሰጣት!
ጨረቃም ወይሳውን ተቀብላ እየነፋች ጥዑም ዜማዋን ማንቆርቆር ጀመረች። በጨረቃ የሙዚቃ ቃና ደልቲ ቀኝ እጁ እየተንከላወሰ ወደ
ነጩ ጭኗ ገባ። ነዘራት
በሽተኛዋን! “በሽታውን የደበቀ..." እንዲሉ እሷም ሃኪሟን ረዳችው የሚያቃጥላትን የሚቆረጥማትን እጁን
በእጅዋ ይዛ አሳየችው።
ጆሮ ግንዱን ፀጉሩን
ማጅራቱን...እየደባበሰች የእርዳኝ ጥሪዋን አሰማችው። ሀኪሟ በስሜቷ እሱም ተሽፈነ። ለጋራ በሽታቸው ግን የሚበጀውን ያውቃል። ስለዚህ ማገገሚያ ቀንዱን አቁሞ ይዞ ከተቀመጠበት ተነሳ።

ሙዚቃው ይስረቀረቃል! ዳንሱ ጦፏል... ጨረቃ
ታዜማለች ! ቅጠሉ እስክስታ ይወርዳል! ነፋሱ አታሞውን
ይደልቃል... ጥቁርና ነጭ ቀለሙ ማራኪ ዜብራም ያናፋል...

ኮንችት ጭፈራውን በጉጉት እያየች እንደቆየች ስለ ነገው
ጉዟቸው ካርለትን ለመጠየቅ ፈልጋ አጣቻት የኩችሩ መንደር ኗሪ
ጥበቃውን አላቆመም። ነጩ እባብና ሎካዬ ግን አልመጡም። ኮንችት
በየዋህነታቸው ብታዝንም ማድረግ የምትችለው ባለመኖሩ በዝምታ
ሁኔታውን ስትከታተል ሰነበተች። የመቆያ ፈቃዷ  እያለቀ ነው:: ስፔን ስትመለስ ብዙ ልትሰራ አስባለች በተለይ ስለ ኢትዮጵያ  ስለ ኩጉዩ፡ ከመሄዷ በፊት ግን ሐመርን ኤርቦሬን ከካርለት ጋር በሷ
መኪና ለማየት ተስማምታለች ጉዞዋን በተመለከተ ግን ከካርለት
ጋር መነጋገር ያለባት ቁም ነገር ነበር።

ኮንቺት ካርለትን ስታጣት ደልቲን በጨረቀዋ ብርሃን  ፈለገችው የለም:

ካርለት የሄደችው እሱ ዘንድ ይሆን?' አብረው ሆነው
ለማየት ጓጓች: ፍቅር ሲለዋወጡ እንዴት ይሆን?' ለማስብ ሞከረች:: መልሳ ደግሞ ሃጢያት እንደሰራች ሁሉ አስበችው አፈረች። ሆኖም ግን አልቻለችም ጉጉቷ ጨመረ።

በዚህ መካከል ድክምክም ያለውን የወይሳውን ድምፅ
ኮንችት ከርቀት ሰማችው። በድፍረት ሄደች  ወደ ጫካው! ድንገት ግን ክው ኦለች ! ባለበት የሚሰግር
ዜብራ አየች ፈራችው
ዜብራውን ይጋልባል ... በስሜት ተውጣ አይኖችዋን ጨፈነች:
"...የፍቅር እንጥሌን ሌሎች ተንጠራርተው ሲያጡት የነካው እሱ ብቻ ነው" ኮንችትን የነገረቻት ትዝ አላት።

“ዋው! ጎመጀች በዜብራው
ግልቢያውን አሰጋገሩን
አደነቀችው። ወደደችው ያን ስሜት ሰላቢ ጥዑም ዜማ... ፈውስ ሰጭ ዳንኪራ… ንፁህ የጫካ ፍቅር... ማራኪ ተፈጥሮ ተጋግዘው እንግዳዋን መልሀቋን አስጥለው በጉጉት ገተሯት!  ተጣራች በሲቃ ሶራ ግን አልሰማትም! ኤጭ! ብላ ከንፈሯን ጣለች። ጎደሎነት
ተሰማት ያማራትን የዜብራ ግልቢያ ግን የሚያቀምሳት አጣች.የጎመጀችለትን ያጣችው ኮንችት አዘነች። ...ዛፉ ቅጠሉም አዘነላት ላልተጠራችው ተመልካች!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

“እ. እ..." አቃሰቱ እምቡዋ እ. እ" ሳግ ተናነቃቸው
ህፃናት ወጣቶች አዛውንቶች ኦሞ ወንዝ ዳር ጫካ ተሰባስበው እንግዶች በእንጨቷ ታንኳ ኦሞን ሲያቋርጡ አያቸው።

ኮንችት እጅዋን አውለበለበችላቸው “ቻው... ባባይ... አለቻቸው። ዝም አሉ ኩዩጉዎች የነሱ የጥልቅ ፍቅር መግለጫቸው ዝምታ ነው። ሳግ ያበት “እ... እ..." እሚያሰኝ ከጥጃዋ በሃይል እንደተነጠለች ላም የሚያንሰፈስፍ ዝምታ! “እ. እ. እምቡዋ.. እያሰኘ የማይፈስ እንባ የሚያስነባ, የማይገልፁት ግን የሚታይ
የሚነካ... የመለየት ጭንቀት የሚታይበት ስሜት..

“እወዳችኋለሁ! ከናንተ በመለየቴ አዝናለሁ. ምንጊዜም አልረሳችሁም..." ኮንችት በስፓኒሽ ለመግለፅ ለፈለፈች¦ ምላሽ ግን
አልነበረም። “ፀጥታ ብቻ! ለኩዩጉዎች የመለየትን መጥፎነት የሚገልፅ ቋንቋ የላቸውም ካለ ዝምታ በቀር።

ኮንችት አነባች::
የካርለትን ትከሻ ተደግፋ አነባች አለቀለች  ሌሎች ግን ዝም ረጭ ብለዋል  እንደ ሌሎች ወንዞች
የማይጮኸው የማይደነፋው.
የኩዩጉዎች ህይወት የመልክ ማያ መስታዋታቸው የሆነው የኦሞ ወንዝም በዝምታ ድባብ እንደ ተዋጠ
ነው: ወፎች ግን ይበራሉ ያዜማሉ! እዕዋት ያሽበሽባሉ...

“እሷ ሄደች በሉ
ሉካዬንና የሰላም አድባራችን
የነበረውን ነጩን እባብ እንጠብቅ ! ተከፍተን ታዩን መምጣቱን እንዳይተዉት እንዝፈን እንጫወት.."
ሽማግሌዎች ለኩችሩ መንደር ህዝባችው ተናገሩ ኮንችት ካርለት ከሎ ሶራ… ኦሞን ከተሻገሩ በኋላ ዞር ብለው አዩ: ኩዩጉዎች የሉም!.ሲደልቁ ግን ይሰማል ለዚህች ተለዋዋጭ ዓለም ለረጅም ጊዜ አልቅሶና አዝኖስ መኖር እንዴት ይቻላል!
👍263👎1🥰1😁1
#ባል_አስይዞ_ቁማር


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


"እግዜር ይስጥህ እንኳን እቤትህ ቁጭ ብለህ ጠብቀህ ልዩ ጥዬሽ ገዳም ልገባ ነው አላልከኝ...ድፍረት ኖሮህ አይን አይኖቼን እያየህ እንደዛ ብትለኝ …የሆነ ቢላዎ ፈልጌ ልብህ ላይ ሽጪ እዚሁ ነበር የማስቀርህ...›ስትል ዛተች..ዛቻዋ ከልቧ ነበር.አድራሻው የማይታወቅ ገዳም ገብቶ ለዘላለም ከምታጣው እዚሁ በገዛ እጇ ገድላው አልቅሳ ከቀበርረችው በኃላ ምርጥ በተባለ እምነ በረድ ሀውልት አሰርታለት በየቀኑ መቃብሩ ጋር እየሄደች ሰታወራው መዋል  ይሻላት ነበር፤

አእምሮውን ሳት እንዳደረገው ትኩስ እብድ በቤቱ ወዲህ ወዲያ በመዟዟር ነበር ቀበጣጥረው

ፓስታውን በእጇ ይዛ እጆቾን ከደቡብ ወደሰሜን እያወናጨፈች አንዴ መኝታ ቤት ደግሞም ሳሎን እየተመላለስች ነው‹‹....አረ እያበድኩ ነው መሰለኝ...››አለችና የሳሎኑን በራፍ በርገዳ ወጣች…

...ሮጣ አሮጌቷ ቤት በረንዳ ላይ እራሷን አገኘችው ።ለማንኳኳት እንኳን ትእግስቱ አልነበራም፡፡ በራፍን በርግዳ ገባች፡፡ አሮጊቷ ተቀምጠውበት ከነበረው ግዙፍ ሶፋ  ቀልጠፍ ብለው ተነስተው ቆሙ..ልክ የሆነ ወንጀል ሰርተው በተደበቁት ድንገት ፓሊስ ቤታቸውን ከፍቶ ፊት ለፊታቸው እንደቆመ ነው ሁኔታቸው..

"ቃልዬ የት ነው?እንዴት እንዲህ ይሰራኛል?እርሶ እንደማፈቅረው አያውቁም?"
ቀስ ብለው ካሉበት ተንቀሳቅሰው ቀረቧት ፤ክንዷን ያዙና ወደራሳቸው በመጎተት እቅፋቸው ውስጥ አስገቧት። የምትፈልገው ይሄንን ነበር..መንሰቅሰቅ ጀመረች..እምባዋ ከጀርባቸው ላይ እያረፈ ወደታች ሲንኳለል ይታያታል…ቢያንስ ለ10 ደቂቃ በቆሙበት ተቃቅፈው እየተላቀሱ ቆዩ ።ከዛ አሮጊቷ ቀድሞ ደከማቸው.. እየጎተቱ ወስደው ሶፋ ላይ አስቀመጧትና  ከጎኗ ተቀመጡ።


‹‹እማማ ልጆት አይደለ እንዴት ዝም ይሉታል?››

"ልጄ ወደእግዚያብሄር ቤት ልሄድ ነው ሲለኝ እንዴት ብዬ አትሂድ አይሆንም እለዎለሁ?"

"እኔስ ፍቅር አሲይዞኝ እንዴት ይሄዳል?  ...እሺ አሁን ምንድነው የማደርገው ?ዛሬ እኮ አይኔን በጨው ታጦቤ ልነግረው ነበር  ..እጮኛዬ እንዲሆነኝ ቀለበት ላስርለት ነበር እኮ... በመዳፏ ጨምድዳ የያዘቻቸውን ሁለት ቀለበቶች ወደ ፊትለፊት ዘርግታ እርስ በርስ በማቅጨልጨል አሳየቻቸው

"ልጄ አልሆነማ ምን ይደረግ...?እሱ የእግዚያብሄር ሙሽራ ብሆን ይሻለኛል አለ?በውሳኔው ጣልቃ መግባት ከእግዜሩም መቀያየም ነው።"አሏት ልስልስ እና ድክም ባለ ድምፀ፡፡

‹‹አልገባዎትም ...በጣም እኳ ነው ያፈቀርኩት...እንሂድ ቢለኝ ምን አለበት..?ያለምንም ማቅማማት አብሬው ሄድ ነበርእኮ"

በእንባ የተዳረሰ ፊታቸውን በከፊል ፈገግ አድሮገው"አይ ልጄ ቢጨንቅሽ እኮ ነው... ገዳም   ፊልም ቤት አይደል አብረን እንግባ የሚልሽ።"

ትከሻዋ ላይ ጣል ያደረጉትን እጃቸውን መንጭቃ ወረወረችና ከተቀመጠችበት ተነሳች..."ይሄ እውነት አይደለም..ቃል አሁን መጥቶ እቤት ይጠብቀኛል ..አዎ እየጠበቀኝ ነው...›በማት ወደውጭ መራመድ ጀመረች....

‹‹አይ ልጄ እግዚያብሄር ይሁንሽ ከማለት ውጭ ምን አረጋለሁ? "አሉ አልመለሰችላቸውም.. ተንደርድራ ቃል ቤት ደረስች …ሙሉ በሙሉ ተበርግዶ እንደተከፈተ ነበር።

‹‹አዎ ቃል ተመልሶ መጥቶል..ቃልዬ አልጋው ላይ ጋደም ብሎ እየጠበቀኝ ነው።አዎ እኔሞ አብሬው ከጎኑ እተኛለሁ...እቅፍ አድርጌው ከንፈሩን ስማለሁ ...እና የፈለገውን ነገር ቢጠይቀኝ በደስታ እሺ እለዋለሁ ...እናም ደግሞ ይሄንን ቀለበት ጣቱ ላይ አጠልቅለትና የዘላለም ባሌ እንዲሆን እጠይቀዋለሁ..እርግጠኛ ነኝ እሱም እሺ ብሎ ሌለኛውን ቀለበት ጣቴ ላይ ያጠልቅልኛል።›› ...ይሄን ሁሉ እየለፈለፈች የሳሎኑ በራፍ ጋር ቆማ የሚብረከረከውን ጉልበቷን ባለመተማመን ጉበኑን ጨምድዳ ይዛ ወደ ውስጥ ባዶውንና ኦናውን ሳሎን አያየች ነው...መቀባጠሯን ሳታቋርጥ ወደ ውሰጥ ገባችሁ ልብን በሚቆራርጥ ፍራቻና አጥንትን በሚከታትፍ ሰቃይ የመኝታ ቤቱን በራፍ ገፋ አደርጋ በመክፈት አይኖቾን ወደውስጥ ላከች  ..ሁሉ ነገር ጥላው እንደወጣችው ነው ...ቃል የለም...ወደ ሳሎን ተመለሰች...ቃል ሰርቶላት የደረደራቸው ምግቦች አጠገብ ተቀመጠች።እጆን ወደምግብ ዘረጋች...ልክ ምግብ ለሳምንት በልቶ እንደማያውቅ ሰው (እርግጥ ቃልን ለማግኘት ስትቆነጃጅ ጊዜ ስላላገኘች ከነጋ ምግብ አልበላችም።)እየተስገበገበች መብላት ጀመረች።ሲበቃት ደረቷ ጠቅላላ በወጥ አጨመላልቃዋለችሁ ...የሀገር ባህል ቀሚስ ላይ ወጥ  ነክትቶ... ይባስ ብላ በወጥ የተጨማለቀ አጇን ጠረገችበት 27 ሺ ብር የወጣበት ልብስ ግማሽ ቀን እንኳን ሳይለበስ ድራሹ ጠፋ...‹‹የት አባቱ ቃልዬም ጠፋቶል እንኳን ልብስ ›አለችና የውስኪ ጠርሙሱንና አንድ ብርጭቆ ይዛ መሬት ያዘች።እዛው ሳሎን የቀኝ ግድግዳውን  ተደግፋ በላይ በላይ እየቀዳች መጋት ቀጠለች...ሩብ ያህሉን እንዳጋመሰች ጊፍቲ ትዝ አለቻት።ተንበርክካ በእንፉቅቅ እየሄደች ስልኳን ካስቀመተችበት አነሳችና ከፈተችው …በርከት ያሉ የተደወሉ ስልኮችና ሚሴጆች አሉ...ምን ያህል እንደደነዘዘቸ ማስረጃው   ይሄ ሁሉ ተደውሎ ስልኩ ሲንጫረር አለመስማቷ ነው...ከሙዚቃው ጋር ደርባ ስትሰማ የቆየችው  ሙዚቃ መስሏት ይሆናል..አሁንም ቢሆን  ማን እንደደወለላት ለማየት  ደንታ አልነበራም።ስልኳን ፈለገችና ደወለችላት… አነሳችው፡፡

"ሄሎ ልዩ "
‹‹አቤት››
‹‹ እቤተ እንድትመጪ እፈልጋለሁ›

‹‹የት ቤት  ነው የምመጣው..?ምን ሆነሻል?››
‹‹ቃል እቤት ነይ..…አሁኑኑ››
‹ልዩ ምን ሆነሻል ቃል ሰላም አይደለም?››
‹‹አለም ተገለባብጧል ..የገሀነም በሮች ተከፍተዋል….ምትመጪ እንደሆነ ነይ››ጆሮዋ ላይ ጠረቀመችባ፡፡ሰከንድ  ሳትቆይ ጊፍቲ መልሳ ደወለችላት.. ስልኳን ሙሉ በሙሉ አጠፋችው፡፡ ውስኪዬን እየተጋተች ሀሳቦን ወደመቃዠቱ ገባች …..

ገዳም ገባ አሉኝ -ደብረሊባኖስ
ነፍስ እየገደሉ- ይማራል ወይ ነፍስ?
ነፍስ እየገደሉ -ከተማረ ነፍስ
እኔም ያው ሞትኩልህ....አንተም ተቀደስ።

የትና መቼ  እንደሰማችው የማታውቀው ዘፈን ግጠም ከነዜማው በአእምሮዋ እያንቃጨለ አስቸገራት፡፡

የሠው ልጅ 70 ትሪሊዬን ከሚሆኑ ህውሶች ተዋቅሮ የተገነባ ፍጡር ነው ።በአሁኑ ጊዜ የአለም ህዝብ ቁጥር 7ቢሊዬን ገደማ ነው። .ይሄ ሁሉ ህዝብ አንድ ላይ ተጨፍልቆ ከአጥናፍ አለም አንፃር ከህዋስ ያለፈ ቦታ የለውም።ግን ደግሞ ታአምር የሚያሰኘው አንድ ነጠላ ሰው አጥናፍ አለምን የሚያስስ ሰፊና ጥልቅ የሆነ  ከመጠኑ ቢሊዬን ጊዜ በላይ የሚገዝፍ  በአዕምሮው ማሽንነት የሚፈጠረ ተስፍፊና ተስፈንጣሪ ምናብ ባለቤት ነው።ሰው...ገራሚ ፍጡር ነው።ለዚህም ነው መሠለኝ ሩሚ "አፅናፍ አለም በሙሉ በውስጥህ ስላለ ብቸኝነት ፈፅሞ አይሰማህ "ያለው።ከዝንት አለም ውስጥ ተመዘን ወጥተን ወደህይወት ለመምጣት በእናትህ ቅድስ ማህፀን ውስጥ ገብተን ተብላልተንና በቅርፅና በመጠን ተስተካክለን መውጣት የግድ ይላል።ይሄ ብቸኛው መንገድ ነው።እንደ ሙሀመድ ነብይ..እንደ እየሱስ የእግዚያብሄር ልጅ ፤እንደ ቡድሀ ታላቅ መንፈሳዊ መገለጥ ላይ የደረስንና  የበራልን ብንሆንም እንኳን ሌላ መንገድ የለም። ሌላው ደግም በዚህ ምድር ቆይታ ላይ ሳለን አነዳንዶቻችን በእግዜያብሄር መንግስት እናምናለን?በዛም አሻግረን ወደ ገነትስ መግባት እንሻለን?ከዚህ በሚቃረን መልኩ ግን ከሞት መዳፍ ለማምለጥ ሰንጥርና ስንለፋ ይታያል?ሞት ማለት እኮ በሚመጣው አለም ወደሚጠብቀህ የዘላለም መኖሪያ ሾልከህ ምትሄድበት ብቸኛው በራፍ
👍8011👏4🤔2🥰1
#ተአምረተ_ኬድሮነ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


‹‹እኮ የምታደርጉትን ነገር አቁሙ ነው እያልንሽ ያለነው  ..በግልጽ እንንገርሽ  መሰለኝ….እርሱ መዳን አይችልም ማለት መዳን የለበትም …..እሱ ከዳነ  እኛ እንጠፋለን ማለት-ነው….ስለዚህ  እረዳሽንም አረዳሽንም እሱን ለመግደል የምናደርገው ጥረት አናቆምም….እኛ በራሳችን ማድረግ  ዳግመኛ  መሞከር ያልፈለግነው  የፖሊሶች አይን እየተከታተለን ስለሆነ ነው፡፡››

‹‹ቆይ እስኪ አሁን የተመረዘበትን መድሀኒት የሰጣችሁት እናንተ ናችሁ….?››

‹‹እሱን ማወቅ ምን ይጠቅምሻል….?›.›

‹‹አይ እሱማ ምን ይጠቅመኛል..እንዲሁ ተገርሜ እንጂ››

‹‹ምንም የሚገርም ነገር የለም..አሁን ባቀረብንልሽ ሀሳብ
ትስማሚያለሽ ወይስ አትስማሚ..

….?››ይጠይቃታል ሰሎሞን ተብዬው….

ወዲያው  አዕምሮዋን አሰርታና የነገሮችን አካሄድ በፍጥነት በመተንበይ ‹‹አረ  እኔ ምን አገባኝ… እናንተ ለራሳችሁ ሰው ያላሰበችሁ እኔ ምን አስጨነቀኝ..እስማማለሁ…››ብላ ትመልሳለች ሰሚራ፡፡

እነሱም ካሰቡት በጣም በፍጥነት  ስለተስማማችላቸው ተደሰቱ..

‹‹አሪፋ…በጣም ጥሩ ውሳኔ ነው››ሰላም፡፡ 

ሰሎሞን  ‹‹እንግዲህ ስንት ቀን እንጠብቅሽ….?››

ሰሚራ ‹‹አንድ ሶስት ቀን እፈልጋለሁ››

‹‹ሶስት ቀን አይበዛም››

ኮስተር ብላ ‹‹ሰው ለመግደል እኮ ነው እየተስማማን ያለነው ..ሰው ለመግደል ሶስት ቀን እንዴት ሆኖ ነው የሚበዛው….?››

ሰሎሞንም በአሪፍ መስመር  እየሄደ ያለው ጠቃሚ ስምምነት ላለመበረዝ  ለስለስ ብሎ‹‹ያው ሞት አፍፍ ላይ ያለ ሰው ለመግዳል ብዙም አይከብድም  ብዬ ነዋ…በተለይ ላንቺ››

‹‹ላንቺ ስትል …….?ስታየኝ ገዳይ እመስላለሁ….?›› መለሰች ሰሚራ ኮስተር ብላ ፡፡

‹‹አይ አረ በፍጽም እንደዛ ማለቴ ሳይሆን የህክምና ዕወቀቱ ስላለሽ..የትኛው መድሀኒት ሰውዬውን በቀላሉ ሊገድለው ይችላል የሚለውን በደንብ ስለምታውቂ ብዬ ነው፡፡››

‹‹እንዳልከው መግደሉ ቀላል ነው..ግን ግድያውን ማንም  ሊደርስበት የማይችል እና  ፖሊስም በምርማራም ሊያረጋግጠው የማይችል መሆን አለበት››

‹‹አየሽ እኔ ቀልቤን በጣም ነው የማምነው…ገና እንዳየውሽ ለዚህ ስራ እንደምትረጂን እርግጠኛ ሆኜ ነበር..እሷ ግን አይሆንም ብላ በጣም ስትከራከረኝ  ነበር የሰነበተችው….እንድረታት አደረግሸኝ …ጀግና ሴት ነሽ..ስራውን በጥንቃቄ እና በፍጥነት ስሪልን እንጂ 100 ሺ ብር ቦነስ አለሽ››ሰሎሞን በፈገግታ ተሞልቶ   አሞገሳት፡፡

‹‹ችግር የለም..ባይሆን እድር ከሌላችሁ እድር ግቡ….››
‹‹ለእሱ አታስቢ›› ብለው  በደስታ ተሰናብተዋት በፈገግታ እደታጀቡ ይሄዳሉ፡፡

ሰሚራ እነሱ እደወጡ ነበር ምን ማድረግ እዳለባት ማሰብ የጀመረችው‹‹…ሰው እዚህ ድረስ መጨካከን የጀመረው መቼ ነው…….?›› ለዛውም በቤተሰብ ደረጃ…እራሷን በድንጋጤ የጠየቀችው የመጀመሪያ ጥያቄ ነበር… ‹‹…ምን ቢያደርጋቸው ነው የራሳቸውን ሰው እንዲህ ለማስገደል የሚጥሩት..….?››ሰው ሰውን  ከሞት ለማትረፍ‹‹…..የሰውን ህይወት ለማስተካከል ይለፋል ገንዘብን ይከሰክሳል እንጂ እንደነዚህ  የራስ ሰውን ለመግደል ምን አነሳሳቸው...….?

ይቀጥላል
👍9912👏2👎1🔥1😁1
#ትንግርት


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ትንግርት ያታሰረችበት ክፍል ሌሎች አራት ሴቶቸ አብረዋት ታስረዋል፡፡አንድ የ18 ዓመት ወጣት ...ሁለቱ ከ25-30 የሚገመት ዕድሜ ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡ከሁለቱ አንደኛዋ ቀጫጫ ቢጤ ስትሆን ስትታይ የቢሮ ሰራተኛ ነገር ትመስላለች.. ሌላኛዋ ግን ደልደል ያለች የተንጨፈረረ ፀጉር ያላት ወንዳወንድ ነገር ነች …አራተኛዋ 4ዐ ዓመት የሚጠጋት ገዘፍ ያለች ሴትዬ ነች፡፡ከእሷና ከልጅ እግሯ ወጣት በስተቀር ሌሎቹ እስር ሲታሰሩ ዛሬ የመጀመሪያቸው እንዳልሆነ ከሁኔታቸው መገንዘብ ይቻላል፡፡

‹‹አቦ አትቆዝሙብን ...እስቲ ወሬ አምጡ ..እናውራ፡፡ ካለዛ የእስር ቤት ተባዬች ደማችንን ሲመጡን በዝምታ ምናዳምጣቸው ከሆነ ስቃዩ ከፍተኛ ነው ሚሆንብን..፡፡ወሬ ግን ማደንዘዣ ነው ..ቀልባችን ወደ ወሬው ከላክን እነሱ ደማችንን ብቻ ነው ሚመጡት፡፡ ካለዛ
ደማችንንም ቀልባቸንንም ምጥጥ ነው የሚያደርጉት፡፡›› ቀጫጫዋ ወጣት ተናገረች

‹‹ተስማምተናል..…እስቲ ከተማሪዋ እንጀምር ..ምን አጥፍተሸ ታሰርሽ?››

‹‹ምንም?›› አለች ፈራ ተባ እያለች፡፡

‹‹ባክሽ አትሽኮርመሚ.. ዝምብለውማ አምጥተው እዚህ አያጉሩሽም... የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነሽ አይደል?››ትልቋ ሴትዬ ጠየቀቻት፡፡

‹‹አዎ... ዋናው ግቢ ነው የምማረው..የሶስተኛ አመት ተማሪ ነኝ፡፡››

‹‹የየት ሀገር ልጅ ነሽ…?››

‹‹የደብረማርቆስ፡፡››

‹‹እሺ ምን ሰርተሸ ታሰርሽ?››

‹‹ፖሊሶቹ ጭፈራ ቤት ለሊት ይዘውኝ፡፡››

‹‹አቦ አትፎግሪ.…ፋራ አረግሺን እንዴ ?››አለቻት ወንዳወንዷ ወጣት፡፡

‹‹እሱማ ዕቃ ይዘውብኝ ነው ፡፡››

‹‹የምን ዕቃ?››

‹‹ሀሽሽ ሚሉትን ዕፅ….፡፡››

‹‹ሀሽሽ !!አይ የዘንድሮ ተማሪ ስትጦዢ ይዘውሽ ነዋ?››

‹‹ወላዲቷን እኔ ነክቼውም አላውቅ ..፡፡ጓደኞቼ ናቸው ቦርሳሽ ውስጥ አስቀምጪልን ፤ የስጦታ ዕቃ ነው አሉኝ፤እውነት መስሎኝ እሺ አልኳቸው፤ከዛ ስንዝናና ስንጠጣ ቆይተን ከሰከርን በኋላ ወደ ጓሮ ይዘውኝ ሄደው ቦርሳዬን ተቀብለው ከውስጡ ያስቀመጡትን ቆንጥረው ወስደው የተቀረውን እዛው በመመለስ የራሴኑ ቦርሳ ለእኔው ካስያዙኝ በኃላ እነሱ እየተቀባበሉ ሲያጬሱ በስካር መንፈስ ናውዤ ቢሆንም በድርጊታቸው ግራ ገብቶኝ ስገረምባቸው ድንገት ከየት እንደፈለቁ
ያላወቅናቸው ፖሊሶች መጥተው ከበቡን..ከዛም አፈሱንና ሲፈትሹን እነሱ ምንም አልተገኘባቸው እኔ ቦርሳ ውስጥ ግን ተገኘ‹‹ካመጣሽበት ጠቁሚ፡፡ ››ተብዬ ይሄው ታስሬያለሁ፡፡

‹‹እና ጓደኞችሽ ምን አሉ?››ትንግርት ጠየቀቻት፡፡

‹‹እንጃላቸው...ምናቀው ነገር የለም መሰለኝ ያሉት..ለዛም መሰለኝ የለቀቋቸው፡፡››

‹‹ታዲያ ምን ይሻልሻል?››

‹‹እንጃልኝ…እቤተሰቦቼ ከሰሙ በቃ ማጣፊያዬ ነው የሚያጥርብኝ... አባቴ ቀጥታ ይገድለኛል..፡፡››

‹‹ቆይ ያልገባኝ ፖሊሶቹ በዛ ሰዓት እንዴት ሊገኙ ቻሉ?›› ትንግርት ነች ግልፅ ስላልሆነላት የጠየቀችው፡፡

‹‹እሱማ ከመካከላችን ሜሪ የሚሏት የዱከም ልጅ በጣም የሚወዳትን ተማሪ ፍቅረኛዋን ችላ ብላ ትልቅ ሀብታም ሰውዬ ጋር ነበር ስትጨፍር ያመሸችው.. ልጁ መጥቶ አብራው ወደ ካምፓስ እንድትመለስ ሲለምናት ነበር..እሷ ግን አልሰማህም ነፍስያዬን ማስደሰት እፈልጋለሁ አለችው፤እያለቀሰና እየፎከረ ነበር ጥሏት የሄደው.....እሱ ይመስለኛል ለፖሊሶች የጠቆመው፡፡››

‹‹እናንተ ፖሊስ እጅ ስትወድቁ ሰውዬው አብሮችሁ ነበር?››

‹‹ነበር ግን ፖሊሶቹ ምንም አላሉትም አልፈተሸትምም..የሚያውት መሰለኝ… ሳስበው ሳስበው ዕፁን እራሱ ለእነሚሪ ያመጣላቸው እሱ ይመስለኛል፡››

‹‹በይ ነገ ይሄንን ሁሉ ለፖሊሶቹ በዝርዝር ንገሪያቸው..ሀሽሽ አለመጠቀምሽንም በምርመራ ማረጋገጥ የሚችሉ ይመስለኛል፡፡››
‹‹እስቲ እግዜር ቢረዳኝ እሞክራለሁ፡፡››ብላ መነፍረቅ ጀመረች፡ሁሉም አባበሏት..ስትረጋጋ ቀጣዩን ባለታሪክ ለማዳመጥ ተዘጋጁ፡፡ቀጣዪ ባለተራ በዕድሜ ከሁሉም አንጋፋ የሆነችው ሴትዬ ነበረች‹‹እሺ ያንቺስ ታሪክ?›› ቀጫጫዋ መጠየቅ ጀመረች፡፡

‹‹የእኔ እንኳን ከበድ ይላል..ከሁለት እስከ አምስት ዓመት ተፈርዶብኝ ወደ ወህኒ መውረዴ አይቀርም፡፡››

‹‹እንዴ !!!እራስሽ ወንጀለኛ እራስሽ ዳኛ ሆነሽ አረፍሺው ?ለማንኛውም እስኪ እንስማው?››

‹‹የባሌን እንትን የማስወገድ ሙከራ አድርጌ ነው፡፡››

‹‹እንትን ምንድነው?››ነገሩ ግራ ገብቷት ጣልቃ በመግባት ሳታስበው ጥያቄ የሰነዘረችው ትንግርት ነበረች፡፡

<< የሚመጠጠው ጀላቲ››አሾፈችባት ወንዳወንዷ፡፡

‹‹አልገባኝም?››

‹‹ባክሽ ሽሮ መብያውን ማለቷ ነው?››ቀጫጫዋ እስረኛ አስረዳቻት፡፡

‹‹በስመአብ ...!!!የባልሽን?››ተማሪዋ ጠየቀች... ሰቅጥጧት፡፡

ትንግርትም...የሴትዬዋ ጭካኔ አንዘርዝሯት‹‹ምነው አንደኛውኑ ብትገይው?››አለቻት፡፡
‹‹ጠላትን ለመበቀል ግድያ የመጨረሻው ቀሺሙ ዘዴ ነው?››መለሰች፡፡

‹‹እንዴት?››ግራ ገብቷት፡፡

‹‹ገደልኩት ማለት እኮ ገላገልኩት ማለት ነው ፤ከሞት በኃላ ፀፀት የለ.... መከራ የለ….ምን ይቀርበታል፡፡ ስለፅድቅና ኩነኔው እንደሆነ ማን እርግጠኛ መሆን ይችላል፡፡እንደውም እኔ ነኝ መከራውን የምቀበለው..እሱን የሰላም ዕንቅልፉ ወደሚያገኝበት ስፍራ ሸኝቼ እራሴን

ለዕድሜ ልክ የእስር ስቃይ አሳልፌ ሰጣለሁ..?ምን በወጣኝ፡፡እኔም እሰቃያለሁ እሱም በቁሙ እየኖረ ይሰቃይ...>>
‹‹ሰማንሽ ...እስቲ ያረግሺውን በዝርዝር አስረጂን?››

‹‹ባሌ ቀለም ቀቢ ነበረ፡፡ ከዛሬ ሁለት አመት
በፊት አንድ ፎቅ ሲቀባ ከሁለተኛ ፎቅ ላይ
መሰላል አንሸራቶት ይፈጠፈጥና የቀኝ እግሩ
ስብርብሩ ይወጣል ይታያችሁ.. እኔ እና ታናሽ
እህቴ በኪራይ ቤት እሱ በሚያመጣው ገቢ
ነበር የምንተዳደረው፡፡እሱ ስብርብሩ ወጥቶ
ቤት ሲቀር የሆነ ነገር ማድረግ የሚጠበቀው
ከእኔ ነው፡፡እራሳችንን መቀለብ ብቻ ሳይሆን
እሱንም አሳክሞ ማዳን የእኔ ኃላፊነት ስለነበር መጣር ጀመርኩ፤ብዙ ነገር ለመስራት ሞከርኩ… ሰው ቤት ፅዳት..ቀን ስራ
ያልሞከርኩት ነገር የለም ፡፡ግን ሁሉም ከልፋት
በስተቀር ለቤተሰቡ የሚበቃ ጠብ የሚል ገንዘብ ሊያስገኝልኝ አልቻለም፡፡ቀለባችንን ችዬ የቤት ኪራይ ከፍዬ ከዛ ተርፎኝ እሱን
ለማሳከም አቅም አነሰኝ…እግሩ ከህክምና እጦት የተነሳ የተነፋፋ ቆሰለ ..ትል ሁሉ ማፍራት ጀመረ፤ምን ላድርግ ?ተሳቀቅኩ፡፡ ሲቸግረኝ ሌላ ዘዴ ቀየስኩ፡፡››

‹‹ምን ዓይነት ዘዴ?››

‹‹የለሊት ስራ ... ፋብሪካ ውስጥ አገኘሁ ብዬ አስወራሁ?››

‹‹ሳታገኚ?››

‹‹ስራውንማ አግኝቼያሁ ...ግን ፋብሪካ ውስጥ አልነበረም፤ ሽርሙጥና ነበር ለመስራት የወሰንኩት፡፡››

ቀጫጫዋ በገረሜታ‹‹ባል እያለሽ?››አለቻት ፡፡

‹‹ባሌማ እኮ ….ዓይኔ እያየ የተሰባበረ እግሩ ከህክምና እጦት የተነሳ መትላት ጀመረ፤ምንበላው አጣን፣የቤት ኪራይ መክፈል አቃተን፣እህቴም ትምህርቷን ልታቋርጥ ጫፍ ደረሰች..እና ምን እንዳደርግ ትጠብቂያለሽ…?

አንዳንዴ ይህቺ አስቀያሚ ህይወት ሁሉንም በራፎች ትከረችምብሽና አዋራጅ እና አስቀያሚ የሆነውን ጭላንጭል የዕድል ቀዳዳ ብቻ ትተውልሻለች፡፡››
‹‹እሺ ቀጥይ ባክሽ፡፡››አለቻት ትንግርት ታሪኳ አጓጉቷት፡፡
👍619👏1😢1
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ባለፋ ሶስት ወር ውስጥ ተሰምቷት የማያውቅ ደስ የሚልና የሚያፅናና ስሜት ተሰማት…..እናም ለመጀመሪያ ጊዜ ሰውነቷን ለመታጠብ ወደ ሻወር ቤት ገባች፡፡ግዙፉ መስታወት ፊት ቆማ የለበስችውን ቢጃማ በቁሟ አወለቀችና እዛው ከእግሯ በታች ወለሉ  ላይ  ረገጠችው…መላ  እሷነቷን  በፅሞና  ተመለከተች…. ፀጉሯ በዛ ርዝመቱና ብዛቱ ጭብርር ብሎ ከመንግስት ተሰውሮ ዋሻ ውስጥ ለአመታት ተደብቆ የኖረ ሽፍታ አስመስሏታል፡፡ ….አማላይ  የነበረው  የሠውነቷ ቅርፅ አሁንም እንዳለ ቢሆንም የሰውነቷ ክብደት ግን በተጋነነ ሁኔታ መቀነሱ ወደፊት ወጥተው በጉልህ የሚታዩት አጥንቶቾና  ወደ  ውስጥ  ጎድጉደው  ጭል ጭል የሚሉ አይኖቾ ምስክር ናቸው፡፡ከሁሉም በላይ ያስደነገጣት  ግን  የብልት ፀጉሯ ነው…ከስራዋ ባህሪ አንጻር ለአመታት በሶስት ቀን አንዴ ስትላጭ የኖረች ሴትዬ  ለወራት  ችላ  የተባለው  የብልቷ  ፀጉር  በአስፈሪ  ሁኔታ   አድጎና ተንጨፍርሮ እርስ በርሱ ተቆጣጥሮ በመሀከል ስንጥቅ መኖሩን እራሱ በእጅ ዳብሰው ካልበረበሩት ማወቅ የማይቻልበት ደረጃ ላይ በመድረሱ አስደነገጣት….
….የቀኝ አጇን  ዘረጋችና  አንገቷን  ጠምዝዛ  ብብቷን  ተመለከተች  ..ተመሳሳይ ነው፡፡ በፀጉር ከመሸፈኑም በተጨማሪ ሽታ ከሩቁ ይገፋተራል፡፡ይሄ ሁኔታ ደግሞ ይበልጥ አስገረማት፡፡
‹‹ለምንድነው ግን በቁማችንም እያለን ጭምር ለጥቂት ቀናት ትኩረታችንን ከራሳችን ላይ ስናነሳ እንዲህ በፍጥነት የምንሸተው..?››ስትል ጠየቀች፡፡መልሱን ለመመለስ ግን ብዙም አላስቸገራትም፡፡  ምክንያቱም ከማሳጅ ስራዋ ጋ ተያይዞ ከወሰደቻቸው ኮርሶች አንደኛው የሰው ልጅ አመጋገብ ስርዓት በተመለከተ ነበር ፡፡ ከሺ አመታት በፊት የሞቱ ሰዎች መቃብር ተቆፍሮ ሲገኝና የጥርሳቸው ጤንነትና ጥንካሬ ሲፈተሸ አሁን ካለው የሰው ልጅ ጋር የማይነፃጸር እጅግ ንጹህና ጠንካራ  እንደሆነ ተረጋግጧል፡፡ምክንያቱም ደግሞ አመጋገባችን ሆኖ ነው የተገኘው፡፡አሁን አብዛኛው ምግቦች ከኬሚካል ጋ ንክኪ ያላቸው… ስኳርነት የበዛባቸውንና  ጤንነትን ሳይሆን ጥፍጥና መሰረት ያደረጉ ናቸው…ስለዚህ እነዚህ ገብተው ተፈጥአዊ ሰውነታችንን በክለዋል….በዛ ላይ ምንቀባቸው ቅባቶች የምንረጫቸው ሽቶዎች፤ የምንታጠብበት ሳሙና በጠቅላላ እንዲህ በቀናት ውስጥ በቁማቸንን እንድንሸት ዋና ምክንያቶች መሆናቸው ለመረዳት ብዙ ምርምርም አያስፈልግም፡፡ ወደመኝታ ቤቷ ተመለሰችና የቁም ሳጥኗን ኪስ ከፈተችና  የፀጉር  መላጫ ማሽኗንና መቀስ አውጥታ በመያዝ ወደ ሻወር ቤት ተመለሰች፡፡ምንም ማሰብ እና መጨነቅ አላስፈለጋትም፡፡ከፀጉሯ ጀመረች…..ከርዝመቱ ወጥራ ወደፊት እየያዘች…..ወገብ ላይ ትጎምደው ጀመር፡፡ ወለሉ በተንጨባረረ እና በተቆጣጠረ
ፀጉር ተሞላ፡፡ ባለከመከም ጎፈሬ ሆነች፡፡በመስታወቱ የተለየች አይነች እስከዛሬ እሷ ራሷ ማታውቃት አይነት ሳባን ተመለከተች፡፡መቀሷን አስቀመጠችና ማሽኗን አመቻቸችና ወደብልቶ ጎንስ ብላ እግሯን ፈርከክ በማድረግ ታጭደው ጀመረ…..ሁሉን ነገር ጨርሳ ሰውነቷን  ታጥባና  ፀድታ ከሻወር ለመውጣት ከ2 ሰዓት በላይ ነው የፈጀባት፡፡
ከዛ ወደመኝታዋ ተመልሳ የተወሰነ እረፍት አደረገች.. ከተኛበት  ብንን  አለችና ስልኳን አነሳች፡፡ እንዲህ አይነት ጥንካሬ እና ፍላጎት በደቂቃ ውስጥ ከየት እንዳመጣች አታወቅም፡፡ደወለች..ከሶስት ጥሪ በኃላ ተነሳ፡፡
‹‹ሄሎ ዶክተር››

‹‹ሳባ ለመሆኑ በህይወት አለሽ…?ምን ነካሽ…?ሌላ ሌላው ይቅር እሺ ህክምናሽን ግን እንዴት ታቋርጪያለሽ…ያልተመቸሽ ነገር ካለም እኮ ተነጋግረን ማስተካከል እንችል ነበር..››
‹‹ምን አልተመቻትም ብለህ አሰብክ…ያደረኩት ነገር አግባብ ነበር እንዴ?›ስትል መልሳ ጠየቀችው፡፡
‹‹እሱን ከህክምናሽ ጋር ምን አገናኘው..ምን አልባት በእኔ ህክምናውን መከታተል የሚከብድሽ ከሆነ እኮ በሀገሪቱ ያለሁት የስነ-ልቦና ሀኪም እኔ  ብቻ አይደለሁም
… ተነጋግረን ሁኔታዎችን መስመር ማስያዝ እንችል ነበር››

‹‹ኖኖ ዶክተር እንደዛ አስቤ አይደለም…እኔ እንደውም አንተ ካላከምከኝ ማንም ሊያክመኝ አይችልም››አለችው፡፡
የተናገረችው ትክክል ይሁን አይን እራሷም እርግጠኛ አይደለችም…እርግጥ ከእሱ ውጭ በሌላ ሀኪም መታከም አትፈልም….ደግሞም በእሱም ቢሆን መታከሙን የምትችል መስሎ አልተሰማትም፡፡ህመሟ አካላዊ ቢሆን ችግር የለውም፡፡ ጉበቷ ወይም ኩላሊቷ ቢሆን ወይም ማህፀኗን አሟት ልብሶቾን አወላልቃ እግሮቾን አንፈርክካ መላ ሚስጥሯን ለእሱ  ማሳየት  ቢሆን  ምንም  አይመስላት ነበር፡፡…..እሱ ፊት ስትቀርብ ከኤፍሬም  ጋር  በገዛ  ምርመራ  ክፍሉ  የሰራችው ነውር ነው ትዝ የሚለው የገዛ ወንድሙን ስታማግጥበት…ዝግንን አላት፡፡
‹‹እና ታዲያ ለምን እራስሽን  ሰወርሽ….?እንዴት  እዲህ  ይጠፋል…..?ደግሞ ለህክምና ፋይል ላይ ያስመዘገብሽ መረጃ በጠቅላላ የተሳሳተ ነው….አድራሻሽን ጭምር  ..አንድ ትክክል የሆነው ስልክ ቁጥርሽ ቢሆንም እሱንም ጠርቅመሽው ይሄው ስንት ወር፡፡››

ደስ አላት…ስለእሷ እንዲህ ሲጨነቅና ሲብሰለሰል መክረሙ ደብዝዞ እና ሊከስም ጫፍ ላይ ደርሶ የነበረ ተስፋዋ በጥቂቱም ቢሆን ቢል ቢል እያለ  እንዲነቃቃ ተጨማሪ ነዳጅ ሆኖ ሲያነቃቃት ተሰማት፡፡
‹‹እና አሁን እንዴት ነሽ…?የት ነሽ..?ሀገር ውስጥ ነሽ?››

‹‹አዎ እዚሁ ነኝ፡፡››

‹‹እና እንዴት ነሽ?፡፡››

‹‹እኔ እንጃ ..ምን ላይ እንደሆንኩ አላውቅም…እንዴት እንደሆንኩ አላውቅም….. መኖሬን እራሱ አላውቅም….ለምን አሁን አንተ ጋ እንደደወልኩም አላውቅም….
››አለችው፡፡

ከንግግሯ አሁን ያለችበት ሁኔታ ከወራት በፊት ለመጨረሻ ጊዜ ካገኛት እጅጉኑ የከፋ እንደሆነ ወዲያው ተረዳ….ስለእሷ ሲያስብና   ሲጨነቅ   የከረመው   ግን ከዚህም የከፋ ነገር ላይ እራሷን ትጥላለች ብሎም ጭምር ስለሰጋ ነበር…እራሱን ያጠፋ ሰው ዜና በሶሻል ሚዲያም ሆነ በሜን እስትሪም ሚዲያ ሲሰማ ደንግጦ በንቃት ዜናውን እስከመጨረሻው ለማየት ሲጥር የነበረው እሷን አስቦ ነው፡፡አሁን  ግን በከፋ ሁኔታ ላይም ሆና ቢሆን በህይወት መኖሯ ብቻ አስደሰተው፡፡
‹‹አይዞሽ ይሄ በማንኛውም ሰው ላይ በሆነ ጊዜ ላይ የሚከሰት ነው..አንቺ ደግሞ ከዕድሜሽ በላይ ብዙ ነገር ያየሽና ብዙ ነገር ምታውቂ ጠንካራ ልጅ ነሽ...እኔም ደግሞ በፈለግሽኝ ጊዜና መንገድ ከጎንሽ ነኝ፡፡››
‹‹አንተ ከጎኔ መሆንህን በመስማቴ ተደስቼያለሁ…አመሰግናለሁ፡፡››

‹‹እና መች ብቅ ትያለሽ?›

‹‹እኔ እንጃ››አለችው የምትለው ግራ ገብቷት…

‹‹እኔ  እንጃ  ማለት  ምን  ማለት  ነው…ህክምናው  ቢቀር  አንኳን  ናፍቀሺኝል… ሆስፒታል መምጣት ካስጠላሽ የፈለግሺው ቦታ መገናኘት እንችላለን፡፡››
‹‹ካልክ ነገ ስንት ሰዓት ይመችሀል?››

‹‹እንቺ የሚመችሽን ሰዓት ነገሪኝ እኔ ፕሮግራሜን አሬንጅ ማድረግ እችላለሁ›› እሷን ከማግኘት የሚቀድምበት ምንም ጉዳይ የለውም፡፡
‹‹በቃ 10 ሰዓት እንገናኝ..››

ደስ አለው….‹‹እሺ የት እንገናኝ?›› ነገረችው
‹‹ችግር  የለም….እንገናኛለን…››

‹‹እሺ ዶ/ር ….አመሰግናለሁ››
👍697👏4🥰2