ድንግል ማርያም አምላክ ልጇን አዝላ ስደት ወጥታ
ምድረ ግብፅ ትደርሳለች:: በወቅቱ ከደረሱባት ችግሮች
አንዱ ደግሞ ረሃብና ጽሙ ነበር:: እንኩዋን ለስደተኛ በቤቱ
ላለም ረሃብና ጥም እንዴት እንደሚከብድ የደረሰበት
ያውቀዋል::
ታዲያ አንድ ቀን የበርሃው ፀሐይ አቃጥሏቸው ባረፉበት
ድንግል እመቤታችን ውሃ ልመና ወጣች:: ብዙ ለመነች :
ግን ጥርኝ እንኩዋ የሚሠጣት አጥታ በሐዘን ተመለሰች::
ስትመለስ ግን ይባስ ብሎ የልጇን ጫማ ሽፍቶች
ወስደውት ደረሰች::
ያን ጊዜ ልጇን ታቅፋ "ውሃ ሳላገኝልሕ : ጫማሕንም
አሰረቅኩብህ" ብላ ምርር ብላ አልቅሳለች::
ይሕንን የተመለከተ ልጇ የቆመችበትን መሬት ቢባርከው
ሕይወትነት ያለው ማይ (ጸበል) ፈለቀ:: # ጌታችን :
#እመቤታችን : #ዮሴፍና_ሰሎሜ ከውሃው ጠጥተጠዋል::
ሲሔዱ ግን ለእንግዶች ጣፋጭ (መድኃኒት) :
ለአካባቢው ሰዎች ግን መራራ ሁኗል::
ከመቶዎች ዓመታት በሁዋላም ጌታ ጸበል ያፈለቀበት :
ድንግል እመቤታችን የቆመችበት ቦታ ላይ በእመ ብርሃን
ስም #ቤተ_ክርስቲያን ታንጿል:: ቅዳሴ ቤቱም ተከብሯል::
ጸበሉም ሲባርክና ሲፈውስ ይኖራል::
ምድረ ግብፅ ትደርሳለች:: በወቅቱ ከደረሱባት ችግሮች
አንዱ ደግሞ ረሃብና ጽሙ ነበር:: እንኩዋን ለስደተኛ በቤቱ
ላለም ረሃብና ጥም እንዴት እንደሚከብድ የደረሰበት
ያውቀዋል::
ታዲያ አንድ ቀን የበርሃው ፀሐይ አቃጥሏቸው ባረፉበት
ድንግል እመቤታችን ውሃ ልመና ወጣች:: ብዙ ለመነች :
ግን ጥርኝ እንኩዋ የሚሠጣት አጥታ በሐዘን ተመለሰች::
ስትመለስ ግን ይባስ ብሎ የልጇን ጫማ ሽፍቶች
ወስደውት ደረሰች::
ያን ጊዜ ልጇን ታቅፋ "ውሃ ሳላገኝልሕ : ጫማሕንም
አሰረቅኩብህ" ብላ ምርር ብላ አልቅሳለች::
ይሕንን የተመለከተ ልጇ የቆመችበትን መሬት ቢባርከው
ሕይወትነት ያለው ማይ (ጸበል) ፈለቀ:: # ጌታችን :
#እመቤታችን : #ዮሴፍና_ሰሎሜ ከውሃው ጠጥተጠዋል::
ሲሔዱ ግን ለእንግዶች ጣፋጭ (መድኃኒት) :
ለአካባቢው ሰዎች ግን መራራ ሁኗል::
ከመቶዎች ዓመታት በሁዋላም ጌታ ጸበል ያፈለቀበት :
ድንግል እመቤታችን የቆመችበት ቦታ ላይ በእመ ብርሃን
ስም #ቤተ_ክርስቲያን ታንጿል:: ቅዳሴ ቤቱም ተከብሯል::
ጸበሉም ሲባርክና ሲፈውስ ይኖራል::
❖✝ እንኩዋን ለሰማዕታት ቅዱስ #እንጣዎስ እና ቅዱስ
#ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✝❖
#ቅዱስ_እንጣዎስ_አሞራዊ ይሕ ቅዱስ በቀደመ ሕይወቱ ክርስቲያኖችን የሚጠላ
አስቸጋሪ አረማዊ ነበር:: ሃገሩ #ሶርያ ( #ደማስቆ ) ሲሆን
ግብሩ ጣዖት ማምለክና መስረቅ ነበር:: በቅድስት ቤተ
ክርስቲያንና በምዕመናን ላይም ግፍን ፈጽሟል:: በሥጋዊ
ጉልበቱ ኃይለኛ ስለ ነበር የተፈራ ነው::
ሁልጊዜ በጠዋት ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ይሔዳል::
የሚሔደው ግን ንዋያተ ቅድሳትን ለመዝረፍ: አንድም
ካህናትን ለመደብደብ ነበር:: የሚገርመው ግን የወቅቱ
ምዕመናንና ካህናት ይህን ሁሉ እያደረገባቸው አይጠሉትም::
ይልቁኑ ይጸልዩለት ነበር እንጂ:: ምክንያቱም ክርስትና ማለት
ጠላትን መውደድ ነውና:: (ማቴ. 7)
የእግዚአብሔር ትዕግስትና የምዕመናን ጸሎት ተደምሮው
አንድ ቀን ፍሬ አፈራ:: እንጣዎስ እንደ ለመደው ለክፉ ሥራ
ወደ # ቅዱስ_ቴዎድሮስ ቤተ ክርስቲያን ይሔዳል:: ከዚያም
እንደ ደረሰ ወደ ውስጥ ገብቶ: የሚማታውን ተማቶ:
የሚዘርፈውንም ዘርፎ: የተረፉትን ንዋያተ ቅድሳት በእሳት
አቃጠላቸው::
#እግዚአብሔር ከዚህም በላይ ታጋሽ ነውና አላጠፋውም::
"ዘኢይፈቅድ ለኃጥእ ሞቶ" እንዲል የኃጢአተኛውን መመለስ
እንጂ መሞቱን አይፈልግም:: ለዚያም ነው ዛሬ ይሔ ሁሉ
ግፍ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየተሠራ እግዚአብሔር
እንደማያይ ዝም የሚለው:: ለሁሉም ቀን አለውና በፈረደ ቀን
ግን በፊቱ የሚቆም አይኖርም::
እንጣዎስ ግን የሠራውን ሠርቶ እወጣለሁ ሲል
አልተሳካለትም:: ከበሩ አካባቢ ሲደርስ: ከወደ ሰማይ
አካባቢ ድምጽ ሰምቶ ቀና ሲል መላእክት እንደሱ ዓይነት
ኃጢአተኞችን አሰልፈው በጦርና በቀስት ሲወጉአቸው
ተመለከተ::
ድንገት ግን ከመላእክቱ አንዱ ዘወር ብሎ አንድ ቀስት ወደ
እንጣዎስ ወረወረ (ተኮሰ):: ቀስቷ አካሉ ውስጥ ገብታለችና
እንጣዎስ መሬት ላይ ወድቆ ለሞት ደረሰ:: ላበቱ በግንባሩ
ላይ በጭንቅ እየፈሰሰ ጮኸ::
"ጌታየ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ማረኝ? ራራልኝ? ይቅር
በለኝ? በድፍረት ባለ ማወቅም በድየሃለሁ:: ይቅር በለኝና
ላምልክህ: ስምህንም ልሸከም" ሲል በጭንቀት ውስጥ ሆኖ
አሰምቶ ጸለየ:: በዚያ የነበሩ ምዕመናን ማን: በምን እንደ
ወጋው ባያውቁም ባዩት ነገር ግን እጅግ ደስ አላቸው::
እነርሱም የፈጉትና የጸለዩለት ነገር ይሔው ነበርና::
ወዲያው ግን እንጣዎስ ከሞት ጫፍ ተመልሶ ተነሳ::
መጀመሪያ በቦታው የነበሩ ካህናትና ምዕመናንን "ይቅር
በሉኝ?" አለ:: ቀጥሎም ወደ ዻዻስ ዘንድ ሔዶ "አጥምቀኝ"
ሲል ጠየቀ:: እርሱ በሚጠመቅበት ቀን ብዙ አሕዛብና
ክርስቲያኖች ተሰብስበው ነበር::
እርሱ በከተማዋ ዝነኛ ነበር:: ሥርዓቱ ሁሉ ተደርሶ ቅዱሱ
ወደ ውሃ ገንዳው ሲገባ ሁሉ እያዩ የብርሃን ምሰሶ ከሰማይ
ወረደ:: ይህንን በገሃድ የተመለከቱ ከ10,000 በላይ አሕዛብ
ወዲያውኑ በክርስቶስ አምነው አብረውት ተጠምቀዋል::
ቅዱስ እንጣዎስ ከዚህ በሁዋላ ምስጉን ክርስቲያን ሆነ::
ስለ ቀደመ ሕይወቱ ፈንታ ጾምን: ጸሎትን: ፍቅርን: ምጽዋትን
ገንዘብ አደረገ:: ሕይወቱም ለብዙ ሰዎች መስታውት ሆነ::
#እመቤታችን ድንግል ማርያምንም ይወዳት ነበርና ወደ
ቅዱሳን ማሕበር ( #ኢየሩሳሌም ) ወስዳው በሥጋዊ አንደበት
ተከናውኖ ሊነገር የማይቻል ምሥጢርን ገልጣለታለች::
እነዚህን የቅድስና ጊዜያት በስኬት ያሳለፈው ቅዱስ
እንጣዎስ መጨረሻው ሰማዕትነት ሆነ:: አረማውያን ወገኖቹና ቀድሞ የሚያውቁት ወደ ቀደመ ክፋትና
ክህደት እንዲመለስ ጠየቁት:: "አይሆንም" አላቸው::
በአደባባይ ለፍርድ አቅርበው ደሙ እስኪፈስ ገረፉት::
ጥርሶቹን በሙሉ በድንጋይ አረገፏቸው:: ደሙና ጥርሶቹ
መሬት ላይ ተዘሩ:: ነገር ግን ይሕ ስቃይ ቅዱሱን ከፍቅረ
ክርስቶስ ሊለየው አልቻለም:: አሕዛብም ተስፋ ቆርጠው
በዚህች ቀን ገድለውታል:: ቅዱስ እንጣዎስም ከሁዋለኛው
ዘመን #ሰማዕታት እንደ አንዱ ተቆጥሯል::
#ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✝❖
#ቅዱስ_እንጣዎስ_አሞራዊ ይሕ ቅዱስ በቀደመ ሕይወቱ ክርስቲያኖችን የሚጠላ
አስቸጋሪ አረማዊ ነበር:: ሃገሩ #ሶርያ ( #ደማስቆ ) ሲሆን
ግብሩ ጣዖት ማምለክና መስረቅ ነበር:: በቅድስት ቤተ
ክርስቲያንና በምዕመናን ላይም ግፍን ፈጽሟል:: በሥጋዊ
ጉልበቱ ኃይለኛ ስለ ነበር የተፈራ ነው::
ሁልጊዜ በጠዋት ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ይሔዳል::
የሚሔደው ግን ንዋያተ ቅድሳትን ለመዝረፍ: አንድም
ካህናትን ለመደብደብ ነበር:: የሚገርመው ግን የወቅቱ
ምዕመናንና ካህናት ይህን ሁሉ እያደረገባቸው አይጠሉትም::
ይልቁኑ ይጸልዩለት ነበር እንጂ:: ምክንያቱም ክርስትና ማለት
ጠላትን መውደድ ነውና:: (ማቴ. 7)
የእግዚአብሔር ትዕግስትና የምዕመናን ጸሎት ተደምሮው
አንድ ቀን ፍሬ አፈራ:: እንጣዎስ እንደ ለመደው ለክፉ ሥራ
ወደ # ቅዱስ_ቴዎድሮስ ቤተ ክርስቲያን ይሔዳል:: ከዚያም
እንደ ደረሰ ወደ ውስጥ ገብቶ: የሚማታውን ተማቶ:
የሚዘርፈውንም ዘርፎ: የተረፉትን ንዋያተ ቅድሳት በእሳት
አቃጠላቸው::
#እግዚአብሔር ከዚህም በላይ ታጋሽ ነውና አላጠፋውም::
"ዘኢይፈቅድ ለኃጥእ ሞቶ" እንዲል የኃጢአተኛውን መመለስ
እንጂ መሞቱን አይፈልግም:: ለዚያም ነው ዛሬ ይሔ ሁሉ
ግፍ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየተሠራ እግዚአብሔር
እንደማያይ ዝም የሚለው:: ለሁሉም ቀን አለውና በፈረደ ቀን
ግን በፊቱ የሚቆም አይኖርም::
እንጣዎስ ግን የሠራውን ሠርቶ እወጣለሁ ሲል
አልተሳካለትም:: ከበሩ አካባቢ ሲደርስ: ከወደ ሰማይ
አካባቢ ድምጽ ሰምቶ ቀና ሲል መላእክት እንደሱ ዓይነት
ኃጢአተኞችን አሰልፈው በጦርና በቀስት ሲወጉአቸው
ተመለከተ::
ድንገት ግን ከመላእክቱ አንዱ ዘወር ብሎ አንድ ቀስት ወደ
እንጣዎስ ወረወረ (ተኮሰ):: ቀስቷ አካሉ ውስጥ ገብታለችና
እንጣዎስ መሬት ላይ ወድቆ ለሞት ደረሰ:: ላበቱ በግንባሩ
ላይ በጭንቅ እየፈሰሰ ጮኸ::
"ጌታየ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ማረኝ? ራራልኝ? ይቅር
በለኝ? በድፍረት ባለ ማወቅም በድየሃለሁ:: ይቅር በለኝና
ላምልክህ: ስምህንም ልሸከም" ሲል በጭንቀት ውስጥ ሆኖ
አሰምቶ ጸለየ:: በዚያ የነበሩ ምዕመናን ማን: በምን እንደ
ወጋው ባያውቁም ባዩት ነገር ግን እጅግ ደስ አላቸው::
እነርሱም የፈጉትና የጸለዩለት ነገር ይሔው ነበርና::
ወዲያው ግን እንጣዎስ ከሞት ጫፍ ተመልሶ ተነሳ::
መጀመሪያ በቦታው የነበሩ ካህናትና ምዕመናንን "ይቅር
በሉኝ?" አለ:: ቀጥሎም ወደ ዻዻስ ዘንድ ሔዶ "አጥምቀኝ"
ሲል ጠየቀ:: እርሱ በሚጠመቅበት ቀን ብዙ አሕዛብና
ክርስቲያኖች ተሰብስበው ነበር::
እርሱ በከተማዋ ዝነኛ ነበር:: ሥርዓቱ ሁሉ ተደርሶ ቅዱሱ
ወደ ውሃ ገንዳው ሲገባ ሁሉ እያዩ የብርሃን ምሰሶ ከሰማይ
ወረደ:: ይህንን በገሃድ የተመለከቱ ከ10,000 በላይ አሕዛብ
ወዲያውኑ በክርስቶስ አምነው አብረውት ተጠምቀዋል::
ቅዱስ እንጣዎስ ከዚህ በሁዋላ ምስጉን ክርስቲያን ሆነ::
ስለ ቀደመ ሕይወቱ ፈንታ ጾምን: ጸሎትን: ፍቅርን: ምጽዋትን
ገንዘብ አደረገ:: ሕይወቱም ለብዙ ሰዎች መስታውት ሆነ::
#እመቤታችን ድንግል ማርያምንም ይወዳት ነበርና ወደ
ቅዱሳን ማሕበር ( #ኢየሩሳሌም ) ወስዳው በሥጋዊ አንደበት
ተከናውኖ ሊነገር የማይቻል ምሥጢርን ገልጣለታለች::
እነዚህን የቅድስና ጊዜያት በስኬት ያሳለፈው ቅዱስ
እንጣዎስ መጨረሻው ሰማዕትነት ሆነ:: አረማውያን ወገኖቹና ቀድሞ የሚያውቁት ወደ ቀደመ ክፋትና
ክህደት እንዲመለስ ጠየቁት:: "አይሆንም" አላቸው::
በአደባባይ ለፍርድ አቅርበው ደሙ እስኪፈስ ገረፉት::
ጥርሶቹን በሙሉ በድንጋይ አረገፏቸው:: ደሙና ጥርሶቹ
መሬት ላይ ተዘሩ:: ነገር ግን ይሕ ስቃይ ቅዱሱን ከፍቅረ
ክርስቶስ ሊለየው አልቻለም:: አሕዛብም ተስፋ ቆርጠው
በዚህች ቀን ገድለውታል:: ቅዱስ እንጣዎስም ከሁዋለኛው
ዘመን #ሰማዕታት እንደ አንዱ ተቆጥሯል::
♥ እንኩዋን ለታላላቁ ቅዱሳን #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት:
#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ እና #ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ
ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ♥
ቅዱስ #ተክለ_ሃይማኖት ሐዋርያዊ "*+ #ልደት
መልካም ዛፍ
መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ: #
ጸጋ_ዘአብ ካህኑና #እግዚእ_ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ:
እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ
ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: +በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ
ቢደርስባቸው #ቅዱስ_ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ
ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል::
በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል:: +አቡነ ተክለ
ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24, በ1206 (1196) ሲሆን
የተወለዱት ታሕሳስ 24, በ1207 (1197) ዓ/ም ነው::
በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም
በበረከት ሞልቷል:: #ዕድገት =>የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው
"#ፍሥሃ_ጽዮን" ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ
ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን
(ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ
አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ #አባ_
ጌርሎስ ተቀብለዋል:: #መጠራት =>አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን
ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ
ተሰማ:: የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ አእላፍ
መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::
+የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ: "ከዛሬ ጀምሮ
ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: አራዊትን
ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ
በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ
ሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ
ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ:: #አገልግሎት
=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል
አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (#
ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው
አጠመቁ:: ያንጊዜ #ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት:: 1.ዮዲት
(ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ
አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ
አምልኮ ተጠምዷል:: 2.ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት
ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: +ግማሹ ሃገር በጨለመበት
ወቅት የደረሱት #ሐዲስ_ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት
ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ::
ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን
(ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: #ገዳማዊ ሕይወት =>ቅዱስ
ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው
ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ
የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::
+እነዚህም በአቡነ #በጸሎተ_ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት:
በአቡነ #ኢየሱስ_ሞዐ_ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ
ዳሞ ከአቡነ #ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26
ዓመታት አገልግለዋል:: +በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ
በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ #ዞረሬ ተመልሰው በአንዲት በዓት
ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም
6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል:: #
ስድስት ክንፍ =>ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ
ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት
መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ #እሥራኤል የገቡት
በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ
ነበር:: +የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት #አባ_ሚካኤል ጋርም
ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ
በሁዋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ
ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ
እንባቸው ይፈስ ነበር:: +ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው
ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
¤በቤተ መቅደስ ብስራቱን ¤በቤተ ልሔም ልደቱን ¤በቤተ ዮሴፍ
ግዝረቱን ¤በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን ¤በቤተ አልዓዛር
ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር:: +የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል
ወደሆነው #ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ
ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን
ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ
#እመቤታችን_ድንግል_ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን
ወደሰማይ አሳረገቻቸው:: +በዚያም:- ¤የብርሃን ዐይን
ተቀብለው ¤6 ክንፍ አብቅለው ¤የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
¤ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው ¤ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም
ተደምረው ¤ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
¤"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ
ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል:: #ተአምራት
=>የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል *ድውያንን ፈውሰዋል *አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል *በክንፍ በረዋል *ደመናን ዙፋን
አድርገዋል:: +ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን
መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት
አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: #ዕረፍት
=>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን
ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: አእላፍ ፍሬን አፍርተው:
በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24,
በ1306 (1296) ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና
ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ
የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::
#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ እና #ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ
ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ♥
ቅዱስ #ተክለ_ሃይማኖት ሐዋርያዊ "*+ #ልደት
መልካም ዛፍ
መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ: #
ጸጋ_ዘአብ ካህኑና #እግዚእ_ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ:
እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ
ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: +በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ
ቢደርስባቸው #ቅዱስ_ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ
ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል::
በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል:: +አቡነ ተክለ
ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24, በ1206 (1196) ሲሆን
የተወለዱት ታሕሳስ 24, በ1207 (1197) ዓ/ም ነው::
በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም
በበረከት ሞልቷል:: #ዕድገት =>የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው
"#ፍሥሃ_ጽዮን" ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ
ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን
(ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ
አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ #አባ_
ጌርሎስ ተቀብለዋል:: #መጠራት =>አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን
ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ
ተሰማ:: የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ አእላፍ
መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::
+የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ: "ከዛሬ ጀምሮ
ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: አራዊትን
ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ
በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ
ሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ
ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ:: #አገልግሎት
=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል
አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (#
ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው
አጠመቁ:: ያንጊዜ #ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት:: 1.ዮዲት
(ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ
አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ
አምልኮ ተጠምዷል:: 2.ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት
ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: +ግማሹ ሃገር በጨለመበት
ወቅት የደረሱት #ሐዲስ_ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት
ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ::
ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን
(ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: #ገዳማዊ ሕይወት =>ቅዱስ
ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው
ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ
የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::
+እነዚህም በአቡነ #በጸሎተ_ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት:
በአቡነ #ኢየሱስ_ሞዐ_ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ
ዳሞ ከአቡነ #ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26
ዓመታት አገልግለዋል:: +በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ
በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ #ዞረሬ ተመልሰው በአንዲት በዓት
ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም
6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል:: #
ስድስት ክንፍ =>ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ
ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት
መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ #እሥራኤል የገቡት
በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ
ነበር:: +የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት #አባ_ሚካኤል ጋርም
ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ
በሁዋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ
ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ
እንባቸው ይፈስ ነበር:: +ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው
ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
¤በቤተ መቅደስ ብስራቱን ¤በቤተ ልሔም ልደቱን ¤በቤተ ዮሴፍ
ግዝረቱን ¤በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን ¤በቤተ አልዓዛር
ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር:: +የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል
ወደሆነው #ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ
ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን
ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ
#እመቤታችን_ድንግል_ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን
ወደሰማይ አሳረገቻቸው:: +በዚያም:- ¤የብርሃን ዐይን
ተቀብለው ¤6 ክንፍ አብቅለው ¤የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
¤ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው ¤ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም
ተደምረው ¤ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
¤"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ
ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል:: #ተአምራት
=>የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል *ድውያንን ፈውሰዋል *አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል *በክንፍ በረዋል *ደመናን ዙፋን
አድርገዋል:: +ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን
መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት
አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: #ዕረፍት
=>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን
ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: አእላፍ ፍሬን አፍርተው:
በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24,
በ1306 (1296) ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና
ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ
የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::
♥ #ቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ ♥
ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነ ዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር
ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: #ቅዱስ_ሉቃስ
ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ
ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "#ዘካርያስ ካህኑና
#ቅድስት_ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ
ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)
✝የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ
መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል!
✝እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው
ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ
ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90
የዘካርያስ 100 ደግሞ ደርሶ ነበር::
✝ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ
እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው
የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን
ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን
ላከላቸው::
✝ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ
ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው
ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት
ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል
#እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች::
ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::
✝የአምላክ እናቱ ስትደርስና "#ሰላም " ስትላቸው መንፈስ
ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ
ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ
በሁዋላ ሰኔ 30 ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው
አንደበቱ
ተፈትቶለታል::
✝ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው
ጊዜ #ሰብአ_ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር
የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም
አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ
የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ
'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ::
✝እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን
ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል::
አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ
ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7)
ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች::
ከሰማይ ዘካርያስና # ስምዖን ወርደው ቀበሯት::
✝ሕጻኑ ዮሐንስ ሲያለቅስ #ድንግል_ማርያም ስንት አገር
አልፋ ሰማችው:: እርሷም ስደት ላይ ነበረችና:: ከጌታ
ጋር በደመና ሒደው ድንግል አቅፋ አጽናናችው:: ጌታንም
"እንውሰደው ይሆን?" አለችው:: ጌታችን ግን
"ለአገልግሎት እስክጠራው እዚህ ይቆይ" አላት::
ባርካው: አጽናንታውም ተለያዩ::
✝ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ በሁዋላ በዚያ ቆላ የግመል
ጠጉር ለብሶ: ጠፍር ታጥቆ ተባሕትዎውን ቀጠለ:: ለ25
(23) ዓመታትም በንጽሕና ሲኖር ከምድር አራዊትና
ከሰማይ መላእክት በቀር ማንንም አላየም:: ይሕችን
ዐመጸኛ ዓለምም አልቀመሳትም::
✝ከዚህ በሁዋላ 30 ዘመን ሲሞላው እግዚአብሔር
ከሰማይ ተናገረው:: "ሒድ! የልጀን ጐዳና ጥረግ"
አለው:: ነቢያት ስለዚህ ነገር ተናግረው ነበርና:: (ኢሳ.
40:3, ሚል. 3:1) አባቱ ዘካርያስም "ወአንተኒ ሕጻን
ነቢየ ልዑል ትሰመይ: እስመ ተሐውር ቅድመ
እግዚአብሔር ከመ ትጺሕ ፍኖቶ" (ሉቃ. 1:76) ብሎ
መንገድ ጠራጊነቱን ተናግሮ ነበርና::
ቅዱስ ዮሐንስ በዚያ ጊዜ በኃይለ #መንፈስ_ቅዱስ
እየገሰገሰ ከበርሃ ወደ ይሁዳ መጣ:: ያዩት ሁሉ ፈሩት:
አከበሩት:: ቁመቱ ቀጥ ያለ: ጽሕሙ እንደ ተፈተለ ሐር
የወረደ: ጸጉሩ የቁራ ያህል የጠቆረ: መልኩ የተሟላ:
ግርማው የሚያስፈራ ገዳማዊ ነውና::
ፈጥኖም ሕዝቡን ለንስሃ ሰበከ:: ለንስሃም በርካቶችን
አጠመቃቸው:: በዚህ አገልግሎት ለ6 ወራት ቆይቶ
ጌታችን ወደ እርሱ ዘንድ መጣ:: ዮሐንስ ሰማይን
ከነግሱ: ምድርን ከነ ልብሱ የያዘ ፈጣሪ 'አጥምቀኝ'
ብሎ ሲመጣ ደነገጠ:: የሚገባበትም ጠፋው::
"እንቢ ጌታየ! አንተ አጥምቀኝ" አለው:: ጌታ ግን
"ፈቅጄልሃለሁ" አለው:: አጠመቀው:: በዚህ ምክንያት
ይሔው እስከ ዛሬም "#መጥምቀ_መለኮት " ሲባል
ይኖራል:: ቅዱስ ዮሐንስ በመጨረሻ ሔሮድስን ገሰጸው::
ንጉሡም ተቀይሞ ለ7 ቀናት አሠረው::
✝በዚህች ቀንም ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ
በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ
ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጐ ሰጣት:: አበው
"እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ
መሐላውን በበላ በተሻለው ነበር" ይላሉ:: የቅዱስ
ዮሐንስ ራሱ በርራ ስትሔድ አካሉን ግን ደቀ መዛሙርቱ
ቀብረውታል:: (ማቴ. 3:1, ማር. 6:14, ሉቃ. 3:1, ዮሐ.
1:6)
ርጉም ሔሮድስ አንገቱን ካስቆረጠው በሁዋላ
የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ራሱ የጸጋ ክንፍ ተሰጥቷት
ጌታችን ወዳለበት #ደብረ_ዘይት ሔዳ በፊቱ ሰገደች::
#ቅዱሳን_ሐዋርያት በአዩት ነገር ተገርመው ራሱን እጅ
ነሷት::
ከዚሕ በሁዋላ ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ለቅዱስ
ዮሐንስ ራስ የማስተማር ስልጣን ሰጥቶ አሰናበታት::
በመላው ዓለም ለ15 ዓመታት ስትሰብክ ኑራ በዚህች
ቀን ዓረቢያ ውስጥ ዓርፋለች::
ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነ ዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር
ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: #ቅዱስ_ሉቃስ
ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ
ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "#ዘካርያስ ካህኑና
#ቅድስት_ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ
ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)
✝የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ
መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል!
✝እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው
ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ
ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90
የዘካርያስ 100 ደግሞ ደርሶ ነበር::
✝ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ
እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው
የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን
ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን
ላከላቸው::
✝ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ
ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው
ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት
ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል
#እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች::
ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::
✝የአምላክ እናቱ ስትደርስና "#ሰላም " ስትላቸው መንፈስ
ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ
ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ
በሁዋላ ሰኔ 30 ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው
አንደበቱ
ተፈትቶለታል::
✝ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው
ጊዜ #ሰብአ_ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር
የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም
አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ
የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ
'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ::
✝እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን
ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል::
አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ
ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7)
ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች::
ከሰማይ ዘካርያስና # ስምዖን ወርደው ቀበሯት::
✝ሕጻኑ ዮሐንስ ሲያለቅስ #ድንግል_ማርያም ስንት አገር
አልፋ ሰማችው:: እርሷም ስደት ላይ ነበረችና:: ከጌታ
ጋር በደመና ሒደው ድንግል አቅፋ አጽናናችው:: ጌታንም
"እንውሰደው ይሆን?" አለችው:: ጌታችን ግን
"ለአገልግሎት እስክጠራው እዚህ ይቆይ" አላት::
ባርካው: አጽናንታውም ተለያዩ::
✝ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ በሁዋላ በዚያ ቆላ የግመል
ጠጉር ለብሶ: ጠፍር ታጥቆ ተባሕትዎውን ቀጠለ:: ለ25
(23) ዓመታትም በንጽሕና ሲኖር ከምድር አራዊትና
ከሰማይ መላእክት በቀር ማንንም አላየም:: ይሕችን
ዐመጸኛ ዓለምም አልቀመሳትም::
✝ከዚህ በሁዋላ 30 ዘመን ሲሞላው እግዚአብሔር
ከሰማይ ተናገረው:: "ሒድ! የልጀን ጐዳና ጥረግ"
አለው:: ነቢያት ስለዚህ ነገር ተናግረው ነበርና:: (ኢሳ.
40:3, ሚል. 3:1) አባቱ ዘካርያስም "ወአንተኒ ሕጻን
ነቢየ ልዑል ትሰመይ: እስመ ተሐውር ቅድመ
እግዚአብሔር ከመ ትጺሕ ፍኖቶ" (ሉቃ. 1:76) ብሎ
መንገድ ጠራጊነቱን ተናግሮ ነበርና::
ቅዱስ ዮሐንስ በዚያ ጊዜ በኃይለ #መንፈስ_ቅዱስ
እየገሰገሰ ከበርሃ ወደ ይሁዳ መጣ:: ያዩት ሁሉ ፈሩት:
አከበሩት:: ቁመቱ ቀጥ ያለ: ጽሕሙ እንደ ተፈተለ ሐር
የወረደ: ጸጉሩ የቁራ ያህል የጠቆረ: መልኩ የተሟላ:
ግርማው የሚያስፈራ ገዳማዊ ነውና::
ፈጥኖም ሕዝቡን ለንስሃ ሰበከ:: ለንስሃም በርካቶችን
አጠመቃቸው:: በዚህ አገልግሎት ለ6 ወራት ቆይቶ
ጌታችን ወደ እርሱ ዘንድ መጣ:: ዮሐንስ ሰማይን
ከነግሱ: ምድርን ከነ ልብሱ የያዘ ፈጣሪ 'አጥምቀኝ'
ብሎ ሲመጣ ደነገጠ:: የሚገባበትም ጠፋው::
"እንቢ ጌታየ! አንተ አጥምቀኝ" አለው:: ጌታ ግን
"ፈቅጄልሃለሁ" አለው:: አጠመቀው:: በዚህ ምክንያት
ይሔው እስከ ዛሬም "#መጥምቀ_መለኮት " ሲባል
ይኖራል:: ቅዱስ ዮሐንስ በመጨረሻ ሔሮድስን ገሰጸው::
ንጉሡም ተቀይሞ ለ7 ቀናት አሠረው::
✝በዚህች ቀንም ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ
በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ
ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጐ ሰጣት:: አበው
"እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ
መሐላውን በበላ በተሻለው ነበር" ይላሉ:: የቅዱስ
ዮሐንስ ራሱ በርራ ስትሔድ አካሉን ግን ደቀ መዛሙርቱ
ቀብረውታል:: (ማቴ. 3:1, ማር. 6:14, ሉቃ. 3:1, ዮሐ.
1:6)
ርጉም ሔሮድስ አንገቱን ካስቆረጠው በሁዋላ
የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ራሱ የጸጋ ክንፍ ተሰጥቷት
ጌታችን ወዳለበት #ደብረ_ዘይት ሔዳ በፊቱ ሰገደች::
#ቅዱሳን_ሐዋርያት በአዩት ነገር ተገርመው ራሱን እጅ
ነሷት::
ከዚሕ በሁዋላ ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ለቅዱስ
ዮሐንስ ራስ የማስተማር ስልጣን ሰጥቶ አሰናበታት::
በመላው ዓለም ለ15 ዓመታት ስትሰብክ ኑራ በዚህች
ቀን ዓረቢያ ውስጥ ዓርፋለች::
🌼" አፄ ልብነ ድንግል "🌼
+እኒህ ንጉሥ ኢትዮዽያን ለዓመታት (ከ1500 እስከ 1532
ዓ/ም) ቢያስተዳድሩም 15ቱ ዓመት ያለቀው በስደት ነው::
ከደጋጉ አፄ ናዖድና ንግሥት ወለተ ማርያም ተወልደው:
በሥርዓቱ አድገው ቢነግሡም: በክፉ መካሪዎች ጠንቅዋይ
ወደ ቤታቸው ገብቶ ሃገሪቱን ለመከራ ዳርጉዋታል::
+ዛሬም ድረስ ጠባሳው ያለቀቀው የግራኝ ወረራ ለ15
ዓመታት ሃገሪቱን ያለ ካህንና ቤተ ክርስቲያን አስቀርቷት ነበር::
ብዙ ክርስቲያኖችም ሰልመው ቀርተዋል:: አፄ ልብነ ድንግል
ግን ደብረ ዳሞ ገዳም ውስጥ ገብተው ንስሃ ጀመሩ: አለቀሱ:
ተማለሉ::
#እመቤታችን ተገልጣም "ይቅርታን በነፍስህ እንጂ በሥጋህ
አታገኝም" አለቻቸው:: እርሳቸውም ሱባኤውን ቀጥለው:
'#ስብሐተ ፍቁርን': '#መልክአ ኤዶምን' የመሰሉ መጻሕፍትን
ደርሰው በዚህች ቀን በ ዓ/ም ዐርፈዋል:: እኛ ክርስቲያኖችም
እናከብራቸዋለን::
🌼የቅዱሳኑ አምላክ የወዳጆቹን ፈተና አስቦ ሃገራችንን
ከጥፋት: ሕዝቡንም ከስደት ይሰውርልን:: ከበረከታቸውም
አይለየን::🌼
+እኒህ ንጉሥ ኢትዮዽያን ለዓመታት (ከ1500 እስከ 1532
ዓ/ም) ቢያስተዳድሩም 15ቱ ዓመት ያለቀው በስደት ነው::
ከደጋጉ አፄ ናዖድና ንግሥት ወለተ ማርያም ተወልደው:
በሥርዓቱ አድገው ቢነግሡም: በክፉ መካሪዎች ጠንቅዋይ
ወደ ቤታቸው ገብቶ ሃገሪቱን ለመከራ ዳርጉዋታል::
+ዛሬም ድረስ ጠባሳው ያለቀቀው የግራኝ ወረራ ለ15
ዓመታት ሃገሪቱን ያለ ካህንና ቤተ ክርስቲያን አስቀርቷት ነበር::
ብዙ ክርስቲያኖችም ሰልመው ቀርተዋል:: አፄ ልብነ ድንግል
ግን ደብረ ዳሞ ገዳም ውስጥ ገብተው ንስሃ ጀመሩ: አለቀሱ:
ተማለሉ::
#እመቤታችን ተገልጣም "ይቅርታን በነፍስህ እንጂ በሥጋህ
አታገኝም" አለቻቸው:: እርሳቸውም ሱባኤውን ቀጥለው:
'#ስብሐተ ፍቁርን': '#መልክአ ኤዶምን' የመሰሉ መጻሕፍትን
ደርሰው በዚህች ቀን በ ዓ/ም ዐርፈዋል:: እኛ ክርስቲያኖችም
እናከብራቸዋለን::
🌼የቅዱሳኑ አምላክ የወዳጆቹን ፈተና አስቦ ሃገራችንን
ከጥፋት: ሕዝቡንም ከስደት ይሰውርልን:: ከበረከታቸውም
አይለየን::🌼
💚💛ቅድስት ጾመ ፍልሠታ ለማርያም💛❤️
ቸር #እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ከሰጠው ጸጋ አንዱ #ጾም ነው:: የሰው ልጅ ከፈጣሪው ክብር እንዲደረግለት ክፋትን መስራት የለበትም:: መልካም መሆንም ይጠበቅበታል:: ለዚህ ምንጮቹ ደግሞ ጾም: ጸሎትና ስግደት ናቸው:: ያለ እነዚህ ምግባራት መቼም ወደ #ጽድቅ መድረስ አይቻልም::
ይቅርና እኛ ክፉዎቹ የሰማይና የምድር ፈጣሪ: የክብር ሁሉ ባለቤት ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ሥጋችንን በተዋሐደ ጊዜ የመጀመሪያ ሥራው ያደረገው ጾምን ነው:: ስለዚህም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን 7 አጽዋማትን በጉባዔ ሠርታ: በአዋጅ እንዲጾሙ ታደርጋለች:: ከእነዚህም አንዱ ጾመ ፍልሠታ ነው::
"ፈለሠ" - ሔደ: ተጉዋዘ እንደ ማለት ሲሆን " #ፍልሠታ" ማለት የእመቤታችን ቅድስት #ድንግል_ማርያምን የዕርገት ጉዞ የሚያዘክር ቃል ነው:: #እመ_ብርሃን በዚህ ዓለም ለ64 ዓመታት ኑራ ካረፈች በሁዋላ ሥጋዋ እንደ እኛ አልፈረሰም::
ለጊዜው በዕጸ ሕይወት ሥር ቆይታ እንደ ልጇ ትንሳኤ ተነስታ ዐርጋለች:: እርሷ በሁሉ ነገሯ ቀዳሚና መሪ ናትና:: ጾመ ፍልሠታን የጀመሩት አበው #ሐዋርያት ሲሆኑ እንድትጾምም ሥርዓት የሠሩ ራሳቸው ናቸው:: ከ7ቱ አጽዋማትም እጅግ ተወዳጅና እየተናፈቀች የምትፈጸም ናት::
ካህናትና ምዕመናንም ጾሟን እንደየአቅማቸው ክብር በሚያሰጥ መንገድ ይፈጽሟታል::
*የቻሉ ወደ ገዳማት ሔደው ጥሬ እየቆረጠሙ: ውሃ እየተጐነጩ ክብርን ያገኛሉ::
*ሌሎቹ ደግሞ ባሉበት ደብር አካባቢ እያደሩ ሌሊት ሰዓታቱን: በነግህ ኪዳኑንና ውዳሴ ማርያም ትርጉዋሜውን: በሰርክ ደግሞ ቅዳሴውን ይሳተፋሉ::
*የኔ ብጤ ደካማ ደግሞ ጠዋት ማታ ወደ ደጇ እየተመላለሰ "አደራሽን ድንግል" ይላታል::
በእርሷ አምነን አፍረን አናውቅምና ነጋ መሸ ሳንል እንማጸናታለን::
#ጽንዕት_በድንግልና: #ሥርጉት_በቅድስና
#እመቤታችን
ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን: ልበለብዎውን: ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን::
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
*ጾሙን የፍሬ: የትሩፋትና የበረከት ያድርግልን::*
From dn yordanos abebe
@senkesar @senkesar
ቸር #እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ከሰጠው ጸጋ አንዱ #ጾም ነው:: የሰው ልጅ ከፈጣሪው ክብር እንዲደረግለት ክፋትን መስራት የለበትም:: መልካም መሆንም ይጠበቅበታል:: ለዚህ ምንጮቹ ደግሞ ጾም: ጸሎትና ስግደት ናቸው:: ያለ እነዚህ ምግባራት መቼም ወደ #ጽድቅ መድረስ አይቻልም::
ይቅርና እኛ ክፉዎቹ የሰማይና የምድር ፈጣሪ: የክብር ሁሉ ባለቤት ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ሥጋችንን በተዋሐደ ጊዜ የመጀመሪያ ሥራው ያደረገው ጾምን ነው:: ስለዚህም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን 7 አጽዋማትን በጉባዔ ሠርታ: በአዋጅ እንዲጾሙ ታደርጋለች:: ከእነዚህም አንዱ ጾመ ፍልሠታ ነው::
"ፈለሠ" - ሔደ: ተጉዋዘ እንደ ማለት ሲሆን " #ፍልሠታ" ማለት የእመቤታችን ቅድስት #ድንግል_ማርያምን የዕርገት ጉዞ የሚያዘክር ቃል ነው:: #እመ_ብርሃን በዚህ ዓለም ለ64 ዓመታት ኑራ ካረፈች በሁዋላ ሥጋዋ እንደ እኛ አልፈረሰም::
ለጊዜው በዕጸ ሕይወት ሥር ቆይታ እንደ ልጇ ትንሳኤ ተነስታ ዐርጋለች:: እርሷ በሁሉ ነገሯ ቀዳሚና መሪ ናትና:: ጾመ ፍልሠታን የጀመሩት አበው #ሐዋርያት ሲሆኑ እንድትጾምም ሥርዓት የሠሩ ራሳቸው ናቸው:: ከ7ቱ አጽዋማትም እጅግ ተወዳጅና እየተናፈቀች የምትፈጸም ናት::
ካህናትና ምዕመናንም ጾሟን እንደየአቅማቸው ክብር በሚያሰጥ መንገድ ይፈጽሟታል::
*የቻሉ ወደ ገዳማት ሔደው ጥሬ እየቆረጠሙ: ውሃ እየተጐነጩ ክብርን ያገኛሉ::
*ሌሎቹ ደግሞ ባሉበት ደብር አካባቢ እያደሩ ሌሊት ሰዓታቱን: በነግህ ኪዳኑንና ውዳሴ ማርያም ትርጉዋሜውን: በሰርክ ደግሞ ቅዳሴውን ይሳተፋሉ::
*የኔ ብጤ ደካማ ደግሞ ጠዋት ማታ ወደ ደጇ እየተመላለሰ "አደራሽን ድንግል" ይላታል::
በእርሷ አምነን አፍረን አናውቅምና ነጋ መሸ ሳንል እንማጸናታለን::
#ጽንዕት_በድንግልና: #ሥርጉት_በቅድስና
#እመቤታችን
ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን: ልበለብዎውን: ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን::
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
*ጾሙን የፍሬ: የትሩፋትና የበረከት ያድርግልን::*
From dn yordanos abebe
@senkesar @senkesar
ባልንጀራህን አትቀየመው ።
ወኢትትቀየም ቢጸከ ⇨ ባልንጀራህን አትቀየም ⇨ be not angry with thy
neighbour" [ሢራ. ፳፰፥፯]
. እመቤታችን ያለ ምንም ነውር ፣ ሰይጣን ግን ያለ ምንም ክብር ሆነው ይኖራሉ።
. ቅዱሳን በሚደነቅ ንጽሕና እኛም በታላቅ ስንፍና የምንመላለስ ነን።
ነገር ግን ከበጎዎች ጥቂት ድክመት ከደካሞች ጥቂት በጎነት አይታጣም ።
ለዚህ ነው መጽሐፋችን ⇨ ፍጡር ከሆነ ከ #እመቤታችን በቀር ጥቂት ጽነት የሌለበት
የለም! ከነጭ ላም ከጉያዋ ከብሻሻዋ (ከብሽሽቷ) ቢፈልጉ ጥቂት ጥቁር እንዳይጠፋ፤
⇨ ፍጡርም ሆኖ ከ #ዲያብሎስ በቀር ጥቂት ቸርነት የሌለው የለምና! ከጥቁር ላም
ከጉያዋ ከብሻሻዋ ቢፈልጉ ጥቂት ነጭ እንዳይጠፋ፤
⇝ የኃጥኡ ምግባር ለጻድቁ ክብር ያበዛለታል የጻድቁም ክፋት በኃጥኡ ፍዳ የመጣበታልና
፦
እንደነ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት
እንደነ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ ያለ ቢሆንሳ ቢሉ ዝክራቸውን ለዘከረ ስማቸውን
ለጠራ ክብር ሲያሰጡ ይኖራሉ ይላል ፍትሕ መንፈሳዊ።(ፍትሐ ነገሥት ምዕ ፲ ቁ ፫፻፶፭
ትርጓሜ)
✧ መቼም #እኔ_ደካማ_ነኝ ! በሀገራችን እና በቤተክርስቲያናችን ላይ በዘመናችን
የመጣው ይኼ ፈተና በእኔ ምክንያት
① ነፍሴን በማጉደሌ፣ ② አምላኬን በመበደሌ እና ③ ባልንጀራዬን በማቃለሌ መሆኑን
አምናለሁ!
☞ለነፍሴ ድርሻዬን ለመወጣት እጥራለሁ!
☞ እግዚአብሔር ይቅር እንዲለኝ ለምኑልኝ (ክፍለ ሥላሴ) መቼም እርሱ እግዚአብሔር
ይቀየም ዘንድ እንደሰው አይደለምና በምሕረቱ እታመናለሁ ( ኢኮነ ከመ ዕጓለ መሕያው
ዘይትቄየም ዮዲ.፰ ፥፲፮)
☞ እናንተን ባልንጀሮቼን አልሜ ሰው ለመጉዳት አልያም ተሳስቼ ለመርዳት በጻፍኩት፣
በተናገርኩት ባደረኩትም ይቅር በሉኝ ከዚህ አልፎም ከእኔ በሚጠበቀውም መጠን
ድርሻዬን ሳልወጣ ሳልጽፍ፣ ሳልናገር እና ሳላደርግ በቀረሁትም ጭምር በእጅጉ ይቅርታ!
ሐሳቤን የበለጠ ያጠነክራል ብዬ ይኽን ከቅዱስ መጽሐፍ [የጠቢቡ ሢራክን ቃልና የሊቁን
የሕማማት ሰላምታ ክፍል] ለትምህርትና ለተማጽኖ አስቀምጬ ለ"ጥቂት" ጊዜ ልሰናበት።
“ አንተ ሰው ሆነህ እንዳንተ ያለውን ሰው ሳትቀየም እግዚአብሔርን እንዴት ይቅር
በለኝ ትለዋለህ? እንዳንተ ያለ ሰው ይቅር ሳትል ኃጢዓትህን ያስተሰርይልህ ዘንድ
እንግዲህ እንዴት ትለምነዋለህ ኃጢዓትህን አስበህ ጠብን ተዋት ሞትን አስበው
መቃብርንም አስበው ትእዛዙንም ጠብቅ፤ ሕጉን አስበህ ባልንጀራህን አትቀየም" ሢራ ፳፰፥
፪–፯
በከመ ልማድኪ በሊ ኀበ ወልድኪ ከሃሊ
.ኦ ርኅሩኅ ኢተበቃሊ
.ያጠፍኦኑ ለሥዕሉ ሠዓሊ ፦ ኪነተከ ዘትካት ኀሊ።
እንደዚህ በዪ እንደልማድሽ
. ሁሉን ወደሚችለው ልጅሽ
. የምትራራ ነህና የማትበቀል
. የእጅህን ድንቅ ሥራ ጠብቅ ፣ የቀደመውን ያንተን አምሳል
ሠዓሊ ሥዕሉን እንደምን ያጠፋል?!
‘እናታችን ድንግል’ ቂም ይዞ ከማይበቀለው ጽድቀ አሚንን ፣ ርትዓተ ልቡናን
ከሚያድለው ልጅሽ ይቅርታውን ይልክልን ዘንድ ለምኚልን!
ወኢትትቀየም ቢጸከ ⇨ ባልንጀራህን አትቀየም ⇨ be not angry with thy
neighbour" [ሢራ. ፳፰፥፯]
. እመቤታችን ያለ ምንም ነውር ፣ ሰይጣን ግን ያለ ምንም ክብር ሆነው ይኖራሉ።
. ቅዱሳን በሚደነቅ ንጽሕና እኛም በታላቅ ስንፍና የምንመላለስ ነን።
ነገር ግን ከበጎዎች ጥቂት ድክመት ከደካሞች ጥቂት በጎነት አይታጣም ።
ለዚህ ነው መጽሐፋችን ⇨ ፍጡር ከሆነ ከ #እመቤታችን በቀር ጥቂት ጽነት የሌለበት
የለም! ከነጭ ላም ከጉያዋ ከብሻሻዋ (ከብሽሽቷ) ቢፈልጉ ጥቂት ጥቁር እንዳይጠፋ፤
⇨ ፍጡርም ሆኖ ከ #ዲያብሎስ በቀር ጥቂት ቸርነት የሌለው የለምና! ከጥቁር ላም
ከጉያዋ ከብሻሻዋ ቢፈልጉ ጥቂት ነጭ እንዳይጠፋ፤
⇝ የኃጥኡ ምግባር ለጻድቁ ክብር ያበዛለታል የጻድቁም ክፋት በኃጥኡ ፍዳ የመጣበታልና
፦
እንደነ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት
እንደነ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ ያለ ቢሆንሳ ቢሉ ዝክራቸውን ለዘከረ ስማቸውን
ለጠራ ክብር ሲያሰጡ ይኖራሉ ይላል ፍትሕ መንፈሳዊ።(ፍትሐ ነገሥት ምዕ ፲ ቁ ፫፻፶፭
ትርጓሜ)
✧ መቼም #እኔ_ደካማ_ነኝ ! በሀገራችን እና በቤተክርስቲያናችን ላይ በዘመናችን
የመጣው ይኼ ፈተና በእኔ ምክንያት
① ነፍሴን በማጉደሌ፣ ② አምላኬን በመበደሌ እና ③ ባልንጀራዬን በማቃለሌ መሆኑን
አምናለሁ!
☞ለነፍሴ ድርሻዬን ለመወጣት እጥራለሁ!
☞ እግዚአብሔር ይቅር እንዲለኝ ለምኑልኝ (ክፍለ ሥላሴ) መቼም እርሱ እግዚአብሔር
ይቀየም ዘንድ እንደሰው አይደለምና በምሕረቱ እታመናለሁ ( ኢኮነ ከመ ዕጓለ መሕያው
ዘይትቄየም ዮዲ.፰ ፥፲፮)
☞ እናንተን ባልንጀሮቼን አልሜ ሰው ለመጉዳት አልያም ተሳስቼ ለመርዳት በጻፍኩት፣
በተናገርኩት ባደረኩትም ይቅር በሉኝ ከዚህ አልፎም ከእኔ በሚጠበቀውም መጠን
ድርሻዬን ሳልወጣ ሳልጽፍ፣ ሳልናገር እና ሳላደርግ በቀረሁትም ጭምር በእጅጉ ይቅርታ!
ሐሳቤን የበለጠ ያጠነክራል ብዬ ይኽን ከቅዱስ መጽሐፍ [የጠቢቡ ሢራክን ቃልና የሊቁን
የሕማማት ሰላምታ ክፍል] ለትምህርትና ለተማጽኖ አስቀምጬ ለ"ጥቂት" ጊዜ ልሰናበት።
“ አንተ ሰው ሆነህ እንዳንተ ያለውን ሰው ሳትቀየም እግዚአብሔርን እንዴት ይቅር
በለኝ ትለዋለህ? እንዳንተ ያለ ሰው ይቅር ሳትል ኃጢዓትህን ያስተሰርይልህ ዘንድ
እንግዲህ እንዴት ትለምነዋለህ ኃጢዓትህን አስበህ ጠብን ተዋት ሞትን አስበው
መቃብርንም አስበው ትእዛዙንም ጠብቅ፤ ሕጉን አስበህ ባልንጀራህን አትቀየም" ሢራ ፳፰፥
፪–፯
በከመ ልማድኪ በሊ ኀበ ወልድኪ ከሃሊ
.ኦ ርኅሩኅ ኢተበቃሊ
.ያጠፍኦኑ ለሥዕሉ ሠዓሊ ፦ ኪነተከ ዘትካት ኀሊ።
እንደዚህ በዪ እንደልማድሽ
. ሁሉን ወደሚችለው ልጅሽ
. የምትራራ ነህና የማትበቀል
. የእጅህን ድንቅ ሥራ ጠብቅ ፣ የቀደመውን ያንተን አምሳል
ሠዓሊ ሥዕሉን እንደምን ያጠፋል?!
‘እናታችን ድንግል’ ቂም ይዞ ከማይበቀለው ጽድቀ አሚንን ፣ ርትዓተ ልቡናን
ከሚያድለው ልጅሽ ይቅርታውን ይልክልን ዘንድ ለምኚልን!