❖✝ እንኩዋን ለሰማዕታት ቅዱስ #እንጣዎስ እና ቅዱስ
#ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✝❖
#ቅዱስ_እንጣዎስ_አሞራዊ ይሕ ቅዱስ በቀደመ ሕይወቱ ክርስቲያኖችን የሚጠላ
አስቸጋሪ አረማዊ ነበር:: ሃገሩ #ሶርያ ( #ደማስቆ ) ሲሆን
ግብሩ ጣዖት ማምለክና መስረቅ ነበር:: በቅድስት ቤተ
ክርስቲያንና በምዕመናን ላይም ግፍን ፈጽሟል:: በሥጋዊ
ጉልበቱ ኃይለኛ ስለ ነበር የተፈራ ነው::
ሁልጊዜ በጠዋት ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ይሔዳል::
የሚሔደው ግን ንዋያተ ቅድሳትን ለመዝረፍ: አንድም
ካህናትን ለመደብደብ ነበር:: የሚገርመው ግን የወቅቱ
ምዕመናንና ካህናት ይህን ሁሉ እያደረገባቸው አይጠሉትም::
ይልቁኑ ይጸልዩለት ነበር እንጂ:: ምክንያቱም ክርስትና ማለት
ጠላትን መውደድ ነውና:: (ማቴ. 7)
የእግዚአብሔር ትዕግስትና የምዕመናን ጸሎት ተደምሮው
አንድ ቀን ፍሬ አፈራ:: እንጣዎስ እንደ ለመደው ለክፉ ሥራ
ወደ # ቅዱስ_ቴዎድሮስ ቤተ ክርስቲያን ይሔዳል:: ከዚያም
እንደ ደረሰ ወደ ውስጥ ገብቶ: የሚማታውን ተማቶ:
የሚዘርፈውንም ዘርፎ: የተረፉትን ንዋያተ ቅድሳት በእሳት
አቃጠላቸው::
#እግዚአብሔር ከዚህም በላይ ታጋሽ ነውና አላጠፋውም::
"ዘኢይፈቅድ ለኃጥእ ሞቶ" እንዲል የኃጢአተኛውን መመለስ
እንጂ መሞቱን አይፈልግም:: ለዚያም ነው ዛሬ ይሔ ሁሉ
ግፍ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየተሠራ እግዚአብሔር
እንደማያይ ዝም የሚለው:: ለሁሉም ቀን አለውና በፈረደ ቀን
ግን በፊቱ የሚቆም አይኖርም::
እንጣዎስ ግን የሠራውን ሠርቶ እወጣለሁ ሲል
አልተሳካለትም:: ከበሩ አካባቢ ሲደርስ: ከወደ ሰማይ
አካባቢ ድምጽ ሰምቶ ቀና ሲል መላእክት እንደሱ ዓይነት
ኃጢአተኞችን አሰልፈው በጦርና በቀስት ሲወጉአቸው
ተመለከተ::
ድንገት ግን ከመላእክቱ አንዱ ዘወር ብሎ አንድ ቀስት ወደ
እንጣዎስ ወረወረ (ተኮሰ):: ቀስቷ አካሉ ውስጥ ገብታለችና
እንጣዎስ መሬት ላይ ወድቆ ለሞት ደረሰ:: ላበቱ በግንባሩ
ላይ በጭንቅ እየፈሰሰ ጮኸ::
"ጌታየ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ማረኝ? ራራልኝ? ይቅር
በለኝ? በድፍረት ባለ ማወቅም በድየሃለሁ:: ይቅር በለኝና
ላምልክህ: ስምህንም ልሸከም" ሲል በጭንቀት ውስጥ ሆኖ
አሰምቶ ጸለየ:: በዚያ የነበሩ ምዕመናን ማን: በምን እንደ
ወጋው ባያውቁም ባዩት ነገር ግን እጅግ ደስ አላቸው::
እነርሱም የፈጉትና የጸለዩለት ነገር ይሔው ነበርና::
ወዲያው ግን እንጣዎስ ከሞት ጫፍ ተመልሶ ተነሳ::
መጀመሪያ በቦታው የነበሩ ካህናትና ምዕመናንን "ይቅር
በሉኝ?" አለ:: ቀጥሎም ወደ ዻዻስ ዘንድ ሔዶ "አጥምቀኝ"
ሲል ጠየቀ:: እርሱ በሚጠመቅበት ቀን ብዙ አሕዛብና
ክርስቲያኖች ተሰብስበው ነበር::
እርሱ በከተማዋ ዝነኛ ነበር:: ሥርዓቱ ሁሉ ተደርሶ ቅዱሱ
ወደ ውሃ ገንዳው ሲገባ ሁሉ እያዩ የብርሃን ምሰሶ ከሰማይ
ወረደ:: ይህንን በገሃድ የተመለከቱ ከ10,000 በላይ አሕዛብ
ወዲያውኑ በክርስቶስ አምነው አብረውት ተጠምቀዋል::
ቅዱስ እንጣዎስ ከዚህ በሁዋላ ምስጉን ክርስቲያን ሆነ::
ስለ ቀደመ ሕይወቱ ፈንታ ጾምን: ጸሎትን: ፍቅርን: ምጽዋትን
ገንዘብ አደረገ:: ሕይወቱም ለብዙ ሰዎች መስታውት ሆነ::
#እመቤታችን ድንግል ማርያምንም ይወዳት ነበርና ወደ
ቅዱሳን ማሕበር ( #ኢየሩሳሌም ) ወስዳው በሥጋዊ አንደበት
ተከናውኖ ሊነገር የማይቻል ምሥጢርን ገልጣለታለች::
እነዚህን የቅድስና ጊዜያት በስኬት ያሳለፈው ቅዱስ
እንጣዎስ መጨረሻው ሰማዕትነት ሆነ:: አረማውያን ወገኖቹና ቀድሞ የሚያውቁት ወደ ቀደመ ክፋትና
ክህደት እንዲመለስ ጠየቁት:: "አይሆንም" አላቸው::
በአደባባይ ለፍርድ አቅርበው ደሙ እስኪፈስ ገረፉት::
ጥርሶቹን በሙሉ በድንጋይ አረገፏቸው:: ደሙና ጥርሶቹ
መሬት ላይ ተዘሩ:: ነገር ግን ይሕ ስቃይ ቅዱሱን ከፍቅረ
ክርስቶስ ሊለየው አልቻለም:: አሕዛብም ተስፋ ቆርጠው
በዚህች ቀን ገድለውታል:: ቅዱስ እንጣዎስም ከሁዋለኛው
ዘመን #ሰማዕታት እንደ አንዱ ተቆጥሯል::
#ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✝❖
#ቅዱስ_እንጣዎስ_አሞራዊ ይሕ ቅዱስ በቀደመ ሕይወቱ ክርስቲያኖችን የሚጠላ
አስቸጋሪ አረማዊ ነበር:: ሃገሩ #ሶርያ ( #ደማስቆ ) ሲሆን
ግብሩ ጣዖት ማምለክና መስረቅ ነበር:: በቅድስት ቤተ
ክርስቲያንና በምዕመናን ላይም ግፍን ፈጽሟል:: በሥጋዊ
ጉልበቱ ኃይለኛ ስለ ነበር የተፈራ ነው::
ሁልጊዜ በጠዋት ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ይሔዳል::
የሚሔደው ግን ንዋያተ ቅድሳትን ለመዝረፍ: አንድም
ካህናትን ለመደብደብ ነበር:: የሚገርመው ግን የወቅቱ
ምዕመናንና ካህናት ይህን ሁሉ እያደረገባቸው አይጠሉትም::
ይልቁኑ ይጸልዩለት ነበር እንጂ:: ምክንያቱም ክርስትና ማለት
ጠላትን መውደድ ነውና:: (ማቴ. 7)
የእግዚአብሔር ትዕግስትና የምዕመናን ጸሎት ተደምሮው
አንድ ቀን ፍሬ አፈራ:: እንጣዎስ እንደ ለመደው ለክፉ ሥራ
ወደ # ቅዱስ_ቴዎድሮስ ቤተ ክርስቲያን ይሔዳል:: ከዚያም
እንደ ደረሰ ወደ ውስጥ ገብቶ: የሚማታውን ተማቶ:
የሚዘርፈውንም ዘርፎ: የተረፉትን ንዋያተ ቅድሳት በእሳት
አቃጠላቸው::
#እግዚአብሔር ከዚህም በላይ ታጋሽ ነውና አላጠፋውም::
"ዘኢይፈቅድ ለኃጥእ ሞቶ" እንዲል የኃጢአተኛውን መመለስ
እንጂ መሞቱን አይፈልግም:: ለዚያም ነው ዛሬ ይሔ ሁሉ
ግፍ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየተሠራ እግዚአብሔር
እንደማያይ ዝም የሚለው:: ለሁሉም ቀን አለውና በፈረደ ቀን
ግን በፊቱ የሚቆም አይኖርም::
እንጣዎስ ግን የሠራውን ሠርቶ እወጣለሁ ሲል
አልተሳካለትም:: ከበሩ አካባቢ ሲደርስ: ከወደ ሰማይ
አካባቢ ድምጽ ሰምቶ ቀና ሲል መላእክት እንደሱ ዓይነት
ኃጢአተኞችን አሰልፈው በጦርና በቀስት ሲወጉአቸው
ተመለከተ::
ድንገት ግን ከመላእክቱ አንዱ ዘወር ብሎ አንድ ቀስት ወደ
እንጣዎስ ወረወረ (ተኮሰ):: ቀስቷ አካሉ ውስጥ ገብታለችና
እንጣዎስ መሬት ላይ ወድቆ ለሞት ደረሰ:: ላበቱ በግንባሩ
ላይ በጭንቅ እየፈሰሰ ጮኸ::
"ጌታየ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ማረኝ? ራራልኝ? ይቅር
በለኝ? በድፍረት ባለ ማወቅም በድየሃለሁ:: ይቅር በለኝና
ላምልክህ: ስምህንም ልሸከም" ሲል በጭንቀት ውስጥ ሆኖ
አሰምቶ ጸለየ:: በዚያ የነበሩ ምዕመናን ማን: በምን እንደ
ወጋው ባያውቁም ባዩት ነገር ግን እጅግ ደስ አላቸው::
እነርሱም የፈጉትና የጸለዩለት ነገር ይሔው ነበርና::
ወዲያው ግን እንጣዎስ ከሞት ጫፍ ተመልሶ ተነሳ::
መጀመሪያ በቦታው የነበሩ ካህናትና ምዕመናንን "ይቅር
በሉኝ?" አለ:: ቀጥሎም ወደ ዻዻስ ዘንድ ሔዶ "አጥምቀኝ"
ሲል ጠየቀ:: እርሱ በሚጠመቅበት ቀን ብዙ አሕዛብና
ክርስቲያኖች ተሰብስበው ነበር::
እርሱ በከተማዋ ዝነኛ ነበር:: ሥርዓቱ ሁሉ ተደርሶ ቅዱሱ
ወደ ውሃ ገንዳው ሲገባ ሁሉ እያዩ የብርሃን ምሰሶ ከሰማይ
ወረደ:: ይህንን በገሃድ የተመለከቱ ከ10,000 በላይ አሕዛብ
ወዲያውኑ በክርስቶስ አምነው አብረውት ተጠምቀዋል::
ቅዱስ እንጣዎስ ከዚህ በሁዋላ ምስጉን ክርስቲያን ሆነ::
ስለ ቀደመ ሕይወቱ ፈንታ ጾምን: ጸሎትን: ፍቅርን: ምጽዋትን
ገንዘብ አደረገ:: ሕይወቱም ለብዙ ሰዎች መስታውት ሆነ::
#እመቤታችን ድንግል ማርያምንም ይወዳት ነበርና ወደ
ቅዱሳን ማሕበር ( #ኢየሩሳሌም ) ወስዳው በሥጋዊ አንደበት
ተከናውኖ ሊነገር የማይቻል ምሥጢርን ገልጣለታለች::
እነዚህን የቅድስና ጊዜያት በስኬት ያሳለፈው ቅዱስ
እንጣዎስ መጨረሻው ሰማዕትነት ሆነ:: አረማውያን ወገኖቹና ቀድሞ የሚያውቁት ወደ ቀደመ ክፋትና
ክህደት እንዲመለስ ጠየቁት:: "አይሆንም" አላቸው::
በአደባባይ ለፍርድ አቅርበው ደሙ እስኪፈስ ገረፉት::
ጥርሶቹን በሙሉ በድንጋይ አረገፏቸው:: ደሙና ጥርሶቹ
መሬት ላይ ተዘሩ:: ነገር ግን ይሕ ስቃይ ቅዱሱን ከፍቅረ
ክርስቶስ ሊለየው አልቻለም:: አሕዛብም ተስፋ ቆርጠው
በዚህች ቀን ገድለውታል:: ቅዱስ እንጣዎስም ከሁዋለኛው
ዘመን #ሰማዕታት እንደ አንዱ ተቆጥሯል::