ድንግል ማርያም አምላክ ልጇን አዝላ ስደት ወጥታ
ምድረ ግብፅ ትደርሳለች:: በወቅቱ ከደረሱባት ችግሮች
አንዱ ደግሞ ረሃብና ጽሙ ነበር:: እንኩዋን ለስደተኛ በቤቱ
ላለም ረሃብና ጥም እንዴት እንደሚከብድ የደረሰበት
ያውቀዋል::
ታዲያ አንድ ቀን የበርሃው ፀሐይ አቃጥሏቸው ባረፉበት
ድንግል እመቤታችን ውሃ ልመና ወጣች:: ብዙ ለመነች :
ግን ጥርኝ እንኩዋ የሚሠጣት አጥታ በሐዘን ተመለሰች::
ስትመለስ ግን ይባስ ብሎ የልጇን ጫማ ሽፍቶች
ወስደውት ደረሰች::
ያን ጊዜ ልጇን ታቅፋ "ውሃ ሳላገኝልሕ : ጫማሕንም
አሰረቅኩብህ" ብላ ምርር ብላ አልቅሳለች::
ይሕንን የተመለከተ ልጇ የቆመችበትን መሬት ቢባርከው
ሕይወትነት ያለው ማይ (ጸበል) ፈለቀ:: # ጌታችን :
#እመቤታችን : #ዮሴፍና_ሰሎሜ ከውሃው ጠጥተጠዋል::
ሲሔዱ ግን ለእንግዶች ጣፋጭ (መድኃኒት) :
ለአካባቢው ሰዎች ግን መራራ ሁኗል::
ከመቶዎች ዓመታት በሁዋላም ጌታ ጸበል ያፈለቀበት :
ድንግል እመቤታችን የቆመችበት ቦታ ላይ በእመ ብርሃን
ስም #ቤተ_ክርስቲያን ታንጿል:: ቅዳሴ ቤቱም ተከብሯል::
ጸበሉም ሲባርክና ሲፈውስ ይኖራል::
ምድረ ግብፅ ትደርሳለች:: በወቅቱ ከደረሱባት ችግሮች
አንዱ ደግሞ ረሃብና ጽሙ ነበር:: እንኩዋን ለስደተኛ በቤቱ
ላለም ረሃብና ጥም እንዴት እንደሚከብድ የደረሰበት
ያውቀዋል::
ታዲያ አንድ ቀን የበርሃው ፀሐይ አቃጥሏቸው ባረፉበት
ድንግል እመቤታችን ውሃ ልመና ወጣች:: ብዙ ለመነች :
ግን ጥርኝ እንኩዋ የሚሠጣት አጥታ በሐዘን ተመለሰች::
ስትመለስ ግን ይባስ ብሎ የልጇን ጫማ ሽፍቶች
ወስደውት ደረሰች::
ያን ጊዜ ልጇን ታቅፋ "ውሃ ሳላገኝልሕ : ጫማሕንም
አሰረቅኩብህ" ብላ ምርር ብላ አልቅሳለች::
ይሕንን የተመለከተ ልጇ የቆመችበትን መሬት ቢባርከው
ሕይወትነት ያለው ማይ (ጸበል) ፈለቀ:: # ጌታችን :
#እመቤታችን : #ዮሴፍና_ሰሎሜ ከውሃው ጠጥተጠዋል::
ሲሔዱ ግን ለእንግዶች ጣፋጭ (መድኃኒት) :
ለአካባቢው ሰዎች ግን መራራ ሁኗል::
ከመቶዎች ዓመታት በሁዋላም ጌታ ጸበል ያፈለቀበት :
ድንግል እመቤታችን የቆመችበት ቦታ ላይ በእመ ብርሃን
ስም #ቤተ_ክርስቲያን ታንጿል:: ቅዳሴ ቤቱም ተከብሯል::
ጸበሉም ሲባርክና ሲፈውስ ይኖራል::