♥እንኩዋን ለሰማዕቱ ቅዱስ #አብሮኮሮንዮስ እና ለመነኮሳት አለቃ #ቅዱስ_መቃርስ ዓመታዊ በዓል በሰላም
አደረሳችሁ♥
✝+ ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ሰማዕት +✝
ቅዱሱ ተወልዶ ያደገው በአንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው መቶ
ክ/ዘመን አካባቢ ነው:: አባቱ ደግ ክርስቲያን የነበረ ሲሆን
ስሙ #ክርስቶፎሮስ ይባላል:: "ለባሴ ክርስቶስ" እንደ ማለት
ነው:: እናቱ ግን #ቴዎዳስያ የምትባል አረማዊት ነበረች::
ምንም እንኩዋ አባቱ ክርስቲያን ቢሆን እናቱ ኃይለኛ የቤተ
መንግስት ሰው ስለነበረች በልጅነቱ አብሮኮሮንዮስ ክርስትናን
ሊማር አልቻለም::
የልጁን አረማዊ መሆን ያልወደደ አባት አማራጩ አንድ ብቻ
ነበር:: እሱም ወደ ጌታ መለመን ነበር:: በእንዲሕ ያለ ግብር
ዘመናት ጐርፈው አብሮኮሮንዮስ ክርስቶስን ሳያውቅ 20
ዓመት ሆነው:: እናቱ ወስዳ: አሰልጥና ለጣዖት አምላኪ
ንጉሥ ሰጠችው:: ንጉሡም የጦር አለቃ አድርጐ ሾመውና
አንድ ትዕዛዝ ሰጠው:: "ክርስቲያኖችን ሁሉ ባገኘህበት ቦታ ጨፍጭፍ:: ቤታቸውንም አቃጥል::" #አብሮኮሮንዮስ የታዘዘውን ሊፈጽም ሠራዊት አስከትሎ ሲወጣ ግን የአባቱ የ20 ዘመናት ለቅሶና ጸሎት ፍሬ አፈራ::
ገና መንገድ ላይ ሳለ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና
መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ድምጹን ከሰማይ ላከለት::
"ወደ እውነተኛ መንገድ ተመለስ:: ካልሆነ ግን ሾተሉን
ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል" አለው:: አብሮኮሮንዮስም እየተንቀጠቀጠ "አቤቱ አንተ ማነህ?" አለው:: ጌታም "ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ" ሲል መለሰለት::
ዳግመኛም "ምልክት ስጠኝ" ቢለው የብርሃን #መስቀል
በሰማይ ላይ ገለጠለት:: ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ጊዜ
አላጠፋም:: ሠራዊቱን ይዞ ወደ ንጉሡ ከተማ ተመልሶ ንጉሡን በድፍረት አለው:- "እኔ ክርስቲያን ነኝ:: ክርስቶስንም አመልካለሁ::"
ካነጋገሩ የተነሳ አባቱን ደስ ሲለው ንጉሡና እናቱ ግን ደነገጡ::
ንጉሡ ሊያስፈራራው ሞከረ:: ግን አልተሳካለትም:: ከዚያማ
ያሰቃየው ገባ:: አንድ ቀን አካሉ እስኪቆራረጥ ገረፉት:: በእሳትም
አቃጠሉት:: ሞተ ብለው አስበው ነበር:: ወደ እርሱ ሲመለሱ
ግን ጌታችን አድኖታልና የሰንበር ምልክት እንኩዋ በአካሉ ላይ
አልተገኘም:: እናቱ #ቴዎዳስያ ከዚህ በላይ ምልክትን
አልፈለገችም:: በደቂቃዎች ልዩነት እርሷም ወደ #ክርስትና
ተመለሰች:: ልጇንም ቀድማ ሐምሌ 6 ቀን ሰማዕት ሆነች::
+ቅዱስ አብሮኮርዮስን ግን ለበርካታ ጊዜያት አሰቃይተው
ከክርስቶስ ፍቅር ሊለዩት ባለመቻላቸው በዚህች ቀን
ገድለውታል:: አባት: እናትና ልጅ (ክርስቶፎሮስ: ቴዎዳስያና
አብሮኮሮንዮስ) ለሰማያዊ ርስት በቅተዋል:: አባት ይሏቹሃል
እንዲህ ነው!
አደረሳችሁ♥
✝+ ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ሰማዕት +✝
ቅዱሱ ተወልዶ ያደገው በአንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው መቶ
ክ/ዘመን አካባቢ ነው:: አባቱ ደግ ክርስቲያን የነበረ ሲሆን
ስሙ #ክርስቶፎሮስ ይባላል:: "ለባሴ ክርስቶስ" እንደ ማለት
ነው:: እናቱ ግን #ቴዎዳስያ የምትባል አረማዊት ነበረች::
ምንም እንኩዋ አባቱ ክርስቲያን ቢሆን እናቱ ኃይለኛ የቤተ
መንግስት ሰው ስለነበረች በልጅነቱ አብሮኮሮንዮስ ክርስትናን
ሊማር አልቻለም::
የልጁን አረማዊ መሆን ያልወደደ አባት አማራጩ አንድ ብቻ
ነበር:: እሱም ወደ ጌታ መለመን ነበር:: በእንዲሕ ያለ ግብር
ዘመናት ጐርፈው አብሮኮሮንዮስ ክርስቶስን ሳያውቅ 20
ዓመት ሆነው:: እናቱ ወስዳ: አሰልጥና ለጣዖት አምላኪ
ንጉሥ ሰጠችው:: ንጉሡም የጦር አለቃ አድርጐ ሾመውና
አንድ ትዕዛዝ ሰጠው:: "ክርስቲያኖችን ሁሉ ባገኘህበት ቦታ ጨፍጭፍ:: ቤታቸውንም አቃጥል::" #አብሮኮሮንዮስ የታዘዘውን ሊፈጽም ሠራዊት አስከትሎ ሲወጣ ግን የአባቱ የ20 ዘመናት ለቅሶና ጸሎት ፍሬ አፈራ::
ገና መንገድ ላይ ሳለ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና
መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ድምጹን ከሰማይ ላከለት::
"ወደ እውነተኛ መንገድ ተመለስ:: ካልሆነ ግን ሾተሉን
ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል" አለው:: አብሮኮሮንዮስም እየተንቀጠቀጠ "አቤቱ አንተ ማነህ?" አለው:: ጌታም "ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ" ሲል መለሰለት::
ዳግመኛም "ምልክት ስጠኝ" ቢለው የብርሃን #መስቀል
በሰማይ ላይ ገለጠለት:: ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ጊዜ
አላጠፋም:: ሠራዊቱን ይዞ ወደ ንጉሡ ከተማ ተመልሶ ንጉሡን በድፍረት አለው:- "እኔ ክርስቲያን ነኝ:: ክርስቶስንም አመልካለሁ::"
ካነጋገሩ የተነሳ አባቱን ደስ ሲለው ንጉሡና እናቱ ግን ደነገጡ::
ንጉሡ ሊያስፈራራው ሞከረ:: ግን አልተሳካለትም:: ከዚያማ
ያሰቃየው ገባ:: አንድ ቀን አካሉ እስኪቆራረጥ ገረፉት:: በእሳትም
አቃጠሉት:: ሞተ ብለው አስበው ነበር:: ወደ እርሱ ሲመለሱ
ግን ጌታችን አድኖታልና የሰንበር ምልክት እንኩዋ በአካሉ ላይ
አልተገኘም:: እናቱ #ቴዎዳስያ ከዚህ በላይ ምልክትን
አልፈለገችም:: በደቂቃዎች ልዩነት እርሷም ወደ #ክርስትና
ተመለሰች:: ልጇንም ቀድማ ሐምሌ 6 ቀን ሰማዕት ሆነች::
+ቅዱስ አብሮኮርዮስን ግን ለበርካታ ጊዜያት አሰቃይተው
ከክርስቶስ ፍቅር ሊለዩት ባለመቻላቸው በዚህች ቀን
ገድለውታል:: አባት: እናትና ልጅ (ክርስቶፎሮስ: ቴዎዳስያና
አብሮኮሮንዮስ) ለሰማያዊ ርስት በቅተዋል:: አባት ይሏቹሃል
እንዲህ ነው!
♥እንኩዋን ለጌታችን ቅዱስ #ዕፀ_መስቀል የተአምር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ♥
✝ #ቅዱስ_ዕፀ_መስቀል +"+
የዕፀዋት ሁሉ ንጉሣቸው የሚሆን ቅዱስ ዕፀ መስቀል
ለእኛም #ኃይላችን: #ቤዛችን: #መዳኛችን: #የድል_
ምልክታችን ነው:: መስቀል #በደመ_ክርስቶስ ተቀድሷልና
አንክሮ: ስግደት ክብርና ምስጋና በፀጋ ይገባዋል::
#ቅዱስ_መስቀለ_ክርስቶስ ላለፉት 2,000 ዓመታት ብዙ
ተአምራትን ሠርቷል:: ከእነዚህ መካከልም አንዱን በዚህ
ዕለት እናዘክራለን:: ታሪኩ: ምሥጢሩስ እንደ ምን ነው
ቢሉ:- በ400 ዓ/ም አካባቢ በግብፅ #አባ_ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ
ሳለ: #ቅዱስ_ቄርሎስም በሊቀ ዲቁና ሲያገለግል ሳለ
በእስክንድርያ ከተማ 2 ደሃ ክርስቲያኖች ይኖሩ ነበር:: የቀን
ሠራተኞች በመሆናቸው ከዕለት ምግብ አይተርፋቸውም
ነበር::
ከ2ቱ አንዱ ፍጹም አማኝ ሲሆን ሌላኛው ግን ተጠራጣሪ
ነበር:: ስለ ምን ነው ቢሉ:- በከተማዋ ብዙ ሃብታም አይሁድ
ነበሩና እነሱን እየተመለከተ ነው:: ለእርሱ #ክርስትና ማለት
ገንዘብ መስሎታልና ዘወትር "ለምን ክርስቶስን እያመለክን ድሃ
እንሆናለን?" እያለ ያማርር ነበር::
"ያዛቆነ ሰይጣን . . . " እንደሚባለው አንድ ቀን ባልጀራውን "ለምን ክርስቶስን አንክደውም? (ሎቱ ስብሐት!) እርሱን ከማምለክ የተረፈን ድህነት ብቻ ነው" አለው:: ባልንጀራው ሊመክረው ሞከረ:-
"እግዚአብሔር አምላከ-ነዳያን ነው:: ቅዱሳን #ነቢያት :
#ሐዋርያት : #ጻድቃን: #ሰማዕታትም በሥጋዊ ሃብት ነዳያን
ነበሩ" ብሎ ቢለውም ሰይጣን ሠልጥኖበታልና
አልሰማውም:: ያ ስሑት ደሃ ወዲያው ወጥቶ ወደ ማሕበረ አይሁድ ሔደ::
እነርሱ በቁጥር ብዙ ሁነው በአንድነት ይኖሩ ነበር::
"ሥራ ቅጠሩኝ" አላቸው:: "በእምነት አትመስለንምና
አይሆንም" አሉት:: ያን ጊዜ ለአለቃቸው ( #ፈለስኪኖስ)
"አንተ ሥራ ቅጠረኝ እንጂ እኔ ክርስቶስን እክዳለሁ" (ሎቱ
ስብሐት!) አለው::
ወዲያው የከተማው ሕዝብ ተጠርቶ: በጉባኤ መካከል
ሊያስክዱት ተዘጋጁ:: በፍጥነትም #መስቀል: ጦር: ሐሞት
አዘጋጁ:: ስዕለ ስቅለቱንም አመጡ:: ያን ደሃ ከሃዲም
"በል-ክርስቶስ ሆይ! ካድኩህ ብለህ ምራቅህን ትፋበት:
ሐሞቱን አፍስበት: በጦርም ውጋው" (ሎቱ ስብሐት!)
አሉት::
ያ ልቡ የደነቆረ መስቀለ ክርስቶስ ላይ ተፋ:: ሐሞትም
አፈሰሰበት:: በመጨረሻ በጦር ሲወጋው ግን ድንቅ ተአምር
ተገለጠ:: በጦር ከተወጋው ከመስቀሉ ጐን ብዙ ደም
ፈሰሰ:: ለረዥም ሰዓትም አላቁዋረጠም:: በዚህች ሰዓት
በአካባቢው የነበሩ ሁሉም አይሁድ በግንባራቸው ተደፍተው
ለክርስቶስና ቅዱስ መስቀሉ ሰገዱ::
ሁሉም በአንድነት "#ክርስቶስ_የአብርሃም_አምላክ_ነው
:: #መድኃኒትም_ነው " ሲሉ እየጮሁ ተናገሩ:: ባለማወቅ
ስላደረጉት እነርሱ ምሕረትን ሲያገኙ ያ አዕምሮ የጐደለውን
ደሃ ግን ዘወር ብለው ሲያዩት ወደ ድንጋይነት ተቀይሮ ነበር::
ነፍሱንም: ሥጋውንም በፈቃዱ አጠፋ::
የአይሁድ አለቃም ዐይነ ሥውር ዘመድ ነበረውና ወዲያው
አምጥቶ ከደሙ ቢቀባው ዐይኑ በራ:: ታላቅ ደስታም በዚያ
ሥፍራ ተደረገ:: ነገሩን የሰሙት #ቅዱሳን #ቴዎፍሎስ እና
#ቄርሎስ ሲመጡ ደሙ ከመፍሰስ አላቆመም ነበር::
በተአምሩ ደስ ተሰኝተው: ከደመ ክርስቶስ ለበረከት ተቀቡ::
የፈሰሰውን #ቅዱስ_ደም ከነ አፈሩ አንስተው: መስቀሉን
በትከሻ ተሸክመው: በፍፁም እልልታና ዝማሬ ወስደው በቤተ
መቅደስ አኑረውታል:: የከተማዋ ሁሉም አይሁድም
በክርስቶስ አምነው ተጠምቀዋል::
✝ #ቅዱስ_ዕፀ_መስቀል +"+
የዕፀዋት ሁሉ ንጉሣቸው የሚሆን ቅዱስ ዕፀ መስቀል
ለእኛም #ኃይላችን: #ቤዛችን: #መዳኛችን: #የድል_
ምልክታችን ነው:: መስቀል #በደመ_ክርስቶስ ተቀድሷልና
አንክሮ: ስግደት ክብርና ምስጋና በፀጋ ይገባዋል::
#ቅዱስ_መስቀለ_ክርስቶስ ላለፉት 2,000 ዓመታት ብዙ
ተአምራትን ሠርቷል:: ከእነዚህ መካከልም አንዱን በዚህ
ዕለት እናዘክራለን:: ታሪኩ: ምሥጢሩስ እንደ ምን ነው
ቢሉ:- በ400 ዓ/ም አካባቢ በግብፅ #አባ_ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ
ሳለ: #ቅዱስ_ቄርሎስም በሊቀ ዲቁና ሲያገለግል ሳለ
በእስክንድርያ ከተማ 2 ደሃ ክርስቲያኖች ይኖሩ ነበር:: የቀን
ሠራተኞች በመሆናቸው ከዕለት ምግብ አይተርፋቸውም
ነበር::
ከ2ቱ አንዱ ፍጹም አማኝ ሲሆን ሌላኛው ግን ተጠራጣሪ
ነበር:: ስለ ምን ነው ቢሉ:- በከተማዋ ብዙ ሃብታም አይሁድ
ነበሩና እነሱን እየተመለከተ ነው:: ለእርሱ #ክርስትና ማለት
ገንዘብ መስሎታልና ዘወትር "ለምን ክርስቶስን እያመለክን ድሃ
እንሆናለን?" እያለ ያማርር ነበር::
"ያዛቆነ ሰይጣን . . . " እንደሚባለው አንድ ቀን ባልጀራውን "ለምን ክርስቶስን አንክደውም? (ሎቱ ስብሐት!) እርሱን ከማምለክ የተረፈን ድህነት ብቻ ነው" አለው:: ባልንጀራው ሊመክረው ሞከረ:-
"እግዚአብሔር አምላከ-ነዳያን ነው:: ቅዱሳን #ነቢያት :
#ሐዋርያት : #ጻድቃን: #ሰማዕታትም በሥጋዊ ሃብት ነዳያን
ነበሩ" ብሎ ቢለውም ሰይጣን ሠልጥኖበታልና
አልሰማውም:: ያ ስሑት ደሃ ወዲያው ወጥቶ ወደ ማሕበረ አይሁድ ሔደ::
እነርሱ በቁጥር ብዙ ሁነው በአንድነት ይኖሩ ነበር::
"ሥራ ቅጠሩኝ" አላቸው:: "በእምነት አትመስለንምና
አይሆንም" አሉት:: ያን ጊዜ ለአለቃቸው ( #ፈለስኪኖስ)
"አንተ ሥራ ቅጠረኝ እንጂ እኔ ክርስቶስን እክዳለሁ" (ሎቱ
ስብሐት!) አለው::
ወዲያው የከተማው ሕዝብ ተጠርቶ: በጉባኤ መካከል
ሊያስክዱት ተዘጋጁ:: በፍጥነትም #መስቀል: ጦር: ሐሞት
አዘጋጁ:: ስዕለ ስቅለቱንም አመጡ:: ያን ደሃ ከሃዲም
"በል-ክርስቶስ ሆይ! ካድኩህ ብለህ ምራቅህን ትፋበት:
ሐሞቱን አፍስበት: በጦርም ውጋው" (ሎቱ ስብሐት!)
አሉት::
ያ ልቡ የደነቆረ መስቀለ ክርስቶስ ላይ ተፋ:: ሐሞትም
አፈሰሰበት:: በመጨረሻ በጦር ሲወጋው ግን ድንቅ ተአምር
ተገለጠ:: በጦር ከተወጋው ከመስቀሉ ጐን ብዙ ደም
ፈሰሰ:: ለረዥም ሰዓትም አላቁዋረጠም:: በዚህች ሰዓት
በአካባቢው የነበሩ ሁሉም አይሁድ በግንባራቸው ተደፍተው
ለክርስቶስና ቅዱስ መስቀሉ ሰገዱ::
ሁሉም በአንድነት "#ክርስቶስ_የአብርሃም_አምላክ_ነው
:: #መድኃኒትም_ነው " ሲሉ እየጮሁ ተናገሩ:: ባለማወቅ
ስላደረጉት እነርሱ ምሕረትን ሲያገኙ ያ አዕምሮ የጐደለውን
ደሃ ግን ዘወር ብለው ሲያዩት ወደ ድንጋይነት ተቀይሮ ነበር::
ነፍሱንም: ሥጋውንም በፈቃዱ አጠፋ::
የአይሁድ አለቃም ዐይነ ሥውር ዘመድ ነበረውና ወዲያው
አምጥቶ ከደሙ ቢቀባው ዐይኑ በራ:: ታላቅ ደስታም በዚያ
ሥፍራ ተደረገ:: ነገሩን የሰሙት #ቅዱሳን #ቴዎፍሎስ እና
#ቄርሎስ ሲመጡ ደሙ ከመፍሰስ አላቆመም ነበር::
በተአምሩ ደስ ተሰኝተው: ከደመ ክርስቶስ ለበረከት ተቀቡ::
የፈሰሰውን #ቅዱስ_ደም ከነ አፈሩ አንስተው: መስቀሉን
በትከሻ ተሸክመው: በፍፁም እልልታና ዝማሬ ወስደው በቤተ
መቅደስ አኑረውታል:: የከተማዋ ሁሉም አይሁድም
በክርስቶስ አምነው ተጠምቀዋል::
#ቅዱስ_ዕፀ_መስቀል
ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ቸር አምላካችንና
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ከሰማያዊ
ክብሩ ወደ ምድር ወርዶ: በማሕጸነ #ማርያም_እግዝእት
በኪነ ጥበቡ ተጸንሶ: በኅቱም ድንግልና ተወልዶ: በፈቃዱ
መከራ መስቀልን ተቀብሎ:
✝ከግራ ቁመት:
✝ከገሃነመ እሳት:
✝ከሰይጣን ባርነት:
✝ከኃጢአት ቁራኝነትም አድኖናል::
✔ እምእቶነ እሳት ዘይነድድ አንገፈነ ✔ እንዳለ
ሊቁ::
✝ምንም መስቀል በብሉይ የወንጀለኞች መቅጫ ሆኖ
ቢቆይም እግዚአብሔር ለዓለም መዳኛነት የመረጠው
ነውና ሕብረ ትንቢቶች ሲነገሩለት: በብዙ ሕብረ
አምሳልም ሲመሰል ኑሯል:: ከተፈጥሯችን ጀምሮ ዓለም
ራሷ አርአያ #ትዕምርተ_መስቀል ናት::
✝እግዚአብሔር ለቃየን እንዳይገድሉት ከሰጠው ምልክት
(ዘፍ. 4:15) ጀምሮ
✝ #ይስሐቅ ሊሰዋ የተሸከመው እንጨት (ዘፍ. 22:6):
✝ #ቅዱስ_ያዕቆብ ያያት የወርቅ መሰላል (ዘፍ. 28:12):
✝ያዕቆብ የዮሴፍን ልጆች የባረከበት መንገድ (ዘፍ.
48:14):
✝ባሕረ ኤርትራን የከፈለችው #የሙሴ_በትር (ዘጸ.
14:15):
✝ # የናሱ_ዕባብ የተሰቀለበት እንጨት (ዘኁ. 21:8)
ጨምሮ በርካታ ምሳሌዎች ለቅዱስ መስቀሉ
መኖራቸውን መተርጉማን ተናግረዋል::
✝ # ቅዱስ_ዳዊትን የመሰሉ ነቢያት ደግሞ "ለሚፈሩሕ
ከቀስት ያመልጡ ዘንድ ምልክትን ሰጠሃቸው" እያሉ
መስቀሉን ከርቀት ተመልክተዋል:: (መዝ. 59:4)
✝በሐዲስ ኪዳን ግን ምሳሌው ገሃድ ሆኖ: ጌታ በዕፀ
መስቀል ላይ ተሰቅሎ ሥጋውን ቆረሰበት: ደሙን
አፈሰሰበት: ዓለምንም አዳነበት::
ስለዚህም "#መስቀል_ብርሃን_ለኩሉ_ዓለም :
#መሠረተ_ቤተ_ክርስቲያን " ተብሎ የሚመሰገን ሆኗል::
✝ #ቅዱስ_ያሬድ ሊቁ አክሎ "መስቀል መልዕልተ ኩሉ
ነገር: ያድኅነነ እምጸር" ብሎ ጠላትን ማሳፈሪያ መሆኑን
ይነግረናል:: #ብርሃነ_ዓለም #ቅዱስ_ዻውሎስም ስለ
መስቀሉ አምልቶ አጉልቶ አስተምሯል:: መመኪያችን
ነውና:: (1ቆሮ. 1:18, ገላ. 6:14)
✝አንዳንዶቹ እኛን 'የተሰቀለውን ትታቹሃል' ይሉናል::
የተሰቀለውማ የጌቶች ጌታ: የነገሥታት ንጉሥ:
የአማልክት አምላክ: ሁሉ በእጁ የተያዘ:
#ኢየሱስ_ክርስቶስ ነውና ከኦርቶዶክስ በላይ የሚያመልክ
በወዴት አለና::
✝ነገር ግን መስቀሉን ንቆ የተሰቀለውን ማክበር
አይቻልምና እኛ ለመስቀሉ የጸጋ ስግደትን እንሰግዳለን:
እናመሰግነዋለን: እናከብረዋለን: ቤዛ: ጽንዕ: መድኃኒት:
ኃይል እያልንም እንጠራዋለን:: አባቶቻችን በመስቀሉ
ምርኩዝነት ማዕበለ ኃጢአትን: ባሕረ እሳትን
ተሻግረዋል::
✝በመስቀሉ ቢመኩ አጋንንትን ድል ነስተዋል:: ጠላትንም
አሳፍረዋል:: እኛም በመስቀሉ አምነን ከብረን: ገነን
እንኖራለን:: ተጠቅመንበታልና ከራሳችን ሕይወት በላይ
ምስክርን አንፈልግም::
ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ቸር አምላካችንና
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ከሰማያዊ
ክብሩ ወደ ምድር ወርዶ: በማሕጸነ #ማርያም_እግዝእት
በኪነ ጥበቡ ተጸንሶ: በኅቱም ድንግልና ተወልዶ: በፈቃዱ
መከራ መስቀልን ተቀብሎ:
✝ከግራ ቁመት:
✝ከገሃነመ እሳት:
✝ከሰይጣን ባርነት:
✝ከኃጢአት ቁራኝነትም አድኖናል::
✔ እምእቶነ እሳት ዘይነድድ አንገፈነ ✔ እንዳለ
ሊቁ::
✝ምንም መስቀል በብሉይ የወንጀለኞች መቅጫ ሆኖ
ቢቆይም እግዚአብሔር ለዓለም መዳኛነት የመረጠው
ነውና ሕብረ ትንቢቶች ሲነገሩለት: በብዙ ሕብረ
አምሳልም ሲመሰል ኑሯል:: ከተፈጥሯችን ጀምሮ ዓለም
ራሷ አርአያ #ትዕምርተ_መስቀል ናት::
✝እግዚአብሔር ለቃየን እንዳይገድሉት ከሰጠው ምልክት
(ዘፍ. 4:15) ጀምሮ
✝ #ይስሐቅ ሊሰዋ የተሸከመው እንጨት (ዘፍ. 22:6):
✝ #ቅዱስ_ያዕቆብ ያያት የወርቅ መሰላል (ዘፍ. 28:12):
✝ያዕቆብ የዮሴፍን ልጆች የባረከበት መንገድ (ዘፍ.
48:14):
✝ባሕረ ኤርትራን የከፈለችው #የሙሴ_በትር (ዘጸ.
14:15):
✝ # የናሱ_ዕባብ የተሰቀለበት እንጨት (ዘኁ. 21:8)
ጨምሮ በርካታ ምሳሌዎች ለቅዱስ መስቀሉ
መኖራቸውን መተርጉማን ተናግረዋል::
✝ # ቅዱስ_ዳዊትን የመሰሉ ነቢያት ደግሞ "ለሚፈሩሕ
ከቀስት ያመልጡ ዘንድ ምልክትን ሰጠሃቸው" እያሉ
መስቀሉን ከርቀት ተመልክተዋል:: (መዝ. 59:4)
✝በሐዲስ ኪዳን ግን ምሳሌው ገሃድ ሆኖ: ጌታ በዕፀ
መስቀል ላይ ተሰቅሎ ሥጋውን ቆረሰበት: ደሙን
አፈሰሰበት: ዓለምንም አዳነበት::
ስለዚህም "#መስቀል_ብርሃን_ለኩሉ_ዓለም :
#መሠረተ_ቤተ_ክርስቲያን " ተብሎ የሚመሰገን ሆኗል::
✝ #ቅዱስ_ያሬድ ሊቁ አክሎ "መስቀል መልዕልተ ኩሉ
ነገር: ያድኅነነ እምጸር" ብሎ ጠላትን ማሳፈሪያ መሆኑን
ይነግረናል:: #ብርሃነ_ዓለም #ቅዱስ_ዻውሎስም ስለ
መስቀሉ አምልቶ አጉልቶ አስተምሯል:: መመኪያችን
ነውና:: (1ቆሮ. 1:18, ገላ. 6:14)
✝አንዳንዶቹ እኛን 'የተሰቀለውን ትታቹሃል' ይሉናል::
የተሰቀለውማ የጌቶች ጌታ: የነገሥታት ንጉሥ:
የአማልክት አምላክ: ሁሉ በእጁ የተያዘ:
#ኢየሱስ_ክርስቶስ ነውና ከኦርቶዶክስ በላይ የሚያመልክ
በወዴት አለና::
✝ነገር ግን መስቀሉን ንቆ የተሰቀለውን ማክበር
አይቻልምና እኛ ለመስቀሉ የጸጋ ስግደትን እንሰግዳለን:
እናመሰግነዋለን: እናከብረዋለን: ቤዛ: ጽንዕ: መድኃኒት:
ኃይል እያልንም እንጠራዋለን:: አባቶቻችን በመስቀሉ
ምርኩዝነት ማዕበለ ኃጢአትን: ባሕረ እሳትን
ተሻግረዋል::
✝በመስቀሉ ቢመኩ አጋንንትን ድል ነስተዋል:: ጠላትንም
አሳፍረዋል:: እኛም በመስቀሉ አምነን ከብረን: ገነን
እንኖራለን:: ተጠቅመንበታልና ከራሳችን ሕይወት በላይ
ምስክርን አንፈልግም::
💚💛ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ሰማዕት 💛❤️
ቅዱሱ ተወልዶ ያደገው በአንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው
መቶ ክ/ዘመን አካባቢ ነው:: አባቱ ደግ ክርስቲያን የነበረ
ሲሆን ስሙ #ክርስቶፎሮስ ይባላል:: "ለባሴ ክርስቶስ" እንደ
ማለት ነው:: እናቱ ግን #ቴዎዳስያ የምትባል አረማዊት ነበረች:: ምንም እንኩዋ አባቱ ክርስቲያን ቢሆን እናቱ ኃይለኛ የቤተ መንግስት ሰው ስለነበረች በልጅነቱ አብሮኮሮንዮስ
ክርስትናን ሊማር አልቻለም::
የልጁን አረማዊ መሆን ያልወደደ አባት አማራጩ አንድ ብቻ
ነበር:: እሱም ወደ ጌታ መለመን ነበር:: በእንዲሕ ያለ ግብር
ዘመናት ጐርፈው አብሮኮሮንዮስ ክርስቶስን ሳያውቅ 20
ዓመት ሆነው:: እናቱ ወስዳ: አሰልጥና ለጣዖት አምላኪ
ንጉሥ ሰጠችው:: ንጉሡም የጦር አለቃ አድርጐ ሾመውና አንድ ትዕዛዝ ሰጠው:: "ክርስቲያኖችን ሁሉ ባገኘህበት ቦታ ጨፍጭፍ:: ቤታቸውንም አቃጥል::"
#አብሮኮሮንዮስ የታዘዘውን ሊፈጽም ሠራዊት አስከትሎ
ሲወጣ ግን የአባቱ የ20 ዘመናት ለቅሶና ጸሎት ፍሬ አፈራ::
ገና መንገድ ላይ ሳለ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና
መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ድምጹን ከሰማይ ላከለት:: "ወደ እውነተኛ መንገድ ተመለስ:: ካልሆነ ግን ሾተሉን ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል" አለው::
አብሮኮሮንዮስም እየተንቀጠቀጠ "አቤቱ አንተ ማነህ?" አለው:: ጌታም "ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ" ሲል መለሰለት:: ዳግመኛም "ምልክት ስጠኝ" ቢለው የብርሃን #መስቀል በሰማይ ላይ ገለጠለት:: ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ጊዜ አላጠፋም:: ሠራዊቱን ይዞ ወደ ንጉሡ ከተማ ተመልሶ ንጉሡን በድፍረት
አለው:- "እኔ ክርስቲያን ነኝ:: ክርስቶስንም አመልካለሁ::"
ካነጋገሩ የተነሳ አባቱን ደስ ሲለው ንጉሡና እናቱ ግን ደነገጡ:: ንጉሡ ሊያስፈራራው ሞከረ:: ግን
አልተሳካለትም:: ከዚያማ ያሰቃየው ገባ:: አንድ ቀን አካሉ እስኪቆራረጥ ገረፉት:: በእሳትም
አቃጠሉት:: ሞተ ብለው አስበው ነበር:: ወደ እርሱ ሲመለሱ
ግን ጌታችን አድኖታልና የሰንበር ምልክት እንኩዋ በአካሉ ላይ
አልተገኘም:: እናቱ #ቴዎዳስያ ከዚህ በላይ ምልክትን
አልፈለገችም:: በደቂቃዎች ልዩነት እርሷም ወደ #ክርስትና
ተመለሰች:: ልጇንም ቀድማ ሐምሌ 6 ቀን ሰማዕት ሆነች::
ቅዱስ አብሮኮርዮስን ግን ለበርካታ ጊዜያት አሰቃይተው
ከክርስቶስ ፍቅር ሊለዩት ባለመቻላቸው በዚህች ቀን
ገድለውታል:: አባት: እናትና ልጅ (ክርስቶፎሮስ: ቴዎዳስያና
አብሮኮሮንዮስ) ለሰማያዊ ርስት በቅተዋል:: አባት ይሏቹሃል
እንዲህ ነው!
ቅዱሱ ተወልዶ ያደገው በአንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው
መቶ ክ/ዘመን አካባቢ ነው:: አባቱ ደግ ክርስቲያን የነበረ
ሲሆን ስሙ #ክርስቶፎሮስ ይባላል:: "ለባሴ ክርስቶስ" እንደ
ማለት ነው:: እናቱ ግን #ቴዎዳስያ የምትባል አረማዊት ነበረች:: ምንም እንኩዋ አባቱ ክርስቲያን ቢሆን እናቱ ኃይለኛ የቤተ መንግስት ሰው ስለነበረች በልጅነቱ አብሮኮሮንዮስ
ክርስትናን ሊማር አልቻለም::
የልጁን አረማዊ መሆን ያልወደደ አባት አማራጩ አንድ ብቻ
ነበር:: እሱም ወደ ጌታ መለመን ነበር:: በእንዲሕ ያለ ግብር
ዘመናት ጐርፈው አብሮኮሮንዮስ ክርስቶስን ሳያውቅ 20
ዓመት ሆነው:: እናቱ ወስዳ: አሰልጥና ለጣዖት አምላኪ
ንጉሥ ሰጠችው:: ንጉሡም የጦር አለቃ አድርጐ ሾመውና አንድ ትዕዛዝ ሰጠው:: "ክርስቲያኖችን ሁሉ ባገኘህበት ቦታ ጨፍጭፍ:: ቤታቸውንም አቃጥል::"
#አብሮኮሮንዮስ የታዘዘውን ሊፈጽም ሠራዊት አስከትሎ
ሲወጣ ግን የአባቱ የ20 ዘመናት ለቅሶና ጸሎት ፍሬ አፈራ::
ገና መንገድ ላይ ሳለ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና
መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ድምጹን ከሰማይ ላከለት:: "ወደ እውነተኛ መንገድ ተመለስ:: ካልሆነ ግን ሾተሉን ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል" አለው::
አብሮኮሮንዮስም እየተንቀጠቀጠ "አቤቱ አንተ ማነህ?" አለው:: ጌታም "ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ" ሲል መለሰለት:: ዳግመኛም "ምልክት ስጠኝ" ቢለው የብርሃን #መስቀል በሰማይ ላይ ገለጠለት:: ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ጊዜ አላጠፋም:: ሠራዊቱን ይዞ ወደ ንጉሡ ከተማ ተመልሶ ንጉሡን በድፍረት
አለው:- "እኔ ክርስቲያን ነኝ:: ክርስቶስንም አመልካለሁ::"
ካነጋገሩ የተነሳ አባቱን ደስ ሲለው ንጉሡና እናቱ ግን ደነገጡ:: ንጉሡ ሊያስፈራራው ሞከረ:: ግን
አልተሳካለትም:: ከዚያማ ያሰቃየው ገባ:: አንድ ቀን አካሉ እስኪቆራረጥ ገረፉት:: በእሳትም
አቃጠሉት:: ሞተ ብለው አስበው ነበር:: ወደ እርሱ ሲመለሱ
ግን ጌታችን አድኖታልና የሰንበር ምልክት እንኩዋ በአካሉ ላይ
አልተገኘም:: እናቱ #ቴዎዳስያ ከዚህ በላይ ምልክትን
አልፈለገችም:: በደቂቃዎች ልዩነት እርሷም ወደ #ክርስትና
ተመለሰች:: ልጇንም ቀድማ ሐምሌ 6 ቀን ሰማዕት ሆነች::
ቅዱስ አብሮኮርዮስን ግን ለበርካታ ጊዜያት አሰቃይተው
ከክርስቶስ ፍቅር ሊለዩት ባለመቻላቸው በዚህች ቀን
ገድለውታል:: አባት: እናትና ልጅ (ክርስቶፎሮስ: ቴዎዳስያና
አብሮኮሮንዮስ) ለሰማያዊ ርስት በቅተዋል:: አባት ይሏቹሃል
እንዲህ ነው!