ስንክሳር
7.32K subscribers
825 photos
4 videos
37 files
237 links
በስንክሳር channal ስንክሳሩ ተገልጦ ቅዱሳን ይዘከራሉ፣ ወቅቱን የጠበቁ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡ ይከታተሉን!
Download Telegram
እንኩዋን ለሰማዕቱ ቅዱስ #አብሮኮሮንዮስ እና ለመነኮሳት አለቃ #ቅዱስ_መቃርስ ዓመታዊ በዓል በሰላም
አደረሳችሁ
+ ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ሰማዕት +
ቅዱሱ ተወልዶ ያደገው በአንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው መቶ
ክ/ዘመን አካባቢ ነው:: አባቱ ደግ ክርስቲያን የነበረ ሲሆን
ስሙ #ክርስቶፎሮስ ይባላል:: "ለባሴ ክርስቶስ" እንደ ማለት
ነው:: እናቱ ግን #ቴዎዳስያ የምትባል አረማዊት ነበረች::
ምንም እንኩዋ አባቱ ክርስቲያን ቢሆን እናቱ ኃይለኛ የቤተ
መንግስት ሰው ስለነበረች በልጅነቱ አብሮኮሮንዮስ ክርስትናን
ሊማር አልቻለም::
የልጁን አረማዊ መሆን ያልወደደ አባት አማራጩ አንድ ብቻ
ነበር:: እሱም ወደ ጌታ መለመን ነበር:: በእንዲሕ ያለ ግብር
ዘመናት ጐርፈው አብሮኮሮንዮስ ክርስቶስን ሳያውቅ 20
ዓመት ሆነው:: እናቱ ወስዳ: አሰልጥና ለጣዖት አምላኪ
ንጉሥ ሰጠችው:: ንጉሡም የጦር አለቃ አድርጐ ሾመውና
አንድ ትዕዛዝ ሰጠው:: "ክርስቲያኖችን ሁሉ ባገኘህበት ቦታ ጨፍጭፍ:: ቤታቸውንም አቃጥል::" #አብሮኮሮንዮስ የታዘዘውን ሊፈጽም ሠራዊት አስከትሎ ሲወጣ ግን የአባቱ የ20 ዘመናት ለቅሶና ጸሎት ፍሬ አፈራ::
ገና መንገድ ላይ ሳለ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና
መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ድምጹን ከሰማይ ላከለት::
"ወደ እውነተኛ መንገድ ተመለስ:: ካልሆነ ግን ሾተሉን
ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል" አለው:: አብሮኮሮንዮስም እየተንቀጠቀጠ "አቤቱ አንተ ማነህ?" አለው:: ጌታም "ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ" ሲል መለሰለት::
ዳግመኛም "ምልክት ስጠኝ" ቢለው የብርሃን #መስቀል
በሰማይ ላይ ገለጠለት:: ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ጊዜ
አላጠፋም:: ሠራዊቱን ይዞ ወደ ንጉሡ ከተማ ተመልሶ ንጉሡን በድፍረት አለው:- "እኔ ክርስቲያን ነኝ:: ክርስቶስንም አመልካለሁ::"
ካነጋገሩ የተነሳ አባቱን ደስ ሲለው ንጉሡና እናቱ ግን ደነገጡ::
ንጉሡ ሊያስፈራራው ሞከረ:: ግን አልተሳካለትም:: ከዚያማ
ያሰቃየው ገባ:: አንድ ቀን አካሉ እስኪቆራረጥ ገረፉት:: በእሳትም
አቃጠሉት:: ሞተ ብለው አስበው ነበር:: ወደ እርሱ ሲመለሱ
ግን ጌታችን አድኖታልና የሰንበር ምልክት እንኩዋ በአካሉ ላይ
አልተገኘም:: እናቱ #ቴዎዳስያ ከዚህ በላይ ምልክትን
አልፈለገችም:: በደቂቃዎች ልዩነት እርሷም ወደ #ክርስትና
ተመለሰች:: ልጇንም ቀድማ ሐምሌ 6 ቀን ሰማዕት ሆነች::
+ቅዱስ አብሮኮርዮስን ግን ለበርካታ ጊዜያት አሰቃይተው
ከክርስቶስ ፍቅር ሊለዩት ባለመቻላቸው በዚህች ቀን
ገድለውታል:: አባት: እናትና ልጅ (ክርስቶፎሮስ: ቴዎዳስያና
አብሮኮሮንዮስ) ለሰማያዊ ርስት በቅተዋል:: አባት ይሏቹሃል
እንዲህ ነው!
💚💛ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ሰማዕት 💛❤️
ቅዱሱ ተወልዶ ያደገው በአንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው
መቶ ክ/ዘመን አካባቢ ነው:: አባቱ ደግ ክርስቲያን የነበረ
ሲሆን ስሙ #ክርስቶፎሮስ ይባላል:: "ለባሴ ክርስቶስ" እንደ
ማለት ነው:: እናቱ ግን #ቴዎዳስያ የምትባል አረማዊት ነበረች:: ምንም እንኩዋ አባቱ ክርስቲያን ቢሆን እናቱ ኃይለኛ የቤተ መንግስት ሰው ስለነበረች በልጅነቱ አብሮኮሮንዮስ
ክርስትናን ሊማር አልቻለም::
የልጁን አረማዊ መሆን ያልወደደ አባት አማራጩ አንድ ብቻ
ነበር:: እሱም ወደ ጌታ መለመን ነበር:: በእንዲሕ ያለ ግብር
ዘመናት ጐርፈው አብሮኮሮንዮስ ክርስቶስን ሳያውቅ 20
ዓመት ሆነው:: እናቱ ወስዳ: አሰልጥና ለጣዖት አምላኪ
ንጉሥ ሰጠችው:: ንጉሡም የጦር አለቃ አድርጐ ሾመውና አንድ ትዕዛዝ ሰጠው:: "ክርስቲያኖችን ሁሉ ባገኘህበት ቦታ ጨፍጭፍ:: ቤታቸውንም አቃጥል::"
#አብሮኮሮንዮስ የታዘዘውን ሊፈጽም ሠራዊት አስከትሎ
ሲወጣ ግን የአባቱ የ20 ዘመናት ለቅሶና ጸሎት ፍሬ አፈራ::
ገና መንገድ ላይ ሳለ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና
መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ድምጹን ከሰማይ ላከለት:: "ወደ እውነተኛ መንገድ ተመለስ:: ካልሆነ ግን ሾተሉን ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል" አለው::
አብሮኮሮንዮስም እየተንቀጠቀጠ "አቤቱ አንተ ማነህ?" አለው:: ጌታም "ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ" ሲል መለሰለት:: ዳግመኛም "ምልክት ስጠኝ" ቢለው የብርሃን #መስቀል በሰማይ ላይ ገለጠለት:: ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ጊዜ አላጠፋም:: ሠራዊቱን ይዞ ወደ ንጉሡ ከተማ ተመልሶ ንጉሡን በድፍረት
አለው:- "እኔ ክርስቲያን ነኝ:: ክርስቶስንም አመልካለሁ::"
ካነጋገሩ የተነሳ አባቱን ደስ ሲለው ንጉሡና እናቱ ግን ደነገጡ:: ንጉሡ ሊያስፈራራው ሞከረ:: ግን
አልተሳካለትም:: ከዚያማ ያሰቃየው ገባ:: አንድ ቀን አካሉ እስኪቆራረጥ ገረፉት:: በእሳትም
አቃጠሉት:: ሞተ ብለው አስበው ነበር:: ወደ እርሱ ሲመለሱ
ግን ጌታችን አድኖታልና የሰንበር ምልክት እንኩዋ በአካሉ ላይ
አልተገኘም:: እናቱ #ቴዎዳስያ ከዚህ በላይ ምልክትን
አልፈለገችም:: በደቂቃዎች ልዩነት እርሷም ወደ #ክርስትና
ተመለሰች:: ልጇንም ቀድማ ሐምሌ 6 ቀን ሰማዕት ሆነች::
ቅዱስ አብሮኮርዮስን ግን ለበርካታ ጊዜያት አሰቃይተው
ከክርስቶስ ፍቅር ሊለዩት ባለመቻላቸው በዚህች ቀን
ገድለውታል:: አባት: እናትና ልጅ (ክርስቶፎሮስ: ቴዎዳስያና
አብሮኮሮንዮስ) ለሰማያዊ ርስት በቅተዋል:: አባት ይሏቹሃል
እንዲህ ነው!