የኢትየጵያ ንግድ ባንክ የ2019 የግሎባል ቢዝነስ አውት ሉክ ሽልማት አሸናፊ ሆነ።
የዘርፉን ሽልማት በማሸነፍም ከደቡብ አፍሪካ እና ናይጄሪያ ባንኮች በመቀጠል በአፍሪካ ሶስተኛው ባንክ መሆን ችሏል።
ባንኩ በ77 ዓመታት ጉዞው ዓለም ዓቀፍ ሽልማት ሲያሸንፍ የመጀመሪያው መሆኑንም አስታውቋል።
@YeneTube @Fikerassefa
የዘርፉን ሽልማት በማሸነፍም ከደቡብ አፍሪካ እና ናይጄሪያ ባንኮች በመቀጠል በአፍሪካ ሶስተኛው ባንክ መሆን ችሏል።
ባንኩ በ77 ዓመታት ጉዞው ዓለም ዓቀፍ ሽልማት ሲያሸንፍ የመጀመሪያው መሆኑንም አስታውቋል።
@YeneTube @Fikerassefa
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ዛሬ የካቲት 6፣ 2012 ከሰዓት በ8፡00 (በአካባቢው የሰዓት አቆጣጠር በ9፡00) ሰዓት ዱባይ ወደሚገኘው ሸባብ አላሕሊ ስቴዲየም በማቅናት በመካከለኛው ምስራቅ በሚገኙ ልዩ ልዩ ሀገራት ከሚኖሩ 15,000 ያህል ኢትዮጵያውያን ጋር ምክክር ያደርጋሉ።
#PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
#PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነቢያት ጌታቸው ዛሬ የካቲት 6 ቀን 2012 ዓ.ም. በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለአገር ውስጥ እና ለውጭ ሚዲያዎች ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል። አቶ ነቢያት በዛሬው መግለጫቸው በ33ኛው መደበኛው የመሪዎች ስብሰባ እና 36ኛው መደበኛው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ የአገራችን ያንፀባረቀችውን አቋም እና የተገኙ ውጤቶች፣ አገራችን ከሌሎች አገሮች ጋር ስላካሄደቻቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች፣ ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ እና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፖምፔዮ የሚቀጥለው ሳምንት የኢትዮጵያ ጉብኝትን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇👇👇
https://telegra.ph/PressRelease-02-14
ተጨማሪ ያንብቡ👇👇👇
https://telegra.ph/PressRelease-02-14
የ75 ዓመቱ ሰው ሊጥ ሰርቆ ታሰረ!
[አዲስ ዘመን ጋዜጣ እሁድ መጋቢት 26 ቀን 1963 ዓ.ም]
አስር ጊዜ የሌብነት ወንጀል ፈጽሞ የዘጠኝ አመት ተኩል ቅጣት ከተቀበለ በኋላ የተቦካ ሊጥ ከነባሊው ሰርቋል በመባል የተከሰሰው ሰው የፈጸመው ወንጀል በህግ ማስረጃ ስለተረጋገጠበት በአንድ አመት ከስድስት ወር እስራት እንዲቀጣ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ባለፈው አርብ ፈረደ፡፡አቶ ንጋቱ ፋንታ የተባለው ተከሳሽ የሚኖረው በአዲስ አበባ ከተማ የካ ሚካኤል አካባቢ ሲሆን ሌብነትን የዘወትር ሙያው በማድረግ የሰውን ቤት በሌሊት እየሰበረ ልዩ ልዩ የእቤት እቃዎችን በተደጋጋሚ ጊዜ ሰርቆ እንደነበር ፍርድ ቤቱ በቀረበለት ማስረጃ መሰረት ለማረጋገጥ መቻሉን ገልጿል፡፡የ75 ዓመቱ ሽማግሌ የተቦካውን ሊጥ ከነባሊው በሰረቀበት ዕለት ሁለት የቡና ሲኒና አንድ የስፌት አገልግልም ጨምሮ መውሰዱን ራሱ ለፍርድ ቤቱ በሰጠው ቃል አረጋግጧል፡፡
ተከሳሹ በየጊዜው በፍርድ ቤት የተወሰነበትን ቅጣት ተራምዶ የተደጋገመ ወንጀል መፈጸሙን ፍርድ ቤቱ ጠቅሶ፤ ከገሰጸው በኋላ የተከሳሹ ዕድሜ የገፋ ስለሆነ ቅጣቱን አሻሽሎለት በአንድ አመት ተኩል እስራት እንዲቀጣ ወስኗል። እንዲሁም ከተከሳሹ ጋር የወንጀል ግብረ አበር ሆኗል በመባል የተከሰሰው ደበበ ጫላ ከዚህ ቀደም የሌባ ተቀባይ መሆኑ ቢረጋገጥም በአሁኑ ጊዜ የፈጽመው ወንጀል ከዚሁ ጋር ተመሳሳይነት ያለው በመሆኑ በአንድ አመት እስራት እንዲቀጣ ተፈርዶበታል፡፡
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
[አዲስ ዘመን ጋዜጣ እሁድ መጋቢት 26 ቀን 1963 ዓ.ም]
አስር ጊዜ የሌብነት ወንጀል ፈጽሞ የዘጠኝ አመት ተኩል ቅጣት ከተቀበለ በኋላ የተቦካ ሊጥ ከነባሊው ሰርቋል በመባል የተከሰሰው ሰው የፈጸመው ወንጀል በህግ ማስረጃ ስለተረጋገጠበት በአንድ አመት ከስድስት ወር እስራት እንዲቀጣ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ባለፈው አርብ ፈረደ፡፡አቶ ንጋቱ ፋንታ የተባለው ተከሳሽ የሚኖረው በአዲስ አበባ ከተማ የካ ሚካኤል አካባቢ ሲሆን ሌብነትን የዘወትር ሙያው በማድረግ የሰውን ቤት በሌሊት እየሰበረ ልዩ ልዩ የእቤት እቃዎችን በተደጋጋሚ ጊዜ ሰርቆ እንደነበር ፍርድ ቤቱ በቀረበለት ማስረጃ መሰረት ለማረጋገጥ መቻሉን ገልጿል፡፡የ75 ዓመቱ ሽማግሌ የተቦካውን ሊጥ ከነባሊው በሰረቀበት ዕለት ሁለት የቡና ሲኒና አንድ የስፌት አገልግልም ጨምሮ መውሰዱን ራሱ ለፍርድ ቤቱ በሰጠው ቃል አረጋግጧል፡፡
ተከሳሹ በየጊዜው በፍርድ ቤት የተወሰነበትን ቅጣት ተራምዶ የተደጋገመ ወንጀል መፈጸሙን ፍርድ ቤቱ ጠቅሶ፤ ከገሰጸው በኋላ የተከሳሹ ዕድሜ የገፋ ስለሆነ ቅጣቱን አሻሽሎለት በአንድ አመት ተኩል እስራት እንዲቀጣ ወስኗል። እንዲሁም ከተከሳሹ ጋር የወንጀል ግብረ አበር ሆኗል በመባል የተከሰሰው ደበበ ጫላ ከዚህ ቀደም የሌባ ተቀባይ መሆኑ ቢረጋገጥም በአሁኑ ጊዜ የፈጽመው ወንጀል ከዚሁ ጋር ተመሳሳይነት ያለው በመሆኑ በአንድ አመት እስራት እንዲቀጣ ተፈርዶበታል፡፡
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አባሎቼና ደጋፊዎቼ በጅምላ እየታሰሩብኝ ነው አለ፡፡
እስሩ እየተፈፀመ ያለው በኦሮሚያ ፖሊስ እንደሆነም ግንባሩ ዛሬ በፅህፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እወቁልኝ ብሏል፡፡እስከ ዛሬዋ ዕለት ድረስም በኦሮሚያ ክልል 7 ዞኖች እና 26 ከተሞች 350 አባሎቹ፣ ደጋፊዎቹና ሌሎች ወጣቶች መታሰራቸውን በመግለጫው አክሏል፡፡ከእነዚህ ውስጥ የ174ቱ ስም ደርሶኛል ሲልም ዘርዝሯቸዋል፡፡
የምዕራብና ደቡብ ኦሮሚያ አካባቢዎች ህጋዊ መሰረት በሌለው እና ቀነገደብ ባልተቀመጠለት ኮማንድ ፖስት እየተዳደሩ ይገኛሉም ብሏል፡፡የአካባቢዎቹ በኮማንድ ፖስት መተዳደር ነዋሪዎቹን ለግድያ፣ ዝርፊያ፣ አስገድዶ መድፈርና ሌሎች ወንጀሎች አጋልጧቸዋል ሲልም አክሏል።በምዕራብና ቄለም ወለጋ አካባቢዎች የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎቶች ከተቋረጡ ከ1 ወር ተኩል በላይ እንደሆነ የግንባሩ ባለስልጣናት በመግለጫው ላይ ተናግረዋል፡፡
በአገሪቱ አጠቃላይ ምርጫ ለማድረግ ዝግጅት እየተካሄደ ባለበት በአሁኑ ወቅት የነገሮች መክፋት አሳስቦኛል ሲልም ኦነግ በመግለጫው ጠቅሷል፡፡መንግስት ለችግሩ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ደግሞ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች እየተፈፀሙ ያሉ የመብት ጥሰቶችን አጣርቶ መረጃውን ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ ጠይቋል፡፡
Via ሸገር ራዲዮ
@YeneTube @FikerAssefa
እስሩ እየተፈፀመ ያለው በኦሮሚያ ፖሊስ እንደሆነም ግንባሩ ዛሬ በፅህፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እወቁልኝ ብሏል፡፡እስከ ዛሬዋ ዕለት ድረስም በኦሮሚያ ክልል 7 ዞኖች እና 26 ከተሞች 350 አባሎቹ፣ ደጋፊዎቹና ሌሎች ወጣቶች መታሰራቸውን በመግለጫው አክሏል፡፡ከእነዚህ ውስጥ የ174ቱ ስም ደርሶኛል ሲልም ዘርዝሯቸዋል፡፡
የምዕራብና ደቡብ ኦሮሚያ አካባቢዎች ህጋዊ መሰረት በሌለው እና ቀነገደብ ባልተቀመጠለት ኮማንድ ፖስት እየተዳደሩ ይገኛሉም ብሏል፡፡የአካባቢዎቹ በኮማንድ ፖስት መተዳደር ነዋሪዎቹን ለግድያ፣ ዝርፊያ፣ አስገድዶ መድፈርና ሌሎች ወንጀሎች አጋልጧቸዋል ሲልም አክሏል።በምዕራብና ቄለም ወለጋ አካባቢዎች የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎቶች ከተቋረጡ ከ1 ወር ተኩል በላይ እንደሆነ የግንባሩ ባለስልጣናት በመግለጫው ላይ ተናግረዋል፡፡
በአገሪቱ አጠቃላይ ምርጫ ለማድረግ ዝግጅት እየተካሄደ ባለበት በአሁኑ ወቅት የነገሮች መክፋት አሳስቦኛል ሲልም ኦነግ በመግለጫው ጠቅሷል፡፡መንግስት ለችግሩ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ደግሞ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች እየተፈፀሙ ያሉ የመብት ጥሰቶችን አጣርቶ መረጃውን ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ ጠይቋል፡፡
Via ሸገር ራዲዮ
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ከየትኛውም አካል ተጽዕኖ ቢኖርም ብሄራዊ ጥቅሟን ያላሰጠበቀ ስምምነት እንደማትፈርም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብያት ጌታቸው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ረፋዱን በሰጡት መግለጫ ፣ በዋሽንግተን ዲ.ሲ. በህዳሴ ግድብ ላይ እየተደረጉ ስላለው ውይይት አብራርተዋል። ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ሲያደርጉት የነበረውን ድርድርና የረቂቅ የስምምነት ሰነድ ዝግጅት ሳይቋጭ መጠናቀቁ ይታወቃል። በድርድሩ ሱዳን የአቋም ለውጥ አድርጋ ከግብጽ ጋር መወገኗን እንዲሁም አሜሪካ እና የዓለም ባንክ ለግብጽ መወገናቸውን አሁን ላይ ጉዳዩ “4 ለ 1” ሆኗል የሚሉና በዚህም ኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ጫና እየተደረገ እንደሆነ በመግለጽ የኢትዮጵያ አቋም ምን እንደሆነ ከጋዜጠኞች ጥያቄ ተነስቷል።
በዚህም ቃል አቀባዩ አቶ ነቢያት በሰጡት ምላሽ፤ በግድቡ ዙሪያ ከየትኛውም አካል ተጽዕኖ ቢኖር ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሟን አሳልፋ እንደማትሰጥና መርህ ላይ የተመሰረተ ጥቅሟን ያስጠበቀ ድርድር እንደምታራምድ አረጋግጠዋል። በዚህም ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሟን አሳልፋ እንደማትሰጥ ነው አጽኖኦት የሰጡት።
በዋሽንግተን ዲ.ሲ. በኢትዮጵያ፣ በሱዳንና በግብጽ መካከል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ አሞላልና አለቃቀቅን በተመለከተ ረቂቅ የስምምነት ሰነድ ለማዘጋጀት ሲካሄድ የነበረው ውይይት በዚህኛውም ዙር ሳይቋጭ ትናንት ማማምሻውን መጠናቀቁ ይታወሳል።የኢትዮጵያ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ በዚህ ሳምንት የሶስቱ አገሮች የህግ ባለሙያዎች የደረሱበትን ረቂቅ ስምምነት ዝግጅት በኢትዮጵያ በኩል ለመገምገም ወደ ስፍራው ማቅናታቸውም እንዲሁ፡፡
Via ENA
@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብያት ጌታቸው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ረፋዱን በሰጡት መግለጫ ፣ በዋሽንግተን ዲ.ሲ. በህዳሴ ግድብ ላይ እየተደረጉ ስላለው ውይይት አብራርተዋል። ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ሲያደርጉት የነበረውን ድርድርና የረቂቅ የስምምነት ሰነድ ዝግጅት ሳይቋጭ መጠናቀቁ ይታወቃል። በድርድሩ ሱዳን የአቋም ለውጥ አድርጋ ከግብጽ ጋር መወገኗን እንዲሁም አሜሪካ እና የዓለም ባንክ ለግብጽ መወገናቸውን አሁን ላይ ጉዳዩ “4 ለ 1” ሆኗል የሚሉና በዚህም ኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ጫና እየተደረገ እንደሆነ በመግለጽ የኢትዮጵያ አቋም ምን እንደሆነ ከጋዜጠኞች ጥያቄ ተነስቷል።
በዚህም ቃል አቀባዩ አቶ ነቢያት በሰጡት ምላሽ፤ በግድቡ ዙሪያ ከየትኛውም አካል ተጽዕኖ ቢኖር ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሟን አሳልፋ እንደማትሰጥና መርህ ላይ የተመሰረተ ጥቅሟን ያስጠበቀ ድርድር እንደምታራምድ አረጋግጠዋል። በዚህም ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሟን አሳልፋ እንደማትሰጥ ነው አጽኖኦት የሰጡት።
በዋሽንግተን ዲ.ሲ. በኢትዮጵያ፣ በሱዳንና በግብጽ መካከል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ አሞላልና አለቃቀቅን በተመለከተ ረቂቅ የስምምነት ሰነድ ለማዘጋጀት ሲካሄድ የነበረው ውይይት በዚህኛውም ዙር ሳይቋጭ ትናንት ማማምሻውን መጠናቀቁ ይታወሳል።የኢትዮጵያ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ በዚህ ሳምንት የሶስቱ አገሮች የህግ ባለሙያዎች የደረሱበትን ረቂቅ ስምምነት ዝግጅት በኢትዮጵያ በኩል ለመገምገም ወደ ስፍራው ማቅናታቸውም እንዲሁ፡፡
Via ENA
@YeneTube @FikerAssefa
ምርጫ ቦርድ አዲስ ድረ-ገጽ (ዌብ ሳይት) አዘጋጅቶ መጨረሱን አስታውቋል። ድረ-ገጹ የምርጫ ውጤቶች ጭምር የሚገለጹበት በመሆኑ ደህንነቱን ለማስጠበቅ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን እና በቅርቡ ወደ ስራ እንደሚገባ ተገልጿል።
#Ethiopia #Election2012
@YeneTube @Fikerassefa
#Ethiopia #Election2012
@YeneTube @Fikerassefa
የኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ የጥቁር ገበያውን ዶላር ምንዛሬ ቀንሶታል
ከሳምንታት በፊት የአንድ የአሜሪካ ዶላር ዋጋ በኢትዮጵያ ህጋዊ ባልሆነው ጥቁር ገበያ 42 ብር ድረስ የሚመነዘር ሲሆን ወደ ቻይና ዶላር ይዘው እቃ ለማምጣት የሚሄዱ ነጋዴዎች ከኮሮና ቫይረስ መከሰት ጋር ስጋት ስለገባቸውና የሚያደርጉትም ጉዞ በመቀነሱ ምክንያት የዶላር ፍላጎት በተወሰነ መልኩም ቀንሷል። በዚህም ምክንያት የአንድ ዶላር መሸጫ ዋጋ በሁለት ብር ቀንሶ በጥቁር ገበያው አርባ ብር አየተሸጠ እንደሚገኝ ፊደል ፓስት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
በባንኮች ደግሞ የዶላር ምንዛሬ ከሁለት ወራት በፊት በየቀኑ አምስት ሳንቲም እየጨመረ ከ32 ብር አልፎ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰአት ዝቅ ብሎ 31. 70 አሰከ 31. 90 ከፍና ዝቅ አያለ ባለፉት ሁለት ሳምንት አየተሸጠ ይገኛል።
Via:- fidelpost
@YeneTube @Fikerassefa
ከሳምንታት በፊት የአንድ የአሜሪካ ዶላር ዋጋ በኢትዮጵያ ህጋዊ ባልሆነው ጥቁር ገበያ 42 ብር ድረስ የሚመነዘር ሲሆን ወደ ቻይና ዶላር ይዘው እቃ ለማምጣት የሚሄዱ ነጋዴዎች ከኮሮና ቫይረስ መከሰት ጋር ስጋት ስለገባቸውና የሚያደርጉትም ጉዞ በመቀነሱ ምክንያት የዶላር ፍላጎት በተወሰነ መልኩም ቀንሷል። በዚህም ምክንያት የአንድ ዶላር መሸጫ ዋጋ በሁለት ብር ቀንሶ በጥቁር ገበያው አርባ ብር አየተሸጠ እንደሚገኝ ፊደል ፓስት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
በባንኮች ደግሞ የዶላር ምንዛሬ ከሁለት ወራት በፊት በየቀኑ አምስት ሳንቲም እየጨመረ ከ32 ብር አልፎ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰአት ዝቅ ብሎ 31. 70 አሰከ 31. 90 ከፍና ዝቅ አያለ ባለፉት ሁለት ሳምንት አየተሸጠ ይገኛል።
Via:- fidelpost
@YeneTube @Fikerassefa
የ2012 ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከልሶ በቀረበው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የድምፅ መስጫ ቀን #ነሀሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ሆኗል።
የምርጫ ባለድርሻ አካላት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው።
በባለ ድርሻ አካላት ኮንፈረንሱ ላይ የምርጫ ሰሌዳ ማሻሻያውን የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ አቅርበውታል።
ከዚህ ቀደም ጊዜያዊ የድምፅ መስጫ ቀን ነሀሴ 10 ቀን እንዲሆን መወሰኑ ይታወሳል ።
የምርጫ ጊዜውን ለማራዘም የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ግንዛቤ ውስጥ ብናስገባም ከህግ አንፃር የድምፅ መስጫ የተከለሰው ቀን ነሀሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ይሆናል ብለዋል።
በክረምት መካሄዱ ሊፈጥር የሚችለውን ተፅእኖ በተመለከተም ከብሄራዊ ሜቲዮሮሎጂ ኤጀንሲ ጋር እየተሰራ መሆኑን ም ተናግረዋል።
#ምርጫ2012
@YeneTube @Fikerassefa
የምርጫ ባለድርሻ አካላት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው።
በባለ ድርሻ አካላት ኮንፈረንሱ ላይ የምርጫ ሰሌዳ ማሻሻያውን የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ አቅርበውታል።
ከዚህ ቀደም ጊዜያዊ የድምፅ መስጫ ቀን ነሀሴ 10 ቀን እንዲሆን መወሰኑ ይታወሳል ።
የምርጫ ጊዜውን ለማራዘም የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ግንዛቤ ውስጥ ብናስገባም ከህግ አንፃር የድምፅ መስጫ የተከለሰው ቀን ነሀሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ይሆናል ብለዋል።
በክረምት መካሄዱ ሊፈጥር የሚችለውን ተፅእኖ በተመለከተም ከብሄራዊ ሜቲዮሮሎጂ ኤጀንሲ ጋር እየተሰራ መሆኑን ም ተናግረዋል።
#ምርጫ2012
@YeneTube @Fikerassefa
በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር የ5 ሴት ወጣቶች ህይወት እንዲጠፋ ያደረገው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ መወሰኑን የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታወቀ።
የፍርድ ቤቱ ዳኛ አቶ ሐኪም ሲራጅ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት አብዱከሪም ጣሂር አብደላ የተባለው ግለሰብ ነዋሪነታቸው በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጉርሱም ወረዳ ዳይፈርስ ቀበሌ ገበሬ ማህበር የሆኑ ወጣት ሴቶችን በህገ ወጥ መንገድ በማስኮብለል ለህልፈተ ህይወት በመዳረጉ ቅጣቱ ተላልፎበታል ።
“በጎረቤት አገር በኩል ሳውድ አረቢያ ወስጄ በከፍተኛ ደመወዝ ስራ እንድትቀጠሩ አደርጋለሁ ” በሚል ማታለያ በ2010 ዓም በተለያዩ ቀናትና ወራት ከቀያቸው ካስኮበለላቸው 8 ወጣት ሴቶችን ላይ ከእያንዳንዳቸው 3 ሺህ ብር ተቀብሏል ።
ስልክ በመደወልና ዘመድ አዝማድ ሳይሰማ ከአደጉበት ቀዬ ጭለማን ተገን በማድረግ ካስኮበለላቸው 8 ሴት መካከል በጀልባ መስጠም ምክንያት 5ቱ ህይወታቸው ማለፉን ዳኛው ገልፀዋል።በተጨማሪም በደላላ አማካኝነት ቤተሰቦቻቸውን በማስጨነቅ ከእያንዳንዳቸው ቤተሰብ 10 ሺህ ብር መቀበሉን ተናግረዋል።
ከአደጋው የተረፉት ወደ ቀያቸው እንደተመለሱ ለሟች ዘመዶች በሰጡት ጥቆማ መሰረት የክስ አቤቱታ የደረሰው የጉርሱም ወረዳ ፖሊስ ወንጀለኛውን አብዱከሪም ጣሂር አብደላ በቁጥጥር ስር በማዋል ክስ ተመስርቶበት የምርመራ መዝገቡ አጣርቶ ለማየት ስልጣን ላለው ለምስራቅ ሐረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንዲተላለፍ ተደርጓል።
ጉዳዩን የተመለከተው ፍርድ ቤት ግለሰቡ ወንጀሉን መፈጸሙ በአቃቢ ህግ፣በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማረጋገጥ የቅጣት ማቅለያና ማክበጃ ከመረመረ በሃላ አላግባብ ጥቅም ለማግኘት ሲል አምራች ሐይል በሆኑት ወጣት ሴቶቹ ላይ የተፈጸመው ድርጊት አሰቃቂ ወንጀል በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ጥር 2 ቀን 2012 በዋለው ችሎት ወንጀለኛው አብዱከሪም ጣሂር አብደላን በሞት እንዲቀጣ መወሰኑን ገልጸዋል።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ተፈፃሚ የሚሆነው ለሀገሪቷ ፕሬዚዳንት ቀርቦ ይሁንታ ሲያገኝ ብቻ ነው ተብሏል ።
Via ENA
@YeneTube @FikerAssefa
የፍርድ ቤቱ ዳኛ አቶ ሐኪም ሲራጅ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት አብዱከሪም ጣሂር አብደላ የተባለው ግለሰብ ነዋሪነታቸው በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጉርሱም ወረዳ ዳይፈርስ ቀበሌ ገበሬ ማህበር የሆኑ ወጣት ሴቶችን በህገ ወጥ መንገድ በማስኮብለል ለህልፈተ ህይወት በመዳረጉ ቅጣቱ ተላልፎበታል ።
“በጎረቤት አገር በኩል ሳውድ አረቢያ ወስጄ በከፍተኛ ደመወዝ ስራ እንድትቀጠሩ አደርጋለሁ ” በሚል ማታለያ በ2010 ዓም በተለያዩ ቀናትና ወራት ከቀያቸው ካስኮበለላቸው 8 ወጣት ሴቶችን ላይ ከእያንዳንዳቸው 3 ሺህ ብር ተቀብሏል ።
ስልክ በመደወልና ዘመድ አዝማድ ሳይሰማ ከአደጉበት ቀዬ ጭለማን ተገን በማድረግ ካስኮበለላቸው 8 ሴት መካከል በጀልባ መስጠም ምክንያት 5ቱ ህይወታቸው ማለፉን ዳኛው ገልፀዋል።በተጨማሪም በደላላ አማካኝነት ቤተሰቦቻቸውን በማስጨነቅ ከእያንዳንዳቸው ቤተሰብ 10 ሺህ ብር መቀበሉን ተናግረዋል።
ከአደጋው የተረፉት ወደ ቀያቸው እንደተመለሱ ለሟች ዘመዶች በሰጡት ጥቆማ መሰረት የክስ አቤቱታ የደረሰው የጉርሱም ወረዳ ፖሊስ ወንጀለኛውን አብዱከሪም ጣሂር አብደላ በቁጥጥር ስር በማዋል ክስ ተመስርቶበት የምርመራ መዝገቡ አጣርቶ ለማየት ስልጣን ላለው ለምስራቅ ሐረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንዲተላለፍ ተደርጓል።
ጉዳዩን የተመለከተው ፍርድ ቤት ግለሰቡ ወንጀሉን መፈጸሙ በአቃቢ ህግ፣በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማረጋገጥ የቅጣት ማቅለያና ማክበጃ ከመረመረ በሃላ አላግባብ ጥቅም ለማግኘት ሲል አምራች ሐይል በሆኑት ወጣት ሴቶቹ ላይ የተፈጸመው ድርጊት አሰቃቂ ወንጀል በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ጥር 2 ቀን 2012 በዋለው ችሎት ወንጀለኛው አብዱከሪም ጣሂር አብደላን በሞት እንዲቀጣ መወሰኑን ገልጸዋል።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ተፈፃሚ የሚሆነው ለሀገሪቷ ፕሬዚዳንት ቀርቦ ይሁንታ ሲያገኝ ብቻ ነው ተብሏል ።
Via ENA
@YeneTube @FikerAssefa
ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ የምርጫ ሰነዶችና ቁሳቁሶች የተከማቹት ከፍተኛ ጥበቃ ባለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የዕቃ ማከማቻ መጋዘን መሆኑን በዛሬው የምርጫ ቦርድ ኮንፍረንስ ላይ ተመልክቷል።ቦርዱ አየር መንገዱን ለዕይታ ባበቃው ቪዲዮ ላይ አመስግኗል።
#ምርጫ2012
@YeneTube @Fikerassefa
#ምርጫ2012
@YeneTube @Fikerassefa
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር እንደሻው ጣሰው ለምርጫ "ሰራዊታችንን በአግባቡ እናሰለጥናለን። የተለያዩ ችግሮች ቢያጋጥሙ እንዴት መከላከል እንደሚቻል በቂ ዝግጅቶች አድርገናል...በከተማም ሆነ በገጠር ሽፍታ ካለ አንቀበልም።ህግ እናስከብራለን" ብለዋል።
#ምርጫ2012
@Yenetube @Fikerassefa
#ምርጫ2012
@Yenetube @Fikerassefa
በምርጫ ቦርድ ኮንፍረንስ የተሳተፉ የህወሓት ተወካይ፤ የኤርትራው ፕሬዝዳንት በቅርቡ በሰጡት ቃለ-ምልልስ ስለ ኢትዮጵያ ምርጫ የተናገሩትን አንስተው ጥያቄ አቅርበዋል። "ኤርትራ ለእኛ ድጋፍ አላደረገችም" ሲሉ ብርቱካን ሚደቅሳ ምላሽ ሰጥተዋል።
#ምርጫ2012
@YeneTube @Fikerassefa
#ምርጫ2012
@YeneTube @Fikerassefa
የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የምርጫ ምዝገባን በተመለከተ "ሎጀስቲክ ላይ ብዙ ወጪ ሳያስወጣ እንዴት መፈጸም እንደምንችል እያየን ነው። እንዴት እንደምንፈጽመው ገና አልወሰንንም" - የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ
#Ethiopia #ምርጫ2012 #Election2020
@YeneTube @Fikerassefa
#Ethiopia #ምርጫ2012 #Election2020
@YeneTube @Fikerassefa
ቻይና የሚገኙ ተማሪዎችን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ግብረኃይል ተቋቋመ!
በኮሮና ቫይረስ ስጋት ውስጥ እንደሆኑ የተነገረላቸው ተማሪዎችን ለማስመጣት ግብረኃይል መቋቋሙን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አርብ የካቲት 6/2012 በወቅታዊ ጉዳይ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አስታወቀ፡፡ በቻይና ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች መንግስት የገንዘብ ድጋፍ መላኩን የገለጹት የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ነብያት ጌታቸው ተማሪዎቹ በቫይረስ እንዳይጠቁ ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
በኮሮና ቫይረስ ስጋት ውስጥ እንደሆኑ የተነገረላቸው ተማሪዎችን ለማስመጣት ግብረኃይል መቋቋሙን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አርብ የካቲት 6/2012 በወቅታዊ ጉዳይ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አስታወቀ፡፡ በቻይና ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች መንግስት የገንዘብ ድጋፍ መላኩን የገለጹት የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ነብያት ጌታቸው ተማሪዎቹ በቫይረስ እንዳይጠቁ ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
የሱዳን ገዳሪፍ ክፍለ ግዛት ዋ/አስተዳዳሪ ሜ/ጀኔራል ነስረዲን አብዲ የተመራ ልዑክ ጎንደር ገባ። ልዑኩ በድንበር አካባቢ ፀጥታና በኮንትሮባንድ ንግድ ዙሪያ ከአማራ ክልል ባለስልጣናት ጋር ነገ በባህርዳር ውይይት እንደሚያካሂድ አምሓራ ብዙኃን መገናኛ ዘግቧል።
@Yenetube @Fikerassefa
@Yenetube @Fikerassefa
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በሸባብ አላሕሊ ስቴዲየም በተገኙበት ባስተላለፉት መልዕክት "መብታችሁ ተጠብቆ እንድትሠሩ ለማድረግ መንግሥት ከየሀገራቱ መንግሥታት ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት አድርጓል፣ መንግሥት እናንተ ስትከበሩ ሀገራችን እንደምትከበር ስለሚገነዘብ፣ መብታችሁን እና ጥቅማችሁን ለማስከበር የሚችለውን ሁሉ ያደርጋል" ብለዋል። ጠ/ሚሩ ለተደረገላቸው አቀባበልም ምስጋናን አቅርበዋል።
#PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
#PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
የአለም ጤና ድርጅት በኮረና ቫይረስ ምክንያት የቶኪዮ ኦሎምፒክን መሰረዝ አያስፈልግም አለ።
ዶ/ር ማይክ ራያን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ "ከአደጋ ዜሮ የሆነ የብዙሀን ስብስብ የለም" ስለሆነም አዘጋጆቹና የአከባቢው የጤና ባለሙያዎች ችግር ሲያጋጥም መፍትሄ ለመስጠት መዘጋጀት አለባቸው ብለዋል።
#AlAln
@YeneTube @Fikerassefa
ዶ/ር ማይክ ራያን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ "ከአደጋ ዜሮ የሆነ የብዙሀን ስብስብ የለም" ስለሆነም አዘጋጆቹና የአከባቢው የጤና ባለሙያዎች ችግር ሲያጋጥም መፍትሄ ለመስጠት መዘጋጀት አለባቸው ብለዋል።
#AlAln
@YeneTube @Fikerassefa