ለምን አልሰለምኩም?
3K subscribers
52 photos
10 videos
42 files
187 links
ይህ ቻነል ቅዱሱ የአምላካችን ቃል በ1ኛ ጴጥ 3:15 ላይ ባዘዘን መሠረት ሙስሊም ወገኖቻችን በክርስትና ላይ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች እና ትችቶች ምላሽ የምንሰጥበት፣ ጥያቄዎቻቸውን ከነመልሳቸው በየጊዜው እያዘጋጀን የምንለጥፍበት፣ ለምን እንዳልሰለምን ፣ እንደማንሰልምም የምንገልጥበት ፣ የኢስላምን የጨለማ መንገድነት በእውነት ብርሀን የሚገልጡ ፅሁፎችን የምናስነብብበት መድረክ ነው።
Download Telegram
Forwarded from ለምን አልሰለምኩም? (Naol Jigy)
 በ አላህ ስሞች ዙሪያ "ሙግት"

የ እስልምና መፅሓፍቶች፣ አላህ 99 ስሞች እንዳለው ይነግሩናል።

Bukhari Vol. 3, Book 50, Hadith 894
Narrated Abu Huraira:

Allah's Messenger (ﷺ) said, "Allah has ninety-nine names, i.e. one-hundred minus one, and whoever knows them will go to Paradise."
አቡ ሁረይራ የዘገበው ሓዲዝ ነው፦ የ አላህ መልዕክተኛ እንዲህ አሉ፣ " አላህ 99 *ስሞች* አሉት ፤ መቶ ሲቀነስ አንድ። ሁሉንም የሚያውቅ ሰው ወደ ገነት ይግባል።

በ Sahih Muslim – Book 35 Hadith 6476 ላይ፤ ከላይ ባነበብነው ሓዲዝ ላይ ጨምሮ እንዲህ ይላል። " አላህ የሚታወቀው በ ጎዶሎ ቁጥር (odd number) ስለሆነ (አንድ ስለሆነ) ጎዶሎ ቁጥርን ይወዳል።"

ጥያቄያችን፦
 1.በ 99ኙ የ አላህ ስሞች ውስጥ "አላህ" የሚልው አልተካተተም። ስለዚህ " አላህ" ከተጨመረበት 99 ሳይሆን 100 ይሆናል። ስለዚህ ከላይ "አላህ 99 ስም አለው" " አላህ የሚወደው ጐዶሉ ቁጥርን ነው" የሚሉ ሓዲዞች ውድቅ ሆኑ ማለት ነው።

2. አይ! "አላህ" የሚለውን አይጨምርም ካላቹ ፣ታዲያ "አላህ"  የሚለው 'ስም' ካልሆነ ምንድን ነው??

3.  አይደለም! 99ኙ ስሞች ለ ፍጡርም ያገለግላሉ፤ ስለዚህ መግለጫ ብቻ ናቸው ('አላህ' ከሚለው ስም ይለያሉ)ካላቹ ደግሞ፣ በ ምሳሌ ብንወስድ ከ 99ኙ ስሞች አንዱ  الْخَالِقُ "አል ኻሊቅ" "ፈጣሪ"  የሚል እንውሰድ። ስለዚህ ፍጡር ሆኖ ፈጣሪ አለ ልትሉን ነው??

4.አይ! ለ ፍጡር አንጠቀማቸውም፣ ካላቹ፤፦ እየሱስ ከ 99ኙ የ አላህ ስሞች በ ብዙ እራሱን ጠርቷል። ስለዚህ እየሱስ ፍጡር ነው ብላቹ የምትሟገቱት ሙግት ውድቅ ይሆናል ማለት ነው። ለምሳሌ፤ ከ 99ኙ የ አላህ ስሞች፦
A. "አል አዋሉ" እና "አል አኺሩ" "የ መጀመሪያ፣ የ መጨረሻ" الأوَّلُ እና الآخِرُ "the beginning and the end" አሉ። ቁርአንም እንዲህ ይላል * ሱራ 57:3

እርሱ ፊትም ያለ ኋላም ቀሪ፣ ግልፅም ስውርም ነው፤ እርሱም ነገርን ሁሉ ዐዋቂ ነው።
He is #the #First and #the #Last, the Ascendant and the Intimate, and He is, of all things, Knowing.

እየሱስም እንዲህ ብሏል

(የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ 1)
----------
17፤ ባየሁትም ጊዜ እንደ ሞተ ሰው ሆኜ ከእግሩ በታች ወደቅሁ። ቀኝ እጁንም ጫነብኝ እንዲህም አለኝ። አትፍራ፤ #ፊተኛውና #መጨረሻው #ሕያውም እኔ ነኝ፥

18፤ #ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ።

B. An-noor النُّورُ The light ሌላ የ አላህ ስም ነው
 
እየሱስም በ ዮሓኒስ 14:6 " ..እኔ ብርሃን ነኝ" " The light"። ልብ በሉ "Al-' ወይም " The" የሚለው definite article ለ አላህም ለ እየሱስም ተጠቅሟል። ይሄ ደግሞ ዝም ብሎ ለተራ ሰው የምንጠቀምው ሳይሆን "ልዩ" መሆናቸውን የሚገልፅ ነው።

C. الباعث አል-ባእዝ "ትንሳኤ" "The resurrection" ወይም "The Resurrector" ወይም  "አዲስ ሕይወት ሰጪ"
እየሱስም በዚህ ስም ተጠርቷል፦

" ኢየሱስም። #ትንሣኤና #ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤"
(የዮሐንስ ወንጌል 11:25)

" ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን #አስነሣዋለሁ።"...The Resurrector!!
(የዮሐንስ ወንጌል 6:54)

ስለዚህ "የ አላህ ስሞች ለ ፍጡር አንጠቀምም" በሚለው ሙግት ከሄድን እየሱስ በ አላህ ስም ስለተጠራ #እየሱስ ፍጡር ሳይሆን #ፈጣሪ ነው ማለት ነው።


 "እየሱስ ዬት ጋር ነው 'እኔ አምላክ ነኝ' ያለው??" ለምትሉ ሙስሊሞች መልሱ ከላይ እንዳነበባችሁት ነው እንላለን!!
@Jesuscrucified
@Jesuscrucified
1
ግራንቪል ሻርፕ፦የዮሓኒስ ወንጌል 20:28

ሙሓመዳውያን መፅሓፍ ቅዱስ ውስጥ ተፅፎ የክርስቶስን አምላክነት በ ግልፅ የሚያሳዩ ጥቅሶችን ከራሳቸው ሳይሆን ከ ስላሴ ተቃዋሚያን፣ ግን ክርስቲያን ነን ባዮች በሚሰበስቡት የወረደና በ ብዙ ምሁራን የፈረሰ ሙግት ይዞ እንደ አዲስ መቅረባቸውን ቀጥሏል። ዮሓኒስ 20:28 ከ ጥቅሶቹ መካከል አንዱ ነው።


(የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 20)
----------
27፤ ከዚያም በኋላ ቶማስን። ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን አለው።

28፤ ቶማስም። #ጌታዬ #አምላኬም ብሎ መለሰለት።

29፤ ኢየሱስም። ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው።

ἀπεκρίθη Θωμᾶς καὶ εἶπεν #αὐτῷ#κύριός μου καὶ ὁ #θεός μου.( ho Kyrios mou kai ho Theos mou)

"28 And Thomas answered and said unto #him, The #Lord of me and The #God of me."
(John 20:28)

ከላይ ያነበብነውን ፅሁፍ በ አጭሩ ስንገልፅ
1. ቶማስ እየሱስን ጌታዬ እና #አምላኬ(θεός) ብሎ ጠራው
2. እየሱስም ቶማስ ለሱ የሰጠውን ስም (ጌታና #አምላክ) ተቀበለ፦ (…ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው)

3. ስለዚህ እየሱስ #አምላክ ነው ማለት ነው።

ይሁን እንጂ ሙሓመዳውያን ይህንን ክፍል ለማፍረስ አሁንም ልክ ቲቶ 2:13 ላይ እንዳነሱት ግራንቪል ሻርፕ ባስቀመጠው ሕግ ይሟገታሉ።  የሚያሳዝነው ግን የ ግራንቪል ሻርፕ ሕጎችን እንኳን ማወቅ ይቅርና ክፍሉን ራሱ እንደላጠኑ ያሳውቅባቸዋል።

የ ሻርፕ ስድስተኛው ሕግ

የ ግሪክ ቋንቋ ስኮላር ግራንቪል ሻርፕ እራሱ በ 1798 "The"( ὁ) የተሰኘች definite article አጠቃቀም ዙሪያ ላይ ባሳተመው መፅሓፍ ውስጥ ስድስተኛው ሕግ ላይ ቀጥሎ ያለውን ሕግ ፅፏል።

"ሁለት ተመሳሳይ ሙያ (same case) ያላቸው ስሞች
 καὶ (እና) በሚለው መስተፃምር ተያይዞ ግን በ ሁለቱም ስሞች ፊትለፊት 'ὁ' 'The' ከገባ፣ ሁለቱ ስሞች ሁለት የተለያዩ አካላትን ይገልፃሉ።... ነገር ግን ሕጉን የሚገድቡ ቅድመ ሁኔታዎች አሉ።

1. የ አረፍተ ነገሩ አውድ
2. ከ አረፍተ ነገሩ ፊትለፊት ሁለቱም ስሞች ለ አንድ አካል መሆኑን የሚያሳይ ገላጭ ካለ (e.g. pronoun) ሁለቱም ስሞች ለ አንድ አካል( person) መሆኑን ያሳያል።

ምሳሌ፦  ራእይ 1:8

" ያለውና የነበረው የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ። አልፋና ዖሜጋ እኔ ነኝ ይላል።"
"Ἐγώ εἰμι #τὸ Ἄλφα καὶ #τὸ Ὦ,.."
I am #The Alpha and #The Omega

በዚህ ምሳሌ ላይ 'አልፋ' ፊትለፊት እንዲውም ደግሞ 'ኦሜጋ' ፊትለፊት "THE" የሚለው አርቲክል ገብቷል። ነገር ግን ሁለቱም "እየሱስን" ለመግለፅ እንጂ 'አልፋ' እየሱስን ገልፆ 'ኦሜጋ' ደግሞ አብን ለመግለፅ አልገባም። ምክኒያቱም፦
1. Ἐγώ (እኔ፣ I) የሚለው personal/possessive pronoun Nominative ሲሆን ሁለቱ ስሞች (አልፋና ኦሜጋ) አንድን አካል (እየሱስን) እንደሚገልፁ ያሳያል።
2. አውዱም (context) እየሱስ እረሱን፣ማንነቱን ለመግለፅ የተጠቀመበት እንደሆነ ግልፅ ነው።

በተመሳሳይ ሙግት የዮሓኒስ ወንጌል 20:28ን እንመልከት

#αὐτῷ#κύριός μου καὶ ὁ #θεός μου

"28 And Thomas answered and said unto #him, The #Lord of me and The #God of me."

በዚህ ክፍል በ ሁለቱም ስሞች ፊትለፊት  (κύριός(ጌታ) እና (θεός) ) ' Ὁ' "The" ገብታለች። ስለዚህ እውነት ሙስሊሞቹ እንደሚሉት "ጌታ" የሚለው ለ እየሱስ ሲሆን " አምላክ" የሚለው ደግሞ ለ አብ ነውን??

በ እርግጥ ይህንን ሙግት የሚያቀርበው ከንቱ ተቺ፣ወይ የ ሕጉን ቅድመ ሆኔታዎች ባለየ አልፎታል ወይም ሕጉን አላጠናም።

መልሱ 'በ ፍፁም አይደለም' ነው። ግራምቪል እራሱ በ መፅሓፉ ገጽ 14-16 ላይ የዮሓኒስ 20:28ን ሰዋ ሰው ሲያብራራ ሁለቱም ስሞች((κύριός(ጌታ) እና (θεός) ) ለ አንድ person እሱም #ለእየሱስ እንደሆነ ማስረጃ አቅርቧል።

1. αὐτῷ( said unto #him; 'አለው') የሚለው personal/possessive pronoun dative ሲሆን፣ ሁለቱም ስሞች (ጌታ እና አምላክ)የሚገልፁት አንድን person እሱም #እየሱስን እንደሆነ ያሳያል። ልብ በል " dative case(ሙያ)" መሆኑ አረፍተ ነገሩ ላይ ችግር አያመጣም።ምክኒያቱም ሕጉ ተመሳሳይ ሙያ እንዲሆኑ የጠየቀው ለ ስሞቹ( nouns) እንጂ ለ pronoun አይደለም።

2. የ ክፍሉ አውድ የሚነግረን ቶማስ ለ እየሱስ ለራሱ ይህንን ንግግር እያደረሰ ስለሆነ ሁለቱም ስሞች እየሱስን የሚገልፁ ናቸው።

ልብ በሉ፤ ይህ ደካማ ተቺ፣ ሙግቱን ያቀረበው ግራንቪል ሻርፕን ምንጭ (reference) አድርጎ ነው። ግን ሒደን ግራንቪል እራሱ በዚህ ክፍል ላይ (ዮሓኒስ 20:28) የሰጠውን ማብራሪያ ስናነብ " ክፍሉ እየሱስን" "አምላክ" እንደሚል ተብራርቶ እናገኛለን።  ለዛም ነው ይህንን ኡስታዝ ነኝ ባይ "ከንቱ" ያልነው።

ግራንቪል በራሱ እጅ የፃፈውን ከታች በፎቶ አያይዝላቹሓለው። አንብቡት!!

እየሱስ ለዘላለም ጌታ ነው!!

" እንግዲህ። በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ አልኋችሁ፤ እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁና አላቸው።"
(የዮሐንስ ወንጌል 8:24)

Reference

Remarks on The Uses of the Definitive Article  in the Greek text of Of the New Testament, Granville Sharp; page 14-16
@Jesuscrucified
@Jesuscrucified
ዮሓኒስ 1:1 ክፍል ሁለት

ዮሓኒስ 1፣ ክፍል 1 ስር "ሎጎስ" ማለት ምን ማለት እንደሆነና ዮሓኒስ ለምን እንደተጠቀመው አይተናል።  አሁን ደግሞ፣ የ ዓረፍተ ነገሩ አወቃቀር እንዴት እየሱስ እና አብ ሁለት የተለያዩ አካል ግን አንድ መሎኮት እንደሆኑ የሚያስተምረን ክፍል የምናይ ይሆናል።

ዮሓኒስ 1:1
Ἐν ἀρχῇ ἦν ὁ Λόγος, καὶ ὁ Λόγος ἦν πρὸς τὸν Θεόν, καὶ Θεὸς ἦν ὁ Λόγος.
(En arche en ho logos, kai ho logos en pros ton theon, Kai theos en ho logos)

ሙግታችን የሚሆነው የመጨረሻዋ ዓ.ነገር ላይ ነው " #Kai_theos_en_ho_logos"። በዚህ አረፍተ ነገር ላይ "ho" የምትለው ግሪክ አርቲክል (በ ኢንግሊዘኛ 'The') የገባቺው ከ "logos" ፊትለፊት ብቻ ነው። "Theos" ፊትለፊት አልገባችም። ይህ ነገር ደግሞ በ ግሪክ ሰዋሰው ውስጥ ትልቅ ትርጉም አለው። ምን ማለት እንደሆነ የታላቁን የግሪክ ስኮላር የሮበርትሰንን ማብራሪያ ልስጣቹ።

Robertson Grammar pp 766-768
"ዮሓኒስ፣ kai theos en ho logos(#The word was God) ብሎ ሲፅፍ በምክኒያት ነው። ምክኒያቱም 'theos' ከሚለው ቃል ፊትለፊትም "'ho' አስገብቶ ቢሆን ኖሮ (ወይም kai HO theos en Ho logos)(The word was The God) ብሎ ቢፅፍ ኖሮ፣ "ሳቤሊያኒዝም"(Sabellianism) የተሰኙ መናፍቃንን ይደግፍ ነበር። ምክኒያቱም 'ho' ከሁለቱም ፊትለፊት ከገባች፣ ሁለቱ (theos እና logos) የተለያዩ አካል አይደሉም ማለት ነው። ይሄ ማለት "አብም" "ወልድም"  አንድ አካል ናቸው፣ ሁለት ስም ተሰጥቶት ነው እንጂ እንደማለት ነው። በሌላ ቋንቋ፣ "ቃልም እግዚያብሔር ነበር" የሚለውን ቦታ አቀያይረን "እግዚያብሔርም ቃሉ ነበር" ማለት በተቻለ ነበር። ይሄ ደግሞ እየሱስና አብ የሚባሉ ሁለት አካል የሉም እንደማለት ነው።  ነገር ግን፣ ዮሓኒስ ይሄን ትርጉም እንዳንሰጥ "ho" የሚለውን አርቲክል ከ 'ሎጎስ' ፊትለፊት ብቻ አስገባ። ይሄ ማለት ቦታ አቀያይሮ " እግዚያብሔርም ቃሉ ነበር" "ወይም ደግሞ "ቃሉ የ እግዚያብሔር የ ይሁን ቃል ነው" ማለት #በፍፁም_አይቻልም ማለት ነው።  ይህ ማለትም "ሎጎስ እራሱ ከ ዘላለም ጀምሮ እግዚያብሔር ነበር" ማለት ነው። በምሳሌ እንይ:
1. John 4:24- God is Spirit "እግዚያብሔር መንፈስ ነው" "#Pneuma_ho_theos
በዚህ ክፍል ላይ "ho" የገባቺው ከ "theos" ፊትለፊት ብቻ ነው። ስለዚህ፣ ቦታ አቀያይሮ "መንፈስ እግዚያብሔር ነው" ማለት አይቻልም።
2.  1 john 4:16- ho theos agape estin ( እግዚያብሔር ፍቅር ነው)። እዚህም ላይ ቦታ አቀያይሮ " ፍቅር እግዚያብሔር ነው" ማለት አይቻልም።

ስለዚህ፣ ዮሓኒስ በግልፅ እንዳሳየን ከሆነ "ሎጎስ"(እየሱስ) ከ እግዚያብሔር አብ የተለየ አንድ personality (ህልውና ወይም አካል) እንደሆነና ይህ አካል (ሎጎስ ) ከ "አብ" ጋር ዘላለማዊ የሆነ አንድ "መሎኮት" እንደሆኑ ( ምክኒያቱም አብም ወልድም እዚህ ክፍል ላይ "Theos" "እግዚያብሔር" ተብሏል። ነገር ግን እግዚያብሔሮች ወይም 'ሁለተኛው እግዚያብሔር' አልተባሉም። መሎኮት አንድ ነውና።)
ልብ በሉ፣ ዮሓኒስ ሲፅፍ "logos en ho theos" ብሎ ከ "theos" ፊትለፊት ብቻ ho አስገብቶ ቢሆን ኖሮ፣ ትርጉሙ " እግዚያብሔር ቃል ነበር" ይሆን ነበር። ሙስሊሞቹንም ደግፎ " እየሱስ በ አካል የተለየ አምላክ አይደለም" ተብሎ ይሰበክ ነበር። አሁን ግን ዮሓኒስ በ አረፍተ ነገር እወቃቀሩ የሙስሊሞችንም ሆነ የሌሎች የክርስቶስ ተቃዋሚ ተቋሞችን ተስፋ አጨልሞባቸዋል።

ክፍል ሶስት ይቀጥላል...
@Jesuscrucified
@Jesuscrucified
ኢስላም ሰላም ነው??

በኢንዶኔዢያ ሁለት ፍቅረኛሞች (እድሜ 18) ስለተቃቀፉ ብቻ በአደባባይ ሲገረፉ!!

#The_Religion_of_Peace ladies and gentlemen

Watch "World News - Teens thrashed for having a cuddle, breaking Indonesia's Sharia law" on YouTube
https://youtu.be/qlA__EaEKM0