ግጥም ብቻ 📘
67.4K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
Forwarded from ሥዕል ብቻ © (👋ገብርዬ)
ሰላም ጤና ይስጥልኝ. አርቲስት #በረከት_ግርማ (አቢቹ) እባላለው የአዲስ አበባ ነዋሪ ስሆን የተለያዩ የኪነ #ቅርፅ እና ኪነ #ቅብ ስራዎችን እሰራለው። ስራዎቼን @artbekiyechalal ገፅ ውስጥ በመቀላቀል እንድትጎበኙልኝ በ አክብሮት ጠይቃለው።.................

@artbekiyechalal @artbekiyechalal

አመሰግናለው!!

@seiloch @seiloch
*በድጋሜ የቀረበ*

////ጎዳናው ይገርማል////
#በረከት_በላይነህ

ይገርማል መንገዱ
እግረኛው ይገርማል

ሸራ ጫማ ባ'ይነት
በነጫጭ ካልሲ
በሲኪኒ ሱሪ
ከመምህሩ ጋራ
አይስክሬም ሚልስ
የሀይስኩል ተማሪ
.
ፀባይኛ ወጣት
ጃንቦ ተከልሎ
በምርቃና ሆኖ
ሀሳብ የሚፈትል
አንዲት ሙ......ደኛ እናት
በ'ድሜ ከልጆቼ አንሳለው የምትል
ፒዛውን የሚገምጥ
ጭማቂ የሚመጥ
አራዳ አባወራ
በሚስቱ ትከሻ
በልጆቹ ምላስ
ቅምጥ የሚጣራ
.
አንድ ፍሬ ሴቶች
በተገዛ ቅንድብ
በተገዛ ፀጉር በተገዛ ጥፍር
በውሰት ወዘና የተብለጨለጩ
ማኪያቶ ከበው
ለውስኪ ሚንጫጩ
ጅናም ጅንሳም ወንዶች በሴቶች ጫጫታ የሚቁለጨለጩ
.
ይገርማል ጎዳናው ይገርማል መንገዱ....
.
ድንቡሽቡሽ ህፃናት
በቶም ኤንድ ጄሪ ሱስ
ቀልባቸው የከሳ
በአይፎኑ አጮልቆ
ያንጀሊናን ከንፈር የሚስም ጎረምሳ
.
ቀውጢ ዳያስፖራ
.
የሎቲው የቁምጣው የቲሸርቱ ጥለት የተንዘረፈፈው
አማርኛ ሲሸሽ "what's happen" የጠለፈው
.
ነቄ ብላቴና
.
ከዮፍታዬ ቀዬ
ካ'ዲስ አለማየሁ
ከመዝገቡ መንደር
የአዲስ አ'ባ ጥሪ
በቁምጣ ያበረረው
ከቅኔ ተጣልቶ
ከግዕዝ ተኳርፎ ሎተሪ ሚያዞረው
.
ፀዴ ብላቴና
.
ከባላገር ዘመን
ከጨለማ ዘመን
ወደ ብርሃን ጥግ ተሸጋገርኩ ብሎ
በሸንኮራ ምርኩዝ ከተማ ሚያካልል መቋሚያውን ጥሎ
ነብሱ እየሰለለች
በከተሜነት ወግ ባ'ራዳነት ልምሻ
ሲያዘግም የሚውል
ሊስትሮውን ጭኖ በታቦት ትከሻ
.
ፎቆቹ
.
በመስታወት ቁመት በቆርቆሮ ገፆች
ባ'ልሙኒየም ጥራዝ የተብረቀረቁ
የጌቶቻቸውን እድሜ ሚያሳብቁ
ሁሉም........ ሁሉም......ሁሉም ጥግ ናቸው
ለወደቀ ወገን ይራራል ልባቸው
.
ሁሉም
...... ሁሉም
.
ከዘለለት ጥድፊያ
ከሰርክ ውጣ ውረድ በተረፈች አንጀት
ለወደቀ ወገን ምርኩዝ ማበጃጀት
ሁሉም...... ሁሉም ይችላሉ
ስለ'ግዚአር ላለ ይመፀውታሉ
.
እኔ ግን........ እኔ ግን .........ቆጥራለው
የ'ድሜ ክቡር ጀንበር
በጎዳና ፅልመት ሲዋጥ አስተውላለው
ጡረታ መንገድ ዳር ሲከፈን አያለው
.
ቆጥራለው.....ቆጥራለው
.
ቆጥራለው አዛውንት
በየአቀበቱ በየቁልቁለቱ
ማረፊያ ፍለጋ የሚንከራተቱ
ቆጥራለው አዛውንት ከልጆቻቸው ፊት
የልመና መዝገብ የገለጡ አሮጊት
ቆጥራለው በየመንገዱ ዳር
እርጅና ሙሽራው ለምፅዋት ሲዳር
ቆጥራለው በየሸንተረሩ በየተፋሰሱ
አቀርቅሮ ሲያዘግም እርጅና ሞገሱ
ቆጥራለው በ'ያደባባዩ
የሽማግሌ አይኖች የልጅ ፊት እያዩ
ቆጥራለው በየሰርጣሰርጡ
በልመና ጉልበት ከሞት ሲፋጠጡ
የ'ርጅና መዳፎች እሾህ ሲጨብጡ
.
ቆጥሬ..... ቆጥሬ.......ቆጥሬ
በለማኝ አዛውንት ብዛት ተሳክሬ
የማሰንበቻ ስንቅ ከኪሴ ቆንጥሬ
ያፅድቆቴን ዋጋ በሳንቲም መንዝሬ
ባ'ዛውንት ምርቃት ከሀገር ከቀዬው ትርፌን ሳመሳስል
በጎዳናው ቀለም ፃድቅ መልኬን ስስል
ጎልቶ ሚታየኝ ግን የሚያሳፍር ምስል
በቀላል ጥያቄ የነተበ ምስል
.
ጥያቄ
.
የዲጄ ኳኳታ የደናሽ ጋጋታ
የድራፍት እርካታ ያ'ረቄ ድንፋታ
ባጣበበው መንገድ
እንደምን ይቻካል
ላ'ያት ሳንቲም ሰጥቶ በ'ርካታ መራመድ?
.
ለወጣት ሹክሹክታ ለገደል ዝምታ
ላስመሳይ ጫጫታ ላድርባይ እሪታ
በተሰራ መንገድ
እውነት ቀላል ነው ወይ
ላ'ያት ሳንቲም ሰቶ በ'ርካታ መራመድ?
.
ለቡቲክ ሰልፈኛ ለካፌ 'ድምተኛ
ለውስኪ ጭሰኛ ለበርገር ምርኮኛ
በተሰራ መንገድ
እንደምን ይቻላል
ላ'ያት ሳንቲም ሰቶ በ'ርካታ መራመድ?
.
አያት....አያት...አያትነት ማለት
በደማቅ አሻራ የሸመኑት ጥለት
ለተራኪ እድሜ የተሰጠ አንደበት
ባ'ባት በ'ናት ፅናት የማይደክም ጉልበት
በልጅ ልጅ መነፅር የማያረጅ ውበት
በልጅ ልጆች ጥበብ የሚታደስ እውቀት
.....................................የሚታደስ እውነት
አያት ሆኑ ማለት
ድርብ አባትነት
ድርብ እናትነት
.
በተለይ እዚህማ.......
በዚህች አይነት ሀገር
ጎጆዋን ላቆመች
በተጋድሎ ካስማ
ባርበኝነት ማገር
በዚህች አይነት ሀገር
ጥያቄና መልሷን
ባ'ዛን በቅዳሴ በምትሰራ መንደር
በዱአ በፀሎት
በምናኔ ምርኩዝ በከረመች ሰፈር
የአያትነት ዋጋው በልኩ ቢሰፈር
ለሳንቲም ምርቃት ባልተሻማን ነበር!
.
ታሪክ በመዳፉ ስላደላደለው
ሁሉም ኢትዮጵያዊ ንጉስ አያት አለው
የልጅ ልጆች ስባት ባያመነምነው
ያያቶቻችን መልክ ሁሌም አንድ አይነት ነው
.
እላለው... እላለው....
.
የልጆች ምፅዋት ያ'ያቶች ልመና
ያ'ባቶች ግርግር በሞላው ጎዳና
መንገዱ አይልቅም
ጎዳናው አያልቅም
ይሰፋል ይረዝማል ይሄዳል ይጓዛል
እግረኛው ሞኝ ነው
ሳንቲሙን ዘርዝሮ
ከወደቁ አዛውንት ምርቃት ይገዛል
.
መንገዱ ያስፈራል
መንገዱ ይጨንቃል
ልጆች ሳቅ ሲያንቃቸው
አያት እምባ ይጨምቃል
መንገዱ ያሰጋል መንገዱ ያረጃል
ከዘናጭ ልጆች ጎን እርዛት ያዘለ አያት ይወለዳል
.
ሰጪ ካለቀሰ ተበዳሪ ስቆ
ጌታ ከለመነ አማኙ 'ግር ወድቆ
ልዑል ከዘመረ ንጉሱ ተዋርዶ
ገፁ ተመሳቅሎ ሽፋኑ ካማረ
ወለሉ ተንቆ ምንጣፍ ከከበረ
ባ'ገርኛ ስሌት ማነው ያልከሰረ?
.
እላለው........እላለው
.
ከየጎዳናው ገፅ ጥያቄ አነሳለው
ጥያቄ እጥላለው
እርጅና ለማምሻው ጎዳናን ካመነ
አያት ከልጅ ልጁ ሳንቲም ከለመነ
ባገርኛ ስሌት ማነው ያልመከነ?
.
በ'ግዚኦታ ዘመን በምዕላ ዘመን
እመንገድ ዳር ወድቆ ትራፊ መለመን
በጥሞና ዘመን የሚያስቡት ማጣት
በማውረሻ እድሜ የሚሰጡት ማጣት
በማልበሻ ዘመን በ'ርዛት መቀጣት
በለጋሽነት ወቅት በማጉረሻ ዘመን
በጥማት መገረፍ በርሀብ መመንመን
ከሆነ እጣችን
ይጠየቅ ትርጉሙ የልጅነታችን
ይፈተሽ መንገዱ የልጅ ልጆቻችን

ግድ የለም እንመን

እንመን

በሰውኛ ስሌት ውጤቱ ሲሰራ
ትውልድ ያደኸያል ያያቶች ኪሳራ
በልጅ ልጆች ዓለም
እንደጉድ ቢደለቅ ቢዘመር ቢዘፈን
አባት ይወራጫል ባ'ያቶች መታፈን
.
አባት ሆይ
.
ለልጆችህ ርዕዮት
ትላንቱን የረሳ ተስፋ ሲደራረት
ህልሜ ነው ይልሀል ያ'ያቶቹ ቅዠት
ከልጅህ አንደበት
ቋንቋ እንደዶፍ ቢዘንብ
ትርጉም ቢንፎለፎል ሺ ቃላት ቢጎርፍም
የልጅ ልጅ አግባቢ ግማሽ ገፅ አይፅፍም
ከልጆችህ ባህር
አሳ የሚያጠግቡ ለአሳ ሚስማሙ
እፅዋት ተክሎች
እንደጉድ ቢራቡ እንደጉድ ቢያብቡ
ገበታው አይሞላም ተቀዷል መረቡ
.
ግድ የለም እንመን........እንመን
.
የስኬት ክብደቱ
የምቾት አይነቱ
የነገ ውበቱ ባሻው ቋት ቢለካ
በምንም ቢሰፈር ባሻው ቃል ቢነገር
ጀግና ልጅ አትወልድም
አያቶቿን ገድላ የምትሸልል ሀገር
.
ከፎቆቹ ጥላ....
ከያስፓልቱ ገላ ሲታተም ድምቀቴ
በመስታወት አጀብ ሲጠገን ጉልበቴ
ይኸው አነበብኩት
አያቶቼ ፊት ላይ ተፅፏል ሽንፈቴ
በመኪና ብዛት
በመስታወት አይነት ሲለካ ፍጥነቴ
በግንብ አጥር መአት
በፎቆች ጋጋታ ሲሰላ ስኬቴ
ይኸው ይታየኛል
አያቴ ገፅ ላይ ተስሏል ውድቀቴ
።።።።።።።።።።።።።ተስሏል ሽንፈቴ!

@getem
@getem
@lula_al_greeko
👍1
ጎዳናው ይገርማል?!

ጋዜጠኛ፣ ገጣሚና ደራሲ ~ #በረከት_በላይነህ

#ETHIOPIA | ይገርማል መንገዱ
እግረኛው ይገርማል

ሸራ ጫማ ባ'ይነት
በነጫጭ ካልሲ
በሲኪኒ ሱሪ
ከመምህሩ ጋራ
አይስክሬም ሚልስ
የሀይስኩል ተማሪ
.
ፀባይኛ ወጣት
ጃንቦ ተከልሎ
በምርቃና ሆኖ
ሀሳብ የሚፈትል
አንዲት ሙ......ደኛ እናት
በ'ድሜ ከልጆቼ አንሳለው የምትል
ፒዛውን የሚገምጥ
ጭማቂ የሚመጥ
አራዳ አባወራ
በሚስቱ ትከሻ
በልጆቹ ምላስ
ቅምጥ የሚጣራ
.
አንድ ፍሬ ሴቶች
በተገዛ ቅንድብ
በተገዛ ፀጉር በተገዛ ጥፍር
በውሰት ወዘና የተብለጨለጩ
ማኪያቶ ከበው
ለውስኪ ሚንጫጩ
ጅናም ጅንሳም ወንዶች በሴቶች ጫጫታ የሚቁለጨለጩ
.
ይገርማል ጎዳናው ይገርማል መንገዱ....
.
ድንቡሽቡሽ ህፃናት
በቶም ኤንድ ጄሪ ሱስ
ቀልባቸው የከሳ
በአይፎኑ አጮልቆ
ያንጀሊናን ከንፈር የሚስም ጎረምሳ
.
ቀውጢ ዳያስፖራ
.
የሎቲው የቁምጣው የቲሸርቱ ጥለት የተንዘረፈፈው
አማርኛ ሲሸሽ "what's happen" የጠለፈው
.
ነቄ ብላቴና
.
ከዮፍታዬ ቀዬ
ካ'ዲስ አለማየሁ
ከመዝገቡ መንደር
የአዲስ አ'ባ ጥሪ
በቁምጣ ያበረረው
ከቅኔ ተጣልቶ
ከግዕዝ ተኳርፎ ሎተሪ ሚያዞረው
.
ፀዴ ብላቴና
.
ከባላገር ዘመን
ከጨለማ ዘመን
ወደ ብርሃን ጥግ ተሸጋገርኩ ብሎ
በሸንኮራ ምርኩዝ ከተማ ሚያካልል መቋሚያውን ጥሎ
ነብሱ እየሰለለች
በከተሜነት ወግ ባ'ራዳነት ልምሻ
ሲያዘግም የሚውል
ሊስትሮውን ጭኖ በታቦት ትከሻ
.
ፎቆቹ
.
በመስታወት ቁመት በቆርቆሮ ገፆች
ባ'ልሙኒየም ጥራዝ የተብረቀረቁ
የጌቶቻቸውን እድሜ ሚያሳብቁ
ሁሉም........ ሁሉም......ሁሉም ጥግ ናቸው
ለወደቀ ወገን ይራራል ልባቸው
.
ሁሉም
...... ሁሉም
.
ከዘለለት ጥድፊያ
ከሰርክ ውጣ ውረድ በተረፈች አንጀት
ለወደቀ ወገን ምርኩዝ ማበጃጀት
ሁሉም...... ሁሉም ይችላሉ
ስለ'ግዚአር ላለ ይመፀውታሉ
.
እኔ ግን........ እኔ ግን .........ቆጥራለው
የ'ድሜ ክቡር ጀንበር
በጎዳና ፅልመት ሲዋጥ አስተውላለው
ጡረታ መንገድ ዳር ሲከፈን አያለው
.
ቆጥራለው.....ቆጥራለው
.
ቆጥራለው አዛውንት
በየአቀበቱ በየቁልቁለቱ
ማረፊያ ፍለጋ የሚንከራተቱ
ቆጥራለው አዛውንት ከልጆቻቸው ፊት
የልመና መዝገብ የገለጡ አሮጊት
ቆጥራለው በየመንገዱ ዳር
እርጅና ሙሽራው ለምፅዋት ሲዳር
ቆጥራለው በየሸንተረሩ በየተፋሰሱ
አቀርቅሮ ሲያዘግም እርጅና ሞገሱ
ቆጥራለው በ'ያደባባዩ
የሽማግሌ አይኖች የልጅ ፊት እያዩ
ቆጥራለው በየሰርጣሰርጡ
በልመና ጉልበት ከሞት ሲፋጠጡ
የ'ርጅና መዳፎች እሾህ ሲጨብጡ
.
ቆጥሬ..... ቆጥሬ.......ቆጥሬ
በለማኝ አዛውንት ብዛት ተሳክሬ
የማሰንበቻ ስንቅ ከኪሴ ቆንጥሬ
ያፅድቆቴን ዋጋ በሳንቲም መንዝሬ
ባ'ዛውንት ምርቃት ከሀገር ከቀዬው ትርፌን ሳመሳስል
በጎዳናው ቀለም ፃድቅ መልኬን ስስል
ጎልቶ ሚታየኝ ግን የሚያሳፍር ምስል
በቀላል ጥያቄ የነተበ ምስል
.
ጥያቄ
.
የዲጄ ኳኳታ የደናሽ ጋጋታ
የድራፍት እርካታ ያ'ረቄ ድንፋታ
ባጣበበው መንገድ
እንደምን ይቻካል
ላ'ያት ሳንቲም ሰጥቶ በ'ርካታ መራመድ?
.
ለወጣት ሹክሹክታ ለገደል ዝምታ
ላስመሳይ ጫጫታ ላድርባይ እሪታ
በተሰራ መንገድ
እውነት ቀላል ነው ወይ
ላ'ያት ሳንቲም ሰቶ በ'ርካታ መራመድ?
.
ለቡቲክ ሰልፈኛ ለካፌ 'ድምተኛ
ለውስኪ ጭሰኛ ለበርገር ምርኮኛ
በተሰራ መንገድ
እንደምን ይቻላል
ላ'ያት ሳንቲም ሰቶ በ'ርካታ መራመድ?
.
አያት....አያት...አያትነት ማለት
በደማቅ አሻራ የሸመኑት ጥለት
ለተራኪ እድሜ የተሰጠ አንደበት
ባ'ባት በ'ናት ፅናት የማይደክም ጉልበት
በልጅ ልጅ መነፅር የማያረጅ ውበት
በልጅ ልጆች ጥበብ የሚታደስ እውቀት
.....................................የሚታደስ እውነት
አያት ሆኑ ማለት
ድርብ አባትነት
ድርብ እናትነት
.
በተለይ እዚህማ.......
በዚህች አይነት ሀገር
ጎጆዋን ላቆመች
በተጋድሎ ካስማ
ባርበኝነት ማገር
በዚህች አይነት ሀገር
ጥያቄና መልሷን
ባ'ዛን በቅዳሴ በምትሰራ መንደር
በዱአ በፀሎት
በምናኔ ምርኩዝ በከረመች ሰፈር
የአያትነት ዋጋው በልኩ ቢሰፈር
ለሳንቲም ምርቃት ባልተሻማን ነበር!
.
ታሪክ በመዳፉ ስላደላደለው
ሁሉም ኢትዮጵያዊ ንጉስ አያት አለው
የልጅ ልጆች ስባት ባያመነምነው
ያያቶቻችን መልክ ሁሌም አንድ አይነት ነው
.
እላለው... እላለው....
.
የልጆች ምፅዋት ያ'ያቶች ልመና
ያ'ባቶች ግርግር በሞላው ጎዳና
መንገዱ አይልቅም
ጎዳናው አያልቅም
ይሰፋል ይረዝማል ይሄዳል ይጓዛል
እግረኛው ሞኝ ነው
ሳንቲሙን ዘርዝሮ
ከወደቁ አዛውንት ምርቃት ይገዛል
.
መንገዱ ያስፈራል
መንገዱ ይጨንቃል
ልጆች ሳቅ ሲያንቃቸው
አያት እምባ ይጨምቃል
መንገዱ ያሰጋል መንገዱ ያረጃል
ከዘናጭ ልጆች ጎን እርዛት ያዘለ አያት ይወለዳል
.
ሰጪ ካለቀሰ ተበዳሪ ስቆ
ጌታ ከለመነ አማኙ 'ግር ወድቆ
ልዑል ከዘመረ ንጉሱ ተዋርዶ
ገፁ ተመሳቅሎ ሽፋኑ ካማረ
ወለሉ ተንቆ ምንጣፍ ከከበረ
ባ'ገርኛ ስሌት ማነው ያልከሰረ?
.
እላለው........እላለው
.
ከየጎዳናው ገፅ ጥያቄ አነሳለው
ጥያቄ እጥላለው
እርጅና ለማምሻው ጎዳናን ካመነ
አያት ከልጅ ልጁ ሳንቲም ከለመነ
ባገርኛ ስሌት ማነው ያልመከነ?
.
በ'ግዚኦታ ዘመን በምዕላ ዘመን
እመንገድ ዳር ወድቆ ትራፊ መለመን
በጥሞና ዘመን የሚያስቡት ማጣት
በማውረሻ እድሜ የሚሰጡት ማጣት
በማልበሻ ዘመን በ'ርዛት መቀጣት
በለጋሽነት ወቅት በማጉረሻ ዘመን
በጥማት መገረፍ በርሀብ መመንመን
ከሆነ እጣችን
ይጠየቅ ትርጉሙ የልጅነታችን
ይፈተሽ መንገዱ የልጅ ልጆቻችን

ግድ የለም እንመን

እንመን

በሰውኛ ስሌት ውጤቱ ሲሰራ
ትውልድ ያደኸያል ያያቶች ኪሳራ
በልጅ ልጆች ዓለም
እንደጉድ ቢደለቅ ቢዘመር ቢዘፈን
አባት ይወራጫል ባ'ያቶች መታፈን
.
አባት ሆይ
.
ለልጆችህ ርዕዮት
ትላንቱን የረሳ ተስፋ ሲደራረት
ህልሜ ነው ይልሀል ያ'ያቶቹ ቅዠት
ከልጅህ አንደበት
ቋንቋ እንደዶፍ ቢዘንብ
ትርጉም ቢንፎለፎል ሺ ቃላት ቢጎርፍም
የልጅ ልጅ አግባቢ ግማሽ ገፅ አይፅፍም
ከልጆችህ ባህር
አሳ የሚያጠግቡ ለአሳ ሚስማሙ
እፅዋት ተክሎች
እንደጉድ ቢራቡ እንደጉድ ቢያብቡ
ገበታው አይሞላም ተቀዷል መረቡ
.
ግድ የለም እንመን........እንመን
.
የስኬት ክብደቱ
የምቾት አይነቱ
የነገ ውበቱ ባሻው ቋት ቢለካ
በምንም ቢሰፈር ባሻው ቃል ቢነገር
ጀግና ልጅ አትወልድም
አያቶቿን ገድላ የምትሸልል ሀገር
.
ከፎቆቹ ጥላ....
ከያስፓልቱ ገላ ሲታተም ድምቀቴ
በመስታወት አጀብ ሲጠገን ጉልበቴ
ይኸው አነበብኩት
አያቶቼ ፊት ላይ ተፅፏል ሽንፈቴ
በመኪና ብዛት
በመስታወት አይነት ሲለካ ፍጥነቴ
በግንብ አጥር መአት
በፎቆች ጋጋታ ሲሰላ ስኬቴ
ይኸው ይታየኛል
አያቴ ገፅ ላይ ተስሏል ውድቀቴ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ተስሏል ሽንፈቴ!
***
@getem
@getem
#jeko
👍3
#እምዬ #ያልታደለች
(በገጣሚ #በረከት #በላይነህ )

እምዬ ያልታደለች
ተመዘኚ ሲሏት ~ መዛኝ ነኝ ትላለች
እምዬ ሰከረች
ልትመዘን ወጥታ ~ መዛኝ ሆና ቀረች!
የቅቤን ስብራት ~ በቅመም ለማከም
በወቀጣ መዛል ~ በድለዛ መድከም
የቅቤን ወለምታ ~ በቅመም ለማሸት
ሲደቁሱ አድረው ~ ሲቀይጡ ማምሸት
የቅቤን ጉብዝና ~ በቅመም ለማትጋት
እያመሱ መዋል ~ እየፈጩ ማንጋት
* * *
ይልቅ ግድ የለሽም !
ለቅቤ ጥፍጥና
ለቅቤ መአዛ
ቅመም ከመደቆስ ~ ቅመም ከማበጠር
ከቅቤያችን በፊት ~ ከብቶቹን ነው ማንጠር
እንስራ ወዝውዞ
በጢሳጢስ ናውዞ
ለቅቤ ከማማጥ ~ ለአይብ ከማማጥ
ከወተቱ በፊት ~ እስቲ ላሟ ትናጥ
ማለቢያ ከማስፋት ~ ማለቢያ ከማጥበብ
ከግቷ አስቀድሞ
ከሆዷ አስቀድሞ ~ ምግቧን ነው ማጠብ
* * *
ለምሽቱ ድምቀት — ቀኑን ሳይበርዙ
እንዲህ ነው ፊተኞች — ‘ሩቅ የሚጓዙ
እንዲህ ነው መስማማት — መግባባት ከዛፉ
ከስር ሳይመትሩ — አይታይም ጫፉ !
* * *
ግራ ነኝ ይለኛል
ቀኝ ነኝ ይለኛል —መሀል ነኝ ይለኛል
ዳሩ ካልተያዘ — መሀል የት ይገኛል?
እውቀት አባ አያልቄ
እውቀት አባ አይፈሬ — ጥያቄ ሲያድለው
ለግራም የራሱ — ግራና ቀኝ አለው
ለቀኝም የራሱ — ቀኝና ግራ አለው
መሃልም ለራሱ — ሌላ መሀል አለው
* * *
እይዉ!
ሰው መጠየቅ ትቷል
ሰው ፍለጋ ትቷል ~ ሰው ማጣጣም ትቷል
ለመንስኤ ዝሏል ~ ለአመክንዮ ታክቷል
በጥድፊያ ሊያስታግስ~የመሰንበት ሱሱን
ጥያቄ ነው ይላል ~ የከሸፈ መልሱን
ነፍስያን ተብትቦ —በስሜት ሰንሰለት
መቀያየጥ ሆኗል —መጠያየቅ ማለት
መመሳሰል ሆኗል —መመላለስ ማለት
* * *
ኩሬ ነው?
ወንዝ ነው?
ሃይቅ ነው?
ባህር ነው? ጎርፍ ነው?
ገባሩ? ጅረቱ? ማእበሉ? ምንጮቹ?
አዞ አለ? አሳ አለ?
.
.
እኮ የምን ጥያቄ ! ~ እኮ የምን ክርክር !
በቃ!
“ዋና ነው!” ይልሽና ~ ከነልብሱ ንክር።
አዎ!
“ዋና ነው!” ይልሻል ~ “አጨብጭቢ!” ይልሻል
“ዋናህስ?” አትበይው
አሽሟጠጠች ብሎ ~ ችሎት ያቆምሻል
ያው!
ችሎቱ የእነሱ — ችሎታው የሌላ
ይልቅ አጨብጭቢ —አዞ እራቱን ይብላ!
ለንክር ጭብጨባ —ለዝፍዝፍ ጭብጨባ
ሆዱ አሳ ሲለው — አዞ ለሚያረባ
* * *
ተመልከች!
ሽንቁራም እውቀትሽ —ንፋሱን ሲነዛ
ከጋላቢሽ ይልቅ —የሚገለብ በዛ
ንፋሳም እውቀትሽ —ውርጩን እየነዛ
ከሚያነደው ይልቅ —የሚያከስለው በዛ
ግልብልብ እውቀትሽ —ወላፈን ደሞዙ
የሚለበለቡት — ከሚበስሉት በዙ።
እይው!
ማእዘን አፍርሶ —ግድግዳ እያደሰ
ወለሉን ሰውቶ —ጣሪያ እየቀለሰ
ቅርንጫፍ ሊያሳምር —ስር እየበጠሰ
እልፍኝ ተደፈረ —አጥር ተገሰሰ
መስማት ጥንቡን —ጣለ ማየት ረከሰ
ቋንቋ መነመነ — ለትርጉም አነሰ
* * *
ቆይ እኔ የምልሽ!
ተፈጥሮ ሂደቷ — እንዲህ ሳይጓደል
ለመሮጥ መንደርደር — ግድ ነበር አይደል?!
ታዲያ! ቀረ እኮ ነው ‘ምልሽ
መንደርደር መመርመር መፈከር መዘርዘር
አኩርፈው የሄዱት — በየት በኩል ነበር?
* * *
የወል ቀማሽ ሁላ
ድፍርስ እየጠጣ — ሽርክት እየበላ
በግርድፍ አኝኮ — ለግርድፍ ተሻምቶ
“ውጫለሁ!” ይልሻል — ወደ ሆዱ ተፍቶ
* * *
የምር ደስ አይልም!
የጥርስን በአንጀት
የጆሮን በምላስ — ʻያፍንጫን በመዳፍ
ግብር እያቀማሙ — ዋጋና ስም መጻፍ
የምር ደስ አይልም!
የልብን ደረት ላይ
የነፍስን ልብስ ላይ— ቀያይጦ በማፍካት
ጣእምን መመርመር — ውበትን መለካት
ደስስስስስ አይልም!
* * *
እምዬ!
አትላፊ አትዳሪ ከእንክርዳድሽ
ይልቅ
ወንፊት ግዢ ለወንፊትሽ
ሰፌድ ግዢ ለሰፌድሽ
* * *
ቀማሽ ሲደራረብ —ጣእም ተቀያየጠ
ባለቤት ሳያጌጥ —ውበት አመለጠ
ከእህሉም አይደለ
ከቅመሙም አይደል
ጨው አንሶም አይደለ
የምላስ ህመም —ነው ጣእም የገደለ
* * *
ምን አረገሽና!
ቀቃዩ ጠባሹ
ከታፊው አማሹ
ወቃጩ ነስናሹ
ለርካሽነትሽ — ይጠየቅ ቀማሹ
ማገዶ ቢራቀቅ
ምጣድ ቢቀያየር — ጋጋሪ ቢንጋጋ
በቀማሽ ልክ ነው —የገበታሽ ዋጋ
* * *
ኧረ ሚዛን! ሚዛን!
ኧረ መዛኝ! መዛኝ!
በልክ የሚሰፍር በልክ የሚገዛኝ!
እንደየቃናችን — ማድመቅ ያላወቀ
ቀማሽ አሳነሰን — እያደባለቀ!!!
====||====

@getem
@getem
@peppa1

(በገጣሚ #በረከት #በላይነህ)
👍1
#እምዬ #ያልታደለች

(በገጣሚ #በረከት #በላይነህ )

እምዬ ያልታደለች
ተመዘኚ ሲሏት ~ መዛኝ ነኝ ትላለች
እምዬ ሰከረች
ልትመዘን ወጥታ ~ መዛኝ ሆና ቀረች!

የቅቤን ስብራት ~ በቅመም ለማከም
በወቀጣ መዛል ~ በድለዛ መድከም
የቅቤን ወለምታ ~ በቅመም ለማሸት
ሲደቁሱ አድረው ~ ሲቀይጡ ማምሸት
የቅቤን ጉብዝና ~ በቅመም ለማትጋት
እያመሱ መዋል ~ እየፈጩ ማንጋት
* * *
ይልቅ ግድ የለሽም !
ለቅቤ ጥፍጥና
ለቅቤ መአዛ
ቅመም ከመደቆስ ~ ቅመም ከማበጠር
ከቅቤያችን በፊት ~ ከብቶቹን ነው ማንጠር
እንስራ ወዝውዞ
በጢሳጢስ ናውዞ
ለቅቤ ከማማጥ ~ ለአይብ ከማማጥ
ከወተቱ በፊት ~ እስቲ ላሟ ትናጥ
ማለቢያ ከማስፋት ~ ማለቢያ ከማጥበብ
ከግቷ አስቀድሞ
ከሆዷ አስቀድሞ ~ ምግቧን ነው ማጠብ
* * *
ለምሽቱ ድምቀት — ቀኑን ሳይበርዙ
እንዲህ ነው ፊተኞች — ‘ሩቅ የሚጓዙ
እንዲህ ነው መስማማት — መግባባት ከዛፉ
ከስር ሳይመትሩ — አይታይም ጫፉ !
* * *
ግራ ነኝ ይለኛል
ቀኝ ነኝ ይለኛል —መሀል ነኝ ይለኛል
ዳሩ ካልተያዘ — መሀል የት ይገኛል?
እውቀት አባ አያልቄ
እውቀት አባ አይፈሬ — ጥያቄ ሲያድለው
ለግራም የራሱ — ግራና ቀኝ አለው
ለቀኝም የራሱ — ቀኝና ግራ አለው
መሃልም ለራሱ — ሌላ መሀል አለው
* * *
እይዉ!
ሰው መጠየቅ ትቷል
ሰው ፍለጋ ትቷል ~ ሰው ማጣጣም ትቷል
ለመንስኤ ዝሏል ~ ለአመክንዮ ታክቷል
በጥድፊያ ሊያስታግስ~የመሰንበት ሱሱን
ጥያቄ ነው ይላል ~ የከሸፈ መልሱን
ነፍስያን ተብትቦ —በስሜት ሰንሰለት
መቀያየጥ ሆኗል —መጠያየቅ ማለት
መመሳሰል ሆኗል —መመላለስ ማለት
* * *
ኩሬ ነው?
ወንዝ ነው?
ሃይቅ ነው?
ባህር ነው? ጎርፍ ነው?
ገባሩ? ጅረቱ? ማእበሉ? ምንጮቹ?
አዞ አለ? አሳ አለ?
.
.
.
እኮ የምን ጥያቄ ! ~ እኮ የምን ክርክር !
በቃ!
“ዋና ነው!” ይልሽና ~ ከነልብሱ ንክር።
አዎ!
“ዋና ነው!” ይልሻል ~ “አጨብጭቢ!” ይልሻል
“ዋናህስ?” አትበይው
አሽሟጠጠች ብሎ ~ ችሎት ያቆምሻል
ያው!
ችሎቱ የእነሱ — ችሎታው የሌላ
ይልቅ አጨብጭቢ —አዞ እራቱን ይብላ!
ለንክር ጭብጨባ —ለዝፍዝፍ ጭብጨባ
ሆዱ አሳ ሲለው — አዞ ለሚያረባ
* * *
ተመልከች!
ሽንቁራም እውቀትሽ —ንፋሱን ሲነዛ
ከጋላቢሽ ይልቅ —የሚገለብ በዛ
ንፋሳም እውቀትሽ —ውርጩን እየነዛ
ከሚያነደው ይልቅ —የሚያከስለው በዛ
ግልብልብ እውቀትሽ —ወላፈን ደሞዙ
የሚለበለቡት — ከሚበስሉት በዙ።
እይው!
ማእዘን አፍርሶ —ግድግዳ እያደሰ
ወለሉን ሰውቶ —ጣሪያ እየቀለሰ
ቅርንጫፍ ሊያሳምር —ስር እየበጠሰ
እልፍኝ ተደፈረ —አጥር ተገሰሰ
መስማት ጥንቡን —ጣለ ማየት ረከሰ
ቋንቋ መነመነ — ለትርጉም አነሰ
* * *
ቆይ እኔ የምልሽ!
ተፈጥሮ ሂደቷ — እንዲህ ሳይጓደል
ለመሮጥ መንደርደር — ግድ ነበር አይደል?!
ታዲያ! ቀረ እኮ ነው ‘ምልሽ
መንደርደር መመርመር መፈከር መዘርዘር
አኩርፈው የሄዱት — በየት በኩል ነበር?
* * *
የወል ቀማሽ ሁላ
ድፍርስ እየጠጣ — ሽርክት እየበላ
በግርድፍ አኝኮ — ለግርድፍ ተሻምቶ
“ውጫለሁ!” ይልሻል — ወደ ሆዱ ተፍቶ
* * *
የምር ደስ አይልም!
የጥርስን በአንጀት
የጆሮን በምላስ — ʻያፍንጫን በመዳፍ
ግብር እያቀማሙ — ዋጋና ስም መጻፍ
የምር ደስ አይልም!
የልብን ደረት ላይ
የነፍስን ልብስ ላይ— ቀያይጦ በማፍካት
ጣእምን መመርመር — ውበትን መለካት
ደስስስስስ አይልም!
* * *
እምዬ!
አትላፊ አትዳሪ ከእንክርዳድሽ
ይልቅ
ወንፊት ግዢ ለወንፊትሽ
ሰፌድ ግዢ ለሰፌድሽ
* * *
ቀማሽ ሲደራረብ —ጣእም ተቀያየጠ
ባለቤት ሳያጌጥ —ውበት አመለጠ
ከእህሉም አይደለ
ከቅመሙም አይደል
ጨው አንሶም አይደለ
የምላስ ህመም —ነው ጣእም የገደለ
* * *
ምን አረገሽና!
ቀቃዩ ጠባሹ
ከታፊው አማሹ
ወቃጩ ነስናሹ
ለርካሽነትሽ — ይጠየቅ ቀማሹ
ማገዶ ቢራቀቅ
ምጣድ ቢቀያየር — ጋጋሪ ቢንጋጋ
በቀማሽ ልክ ነው —የገበታሽ ዋጋ
* * *
ኧረ ሚዛን! ሚዛን!
ኧረ መዛኝ! መዛኝ!
በልክ የሚሰፍር በልክ የሚገዛኝ!
እንደየቃናችን — ማድመቅ ያላወቀ
ቀማሽ አሳነሰን — እያደባለቀ!!!

©በረከት በላይነህ
@getem
@getem
@getem
👍4
ወደድኩሽ .....ጅል እስክሆን
ሄድሽ ደሞ .......ያንን ሰሞን
አንቺዬ
የተነሳሽበት ማልደርስበት መንገድ
ናፍቆትሽን ይዤ ዘላለም ል'ራመድ
ከበደኝ
ቀድሞውንስ መች ቀለለኝ።

ታድያ ይሄን እየሰማሽ
እንደምን ነህ አልሺኝ
እኔማ...
አለው እንደምንም ምንም ባለመሆን
ታውቂው የለ አፍቃሪን ያፈቀረ ሰሞን
አንዲያ ነኝ....

አዎን
የናፍቆቴን መራብ ትውስታ ላይገታው
ዝምብዬ ምኳትን ህመሜን ላይረታው
መጣው ስላልሺኝ ነው አሁንም ምበረታው።
አንቺዬ
ውዬ አድሪያለው እና እስክትመጪ በፆም
ባክሽ ብቅ በዪ እስትንፋሴ እንዳትቆም።

✍️#በረከት_ሐ(@berii34)
@getem
@getem
@getem
👍4122👎5
በይ.አኩርፊ💜
#በረከት_ሐ
የፈገግታሽ አለም ቢኖረውም እውነት
መሳቅ ብቻ አይደለም የሁሉ ሰው ውበት።

አንቺዬ
ሳቅሽንም ተይው ጥርስሽም ይ'ከደን
ድንገት አኩርፊ እና ጉድ ይበል ይህ ዘመን።

#በረከት_ሐ
(
@berii34)
@getem
@getem
@getem
👍2911
በይ.አኩርፊ💜
#በረከት_ሐ
የፈገግታሽ አለም ቢኖረውም እውነት
መሳቅ ብቻ አይደለም የሁሉ ሰው ውበት።

አንቺዬ
ሳቅሽንም ተይው ጥርስሽም ይ'ከደን
ድንገት አኩርፊ እና ጉድ ይበል ይህ ዘመን።

#በረከት_ሐ
(
@berii34)
@getem
@getem
@getem
16👍16
የፍቅርን እንባ የመውደድን እንባ በሳቅሽ አነባው
ፈገግታሽን ልስል ከአፀድሽ ገባው።

አንቺ
አፀድ አለሽ ህይወት የሚዘራ
ህይወት አለሽ አፍቃሪን ሚጠራ..

አጀብ አጀብ ነው ፈገግታሽ
ፈውስ አለሽ አሉ በፍቅር ለነካሽ
... አጀብ

#በረከት_ሐ
(@berii34)

@getem
@getem
@getem
👍179🤩2
ልብህ ከታወረ ......ፅልመት ከወረሰው
እንደምን ቆጠርከው እራስህን እንደሰው?
እንደምን?
እንደማን?
ሰው መሆን ከባድ ነው መሸንገል ህሊናን ።
ይልቅ
ከጠቆረው ቤትህ ሰው መሆንን አስስ
አልያም ከቻልክበት መኖሪያህን አፍርስ
ወዳጄ
የነገሩን ሁሉ ሀቅ እርቆታል ከእውነት አይዋደድ
ዘር......... ከእህል እንጂ ........ከሰው አይዛመድ
ታድያ
ከዚህ ...እግዜሩን ከረሳ ከባከነ ዘመን
ያዩልህን ሳይሆን ያየኸውን እመን
በል ንቃ
በል አሁን ውጣ ጫጫታውን ትተህ
ብራንህን ፈልግ ሽንቁር አበጃጅተህ
በል አሁን ተነስ
ስንኩል ልብህን አቅና
ሰው መምሰል አደለም ሰው መሆን ነው ደህና
             ይቅናህ.....።

               #በረከት_ሐ
(@berii34)
@getem
@getem
@getem
👍4419
.
ናፍቆት ያለ ፍቅር
ገጣሚ ያለ ብእር ፣ እንደምን ይውላሉ
ባንዳች ነገር ታስረው እስከተፈጠሩ።

አየሽ
እንዲያ ነበርን እኛ፣ ምንም ያልጎደለን
አንዳች ነገር ቀልሞ ፣ አንድ ለይ የሳለን
አንድ ለይ ያዋለን።

ደግሞም እንደ ንፋስ ፣ ባህር ውቅያኖሱን
ተራራ እና የብሱን ፣ ነፍሰን እንዳላለፍነው
በነበር እንዲቀር ፣ እግዜር አስኪፅፈው።

እንቺዬ
እንዴት ነበርን ብልሽ
ምን ይሆን ግን መልስሽ?።

እንዳልተዋደድን ፣ እንዳልተፋቀርን
በእግዜርሽ ፣ በሞቴ እንዳልተማማልን
እንዴት ግማሽ ጣዖት
እንዴት ግማሽ ጽላት ሆንን?።
እንዴት?....

#በረከት_ሐ
(@berii34)
@getem
@getem
@getem
👍28😢3🔥2😱2😁1
ረሀብ አምጦት ፣ ማጣት የወለደው
ከሐበሻ ሰማይ ስር ፣ ለቅሶ በዛ ምነው?
ጩኸት በዛ ፣ ረሀብ እና እንባ
ክፋትም አየለ ፣ ቅናት እና ደባ።
እግዜሩም ዝም አለ
ተማፅኖን ዝም አለ ፣ ወይ አይሰጠን ፍቅር
ምስኪኑ አለቀሰ ፣ ከጥቁር ሰማይ ስር።
አስኪ ጠይቋቸው
እስኪ ጠይቋቸው ፣ የጦቢያዬን ልጆች
ዳቦ ሚለምኑ እነዛን ፣ ውብ አይኖች
እንደምን ውለዋል ፣ እንደምን አድረዋል
የዛሬን ባያውቁም ፣ ትናንት አልቅሰዋል።
ነገስ?

                               #በረከት_ሐ
                  (@berii34)
@getem
@getem
@getem
👍38😢1110👎3
"እንቆቅልሽ ፣ ምን አው...ህ/ሽ"

ሰከን ያለ ልብ ፣ በለሆሳስ ሚጓዝ
ደግሞም
ፀጥ ያለች ነብስ ፣ ወደራስ የምትፈስ
ሁካታን የጠላች ፣ ጫጫታን የቀጣች
ከዚህ ሁሉ ፍጡር ፣ ፍጥረት ላለመባል ብቻዋን የከሳች ፣ ብቻዋን የወዛች።
ሁሉን የምታክል ፣ ሁሉን የምትስል
በፊደል ምትደማ ፣ በቃል የምትቆስል
ከውብ ግጥሞች ስንኝ ፣ አንዷን የምትመስል::
ማንናት ?
ማነች ?
በራስ ክራር ስልቷ ትዝታን የቃኘች...
ማነች ?
       ካላወቃቹ እንግዲህ ሀገር ስጡኝ...

                  
#በረከት_ሐ
@getem (@berii34)
@getem
@getem
👍3112👎1🔥1
ቃሉዋን ይዤ ድንገት
ትንሽ ትንሽ እምነት ፣ ያሳየዋት ሰሞን
እቀፈኝ አለችኝ ፣ ከእቅፌ ለመሆን።
አቀፍኳት
ልክ እንደ ወዳጅ እንደ ጓደኛ
አሷ ግን
እንደመውደድ እንደ ፍቅረኛ።
እቅፍ ፣ ጥምጥም ፣ ጋደም አለች
ደግሞም ቀና ብላ ፣ አይኖቼን እያየች
             ትወደኛለህ ብትለኝ
             ቃል አጣው ጨነቀኝ
እኔ...
እኔ...ኡፍፍፍፍፍፍፍፍፍፍ ምን ልበላት ?


                                      #በረከት_ሐ (@berii34)
@getem
@getem
@getem
31👍15👎4😁4
መንገድ ይወስዳል
መንገድ ይመልሳል ብለው ያሉኝ ጊዜ
ጉዞዬን ጀመርኩኝ የያዝኩትን ይዤ።
                             ሁዋላ  
ደ.ከ.መ.ኝ
መ.ረ.ረ.ኝ
አ.ቃ.ተ.ኝ...
ጫፍ የለውም መንገድ  ፣ እስከመች ልጓዘው
ምን ነበር ቀድሞውንስ ፣ ልብን ያፈዘዘው።
ልመለስ ብል እንኳ
ልመለስ ብል እንኳ ፣ እልፍ መንገዶች ታዩኝ
የትኛው ነበረ ይመልሳል ያሉኝ?

                   #በረከት_ሐ ( @berii34 )
@getem
@getem
@getem
👍5534👎4
እድሜ እያላላኝ ፡
ግዜ እየቀጣኝ
ብሸራረፍ እንኳን ፡
አረሳውም መልኳን።
እጇን ...
ትናንት ይመስላል የዳበስኩት፣
መጠበቅ አርቆኝ ያስተዋልኩት።
ደሞ..
የናፈኳት ሰሞን
አመት ቅፅበት ሲሆን
ግዜ ሚዛኑ ሲላወስ
አብራው ምታዘግም የኔ ነብስ
ትታያለች........ደጇን እንዳጠረች...።💔

                            #በረከት_ሐ ( @berii34 )
@getem
@getem
@getem
40👍36😱4🔥3👎1🎉1
ማንነቴን  ባልኩኝ
ቀለሜ ነው ባልኩኝ የእምዬን ሰንደቅ
                 ዛሬ
ለምን ያዝክ ተብዬ ለነብሴ ልሳቀቅ።

ልጠይቅ ሀገሬ ጠይቂ ለምን በይ
ላንቺ መኖራችን
ላንቺ መሞታችን ብኩንነት ነው ወይ?

ቢገባቸው እንጂ
ቢመሰላቸው እንጂ
ቃላት የማይወጣን
ታድያ ለምንድነው
ቀና ባልን ቁጥር ጥይት የማያጣን?!

ለምን በይ ሀገሬ!!!

                                          #በረከት_ሐ( @berii34 )
@getem
@getem
@getem
🔥39👍25👎1
ፍቅር ፡ ያልነካካው
ናፍቆት ፡ ያላቦካው
ንፁ ልብ እንዳለኝ
አሎዳትም እላለሁ ፡ መሄዷ እያመመኝ።

አልወዳትም !!

#በረከት_ሐ(ይሉ) @berii34

@getem
@getem
@getem
🔥2814👍13😢3
ግዜ ጓዙን ጥሎ ፡ ሲያዘግም ተገኘ
አልመሽ ላለላት ፡ ነብስ ጥፋተኛ ሆኖ ፍርድ ቤት ተዳኘ
ፈራጅ እግዜር ነበር ፡ እግዜር ፈራጅ ነበር
ከሳሽም ያቺው ነፍስ ፡ ምስክርም አላት
ሲመሽ እንደምታልፍ ፡ ማን በነገራት።

#በረከት_ሐ(ይሉ) @berii34

@getem
@getem
@getem
33👍13😢6🔥5
.      .ለሷ
ከግጥሞቼ መሀል ፡ አንዱን አበደርኳት
''ናፍቆት'' ከሚል እርስ ፡ ጨምሬ ደገምኳት
                                .  ግን እሷ
ግጥም ፡ ምን ግዷ
ስዕል ፡ ምን ግዷ
ሙዚቃ ፡ ምን ግዷ
ፀጥጥጥ ያለ ፡ ባህር ነው  
ልቦናና ነብሷ።  
                      .    እሷ

         #በረከት_ሐ(ይሉ) @berii34

@getem
@getem
@paappii
21👍9🤩3