ኧረ ሚዛን አምጡ!!!!!
በጀማው መሃከል፤
ሁሉም ወንበር ይዞ፤
ማን ጀባታ ያምጣ ፤
ማን በረካ ያለው ፤
ማን አሚን ባይ ይምጣ ? ማን እንደ ደረጃው ይጎናበስ ቀልቡ??
ቁጢጥ ብለዋል፤
ሊቅና ጃሂሉ ፤
ያለ ማእዳቸው ያለ ወንበራቸው እየተናቸፉ እየተካለቡ፤
እንደትላንትናው፤
ዛሬም ጫጫታ ነው፤
ላይ ታቹ ተዛንፎ ጨምሯል ውካታው ጨምሯል አጀቡ።
ይኸው በዚያ ቀዬ፤
አገር ሙሉ ጀማ፤
እንደጠኔ ገላ እንደ ተሳበ አንጀት ወንበር በመራቡ፤
በነጋ በጠባ ምን ጀማው ቢሞላ፤ ቢደገስ በአህሪቡ፤
ካዳሚ አልተገኘም፤
ሁሉም ጠመጠመ ፤ ሁሉም ካድሙኝ አለ፤ ወጣ ከመደቡ፤
በሰው ይዤሃለሁ፤ የሰው ሚዛን ስጠኝ፤ ወሎ ማር ዘነቡ።
መገን መዛኝ ማጣት!!!
(( ጃ ኖ ))💚💛❤
@getem
@getem
@balmbaras
በጀማው መሃከል፤
ሁሉም ወንበር ይዞ፤
ማን ጀባታ ያምጣ ፤
ማን በረካ ያለው ፤
ማን አሚን ባይ ይምጣ ? ማን እንደ ደረጃው ይጎናበስ ቀልቡ??
ቁጢጥ ብለዋል፤
ሊቅና ጃሂሉ ፤
ያለ ማእዳቸው ያለ ወንበራቸው እየተናቸፉ እየተካለቡ፤
እንደትላንትናው፤
ዛሬም ጫጫታ ነው፤
ላይ ታቹ ተዛንፎ ጨምሯል ውካታው ጨምሯል አጀቡ።
ይኸው በዚያ ቀዬ፤
አገር ሙሉ ጀማ፤
እንደጠኔ ገላ እንደ ተሳበ አንጀት ወንበር በመራቡ፤
በነጋ በጠባ ምን ጀማው ቢሞላ፤ ቢደገስ በአህሪቡ፤
ካዳሚ አልተገኘም፤
ሁሉም ጠመጠመ ፤ ሁሉም ካድሙኝ አለ፤ ወጣ ከመደቡ፤
በሰው ይዤሃለሁ፤ የሰው ሚዛን ስጠኝ፤ ወሎ ማር ዘነቡ።
መገን መዛኝ ማጣት!!!
(( ጃ ኖ ))💚💛❤
@getem
@getem
@balmbaras
👍1
ለምሽታችን
💚
#ዛሬ በወዳጄ በቀረበልኝ ግብዣ ምክንያት መሀል ሸገር አብዮት አደባባይ ላይ #አዲስአበባ ሙዚየም አደይ ሚክስድ አርት ኤግዚቢሽን ታድሜ ነበር .....ሸጋ ሸጋ የሆኑ የሚገራርሙ ሀሳብ ያላቸው ሚክስድ አርት አይቻለሁኝ...በጣም የወደድኳቸውን በስልኬ አስቀምጫለሁኝ አንድ ስዕል ብቻ ሳላነሳው መውጣቴ ቆጭቶኛል !!
ልጆቹ ከዚህም በላይ መስራት እንደሚችሉ ያስታውቃሉ.....ሁሉም ማለት ይቻላል ስለ ስራዎቻቸው ገለፃ ለማድረግ ያላቸው ፍላጎትና ተነሳሽነት የሚያስደስ ነው !!
ስዕል እና ግጥም የጥበብ ቁንጮ ናቸው በትንሽ ነገር ነፍፍፍፍፍፍፍፍ መልእክት ማስተላለፍ የሚችሉ የጥበብ ቁንጮዎች ንግስትና 👑 ንጉስ ናቸው #ለኔ!!
#በመጨረሻም እኔ አይቼ የወደድኳቸውን ሀሳባቸው እይታቸው ወድኩላቸው ስራዎችን ጀባ ልበላቹ እና ልሰናበት!
ሸጋ ምሽት!💚
@getem
@balmbaras
💚
#ዛሬ በወዳጄ በቀረበልኝ ግብዣ ምክንያት መሀል ሸገር አብዮት አደባባይ ላይ #አዲስአበባ ሙዚየም አደይ ሚክስድ አርት ኤግዚቢሽን ታድሜ ነበር .....ሸጋ ሸጋ የሆኑ የሚገራርሙ ሀሳብ ያላቸው ሚክስድ አርት አይቻለሁኝ...በጣም የወደድኳቸውን በስልኬ አስቀምጫለሁኝ አንድ ስዕል ብቻ ሳላነሳው መውጣቴ ቆጭቶኛል !!
ልጆቹ ከዚህም በላይ መስራት እንደሚችሉ ያስታውቃሉ.....ሁሉም ማለት ይቻላል ስለ ስራዎቻቸው ገለፃ ለማድረግ ያላቸው ፍላጎትና ተነሳሽነት የሚያስደስ ነው !!
ስዕል እና ግጥም የጥበብ ቁንጮ ናቸው በትንሽ ነገር ነፍፍፍፍፍፍፍፍ መልእክት ማስተላለፍ የሚችሉ የጥበብ ቁንጮዎች ንግስትና 👑 ንጉስ ናቸው #ለኔ!!
#በመጨረሻም እኔ አይቼ የወደድኳቸውን ሀሳባቸው እይታቸው ወድኩላቸው ስራዎችን ጀባ ልበላቹ እና ልሰናበት!
ሸጋ ምሽት!💚
@getem
@balmbaras
""ህገ ሰካራም!"""
(በላይ በቀለ ወያ)
‹‹ነገሩ ነው እንጂ ፤ አረቄ አያሰክርም
አሳሪ ከሌለ ፣ ገመድ ሰው አያስርም
ወዳጅ ዘመድ እንጂ….
አፈር ሰው አይቀብርም ፡፡››
ይላል የሰከረ !
አረቄ ቤት ሆኖ ፣
መተዳደሪያውን ፤ ህግ እያዋቀረ፡፡
እንደሰካራም ህግ፤ እንደስካር ወሬ
አረቄ ቤት ሆኜ...
አረቄ እየጠጣሁ፤ በነገር ሰክሬ
ስለ ሰካራም ህግ ፤ ላውራሽማ ፍቅሬ፡፡
እዚህ አረቄ ቤት...
ከተሰበሰበው ፤ የሰካራም አባል
ስሙን የማላውቀው፤ ‹‹ሰካራም›› የሚባል
አንድ የሰከረ ሰው፤ እንደተናገረው
ሀገርሽ ሀገሬ….
‹‹መልሱን ጠጣንበት›› ፣
በሚለው ህግ ነው ፣ የሚተዳደረው፡፡
‹‹ለመብራት›› እያሉን ፤ ገንዘብ እያዋጣን፤
‹‹ለመንገድ›› እያሉን ፤ ገንዘብ እያዋጣን፤
‹‹ለውሀ›› እያሉን ፤ገንዘብ እያዋጣን
ለምን መብራት ጠፋ?
ለምን ውሃ የለም?
እንዴት መንገድ አጣን? ፣ ብሎ ከመጠየቅ፤
ሳይሻል አይቀርም….
መልሱን ጠጣንበት፤ የሚል ህግ ማፅደቅ፡
ወንጀለኛው ሁላ….
ዳኛውን ጠብቆ ገንዘብ ካቀበለ
በ ሺህ ምስክር ፊት…
የመሰረትነው ክስ፤ ‹‹ውድቅ›› ከተባለ
ለምን እዴት? የሚል…
የከሳሽ ጥያቄ ፤መልስ ካልተሰጠው፤
በሰካራም አንቀፅ…
መልሱን ጠጣንበት!
የሚለው ህግ ነው ፤የሚረጋገጠው፡፡
እንደ ህገ መንግስት…
ተፈፃሚነቱ፤ ቢሰራም ባይሰራም
መልሱን ጠጣንበት!
ብሎ ያፀደቀው፤ ህግ አለው ሰካራም፡፡
እንደሰካራም ህግ፤ እንደስካር ወሬ
አረቄ ቤት ሆኜ...
አረቄ እየጠጣሁ፤ በነገር ሰክሬ
እኔን አረቄ ቤት፤ምን እንደወሰደኝ
አረቄ መጠጣት ፤ማን እንዳስለመደኝ፤
አትጠይቂኝ ፍቅሬ፡፡
መልሱን ጠጣሁበት!!
@getem
@getem
@gebriel_19
(በላይ በቀለ ወያ)
‹‹ነገሩ ነው እንጂ ፤ አረቄ አያሰክርም
አሳሪ ከሌለ ፣ ገመድ ሰው አያስርም
ወዳጅ ዘመድ እንጂ….
አፈር ሰው አይቀብርም ፡፡››
ይላል የሰከረ !
አረቄ ቤት ሆኖ ፣
መተዳደሪያውን ፤ ህግ እያዋቀረ፡፡
እንደሰካራም ህግ፤ እንደስካር ወሬ
አረቄ ቤት ሆኜ...
አረቄ እየጠጣሁ፤ በነገር ሰክሬ
ስለ ሰካራም ህግ ፤ ላውራሽማ ፍቅሬ፡፡
እዚህ አረቄ ቤት...
ከተሰበሰበው ፤ የሰካራም አባል
ስሙን የማላውቀው፤ ‹‹ሰካራም›› የሚባል
አንድ የሰከረ ሰው፤ እንደተናገረው
ሀገርሽ ሀገሬ….
‹‹መልሱን ጠጣንበት›› ፣
በሚለው ህግ ነው ፣ የሚተዳደረው፡፡
‹‹ለመብራት›› እያሉን ፤ ገንዘብ እያዋጣን፤
‹‹ለመንገድ›› እያሉን ፤ ገንዘብ እያዋጣን፤
‹‹ለውሀ›› እያሉን ፤ገንዘብ እያዋጣን
ለምን መብራት ጠፋ?
ለምን ውሃ የለም?
እንዴት መንገድ አጣን? ፣ ብሎ ከመጠየቅ፤
ሳይሻል አይቀርም….
መልሱን ጠጣንበት፤ የሚል ህግ ማፅደቅ፡
ወንጀለኛው ሁላ….
ዳኛውን ጠብቆ ገንዘብ ካቀበለ
በ ሺህ ምስክር ፊት…
የመሰረትነው ክስ፤ ‹‹ውድቅ›› ከተባለ
ለምን እዴት? የሚል…
የከሳሽ ጥያቄ ፤መልስ ካልተሰጠው፤
በሰካራም አንቀፅ…
መልሱን ጠጣንበት!
የሚለው ህግ ነው ፤የሚረጋገጠው፡፡
እንደ ህገ መንግስት…
ተፈፃሚነቱ፤ ቢሰራም ባይሰራም
መልሱን ጠጣንበት!
ብሎ ያፀደቀው፤ ህግ አለው ሰካራም፡፡
እንደሰካራም ህግ፤ እንደስካር ወሬ
አረቄ ቤት ሆኜ...
አረቄ እየጠጣሁ፤ በነገር ሰክሬ
እኔን አረቄ ቤት፤ምን እንደወሰደኝ
አረቄ መጠጣት ፤ማን እንዳስለመደኝ፤
አትጠይቂኝ ፍቅሬ፡፡
መልሱን ጠጣሁበት!!
@getem
@getem
@gebriel_19
👍2
#የማታ_ቀጠሮ 🕊
እና .....እንደነገርኩሽ !!
አዲስ ቀን ተስፋ ጥሎ .....ከሚሰነቅ ስንቅ
የራእይ ወቅቱ ፥ በበነጋ ሲርቅ
እስትንፋሰ እድሜ ተኮላሽቶ
ሬሳ ለቃሚ ፥ ከየ ስርፋው በዝቶ
እምነታችን መንገድ ሳተ ....አካሄዱ ተሸረፈ
መኖር መሰንበቱ ፥ ፍርሀት ሸከፈ
ሰው እንደ ባህር ዛፍ ፥ በምሳር ታጠፈ
ሀሳባችን ታጥሮ
የተስፋችን ፋኖስ አይሆኑ ተሰብሮ
በኔና ባንቺ አገር ፥ መሞት ዋዛ ቀረ
የለትተለት ዜና
ልጅ አሞራ በላው ፥ ወላጅ ተሸበረ
የተማረው ብሶ
ወደ እናት አባት ቤት ፥ ሳጥን ተሳፈረ።
አየሽ !!
በግብሬ ፣ በክፍሌ ፥ በስጋ ላደረ
ሰብነት ሸክፎ
በህላዌ ተስፋ ፥ ኑሮ ለመተረ
ከሊቅ እስከ ደቂቅ ፥ ለትልቅ ትንሹ
ለነ ንዋይ ዘገን !!
ለነ አመድ አፋሹ !!
እኩል እንደ አቅሙ ፥ ብስራተ ጥሞና
የመኝታ ደወል ፥ የህልም መዲና
ከምሽቱ በላይ ፥ ፅልመታም ጀበርና
ከሚታወጅበት...
የውድቅት ጀምበር ፥ የጨለማ ጋራ
ገላጣና ግልፁን ፥ ቀኑን ነው ምፈራ !!
ቀኑን ነው ምፈራ !!
አለሰአት ስንጦሎጦል.... ከሚያገኘኝ አውሬ
በለሊት ከሚያፍን ፥ ከቅጥረኛ ካድሬ
ሌት ከሾመው ፥ ኪስ አውላቂ ፥ ንብረተ ወዝ ከሚጋራ
ድንቡሎ ላየገኝ ፥ ደሜን የሚዘራ
ማጅራት ከሚመታ
በድቡልቡል ድንጋይ ፥ በሰላ ቆንጨራ
ከውድቅት ልክፍት ፥ ከቄሳር አሞራ
ከዚህ ....ከዚህ በላይ
ባማረበት ጀምበር ፥ በገላጣው ፀሀይ
በኔና አንቺ ሰማይ
ክልክል ባረጉብኝ ፥ በጋረዱኝ ቦታ
ነቃይ
አስነቃዩ
ባለ መሬት ጋንታ
በጠራራ ፀሀይ ፥ የሰየመው ሽፍታ
ቀለሀውን ዘግኖ
እርሳስ በሰው ገላ ፥ ቃታውን ሲፈታ
የሰፈር ተጠሪ ፥ ቀን የሰጠው ጌታ
ሮንድ የሚቃርም ፥ አለሁ ባይ ኮማንዶ
በዘረኛ ምላስ ፥ መቃቃር ሞርዶ
እንደ መብረቅ መአት ፥ ደቦ ጎኔ ወርዶ
መታወቂያ አውጣ !!
የሚለኝ ኮበሌ
በብሄር መታደን
የፈቀደ ገዢ፥ ያወጀ ቀበሌ
ደፍቶ መጣያውን ፥
አቅም አደርጅቶ ፥ ቀብር አስተካክሎ
በስመኔ ...ለኔ
በገዛ ፈቃዱ ፥ ራሱን ወክሎ
የናቴን ልጅ....... እቴን
በነገር ጥላሸት
በበቀል ስንደዶ ፥ አይነስቧን ኩሎ
ለወንድሜ ባዳ
ለህቴ ባይተዋር ፥ አዲስ ችካል ተክሎ
ባላንጣ !!
ደመኛ !!
ቀበኛ !! ያረገኝ
ጥማዴን ሻሽጬ ፥ ክላሽ ያስታጠቀኝ
ሰላም ሰልፍ ጠርቶ ፥ ሰላሜን የነሳ
ዝጋ !!
ክፈት !! ብሎ ፥ አርጩሜ ያነሳ
መንግስትለይ የሚሸፍት.... አለቃላይ የሚነሳ
እረ'ፍ... የሚል ብርቱ !!
ማስታረቂያ ገመድ ፥ ከስጋንት ያጣ
አሻግሮ ከማየት
በደንጋዛ ግዜ ፥ መነፀር ደርቦ ፥ እራሱን የቀጣ
ፅድቅ ያላጀገነው ፥ ኩነኔ ያልፈራ
የዘመን ውልክፍክፍ ፥ ከንቱ የሰው ተራ
ይህንን ያቀፈ ፥ ቀን ነው የምፈራ !!
እናልሽ ውዴዋ....
ከገነተ ምድር ፥ የፍቅራችን ጠበል
በሰማዩ ጎማ ፥ በእግዜሩ ተጠልፎ
በድንግል መቀነት
በራማ ወገብ ላይ ፥ ቁልቁል ተሰልፎ
ለፍቅራችን አፈር
የሰላም እርጥበት ፥ ከላይ እስኪደፋ
ቀን ከሚሮጡት ጋራ
አብረን ተሯሩጠን ፥ ሞሰብ እንዳንደፋ
ወድቀን እንዳንጋጥ ፥ በርግጫ እንዳንጠፋ
ለዚህ ነው...
ቀን ቀን ላይ ፥ ስልኬን የምዘጋ ፥ ድምጤን የማጠፋ።
እኔ ያንቺ አፍቃሪ ፥
ጭን ፍለጋ መስሎሽ ፥ነይ ማታ ማለቴ
ዋልጌ ነው አትበይ ሳይገባሽ ስጋቴ
የአራዊቶቹን ቀን ፥ ጨለማን አውቄ
እለቱን ጠልቼ ፥ ፅልመቱን ታርቄ
ቢጨንቀኝ ነው እንጂ እኔስ ማስጨነቄ
ጥንታዊ አዋዋል
ኢትዮጵያዊ ቀኔን ፥ ዛሬ መናፈቄ
አንቺም ታውቂዋለሽ ፥ የቀደመውን ቀን
ጨቅላነት ሲጥመን ፥ ጉዲፈቻ ሲያቅፈን
ድክ ድክ ስንል
እስላም ክርስቲያኑ ፥ አዝሎ ሲታቀፈን
በልጅ ቡረቃችን ፥ ዝምድና ሳንፈራ
ጎረቤት በሙሉ
ጡት እያጎረሰን ፥ በለት እለት ተራ
እንኳን ሰው ሊገደል ፥ አይናችን እያየ
ምንኛ በዳዩ ፥ አፈሩን ሲቀምሰው
ነብስ ይማር !! ብለን ነው ፥ ደጁን የምናልፈው
ደስታችን ሰው አይመርጥ ሀዘኑ የጋራ
ልእለ ሰውነት ነው !! ኢትዮጵያዊ ዳራ
ለማያውቁት ማዘን
ለእግዚሀር እንግዳ ፥ ላይ እታች መባዘን
ፀዲቅ እና ዘካ ፥ ወንጌል ቁርአኑ ፥ ከቀዲም ያዘዘን።
እኔ ብቻ አይደለሁ
እንቺም ታውቂዋለሽ ፥ እንዴት እንደነበር
ወረንጦ ፍቅራችን
ከጥላቻ እሾህ ፥ ፈውሶ ያስታርቀን።
እስከዛው ድረስ ግን.....
ለምንመኘው ቀን ፥ ፍቅርን ዘውሪ
አቅምሽ እስከቻለ
ትንፋሽሽ እስካለ ፥ ሰላምን ዘምሪ
ገራ ገር ማንነት
ጥቂት ፀበል ቢያጣ ፥ ተለከፈ ብለሽ አትደናገሪ
ወዶ ማን ሰው ያብዳል ፥ በዲያቢሎስ ጋሪ ??
እኔም በፈቀደ ፥ እድሌ በሰጠኝ
እምነቴን የበላ ፥ ፍርሀቴ እስኪለቀኝ
ከወራት ግርግር ፥ እራሴን መንጭቄ
ያቻዬን አብሮነት ፥ ፍስሀ ናፍቄ
ፈረሰች ለሚለኝ !!
ወደቀች ለሚለኝ !!
የሀገር ሟርተኛ ፥ እሬት እየጋትኩኝ
ማዕልት ሳላጎል ፥ ፍቅር እየዳርኩኝ
ሰርክ ማታ ማታ እጠብቅሻለው
አንቺም መውደድ አለሽ ፥ ሀበሻም ቀልብ አለው።
እስከዛው ድረስ ግን....ሲመሽ እንገናኝ !!
#ያንቺው_አፍቃሪ !!
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
✍ #አብርሀም_ተክሉ
contact ፦ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
እና .....እንደነገርኩሽ !!
አዲስ ቀን ተስፋ ጥሎ .....ከሚሰነቅ ስንቅ
የራእይ ወቅቱ ፥ በበነጋ ሲርቅ
እስትንፋሰ እድሜ ተኮላሽቶ
ሬሳ ለቃሚ ፥ ከየ ስርፋው በዝቶ
እምነታችን መንገድ ሳተ ....አካሄዱ ተሸረፈ
መኖር መሰንበቱ ፥ ፍርሀት ሸከፈ
ሰው እንደ ባህር ዛፍ ፥ በምሳር ታጠፈ
ሀሳባችን ታጥሮ
የተስፋችን ፋኖስ አይሆኑ ተሰብሮ
በኔና ባንቺ አገር ፥ መሞት ዋዛ ቀረ
የለትተለት ዜና
ልጅ አሞራ በላው ፥ ወላጅ ተሸበረ
የተማረው ብሶ
ወደ እናት አባት ቤት ፥ ሳጥን ተሳፈረ።
አየሽ !!
በግብሬ ፣ በክፍሌ ፥ በስጋ ላደረ
ሰብነት ሸክፎ
በህላዌ ተስፋ ፥ ኑሮ ለመተረ
ከሊቅ እስከ ደቂቅ ፥ ለትልቅ ትንሹ
ለነ ንዋይ ዘገን !!
ለነ አመድ አፋሹ !!
እኩል እንደ አቅሙ ፥ ብስራተ ጥሞና
የመኝታ ደወል ፥ የህልም መዲና
ከምሽቱ በላይ ፥ ፅልመታም ጀበርና
ከሚታወጅበት...
የውድቅት ጀምበር ፥ የጨለማ ጋራ
ገላጣና ግልፁን ፥ ቀኑን ነው ምፈራ !!
ቀኑን ነው ምፈራ !!
አለሰአት ስንጦሎጦል.... ከሚያገኘኝ አውሬ
በለሊት ከሚያፍን ፥ ከቅጥረኛ ካድሬ
ሌት ከሾመው ፥ ኪስ አውላቂ ፥ ንብረተ ወዝ ከሚጋራ
ድንቡሎ ላየገኝ ፥ ደሜን የሚዘራ
ማጅራት ከሚመታ
በድቡልቡል ድንጋይ ፥ በሰላ ቆንጨራ
ከውድቅት ልክፍት ፥ ከቄሳር አሞራ
ከዚህ ....ከዚህ በላይ
ባማረበት ጀምበር ፥ በገላጣው ፀሀይ
በኔና አንቺ ሰማይ
ክልክል ባረጉብኝ ፥ በጋረዱኝ ቦታ
ነቃይ
አስነቃዩ
ባለ መሬት ጋንታ
በጠራራ ፀሀይ ፥ የሰየመው ሽፍታ
ቀለሀውን ዘግኖ
እርሳስ በሰው ገላ ፥ ቃታውን ሲፈታ
የሰፈር ተጠሪ ፥ ቀን የሰጠው ጌታ
ሮንድ የሚቃርም ፥ አለሁ ባይ ኮማንዶ
በዘረኛ ምላስ ፥ መቃቃር ሞርዶ
እንደ መብረቅ መአት ፥ ደቦ ጎኔ ወርዶ
መታወቂያ አውጣ !!
የሚለኝ ኮበሌ
በብሄር መታደን
የፈቀደ ገዢ፥ ያወጀ ቀበሌ
ደፍቶ መጣያውን ፥
አቅም አደርጅቶ ፥ ቀብር አስተካክሎ
በስመኔ ...ለኔ
በገዛ ፈቃዱ ፥ ራሱን ወክሎ
የናቴን ልጅ....... እቴን
በነገር ጥላሸት
በበቀል ስንደዶ ፥ አይነስቧን ኩሎ
ለወንድሜ ባዳ
ለህቴ ባይተዋር ፥ አዲስ ችካል ተክሎ
ባላንጣ !!
ደመኛ !!
ቀበኛ !! ያረገኝ
ጥማዴን ሻሽጬ ፥ ክላሽ ያስታጠቀኝ
ሰላም ሰልፍ ጠርቶ ፥ ሰላሜን የነሳ
ዝጋ !!
ክፈት !! ብሎ ፥ አርጩሜ ያነሳ
መንግስትለይ የሚሸፍት.... አለቃላይ የሚነሳ
እረ'ፍ... የሚል ብርቱ !!
ማስታረቂያ ገመድ ፥ ከስጋንት ያጣ
አሻግሮ ከማየት
በደንጋዛ ግዜ ፥ መነፀር ደርቦ ፥ እራሱን የቀጣ
ፅድቅ ያላጀገነው ፥ ኩነኔ ያልፈራ
የዘመን ውልክፍክፍ ፥ ከንቱ የሰው ተራ
ይህንን ያቀፈ ፥ ቀን ነው የምፈራ !!
እናልሽ ውዴዋ....
ከገነተ ምድር ፥ የፍቅራችን ጠበል
በሰማዩ ጎማ ፥ በእግዜሩ ተጠልፎ
በድንግል መቀነት
በራማ ወገብ ላይ ፥ ቁልቁል ተሰልፎ
ለፍቅራችን አፈር
የሰላም እርጥበት ፥ ከላይ እስኪደፋ
ቀን ከሚሮጡት ጋራ
አብረን ተሯሩጠን ፥ ሞሰብ እንዳንደፋ
ወድቀን እንዳንጋጥ ፥ በርግጫ እንዳንጠፋ
ለዚህ ነው...
ቀን ቀን ላይ ፥ ስልኬን የምዘጋ ፥ ድምጤን የማጠፋ።
እኔ ያንቺ አፍቃሪ ፥
ጭን ፍለጋ መስሎሽ ፥ነይ ማታ ማለቴ
ዋልጌ ነው አትበይ ሳይገባሽ ስጋቴ
የአራዊቶቹን ቀን ፥ ጨለማን አውቄ
እለቱን ጠልቼ ፥ ፅልመቱን ታርቄ
ቢጨንቀኝ ነው እንጂ እኔስ ማስጨነቄ
ጥንታዊ አዋዋል
ኢትዮጵያዊ ቀኔን ፥ ዛሬ መናፈቄ
አንቺም ታውቂዋለሽ ፥ የቀደመውን ቀን
ጨቅላነት ሲጥመን ፥ ጉዲፈቻ ሲያቅፈን
ድክ ድክ ስንል
እስላም ክርስቲያኑ ፥ አዝሎ ሲታቀፈን
በልጅ ቡረቃችን ፥ ዝምድና ሳንፈራ
ጎረቤት በሙሉ
ጡት እያጎረሰን ፥ በለት እለት ተራ
እንኳን ሰው ሊገደል ፥ አይናችን እያየ
ምንኛ በዳዩ ፥ አፈሩን ሲቀምሰው
ነብስ ይማር !! ብለን ነው ፥ ደጁን የምናልፈው
ደስታችን ሰው አይመርጥ ሀዘኑ የጋራ
ልእለ ሰውነት ነው !! ኢትዮጵያዊ ዳራ
ለማያውቁት ማዘን
ለእግዚሀር እንግዳ ፥ ላይ እታች መባዘን
ፀዲቅ እና ዘካ ፥ ወንጌል ቁርአኑ ፥ ከቀዲም ያዘዘን።
እኔ ብቻ አይደለሁ
እንቺም ታውቂዋለሽ ፥ እንዴት እንደነበር
ወረንጦ ፍቅራችን
ከጥላቻ እሾህ ፥ ፈውሶ ያስታርቀን።
እስከዛው ድረስ ግን.....
ለምንመኘው ቀን ፥ ፍቅርን ዘውሪ
አቅምሽ እስከቻለ
ትንፋሽሽ እስካለ ፥ ሰላምን ዘምሪ
ገራ ገር ማንነት
ጥቂት ፀበል ቢያጣ ፥ ተለከፈ ብለሽ አትደናገሪ
ወዶ ማን ሰው ያብዳል ፥ በዲያቢሎስ ጋሪ ??
እኔም በፈቀደ ፥ እድሌ በሰጠኝ
እምነቴን የበላ ፥ ፍርሀቴ እስኪለቀኝ
ከወራት ግርግር ፥ እራሴን መንጭቄ
ያቻዬን አብሮነት ፥ ፍስሀ ናፍቄ
ፈረሰች ለሚለኝ !!
ወደቀች ለሚለኝ !!
የሀገር ሟርተኛ ፥ እሬት እየጋትኩኝ
ማዕልት ሳላጎል ፥ ፍቅር እየዳርኩኝ
ሰርክ ማታ ማታ እጠብቅሻለው
አንቺም መውደድ አለሽ ፥ ሀበሻም ቀልብ አለው።
እስከዛው ድረስ ግን....ሲመሽ እንገናኝ !!
#ያንቺው_አፍቃሪ !!
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
✍ #አብርሀም_ተክሉ
contact ፦ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
👍1
"ይሁና"
.
ጦሜን ታስገድፈኝ መስሎኝ ከምናኔ ሸሽቼ
እንደተገደመ ደብር ልቤን በ'ምነቴ ሠፍቼ
...
እከርም መስሎኝ ...
አለመቻል በጆሮዬ ሹክ እያለኝ
ምናብ ስሎ ከደጃፍህ አስጠለለኝ
...ምን ተሻለኝ ...
አይኔን ከድኜ ስገልጠው
ውብ ፀዳልህ መናኝ ነፍሴን አቀለጠው
.
.
.
እሩቅ መስሎን የሸኘሁህ
ላልደርስብህ የሠቀልኩህ
ጎኔ ኑረህ ነው ለካ
ልቤ በናፍቆት ስላቅ የፈካ
...
ከሞት እንደሸሸ እስትንፋስ ነፍሴ በምኞት ቃተተ
ፀሎቴ አዉዱን ቀይሮ ከአለም ምኩራብ ዘመተ
.
...ምን ተሻለኝ...
ነፍሴን አፀድቃት ብዬ በ'ምነቴ ላይ ዕምነት ጥዬ
ልቤ ከእኔ ሸሽቶ ዋሾ አረገኝ ያልታመነ
ለፅድቅ ያልኩት አስቀፀፈኝ ፀሎቴ ላይደርስ በነነ
.
ምን ተሻለኝ ?
ላጠብቅ ያልኩት መቀነቴ እ.የ.ላ.ላ
ይኸው ዛሬ በጉድለቴ ህልሜ ሞላ
....ይ .ሁ .ና....
.
ሔለን ፋንታሁን
@getem
@getem
@getem
.
ጦሜን ታስገድፈኝ መስሎኝ ከምናኔ ሸሽቼ
እንደተገደመ ደብር ልቤን በ'ምነቴ ሠፍቼ
...
እከርም መስሎኝ ...
አለመቻል በጆሮዬ ሹክ እያለኝ
ምናብ ስሎ ከደጃፍህ አስጠለለኝ
...ምን ተሻለኝ ...
አይኔን ከድኜ ስገልጠው
ውብ ፀዳልህ መናኝ ነፍሴን አቀለጠው
.
.
.
እሩቅ መስሎን የሸኘሁህ
ላልደርስብህ የሠቀልኩህ
ጎኔ ኑረህ ነው ለካ
ልቤ በናፍቆት ስላቅ የፈካ
...
ከሞት እንደሸሸ እስትንፋስ ነፍሴ በምኞት ቃተተ
ፀሎቴ አዉዱን ቀይሮ ከአለም ምኩራብ ዘመተ
.
...ምን ተሻለኝ...
ነፍሴን አፀድቃት ብዬ በ'ምነቴ ላይ ዕምነት ጥዬ
ልቤ ከእኔ ሸሽቶ ዋሾ አረገኝ ያልታመነ
ለፅድቅ ያልኩት አስቀፀፈኝ ፀሎቴ ላይደርስ በነነ
.
ምን ተሻለኝ ?
ላጠብቅ ያልኩት መቀነቴ እ.የ.ላ.ላ
ይኸው ዛሬ በጉድለቴ ህልሜ ሞላ
....ይ .ሁ .ና....
.
ሔለን ፋንታሁን
@getem
@getem
@getem
እስቲ!!!!!
ምንድር ነው ብቻህን??
ከወዲያ ከወዲህ፤
ወንበር ማንቀሳቀስ??ወንበር ማተራመስ ፤
እስኪ እንደወንበሩ፤
ትንሽ አረፍ በል ፤ ኧረ ቀስ ኧረ ቀስ።
በሚል ያገሬው ድምፅ ስለደነቆረ፤
እኔም ከወንበር ጋር፤
ልመሳሰል ብሎ ፤ ልብስ እንደቀየረ፤
ከወንበሮች መሃል፤
ልረፍ ብሎ ገብቶ ፤ ተቀምጦ ቀረ።
መገን መመሳሰል!!!
(( ጃ ኖ ))💚💛❤
@getem
@getem
@balmbaras
ምንድር ነው ብቻህን??
ከወዲያ ከወዲህ፤
ወንበር ማንቀሳቀስ??ወንበር ማተራመስ ፤
እስኪ እንደወንበሩ፤
ትንሽ አረፍ በል ፤ ኧረ ቀስ ኧረ ቀስ።
በሚል ያገሬው ድምፅ ስለደነቆረ፤
እኔም ከወንበር ጋር፤
ልመሳሰል ብሎ ፤ ልብስ እንደቀየረ፤
ከወንበሮች መሃል፤
ልረፍ ብሎ ገብቶ ፤ ተቀምጦ ቀረ።
መገን መመሳሰል!!!
(( ጃ ኖ ))💚💛❤
@getem
@getem
@balmbaras
ቀለም እና እውነት!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።
በተዋበ ሳሎን ፥ በሰፊ አዳራሽ
በመቶ እቁባቶች ፥ በአፋሽ አከንፋሽ
ታጅቦ ሰለሞን ...
እንዲች ብሎ ሳይዋሽ
ሁሉም ከንቱ ከንቱ ፥ የከንቱ ከንቱ ነው
ብሎ ተናገረ
ይሄን ባለ ማግስት...
ፅድቁን አደላድሎ ፥ ነፍሱን አሻገረ ።
#ደግሞ ወዲህ ግድም.. .
ታብዮ ለስሙ ፥ ዝናን የሚያስቀድም
በጭብጨባ ብዛት.. .
ስጋውን አግዝፎ ፥ ነፍሱን የሚያለግም
አሳቢ ተብሎ ፥ ሙገሳ የደረሰው
ፈላስፋ ተነስቶ ፥ እግዜሩን ዘለፈው ።
ይሄን ባለ ማግስት...
ለዓለም ተሞሽሮ ፥ ህግን ጥሶ ሻረ
ሰለሞን እንዳለው ፥ ከንቱ ሆኖ ቀረ።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።
በተዋበ ሳሎን ፥ በሰፊ አዳራሽ
በመቶ እቁባቶች ፥ በአፋሽ አከንፋሽ
ታጅቦ ሰለሞን ...
እንዲች ብሎ ሳይዋሽ
ሁሉም ከንቱ ከንቱ ፥ የከንቱ ከንቱ ነው
ብሎ ተናገረ
ይሄን ባለ ማግስት...
ፅድቁን አደላድሎ ፥ ነፍሱን አሻገረ ።
#ደግሞ ወዲህ ግድም.. .
ታብዮ ለስሙ ፥ ዝናን የሚያስቀድም
በጭብጨባ ብዛት.. .
ስጋውን አግዝፎ ፥ ነፍሱን የሚያለግም
አሳቢ ተብሎ ፥ ሙገሳ የደረሰው
ፈላስፋ ተነስቶ ፥ እግዜሩን ዘለፈው ።
ይሄን ባለ ማግስት...
ለዓለም ተሞሽሮ ፥ ህግን ጥሶ ሻረ
ሰለሞን እንዳለው ፥ ከንቱ ሆኖ ቀረ።
@getem
@getem
@getem
አንቆርስም!!!!!!!!
በእናቶቻችን ደጅ፣ ባባቶቻችን ቤት፣
በእነ አባ ጉባኤ፣ በአሊሞቹ ፅህፈት፣
በፍቅር ተቃቅፈን፣
የተቀበልነውን፣
የደም ዋጋ ጥሪት፣ መሃላ አናፈርስም፣
ይሁን አሜን ብለን፣
ዳቦውን ነው እንጅ፣ ድካውን አንቆርስም!!!!!!!!
አ፣፣፣፣ን፣፣፣፣ቆ፣፣፣፣ር፣፣፣፣ስ፣፣፣ም!!!!!!!!!!
(((((((( ልብ በሉ!!!!!! ድካ ማለት ትርጉሙ ፣ድንበር፣
ወሰን ማለት ነው።))))))))))
((( ጃ ኖ )))💚💛❤️
ሸጋ የጁምኣ ና የመስቀል በዓል!💚
@getem
@getem
@balmbaras
በእናቶቻችን ደጅ፣ ባባቶቻችን ቤት፣
በእነ አባ ጉባኤ፣ በአሊሞቹ ፅህፈት፣
በፍቅር ተቃቅፈን፣
የተቀበልነውን፣
የደም ዋጋ ጥሪት፣ መሃላ አናፈርስም፣
ይሁን አሜን ብለን፣
ዳቦውን ነው እንጅ፣ ድካውን አንቆርስም!!!!!!!!
አ፣፣፣፣ን፣፣፣፣ቆ፣፣፣፣ር፣፣፣፣ስ፣፣፣ም!!!!!!!!!!
(((((((( ልብ በሉ!!!!!! ድካ ማለት ትርጉሙ ፣ድንበር፣
ወሰን ማለት ነው።))))))))))
((( ጃ ኖ )))💚💛❤️
ሸጋ የጁምኣ ና የመስቀል በዓል!💚
@getem
@getem
@balmbaras