ይብላኝለት ለኔ
።።።።።።።።።።።
ያልወረደ መና ፣
ልቡን ለሰቀዘው፣
ያልተበላ ዳቦ፣
፣አንጀቱን ለያዘው።
ባልተጠጣ ወተት ፣
ምናቡ እያገሳ፣
ስጋው ሲደነድን፣
ልቡ ለሚከሳ።
ይብላኝለት ለኔ...
ኖርኩ እያለ ሲሞት፣
አፈር ለማይለብሰው፣
ይብላኝለት ለኔ
በነፍስና ስጋ፣ ድንበር ተገትሮ፣
መኖር ላልቀመሰው።
ዛሬ ቀኑ ፀሀይ ፣ ነግ ደሞ ዳመና፣
ታቻምና ረሀብ ነው ፣ አሁን ብልፅግና።
ፍቅር ይተኮሳል፣ ከወዲያኛው ማዶ፣
ዘመድ ይገናኛል፣ ተራራው ተንዶ።
ምናምን ምናምን...
ይሉት እንቶፈንቶ...
ቢያገኝ ለሚበላ ፣ቢያጣ ለሚጋደም፣ ተመስገኑን በልቶ፣
ምን ሊፈይድለት፣ አንዱ አደረ ቢባል፣ በሰው ስጋ አግስቶ?
ይብላኝለት ለኔ...
ከሰው አብራክ ወጥቶ ፣
ሰው ለማይናፍቀው፣
ዕልፍ ችግኝ መሀል፣
ተስፋው ለደረቀ
እኔን ባይ ለራቀው።
ይብላኝለት ልቤን ፣
ይብላኝለት ገላ፣
ብርድ አያውቅ ሙቀት፣
የአፍላነት ዘለላ።
እንባ የለው ዐይኔ፣
ላብ የል ከአካላቴ፣
እንዲህ ያል ድርቅናን፣
ከማን ሸመትኩ እቴ?
ሳቅ እማያስቀኝ ፣
ሰቆቃ እማይገደኝ፣
ምን ያል የሰው አውሬ ፣
አምጦ ወለደኝ?
ይብላኝለት ዐይኔን ...
የሱ ብጤ በርባን፣
አማትሮ ለሚያጣ፣
ውንብድናው አንሶት፣
አምላክ ለሚቀጣ።
ባልሰመረ ቅኝት፣
ለሚደክር ከንፈር፣
መሳም ላልታከተው
ያለመተፋፈር።
ለማይደክም እግሬ፣
በየብስ ባህሩ፣
ንዳድ ለሚነዳው
አልፎ ከድንበሩ።
ይብላኝለት ለኔ...
ሰው ተብሎ ላልሞላው፣
የ "ሰ"ን አንድ ቅኔ።
ይብላኝለት ለኔ!
በማዕዶት ያየህ
18/09/2014 ዓ.ም.
@getem
@getem
@getem
።።።።።።።።።።።
ያልወረደ መና ፣
ልቡን ለሰቀዘው፣
ያልተበላ ዳቦ፣
፣አንጀቱን ለያዘው።
ባልተጠጣ ወተት ፣
ምናቡ እያገሳ፣
ስጋው ሲደነድን፣
ልቡ ለሚከሳ።
ይብላኝለት ለኔ...
ኖርኩ እያለ ሲሞት፣
አፈር ለማይለብሰው፣
ይብላኝለት ለኔ
በነፍስና ስጋ፣ ድንበር ተገትሮ፣
መኖር ላልቀመሰው።
ዛሬ ቀኑ ፀሀይ ፣ ነግ ደሞ ዳመና፣
ታቻምና ረሀብ ነው ፣ አሁን ብልፅግና።
ፍቅር ይተኮሳል፣ ከወዲያኛው ማዶ፣
ዘመድ ይገናኛል፣ ተራራው ተንዶ።
ምናምን ምናምን...
ይሉት እንቶፈንቶ...
ቢያገኝ ለሚበላ ፣ቢያጣ ለሚጋደም፣ ተመስገኑን በልቶ፣
ምን ሊፈይድለት፣ አንዱ አደረ ቢባል፣ በሰው ስጋ አግስቶ?
ይብላኝለት ለኔ...
ከሰው አብራክ ወጥቶ ፣
ሰው ለማይናፍቀው፣
ዕልፍ ችግኝ መሀል፣
ተስፋው ለደረቀ
እኔን ባይ ለራቀው።
ይብላኝለት ልቤን ፣
ይብላኝለት ገላ፣
ብርድ አያውቅ ሙቀት፣
የአፍላነት ዘለላ።
እንባ የለው ዐይኔ፣
ላብ የል ከአካላቴ፣
እንዲህ ያል ድርቅናን፣
ከማን ሸመትኩ እቴ?
ሳቅ እማያስቀኝ ፣
ሰቆቃ እማይገደኝ፣
ምን ያል የሰው አውሬ ፣
አምጦ ወለደኝ?
ይብላኝለት ዐይኔን ...
የሱ ብጤ በርባን፣
አማትሮ ለሚያጣ፣
ውንብድናው አንሶት፣
አምላክ ለሚቀጣ።
ባልሰመረ ቅኝት፣
ለሚደክር ከንፈር፣
መሳም ላልታከተው
ያለመተፋፈር።
ለማይደክም እግሬ፣
በየብስ ባህሩ፣
ንዳድ ለሚነዳው
አልፎ ከድንበሩ።
ይብላኝለት ለኔ...
ሰው ተብሎ ላልሞላው፣
የ "ሰ"ን አንድ ቅኔ።
ይብላኝለት ለኔ!
በማዕዶት ያየህ
18/09/2014 ዓ.ም.
@getem
@getem
@getem
እኔ ቅብዝ ቅብዝብዚት
ችኩል ችኩልኩሊት
ወረት ወርትሪትሪት
አቋም አልባ ሽክርክሪት
ቀን ለሰላት የምፋጠን
ጎህ ሲቀዳድ የ'እግዜር መቅደሱን የማጥን።
ድንጉጥ ድንጉጥጉጢት
ፓስተር ይዞኝ መፅሀፍ ሲገልጥ
የጌታ ነኝ ብዬ ማቀልጥ።
እኔ ልጂት
ጅላ ጅሊት
ቂላ ቂሊት
ያዋቂ ቤት ተንበርካኪ
የ'አትሮንሱ ፊት ሰባኪ
ቀን የሚያምረኝ ቲሪኪሚሪኪ
ማታ ሚያምረኝ መጠጥ ዉስኪ
የማለዳዉ ቅዱስ ባሪያ
የከሰዓት የ'አላህ ባሪያ
የፓስተሩ አማካሪ
ድምብር ደምበርባሪ።
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
✍ትዝታ ወልዴ
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
@TIZITA21
@getem
@getem
@getem
ችኩል ችኩልኩሊት
ወረት ወርትሪትሪት
አቋም አልባ ሽክርክሪት
ቀን ለሰላት የምፋጠን
ጎህ ሲቀዳድ የ'እግዜር መቅደሱን የማጥን።
ድንጉጥ ድንጉጥጉጢት
ፓስተር ይዞኝ መፅሀፍ ሲገልጥ
የጌታ ነኝ ብዬ ማቀልጥ።
እኔ ልጂት
ጅላ ጅሊት
ቂላ ቂሊት
ያዋቂ ቤት ተንበርካኪ
የ'አትሮንሱ ፊት ሰባኪ
ቀን የሚያምረኝ ቲሪኪሚሪኪ
ማታ ሚያምረኝ መጠጥ ዉስኪ
የማለዳዉ ቅዱስ ባሪያ
የከሰዓት የ'አላህ ባሪያ
የፓስተሩ አማካሪ
ድምብር ደምበርባሪ።
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
✍ትዝታ ወልዴ
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
@TIZITA21
@getem
@getem
@getem
#እንዳትረሺኝ_ብዬ
:
:
እንድታስታውሺኝ ሁሌም እንዳትረሺኝ ብዙ ለፍቻለሁ፤
ግን ይህ ድካሜ ፍሬ እንዳላፈራ በርግጥ አይቻለሁ።
:
:
ብዙ ቀልድ አውርቼሽ ብዙ ሳቅ ስቀሻል፤
ደግሞም በማግስቱ ሁሉን ረስተሻል።
ስጦታም ስሰጥሽ ወስደሻል በደስታ፤
ይረሳሻል እንጂ ያኖርሽበት ቦታ።
ናፍቀሺኛል ብዬ « አንቺስ?» ያልኩሽ እንደው፤
መልስሽ «ምንም» ነው እንደተለመደው።
:
:
ታዲያ እንደው ምን ላድርግ እስኪ እንደው ምን በጀኝ፤
በሷ መረሳቴ ውስጤን እኮ ፈጀኝ፤
እያልኩኝ ስጨነቅ ስንት ቀን አለፈ፤
ተመስገን ነው ዛሬስ ዕድሜ «ለአበው» ተረት ገልግሎኝ አረፈ።
:
:
አዎ...
ክብሩ ለአበው ይሁን አበው ይሰንብቱ፤
«የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳም»ብለው ለተረቱ።
:
:
እናምልሽ ፍቅሬ...
ከዛሬ ጀምሮ ቀልድም አልነግርሽም፤
ስጦታ አልሰጥሽም፤
ናፈኩሽ ወይ ብዬም ከቶ አልጠይቅሽም።
:
:
ይልቅ በዚ ፈንታ...
ጤና ለተረቱ ማድረግ ያለበትን ውስጤ ስለነቃ፤
ከሰሞኑን ውዴ እንዳትረሺኝ ብዬ ልወጋሽ ነው በቃ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henockba
@getem
@getem
@getem
:
:
እንድታስታውሺኝ ሁሌም እንዳትረሺኝ ብዙ ለፍቻለሁ፤
ግን ይህ ድካሜ ፍሬ እንዳላፈራ በርግጥ አይቻለሁ።
:
:
ብዙ ቀልድ አውርቼሽ ብዙ ሳቅ ስቀሻል፤
ደግሞም በማግስቱ ሁሉን ረስተሻል።
ስጦታም ስሰጥሽ ወስደሻል በደስታ፤
ይረሳሻል እንጂ ያኖርሽበት ቦታ።
ናፍቀሺኛል ብዬ « አንቺስ?» ያልኩሽ እንደው፤
መልስሽ «ምንም» ነው እንደተለመደው።
:
:
ታዲያ እንደው ምን ላድርግ እስኪ እንደው ምን በጀኝ፤
በሷ መረሳቴ ውስጤን እኮ ፈጀኝ፤
እያልኩኝ ስጨነቅ ስንት ቀን አለፈ፤
ተመስገን ነው ዛሬስ ዕድሜ «ለአበው» ተረት ገልግሎኝ አረፈ።
:
:
አዎ...
ክብሩ ለአበው ይሁን አበው ይሰንብቱ፤
«የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳም»ብለው ለተረቱ።
:
:
እናምልሽ ፍቅሬ...
ከዛሬ ጀምሮ ቀልድም አልነግርሽም፤
ስጦታ አልሰጥሽም፤
ናፈኩሽ ወይ ብዬም ከቶ አልጠይቅሽም።
:
:
ይልቅ በዚ ፈንታ...
ጤና ለተረቱ ማድረግ ያለበትን ውስጤ ስለነቃ፤
ከሰሞኑን ውዴ እንዳትረሺኝ ብዬ ልወጋሽ ነው በቃ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henockba
@getem
@getem
@getem
አመል አይለቅ ነገር ከራስ ውሎ ያድራል
የዘመመዉ ልብሽ ሄዶም መች ይቀናል።
አንቺ
መሄድ መጓዝ ስራሽ ባገኙበት መፍሰስ
ይህ ተቀማጭ ልቤ ሄደች ብሎ ማልቀስ
አዎን
ተቀማጭ ነው ልቤ በ.ቃ.ል የታሰረ
ቃልሽን ...ከቅዱስ ቃል እኩል የቆጠረ።
ጠዋት እና ማታ ጡዋፍ እና መባ
አንቺን ከሰጠኝ ብዬ በ'እንባ.....
ለመንኩት
ከቃልሽ ቃል ጠቅሼ አምላኬን ሰበኩት
ግና
ልብሽ መቼ ቀና.....!!!
ያልቀደሰች
ያልመነነች ነፍሴን ማረፊያ አታሳጫት
መሄዴ ነው እያልሽ ተይ አታበሳጫት💔
✍ በረከት ( @berii34 )
@getem
@getem
@getem
የዘመመዉ ልብሽ ሄዶም መች ይቀናል።
አንቺ
መሄድ መጓዝ ስራሽ ባገኙበት መፍሰስ
ይህ ተቀማጭ ልቤ ሄደች ብሎ ማልቀስ
አዎን
ተቀማጭ ነው ልቤ በ.ቃ.ል የታሰረ
ቃልሽን ...ከቅዱስ ቃል እኩል የቆጠረ።
ጠዋት እና ማታ ጡዋፍ እና መባ
አንቺን ከሰጠኝ ብዬ በ'እንባ.....
ለመንኩት
ከቃልሽ ቃል ጠቅሼ አምላኬን ሰበኩት
ግና
ልብሽ መቼ ቀና.....!!!
ያልቀደሰች
ያልመነነች ነፍሴን ማረፊያ አታሳጫት
መሄዴ ነው እያልሽ ተይ አታበሳጫት💔
✍ በረከት ( @berii34 )
@getem
@getem
@getem
ጦሩ ፍቅርሽ
ልቤን ወጋው፤
እንዳልነግርሽ
በጣም ፈራሁ።
አያልቅብሽ ጦር ውርወራው፤
ስንቱን አዳም ልቡን ገዛው።
ልክ እንደንብ እኛ ሆነን፤
አበባ አንቺን፤
ልንቀስምሽ በጣም ጓጉተን።
በዙሪያሽ ስንዞር
ልንከብሽ ስንሞክር።
ገለል አርጎ የከለለሽ።
አንቺን ያዘ ብልጡ አፍቃሪሽ።
ላንቺ ብለን ንብ ስንሆን፤
በብልሁ በአትክልተኛው ተቀደምን።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
ልቤን ወጋው፤
እንዳልነግርሽ
በጣም ፈራሁ።
አያልቅብሽ ጦር ውርወራው፤
ስንቱን አዳም ልቡን ገዛው።
ልክ እንደንብ እኛ ሆነን፤
አበባ አንቺን፤
ልንቀስምሽ በጣም ጓጉተን።
በዙሪያሽ ስንዞር
ልንከብሽ ስንሞክር።
ገለል አርጎ የከለለሽ።
አንቺን ያዘ ብልጡ አፍቃሪሽ።
ላንቺ ብለን ንብ ስንሆን፤
በብልሁ በአትክልተኛው ተቀደምን።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
#አልልሽም
:
:
:
ከፍጥረት ለይቶ እንደሰራሽ በማር፤
የውበትሽና የፀባይሽ ማማር፤
ባንድ ተሰባጥሮ አቅሌን አስቶኛል፤
አንደኛዬ ነሽ ግን ማለት ይከብደኛል።
:
:
ጡት እንዳጣ ዕፃን ልጅ ስነፋረቅ ውዬ፤
ልክ ዐይንሽን ሳየው በደስታ ዘልዬ፤
ማልቀሴን ረስቼ ሰላም አድሬያለሁ፤
አንደኛዬ እኮ ነሽ ማለት ግን ፈራለሁ።
:
:
የህይወቴ ግማድ የመኖሬ ጉዳይ፤
የደስታዬ ወሰን የአንድ ልቤ ሙዳይ፤
አንቺ እንደሆንሽ ባውቅም፤
የኔ አንደኛ ብዬሽ አልመፃደቅም።
:
:
ተንጠራርተሽ ደርሰሽ አቅፈሽ በሹክሹክታ፤
ዓይን ዓይኔን እያየሽ ስትዪኝ የኔ ጌታ፤
ሀሴት ይወረኛል ከእግር እስከ ፀጉሬ፤
አንደኛዬ ነሽ ግን አልልም ደፍሬ።
:
:
እውነት ነው የኔ ውድ እንዴትስ ደፍራለሁ፤
አንቺን እንዲ ማለት በጣሙን አፍራለሁ።
:
:
አንቺን አቅፎ ኖሮ አንቺን አቅፎ መሞት ምን ልቤ ቢመኝም፤
ተቀየሚኝ እንጂ አፈር እስክገባ አንደኛዬ አትሆኚም።
እንደው ቢሆን እንኳን አንደኛዬ እንድልሽ እውን ፈልገሽም፤
ሲያምርሽ ይቅር እንጂ መቼም አልልሽም።
:
:
ለምን ካልሺኝ ውዴ ...
አንደኛ ነው ሲባል አንድ ነገር ደርሶ፤
ሁለተኛ ሆኖ ከእርሱ ትንሽ አንሶ፤
የሚፎካከረው ሌላ አካል እንዳለ፤
መረዳት አይከብድም ቃሉን ላስተዋለ።
:
:
ስለዚም እንቁዬ ...
በውበት በፀባይ ሁለተኛ ሆኖ ካንቺ ሚወዳደር፤
ቢፈለግ አንዳች ሰው በሌለበት ሀገር፤
አንደኛዬ እኮ ነሽ እንዴትስ እላለሁ፤
ብቸኛዬ ሆነሽ ብቻሽ ሆኜ ሳለሁ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henockba
@getem
@getem
@getem
:
:
:
ከፍጥረት ለይቶ እንደሰራሽ በማር፤
የውበትሽና የፀባይሽ ማማር፤
ባንድ ተሰባጥሮ አቅሌን አስቶኛል፤
አንደኛዬ ነሽ ግን ማለት ይከብደኛል።
:
:
ጡት እንዳጣ ዕፃን ልጅ ስነፋረቅ ውዬ፤
ልክ ዐይንሽን ሳየው በደስታ ዘልዬ፤
ማልቀሴን ረስቼ ሰላም አድሬያለሁ፤
አንደኛዬ እኮ ነሽ ማለት ግን ፈራለሁ።
:
:
የህይወቴ ግማድ የመኖሬ ጉዳይ፤
የደስታዬ ወሰን የአንድ ልቤ ሙዳይ፤
አንቺ እንደሆንሽ ባውቅም፤
የኔ አንደኛ ብዬሽ አልመፃደቅም።
:
:
ተንጠራርተሽ ደርሰሽ አቅፈሽ በሹክሹክታ፤
ዓይን ዓይኔን እያየሽ ስትዪኝ የኔ ጌታ፤
ሀሴት ይወረኛል ከእግር እስከ ፀጉሬ፤
አንደኛዬ ነሽ ግን አልልም ደፍሬ።
:
:
እውነት ነው የኔ ውድ እንዴትስ ደፍራለሁ፤
አንቺን እንዲ ማለት በጣሙን አፍራለሁ።
:
:
አንቺን አቅፎ ኖሮ አንቺን አቅፎ መሞት ምን ልቤ ቢመኝም፤
ተቀየሚኝ እንጂ አፈር እስክገባ አንደኛዬ አትሆኚም።
እንደው ቢሆን እንኳን አንደኛዬ እንድልሽ እውን ፈልገሽም፤
ሲያምርሽ ይቅር እንጂ መቼም አልልሽም።
:
:
ለምን ካልሺኝ ውዴ ...
አንደኛ ነው ሲባል አንድ ነገር ደርሶ፤
ሁለተኛ ሆኖ ከእርሱ ትንሽ አንሶ፤
የሚፎካከረው ሌላ አካል እንዳለ፤
መረዳት አይከብድም ቃሉን ላስተዋለ።
:
:
ስለዚም እንቁዬ ...
በውበት በፀባይ ሁለተኛ ሆኖ ካንቺ ሚወዳደር፤
ቢፈለግ አንዳች ሰው በሌለበት ሀገር፤
አንደኛዬ እኮ ነሽ እንዴትስ እላለሁ፤
ብቸኛዬ ሆነሽ ብቻሽ ሆኜ ሳለሁ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henockba
@getem
@getem
@getem
ይድረስ ለአንቺው፣
በከተማው መሀል መናኝ ላደረግሽኝ
አለምን ጠቅልዬ፣ ስሄድ ለሽኘሽኝ
ደንዳናውን ልቤን ላደረግሽው አመድ
ምን ነክቶት ነው?
ብሎ ሰው ሁሉ እስኪፈርድ
አለም ይወቅልኝ እኔስ መንኛልሁ
ከልብሽ ገብቼ ምርኰኛ ሆኛለሁ
ማን በነገረሽ፣
በፍቅርሽ ወድቄ ከራሴ እንደተጣላሁ
አንድ ሺ አንድ ሌሊት ላንቺ እንዳነባሁ
በዚህ ሰፊ ምድር ሴትም በሞላበት
ምን ይሆን ምስጢሩ እንዲህ ምሆንበት
የፍቅሬንም መጠን ትራሴ ይንገርሽ
ሁሌ ማታ ሲሆን እንዳነባሁልሽ
ፈጣሪን ተቀየምኩ፣
የዳዊትን ትግል አግዝፎ ሲሰጠኝ
በጐልያድ ምትክ አንችን ሲልክብኝ
ዳዊት በጠጠሩ ጐልያድን ጣለው
ምን ይወርውር ልቤ ምርኮኛሽ የሆነው
ያሬድ መኮነን(ሳላዶር)
@pappilon36
@getem
@getem
@getem
በከተማው መሀል መናኝ ላደረግሽኝ
አለምን ጠቅልዬ፣ ስሄድ ለሽኘሽኝ
ደንዳናውን ልቤን ላደረግሽው አመድ
ምን ነክቶት ነው?
ብሎ ሰው ሁሉ እስኪፈርድ
አለም ይወቅልኝ እኔስ መንኛልሁ
ከልብሽ ገብቼ ምርኰኛ ሆኛለሁ
ማን በነገረሽ፣
በፍቅርሽ ወድቄ ከራሴ እንደተጣላሁ
አንድ ሺ አንድ ሌሊት ላንቺ እንዳነባሁ
በዚህ ሰፊ ምድር ሴትም በሞላበት
ምን ይሆን ምስጢሩ እንዲህ ምሆንበት
የፍቅሬንም መጠን ትራሴ ይንገርሽ
ሁሌ ማታ ሲሆን እንዳነባሁልሽ
ፈጣሪን ተቀየምኩ፣
የዳዊትን ትግል አግዝፎ ሲሰጠኝ
በጐልያድ ምትክ አንችን ሲልክብኝ
ዳዊት በጠጠሩ ጐልያድን ጣለው
ምን ይወርውር ልቤ ምርኮኛሽ የሆነው
ያሬድ መኮነን(ሳላዶር)
@pappilon36
@getem
@getem
@getem
//ልጠብቃት\\
አንዲት ቆንጆ መልከ ቀና፤
ቀና ብዬ አየሁና፤
ባለማመን ሳለሁ ገና።
ፊቴን ሳብስ በተደሞ፤
በአለም ካለሁ
ወይም ደግሞ።
እውነት ከሆንኩ ሳረጋግጥ፤
እኔን ጥላ እሷ ጥፍት።
እፉዬ ነች የኔ ገላ፤
ታይታ የጠፋች እንደ ጥላ።
ገነት ይሁን እኔ የሄድኩት፤
ሴት መላእክት ነው ያየሁት፤
ግን እፆታ መች አላቸው፤
መላእክትስ አንድ ናቸው።
ብዬ ብዙ ስደናገር፤
ሳላናግር ስግደረደር።
ንፋስ መጥቶ አበነናት፤
እፉዬ ነች በቃ አወኳት፤
ስትዞር ውላ የማይደክማት፤
ንፋስ ወስዶ እንዳራቃት፤
ማረፊያዋን ካላገኘች
እየገፋ ከመለሳት፤
ተስፋ አልቆርጥም.........
..................ልጠብቃት።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
አንዲት ቆንጆ መልከ ቀና፤
ቀና ብዬ አየሁና፤
ባለማመን ሳለሁ ገና።
ፊቴን ሳብስ በተደሞ፤
በአለም ካለሁ
ወይም ደግሞ።
እውነት ከሆንኩ ሳረጋግጥ፤
እኔን ጥላ እሷ ጥፍት።
እፉዬ ነች የኔ ገላ፤
ታይታ የጠፋች እንደ ጥላ።
ገነት ይሁን እኔ የሄድኩት፤
ሴት መላእክት ነው ያየሁት፤
ግን እፆታ መች አላቸው፤
መላእክትስ አንድ ናቸው።
ብዬ ብዙ ስደናገር፤
ሳላናግር ስግደረደር።
ንፋስ መጥቶ አበነናት፤
እፉዬ ነች በቃ አወኳት፤
ስትዞር ውላ የማይደክማት፤
ንፋስ ወስዶ እንዳራቃት፤
ማረፊያዋን ካላገኘች
እየገፋ ከመለሳት፤
ተስፋ አልቆርጥም.........
..................ልጠብቃት።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
ይቅር
""""""
እንዴት?
ለክፋት ፊት ሰጠን፥
ፍቅር አመለጠን...
ጥላቻ ወረሰ፥
ውሸት እውነት ጣሰ...
እንዴት?
ለመኳረፍ ተጋን፥
ለመታረቅ ሰጋን...
ብዙ ደስታ መዘን፥
ሀዘን ገዘገዘን...
እንዴት?
ላሳለፍነው ተድላ
ጉድ እስከሚለን ሰው፤
ምን ክፉ በቅሎ ነው
ውዴታውን ትተን ስህተት የም'ነቅሰው?
እንዴት?
ሰይጣን ገዘፈብን
ፈጣሪ ኮስሶ፤
ነቅንቀን ዘመመ
የቤቱ ምሰሶ...
ለቆፈን ገላችን
ሙቀት ላያዘልቀው፤
እንዴት ነው ጎጆዋችን
ተቃጥሎ የሞቅነው?
እንዴት?
ላጠፋነው ሁሉ
ለጠፋብን ነገር፤
አደላድሎን ኖሮ
ለሰበርነው ወንበር፤
በአንድ አቆራኝቶ
ፍቅር ከፍ አድርጎ ላቀናጀን መንበር፤
እልህ ገፍቶን እንጂ
ላሳለፍነው ሁሉ እርቅ አያንስም ነበር።
....ይቅርታ....
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@getem
@getem
@paappii
""""""
እንዴት?
ለክፋት ፊት ሰጠን፥
ፍቅር አመለጠን...
ጥላቻ ወረሰ፥
ውሸት እውነት ጣሰ...
እንዴት?
ለመኳረፍ ተጋን፥
ለመታረቅ ሰጋን...
ብዙ ደስታ መዘን፥
ሀዘን ገዘገዘን...
እንዴት?
ላሳለፍነው ተድላ
ጉድ እስከሚለን ሰው፤
ምን ክፉ በቅሎ ነው
ውዴታውን ትተን ስህተት የም'ነቅሰው?
እንዴት?
ሰይጣን ገዘፈብን
ፈጣሪ ኮስሶ፤
ነቅንቀን ዘመመ
የቤቱ ምሰሶ...
ለቆፈን ገላችን
ሙቀት ላያዘልቀው፤
እንዴት ነው ጎጆዋችን
ተቃጥሎ የሞቅነው?
እንዴት?
ላጠፋነው ሁሉ
ለጠፋብን ነገር፤
አደላድሎን ኖሮ
ለሰበርነው ወንበር፤
በአንድ አቆራኝቶ
ፍቅር ከፍ አድርጎ ላቀናጀን መንበር፤
እልህ ገፍቶን እንጂ
ላሳለፍነው ሁሉ እርቅ አያንስም ነበር።
....ይቅርታ....
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@getem
@getem
@paappii
ንገሪኝ ካልከኝስ💔
ደረቅ፣ግትር፣ጨካኝ ልብ የለሽም አልከኝ
ድንጋይ መሆኔንም በሰዉ አስነገርከኝ
አዎ ነኝ ይግረምህ
እረግጠሀኝ ብትሄድ ምትህ እንዳይገባኝ
አንስተህ ብትጥለኝ ዉስጤን እንዳትጎዳኝ
በሚያማምር ቃላት ልቤን አረስርሰህ
ደርሰህ እንዳታደማኝ
በጥርስህ እየሳክ ልቤን እንዳትወጋኝ
አይዞሽ አይዞሽ ብለህ ሂጅ ጥፊ እንዳትለኝ
ወደድኩሽ እያልከኝ ፍቅሬን እንዳትቀማኝ
ድረሺልኝ ብለህ አልይሽ እንዳትል
በሳቅህ እኔም ስቄ
በደስታህ ቦርቄ
ሲከፋህ አልቅሼ
ስታዝን ሳይ ደሞ ማቅ አመድ ለብሼ
ስኖር እኖርና.................
ድንገት ብትቀየር
ሳቄ ጣዕሙን ያጣል
ሀዘኔ ያስቃል
ደስታዬ ያስለቅሳል
ለቅሶዬ የደስታ መገለጫ ይሆናል
እና በአጠቃላይ ትርጉሜ ይጠፋል
እናምልህ ስማኝ
እህ ብለህ አድምጠኝ
ይህ ዝርክርክ ልቤን በደምብ ስለማቀዉ
ለዛ ነዉ ደንድኜ በሩን የማልከፍተዉ
አንዳንድ ልጆች አሉ
አንኳክተዉ መሮጥን ጀግንነት ያስባሉ።
❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
በትዝታ ወልዴ እንደተፃፈ✍
❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
@TIZITA21
@TIZITA21
@getem
@getem
ደረቅ፣ግትር፣ጨካኝ ልብ የለሽም አልከኝ
ድንጋይ መሆኔንም በሰዉ አስነገርከኝ
አዎ ነኝ ይግረምህ
እረግጠሀኝ ብትሄድ ምትህ እንዳይገባኝ
አንስተህ ብትጥለኝ ዉስጤን እንዳትጎዳኝ
በሚያማምር ቃላት ልቤን አረስርሰህ
ደርሰህ እንዳታደማኝ
በጥርስህ እየሳክ ልቤን እንዳትወጋኝ
አይዞሽ አይዞሽ ብለህ ሂጅ ጥፊ እንዳትለኝ
ወደድኩሽ እያልከኝ ፍቅሬን እንዳትቀማኝ
ድረሺልኝ ብለህ አልይሽ እንዳትል
በሳቅህ እኔም ስቄ
በደስታህ ቦርቄ
ሲከፋህ አልቅሼ
ስታዝን ሳይ ደሞ ማቅ አመድ ለብሼ
ስኖር እኖርና.................
ድንገት ብትቀየር
ሳቄ ጣዕሙን ያጣል
ሀዘኔ ያስቃል
ደስታዬ ያስለቅሳል
ለቅሶዬ የደስታ መገለጫ ይሆናል
እና በአጠቃላይ ትርጉሜ ይጠፋል
እናምልህ ስማኝ
እህ ብለህ አድምጠኝ
ይህ ዝርክርክ ልቤን በደምብ ስለማቀዉ
ለዛ ነዉ ደንድኜ በሩን የማልከፍተዉ
አንዳንድ ልጆች አሉ
አንኳክተዉ መሮጥን ጀግንነት ያስባሉ።
❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
በትዝታ ወልዴ እንደተፃፈ✍
❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
@TIZITA21
@TIZITA21
@getem
@getem