#እንዳትረሺኝ_ብዬ
:
:
እንድታስታውሺኝ ሁሌም እንዳትረሺኝ ብዙ ለፍቻለሁ፤
ግን ይህ ድካሜ ፍሬ እንዳላፈራ በርግጥ አይቻለሁ።
:
:
ብዙ ቀልድ አውርቼሽ ብዙ ሳቅ ስቀሻል፤
ደግሞም በማግስቱ ሁሉን ረስተሻል።
ስጦታም ስሰጥሽ ወስደሻል በደስታ፤
ይረሳሻል እንጂ ያኖርሽበት ቦታ።
ናፍቀሺኛል ብዬ « አንቺስ?» ያልኩሽ እንደው፤
መልስሽ «ምንም» ነው እንደተለመደው።
:
:
ታዲያ እንደው ምን ላድርግ እስኪ እንደው ምን በጀኝ፤
በሷ መረሳቴ ውስጤን እኮ ፈጀኝ፤
እያልኩኝ ስጨነቅ ስንት ቀን አለፈ፤
ተመስገን ነው ዛሬስ ዕድሜ «ለአበው» ተረት ገልግሎኝ አረፈ።
:
:
አዎ...
ክብሩ ለአበው ይሁን አበው ይሰንብቱ፤
«የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳም»ብለው ለተረቱ።
:
:
እናምልሽ ፍቅሬ...
ከዛሬ ጀምሮ ቀልድም አልነግርሽም፤
ስጦታ አልሰጥሽም፤
ናፈኩሽ ወይ ብዬም ከቶ አልጠይቅሽም።
:
:
ይልቅ በዚ ፈንታ...
ጤና ለተረቱ ማድረግ ያለበትን ውስጤ ስለነቃ፤
ከሰሞኑን ውዴ እንዳትረሺኝ ብዬ ልወጋሽ ነው በቃ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henockba
@getem
@getem
@getem
:
:
እንድታስታውሺኝ ሁሌም እንዳትረሺኝ ብዙ ለፍቻለሁ፤
ግን ይህ ድካሜ ፍሬ እንዳላፈራ በርግጥ አይቻለሁ።
:
:
ብዙ ቀልድ አውርቼሽ ብዙ ሳቅ ስቀሻል፤
ደግሞም በማግስቱ ሁሉን ረስተሻል።
ስጦታም ስሰጥሽ ወስደሻል በደስታ፤
ይረሳሻል እንጂ ያኖርሽበት ቦታ።
ናፍቀሺኛል ብዬ « አንቺስ?» ያልኩሽ እንደው፤
መልስሽ «ምንም» ነው እንደተለመደው።
:
:
ታዲያ እንደው ምን ላድርግ እስኪ እንደው ምን በጀኝ፤
በሷ መረሳቴ ውስጤን እኮ ፈጀኝ፤
እያልኩኝ ስጨነቅ ስንት ቀን አለፈ፤
ተመስገን ነው ዛሬስ ዕድሜ «ለአበው» ተረት ገልግሎኝ አረፈ።
:
:
አዎ...
ክብሩ ለአበው ይሁን አበው ይሰንብቱ፤
«የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳም»ብለው ለተረቱ።
:
:
እናምልሽ ፍቅሬ...
ከዛሬ ጀምሮ ቀልድም አልነግርሽም፤
ስጦታ አልሰጥሽም፤
ናፈኩሽ ወይ ብዬም ከቶ አልጠይቅሽም።
:
:
ይልቅ በዚ ፈንታ...
ጤና ለተረቱ ማድረግ ያለበትን ውስጤ ስለነቃ፤
ከሰሞኑን ውዴ እንዳትረሺኝ ብዬ ልወጋሽ ነው በቃ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henockba
@getem
@getem
@getem
😁94👍44❤28🔥5😱3