ይህ ፍጽም ስህተት ነው በሥርዋጽ (በቃል ስሕተት) የገባ ነው::
ትክክለኛ ቃል #ኢንብሎ ፍጡረ እስመ ውእቱ ተወልደ በሥጋ እምብእሲት ነው የሚለው #ኢ በግእዙ አፍራሽ ነች ለምሳሌ
👉ይመውት ብንል #የሚሞት ማለት ሲሆን
#ኢይመውት ስንል ደግሞ ኢ #አፍራሽ በመሆኗ የማይሞት ማለት ይሆናል ማለት ነው:: በዚህ መሠረት
ለ ንብሎ ፍጡም እስመ ውእቱ ተወልደ በሥጋ እምብሲ ከተባለ ከሴት በሥጋ ስለ ተወለደ ፍጡር ነው ወደሚል ፍጽም ስህተትና ኑፋቄ ውስጥ ይከተናል በትክክለኛው ግን
#ኢንብሎ ፍጡረ እስመ ውእቱ ተወልደ በሥጋ እምብእሲ የሚል ነው ይህም "ከሴት በሥጋ ስለተወለደ ፍጡር አንለውም የሚል ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጋር የማይጋጭ ትርጓሜን ይሰጠናል "
እንኳን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይቅርና እኛ ተራ ሰዎች እራሱ ከሴት ስለተወለድን ተፈጠርን አያሰኝም ምክንያቱም #እናቶቻችን #ፈጥረው አይወልዱምና ወይም የወለዱትን #አይፈጥሩትምና ጥንተ ተፈጥሯችን ያኜ በገነት ከአፈር የተገነው መገኘት ካለ መኖር ወደ መኖር የመጣነው መምጣት ብቻ ነው ተፈጠርን የሚያሰኘው ከዛ ወዲ ተዋለድን እንጂ አልተፈጣጠርንም ልንፈጥርም ልንፈጥረም እንችልም::
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ፈጣሪ ፍጥረታት ነውና ለና ከእናታችን ስለተወለድን ተፈጠርን የሚለው ቃል ያልተስማማን እርሱ እንዴት ከሴት ስለተወለደ ፍጡር መባል ይስማዋል ?በፍጽም #አይስማማውም በፍጹም
ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ኤፍሬም ድንግልም ፈጣሪዋን ወለደችው እርሱም እናቱ ፈጠረ የፈጠረውን ሥጋ መልሶ ተዋሐደ " ይላል
ሰልስቱ ምዕትም ቢሆኑ የቅዱስ ኤፍሬምም ንግግርን አጠንክረውታል ዘወትር በጸሎታችንም የተወለደ እንጂ ያልተፈጠረ ብለን እንንጸልይ ትዕዛዝን አስተላልፈውልናል
"፤ በእነዚያ ዘንድ ለማስተዋል የሚያስቸግር ነገር አለ፥ ያልተማሩትና የማይጸኑትም ሰዎች ሌሎችን መጻሕፍት እንደሚያጣምሙ እነዚህን ደግሞ ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ። "
(2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3: 16) ተብሏልና ከቤተ ክርስቲያን #የውስጥ ጠላቶች አዋቂ መሳይ ጠምጣሚዎች ልንጠነቀቅ ይገባናል መልእክታች ነው........ ይቆየን.......
#ሎቱ ስብሐት ክብር ምስጋና ይግባውና ከሴት ስለ ተወለደ በሥጋው ፍጡር ነው አይባልም ከሴት የተወለደው መለኮት ጭምር እንጂ ሥጋ ብቻ አይደለምና መወለድን ለሥጋ ብቻ የምንሰጥ ከሆነ ከነገረ ተዋሕዶ አፈንግጠናልና በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ ስለሚሆንብን መጨረሻችን #የሞት ገደል ነው
"፤ እርሱ ግን ሌላ ወንጌል አይደለም፤ የሚያናውጡአችሁ የክርስቶስንም ወንጌል #ሊያጣምሙ የሚወዱ #አንዳንዶች አሉ እንጂ። ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል #የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ #የተረገመ ይሁን። "፤ አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን #ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት #የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን። " (ወደ ገላትያ ሰዎች 1÷7- 9)
#ከአባቶቻችን ከቅዱሳን ሐዋርያት የተቀበልነው ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው የአብ ልጅ የድንግል ልጅ ወልድ ዋሕድ #የምትለው የቅዱስ ጴጥሮስ እምነት #ኦርቶዶክስ #ተዋሕዶ ነች!!! ማቴ 6÷13
ወስብሐት ለእግዚአብሔር !
ወለ ወላዲተ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክቡር🙏
ትክክለኛ ቃል #ኢንብሎ ፍጡረ እስመ ውእቱ ተወልደ በሥጋ እምብእሲት ነው የሚለው #ኢ በግእዙ አፍራሽ ነች ለምሳሌ
👉ይመውት ብንል #የሚሞት ማለት ሲሆን
#ኢይመውት ስንል ደግሞ ኢ #አፍራሽ በመሆኗ የማይሞት ማለት ይሆናል ማለት ነው:: በዚህ መሠረት
ለ ንብሎ ፍጡም እስመ ውእቱ ተወልደ በሥጋ እምብሲ ከተባለ ከሴት በሥጋ ስለ ተወለደ ፍጡር ነው ወደሚል ፍጽም ስህተትና ኑፋቄ ውስጥ ይከተናል በትክክለኛው ግን
#ኢንብሎ ፍጡረ እስመ ውእቱ ተወልደ በሥጋ እምብእሲ የሚል ነው ይህም "ከሴት በሥጋ ስለተወለደ ፍጡር አንለውም የሚል ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጋር የማይጋጭ ትርጓሜን ይሰጠናል "
እንኳን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይቅርና እኛ ተራ ሰዎች እራሱ ከሴት ስለተወለድን ተፈጠርን አያሰኝም ምክንያቱም #እናቶቻችን #ፈጥረው አይወልዱምና ወይም የወለዱትን #አይፈጥሩትምና ጥንተ ተፈጥሯችን ያኜ በገነት ከአፈር የተገነው መገኘት ካለ መኖር ወደ መኖር የመጣነው መምጣት ብቻ ነው ተፈጠርን የሚያሰኘው ከዛ ወዲ ተዋለድን እንጂ አልተፈጣጠርንም ልንፈጥርም ልንፈጥረም እንችልም::
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ፈጣሪ ፍጥረታት ነውና ለና ከእናታችን ስለተወለድን ተፈጠርን የሚለው ቃል ያልተስማማን እርሱ እንዴት ከሴት ስለተወለደ ፍጡር መባል ይስማዋል ?በፍጽም #አይስማማውም በፍጹም
ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ኤፍሬም ድንግልም ፈጣሪዋን ወለደችው እርሱም እናቱ ፈጠረ የፈጠረውን ሥጋ መልሶ ተዋሐደ " ይላል
ሰልስቱ ምዕትም ቢሆኑ የቅዱስ ኤፍሬምም ንግግርን አጠንክረውታል ዘወትር በጸሎታችንም የተወለደ እንጂ ያልተፈጠረ ብለን እንንጸልይ ትዕዛዝን አስተላልፈውልናል
"፤ በእነዚያ ዘንድ ለማስተዋል የሚያስቸግር ነገር አለ፥ ያልተማሩትና የማይጸኑትም ሰዎች ሌሎችን መጻሕፍት እንደሚያጣምሙ እነዚህን ደግሞ ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ። "
(2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3: 16) ተብሏልና ከቤተ ክርስቲያን #የውስጥ ጠላቶች አዋቂ መሳይ ጠምጣሚዎች ልንጠነቀቅ ይገባናል መልእክታች ነው........ ይቆየን.......
#ሎቱ ስብሐት ክብር ምስጋና ይግባውና ከሴት ስለ ተወለደ በሥጋው ፍጡር ነው አይባልም ከሴት የተወለደው መለኮት ጭምር እንጂ ሥጋ ብቻ አይደለምና መወለድን ለሥጋ ብቻ የምንሰጥ ከሆነ ከነገረ ተዋሕዶ አፈንግጠናልና በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ ስለሚሆንብን መጨረሻችን #የሞት ገደል ነው
"፤ እርሱ ግን ሌላ ወንጌል አይደለም፤ የሚያናውጡአችሁ የክርስቶስንም ወንጌል #ሊያጣምሙ የሚወዱ #አንዳንዶች አሉ እንጂ። ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል #የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ #የተረገመ ይሁን። "፤ አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን #ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት #የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን። " (ወደ ገላትያ ሰዎች 1÷7- 9)
#ከአባቶቻችን ከቅዱሳን ሐዋርያት የተቀበልነው ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው የአብ ልጅ የድንግል ልጅ ወልድ ዋሕድ #የምትለው የቅዱስ ጴጥሮስ እምነት #ኦርቶዶክስ #ተዋሕዶ ነች!!! ማቴ 6÷13
ወስብሐት ለእግዚአብሔር !
ወለ ወላዲተ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክቡር🙏
ባለማወቅ ማወቅ !
" #አንቺ የፈጠርሽኝ ማርያም .... "
ደመና ከማረግ ከማይጋርደው ከእናቶቻችን ጸሎቶች መካከል አልፎ አልፎ የምንሰማው ንግግር ነው። አንቺ የፈጠርሽኝ ማርያም ፣ አንተ የፈጠርከኝ ሚካኤል ....ወ.ዘ.ተ
ታድያ ይህን የየዋሃን ጸሎት የሰማ እንደኔ ያለ በማወቅ ያላወቀ ሰው "እናቴ የፈጠረሽኮ እግዚአብሔር ነው ለምን እንደሱ ትጸልያለሽ ? " ብሎ ለማረም ይቃጣዋል።
በርግጥም ሥነ ፍጥረትን ካለመኖር ወደ መኖር ካለመታየት ወደ መታየት አምጥቶ የፈጠረው ፈጣሪ ዓለማት እግዚአብሔር ብቻ ነው። ሆኖም ግን ይህ የእናቶቻችን የዋህትን ገንዘብ ያደረገች ንግግራቸው በኃያሌው ትክክል ነች ! እንዴት የሚል ካለ ጥቂት ያንብብ ።
#እናቶቻችን የመረዳት እምነት ሲኖራቸው እኛ ደግሞ የማወቅ እምነት አለን ። እውቀት ተኮር እምነት ለሰዋሰው ፣ ለንግግር ጠባይ ፣ ለነጠላና ብዙ ቁጥር እንዲሁም መደብን ጠብቆ አሳክቶ መናገር ወይም መጻፍ ሲሆን ይህን ያላሞላ ንግግርና ጽሁፍም ስሕተት እንደሆነ እናስባለን ስለዚህ የእናቶቻችን ንግግሮችና ጸሎቶች የሚሰምር አይመስለንም። የመረዳት እምነት ያላቸው እናቶቻችንና አባቶቻችን ግን ትክክለኛውን የእምነት መሠረት በልባቸው ይዘው እና አውቀው ማለትም #እግዚአብሔርን ፈጣሪ #እመቤታችንን እመ ፈጣሪ /የፈጣሪ እናት/ እንደሆኑና እንደሚባሉ እያወቁ ለቋንቋ አጠቃቀማቸው ሳይጨነቁ እርሱ የማያውቀው የለም በማለት በየዋህነት ብቻ አንዱን በአንዱ ሊጣሩበት ይችላሉ።
ለምሳሌ እግዚአብሔር ጠባቂያችን ነው ። ቅዱሳን መላእክትም ጠባቂዎቻችን ናቸው። ታድያ አንድ ሰው ተነስቶ ጠባቂዎቼ ቅዱሳን መላእክ ሆይ ብሎ ቢጸልዬ መላእክቱን ፈጣሪ አደረጋቸው አያሰኝም ።ከፈጣሪ ጋር የሚያመሳስላቸውን አንድ ዘርፍ መርጦ ለጸሎት ተጠቀማቸው እንጂ ፈጣሪና ፍጡርን አስተካለ እኩል አደረገም አያሰኝም። በተመሳሳይ እናቶቻችንም የፈጠርሽኝ እመቤቴ ሲሉ እንደ ፈጣሪ የሆንሽ ፈጣሪን የምትመስይ ማለታቸው ነው። የእመቤታችን የማርያም መልክ የአምላክን መልክ ይመስላል እንደሚል /ተአምረ ማርያም መቅድም / አያይዞም ዓለሙ ሁሉ የተፈጠረው ስለ ድንግል ማርያም እንደሆነ ሲያስረዳ አዳምና ሔዋንም እመቤታችን ከነርሱ (ዘር) እንድትወለድ ተፈጠሩ ይላል።
#ሌላው አዳሪ በማኅደሩ ማኅደርም በአዳሪው ይጠራል። ለምሳሌ ሰይፍ በሰገባው ያድራል ይህን የሚያውቅ ሰው ሰይፉ የተለየው ሰገባን ቢያይና ሰይፉ በሰገባው እንደሌለ ባያስተውል ሰገባውን ሰይፍ ብሎ በአዳሪው ሊጠራው ይችላል ።በተመሳሳይ ዳዊት የሌለው ማኅደር ያየ አንድ ሰውም ማኅደሩን አይቶ ብቻ ዳዊቱን አቀብለኝ ብሎ ማኅደሩን ዳዊት ብሎ ሊጠራው ይችላል ትክክል ነው አዳሪ በማኅደሩ ማኅደሩም በአዳሪው መጥራት ልማድ ነውና ሰውየውን ከመግባባት አያግደውም ።
እናቶቻችንም እመቤታችንን አንቺ የፈጠርሽኝ ማርያም ሲሉ ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣሽን ፈጥረሽ የምትመግቢን በኃላም እንደ ብራና ጠቅልለሽ ዓለምን የምታሳልፊ ፈጣሪያችን ነሽ ማለታቸው አይደለም 9ወር ከ5ቀን በማኅጸንሽ ያደረብሽ (የተዋሕደሽ ) ሦስት ዓመት በጀርባሽ ያዘልሽው ሁለት ዓመት ከድንግልና የተገኘ አሊበ ወተት ያጠባሽው እመ ፈጣሪ የፈጣሪ እናት ነሽ፤ እንደ ፈጣሪ የሆነሽ ማለታቸው ነው።
#በርሷ ባደረ በፈጣሪ ልጇ እርሷን ፈጣሪተ ዓለም /የመፈጠር ምክንያት/ ብሎ እንደ መጥራት ነው። ልክ ሰገባውን ሰይፍ ማኅደሩንም ዳዊት ብሎ እንደመጥራት ያለ አጠራር። አንድም በቀደመች ሔዋን እናታችን አማካኝነት ሞት ወደ ዓለም መጣ በዳግሚት ሔዋን በእመቤታችን አማካኝነት ደግሞ በዳግም ተፈጥሮ ሕይወት ተሰጠን ።
ስለሆነም እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የመዳን ምክንያት ብቻ ሳትሆን አዳምና ሔዋንም (የሰው ልጅ ሁሉ) ድንግል ማርያምን ለማመስገን የተፈጠሩ በመሆናቸው የመፈጠራችን ምክንያት ናትና የተፈጠርንብሽ ብለው መጥራታቸው ለእውነት የቀረበ እንጂ ስሕተት አይደለም። ይህን በመሰለችሁ በመረዳት ላይ በተመሠረተችሁ የዋህትን ገንዘብ ባደረገች የእናቶቻችንና የአባቶቻችን ንጽህት ሃይማኖት እናምናለን እንታመናለን !።
ዋቢ :- #ተአምረ ማርያም መቅድም ዘዘወትር
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥቅምት 10/2015 ዓ.ም
" #አንቺ የፈጠርሽኝ ማርያም .... "
ደመና ከማረግ ከማይጋርደው ከእናቶቻችን ጸሎቶች መካከል አልፎ አልፎ የምንሰማው ንግግር ነው። አንቺ የፈጠርሽኝ ማርያም ፣ አንተ የፈጠርከኝ ሚካኤል ....ወ.ዘ.ተ
ታድያ ይህን የየዋሃን ጸሎት የሰማ እንደኔ ያለ በማወቅ ያላወቀ ሰው "እናቴ የፈጠረሽኮ እግዚአብሔር ነው ለምን እንደሱ ትጸልያለሽ ? " ብሎ ለማረም ይቃጣዋል።
በርግጥም ሥነ ፍጥረትን ካለመኖር ወደ መኖር ካለመታየት ወደ መታየት አምጥቶ የፈጠረው ፈጣሪ ዓለማት እግዚአብሔር ብቻ ነው። ሆኖም ግን ይህ የእናቶቻችን የዋህትን ገንዘብ ያደረገች ንግግራቸው በኃያሌው ትክክል ነች ! እንዴት የሚል ካለ ጥቂት ያንብብ ።
#እናቶቻችን የመረዳት እምነት ሲኖራቸው እኛ ደግሞ የማወቅ እምነት አለን ። እውቀት ተኮር እምነት ለሰዋሰው ፣ ለንግግር ጠባይ ፣ ለነጠላና ብዙ ቁጥር እንዲሁም መደብን ጠብቆ አሳክቶ መናገር ወይም መጻፍ ሲሆን ይህን ያላሞላ ንግግርና ጽሁፍም ስሕተት እንደሆነ እናስባለን ስለዚህ የእናቶቻችን ንግግሮችና ጸሎቶች የሚሰምር አይመስለንም። የመረዳት እምነት ያላቸው እናቶቻችንና አባቶቻችን ግን ትክክለኛውን የእምነት መሠረት በልባቸው ይዘው እና አውቀው ማለትም #እግዚአብሔርን ፈጣሪ #እመቤታችንን እመ ፈጣሪ /የፈጣሪ እናት/ እንደሆኑና እንደሚባሉ እያወቁ ለቋንቋ አጠቃቀማቸው ሳይጨነቁ እርሱ የማያውቀው የለም በማለት በየዋህነት ብቻ አንዱን በአንዱ ሊጣሩበት ይችላሉ።
ለምሳሌ እግዚአብሔር ጠባቂያችን ነው ። ቅዱሳን መላእክትም ጠባቂዎቻችን ናቸው። ታድያ አንድ ሰው ተነስቶ ጠባቂዎቼ ቅዱሳን መላእክ ሆይ ብሎ ቢጸልዬ መላእክቱን ፈጣሪ አደረጋቸው አያሰኝም ።ከፈጣሪ ጋር የሚያመሳስላቸውን አንድ ዘርፍ መርጦ ለጸሎት ተጠቀማቸው እንጂ ፈጣሪና ፍጡርን አስተካለ እኩል አደረገም አያሰኝም። በተመሳሳይ እናቶቻችንም የፈጠርሽኝ እመቤቴ ሲሉ እንደ ፈጣሪ የሆንሽ ፈጣሪን የምትመስይ ማለታቸው ነው። የእመቤታችን የማርያም መልክ የአምላክን መልክ ይመስላል እንደሚል /ተአምረ ማርያም መቅድም / አያይዞም ዓለሙ ሁሉ የተፈጠረው ስለ ድንግል ማርያም እንደሆነ ሲያስረዳ አዳምና ሔዋንም እመቤታችን ከነርሱ (ዘር) እንድትወለድ ተፈጠሩ ይላል።
#ሌላው አዳሪ በማኅደሩ ማኅደርም በአዳሪው ይጠራል። ለምሳሌ ሰይፍ በሰገባው ያድራል ይህን የሚያውቅ ሰው ሰይፉ የተለየው ሰገባን ቢያይና ሰይፉ በሰገባው እንደሌለ ባያስተውል ሰገባውን ሰይፍ ብሎ በአዳሪው ሊጠራው ይችላል ።በተመሳሳይ ዳዊት የሌለው ማኅደር ያየ አንድ ሰውም ማኅደሩን አይቶ ብቻ ዳዊቱን አቀብለኝ ብሎ ማኅደሩን ዳዊት ብሎ ሊጠራው ይችላል ትክክል ነው አዳሪ በማኅደሩ ማኅደሩም በአዳሪው መጥራት ልማድ ነውና ሰውየውን ከመግባባት አያግደውም ።
እናቶቻችንም እመቤታችንን አንቺ የፈጠርሽኝ ማርያም ሲሉ ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣሽን ፈጥረሽ የምትመግቢን በኃላም እንደ ብራና ጠቅልለሽ ዓለምን የምታሳልፊ ፈጣሪያችን ነሽ ማለታቸው አይደለም 9ወር ከ5ቀን በማኅጸንሽ ያደረብሽ (የተዋሕደሽ ) ሦስት ዓመት በጀርባሽ ያዘልሽው ሁለት ዓመት ከድንግልና የተገኘ አሊበ ወተት ያጠባሽው እመ ፈጣሪ የፈጣሪ እናት ነሽ፤ እንደ ፈጣሪ የሆነሽ ማለታቸው ነው።
#በርሷ ባደረ በፈጣሪ ልጇ እርሷን ፈጣሪተ ዓለም /የመፈጠር ምክንያት/ ብሎ እንደ መጥራት ነው። ልክ ሰገባውን ሰይፍ ማኅደሩንም ዳዊት ብሎ እንደመጥራት ያለ አጠራር። አንድም በቀደመች ሔዋን እናታችን አማካኝነት ሞት ወደ ዓለም መጣ በዳግሚት ሔዋን በእመቤታችን አማካኝነት ደግሞ በዳግም ተፈጥሮ ሕይወት ተሰጠን ።
ስለሆነም እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የመዳን ምክንያት ብቻ ሳትሆን አዳምና ሔዋንም (የሰው ልጅ ሁሉ) ድንግል ማርያምን ለማመስገን የተፈጠሩ በመሆናቸው የመፈጠራችን ምክንያት ናትና የተፈጠርንብሽ ብለው መጥራታቸው ለእውነት የቀረበ እንጂ ስሕተት አይደለም። ይህን በመሰለችሁ በመረዳት ላይ በተመሠረተችሁ የዋህትን ገንዘብ ባደረገች የእናቶቻችንና የአባቶቻችን ንጽህት ሃይማኖት እናምናለን እንታመናለን !።
ዋቢ :- #ተአምረ ማርያም መቅድም ዘዘወትር
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥቅምት 10/2015 ዓ.ም