ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#የነገረ_ቅዱሳን ጥያቄዎች ትክክለኛ ምላሾች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ_ ቅዱስ የሚለው ቃል ቀደሰ ካለው የግዕዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጓሜውም የተለየ ፣ የተከበረ ፣ ማለት ነው::

ሀ) እውነት ለ ) ሐሰት

#ኛ_የቅዱሳን ቅድስናቸው የባህሪ ቅድስና ነው ::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

ምክንያቱም:- #የባህሪ ቅድስና ያለው እግዚአብሔር ብቻ ነው

#ኛ_ "ሁሰት" ከ አሥሩ የቅዱሳን ማዕረጋት መካከል አይካተትም::

ሀ)እውነት ለ) ሐሰት


#ኛ_ቅዱሳን የሚለው ገላጭ ለ ቅዱሳን #ሰዎች ብቻ የሚቀፀል ቅጽል ነው::

ሀ) እውነት ለ)ሐሰት

ምክንያቱም :-ከቅዱሳን ሰዎች ባሻገር
#ለቅዱሳን መላእክት
#ለቅዱሳን መጻሕፍት
#ለቅዱሳን መካናት ይቀጸላልና

#ኛ_ቅዱሳን ሰዎች ፈተና የሚገጥማቸው ከፍቃደ ሥጋቸው ብቻ ነው

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት
ከፍቃደ ሥጋ ብቻ ሳይሆን #ለበረከት_ከእግዚአብሔር ለማሰናከል #ከሰይጣን #ከአላዊያን ነገስታት #ከጠንቆዮች ጭምር ይገጥማቸዋልና


#ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ብቻ ምረጡ

#ኛ_ከሚከተሉት ማዕረጋተ ቅዱሳን መካከል #በወጣኒነት ክፍል ውስጥ የማይመደበው ማዕረግ የቱ

ሀ )ጽዋሜ (ዝምታ ፣ አርምሞ)
ለ )ልባዌ (ልብ ማድረግ )
ሐ ) ከዊነ እሳት
መ )አንብዕ

ሐ)በፍጽምነት የሚገኝ ማዕረግ ነው

#ኛ_መፍቀሬ ጥበብ የተባለው ቅዱስ ሰለሞን "ከሞተ አንበሳ ያልሞተ ውሻ ይሻላል" ብሎ ተናግሯል:: ለመሆኑ በአንበሳና በውሻ የመሰላቸው እነማንን ነው


ሀ ) ጻድቃንን
ለ ) ኃጥዐንን
ሐ ) ጻድቃንን እና ኃጥዐንን

#ኛ_የቅዱሳን መላእክት አገልግሎት የሆነው የቱ ነው

ሀ) ማማለድ (መለመን)
ለ) ማበርታት ፣ማጽናናት
ሐ) መቅጣት
መ) ሁሉም

#ኛ_ነገረ ቅዱሳን ሲባል ከቅዱሳን ሰዎች ባሻገር ሊያጠቃልል የሚገባው እነ ማንን ነው

ሀ) ቅዱሳት መላእክት
ለ) ቅዱሳት መካናትን
ሐ) ቅዱሳት መጻሕፍትን
መ) ሁሉንም


#ኛ_ ለቅዱሳን ሁሉ ሊቀርብ የሚገባው የስግደት ዓይነት የቱ ነው

ሀ) የጸጋ ወይም የአክብሮት ስግደት
ለ) የአምልኮት ወይም የባህሪ ስግደት
ሐ) የአስተብርኮ ስግደት
መ) ከእግዚአብሔር በስተቀር ለማንም አይሰገድም


#በአጭሩ_መልሱ

፲ ፩ #_ቅዱሳን ፈተና የሚገጥማቸው ከነማነው

#መልስ
#ከእግዚአብሔር ለበረከት
#ከሥጋ ፍቃዳቸው
#ከአላዊያን ነገስታት
#ከጠንቆዮች
#ከሰይጣን


፲ ፪ #_አስሩ የቅዱሳን መዐረጋት በሦስት ክፍል ይከፈላሉ ::ምን ምን ተብለው በአጭሩ ይብራራ(ሪ)

#መልስ
#ጸጣኒነት (ጀማሪ)
#ማዕከላዊነት
#ፍጽምነት
ወይም
#ንጽሐ ሥጋ
#ንጽሐ ነፍስ
#ንጽሐ ልቡናም ተብለው ይጠራሉ
፲ ፫ #ኛ ቅዱሳን ከአፀደ ሥጋ ባሻገር በአፀደ ነፍስ ጭምር እንደሚያማልዱ ቅዱሳት መጻሕፍትን በመጥቀስ አስረዳ(ጂ)

#መልስ
#ሊቀ_ነቢያት_ቅዱስ_ሙሴ በዘመኑ ባልነበሩ ቅዱሳን ሰዎች ወደ እግዚአብሔር መለመኑ እና መልስ ማግኘቱ
"፤ ዘራችሁን እንደ ሰማይ ከዋክብት አበዛለሁ፥ ይህችንም የተናገርኋትን ምድር ሁሉ ለዘራችሁ እሰጣታለሁ፥ ለዘላለምም ይወርሱአታል ብለህ በራስህ #የማልህላቸውን ባሪያዎችህን አብርሃምንና ይስሐቅን እስራኤልንም #አስብ።"
#እግዚአብሔርም በሕዝቡ ላይ ሊያደርግ ስላሰበው #ክፋት_ራራ።"
(ኦሪት ዘጸአት 32÷14-14)


፲ ፬ #ኛ ሦስቱን የመላክት ከተማ ስም ማን ማን ይባላሉ

#መልስ
#ኢዮር
#ራማ
#ኤረር


፲ ፭ #_ቅዱሳንን ማክበር #እግዚአብሔርን ማክበር ማለት እንደሆነ በራስህ (ሺ) አረዳድና አገላጽ በአጭሩ አስረዳ(ጂ)

#መልስ
"፤ #እግዚአብሔር#በቅዱሳኑ ላይ #ድንቅ_ነው፤ የእስራኤል አምላክ እርሱ ኃይልን ብርታትንም ለሕዝቡ ይሰጣል፤ እግዚአብሔርም ይመስገን።"
(መዝሙረ ዳዊት 67÷35)


"፤#እግዚአብሔር_በጻድቁ_እንደ_ተገለጠ_እወቁ፤ ።"
(መዝሙረ ዳዊት 3(4)÷3)


#መልሶቹ ዙሪያ ማንኛውንም ጥያቄ ሀሳብና አስተያየት
👇👇👇👇👇
@Amtcombot
@Amtcombot
ላይ ይላኩልን ::

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#ኑ_ይህን_ድንቅ_እዩ !
______________

#የእመቤታችን በደብረ ምጥማቅ ለ"፭ ቀናት ያክል የመገለጥ በዓል


#ከቅዱሳን_ክብር_የማርያም_ክብር_ይበልጣል ፤ የአብን ቃል ለመቀበል በተገባ ተገኝታለችና። መላእክት የሚፈሩትን ትጉሆች በሰማያት የሚያመሰግኑትን ድንግል ማርያም በማሕፀንዋ ተሸከመችው። ይህች ከኪሩቤል ትበልጣለች፤ ከሱራፌልም ትበልጣለች ከሦስቱ አካል ለአንዱ ማደሪያ ሆናለችና። የነቢያት ሀገራቸው ኢየሩሳሌም ይህች ናት።
#ለቅዱሳን_ሁሉ የደስታቸው ማደሪያ ናት። በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሁኗልና።

#ኑ_ይህንድንቅ_እዩ። ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና፤ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፤ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት።

የማይታወቅ ተገለጠ፤ የማይታይ ታየ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በርግጥ ሰው ሆነ። ትላንት የነበረው ዛሬም ያለው መቼም የሚኖረው ኢየሱስ ክርስቶስ እንሰግድለትና እናመስግነው ዘንድ አንድ ባሕርይ ነው። #ቅድስት_ሆይ_ለምኝልን


____ሶሪያዊው_ቅዱስ_ኤፍሬም_የረቡዕ ውዳሴ ማርያም____