#አዲስ_መልአክ_ተክለ_ኤል
________
ተፈጥሮ ከመላእክት ወገን ያልሆነ ሰው ሆኖ ሳለ ነገር ግን በሃይማኖቱ ጽናት በምግባሩ ቅንሐት እና በተጋድሎዎ ብዛት ምድራዊ ሲሆን ሰማያዊ አዳማዊ ሲሆን መላእካዊ ለመሆን የበቃ ሐዲስ መላእክ ነው :: ተክለ ኤል
ቅዱሳን መላእክት በዘር የተገኙ አይደሉም ተክለ ኤል ( #ተክለ_ሃይማኖት ) ግን ከሕግ ዘር የተገኘ ሰው የሆነ አዲስ መላእክ ነው ::
‹ #ተክል › ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣፣ የሚሸተት፣ቢበሉት ጥጋብ ፣ቢያርፉበት ጥላ የሚሆን ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ ሥርዓት ማለት ነው /ማቴ.፲፭፥፲፫/፡፡
" #ኤል " ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ማለት ነው :: ስመ መላእክት ስመ እግዚአብሔርን ያዘለ በመሆኑ የሁሉም ቅዱሳን መላእክ ስም "ኤል" የሚል መቀጽል አለው #ለምሳሌ :-ሚካ-ኤል ፣ ገብር-ኤል ፣ ዑራ -ኤል፣ ወዘተ .... ስለዚህ ተክለ ኤል ስንልም #የእግዚአብሔር _ተክል ማለታችን ነው :: ታላቁ ሊቅ ቅዱስ #ባስልዮስ ዘ ቄሳሪያ እኔስ #እግዚአብሔር ባልኩ ጊዜ #አብ_ወልድ_መንፈስ_ቅዱስ ማለቴ ነው ብሎ እንደተናገረ እኛም እግዚአብሔር ስንል አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለታችንነውና #ተክለ_ኤል ስንለውም የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተክል ማለታችን ጭምር ነው::
#ቦታው በሸዋ ክፍለ ሀገር ዛሬ ኢቲሳ በመባል በሚታወቀው ከከሰም ጅረት አካባቢ ባለ ቦታ በጥንቱ ፈጠጋር ቡልጋ በደብረ ጽላልሽ አውራጃ ዞረሬ በተባለው ሥፍራ ነው ። በዚሁ ሥፍራ (ዘርዐ ዮሐንስ) ፀጋ ዘአብ የሚባል የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህን የነበረ ጻድቅ ሰው ነበር "ጸጋ ዘአብ " ማለት የአብ ሥጦታ ማለት ነው ካህኑ ጸጋ ዘአብ በሃገሩ ደጋግ ከሆኑ ሰዎች ወገን ሣራ የምትባል ሴት አገባ ።
ሁለቱም ፈሪያ እግዚአብሔር ያደረባቸው በጎ ሥራን የሚሠሩ ሰዎች ነበሩ የፀጋ ዘአብ ሚስት ሣራ ሃይማኖት ከምግባር መልክና ደም ግባት ከሙያ ጋር አሟልቷ የሰጣት ሴት ነበረች ። አማቷ የፀጋ ዘአብ አባት " ወረደ ምሕረት " የሥራዋን ደግነት አይተው " እግዚኀረያ " ብለው ስም አወጡላት ጌታ የመረጣት ማለታቸው ነው።
#በሊቀ_መላእክት_በቅዱስ_ሚካኤል አብሳሪነት ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ተወለዱ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ፂዮን ።(የጽዮን ደስታዋ)ብለው ሰየሟቸው፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹ አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ማለትም ‹‹አንዱ አብ ቅዱስ ነው አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነዋል። ይህን ጊዜ እናታቸው እግዚ ኀረያም በመገረም ሆና " ይህ ሥራ የአባት ነው ላንተ የሚገባህ ጡት መጥባት ነው" ብላ ጡቷን አጎረሰችሁ ፡፡
#ቅዱሳን_መላእክት ቀን ከሌት #ቅዱስ_ቅዱስ_ቅዱስ እያሉ ያመሰግናሉ ኢሳ 6፥÷6 ይህም የህጻኑ ሁኔታ መላእካዊ ግብሩን ገና በህጻንነት የገለጠ ሁኔታ ነበር። ካህኑ ፀጋ ዘአብ የወቅቱን የቤተ ክርሰቲያን አገልግሎታቸውን ጨርሰው ወደ ቤታቸው ሲገቡ ሚስታቸው እግዚ ኀረያ በመገረም ሆና የሦስት ቀን ልጃቸው ፍስሐ ፂዮን እንዴት ባለ ምሥጋና ፈጣሪያቸውን እንዳመሰገነ ነገረቻቸው ጸጋ ዘአብም ህጻኑን ተቀብለው ታቅፈው እየሳሙ ልጄ ሺህ ዘመን ኑርልኝ እንዲ እያልክ በቤተ መቅደስ ስትቀድስ አይህ ዘንድ እመኛለው አሉ።
‹‹ #ተክለ_ሃይማኖት ›› ብሎ #የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ፍስሐ ፂዮን የሚለውን ስሙን በፈጣሪው ትዛዝ መሠረት ጠራቸው፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው ዲቊናን፤ በ22 ዓመታቸው ደግሞ ቅስናን ከግብፃዊው ጳጳስ ከአባ ጌርሎስ ወይም (አባ ቄርሎስ) ዘንድ ተቀብለዋል፡፡
ሐዋርያዊ ተግባርንም በከተታ እና በፈጠጋር (በጽላልሽና በአካባቢዋ፣በዳሞት በምድረ ወላይታና አካባቢው ፣በአምሓራና በሸዋ በሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ በኣድያማተ ትግራይ፣በገዳመ ዋሊ (ዋልድባ) ፣በገነተ ማርያም ላስታ በደብረ ዘመዶ ማርያም ገዳም በዚያው በላስታ፣ በኤርትራ ገዳማት ፣በደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ ገዳም ወዘተ በአገሪቱ ወንጌል ባልተዳረሰበት ቦታ ሁሉ እየተዘዋወሩ ኢትዮጵያ አንዲት የሐዋርያት ወንጌል ሰፍተዋታል ።
#ጻድቁ_አባታችን ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደ ገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና በመኖራቸው፤ እርሳቸው በአሚነ ሥላሴ ጸንተው ሌሎችንም እንዲጸኑና እንዲያምኑ በማድረጋቸው፤ እንደዚሁም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ በመስበክ በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሰባኬ ወንጌል በመኾናቸው ‹‹ #ተክለ_ሃይማኖት ›› ተብለው ይጠራሉ::
#በየ_ደረሱበትም ከሥራው ጽናት ከተአምራቱ ብዛት የተነሳ አንተ ሰውነህን ወይስ መላእክ ነህ ንገረን ይሉት ነበር በዚህም በደብረ ዳሞት አቡነ አረጋዊ ገዳም 10 ዓመት ከቆዮ በኃላ ተሰናብቷቸው ሊሄድ ተነሳ ሁሉም ከፍቅሩ ጽናት የተነሳ አለቀሱለት አበምኔቱም ይህን ሰው ኃጢያቴ አባሮታልና ወየውልኝ ብሎ መነኮሳቱን ሰብስቦ ሊሸኙት ተነሱ ከገዳሞም ያለ እረጅም ገመድ (ጠፈር) መውረድም ሆነ መውጣት አይቻልም ነበርና የመውረጃውን ገመድ (ጠፍር) ይዞ ይወርድ ዘንድ ጀመረ ጥንተ ጠላት ዲያቢሎስ ገመዱን ከካስማው ላይ ቆረጠው አባታችንም ይህን አስደንጋጭ ክስሀት ተከትሎ የተሰጣቸው የፀጋ ክንፍ በገዐድ ተገለጠ አበ ምኔቱና መነኮሳቱም ከገዳሙ አፈፍ ሆነው የሚሆነውን ያዮ ነበር ጻድቁም እንደ ሰማያዊ መላእክ በክንፉቸው በረው በደህና ከመሬት ደረሱ መነኮሳቱም መንክር እግዚአብሔር በላዕለ ቅዱሳኒሁ ብለው አደነቁ::
ከዚህም ባለፈ ህዳር 24ቀን መላእኩ ከምድራዊ ቦታቸው ነጥቆ ወስዶ ከሱራፌል ጋር ቀላቀላቸው በልጅነት አንደበታቸው አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ብለው ያመሠገኑት አግአስተ ዓለም ቅድስት ሥላሴን ዛሬ ደግሞ በዙፋኑ ላይ እናዳለ እያዮት በከንፈሮቻቸው ሰለሱት ቀደሱት በወርቅ ማዕጥንትም ዙፋኑን አጠኑ ።ወደ ቀደመም ኑሯቸው መላኩ መለሳቸውና ተጋድሏቸውን ቀጠሉ።
#በገዳመ አስቄጥስ ግብጽ እና ከኢየሩሳሌም።ጉብኝት በኃላ እየዞሩ ወንጌልን ለማስተማር ባይቻላቸው ስለዚህ በአንድ ቦታ መቆምን መረጡ ከፊት ከኃላ ከግራ ከቀኝ የሚያነቃ የሶር ሶማያ ስለው በመትከል በደብረ አስቦ በደብረ አስቦ ዋሻ ከዘረጉ ሳያጥፉ ከቆሙ ሳይቀመጡ ለ22 ዓመታት በጸሎት ጸኑ ጥር 4 ቀን 12 88ዓ.ም በ92 ዓመት ሲሆናቸው አንዲቱ የእግራቸው አገዳ ከመቆም ብዛት ተሰብራ ወደቀች ጸሎታቸውንም ሳያቆርጡ በአንድ እግራቸው 7 ዓመት አክለው በጸሎት ተጎ በድምሩም 29 ዓመት በጸሎት ተጋደሉ :: ከፈጣሪ ዘንድም ብዙ ጸጋና ቃል ኪዳን ከተቀበሉ በኃላ በ99ዓመት ከ10ወር ከ10ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በክብር አርፈዋል:: እንደ ሰው በምድር ተወልደው እንደ መላክት የኖሩ አዲስ መላክ ያልናቸውም ለዚሁ ነው።
የጻድቁ አባት የአቡነ #ተክለ_ሃይማኖት እረድኤት በረከታቸው በአማላጅነታቸው የምትገኝ ጸጋ ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትኑር .....አሜን!
________
ተፈጥሮ ከመላእክት ወገን ያልሆነ ሰው ሆኖ ሳለ ነገር ግን በሃይማኖቱ ጽናት በምግባሩ ቅንሐት እና በተጋድሎዎ ብዛት ምድራዊ ሲሆን ሰማያዊ አዳማዊ ሲሆን መላእካዊ ለመሆን የበቃ ሐዲስ መላእክ ነው :: ተክለ ኤል
ቅዱሳን መላእክት በዘር የተገኙ አይደሉም ተክለ ኤል ( #ተክለ_ሃይማኖት ) ግን ከሕግ ዘር የተገኘ ሰው የሆነ አዲስ መላእክ ነው ::
‹ #ተክል › ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣፣ የሚሸተት፣ቢበሉት ጥጋብ ፣ቢያርፉበት ጥላ የሚሆን ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ ሥርዓት ማለት ነው /ማቴ.፲፭፥፲፫/፡፡
" #ኤል " ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ማለት ነው :: ስመ መላእክት ስመ እግዚአብሔርን ያዘለ በመሆኑ የሁሉም ቅዱሳን መላእክ ስም "ኤል" የሚል መቀጽል አለው #ለምሳሌ :-ሚካ-ኤል ፣ ገብር-ኤል ፣ ዑራ -ኤል፣ ወዘተ .... ስለዚህ ተክለ ኤል ስንልም #የእግዚአብሔር _ተክል ማለታችን ነው :: ታላቁ ሊቅ ቅዱስ #ባስልዮስ ዘ ቄሳሪያ እኔስ #እግዚአብሔር ባልኩ ጊዜ #አብ_ወልድ_መንፈስ_ቅዱስ ማለቴ ነው ብሎ እንደተናገረ እኛም እግዚአብሔር ስንል አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለታችንነውና #ተክለ_ኤል ስንለውም የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተክል ማለታችን ጭምር ነው::
#ቦታው በሸዋ ክፍለ ሀገር ዛሬ ኢቲሳ በመባል በሚታወቀው ከከሰም ጅረት አካባቢ ባለ ቦታ በጥንቱ ፈጠጋር ቡልጋ በደብረ ጽላልሽ አውራጃ ዞረሬ በተባለው ሥፍራ ነው ። በዚሁ ሥፍራ (ዘርዐ ዮሐንስ) ፀጋ ዘአብ የሚባል የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህን የነበረ ጻድቅ ሰው ነበር "ጸጋ ዘአብ " ማለት የአብ ሥጦታ ማለት ነው ካህኑ ጸጋ ዘአብ በሃገሩ ደጋግ ከሆኑ ሰዎች ወገን ሣራ የምትባል ሴት አገባ ።
ሁለቱም ፈሪያ እግዚአብሔር ያደረባቸው በጎ ሥራን የሚሠሩ ሰዎች ነበሩ የፀጋ ዘአብ ሚስት ሣራ ሃይማኖት ከምግባር መልክና ደም ግባት ከሙያ ጋር አሟልቷ የሰጣት ሴት ነበረች ። አማቷ የፀጋ ዘአብ አባት " ወረደ ምሕረት " የሥራዋን ደግነት አይተው " እግዚኀረያ " ብለው ስም አወጡላት ጌታ የመረጣት ማለታቸው ነው።
#በሊቀ_መላእክት_በቅዱስ_ሚካኤል አብሳሪነት ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ተወለዱ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ፂዮን ።(የጽዮን ደስታዋ)ብለው ሰየሟቸው፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹ አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ማለትም ‹‹አንዱ አብ ቅዱስ ነው አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነዋል። ይህን ጊዜ እናታቸው እግዚ ኀረያም በመገረም ሆና " ይህ ሥራ የአባት ነው ላንተ የሚገባህ ጡት መጥባት ነው" ብላ ጡቷን አጎረሰችሁ ፡፡
#ቅዱሳን_መላእክት ቀን ከሌት #ቅዱስ_ቅዱስ_ቅዱስ እያሉ ያመሰግናሉ ኢሳ 6፥÷6 ይህም የህጻኑ ሁኔታ መላእካዊ ግብሩን ገና በህጻንነት የገለጠ ሁኔታ ነበር። ካህኑ ፀጋ ዘአብ የወቅቱን የቤተ ክርሰቲያን አገልግሎታቸውን ጨርሰው ወደ ቤታቸው ሲገቡ ሚስታቸው እግዚ ኀረያ በመገረም ሆና የሦስት ቀን ልጃቸው ፍስሐ ፂዮን እንዴት ባለ ምሥጋና ፈጣሪያቸውን እንዳመሰገነ ነገረቻቸው ጸጋ ዘአብም ህጻኑን ተቀብለው ታቅፈው እየሳሙ ልጄ ሺህ ዘመን ኑርልኝ እንዲ እያልክ በቤተ መቅደስ ስትቀድስ አይህ ዘንድ እመኛለው አሉ።
‹‹ #ተክለ_ሃይማኖት ›› ብሎ #የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ፍስሐ ፂዮን የሚለውን ስሙን በፈጣሪው ትዛዝ መሠረት ጠራቸው፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው ዲቊናን፤ በ22 ዓመታቸው ደግሞ ቅስናን ከግብፃዊው ጳጳስ ከአባ ጌርሎስ ወይም (አባ ቄርሎስ) ዘንድ ተቀብለዋል፡፡
ሐዋርያዊ ተግባርንም በከተታ እና በፈጠጋር (በጽላልሽና በአካባቢዋ፣በዳሞት በምድረ ወላይታና አካባቢው ፣በአምሓራና በሸዋ በሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ በኣድያማተ ትግራይ፣በገዳመ ዋሊ (ዋልድባ) ፣በገነተ ማርያም ላስታ በደብረ ዘመዶ ማርያም ገዳም በዚያው በላስታ፣ በኤርትራ ገዳማት ፣በደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ ገዳም ወዘተ በአገሪቱ ወንጌል ባልተዳረሰበት ቦታ ሁሉ እየተዘዋወሩ ኢትዮጵያ አንዲት የሐዋርያት ወንጌል ሰፍተዋታል ።
#ጻድቁ_አባታችን ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደ ገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና በመኖራቸው፤ እርሳቸው በአሚነ ሥላሴ ጸንተው ሌሎችንም እንዲጸኑና እንዲያምኑ በማድረጋቸው፤ እንደዚሁም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ በመስበክ በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሰባኬ ወንጌል በመኾናቸው ‹‹ #ተክለ_ሃይማኖት ›› ተብለው ይጠራሉ::
#በየ_ደረሱበትም ከሥራው ጽናት ከተአምራቱ ብዛት የተነሳ አንተ ሰውነህን ወይስ መላእክ ነህ ንገረን ይሉት ነበር በዚህም በደብረ ዳሞት አቡነ አረጋዊ ገዳም 10 ዓመት ከቆዮ በኃላ ተሰናብቷቸው ሊሄድ ተነሳ ሁሉም ከፍቅሩ ጽናት የተነሳ አለቀሱለት አበምኔቱም ይህን ሰው ኃጢያቴ አባሮታልና ወየውልኝ ብሎ መነኮሳቱን ሰብስቦ ሊሸኙት ተነሱ ከገዳሞም ያለ እረጅም ገመድ (ጠፈር) መውረድም ሆነ መውጣት አይቻልም ነበርና የመውረጃውን ገመድ (ጠፍር) ይዞ ይወርድ ዘንድ ጀመረ ጥንተ ጠላት ዲያቢሎስ ገመዱን ከካስማው ላይ ቆረጠው አባታችንም ይህን አስደንጋጭ ክስሀት ተከትሎ የተሰጣቸው የፀጋ ክንፍ በገዐድ ተገለጠ አበ ምኔቱና መነኮሳቱም ከገዳሙ አፈፍ ሆነው የሚሆነውን ያዮ ነበር ጻድቁም እንደ ሰማያዊ መላእክ በክንፉቸው በረው በደህና ከመሬት ደረሱ መነኮሳቱም መንክር እግዚአብሔር በላዕለ ቅዱሳኒሁ ብለው አደነቁ::
ከዚህም ባለፈ ህዳር 24ቀን መላእኩ ከምድራዊ ቦታቸው ነጥቆ ወስዶ ከሱራፌል ጋር ቀላቀላቸው በልጅነት አንደበታቸው አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ብለው ያመሠገኑት አግአስተ ዓለም ቅድስት ሥላሴን ዛሬ ደግሞ በዙፋኑ ላይ እናዳለ እያዮት በከንፈሮቻቸው ሰለሱት ቀደሱት በወርቅ ማዕጥንትም ዙፋኑን አጠኑ ።ወደ ቀደመም ኑሯቸው መላኩ መለሳቸውና ተጋድሏቸውን ቀጠሉ።
#በገዳመ አስቄጥስ ግብጽ እና ከኢየሩሳሌም።ጉብኝት በኃላ እየዞሩ ወንጌልን ለማስተማር ባይቻላቸው ስለዚህ በአንድ ቦታ መቆምን መረጡ ከፊት ከኃላ ከግራ ከቀኝ የሚያነቃ የሶር ሶማያ ስለው በመትከል በደብረ አስቦ በደብረ አስቦ ዋሻ ከዘረጉ ሳያጥፉ ከቆሙ ሳይቀመጡ ለ22 ዓመታት በጸሎት ጸኑ ጥር 4 ቀን 12 88ዓ.ም በ92 ዓመት ሲሆናቸው አንዲቱ የእግራቸው አገዳ ከመቆም ብዛት ተሰብራ ወደቀች ጸሎታቸውንም ሳያቆርጡ በአንድ እግራቸው 7 ዓመት አክለው በጸሎት ተጎ በድምሩም 29 ዓመት በጸሎት ተጋደሉ :: ከፈጣሪ ዘንድም ብዙ ጸጋና ቃል ኪዳን ከተቀበሉ በኃላ በ99ዓመት ከ10ወር ከ10ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በክብር አርፈዋል:: እንደ ሰው በምድር ተወልደው እንደ መላክት የኖሩ አዲስ መላክ ያልናቸውም ለዚሁ ነው።
የጻድቁ አባት የአቡነ #ተክለ_ሃይማኖት እረድኤት በረከታቸው በአማላጅነታቸው የምትገኝ ጸጋ ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትኑር .....አሜን!
" #ኢትዮጵያዊው_ኤልሳዕ
#በአጽሙ_ሙት_ያስነሳ "
_
፪ኛ ነገሥት ፲ ፫÷፳ -፳ ፩
ገ/ተ #ሃይማኖት ም/፶ ፫
አጥንት በመጻሕፍ ቅዱስ ውስጥ በምሳሌነት ሲጠቀስ ሦስት ነገሮችን ያመለክታል።
፩ የሰው ኃይልን ያመላክታል መዝ ፶ ፫፥፭ ኢሳ፴ ፰፥፲ ፫
፪ የቅርብ ዝምድና መግለጫ ሆኖ ቀርቧል ዘፍ ፳ ፱÷፲ ፬ ሳሙ ፱÷፪
፫ የሞተ ሰውን ክብር ያስረዳል ዘፍ ፶÷፳ ፭ ዕብ ፲ ፩÷፳ ፪
#ይበልጡኑ_የቅዱሳን_ሰዎች ሞት /አጥንት (አጽም)/ እጅግ የከበረ ነው ። መዝ ፻ ፲ ፭ (፻ ፲ ፮) ÷፲ ፭ ለአብነትም ተቀብሮ የነበረው የኤልሳዕ አጥንት /አጽም/ ሌላ የሞተ ሰው ከሞት እንዳስነሳ መመልከት በቂ ነው። ከሞዓብም አደጋ ጣዮች በየዓመቱ ወደ አገሩ ይገቡ ነበር።ሰዎችም አንድ ሰው ሲቀብሩ አደጋ ጣዮችን አዩ፥ ሬሳውንም በኤልሳዕ መቃብር ጣሉት፤ የኤልሳዕንም አጥንት በነካ ጊዜ ሰውዮው ድኖ በእግሩ ቆመ። ፪ኛ ነገሥት ፲ ፫÷፳ -፳ ፩
በተመሳሳይ ኢትዮጵያዊው ኤልሳዕ ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖትም የሥጋ ድካም ከትጋቱ እንዳያስታጉለው በስምንት ሰለታም ጦር እራሱን ከቦ ከደብረ አስቦ ዋሻ ከቆመ ሳይቀመጥ ከዘረጋ ሳያጥፍ ፳ ፪ ዓመት ሲጋደል ሳለ ከመቆም ብዛት አንዲቷ የእግሩ አገዳ ተሰበረችና ከሰውነቱ ተለይታ ወደቀች።
#ደቀ_መዛሙርቱም እንደ ማንም መስሏቸው ስባረ እግሩን ከመቃብር ሥፍራ ወረወሯት የኤልሳዕን አጽም ሲነካው ከሞት ድኖ እንደተነሳው ሰው የአባታችን የእግራቸው አጥንት የነካው በመቃብሩ ሥፍራ ተቀብሮ የነበረ አንድ ሰው አፈፍ ብሎ ድኖ በእግሩ ቆመ ። ገ/ተ ሃይማኖት ፶ ፫
የአባታችንንም ስባረ አጽም (ስባረ እግር) እያመሰገነ ሰላምታ ሰጠ " ይህን ያዮ ደቀ መዛሙርቶቻቸውም የጻድቁ ስባረ አጽም ገባሬ ተአምራት መሆኗን አውቀው ከመንበሩ እግር በታች አክብረው በሰበን ጠቅልለው ቀብረዋታል::
" #የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፥ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል። እግዚአብሔር አጥንቶቻቸውን ሁሉ ይጠብቃል፥ ከእነርሱም አንድ አይሰበርም። " መዝ ፴ ፫{፴ ፬}÷፲ ፱-፳ ይህ የቅዱሳን አጥንት (አጽም) እግዚአብሔር የማይለየውና ሌት ተቀን የሚጠብቀው ነውና ቅዱሳን ጻድቃን ካረፉበት ሄዶ መሳለም በረከትን ያሰጣል ከሥጋም ከነፍስም ህመም አድኖ በጤና ያቆማልና የአጽማቸውን በዓል ማክበር እጅግ የሚገባ ነው ::
ቅዱስ ጳውሎስ በልብሱ ጨርቅ " (ሐዋ፲ ፱÷፲ ፩-፲ ፪) ቅዱስ ጴጥሮስ በሰውነቱ ጥላ ድውያንን ሁሉ ይፈውሳቸው ነበር ። ( ሐዋ ፭÷፲ ፭ ) ቅዱሳን የነፍሳቸው ቅድስና ለሥጋቸው፣ የሥጋቸው ቅድስና ለለበሱት ልብስና ለአካላቸው ጥላ ተርፎ ድንቅ ተአምራትን የሚሰራ ከሆነ እግዚአብሔር የሚጠብቀው አጽማቸውማ እንዴት አብልጦ ድንቆችን አይሰራ?!::
#አጥንት_ለሰዉ ልጅ ተክለ ሰውነት ወሳኝ ድርሻ አለው። ከሚሰጣቸው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች መካከል የተወሰኑት ብንዳስስ፤ ለሰዉነታችን ቅርፅ ለመስጠት፣ የሰዉነት የውስጥ አካላት (Organs) ከአደጋ ለመከላከል #ለምሳሌ ደረት የሚያርፍበት ክፍለ አጥንት ለሳንባና ለልብ ከለላ(covering) ይሰጣል፤ የራስ ቅል አጥንት አንጎል ምንም አይነት ጉዳት እንዳይገጥመው ጠንካራ ልባስ ሆኖ ይከላከላል ፣ ሥጋና ጡነቻዎቻችንን አጣብቆ ለመያዝና የካልስየም ንጥረ ነገርን ለማጠራቀም ይረዳል፡፡
ክቡር የሆነ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖትም ለቀናች ሃይማኖቱ አጥንት ነው። አጥንት የሌለው አካል ጤፍ እንደሌለው ማዳበሪያ መቆም አይቻለሁም:: ሀገሪቱና ቤተክርስቲያኒቱ ዶግማ ቀኖናና ትውፊቷን ይዛ ቅርጻን ሳትለቅ ቀጥ ብላ እንድትቆም አድርጓታልና።
# ምዕመኗ ልዮ ልዮ በሆነ በእግዳ ትምህርት ከበረትቷ እንዳይኮበልሉ ኖላዊ ትጉሁ ሆኖ
በጾም በጸሎቱ የሀገር ዋልታ በመሆንም አካል ለምትባል ቅድስት ቤተክርስቲያን እንደ
አጥንት ጋሻ፣ መከታ፣ ጥላ ፣ከለላ ሆነላት።
የሃይማኖት ማነስ የምግባር ጉድለት እንዳያጋጥማትም በቃሉ ትምህር በእጁ ተአምራት
በበረከቱ ሞላት፤ በረድኤቱ ጋረዳት እንደ አጥንት የሃይማኖት መፍሰሻ ነቅ የወንጌል
መፍለቂያ ምንጭም አደረጋት።
#የምታበረታ_አጥንት_በረከቱ_ትደርብን ! #አሜን!!
ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
ጥር ፳ ፬\፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#በአጽሙ_ሙት_ያስነሳ "
_
፪ኛ ነገሥት ፲ ፫÷፳ -፳ ፩
ገ/ተ #ሃይማኖት ም/፶ ፫
አጥንት በመጻሕፍ ቅዱስ ውስጥ በምሳሌነት ሲጠቀስ ሦስት ነገሮችን ያመለክታል።
፩ የሰው ኃይልን ያመላክታል መዝ ፶ ፫፥፭ ኢሳ፴ ፰፥፲ ፫
፪ የቅርብ ዝምድና መግለጫ ሆኖ ቀርቧል ዘፍ ፳ ፱÷፲ ፬ ሳሙ ፱÷፪
፫ የሞተ ሰውን ክብር ያስረዳል ዘፍ ፶÷፳ ፭ ዕብ ፲ ፩÷፳ ፪
#ይበልጡኑ_የቅዱሳን_ሰዎች ሞት /አጥንት (አጽም)/ እጅግ የከበረ ነው ። መዝ ፻ ፲ ፭ (፻ ፲ ፮) ÷፲ ፭ ለአብነትም ተቀብሮ የነበረው የኤልሳዕ አጥንት /አጽም/ ሌላ የሞተ ሰው ከሞት እንዳስነሳ መመልከት በቂ ነው። ከሞዓብም አደጋ ጣዮች በየዓመቱ ወደ አገሩ ይገቡ ነበር።ሰዎችም አንድ ሰው ሲቀብሩ አደጋ ጣዮችን አዩ፥ ሬሳውንም በኤልሳዕ መቃብር ጣሉት፤ የኤልሳዕንም አጥንት በነካ ጊዜ ሰውዮው ድኖ በእግሩ ቆመ። ፪ኛ ነገሥት ፲ ፫÷፳ -፳ ፩
በተመሳሳይ ኢትዮጵያዊው ኤልሳዕ ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖትም የሥጋ ድካም ከትጋቱ እንዳያስታጉለው በስምንት ሰለታም ጦር እራሱን ከቦ ከደብረ አስቦ ዋሻ ከቆመ ሳይቀመጥ ከዘረጋ ሳያጥፍ ፳ ፪ ዓመት ሲጋደል ሳለ ከመቆም ብዛት አንዲቷ የእግሩ አገዳ ተሰበረችና ከሰውነቱ ተለይታ ወደቀች።
#ደቀ_መዛሙርቱም እንደ ማንም መስሏቸው ስባረ እግሩን ከመቃብር ሥፍራ ወረወሯት የኤልሳዕን አጽም ሲነካው ከሞት ድኖ እንደተነሳው ሰው የአባታችን የእግራቸው አጥንት የነካው በመቃብሩ ሥፍራ ተቀብሮ የነበረ አንድ ሰው አፈፍ ብሎ ድኖ በእግሩ ቆመ ። ገ/ተ ሃይማኖት ፶ ፫
የአባታችንንም ስባረ አጽም (ስባረ እግር) እያመሰገነ ሰላምታ ሰጠ " ይህን ያዮ ደቀ መዛሙርቶቻቸውም የጻድቁ ስባረ አጽም ገባሬ ተአምራት መሆኗን አውቀው ከመንበሩ እግር በታች አክብረው በሰበን ጠቅልለው ቀብረዋታል::
" #የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፥ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል። እግዚአብሔር አጥንቶቻቸውን ሁሉ ይጠብቃል፥ ከእነርሱም አንድ አይሰበርም። " መዝ ፴ ፫{፴ ፬}÷፲ ፱-፳ ይህ የቅዱሳን አጥንት (አጽም) እግዚአብሔር የማይለየውና ሌት ተቀን የሚጠብቀው ነውና ቅዱሳን ጻድቃን ካረፉበት ሄዶ መሳለም በረከትን ያሰጣል ከሥጋም ከነፍስም ህመም አድኖ በጤና ያቆማልና የአጽማቸውን በዓል ማክበር እጅግ የሚገባ ነው ::
ቅዱስ ጳውሎስ በልብሱ ጨርቅ " (ሐዋ፲ ፱÷፲ ፩-፲ ፪) ቅዱስ ጴጥሮስ በሰውነቱ ጥላ ድውያንን ሁሉ ይፈውሳቸው ነበር ። ( ሐዋ ፭÷፲ ፭ ) ቅዱሳን የነፍሳቸው ቅድስና ለሥጋቸው፣ የሥጋቸው ቅድስና ለለበሱት ልብስና ለአካላቸው ጥላ ተርፎ ድንቅ ተአምራትን የሚሰራ ከሆነ እግዚአብሔር የሚጠብቀው አጽማቸውማ እንዴት አብልጦ ድንቆችን አይሰራ?!::
#አጥንት_ለሰዉ ልጅ ተክለ ሰውነት ወሳኝ ድርሻ አለው። ከሚሰጣቸው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች መካከል የተወሰኑት ብንዳስስ፤ ለሰዉነታችን ቅርፅ ለመስጠት፣ የሰዉነት የውስጥ አካላት (Organs) ከአደጋ ለመከላከል #ለምሳሌ ደረት የሚያርፍበት ክፍለ አጥንት ለሳንባና ለልብ ከለላ(covering) ይሰጣል፤ የራስ ቅል አጥንት አንጎል ምንም አይነት ጉዳት እንዳይገጥመው ጠንካራ ልባስ ሆኖ ይከላከላል ፣ ሥጋና ጡነቻዎቻችንን አጣብቆ ለመያዝና የካልስየም ንጥረ ነገርን ለማጠራቀም ይረዳል፡፡
ክቡር የሆነ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖትም ለቀናች ሃይማኖቱ አጥንት ነው። አጥንት የሌለው አካል ጤፍ እንደሌለው ማዳበሪያ መቆም አይቻለሁም:: ሀገሪቱና ቤተክርስቲያኒቱ ዶግማ ቀኖናና ትውፊቷን ይዛ ቅርጻን ሳትለቅ ቀጥ ብላ እንድትቆም አድርጓታልና።
# ምዕመኗ ልዮ ልዮ በሆነ በእግዳ ትምህርት ከበረትቷ እንዳይኮበልሉ ኖላዊ ትጉሁ ሆኖ
በጾም በጸሎቱ የሀገር ዋልታ በመሆንም አካል ለምትባል ቅድስት ቤተክርስቲያን እንደ
አጥንት ጋሻ፣ መከታ፣ ጥላ ፣ከለላ ሆነላት።
የሃይማኖት ማነስ የምግባር ጉድለት እንዳያጋጥማትም በቃሉ ትምህር በእጁ ተአምራት
በበረከቱ ሞላት፤ በረድኤቱ ጋረዳት እንደ አጥንት የሃይማኖት መፍሰሻ ነቅ የወንጌል
መፍለቂያ ምንጭም አደረጋት።
#የምታበረታ_አጥንት_በረከቱ_ትደርብን ! #አሜን!!
ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
ጥር ፳ ፬\፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በስመ አብ፤ ወወልድ፤ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከጥር ፳፱ እስከ የካቲት ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ለ ፫ ተከታታይ ቀናት በመላው ዓለም የታወጀው የነነዌ ፆም እና ምሕላ መጠናቀቅን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ::
#Ethiopia | በትንቢተ ዮናስ በሰፊው እንደተጠቀሰው የነነዌ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት ላይ ስለአመጹ እና ግብራቸውም በእግዚአብሔር ፊት አጸያፊ በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር ዮናስን “ተነስተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፤ ክፋታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቷልና በእርስዋ ላይ ስበክ” በማለት አዘዘው፡፡ ትንቢተ ዮናስ ምዕ ፩ ቁጥር ፪ ዮናስም ድምፁን ከፍ አድርጎ ለነነዌ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል ሲሰብክ “የነነዌ ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ፤ ለጾም አዋጅ ነገሩ፤ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ፡፡ ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ፤ እርሱም ከዙፋኑ ተነስቶ መጎናጸፊያውን አወለቀ ማቅም ለበሰ፤ በአመድም ላይ ተቀመጠ፡፡ አዋጅም አስነገረ፤ በነነዌ ውስጥ የንጉሡንና የመኳንንቱን ትእዛዝ አሳወጀ፤ እንዲህም አለ ሰዎችና እንስሶች፤ ላሞችና በጎች አንዳችን አይቅመሱ፣ አይሰማሩ፣ ውኃንም አይጠጡ፤ ሰዎችና እንስሶችም በማቅ ይከደኑ፣ ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ጩኸት ይጩኹ፤ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ፡፡ እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይጸጸት እንደሆነ ማን ያውቃል፡፡ እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደተመለሱ ሥራቸውንም አየ፤ እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም” ትንቢተ ዮናስ ፫፡ ፭-፲
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም ይህን የነነዌ ሰዎች ፆም መነሻ በማድረግ የነነዌ ሰዎችን በምሕረቱ የጎበኘ አምላክ እኛንም በምሕረቱ ይቅር ይለን ዘንድ በየዓመቱ በአዋጅ በመፆም አምላካችንን ስንማጸንበት ኖረናል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባዔ በጥር ፳፮ ቀን ፳፻፲፭ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ በወሰነው መሠረት የካቲት ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የተጠናቀቀው የነነዌ ፆምና ምሕላ ልዩ በሆነ በመንፈሳዊ የንስሐ ጸሎት በሰላም ተጠናቋል፡፡
በምሕላውም ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ጀምሮ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ካህናት፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ አገልጋዮች እና ምእመናን እንደነነዌ ሰዎች ጥቁር ለብሰን ጠዋትና ማታ በጸሎት ፤ በምሕላ፤ ቀን በቅዳሴ እንዲሁም በሰባቱ የጸሎት ጊዜያት ፈጣሪያችንን ስንለምን እና ስንማጸን የቆየንበት ምክንያት በቤተክርስቲያናችን ላይ የመጣው ፈተና እጅግ በጣም ከባድ በመሆኑ ነው፡፡
በዚህ የጾምና የንስሐ ወቅት ምእመናን ልጆቻችን የአባቶቻችሁን ጥሪ ሰምታችሁ፤ የሹመኞችን ማዋክብና እስር ሳትፈሩ ጥቁር ለብሳችሁ ጠዋትና ማታ በጾምና በምሕላ፣ ቀን በቅዳሴ በቤተክርስቲያን ቅጥር እየተገኛችሁ ለአምላካችን ያቀረባችሁትን ጸሎት እና ምሕላ እግዚአብሔር ሰምቶ ለችግራችን መፍትሄ፣ ለሀገራችን ሰላምን እንደሚሰጠን እምነታችን ጽኑ ነው፡፡ እናንተም ምእመናን የቤተ ክርስቲያንን ጥሪ ሰምታችሁ ለሃይማኖታችሁ፣ ለሀገራችሁ አንድነትና ሰላም ያላችሁን ጥልቅ ፍቅር ስለገለፃችሁም ያገኘነው መንፈሳዊ ብርታት ሳንገልፅላችሁ አናልፍም፡፡
በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቅዱሳን አማላጅነት፣ በመላእክት ተራዳኢነት በፍፁም ፍቅርና አንድነት የያዝነውን ጸሎት እና ምሕላ አጠናቀናል፡፡ ችግራችንን ለአምላካችን በለቅሶ እና በጩኸት ነግረናል፡፡ ከዚህ በኋላ መከራው ቢጸና፣ የመከራው ጊዜ እንኳን ቢረዝም እግዚአብሔር በመከራ ውስጥ ሊያፀናን እና ሊያበረታታን አስቦ በመሆኑ በፍፁም አንናወጽም፡፡ ከእነኚህ መከራዎች በኃላም ታሪክን ጽፈን ሃይማኖታችንን ጠብቀን እና አስጠብቀን በመንፈሳዊ ጽናት እና ተጋድሎ እንሻገራለን፡፡
ጥቃቱ የቤተ ክርስቲያንን እውነት በካዱና በእውነተኛዋ ቤተ ክርስቲያን መካከል ነው፡፡ ይህም የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሃይማኖት፤ ቀኖና እና አስተዳደራዊ ሕግጋትን ጥሰው ሕገወጥ የጳጳሳት ሢመት በመደረጉ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ቅዱስ ሲኖዶስ በሕገ ቤተ ክርስቲያንና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት በጥር ፲፰ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ይህን ጥሰት የፈፀሙትን ግለሰቦች አውግዛ ከቤተ ክርስቲያን ኅብረት የለየቻቸው ቢሆንም ጉዳዩ ከግለሰቦቹ በላይ በመንግሥት ስልጣን ላይ ባሉና ጽንፈኛ በሆኑ ፖለቲከኞች እንዲሁም የሌላ እምነት ተከታዮች ጭምር የሚደገፍ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያንን ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈላት ይገኛል፡፡
እየተፈጸመ ያለው ድርጊት በሰማያዊ መንፈሳዊ ዓለምና በምድራዊ ሥጋዊ ዓለም መካከል ስለሆነ በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥም የቤተ ክርስቲያን ክብርና ተቋማዊ ልዕልና ተደፍሯል፡፡ የቤተክርስቲያን ቅጥሮች መሣሪያ በያዙ አካላትና በመንግሥት የጸጥታ መዋቅር በኃይልና በጉልበት ተወሯል፡፡ ሊቃነ ጳጳሳት አባቶች ለብዙ ዓመታት ከኖሩበት አህጉረ ስብከት ያለአንዳች የሕግ መሠረት በጸጥታ መዋቅሮች ተባረዋል፡፡ በነጻነት የመንቀሳቀስ መብቶቻቸው ተገድቦም በግዞት ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ተደርገዋል፡፡ ወደ አህጉረ ስብከታቸውም ተመልሰው መግባት እንዳይችሉ እቀባ ተደርጎባቸዋል፡፡ ካህናት አባቶች እና ምእመናንም ያለአንዳች የሕግ መሠረት በየእስር ቤቱ ያለበቂ ምክንያት በሕገወጥ መንገድ ታጉረዋል፡፡ በጸጥታ ኃይል ከመጠን በላይ ከመደብደባቸው የተነሳ የሞት፣ የከባድ እና ቀላል አካል ጉዳት እንዲደርስባቸው ምክንያት ሆኗል፡፡ በአጠቃላይም በመንግሥት ኃይሎች ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈፅሞባቸዋል፡፡
ቤተ ክርስቲያን ይህ ሁሉ በደል ቢፈጸምባትም ናዛዜ ሕዙናን የሆነው አምላካችን ለቤተ ክርስቲያናችን እና ለሀገራችን መፍትሔ እንዲያመጣልን፣ መንግሥትም ወደ ልቡ ተመልሶ ቤተክርስቲያንን እንዲያከብርና እንዲጠብቅ በሚል ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ ይህን ጾም የነነዌ ሰዎች እንዳደረጉት ጥቁር ለብሰን በፍፁም ኃዘን ወደ አምላካችን እንድንጮህ ቅዱስ ሲኖዶስ ትእዛዝ ባስተላለፈበት ማግስት በሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ሕገወጡን ቡድን በኃይል ለማስገባት በመንግሥት የጸጥታ መዋቅሮች በተወሰደ አሰቃቂ እርምጃ እስከ አሁን በደረሰን መረጃ ቁጥራቸው ከ፴ በላይ የሚሆኑ ካህናትን እና አገልጋዮችን ጨምሮ የቤተ ክርስቲያናችን ልጆች ቅጥሯ አይደፈርም፣ ቤተክርስቲያን በተወገዙ ግለሰቦች አትረክስም በሚል ለሃይማኖታቸው ሰማእትነትን ተቀብለዋል፡፡ ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆኑ ልጆቿም በደረሰባቸው ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ምክንያት በሕክምና ላይ ይገኛሉ፡፡ ከዚህ ሁሉ በደል በኋላም እስከ አሁን ድረስ የሞቱትን በአግባቡ መቅበርና የተጎዱትን በበቂ ሁኔታ ማሳከም ሳንችል ቀርተናል፡፡ እነዚህ ሰማዕታት በዚህ ኃጢያት በበዛበት ዘመን ለቤተክርስቲያን እስከሞት ድረስ በመታመን ለቤተ ክርስቲያንና ለምእመናን የጽናት ተምሳሌት በመሆናቸው ቤተክርስቲያን ስትዘክራቸው ትኖራለች፡፡ እንዲሁም ቤተ ክርስቲያን በልጆቿ ላይ እየደረሰ ባለው ሞት፤ እርዛት፤ እስራት እና መልከ ብዙ በሆነው መከራ ብታዝንም ለክርስትና እውነተኛነት ምስክሮች የሆኑ አዳዲስ ቅዱሳን ሰማእታትን በማግኘቷም እጅግ ደስ ትሰኛለች፡፡
በስመ አብ፤ ወወልድ፤ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከጥር ፳፱ እስከ የካቲት ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ለ ፫ ተከታታይ ቀናት በመላው ዓለም የታወጀው የነነዌ ፆም እና ምሕላ መጠናቀቅን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ::
#Ethiopia | በትንቢተ ዮናስ በሰፊው እንደተጠቀሰው የነነዌ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት ላይ ስለአመጹ እና ግብራቸውም በእግዚአብሔር ፊት አጸያፊ በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር ዮናስን “ተነስተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፤ ክፋታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቷልና በእርስዋ ላይ ስበክ” በማለት አዘዘው፡፡ ትንቢተ ዮናስ ምዕ ፩ ቁጥር ፪ ዮናስም ድምፁን ከፍ አድርጎ ለነነዌ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል ሲሰብክ “የነነዌ ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ፤ ለጾም አዋጅ ነገሩ፤ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ፡፡ ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ፤ እርሱም ከዙፋኑ ተነስቶ መጎናጸፊያውን አወለቀ ማቅም ለበሰ፤ በአመድም ላይ ተቀመጠ፡፡ አዋጅም አስነገረ፤ በነነዌ ውስጥ የንጉሡንና የመኳንንቱን ትእዛዝ አሳወጀ፤ እንዲህም አለ ሰዎችና እንስሶች፤ ላሞችና በጎች አንዳችን አይቅመሱ፣ አይሰማሩ፣ ውኃንም አይጠጡ፤ ሰዎችና እንስሶችም በማቅ ይከደኑ፣ ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ጩኸት ይጩኹ፤ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ፡፡ እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይጸጸት እንደሆነ ማን ያውቃል፡፡ እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደተመለሱ ሥራቸውንም አየ፤ እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም” ትንቢተ ዮናስ ፫፡ ፭-፲
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም ይህን የነነዌ ሰዎች ፆም መነሻ በማድረግ የነነዌ ሰዎችን በምሕረቱ የጎበኘ አምላክ እኛንም በምሕረቱ ይቅር ይለን ዘንድ በየዓመቱ በአዋጅ በመፆም አምላካችንን ስንማጸንበት ኖረናል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባዔ በጥር ፳፮ ቀን ፳፻፲፭ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ በወሰነው መሠረት የካቲት ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የተጠናቀቀው የነነዌ ፆምና ምሕላ ልዩ በሆነ በመንፈሳዊ የንስሐ ጸሎት በሰላም ተጠናቋል፡፡
በምሕላውም ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ጀምሮ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ካህናት፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ አገልጋዮች እና ምእመናን እንደነነዌ ሰዎች ጥቁር ለብሰን ጠዋትና ማታ በጸሎት ፤ በምሕላ፤ ቀን በቅዳሴ እንዲሁም በሰባቱ የጸሎት ጊዜያት ፈጣሪያችንን ስንለምን እና ስንማጸን የቆየንበት ምክንያት በቤተክርስቲያናችን ላይ የመጣው ፈተና እጅግ በጣም ከባድ በመሆኑ ነው፡፡
በዚህ የጾምና የንስሐ ወቅት ምእመናን ልጆቻችን የአባቶቻችሁን ጥሪ ሰምታችሁ፤ የሹመኞችን ማዋክብና እስር ሳትፈሩ ጥቁር ለብሳችሁ ጠዋትና ማታ በጾምና በምሕላ፣ ቀን በቅዳሴ በቤተክርስቲያን ቅጥር እየተገኛችሁ ለአምላካችን ያቀረባችሁትን ጸሎት እና ምሕላ እግዚአብሔር ሰምቶ ለችግራችን መፍትሄ፣ ለሀገራችን ሰላምን እንደሚሰጠን እምነታችን ጽኑ ነው፡፡ እናንተም ምእመናን የቤተ ክርስቲያንን ጥሪ ሰምታችሁ ለሃይማኖታችሁ፣ ለሀገራችሁ አንድነትና ሰላም ያላችሁን ጥልቅ ፍቅር ስለገለፃችሁም ያገኘነው መንፈሳዊ ብርታት ሳንገልፅላችሁ አናልፍም፡፡
በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቅዱሳን አማላጅነት፣ በመላእክት ተራዳኢነት በፍፁም ፍቅርና አንድነት የያዝነውን ጸሎት እና ምሕላ አጠናቀናል፡፡ ችግራችንን ለአምላካችን በለቅሶ እና በጩኸት ነግረናል፡፡ ከዚህ በኋላ መከራው ቢጸና፣ የመከራው ጊዜ እንኳን ቢረዝም እግዚአብሔር በመከራ ውስጥ ሊያፀናን እና ሊያበረታታን አስቦ በመሆኑ በፍፁም አንናወጽም፡፡ ከእነኚህ መከራዎች በኃላም ታሪክን ጽፈን ሃይማኖታችንን ጠብቀን እና አስጠብቀን በመንፈሳዊ ጽናት እና ተጋድሎ እንሻገራለን፡፡
ጥቃቱ የቤተ ክርስቲያንን እውነት በካዱና በእውነተኛዋ ቤተ ክርስቲያን መካከል ነው፡፡ ይህም የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሃይማኖት፤ ቀኖና እና አስተዳደራዊ ሕግጋትን ጥሰው ሕገወጥ የጳጳሳት ሢመት በመደረጉ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ቅዱስ ሲኖዶስ በሕገ ቤተ ክርስቲያንና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት በጥር ፲፰ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ይህን ጥሰት የፈፀሙትን ግለሰቦች አውግዛ ከቤተ ክርስቲያን ኅብረት የለየቻቸው ቢሆንም ጉዳዩ ከግለሰቦቹ በላይ በመንግሥት ስልጣን ላይ ባሉና ጽንፈኛ በሆኑ ፖለቲከኞች እንዲሁም የሌላ እምነት ተከታዮች ጭምር የሚደገፍ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያንን ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈላት ይገኛል፡፡
እየተፈጸመ ያለው ድርጊት በሰማያዊ መንፈሳዊ ዓለምና በምድራዊ ሥጋዊ ዓለም መካከል ስለሆነ በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥም የቤተ ክርስቲያን ክብርና ተቋማዊ ልዕልና ተደፍሯል፡፡ የቤተክርስቲያን ቅጥሮች መሣሪያ በያዙ አካላትና በመንግሥት የጸጥታ መዋቅር በኃይልና በጉልበት ተወሯል፡፡ ሊቃነ ጳጳሳት አባቶች ለብዙ ዓመታት ከኖሩበት አህጉረ ስብከት ያለአንዳች የሕግ መሠረት በጸጥታ መዋቅሮች ተባረዋል፡፡ በነጻነት የመንቀሳቀስ መብቶቻቸው ተገድቦም በግዞት ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ተደርገዋል፡፡ ወደ አህጉረ ስብከታቸውም ተመልሰው መግባት እንዳይችሉ እቀባ ተደርጎባቸዋል፡፡ ካህናት አባቶች እና ምእመናንም ያለአንዳች የሕግ መሠረት በየእስር ቤቱ ያለበቂ ምክንያት በሕገወጥ መንገድ ታጉረዋል፡፡ በጸጥታ ኃይል ከመጠን በላይ ከመደብደባቸው የተነሳ የሞት፣ የከባድ እና ቀላል አካል ጉዳት እንዲደርስባቸው ምክንያት ሆኗል፡፡ በአጠቃላይም በመንግሥት ኃይሎች ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈፅሞባቸዋል፡፡
ቤተ ክርስቲያን ይህ ሁሉ በደል ቢፈጸምባትም ናዛዜ ሕዙናን የሆነው አምላካችን ለቤተ ክርስቲያናችን እና ለሀገራችን መፍትሔ እንዲያመጣልን፣ መንግሥትም ወደ ልቡ ተመልሶ ቤተክርስቲያንን እንዲያከብርና እንዲጠብቅ በሚል ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ ይህን ጾም የነነዌ ሰዎች እንዳደረጉት ጥቁር ለብሰን በፍፁም ኃዘን ወደ አምላካችን እንድንጮህ ቅዱስ ሲኖዶስ ትእዛዝ ባስተላለፈበት ማግስት በሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ሕገወጡን ቡድን በኃይል ለማስገባት በመንግሥት የጸጥታ መዋቅሮች በተወሰደ አሰቃቂ እርምጃ እስከ አሁን በደረሰን መረጃ ቁጥራቸው ከ፴ በላይ የሚሆኑ ካህናትን እና አገልጋዮችን ጨምሮ የቤተ ክርስቲያናችን ልጆች ቅጥሯ አይደፈርም፣ ቤተክርስቲያን በተወገዙ ግለሰቦች አትረክስም በሚል ለሃይማኖታቸው ሰማእትነትን ተቀብለዋል፡፡ ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆኑ ልጆቿም በደረሰባቸው ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ምክንያት በሕክምና ላይ ይገኛሉ፡፡ ከዚህ ሁሉ በደል በኋላም እስከ አሁን ድረስ የሞቱትን በአግባቡ መቅበርና የተጎዱትን በበቂ ሁኔታ ማሳከም ሳንችል ቀርተናል፡፡ እነዚህ ሰማዕታት በዚህ ኃጢያት በበዛበት ዘመን ለቤተክርስቲያን እስከሞት ድረስ በመታመን ለቤተ ክርስቲያንና ለምእመናን የጽናት ተምሳሌት በመሆናቸው ቤተክርስቲያን ስትዘክራቸው ትኖራለች፡፡ እንዲሁም ቤተ ክርስቲያን በልጆቿ ላይ እየደረሰ ባለው ሞት፤ እርዛት፤ እስራት እና መልከ ብዙ በሆነው መከራ ብታዝንም ለክርስትና እውነተኛነት ምስክሮች የሆኑ አዳዲስ ቅዱሳን ሰማእታትን በማግኘቷም እጅግ ደስ ትሰኛለች፡፡
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (ተርቢኖስ ሰብስቤ)
ሶ የፈጠረ አምላክ ተራቆተ፡፡ ጸጋውን ለዕሩቃን የሚያለብስ አምላክ ልብሱን ተገፍፎ ዕራቁቱን ቆመ፡፡ ጨለማን ለብሶ ጨለማን ተንተርሶ ይኖር የነበረውን ሰው መልሶ ብርሃን ያለብሰው ዘንድ የብርሃናት ጌታ፣ የጸጋ ሁሉ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ተገፈፈ፤ ተራቆተ፡፡
የሲኦል ወታደሮች የሆኑት አጋንንት የሰውን ልጅ ጸጋ ገፍፈውት ነበርና ጲላጦስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አሳልፎ በሰጣቸው ሰዓት ወታደሮች ልብሱን ገፍፈውታል (ማቴ 27¸27)፡፡ የሰው ልጅ ለቀረበለት ምርጫ የሰው ምላሽ ዘራፊው፤ ገራፊው ወንበዴ በርባን እንዲፈታለት ነበር፡፡ ‹‹አቅረብኩ ለከ እሳተ ወማየ፣ ደይ እዴከ ኅበ ዘፈቀድከ! እነሆ እሳትና ውኃን አቅርቤልሃለሁ፣ እጅህን ወደ ፈቀድከው ስደድ›› ሲባል የሰው ልጅ እጁን ወደ እሳት ሰደደ፡፡
7. ርግዘተ ገቦ (ጎንን መወጋት)፤
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ከሰጠ በኋላ ጎኑን በስለታም ጦር መወጋቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ርግዘት›› የሚለው ቃል ረገዘ- ወጋ ከተሰኘ የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ገቦ ማለት ደግሞ ጎን ማለት ነው፡፡ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ አጠገብ፣ በግራና በቀኙ ሁለት ወንበዴዎች ተሰቅለው ነበር፡፡ ሥጋቸው በሰንበት በመስቀል ላይ እንዳይኖር ጭናቸው ተሰብሮ እንዲወርዱ አይሁድ ጲላጦስን በለመኑት መሠረት ጭፍሮቹ የሁለቱን ወንበዴዎች ጭን ጭናቸውን ከሰበሩ በኋላ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ሲመጡ ፈጽሞ እንደሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም፡፡ ነገር ግን ከጭፍሮቹ አንዱ ጎኑን በጦር ስለወጋው ወዲያው ከጎኑ ደምና ውኃ ፈሰሰ (ዮሐ 19¸33)፡፡
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል ያደርገው ዘንድ ሞተ፤ የሰው ልጅ በዘለዓለማዊ ሞት ተይዞ ነበርና፡፡ ትልቁ ሞት በኃጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር መለየት ነው፡፡ በጌታችን ሞት ግን ሞት ራሱ ድል ተነሣ፡፡ የሞት መውጊያ በሆነ ኃጢአት የሞተውን ሰው ለማዳን ጎኑን በጦር ተወጋ፡፡ በሰው ልቡና ተተክሎ የነበረውን ኃጢአት ከነሥሩ ነቅሎ ስለጣለው ‹‹ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ?›› ተባለ፡፡ የሞት መውጊያው ኃጢአት ነበርና (1ቆሮ 15¸54-55፤ ኢሳ 25¸8፤ ሆሴ 13¸14)፡፡
ከተወጋው የጌታችን ጎን ደምና ውኃ መፍሰሱም የእግዚአብሔርን ልጅነትና የዘለዓለምን ሕይወት አጥቶ የነበረው ሰው ልጅነቱና ሕይወቱ እንደተመለሰለት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ምክንያቱም ከጎኑ በፈሰሰው ውኃ ተጠምቆ ልጅነትን፣ ደሙንም ጠጥቶ የዘለዓለም ሕይወትን ያገኛልና (ዮሐ 3¸5፤ ዮሐ 6¸54)፡፡
8. ተአሮተ ድኅሪት (ወደ ኋላ መታሠር)፤
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት እጆቹን ወደኋላ የፊጥኝ መታሠሩን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ ተአሥሮት›› የሚለው ቃል አሠረ (ሲነበብ ይላላል) ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም አሠረ ማለት ነው፡፡ ‹‹ ድኅሪት ›› የሚለው ቃል ደግሞ ተድኅረ- ወደኋላ አለ ከሚለው ግሥ የወጣ ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጊዜው በደረሰ ሰዓት ራሱን ለአይሁድ አሳልፎ በሰጠባት በዚያች ዕለትና ሰዓት ሻለቃውና ጭፍሮቹ የአይሁድም ሎሌዎች እጁን የኋሊት አሥረው መሬት ለመሬት ጎትተውታል፡፡ አፍገምግመውታል (ዮሐ 18¸12)፡፡
በኃጢአት ሰንሰለት የኋሊት ታሥሮ ጠላት ዲያብሎስ የሚያፍገመግመውን የሰው ልጅ ለማዳን፣ ሰውንም ከኃጢአት እሥራት ይፈታ ዘንድ ሲል መድኃኔዓለም ክርስቶስ በጠላቶቹ በአይሁድ እጅ የኋሊት ታሠረ፡፡
9. አምሥቱ ቅንዋተ መስቀል፤
መድኃኒታችን በመስቀል ላይ የተቸነከረባቸውን ጠንካራ የብረት ችንካሮች (ምስማሮች) የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ ቅንዋት›› የሚለው ቃል
ቀነወ- ቸነከረ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ መስቀል ማለት ደግሞ ዝም ብሎ የቆመ ግንድ ሳይሆን አሁን በየሥፍራው እንደምናየው ምልክት የተመሳቀለ እንጨት ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቸነከረባቸው አምስቱ ችንካሮች ሳዶር፣ አላዶር፣ዳናት፣ አዴራ፤ ሮዳስ ይባላሉ፡፡ እነዚህም የአምሥቱ አዕማደ ምሥጢራት ምሳሌዎች መሆናቸውን አበው ያስተምራሉ፡፡
ሐዋርያው ቶማስ ከትንሣኤ በኋላ ወንድሞቹ ሐዋርያት ስለ ትንሣኤው በነገሩት ጊዜ ‹‹የችንካሩን ምልክት በዓይኖቼ ካላየሁ፣ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላስገሁ፣ በእጄም የተወጋውን ጎኑን ካልዳሰስኩ አላምንም›› ማለቱ በብረት ቀኖት በመቸንከሩ ነበር (ዮሐ 2ዐ¸25)፡፡ መድኃኒታችን በኃጢአት ቀኖት (ምስማር) ተይዞ የነበረውን ሰው ለማዳን በብረት ቀኖት ተቸነከረ፡፡
እንግዲህ አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል የሚባሉት እነዚህ ናቸው፡፡ ድሀ ያይደለ ጌታ፤ ፍጡር ያይደለ የፈጠረውን ሥጋ ገንዘብ ያደረገ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጅ ብሎ ተናቀ፡፡ የሕማም ሰው፤ ደዌንም የሚያውቅ ሆነ፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፡፡ ሕማማችንንም ተሸከመ፡፡ ይህም የሰውን ልጅ ለማዳን ማለትም እኛን ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ ይፈውሰንና ከሕማመ ሥጋ ከሕማመ ነፍስ ሥቃይ ያሳርፈን ዘንድ ነው፡፡ ቁስለ ኃጢአታችንን ያደርቅልን ዘንድ ስለ መተላለፋችን ቆሰለ፡፡ በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን፡፡ በደላችንን ይደመስስ ዘንድ ስለ በደላችን ደቀቀ፡፡ ሊያረጋጋን ተጨነቀ፡፡ ሊያሣርፈን ተሠቃየ፡፡ አፉንም አልከፈተም፡፡
የእግዚአብሔር የመሥዋዕቱ በግ ኢየሱስ ክርስቶስ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት በሸላቾቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ እንዲሁ አፉን አልከፈተም፡፡ መልካምን እንጂ ግፍን አላደረገም ነበር፡፡ ልብንና ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ ወሰብእ ወልድ ዋህድ ኢየሱስ ክርስቶስ በጲላጦስ በተመረመረ ጊዜ በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም፡፡ በፈቃዱ ነፍሱን ስለ እኛ መሥዋእት አደረገ፡፡ ፋሲካችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሥጋውን ቆረሰልን፣ ደሙንም አፈሰሰልን (ኢሳ. 53¸1-13፤ ዮሐ. 10¸18፤ ዮሐ. 19¸30፤ 1ኛቆሮ. 5¸7)፡፡ በዚህ የተቀደሰው ሳምንት ይህንን የጌታን ውለታና የድኅነት ሥራ እናስተውል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
ምንጭ :-ማህበረ ቅዱሳን ዕለተ ቀዳሚት ሰንበት
ዓውደ ምህረት የእናንተ
የሲኦል ወታደሮች የሆኑት አጋንንት የሰውን ልጅ ጸጋ ገፍፈውት ነበርና ጲላጦስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አሳልፎ በሰጣቸው ሰዓት ወታደሮች ልብሱን ገፍፈውታል (ማቴ 27¸27)፡፡ የሰው ልጅ ለቀረበለት ምርጫ የሰው ምላሽ ዘራፊው፤ ገራፊው ወንበዴ በርባን እንዲፈታለት ነበር፡፡ ‹‹አቅረብኩ ለከ እሳተ ወማየ፣ ደይ እዴከ ኅበ ዘፈቀድከ! እነሆ እሳትና ውኃን አቅርቤልሃለሁ፣ እጅህን ወደ ፈቀድከው ስደድ›› ሲባል የሰው ልጅ እጁን ወደ እሳት ሰደደ፡፡
7. ርግዘተ ገቦ (ጎንን መወጋት)፤
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ከሰጠ በኋላ ጎኑን በስለታም ጦር መወጋቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ርግዘት›› የሚለው ቃል ረገዘ- ወጋ ከተሰኘ የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ገቦ ማለት ደግሞ ጎን ማለት ነው፡፡ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ አጠገብ፣ በግራና በቀኙ ሁለት ወንበዴዎች ተሰቅለው ነበር፡፡ ሥጋቸው በሰንበት በመስቀል ላይ እንዳይኖር ጭናቸው ተሰብሮ እንዲወርዱ አይሁድ ጲላጦስን በለመኑት መሠረት ጭፍሮቹ የሁለቱን ወንበዴዎች ጭን ጭናቸውን ከሰበሩ በኋላ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ሲመጡ ፈጽሞ እንደሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም፡፡ ነገር ግን ከጭፍሮቹ አንዱ ጎኑን በጦር ስለወጋው ወዲያው ከጎኑ ደምና ውኃ ፈሰሰ (ዮሐ 19¸33)፡፡
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል ያደርገው ዘንድ ሞተ፤ የሰው ልጅ በዘለዓለማዊ ሞት ተይዞ ነበርና፡፡ ትልቁ ሞት በኃጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር መለየት ነው፡፡ በጌታችን ሞት ግን ሞት ራሱ ድል ተነሣ፡፡ የሞት መውጊያ በሆነ ኃጢአት የሞተውን ሰው ለማዳን ጎኑን በጦር ተወጋ፡፡ በሰው ልቡና ተተክሎ የነበረውን ኃጢአት ከነሥሩ ነቅሎ ስለጣለው ‹‹ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ?›› ተባለ፡፡ የሞት መውጊያው ኃጢአት ነበርና (1ቆሮ 15¸54-55፤ ኢሳ 25¸8፤ ሆሴ 13¸14)፡፡
ከተወጋው የጌታችን ጎን ደምና ውኃ መፍሰሱም የእግዚአብሔርን ልጅነትና የዘለዓለምን ሕይወት አጥቶ የነበረው ሰው ልጅነቱና ሕይወቱ እንደተመለሰለት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ምክንያቱም ከጎኑ በፈሰሰው ውኃ ተጠምቆ ልጅነትን፣ ደሙንም ጠጥቶ የዘለዓለም ሕይወትን ያገኛልና (ዮሐ 3¸5፤ ዮሐ 6¸54)፡፡
8. ተአሮተ ድኅሪት (ወደ ኋላ መታሠር)፤
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት እጆቹን ወደኋላ የፊጥኝ መታሠሩን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ ተአሥሮት›› የሚለው ቃል አሠረ (ሲነበብ ይላላል) ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም አሠረ ማለት ነው፡፡ ‹‹ ድኅሪት ›› የሚለው ቃል ደግሞ ተድኅረ- ወደኋላ አለ ከሚለው ግሥ የወጣ ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጊዜው በደረሰ ሰዓት ራሱን ለአይሁድ አሳልፎ በሰጠባት በዚያች ዕለትና ሰዓት ሻለቃውና ጭፍሮቹ የአይሁድም ሎሌዎች እጁን የኋሊት አሥረው መሬት ለመሬት ጎትተውታል፡፡ አፍገምግመውታል (ዮሐ 18¸12)፡፡
በኃጢአት ሰንሰለት የኋሊት ታሥሮ ጠላት ዲያብሎስ የሚያፍገመግመውን የሰው ልጅ ለማዳን፣ ሰውንም ከኃጢአት እሥራት ይፈታ ዘንድ ሲል መድኃኔዓለም ክርስቶስ በጠላቶቹ በአይሁድ እጅ የኋሊት ታሠረ፡፡
9. አምሥቱ ቅንዋተ መስቀል፤
መድኃኒታችን በመስቀል ላይ የተቸነከረባቸውን ጠንካራ የብረት ችንካሮች (ምስማሮች) የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ ቅንዋት›› የሚለው ቃል
ቀነወ- ቸነከረ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ መስቀል ማለት ደግሞ ዝም ብሎ የቆመ ግንድ ሳይሆን አሁን በየሥፍራው እንደምናየው ምልክት የተመሳቀለ እንጨት ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቸነከረባቸው አምስቱ ችንካሮች ሳዶር፣ አላዶር፣ዳናት፣ አዴራ፤ ሮዳስ ይባላሉ፡፡ እነዚህም የአምሥቱ አዕማደ ምሥጢራት ምሳሌዎች መሆናቸውን አበው ያስተምራሉ፡፡
ሐዋርያው ቶማስ ከትንሣኤ በኋላ ወንድሞቹ ሐዋርያት ስለ ትንሣኤው በነገሩት ጊዜ ‹‹የችንካሩን ምልክት በዓይኖቼ ካላየሁ፣ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላስገሁ፣ በእጄም የተወጋውን ጎኑን ካልዳሰስኩ አላምንም›› ማለቱ በብረት ቀኖት በመቸንከሩ ነበር (ዮሐ 2ዐ¸25)፡፡ መድኃኒታችን በኃጢአት ቀኖት (ምስማር) ተይዞ የነበረውን ሰው ለማዳን በብረት ቀኖት ተቸነከረ፡፡
እንግዲህ አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል የሚባሉት እነዚህ ናቸው፡፡ ድሀ ያይደለ ጌታ፤ ፍጡር ያይደለ የፈጠረውን ሥጋ ገንዘብ ያደረገ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጅ ብሎ ተናቀ፡፡ የሕማም ሰው፤ ደዌንም የሚያውቅ ሆነ፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፡፡ ሕማማችንንም ተሸከመ፡፡ ይህም የሰውን ልጅ ለማዳን ማለትም እኛን ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ ይፈውሰንና ከሕማመ ሥጋ ከሕማመ ነፍስ ሥቃይ ያሳርፈን ዘንድ ነው፡፡ ቁስለ ኃጢአታችንን ያደርቅልን ዘንድ ስለ መተላለፋችን ቆሰለ፡፡ በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን፡፡ በደላችንን ይደመስስ ዘንድ ስለ በደላችን ደቀቀ፡፡ ሊያረጋጋን ተጨነቀ፡፡ ሊያሣርፈን ተሠቃየ፡፡ አፉንም አልከፈተም፡፡
የእግዚአብሔር የመሥዋዕቱ በግ ኢየሱስ ክርስቶስ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት በሸላቾቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ እንዲሁ አፉን አልከፈተም፡፡ መልካምን እንጂ ግፍን አላደረገም ነበር፡፡ ልብንና ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ ወሰብእ ወልድ ዋህድ ኢየሱስ ክርስቶስ በጲላጦስ በተመረመረ ጊዜ በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም፡፡ በፈቃዱ ነፍሱን ስለ እኛ መሥዋእት አደረገ፡፡ ፋሲካችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሥጋውን ቆረሰልን፣ ደሙንም አፈሰሰልን (ኢሳ. 53¸1-13፤ ዮሐ. 10¸18፤ ዮሐ. 19¸30፤ 1ኛቆሮ. 5¸7)፡፡ በዚህ የተቀደሰው ሳምንት ይህንን የጌታን ውለታና የድኅነት ሥራ እናስተውል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
ምንጭ :-ማህበረ ቅዱሳን ዕለተ ቀዳሚት ሰንበት
ዓውደ ምህረት የእናንተ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
++ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ! ++ (መዝ 91:13)
☞ ሞተ ሥጋ ሳያገኛቸው እግዚአብሔር የሠወራቸው ብዙ ቅዱሳን አሉ። ከነዚህም መካከል ከአዳም ጀምሮ ሰባተኛ የሆነ ሄኖክ አንዱ ነው። መጽሐፍ ቅዱሱ ሰው ሄኖክ ሞት ሳያገኘው የተሰወረበትን ምክንያት ሲገልጽ “ሄኖክም አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ አልተገኘም፤ እግዚአብሔር ወስዶታልና።” ይላል አካሄድን ከእግዚአብሔር ጋር ማድረግ እስከምን እንደሚያደርስ ተመልከት። (ዘፍ 5፥24) አካሄዳቸውን ከእርሱ ጋር ባደረጉ ወዳጆቹ ቅዱሳን የእግዚአብሔር ቸርነትና ከኃሊነት ተገልጦአልና ነቢዩ “እግዚአብሔር በጻድቁ እንደ ተገለጠ እወቁ።” በማለት ተናገረ። (መዝ 4፥3) በቅዱስ ሰው ሃይማኖት፣ በጎ ምግባርና መልካምነት ኢየሱስ ክርስቶስ ይገለጣል እንጂ አይሸፈንም።
☞ ከቅዱሱ ሰው ከሄኖክ ሌላ ቀናተኛው ነቢዩ ኤልያስም ሞት ሳያገኘው በእሳት ሠረገላ ወደ ሰማይ ተነጥቆዋል። ይህንም መጽሐፍ ሲነግረን “ሲሄዱም፦ እያዘገሙም ሲጫወቱ፥ እነሆ፥ የእሳት ሰረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ።” ከነቢዩ ጋር የነበረ ይህን የተመለከተና ለእግዚአብሔር የተገዛ ኤልሳዕም የነቢዩ ኤልያስ በረከት አድሮበት ተመሷል። (2ኛ ነገ 2፥11) መጽሐፍ በቅድስናቸው ለዚህ የበቁ እንዳሉ ሲነግርህ ዕፁብ ድንቅ ብለህ ማመን ማሰብም አንተንም ለክብር ያበቃሃል። ክርስቶስን በእነርሱ ሕይወት ትመለከተዋለህ እንጂ አይሠወርብህም። እንዲያም ባይሆን “የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።” ባላለህም ነበር። (ዕብ 13፥7)
👇ይቀጥላል 👇
https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
☞ ሞተ ሥጋ ሳያገኛቸው እግዚአብሔር የሠወራቸው ብዙ ቅዱሳን አሉ። ከነዚህም መካከል ከአዳም ጀምሮ ሰባተኛ የሆነ ሄኖክ አንዱ ነው። መጽሐፍ ቅዱሱ ሰው ሄኖክ ሞት ሳያገኘው የተሰወረበትን ምክንያት ሲገልጽ “ሄኖክም አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ አልተገኘም፤ እግዚአብሔር ወስዶታልና።” ይላል አካሄድን ከእግዚአብሔር ጋር ማድረግ እስከምን እንደሚያደርስ ተመልከት። (ዘፍ 5፥24) አካሄዳቸውን ከእርሱ ጋር ባደረጉ ወዳጆቹ ቅዱሳን የእግዚአብሔር ቸርነትና ከኃሊነት ተገልጦአልና ነቢዩ “እግዚአብሔር በጻድቁ እንደ ተገለጠ እወቁ።” በማለት ተናገረ። (መዝ 4፥3) በቅዱስ ሰው ሃይማኖት፣ በጎ ምግባርና መልካምነት ኢየሱስ ክርስቶስ ይገለጣል እንጂ አይሸፈንም።
☞ ከቅዱሱ ሰው ከሄኖክ ሌላ ቀናተኛው ነቢዩ ኤልያስም ሞት ሳያገኘው በእሳት ሠረገላ ወደ ሰማይ ተነጥቆዋል። ይህንም መጽሐፍ ሲነግረን “ሲሄዱም፦ እያዘገሙም ሲጫወቱ፥ እነሆ፥ የእሳት ሰረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ።” ከነቢዩ ጋር የነበረ ይህን የተመለከተና ለእግዚአብሔር የተገዛ ኤልሳዕም የነቢዩ ኤልያስ በረከት አድሮበት ተመሷል። (2ኛ ነገ 2፥11) መጽሐፍ በቅድስናቸው ለዚህ የበቁ እንዳሉ ሲነግርህ ዕፁብ ድንቅ ብለህ ማመን ማሰብም አንተንም ለክብር ያበቃሃል። ክርስቶስን በእነርሱ ሕይወት ትመለከተዋለህ እንጂ አይሠወርብህም። እንዲያም ባይሆን “የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።” ባላለህም ነበር። (ዕብ 13፥7)
👇ይቀጥላል 👇
https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
---የቀጠለ---
☞ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከደቀመዛሙርቱ መካከል ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ የሥጋ ሞት እንደማያገኘው ደጋግሞ ፍንጭ ሰጥቶ ነበር። በዚህም ቃሉ መሠረት ወንጌላዊው እንደተሠወረ የቤተክርስቲያን ታሪክ ይመሰክራል። (ማቴ 16:28፣ ዮሐ 21:23)
☞በዚህ መልኩ የተሠወሩ ቅዱሳን እነዚህ ብቻ ናቸው ማለት አይደለም። እግዚአብሔር የዘመናት ባለቤት ነውና በየዘመኑ እንዲህ አይነቱን የቸርነቱን ሥራ የሚሠራላቸው የሠራላቸውም ብዙ ወዳጆቹ አሉ። ከእነዚህም ወዳጆቹ በመለካውያን ተሰደው ወደ ኢትዮጵያ ምድር መጥተው የነበሩት ጻድቁ አቡነ አረጋዊ አንዱ ናቸው። እንደ ሄኖክ አካሄዳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር አድርገዋልና እግዚአብሔር ከሞተ ሥጋ ሰውሮ ወስዷቸዋል። ጻድቁ አቡነ አረጋዊ አምላካችን እግዚአብሔር "በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ።" በማለት አስቀድሞ የተናገረው ቃል እንዲሁም በኋለኛው ዘመን ጌታችን “ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤....... እባቦችን ይይዛሉ፥” ብሎ የተናገረው ቃል በተግባር የተፈጸመባቸውና የተፈጸመላቸው ጻድቅ ናቸው። (ማር16፥17፣ መዝ 90:13) ልዑል አምላክ ክርስቶስ ከወዳጆቹ የምንደመርበትን መልካም ሥራ ለመሥራት ያብቃን!!
ቢትወደድ ወርቁ
ጥቅምት 14 ቀን 2016 ዓ ም
☞ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከደቀመዛሙርቱ መካከል ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ የሥጋ ሞት እንደማያገኘው ደጋግሞ ፍንጭ ሰጥቶ ነበር። በዚህም ቃሉ መሠረት ወንጌላዊው እንደተሠወረ የቤተክርስቲያን ታሪክ ይመሰክራል። (ማቴ 16:28፣ ዮሐ 21:23)
☞በዚህ መልኩ የተሠወሩ ቅዱሳን እነዚህ ብቻ ናቸው ማለት አይደለም። እግዚአብሔር የዘመናት ባለቤት ነውና በየዘመኑ እንዲህ አይነቱን የቸርነቱን ሥራ የሚሠራላቸው የሠራላቸውም ብዙ ወዳጆቹ አሉ። ከእነዚህም ወዳጆቹ በመለካውያን ተሰደው ወደ ኢትዮጵያ ምድር መጥተው የነበሩት ጻድቁ አቡነ አረጋዊ አንዱ ናቸው። እንደ ሄኖክ አካሄዳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር አድርገዋልና እግዚአብሔር ከሞተ ሥጋ ሰውሮ ወስዷቸዋል። ጻድቁ አቡነ አረጋዊ አምላካችን እግዚአብሔር "በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ።" በማለት አስቀድሞ የተናገረው ቃል እንዲሁም በኋለኛው ዘመን ጌታችን “ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤....... እባቦችን ይይዛሉ፥” ብሎ የተናገረው ቃል በተግባር የተፈጸመባቸውና የተፈጸመላቸው ጻድቅ ናቸው። (ማር16፥17፣ መዝ 90:13) ልዑል አምላክ ክርስቶስ ከወዳጆቹ የምንደመርበትን መልካም ሥራ ለመሥራት ያብቃን!!
ቢትወደድ ወርቁ
ጥቅምት 14 ቀን 2016 ዓ ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
+ ጨለማን አስወግዶ በዓለም ላይ ያበራ ፀሐይ +
“በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።” አለ :- የጽድቅ ፀሐይ ኢየሱስ ክርስቶስ (ማቴ 13፥43)
የመልክዐ ተክለሃይማኖት ደራሲ በመልክዑ አርኬ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን "ቅዱስ አባት ሆይ አምልኰተ ጣዖት ጨለማን አስወግደህ በዓለም የምታበራ ፀሐይ አንተ መዓዛህ የተወደደ ደብረ ከርቤን ነህ? ወይስ መሠወር የማይቻላት ደብረ ጽጌን ነህ? " በማለት ያመሰግናል፡፡ ቅዱሳን ነቢያት ሐዋርያት እንዲሁም በየዘመኑ የተነሡ መምህራን ዋና ተልዕኮ ጣዖት አምልኰን በቃለ ወንጌል ማስወገድ ነው፡፡ በሰዎች ዘንድ የሚታይ የሚዳሰስ ጣዖት አለ፡፡ እንዲሁም የማይታይ የማይዳሰስ ልብም የማይባል ረቂቅ ጣዖትም አለ፡፡
በኑሯችንና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን ልብ ሳንላቸው ከእግዚአብሔር አስቀድመን ቅድሚያ የምንሰጣቸው ነገሮች ሁሉ ሳናውቃቸው ጣዓታት እንደሆኑብን ልናስተውል ይገባናል፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን በየዘመናቸው ከሰዎች ልቡና የሚታዩትንም ሆነ የማይታዩትን ጣዖታት በቃለ እግዚአብሔር ሲያጠፉ ኑረዋል፡፡ በዚህም በነቢዩ ዳንኤል የትንቢት መጽሐፍ "ጥበበኞቹ እንደሰማይ ፀዳል ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ፡፡" (ዳን 12፡4) ተብሎ ትንቢት ተነግሮላቸዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት በገድላቸው እንደተጻፈልን በዘመናቸው ጣዖታትን አጥፍተዋል፡፡ በጣዖታቱ ላይ አድረው ክርስቶስ በክቡር ደሙ የዋጃቸውን ሰዎች ሲያታልሉ የኖሩትንም እኵያን አጋንንት በወንጌል ትምህርት ሲያሳፍሩና ሲበቀሏቸው ኑረዋል፡፡ በዚህም ለብዙዎች ብርሃን ሆነዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ምን ያህል ጣዖታትን እንዳጠፉ ስንቶችን ከጣዖት አምልኰ እንዳላቀቁና አጋንንትን በወንጌል ትምህርት እንዴት እንዳወጡ ለመረዳት ገድላቸውን በእምነት ሆኖ ማንበቡ ተገቢ ይሆናል፡፡ ይኽን በሕሊናችን እንያዝና በዚህ ክፍል ጻድቁ የተገለጡበትን የምስጋና ቃል እንመልከት፡፡
+++ ተክለሃይማኖት ፀሐይ +++
በቅዱስ መጽሐፍ እንደተጻፈልን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ብርሃን ፀሐይ ተብሏል፡፡ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "እግዚአብሔር ብሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማነው?" (መዝ 26፡1) በማለት ዘምሯል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም፡፡" (ዮሐ 8፡12) በማለት አስተምሯል፡፡ ጌታችን ጨለማ ያለው እርሱን አለማወቅ እንደፈቃዱ አለመመላለስ በኃጢአትና በክሕደት መኖርን ነው፡፡ (ሮሜ 13፡11-13) ብርሃን የተባለ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር በእምነት ጸንተው በምግባር ቀንተው በትሩፋት አጊጠው እንደፈቃዱ የተመላለሱትንና ያገለገሉትን ወዳጆቹችንም ብርሃናት መሆናቸውን "እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ" በማለት መስክሮላቸዋል፡፡ ጌታችን ወዳጆቹ የዓለም ብርሃን የሚባሉት ብርሃን ሲሆኑ መሆኑን ሲናገርም "መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ፡፡" (ማቴ 5፡14-16) ብሎዋል፡፡ በመነሻችን እንደተመለከትነው ጻድቁ ጨለማ ጣዖትን በማስወገድ ለዓለም ብርሃን ሆነዋል፡፡ ሰዎች ልቡናቸውን ከጣዖታት መልሰው እግዚአብሔርን እንዲያከብሩትም ምክንያት ሆነዋል፡፡ በመሆኑም ደራሲው የጌታችንን ቃል ይዞ ጻድቁን "ብርሃን ፀሐይ" በማለት አመሰገነ፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን "መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ፡፡"(ያዕ 1፡17-18) በማለት የብርሃናት አባት ብሎ ጠርቶታል፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ ብርሃናት ብሎ የጠራቸው የብርሃን ክርስቶስ ልጆች ወዳጆቹ ቅዱሳን መሆናቸው የታወቀ ነው፡፡ አምልኮ ጣዖትን እንዲያስወግዱ ኑፋቄንና ክሕደትንና እንዲያጠፋ የሰዎች ልጆችን ሕይወት በቅዱስ ቃሉ አማካኝነት እንዲያርሙና እንዲያስተካክሉ ወደ ዓለም የተላኩ ቅዱሳን ነቢያት፣ ቅዱሳን ሐዋርያት በኋላ ዘመን የተነሡ ጻድቃን ሰማዕታት ሁሉ "እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ለማዳን ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለሁ ብሎ እግዚአብሔር አዞናል፡፡" በማለት በአንድ ቃል ተናግረዋል፡፡ (የሐዋ 13፡47) ቅዱሳን ጨለማ (ኃጢአት) በሞላው በሰው ልቡና ብርሃን ክርስቶስን የሚያበሩ ብርሃናት መሆናቸውን ትመለከታላችሁን? ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የንስሐ ስብከትን እየሰበከ የንስሐ ጥምቀትን እያጠመቀ በመንገድ የተመሰለ የሰውን ልቡና እያስተካከለ የተቀበለውን መጥምቁ ዮሐንስን "የሚነድና የሚያበራ ብርሃን" ብሎ ጠርቶታል፡፡ (ዮሐ 5፡35) መጥምቁ ዮሐንስ በጌታችን አንደበት የሚነድና የሚያበራ መብራት ተብሎ ስለምን ተመሰገነ? ወንጌልን በመስበኵ ጣዖታትን በማጥፋቱ ሰዎችን ከሞት ወደ ሕይወት ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን በመመለሱ አይደለምን? ቅዱሳን በእግዚአብሔር ፍቅር ነድደው ሰይጣንን ድል ነሥተዋል፡፡ በሕይወታቸው ክርስቶስን አብርተው በሰው ልቡና ነግሦ የነበረውን ጨለማ ኃጢአት ደርምሰዋል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጽድቅ (የእውነት ፀሐይ) እንደሆነ መንገዱን የተከተሉ ወዳጆቹም ፀሐይ ሆነው ፀሐይ ተብለዋል፡፡ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዘሪውን ምሳሌ ባስተማረበት ክፍል "በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡ የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ፡፡" (ማቴ 13፡44) በማለትም ጭምር አስተምሮዋል፡፡ እርሱ መድኃኒተ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ፀሐይ ሲሆን ወዳጆቹ ደግሞ ጨረቃ ናቸው፡፡ ጨረቃ ብርሃንን የምታገኘው ከፀሐይ እንደሆነ ቅዱሳንም ጸጋን ክብርን ሥልጣንንም ያገኙት ከክርስቶስ ነውና ጌታችን "እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡" ብሎ አስተማረ፡፡ እንግዲህ በቅዱሳት መጻሕፍት እግዚአብሔርን ተከትለው ጨለማ ጣዖትን ያጠፉ ደጋግ አባቶችና እናቶች ብርሃናት ፀሐይ ከዋክብት መባላቸውን ስንመለከት ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን ብርሃን ፀሐይ ብለን እንጠራቸዋለን እንጂ በጥርጥር መንፈስ ሆነን እንዴት? ለምን? ብለን አንጠይቅም፡፡
©️ መምህር ቢትወደድ ወርቁ
ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ ም
“በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።” አለ :- የጽድቅ ፀሐይ ኢየሱስ ክርስቶስ (ማቴ 13፥43)
የመልክዐ ተክለሃይማኖት ደራሲ በመልክዑ አርኬ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን "ቅዱስ አባት ሆይ አምልኰተ ጣዖት ጨለማን አስወግደህ በዓለም የምታበራ ፀሐይ አንተ መዓዛህ የተወደደ ደብረ ከርቤን ነህ? ወይስ መሠወር የማይቻላት ደብረ ጽጌን ነህ? " በማለት ያመሰግናል፡፡ ቅዱሳን ነቢያት ሐዋርያት እንዲሁም በየዘመኑ የተነሡ መምህራን ዋና ተልዕኮ ጣዖት አምልኰን በቃለ ወንጌል ማስወገድ ነው፡፡ በሰዎች ዘንድ የሚታይ የሚዳሰስ ጣዖት አለ፡፡ እንዲሁም የማይታይ የማይዳሰስ ልብም የማይባል ረቂቅ ጣዖትም አለ፡፡
በኑሯችንና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን ልብ ሳንላቸው ከእግዚአብሔር አስቀድመን ቅድሚያ የምንሰጣቸው ነገሮች ሁሉ ሳናውቃቸው ጣዓታት እንደሆኑብን ልናስተውል ይገባናል፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን በየዘመናቸው ከሰዎች ልቡና የሚታዩትንም ሆነ የማይታዩትን ጣዖታት በቃለ እግዚአብሔር ሲያጠፉ ኑረዋል፡፡ በዚህም በነቢዩ ዳንኤል የትንቢት መጽሐፍ "ጥበበኞቹ እንደሰማይ ፀዳል ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ፡፡" (ዳን 12፡4) ተብሎ ትንቢት ተነግሮላቸዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት በገድላቸው እንደተጻፈልን በዘመናቸው ጣዖታትን አጥፍተዋል፡፡ በጣዖታቱ ላይ አድረው ክርስቶስ በክቡር ደሙ የዋጃቸውን ሰዎች ሲያታልሉ የኖሩትንም እኵያን አጋንንት በወንጌል ትምህርት ሲያሳፍሩና ሲበቀሏቸው ኑረዋል፡፡ በዚህም ለብዙዎች ብርሃን ሆነዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ምን ያህል ጣዖታትን እንዳጠፉ ስንቶችን ከጣዖት አምልኰ እንዳላቀቁና አጋንንትን በወንጌል ትምህርት እንዴት እንዳወጡ ለመረዳት ገድላቸውን በእምነት ሆኖ ማንበቡ ተገቢ ይሆናል፡፡ ይኽን በሕሊናችን እንያዝና በዚህ ክፍል ጻድቁ የተገለጡበትን የምስጋና ቃል እንመልከት፡፡
+++ ተክለሃይማኖት ፀሐይ +++
በቅዱስ መጽሐፍ እንደተጻፈልን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ብርሃን ፀሐይ ተብሏል፡፡ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "እግዚአብሔር ብሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማነው?" (መዝ 26፡1) በማለት ዘምሯል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም፡፡" (ዮሐ 8፡12) በማለት አስተምሯል፡፡ ጌታችን ጨለማ ያለው እርሱን አለማወቅ እንደፈቃዱ አለመመላለስ በኃጢአትና በክሕደት መኖርን ነው፡፡ (ሮሜ 13፡11-13) ብርሃን የተባለ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር በእምነት ጸንተው በምግባር ቀንተው በትሩፋት አጊጠው እንደፈቃዱ የተመላለሱትንና ያገለገሉትን ወዳጆቹችንም ብርሃናት መሆናቸውን "እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ" በማለት መስክሮላቸዋል፡፡ ጌታችን ወዳጆቹ የዓለም ብርሃን የሚባሉት ብርሃን ሲሆኑ መሆኑን ሲናገርም "መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ፡፡" (ማቴ 5፡14-16) ብሎዋል፡፡ በመነሻችን እንደተመለከትነው ጻድቁ ጨለማ ጣዖትን በማስወገድ ለዓለም ብርሃን ሆነዋል፡፡ ሰዎች ልቡናቸውን ከጣዖታት መልሰው እግዚአብሔርን እንዲያከብሩትም ምክንያት ሆነዋል፡፡ በመሆኑም ደራሲው የጌታችንን ቃል ይዞ ጻድቁን "ብርሃን ፀሐይ" በማለት አመሰገነ፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን "መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ፡፡"(ያዕ 1፡17-18) በማለት የብርሃናት አባት ብሎ ጠርቶታል፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ ብርሃናት ብሎ የጠራቸው የብርሃን ክርስቶስ ልጆች ወዳጆቹ ቅዱሳን መሆናቸው የታወቀ ነው፡፡ አምልኮ ጣዖትን እንዲያስወግዱ ኑፋቄንና ክሕደትንና እንዲያጠፋ የሰዎች ልጆችን ሕይወት በቅዱስ ቃሉ አማካኝነት እንዲያርሙና እንዲያስተካክሉ ወደ ዓለም የተላኩ ቅዱሳን ነቢያት፣ ቅዱሳን ሐዋርያት በኋላ ዘመን የተነሡ ጻድቃን ሰማዕታት ሁሉ "እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ለማዳን ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለሁ ብሎ እግዚአብሔር አዞናል፡፡" በማለት በአንድ ቃል ተናግረዋል፡፡ (የሐዋ 13፡47) ቅዱሳን ጨለማ (ኃጢአት) በሞላው በሰው ልቡና ብርሃን ክርስቶስን የሚያበሩ ብርሃናት መሆናቸውን ትመለከታላችሁን? ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የንስሐ ስብከትን እየሰበከ የንስሐ ጥምቀትን እያጠመቀ በመንገድ የተመሰለ የሰውን ልቡና እያስተካከለ የተቀበለውን መጥምቁ ዮሐንስን "የሚነድና የሚያበራ ብርሃን" ብሎ ጠርቶታል፡፡ (ዮሐ 5፡35) መጥምቁ ዮሐንስ በጌታችን አንደበት የሚነድና የሚያበራ መብራት ተብሎ ስለምን ተመሰገነ? ወንጌልን በመስበኵ ጣዖታትን በማጥፋቱ ሰዎችን ከሞት ወደ ሕይወት ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን በመመለሱ አይደለምን? ቅዱሳን በእግዚአብሔር ፍቅር ነድደው ሰይጣንን ድል ነሥተዋል፡፡ በሕይወታቸው ክርስቶስን አብርተው በሰው ልቡና ነግሦ የነበረውን ጨለማ ኃጢአት ደርምሰዋል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጽድቅ (የእውነት ፀሐይ) እንደሆነ መንገዱን የተከተሉ ወዳጆቹም ፀሐይ ሆነው ፀሐይ ተብለዋል፡፡ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዘሪውን ምሳሌ ባስተማረበት ክፍል "በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡ የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ፡፡" (ማቴ 13፡44) በማለትም ጭምር አስተምሮዋል፡፡ እርሱ መድኃኒተ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ፀሐይ ሲሆን ወዳጆቹ ደግሞ ጨረቃ ናቸው፡፡ ጨረቃ ብርሃንን የምታገኘው ከፀሐይ እንደሆነ ቅዱሳንም ጸጋን ክብርን ሥልጣንንም ያገኙት ከክርስቶስ ነውና ጌታችን "እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡" ብሎ አስተማረ፡፡ እንግዲህ በቅዱሳት መጻሕፍት እግዚአብሔርን ተከትለው ጨለማ ጣዖትን ያጠፉ ደጋግ አባቶችና እናቶች ብርሃናት ፀሐይ ከዋክብት መባላቸውን ስንመለከት ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን ብርሃን ፀሐይ ብለን እንጠራቸዋለን እንጂ በጥርጥር መንፈስ ሆነን እንዴት? ለምን? ብለን አንጠይቅም፡፡
©️ መምህር ቢትወደድ ወርቁ
ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ ም
#አንዳንድ ልጆች ከወላጆቻቸው የሚበልጡበት ጊዜ አለ አንዳንድ ወላጆች ደግሞ በነገሮች ዕይታ ከልጆቻቸው የሚያንሱበትም ጊዜ አለ ። እናታችን ቅድስት ኢየሉጣ ይህን በመገንዘቧ ነበር ልጇን ሕፃኑ ቂርቆስን ስለ መልካም ምክሩ ልጇ ሆኖ ሳለ አባቴ ብላ ለመጥራት የተገደደችሁ ።
በእርግጥም የሥጋ ሞት እጅግ መራራና አስፈሪ ነው ። መድኅን ዓለም ክርስቶስ እንኳን ወዶ ፣ፈቅዶ የሞታችንን ጽዋ ሊጠጣልን ለካሳ፣ ለቤዛ መጥቶ ሳለ ጊዜው ደርሶ በአሙስ ምሽት የአይሁድ ወታደሮች ሊይዙት ሲመጡ ግን በአትክልት ቦታ በጌቴ ሰማኔ ሆኖ "አባት ሆይ ብትወድስ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ " ሲል ጸሎትን አድርጓል። #ማቴ 26÷39
#ይህም የሚያሳየን በመከራችን ጊዜ ወደ ሰማይ አባታችን መጸለይ እንደሚገባን ብቻ ሳይሆን የሥጋ ሞት ምነኛ አሰቃቂ ና አስፈሪ እንደሆነ ጭምር የሚያሳይ ነው ። ስለሆነም የቅድስት እየሉጣ ፍርሃት አያስደንቅም የሚያስደንቀውስ የልጇ እሳት መድፈር ነው ። “ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና።” #ሉቃስ 10፥21
በቤተክርስቲያናችን ታሪክ ገና በአፍላ ዕድሜያቸው በበሳልነታቸውና በአስተሳሰብ አድማሳቸው የተነሳ አረጋዊ ወይም ሽማግሌ ተብለው የተጠሩ ቅዱሳን አሉ ለምሳሌ ወደ ሀገራችን ከመጡ ከዘጠኑ ቅዱሳን መካከል ሮማዊው ኮከብ ዘሚካኤል(አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ) ማንሳት ይቻላል:: ዘሚካኤል አረጋዊ የሚል ስያሜን ያገኙት ገና አስራ አምስት ዓመት እንኳን ሳይሞላቸው ነበር።
#ቅዱስ_ወንጌል ከአንዱ ከተማ ቢያሳድዷችሁ ወደ ሌላይቱ ከተማ ሽሹ እንዳለ ከሮም መኮንን ሸሽታ ወደ ሌላ ሀገር ልጇን ይዛ ብትሄድ ያን የሸሸችሁ ክፉ መኮንን በዚህም ሀገር አገኛት የምታመልከውን አምላክ ክዳ የእርሱን ጣዖት እድታመልክም ጠየቃት ቅድስት ኢየሉጣ ግን ከእግዚአብሔር በቀር ሌሎች አማልክትን ማምለክ የሚገባ ወይም የማይገባ መሆኑን ይህን የሦስት ዓመት ልጄን ጠይቀው እርሱ ይንገርህ አለችሁ
መኮንኑም ቅዱስ ቂርቆስን በተመለከተው ጊዜ ፊቱ ብሩህና ደስተኛ ሕፃን እንደሆነ አስተዋለ ቀርቦም አንተ ደስተኛ ሕፃን እንዴት ነህ ሲል የማግባባት ሰላምታን አቀረበለት ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን አዎን የኔ ደስታ ተጠብቆልኛል አንተ ግን ከዚህ እኩይ ሥራህ ካልተመለስ ልቅሶና ጥርስ ማፏጨት ጥልቅ ሐዘንም ይቆይሃል መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላና ደስታ የላቸውም ይላልና አለው።“ለክፉዎች ሰላም የላቸውም ይላል አምላኬ።” #ኢሳ 57፥21
#መኳንንቱንና ጣዖታቱንም ሁሉ እረገማቸው ከኃይሉም ጽናት የተነሳ ሁሉ አደነቁ እግዚአብሔር ንግግርንና ኃይልን ሰጥቶታልና "ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና። ተብሎ እንደተጻፈ #ማቴ 10÷18-20
መኮንኑም የሕፃኑን ንግግር በሰማ ጊዜ አፈረ ታላቅ የውኃ ጋን አዘጋጅታችሁ ውኃው እስከሚፍለቀለቅ በእሳት ላይ ጣዱት ውኃውም ሲፈላ ሕፃኑንና እናቱን በዚያ ጨምሯቸው ብሎ አዘዘ ።
#ጭፍሮችም እንደተባሉት አደረጉ የውኃው ፍላትም ድምጹ እንደ ክረምት ጊዜ ነጎድጓድ የሚያስፈራና የሚያስገመግም ሆነ ይህ ጊዜ የሕፃኑ እናት ቅድስት ኢየሉጣ ፈራች ሃይማኖቷም ከልቧ ተሸረሸረ ልጄ ሆይ ይህ ነገር ይቅርብን ንጉሥ ያለንን እንፈጽም አለችው።
ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ወደ ሰማይ አንጋጦ መላእክትን በጽረ አርያም ፣ ሐዋርያትን በስብከተ ዓለም ፣ ጻድቃንን በገዳም፣ ሰማዕታትን በደም ያጸናህ እናቴንም በሃይማኖት አጽናት ሲል ስለ እናቱ የእምነት መጉደል ወደ ፈጣሪው ጸለየ።
#እግዚአብሔርም የእናቱን ዐይነ ልቡና ገልጦ ለቅዱሳን ሰማዕታቱ ያዘጋጀውን የጽድቅ አክሊልን አሳያት ያን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ በመንፈስ ተጽናናች ፣ በሃይማኖት ጸናች ንጉሡንና ጣዖታቱን ናቀች ልጇ ቂርቆስንም " #ልጄ_ስትሆን_አባት_ሆንክኝ " አለችሁ ተያይዘውም በእሳት ወደ ተፍለቀለቀው የውኃ ጋን ውስጥ ገቡ
#ከእግዚአብሔር_የተላከ_የመላእክት_አለቃ_ቅዱስ ገብርኤልም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጥቶ #በጌታችን_በመድኃኒታችን_በኢየሱስ_ክርስቶስ_መስቀል ያን ፍል ውኃ እንደ ክረምት ጊዜ ውርጭ አቀዘቀዘው። ሕፃኑና እናቱም ያለ ምንም ጉዳት ከጋኑ ወጡ። " #የእግዚአብሔር_መላእክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል " እንዲል #መዝ 33÷7
.......... #ይቆየን............
#የእግዚአብሔር ቸርነት የመላእኩ ጠባቂየት የቅዱሳኑ የእናትና ልጅ በረከታቸው አይለየን !
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፲ ፰/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
በእርግጥም የሥጋ ሞት እጅግ መራራና አስፈሪ ነው ። መድኅን ዓለም ክርስቶስ እንኳን ወዶ ፣ፈቅዶ የሞታችንን ጽዋ ሊጠጣልን ለካሳ፣ ለቤዛ መጥቶ ሳለ ጊዜው ደርሶ በአሙስ ምሽት የአይሁድ ወታደሮች ሊይዙት ሲመጡ ግን በአትክልት ቦታ በጌቴ ሰማኔ ሆኖ "አባት ሆይ ብትወድስ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ " ሲል ጸሎትን አድርጓል። #ማቴ 26÷39
#ይህም የሚያሳየን በመከራችን ጊዜ ወደ ሰማይ አባታችን መጸለይ እንደሚገባን ብቻ ሳይሆን የሥጋ ሞት ምነኛ አሰቃቂ ና አስፈሪ እንደሆነ ጭምር የሚያሳይ ነው ። ስለሆነም የቅድስት እየሉጣ ፍርሃት አያስደንቅም የሚያስደንቀውስ የልጇ እሳት መድፈር ነው ። “ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና።” #ሉቃስ 10፥21
በቤተክርስቲያናችን ታሪክ ገና በአፍላ ዕድሜያቸው በበሳልነታቸውና በአስተሳሰብ አድማሳቸው የተነሳ አረጋዊ ወይም ሽማግሌ ተብለው የተጠሩ ቅዱሳን አሉ ለምሳሌ ወደ ሀገራችን ከመጡ ከዘጠኑ ቅዱሳን መካከል ሮማዊው ኮከብ ዘሚካኤል(አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ) ማንሳት ይቻላል:: ዘሚካኤል አረጋዊ የሚል ስያሜን ያገኙት ገና አስራ አምስት ዓመት እንኳን ሳይሞላቸው ነበር።
#ቅዱስ_ወንጌል ከአንዱ ከተማ ቢያሳድዷችሁ ወደ ሌላይቱ ከተማ ሽሹ እንዳለ ከሮም መኮንን ሸሽታ ወደ ሌላ ሀገር ልጇን ይዛ ብትሄድ ያን የሸሸችሁ ክፉ መኮንን በዚህም ሀገር አገኛት የምታመልከውን አምላክ ክዳ የእርሱን ጣዖት እድታመልክም ጠየቃት ቅድስት ኢየሉጣ ግን ከእግዚአብሔር በቀር ሌሎች አማልክትን ማምለክ የሚገባ ወይም የማይገባ መሆኑን ይህን የሦስት ዓመት ልጄን ጠይቀው እርሱ ይንገርህ አለችሁ
መኮንኑም ቅዱስ ቂርቆስን በተመለከተው ጊዜ ፊቱ ብሩህና ደስተኛ ሕፃን እንደሆነ አስተዋለ ቀርቦም አንተ ደስተኛ ሕፃን እንዴት ነህ ሲል የማግባባት ሰላምታን አቀረበለት ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን አዎን የኔ ደስታ ተጠብቆልኛል አንተ ግን ከዚህ እኩይ ሥራህ ካልተመለስ ልቅሶና ጥርስ ማፏጨት ጥልቅ ሐዘንም ይቆይሃል መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላና ደስታ የላቸውም ይላልና አለው።“ለክፉዎች ሰላም የላቸውም ይላል አምላኬ።” #ኢሳ 57፥21
#መኳንንቱንና ጣዖታቱንም ሁሉ እረገማቸው ከኃይሉም ጽናት የተነሳ ሁሉ አደነቁ እግዚአብሔር ንግግርንና ኃይልን ሰጥቶታልና "ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና። ተብሎ እንደተጻፈ #ማቴ 10÷18-20
መኮንኑም የሕፃኑን ንግግር በሰማ ጊዜ አፈረ ታላቅ የውኃ ጋን አዘጋጅታችሁ ውኃው እስከሚፍለቀለቅ በእሳት ላይ ጣዱት ውኃውም ሲፈላ ሕፃኑንና እናቱን በዚያ ጨምሯቸው ብሎ አዘዘ ።
#ጭፍሮችም እንደተባሉት አደረጉ የውኃው ፍላትም ድምጹ እንደ ክረምት ጊዜ ነጎድጓድ የሚያስፈራና የሚያስገመግም ሆነ ይህ ጊዜ የሕፃኑ እናት ቅድስት ኢየሉጣ ፈራች ሃይማኖቷም ከልቧ ተሸረሸረ ልጄ ሆይ ይህ ነገር ይቅርብን ንጉሥ ያለንን እንፈጽም አለችው።
ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ወደ ሰማይ አንጋጦ መላእክትን በጽረ አርያም ፣ ሐዋርያትን በስብከተ ዓለም ፣ ጻድቃንን በገዳም፣ ሰማዕታትን በደም ያጸናህ እናቴንም በሃይማኖት አጽናት ሲል ስለ እናቱ የእምነት መጉደል ወደ ፈጣሪው ጸለየ።
#እግዚአብሔርም የእናቱን ዐይነ ልቡና ገልጦ ለቅዱሳን ሰማዕታቱ ያዘጋጀውን የጽድቅ አክሊልን አሳያት ያን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ በመንፈስ ተጽናናች ፣ በሃይማኖት ጸናች ንጉሡንና ጣዖታቱን ናቀች ልጇ ቂርቆስንም " #ልጄ_ስትሆን_አባት_ሆንክኝ " አለችሁ ተያይዘውም በእሳት ወደ ተፍለቀለቀው የውኃ ጋን ውስጥ ገቡ
#ከእግዚአብሔር_የተላከ_የመላእክት_አለቃ_ቅዱስ ገብርኤልም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጥቶ #በጌታችን_በመድኃኒታችን_በኢየሱስ_ክርስቶስ_መስቀል ያን ፍል ውኃ እንደ ክረምት ጊዜ ውርጭ አቀዘቀዘው። ሕፃኑና እናቱም ያለ ምንም ጉዳት ከጋኑ ወጡ። " #የእግዚአብሔር_መላእክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል " እንዲል #መዝ 33÷7
.......... #ይቆየን............
#የእግዚአብሔር ቸርነት የመላእኩ ጠባቂየት የቅዱሳኑ የእናትና ልጅ በረከታቸው አይለየን !
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፲ ፰/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
ይጠጣ ነበር።(1ኛ ነገ 17:2-6) በጥቂት ብቻ በእግዚአብሔር ተአምር የኖሩ ቅዱሳን ብዙ ናቸው።በተለይም ርእሰ ባሕታውያን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ናቸው።562 ዓመት ሙሉ የእናታቸውን ጡት ጨምሮ ያለ ምግብ ፣ ያለ ልብስና ያለ መጠለያ በጾምና በጸሎት ያውም ከብዙ ሺ ስግደቶችና ተጋድሎዎች ጋር ተጸምዶ መኖር ያልተደነቀ ምን ይደነቃል!?ይኸውም የሆነው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል (በተአምር) ነው እንጂ በሌላ አይደለም።እግዚአብሔር "ይሁን" ያለው ይሆናል፤"ይሁን" ያላለውም አይሆንምና።በተፈጥሮ ለሰው ምግብ እንዲያስፈልገው ያደረገ አምላክ እንዳያስፈልገውም ማድረግ ይችላል።አሁንም ቢሆን በጥቂት ብቻ በበረከቱ የሚያኖራቸው ደጋግ ክርስቲያኖች ሞልተዋል።
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" አካላዊ ቃል ወልደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።ስለዚህ በእርሱ በማመን በሃይማኖት በር ገብተን፤በቀጠነችው መንገድ በፈቃደ ነፍስ ተጉዘን፤ሕይወት የሆነው እርሱ ጋር ደርሰን በሕይወት እንኖራለን።ይህንን ሐሳብ ራሱ አምላካችን እንዲህ ሲል ገልጦታል።"በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።" (ማቴ 7:13) ስለዚህ ሰው ጠባብ በር በተባለው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክነትና የዘለዓለም ሕይወትነት (1ኛ ዮሐ 5:20) አምኖ ፤ በቀጠነው መንገድ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተጉዞ ፤ የአካላዊ ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብሎ፤ራሱ ሕይወት የሆነው እግዚአብሔር ጋር ይደርሳል።መነሻውም መገስገሻውም መዳረሻውም እውነተኛ አምላኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል ማለት ነው።እግዚአብሔር በቸርነቱ ጾሙን ስስትን ድል የምንነሣበት ያድርግልን!!!
መጋቢት 2/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" አካላዊ ቃል ወልደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።ስለዚህ በእርሱ በማመን በሃይማኖት በር ገብተን፤በቀጠነችው መንገድ በፈቃደ ነፍስ ተጉዘን፤ሕይወት የሆነው እርሱ ጋር ደርሰን በሕይወት እንኖራለን።ይህንን ሐሳብ ራሱ አምላካችን እንዲህ ሲል ገልጦታል።"በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።" (ማቴ 7:13) ስለዚህ ሰው ጠባብ በር በተባለው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክነትና የዘለዓለም ሕይወትነት (1ኛ ዮሐ 5:20) አምኖ ፤ በቀጠነው መንገድ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተጉዞ ፤ የአካላዊ ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብሎ፤ራሱ ሕይወት የሆነው እግዚአብሔር ጋር ይደርሳል።መነሻውም መገስገሻውም መዳረሻውም እውነተኛ አምላኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል ማለት ነው።እግዚአብሔር በቸርነቱ ጾሙን ስስትን ድል የምንነሣበት ያድርግልን!!!
መጋቢት 2/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from Eyob kinfe
❤ "ሕይወትን በሚሰጥ አዳኝ በሆነ ከአብ በሠረጸ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን" (ጸሎተ ሃይማኖት)❤
#እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በዛሬው ዕለት በእሳትና በነፋስ ተመስሎ ለቅዱሳን ሐዋርያት ወረደ።ይኸውም በቅዱስ ማርቆስ እናት በማርያም ቤት የደስታ መፍሰሻ ወላዲተ አምላክን ከብበው በአንድ ልብ ሲጸልዩ ነው።
#ፍስሕት (ደስተኛዪቱን) ይዘው ቢጸልዩ የደስታ መንፈስ የሆነ መንፈስቅዱስ ወረደላቸው።
#መዝገበ ምሥጢር ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ከሣቴ ምሥጢር (ምሥጢርን የሚገልጥ) መንፈስ ቅዱስ ወረደላቸው።በዚህም በሚያውቁት አንድ ቋንቋ ላይ ሰባ አንድ ቋንቋ ተገልጦላቸው ቅዱስ ወንጌልን ሰብከዋል።
#ናዛዚት (የምታረጋጋ) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ናዛዚ (የሚያረጋጋ) መንፈስ ቅዱስ ተሰጥቷቸዋል።
#ንጽሕት ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መንጽሒ (ከኃጢአት የሚያነጻ) መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።
#ጽንዕት (የጸናች) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መጽንሒ (የሚያጸና) መንፈስቅዱስን ተቀበሉ።
#መስተሥርዪ ኃጢአት (ኃጢአትን ይቅር የምታስብል) ርኅርኂተ ኅሊና ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ኃጢአትን ይቅር የሚል መንፈስ ቅዱስ በእሳት ተመስሎ ወደ እነርሱ መጣ።
#እናታቸውን ይዘው ምን ሊያጡ ኖሯል?ጽዮንን (እመቤታችንን) ከብበው ቢጸልዩ በደብረ ጽዮን የሚኖር መንፈስ ቅዱስ አደረባቸው።
#ይህቺ ቀን የቅድስት ቤተክርስቲያን የልደት ቀን ናት።ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው እንደ ጌታቸው ሁሉ ጾሙ ጸለዩ።መንፈስ ቅዱስ ያደረበት እንደሚጾም እንደሚጸልይ ያጠይቃል።በዓለም ሁሉ ዞረው ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ሰበኩ።
#አምላካችን መንፈስ ቅዱስ በቸርነቱ በእመቤታችንና በቅዱሳን ሐዋርያት አማላጅነት ከመፍገምገም ወደ ጽናት ፣ ከኃዘን ወደ ደስታ ፣ ከኃጢአት ወደ ንጽሕና ፣ ከመቅበዝበዝ ወደ መረጋጋት ፣ ከድንቁርና ወደ ዕውቀት ይመልሰን!!! አሜን !!!
#በዓለ ጰራቅሊጦስ
ወርኃ ሰኔ 16 / 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በዛሬው ዕለት በእሳትና በነፋስ ተመስሎ ለቅዱሳን ሐዋርያት ወረደ።ይኸውም በቅዱስ ማርቆስ እናት በማርያም ቤት የደስታ መፍሰሻ ወላዲተ አምላክን ከብበው በአንድ ልብ ሲጸልዩ ነው።
#ፍስሕት (ደስተኛዪቱን) ይዘው ቢጸልዩ የደስታ መንፈስ የሆነ መንፈስቅዱስ ወረደላቸው።
#መዝገበ ምሥጢር ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ከሣቴ ምሥጢር (ምሥጢርን የሚገልጥ) መንፈስ ቅዱስ ወረደላቸው።በዚህም በሚያውቁት አንድ ቋንቋ ላይ ሰባ አንድ ቋንቋ ተገልጦላቸው ቅዱስ ወንጌልን ሰብከዋል።
#ናዛዚት (የምታረጋጋ) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ናዛዚ (የሚያረጋጋ) መንፈስ ቅዱስ ተሰጥቷቸዋል።
#ንጽሕት ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መንጽሒ (ከኃጢአት የሚያነጻ) መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።
#ጽንዕት (የጸናች) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መጽንሒ (የሚያጸና) መንፈስቅዱስን ተቀበሉ።
#መስተሥርዪ ኃጢአት (ኃጢአትን ይቅር የምታስብል) ርኅርኂተ ኅሊና ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ኃጢአትን ይቅር የሚል መንፈስ ቅዱስ በእሳት ተመስሎ ወደ እነርሱ መጣ።
#እናታቸውን ይዘው ምን ሊያጡ ኖሯል?ጽዮንን (እመቤታችንን) ከብበው ቢጸልዩ በደብረ ጽዮን የሚኖር መንፈስ ቅዱስ አደረባቸው።
#ይህቺ ቀን የቅድስት ቤተክርስቲያን የልደት ቀን ናት።ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው እንደ ጌታቸው ሁሉ ጾሙ ጸለዩ።መንፈስ ቅዱስ ያደረበት እንደሚጾም እንደሚጸልይ ያጠይቃል።በዓለም ሁሉ ዞረው ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ሰበኩ።
#አምላካችን መንፈስ ቅዱስ በቸርነቱ በእመቤታችንና በቅዱሳን ሐዋርያት አማላጅነት ከመፍገምገም ወደ ጽናት ፣ ከኃዘን ወደ ደስታ ፣ ከኃጢአት ወደ ንጽሕና ፣ ከመቅበዝበዝ ወደ መረጋጋት ፣ ከድንቁርና ወደ ዕውቀት ይመልሰን!!! አሜን !!!
#በዓለ ጰራቅሊጦስ
ወርኃ ሰኔ 16 / 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
🔴"በኢዮር በራማ " ዘማሪ ዳዊት ክብሩ | Zemari Dawit Kibru New 'Be Eyor Berama' Orthodox Tewahdo Mezmur
በኢዮር በራማ
በኢዮር በራማ በኤረር ላይ ያለች
የምትመሰገን በክብር የገነነች
የመላእክት ግርማ የክብር አክሊላቸው
የሥላሴ ዙፋን አንቺ ነሽ ጌጣቸው
አዝ.............
በምድረ ሎዛ ያዕቆብ ያየሽ
የወርቅ መሰላል ድንግል አንቺ ነሽ
የአምላክ ማደሪያ እናቱ የሆንሽ
ምዕራገ ጸሎት ንጽሕትም ነሽ
የአሕዛብ በረከት የአብርሃም ዘር
መርገም ተሻረልን /3/ አገኘን በአንቺ ክብር
የተነገረልሽ ትንቢቱ በምድር…
በኢዮር በራማ በኤረር ላይ ያለች
የምትመሰገን በክብር የገነነች
የመላእክት ግርማ የክብር አክሊላቸው
የሥላሴ ዙፋን አንቺ ነሽ ጌጣቸው
አዝ.............
በምድረ ሎዛ ያዕቆብ ያየሽ
የወርቅ መሰላል ድንግል አንቺ ነሽ
የአምላክ ማደሪያ እናቱ የሆንሽ
ምዕራገ ጸሎት ንጽሕትም ነሽ
የአሕዛብ በረከት የአብርሃም ዘር
መርገም ተሻረልን /3/ አገኘን በአንቺ ክብር
የተነገረልሽ ትንቢቱ በምድር…
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
እመቤታችን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም እንደ ልጇ ተነሥታ ዐርጋለች።"አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት"(መዝ 131:8) በማለት ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት የጌታችንና የእናቱን የእመቤታችንን ትንሣኤ አስተባብሮ ተናግሯል።"አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ" ብሎ የጌታን "አንተና የመቅደስህ ታቦት" በማለት ጌታችን ብቻ ሳይሆን እናቱም እንደምትነሣ በእውነት ተነበየ።
#ኋላ ጻድቃን የሚቆሙትን የቀኝ ቁመት እመቤታችን ዛሬ ቆማዋለች።"በወርቅ ልብስ ተሸፋፍና ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" እንዳለ አባቷ ቅዱስ ዳዊት።
#ልጇ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ኋላ ለጻድቃን የሚያወርሳቸውን "ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀውን" (1ኛ ቆሮ 2:9) ዛሬ ለእናቱ አውርሷታል።
ለነገሩ ራሷ መንግሥተ ሰማያት ናት።ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ንጉሠ ሰማያት ወምድር ማኅፀኗን መናገሻ አድርጎ ነግሦባታልና።
#ልጇ "ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።"(ዮሐ14:3) እንዳለ እርሷም እርሷ ባለችበት እንሆን ዘንድ ከልጇ ታማልደናለች።ማርያም ማለት መርኅ ለመንግሥተ ሰማያት (በቃልኪዳኗ በአማላጅነቷ ረድታ መንግሥተ ሰማያት የምታገባ) ማለት ነውና።
#ጌታ መጋቢት 27 በመስቀል ላይ ሞቶ መጋቢት 29 በሦስተኛው ቀን እንደተነሣ እመቤታችንም በጥር 21 ዐርፋ ገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ቆይታ በነሐሴ 14 ቀን በጌቴሴማኒ ተቀብራ በነሐሴ 16 ቀን በክብር፣በይባቤ መላእክት ተነሥታ ዐርጋለች።
#አይ የሞተ አይነሣም ለምትሉ አባታችን ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስን በመንፈስ እንጠራዋለን "ነገር ግን ሰው፤ሙታን እንዴት ይነሣሉ? በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ይኖር ይሆናል።አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም።"(1ኛ ቆሮ 15:35) ብሎ ይዘልፍናል።
#ተነሥቶ ወደ ሰማይ አይወጣም የሚል ቢኖር ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስን በሃይማኖት እንጠራዋለን፤እንዴትም ወደ ሰማይ እንደወጣ እንጠይቀዋለን።"ሲሄዱም እያዘገሙም ሲጫወቱ፤ እነሆ የእሳት ሰረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ።”(2ኛ ነገ 2:11)
ሞቶ ተነሥቶ ያረገ የለም የሚል ማንም ቢኖር ዳግመኛ ቅዱስ ጳውሎስ
"ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤
ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፤ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።"(1ኛ ተሰ 4:16-17) ሲል ይነግርልናል።
#አስተውሉ ያቀረብነው ማስረጃ ጻድቃንን የሚመለከት ነው።ጻድቃን እንዲህ ከከበሩ የጻድቃን እናታቸው የአምላክ እናት ቅደስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምማ ክብሯ ምን ያህል ይሆን !!!!!!!!???
እኛስ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም "አሕዛብ ሁላችሁ ኑ ድንግል ማርያምን እናመስግናት" እንላለን!!!
ነሐሴ ኪዳነምሕረት 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ኋላ ጻድቃን የሚቆሙትን የቀኝ ቁመት እመቤታችን ዛሬ ቆማዋለች።"በወርቅ ልብስ ተሸፋፍና ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" እንዳለ አባቷ ቅዱስ ዳዊት።
#ልጇ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ኋላ ለጻድቃን የሚያወርሳቸውን "ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀውን" (1ኛ ቆሮ 2:9) ዛሬ ለእናቱ አውርሷታል።
ለነገሩ ራሷ መንግሥተ ሰማያት ናት።ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ንጉሠ ሰማያት ወምድር ማኅፀኗን መናገሻ አድርጎ ነግሦባታልና።
#ልጇ "ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።"(ዮሐ14:3) እንዳለ እርሷም እርሷ ባለችበት እንሆን ዘንድ ከልጇ ታማልደናለች።ማርያም ማለት መርኅ ለመንግሥተ ሰማያት (በቃልኪዳኗ በአማላጅነቷ ረድታ መንግሥተ ሰማያት የምታገባ) ማለት ነውና።
#ጌታ መጋቢት 27 በመስቀል ላይ ሞቶ መጋቢት 29 በሦስተኛው ቀን እንደተነሣ እመቤታችንም በጥር 21 ዐርፋ ገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ቆይታ በነሐሴ 14 ቀን በጌቴሴማኒ ተቀብራ በነሐሴ 16 ቀን በክብር፣በይባቤ መላእክት ተነሥታ ዐርጋለች።
#አይ የሞተ አይነሣም ለምትሉ አባታችን ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስን በመንፈስ እንጠራዋለን "ነገር ግን ሰው፤ሙታን እንዴት ይነሣሉ? በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ይኖር ይሆናል።አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም።"(1ኛ ቆሮ 15:35) ብሎ ይዘልፍናል።
#ተነሥቶ ወደ ሰማይ አይወጣም የሚል ቢኖር ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስን በሃይማኖት እንጠራዋለን፤እንዴትም ወደ ሰማይ እንደወጣ እንጠይቀዋለን።"ሲሄዱም እያዘገሙም ሲጫወቱ፤ እነሆ የእሳት ሰረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ።”(2ኛ ነገ 2:11)
ሞቶ ተነሥቶ ያረገ የለም የሚል ማንም ቢኖር ዳግመኛ ቅዱስ ጳውሎስ
"ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤
ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፤ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።"(1ኛ ተሰ 4:16-17) ሲል ይነግርልናል።
#አስተውሉ ያቀረብነው ማስረጃ ጻድቃንን የሚመለከት ነው።ጻድቃን እንዲህ ከከበሩ የጻድቃን እናታቸው የአምላክ እናት ቅደስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምማ ክብሯ ምን ያህል ይሆን !!!!!!!!???
እኛስ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም "አሕዛብ ሁላችሁ ኑ ድንግል ማርያምን እናመስግናት" እንላለን!!!
ነሐሴ ኪዳነምሕረት 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
+ የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ ክቡር ነው! +
መዝ 115(116)፥6)
እንኳን አደረሰን!! (ለወዳጆችዎ ቃለ እግዚአብሔር ያጋሩ)
ጻድቁ ረጅሙን የዚኽ ዓለም ጉዞ በድል ያጠናቀቁበት ዋዜማ በመኾኑ ጽሑፉን አረዘምኩ። ላረዘምኩባችኹ "ይቅርታ" እየጠየቅኹ "ዘለግ" ወዳለው ጽሑፍ ልዝለቅ:-
ቤተክርስቲያናችን ቅዱሳት መጻሕፍትን መሠረት በማድረግ የቅዱሳን አበውና እማትን በዓለ ዕረፍት ስብሐተ እግዚአብሔርን በማቅረብ በዓሉ የሚከበርለትን ጻድቅ ገድል በማንበብና ተጋድሎውን በማሰብ ምዕመናንም የጻድቃንን ጎዳና እንዲከተሉ በማስተማር ታከብራለች፡፡
ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እንደተናገረውም "የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።" እያለች ትሰብካለች፡፡ (መዝ 115፥15)
ቅዱሳን ከልደታቸውም ቀን ይልቅ ወደ ፈጣሪያቸው የሄዱበት የዕረፍታቸው ቀን እጅግ የከበረና ገናና ነው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን ይህን በተመለከተ ሲናገር "ከመወለድ ቀን የሞት ቀን ይሻላል።" ይላል። (መክ 7፥2) ጠቢቡ በግልጽ እንደተናገረ ቅዱሳን ሰዎች ከተወለዱበት ቀን የሞቱበት ቀን ይሻላል ይበልጣልም ፡፡ ለምን? ቢሉ የልደታቸው ቀን ወደ ተጋድሎ የገቡበት ቀን ሲሆን የሞታቸው ቀን ደግሞ ተጋድሎን የፈጸሙበትና የድል አክሊልን ለመቀበል የሚዘጋጁበት ቀን በመሆኑ ነው፡፡
- ይቀጥላል......
👉የዩትዩብ ቻናሌን ይቀላቀሉ 🙏🙏🙏
https://youtube.com/@zemaridawitkibru2405?si=FhlrmjjdcgwzXO_2
👉ቴሌግራም ቻናል
https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
መዝ 115(116)፥6)
እንኳን አደረሰን!! (ለወዳጆችዎ ቃለ እግዚአብሔር ያጋሩ)
ጻድቁ ረጅሙን የዚኽ ዓለም ጉዞ በድል ያጠናቀቁበት ዋዜማ በመኾኑ ጽሑፉን አረዘምኩ። ላረዘምኩባችኹ "ይቅርታ" እየጠየቅኹ "ዘለግ" ወዳለው ጽሑፍ ልዝለቅ:-
ቤተክርስቲያናችን ቅዱሳት መጻሕፍትን መሠረት በማድረግ የቅዱሳን አበውና እማትን በዓለ ዕረፍት ስብሐተ እግዚአብሔርን በማቅረብ በዓሉ የሚከበርለትን ጻድቅ ገድል በማንበብና ተጋድሎውን በማሰብ ምዕመናንም የጻድቃንን ጎዳና እንዲከተሉ በማስተማር ታከብራለች፡፡
ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እንደተናገረውም "የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።" እያለች ትሰብካለች፡፡ (መዝ 115፥15)
ቅዱሳን ከልደታቸውም ቀን ይልቅ ወደ ፈጣሪያቸው የሄዱበት የዕረፍታቸው ቀን እጅግ የከበረና ገናና ነው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን ይህን በተመለከተ ሲናገር "ከመወለድ ቀን የሞት ቀን ይሻላል።" ይላል። (መክ 7፥2) ጠቢቡ በግልጽ እንደተናገረ ቅዱሳን ሰዎች ከተወለዱበት ቀን የሞቱበት ቀን ይሻላል ይበልጣልም ፡፡ ለምን? ቢሉ የልደታቸው ቀን ወደ ተጋድሎ የገቡበት ቀን ሲሆን የሞታቸው ቀን ደግሞ ተጋድሎን የፈጸሙበትና የድል አክሊልን ለመቀበል የሚዘጋጁበት ቀን በመሆኑ ነው፡፡
- ይቀጥላል......
👉የዩትዩብ ቻናሌን ይቀላቀሉ 🙏🙏🙏
https://youtube.com/@zemaridawitkibru2405?si=FhlrmjjdcgwzXO_2
👉ቴሌግራም ቻናል
https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
ከላይኛው የቀጠለ ......
ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እንደመሠከረው የደጋግ ሰዎች ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የከበረ ነው ፡፡ ክብራቸውንም በቃላት ተናግረን በብዕር (ብርዕ) ጽፈን ልንፈጽመው እንደማንችል መረዳት ይኖርብናል ፡፡ ዓለም የራሱ የሆነውን ሰዎች ዕረፍት ቀን በደመቀ ሥነ ሥርዓት ያከብራል ፡፡ እግዚአብሔርም በሕይወታቸው ሁሉ እርሱን እያመለኩ ለእርሱ እየተገዙ ፈቃዱን እየፈጸሙና የዚህ ዓለም ተጋድሏቸውም በሞተ ሥጋ የተቋጨ ወዳጆቹን ዕረፍት በማያልፍና ቃላት በማይገልጡት ክብር ያከብራል፡፡
የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው
ለምን ተባለ?
☞ የሥጋ ሞቱ ሕያው መሆኑ የሚገለጥበት በመሆኑ
በክርስትና ሃይማኖት መሠረታዊ አስተምህሮ መሠረት ሞት የሰው ልጅ የጉዞ ፍጻሜ አይደለም ፡፡ ከሞት በኋላ ዘላለማዊ ሕይወት ከመቃብር በኋላም ትንሣኤ አለና ፡፡ ሰው ከሞት በኋላ ለሚገጥመው ሕይወትና ለሚያገኘው ጸጋ ለሚወርሰው የማያልፍ ርስት የሚፈተነው በዚህ ዓለም በሚኖረው ቆይታ ነው ፡፡ ጌታችን በወንጌል "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።" ሲል ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ "ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ ልንገባ ያስፈልገናል።" ማለቱ ይህ ዓለም ለደጋግ ሰዎች የመከራና የኋዘን ምክንያት መሆኑን ያሳየናል፡፡ (ዮሐ 16፥33፣ የሐዋ 14 ፥22)
ቅዱስ ጴጥሮስም የእምነታችንን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችንን መዳን (መንግሥተ ሰማያትን መውረስ) የምናገኘው በዚህ ዓለም የሚገጥመንን ፈተና፣ መከራና ኃዘን በድል ከተወጣን በኋላ መሆኑን ደጋግሞ መስክሯል። (1ጴጥ 4፥14 2ጴጥ 1፥5-9)
ይህ ዓለም የተጋድሎ ዓለም መሆኑን የተረዳ ሰው ደጋግ ሰዎች ነፍሳቸው ከሥጋቸው የሚለይበት በሥጋ ሞት ከዚህ ዓለም የሚወሰዱበት ቀን ሕያዋን መሆናችው የሚታወቅበት ቀን መሆኑን ለመረዳት አይቸገርም ፡፡ በዚህ ዓለም ስንኖር የነፍስ ከእግዚአብሔር ለመለየት መንሥኤ በሆነ ኃጢአት የመያዛችን ዕድል ሰፊ ነው ፡፡ ስለሆነም በአምልኮተ እግዚአብሔር ጸንቶ በምግባር ቀንቶ ለኖረ ሰው ዕለተ ሞቱ ወደ ኃጢአት ከሚያንደረድሩ ክፉ ምኞቶች ጋር የሚያደርገው ትግል የሚያበቃበትና ጽድቅ በተባለች የእግዚአብሔር መንግሥት በሕይወት ለዘላለም እንደሚኖር የሚታወቅበት ቀን ነው፡፡ ጌታችን በወንጌል "ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ነው።" ብሎ መናገሩ ይህን የሚያጸናልን ነው፡፡ (ዮሐ 11፥25) "ቢሞት እንኳን" ሲል በሥጋ ሞት ቢወሰድ እንኳ ማለቱ ግልጽ ነውና፡፡
ጌታችን በዚህ ስፍራ ብቻ ሳይሆን ደጋግሞ እርሱን አምነውና ትእዛዛቱን በመፈጸም አስደስተውት በበጎ ምግባርም ተሸልመው በሥጋ ሞት ያለፉ እንደነ አብርሃም ያሉ ደጋጎች ዳግም ሞትን እንደማያዩና ሕያዋን እንደሆኑ መስክሯል ፡፡ "እውነት እውነት እላችኋለሁ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም" እንዲል። (ዮሐ 8፥51)
☞ የዚህ ዓለም ተጋድሎው የሚያበቃበት በመሆኑ
ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚመሠክሩት እውነተኛ ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ከሰይጣን ክፉ ከሆነ የዓለም ምኞት ከሥጋ ፈቃድና እና ከክፉ ሀሳቦች ጋር የማያቋርጥ ተጋድሎ አለባቸው፡፡ ሐዋርያው "መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና ነገር ግን በዚህ ዓለም ካሉ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።" ብሎ እንደተናገረ፡፡ (ኤፌ 6፥12-16) ተጋድሎ አንዱ እውነተኛ የክርስትና ሕይወት መገለጫ ነው ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለደቀ መዝሙሩ ለጢሞቴዎስ "መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል።" በማለት የመከረውም ምክር ይህንኑ ያስገነዝበናል ፡፡ (1ጢሞ 6፥12) ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ከርኩሳን መናፍስትና ከሠለጠኑባቸው ሰዎች ጋር ስለ ክርስቶስ የሚያደርጉት ተጋድሎ የክብር አክሊል የሚያገኙበት ጉዞ ነው ፡፡ በተጋድሎ ጸንቶ መኖር እንደሚገባ ሐዋርያው ሲያስተምር "ወዳጆች ሆይ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኳችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።" ይላል (ይሁዳ 1፥3) የክርስትና ሃይማኖት የተጋድሎ ሕይወት የሞላበት መንገድ ነው የሚባለውም ለዚሁ ነው ፡፡ ክርስቲያናዊ ሕይወትን ያለ ተጋድሎ ማሰብ ጉዞውን ሳይጀምሩ ከመንገድ መቅረትን በመሐል መደነቃቀፍንና ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን ወደ ማማረር ያደርሳል። (ያዕ 5፥9) ሐዋርያት በመልእክቶቻቸው "ይሁን እንጂ መጥቼ ባያችሁ ወይም ብርቅ በአንድ ልብ ስለወንጌል ሃይማኖት አብራችሁ እየተጋደላችሁ በአ ንድ መንፈስ እንድትቆሙ ስለ ኑሯችሁ እሰማ ዘንድ ለክርስቶስ ወንጌል እንደሚገባ ኑሩ ...በእኔ ያያችሁት አሁንም በእኔ እንዳለ የምትሰሙት ያው መጋደል ደርሶባችኋልና። " በማለት ያስተማሩን ትምህርት የክርስትናን መንገድ የሚከተል ሰው መከራ መንገዱ፤ መስቀል ምርኩዙ፤ እግዚአብሔር መሪው፤ ወንጌል መመሪያው፤ መንግሥተ ሰማያት ዓላማው መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡ (ፊልጵ 1፥27-30)
ቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችን የዕረፍታቸው ቀን በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው "ከተወለዱበትም ቀን የሚሞቱበት ቀን ይሻላል" የተባለውም ከሥጋ ሞታቸውም በኋላ ዳግመኛ ወደማያለቅሱበት፣ ወደማይራቡበት፣ ወደማይጠሙበት፣ ዕንባቸውም ሁሉ ወደሚታበስበት ዓለም ስለሚጓዙ ነው፡፡ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራእዩ የተመለከታቸው አንድስ እንኳ ሊቆጥራቸው አይችልም የተባለላቸው ነጫጭ ልብስ ለብሰው የተገለጡት እነዚያ ቅዱሳን እነማን እንደሆኑ "እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው ልብሳቸውንም አጥበው (ንስሐ ገብተው) በበጉ ደም አነጹ (በሥጋ ወደሙ ታተሙ) ስለዚህ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት አሉ ሌሊትና ቀንም በመቅደሱ ያመልኩታል ከእንግዲህ ወዲህ አይራቡም አይጠሙም ፀሐይም ትኩሳትም ሁሉ ከቶ አይወርድባቸውም በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናልና ወደ ሕይወትም ውኃ ምንጭ ይመራቸዋልና እግዚአብሔር ዕንባዎችን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል።" ተብሎ ተነግሮታል። (ራዕይ 7፥14-17)
☞ የድል አክሊል የሚቀዳጁበት ቀን በመሆኑ
ጌታችን "እስከሞት ድረስ የታመንክ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለው ።" ብሎ የተናገረው ቃል የሕይወት አክሊል የተባለች መንግሥተ ሰማያት የምትሰጠው ከሥጋ ሞት በኋላ መሆኑን ይመሠክርልናል፡፡ (ራእይ 2፥9)
"የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው " መባሉም የጻድቅ ሰው ዕለተ ሞት የክብር አክሊል የመቀዳጀቱ ማብሠሪያ ቀን በመሆኑ ነው ፡፡ ጌታችንም "እስከ መጨረሻው (እስከ ዕለተ ሞቱ) የሚጸና እርሱ ይድናል (መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳል)።" ማለቱ ይህን ያጠነክርልናል፡፡ (ማቴ 24፥12)
ቅዱሳን የዚህን ዓለም ተጋድሎ ፈጽመው ፈተናውን አሸንፈው መከራውን አልፈው በሞተ ሥጋ ሲወሰዱ በፍጡር ሚዛን የማይለካ በፍጡር አንደበት ተዘርዝሮ የማያልቅ ከፍጡር ሕሊና በላይ የሆነ ክብርን ይቀዳጃሉ ፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን "ጻድቃን ድል ባደረጉ ጊዜ ብዙ ክብር አለ።" ብሎ እንደተናገረ፡፡ (ምሳ 28፥12) ጠቢቡ ቅዱሳን ከሥጋ ሞታቸው በኋላ የሚጠብቃቸውን የክብር መጠን በቁጥር ሳይገድብ "ብዙ ክብር" ማለቱን ልብ ማለት ይገባል፡፡
ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እንደመሠከረው የደጋግ ሰዎች ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የከበረ ነው ፡፡ ክብራቸውንም በቃላት ተናግረን በብዕር (ብርዕ) ጽፈን ልንፈጽመው እንደማንችል መረዳት ይኖርብናል ፡፡ ዓለም የራሱ የሆነውን ሰዎች ዕረፍት ቀን በደመቀ ሥነ ሥርዓት ያከብራል ፡፡ እግዚአብሔርም በሕይወታቸው ሁሉ እርሱን እያመለኩ ለእርሱ እየተገዙ ፈቃዱን እየፈጸሙና የዚህ ዓለም ተጋድሏቸውም በሞተ ሥጋ የተቋጨ ወዳጆቹን ዕረፍት በማያልፍና ቃላት በማይገልጡት ክብር ያከብራል፡፡
የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው
ለምን ተባለ?
☞ የሥጋ ሞቱ ሕያው መሆኑ የሚገለጥበት በመሆኑ
በክርስትና ሃይማኖት መሠረታዊ አስተምህሮ መሠረት ሞት የሰው ልጅ የጉዞ ፍጻሜ አይደለም ፡፡ ከሞት በኋላ ዘላለማዊ ሕይወት ከመቃብር በኋላም ትንሣኤ አለና ፡፡ ሰው ከሞት በኋላ ለሚገጥመው ሕይወትና ለሚያገኘው ጸጋ ለሚወርሰው የማያልፍ ርስት የሚፈተነው በዚህ ዓለም በሚኖረው ቆይታ ነው ፡፡ ጌታችን በወንጌል "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።" ሲል ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ "ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ ልንገባ ያስፈልገናል።" ማለቱ ይህ ዓለም ለደጋግ ሰዎች የመከራና የኋዘን ምክንያት መሆኑን ያሳየናል፡፡ (ዮሐ 16፥33፣ የሐዋ 14 ፥22)
ቅዱስ ጴጥሮስም የእምነታችንን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችንን መዳን (መንግሥተ ሰማያትን መውረስ) የምናገኘው በዚህ ዓለም የሚገጥመንን ፈተና፣ መከራና ኃዘን በድል ከተወጣን በኋላ መሆኑን ደጋግሞ መስክሯል። (1ጴጥ 4፥14 2ጴጥ 1፥5-9)
ይህ ዓለም የተጋድሎ ዓለም መሆኑን የተረዳ ሰው ደጋግ ሰዎች ነፍሳቸው ከሥጋቸው የሚለይበት በሥጋ ሞት ከዚህ ዓለም የሚወሰዱበት ቀን ሕያዋን መሆናችው የሚታወቅበት ቀን መሆኑን ለመረዳት አይቸገርም ፡፡ በዚህ ዓለም ስንኖር የነፍስ ከእግዚአብሔር ለመለየት መንሥኤ በሆነ ኃጢአት የመያዛችን ዕድል ሰፊ ነው ፡፡ ስለሆነም በአምልኮተ እግዚአብሔር ጸንቶ በምግባር ቀንቶ ለኖረ ሰው ዕለተ ሞቱ ወደ ኃጢአት ከሚያንደረድሩ ክፉ ምኞቶች ጋር የሚያደርገው ትግል የሚያበቃበትና ጽድቅ በተባለች የእግዚአብሔር መንግሥት በሕይወት ለዘላለም እንደሚኖር የሚታወቅበት ቀን ነው፡፡ ጌታችን በወንጌል "ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ነው።" ብሎ መናገሩ ይህን የሚያጸናልን ነው፡፡ (ዮሐ 11፥25) "ቢሞት እንኳን" ሲል በሥጋ ሞት ቢወሰድ እንኳ ማለቱ ግልጽ ነውና፡፡
ጌታችን በዚህ ስፍራ ብቻ ሳይሆን ደጋግሞ እርሱን አምነውና ትእዛዛቱን በመፈጸም አስደስተውት በበጎ ምግባርም ተሸልመው በሥጋ ሞት ያለፉ እንደነ አብርሃም ያሉ ደጋጎች ዳግም ሞትን እንደማያዩና ሕያዋን እንደሆኑ መስክሯል ፡፡ "እውነት እውነት እላችኋለሁ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም" እንዲል። (ዮሐ 8፥51)
☞ የዚህ ዓለም ተጋድሎው የሚያበቃበት በመሆኑ
ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚመሠክሩት እውነተኛ ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ከሰይጣን ክፉ ከሆነ የዓለም ምኞት ከሥጋ ፈቃድና እና ከክፉ ሀሳቦች ጋር የማያቋርጥ ተጋድሎ አለባቸው፡፡ ሐዋርያው "መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና ነገር ግን በዚህ ዓለም ካሉ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።" ብሎ እንደተናገረ፡፡ (ኤፌ 6፥12-16) ተጋድሎ አንዱ እውነተኛ የክርስትና ሕይወት መገለጫ ነው ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለደቀ መዝሙሩ ለጢሞቴዎስ "መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል።" በማለት የመከረውም ምክር ይህንኑ ያስገነዝበናል ፡፡ (1ጢሞ 6፥12) ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ከርኩሳን መናፍስትና ከሠለጠኑባቸው ሰዎች ጋር ስለ ክርስቶስ የሚያደርጉት ተጋድሎ የክብር አክሊል የሚያገኙበት ጉዞ ነው ፡፡ በተጋድሎ ጸንቶ መኖር እንደሚገባ ሐዋርያው ሲያስተምር "ወዳጆች ሆይ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኳችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።" ይላል (ይሁዳ 1፥3) የክርስትና ሃይማኖት የተጋድሎ ሕይወት የሞላበት መንገድ ነው የሚባለውም ለዚሁ ነው ፡፡ ክርስቲያናዊ ሕይወትን ያለ ተጋድሎ ማሰብ ጉዞውን ሳይጀምሩ ከመንገድ መቅረትን በመሐል መደነቃቀፍንና ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን ወደ ማማረር ያደርሳል። (ያዕ 5፥9) ሐዋርያት በመልእክቶቻቸው "ይሁን እንጂ መጥቼ ባያችሁ ወይም ብርቅ በአንድ ልብ ስለወንጌል ሃይማኖት አብራችሁ እየተጋደላችሁ በአ ንድ መንፈስ እንድትቆሙ ስለ ኑሯችሁ እሰማ ዘንድ ለክርስቶስ ወንጌል እንደሚገባ ኑሩ ...በእኔ ያያችሁት አሁንም በእኔ እንዳለ የምትሰሙት ያው መጋደል ደርሶባችኋልና። " በማለት ያስተማሩን ትምህርት የክርስትናን መንገድ የሚከተል ሰው መከራ መንገዱ፤ መስቀል ምርኩዙ፤ እግዚአብሔር መሪው፤ ወንጌል መመሪያው፤ መንግሥተ ሰማያት ዓላማው መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡ (ፊልጵ 1፥27-30)
ቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችን የዕረፍታቸው ቀን በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው "ከተወለዱበትም ቀን የሚሞቱበት ቀን ይሻላል" የተባለውም ከሥጋ ሞታቸውም በኋላ ዳግመኛ ወደማያለቅሱበት፣ ወደማይራቡበት፣ ወደማይጠሙበት፣ ዕንባቸውም ሁሉ ወደሚታበስበት ዓለም ስለሚጓዙ ነው፡፡ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራእዩ የተመለከታቸው አንድስ እንኳ ሊቆጥራቸው አይችልም የተባለላቸው ነጫጭ ልብስ ለብሰው የተገለጡት እነዚያ ቅዱሳን እነማን እንደሆኑ "እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው ልብሳቸውንም አጥበው (ንስሐ ገብተው) በበጉ ደም አነጹ (በሥጋ ወደሙ ታተሙ) ስለዚህ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት አሉ ሌሊትና ቀንም በመቅደሱ ያመልኩታል ከእንግዲህ ወዲህ አይራቡም አይጠሙም ፀሐይም ትኩሳትም ሁሉ ከቶ አይወርድባቸውም በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናልና ወደ ሕይወትም ውኃ ምንጭ ይመራቸዋልና እግዚአብሔር ዕንባዎችን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል።" ተብሎ ተነግሮታል። (ራዕይ 7፥14-17)
☞ የድል አክሊል የሚቀዳጁበት ቀን በመሆኑ
ጌታችን "እስከሞት ድረስ የታመንክ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለው ።" ብሎ የተናገረው ቃል የሕይወት አክሊል የተባለች መንግሥተ ሰማያት የምትሰጠው ከሥጋ ሞት በኋላ መሆኑን ይመሠክርልናል፡፡ (ራእይ 2፥9)
"የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው " መባሉም የጻድቅ ሰው ዕለተ ሞት የክብር አክሊል የመቀዳጀቱ ማብሠሪያ ቀን በመሆኑ ነው ፡፡ ጌታችንም "እስከ መጨረሻው (እስከ ዕለተ ሞቱ) የሚጸና እርሱ ይድናል (መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳል)።" ማለቱ ይህን ያጠነክርልናል፡፡ (ማቴ 24፥12)
ቅዱሳን የዚህን ዓለም ተጋድሎ ፈጽመው ፈተናውን አሸንፈው መከራውን አልፈው በሞተ ሥጋ ሲወሰዱ በፍጡር ሚዛን የማይለካ በፍጡር አንደበት ተዘርዝሮ የማያልቅ ከፍጡር ሕሊና በላይ የሆነ ክብርን ይቀዳጃሉ ፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን "ጻድቃን ድል ባደረጉ ጊዜ ብዙ ክብር አለ።" ብሎ እንደተናገረ፡፡ (ምሳ 28፥12) ጠቢቡ ቅዱሳን ከሥጋ ሞታቸው በኋላ የሚጠብቃቸውን የክብር መጠን በቁጥር ሳይገድብ "ብዙ ክብር" ማለቱን ልብ ማለት ይገባል፡፡
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
"መንገድ"
በደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የም/ደ/ማ/ወ/መ/ማ (ሰንበት ትምህርት ቤት) "መንገድ" የተሰኘ ልዩ መንፈሳዊ ቴአትር አዘጋጅቶላችኋል።እርስዎም በዕለተ እሑድ መስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት በመገኘት ይህን መንፈሳዊ ቴአትር እንዲመለከቱ በክብር ተጋብዘዋል።
ቦታ:- በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ
የመግቢያ ዋጋ:- 100 ብር
የመግቢያ ትኬቱን በ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ነዋየ ቅዱሳን መሸጫ ያገኙታል።
"መንገድ"
በደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የም/ደ/ማ/ወ/መ/ማ (ሰንበት ትምህርት ቤት) "መንገድ" የተሰኘ ልዩ መንፈሳዊ ቴአትር አዘጋጅቶላችኋል።እርስዎም በዕለተ እሑድ መስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት በመገኘት ይህን መንፈሳዊ ቴአትር እንዲመለከቱ በክብር ተጋብዘዋል።
ቦታ:- በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ
የመግቢያ ዋጋ:- 100 ብር
የመግቢያ ትኬቱን በ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ነዋየ ቅዱሳን መሸጫ ያገኙታል።
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በሁለት የቀደሙ የመጻሕፍት አበርክቷቸው የምናውቃቸው መምህራችን መካሪያችን አባታችን የጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተ ብርሐን ሰንበት ት/ቤት ፍሬ እና በቀድሞ አገልግሎታቸው በኮተቤ ሐገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አገልጋይ እና በአሁኑ ሰዓት በገነተ ጽጌ አራዳ ጊዮርጊስ የስብከተ ወንጌል አገልጋይ መምህር በማኅበረ ቅዱሳን የሬድዮ መርሐግብር ባለሙያና አገልጋይ
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
የክርስቲያናዊ ሕይወት መገለጫዎቹና ተጋድሎው
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በሁለት የቀደሙ የመጻሕፍት አበርክቷቸው የምናውቃቸው መምህራችን መካሪያችን አባታችን የጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተ ብርሐን ሰንበት ት/ቤት ፍሬ እና በቀድሞ አገልግሎታቸው በኮተቤ ሐገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አገልጋይ እና በአሁኑ ሰዓት በገነተ ጽጌ አራዳ ጊዮርጊስ የስብከተ ወንጌል አገልጋይ መምህር በማኅበረ ቅዱሳን የሬድዮ መርሐግብር ባለሙያና አገልጋይ
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
የክርስቲያናዊ ሕይወት መገለጫዎቹና ተጋድሎው
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በሁለት የቀደሙ የመጻሕፍት አበርክቷቸው የምናውቃቸው መምህራችን መካሪያችን አባታችን የጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተ ብርሐን ሰንበት ት/ቤት ፍሬ እና በቀድሞ አገልግሎታቸው በኮተቤ ሐገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አገልጋይ እና በአሁኑ ሰዓት በገነተ ጽጌ አራዳ ጊዮርጊስ የስብከተ ወንጌል አገልጋይ መምህር በማኅበረ ቅዱሳን የሬድዮ መርሐግብር ባለሙያና አገልጋይ
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
የክርስቲያናዊ ሕይወት መገለጫዎቹና ተጋድሎው
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
ይነበብ 🙏🙏🙏🙏
መንፈሳዊ መርሐግብር ጥሪ !!!!
ላልሰሙ እንድታሰሙ በእመቤታችን ስም እንጠይቃለን !🙏🙏🙏
የታኅሳስዳር ደብረ ጽዮን ማርያም ልጆች ማኅበር
መንፈሳዊ መርሐግብር ጥሪ !!!!
ለኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምዕመናን በሙሉ በቅድሚያ የታኃሳስዳር ደብረ ጽዮን ህንፃ ቤተክርስቲያን ለማሰራት እያደረጋችሁልን ስላለው ሁለንተናዊ ድጋፍ ከልብ እያመሰገንን ፤ ይህንን ስራ አጠናክረን ለማስቀጠል እና ለህንፃ ማሠሪያው ከዚህ የተሻለ እርዳታ ለማድረግ ያስችለን ዘንድ በአይነቱ የተለየ መርሐ ግብር በማዘጋጀት ለተለያዩ ሰዎች ጥሪ በማድረግ ላይ እንገናኛለን ። በመሆኑም ግንቦት 24/9/2017 ዓ.ም ከ 5:30 ጀምሮ በሚኖረን ልዩ መርሐ ግብር ለመሳተፍ 5 ኪሎ በሚገኘው መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም እንድትገኙልን ስንል በእመቤታችን ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።።
ላልሰሙ እንድታሰሙ በእመቤታችን ስም እንጠይቃለን !🙏🙏🙏
የታኅሳስዳር ደብረ ጽዮን ማርያም ልጆች ማኅበር