<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
አዝዤ ልጎርሰው፥
ያጠቀስኩት ሽሮ፥ አፌን ገፍቶ ይርቃል
ማባያ የሰነግኩት፥
አረንጓዴ ቃርያ፥ በቅፅበት ይደርቃል
እንደ በረኅ ምድር፥
እንጀራዬ ከስሎ፥ ይሰነጣጠቃል።
ጆሮዬ ከፒያሳ፥
ቦሌ እሚንቆረቆር፥ ይሰማዋል ድራፍት
አይኔ ካራት ኪሎ፥
ቄራ የሚፈረሽ፥ ይታየዋል ፍትፍት።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ያበዳሪን ሰፈር፥
በጀግና አረማመድ፥ ሄዳለሁ ሰንጥቄ
የቡቲኩን ጌታ፥
የጃኬቱን ዋጋ፥ አልፋለሁ ጠይቄ
ስቸስት የከዳኝ፥
ወዳጄን ፈልጌ፥ አልሳለሁ ጥፊ
እንዳያዩኝ ብዬ፥
ከተደበቅኋቸው፥
ካ'ከራዬ ጋራ፥ እነሳለሁ ሰልፊ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ኤድናሞል ደጃፍ፥ ላይ እንጎራደዳለሁ...
ቮድካ እንኳ ባይገኝ፥
የሜንት ያ'ፕሬቲቭ፥ ቦትል አወርዳለሁ
ባለረዥም ፀጉር፥
ባለ ለስላሳ ድምፅ፥ ባለ አይን ባለ አንገት
እያልኩ የተውኳቸው፥
የቸከሶቼ ስልክ፥ ትዝ ይለኛል ድንገት።
ፀሃይ ሲያዘቀዝቅ፥
እያንገሸገሸኝ፥
እያንቀጠቀጠኝ፥ ፀጥ ያለው ሰፈሬ
ወደ ሃያሁለት፥
ቦሌ መድሃኒያለም፥
ወደ አትላስ ጀርባ፥ይመራኛል እግሬ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
በቅንነት #Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰቦች ተባበሩ #Subscriber
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
አዝዤ ልጎርሰው፥
ያጠቀስኩት ሽሮ፥ አፌን ገፍቶ ይርቃል
ማባያ የሰነግኩት፥
አረንጓዴ ቃርያ፥ በቅፅበት ይደርቃል
እንደ በረኅ ምድር፥
እንጀራዬ ከስሎ፥ ይሰነጣጠቃል።
ጆሮዬ ከፒያሳ፥
ቦሌ እሚንቆረቆር፥ ይሰማዋል ድራፍት
አይኔ ካራት ኪሎ፥
ቄራ የሚፈረሽ፥ ይታየዋል ፍትፍት።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ያበዳሪን ሰፈር፥
በጀግና አረማመድ፥ ሄዳለሁ ሰንጥቄ
የቡቲኩን ጌታ፥
የጃኬቱን ዋጋ፥ አልፋለሁ ጠይቄ
ስቸስት የከዳኝ፥
ወዳጄን ፈልጌ፥ አልሳለሁ ጥፊ
እንዳያዩኝ ብዬ፥
ከተደበቅኋቸው፥
ካ'ከራዬ ጋራ፥ እነሳለሁ ሰልፊ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ኤድናሞል ደጃፍ፥ ላይ እንጎራደዳለሁ...
ቮድካ እንኳ ባይገኝ፥
የሜንት ያ'ፕሬቲቭ፥ ቦትል አወርዳለሁ
ባለረዥም ፀጉር፥
ባለ ለስላሳ ድምፅ፥ ባለ አይን ባለ አንገት
እያልኩ የተውኳቸው፥
የቸከሶቼ ስልክ፥ ትዝ ይለኛል ድንገት።
ፀሃይ ሲያዘቀዝቅ፥
እያንገሸገሸኝ፥
እያንቀጠቀጠኝ፥ ፀጥ ያለው ሰፈሬ
ወደ ሃያሁለት፥
ቦሌ መድሃኒያለም፥
ወደ አትላስ ጀርባ፥ይመራኛል እግሬ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
በቅንነት #Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰቦች ተባበሩ #Subscriber
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😁39👍19👏7❤3
#ስኳር_መች_ይጣፍጣል?!
በዚህ እጅ ያልነካው ወዳጅ በማይገኝበት ክፉ ዘመን ሰላሳ አራት አመት እስኪሞላት ድረስ የማንም እጅ ሳይነካካት ከወር በፊት የተሞሸረች ልጃገረድ ወዳጅ አለችኝ።
‹‹ያላገባኝ አይነካኝም!›› ብላ….
‹‹ወንድ ልጅ ወተቱን በነፃ ካገኘ ላሚቱን አይገዛም›› ብላ…
ስንቱን የወንድ ፈንጂ በጥንቃቄ እንጣጥ ብላ፣ ስንቱን አማላይና አታላይ አምልጣ፣ እሷም እንደማንም ግጣሟን አገኘችና ጎጆ ወጣች። ተሰበሰበች። አገባች….ተነካች።
በቃል እና በእምነቷ መሰረት፣ ክብር እና ንፅህንናዋን ጠብቃ ኖረ ተዳረች። ከባሏ ተኛች።
በዚህ ዘመን ቀረ ብለን የምንገረምበት ወግ አጥባቂነቷ የአስናቀች ወርቁን ዘፈን ያስታውሰኝ ነበር። አስናቀች ቀኑን ሙሉ ከምታፈቅረው ልጅ ውላ ልክ ሲመሽ ሌላ እንዳያስብ ‹‹ልሂድ›› ስለምትል ወዳጄን የምትመስል ሴት ዘፍናልን ነበር።
‹‹ፍቅርዬ- ፍቅርዬ ደህና ሁን
ሊመሽ ስለሆነ መሄዴ ነው አሁን…..
…እኔ እንደምወድህ – ፍቅሬ ሆይ ውደደኝ
በህጋዊ ስርአት ማልድና ውሰደኝ…
አፍቅረኝ ላፍቅርህ ኑሯችን ባንድ ይሁን
እስከዚያው ድረስ ግን- ፍቅርዬ ደህና ሁን›› እያለች ዘፍናልን ነበር።
እናም…የ34 አመቷ ወዳጄም በህጋዊ ስርአት፣ በአማላጅና በምልጃ የፈለገችውና የፈለገችውን አገኘችና፣ ወሰዳትና አገባች። ተነካች።
ሰርጉ ተከናውኖ…
ጫጉላው አብቦ…
ከስንት ያመለጠው ብር አምባር ተሰብሮ ጥቂት ቀናት ካለፉ በኋላ አሁንስ ይበቃታል ብዬ ደወልኩላት። እንዴት ሆንሽ….አጥሚትና ገንፎ የት ይዘን እንምጣ ልል እና ላጫውታት ደወልኩላት።
ብዙ ሳይጠራ አነሳች።
(በቅቷታል ማለት ነው…)
ሰላምታችን ሲያልቅ ወደ አንገብጋቢውጉዳይ ገባሁና..
‹‹እህስ…ነገሩስ? እንደጠበቅሸው አገኘሽው ወይስ ቅር አለሽ?›› አልኳት።
‹‹ቅር አለሽ ወይ? ወይ ጉድ…አንቺ….ስኳር መች ይጣፍጣል?!›› ብላ መለሰችልኝ።
ከአንጀቴ ሳቅሁ።
እንዲህ ትላለች ብዬ ስላልጠበቅኩም፣ ያ ከአመታት በፊት የሰማሁት ታሪክ ላይ ያለችው ልጅንም አስታወሰችኝና ሳቅሁ።
(ታሪኩ እንዲህ ነው። ልጅቱ ለስኳር ያላት ፍቅር የትዬሌሌ ነው። ‹‹ከስኳር የሚጥም፣ ከስኳር የሚጣፍጥ ነገር በአለም ላይ…አንዳችም ነገር የለም›› የምትል አይነት። እጮኛዋ ‹‹ተይ ተጋብተን ፍቅር ስንሰራ ኋላ ሃሳብሽን ትለውጫለሽ›› ቢላትም እሷ ግን ወይ ፍንክች! በኋላ ጋብቻው ተከናውኖ ባልና ሚስት ለመጀመሪያ ጊዜ ፍቅር እየሰሩ ወደ ማገባደዱ ሲደርሱ የሚስቱን ሁኔታ ያየው ባል በእጁ የጨበጠውን ስኳር በተከፈተ አፏ ውስጥ ሙጅር ያደርጋል። ይሄን ጊዜ የስኳር ነገር የማይሆንላት ሚስቱ ምን አለች? ‹‹ውይ ውዴ…! የምን አፈር ነው አፌ ውስጥ የጨመርከው?!››)
‹‹ወይ አንቺ…እና ታዲያ ይሄን ያህል ጊዜ በመቆየትሽ ትንሽ አልተቆጨሽም ታዲያ?›› አልኳት
ለመመለስ ሰከንድ አልፈጀባትም።
‹‹በጭራሽ! መቆየቴ መቼም አይቆጨኝም….ግን እንዲህ መሆኑን ግን ነገራችሁኝ አታውቁም….››
‹‹ ብንነግርሽስ ኖሮ?››
‹‹እሱስ ምንም ለውጥ አያመጣም ነበር…ያው ምናልባት ትንሽ…ይበልጥ ልጓጓ ግን እችል ነበር……..››
ወሬያችን አልቆ ስልኩን ስዘጋ በዚህ ሁሉም ሰው ሁሉንም ሰው ለመምሰል በሚሮጥበት ጊዜ፣ ለግል አቋምና እምነቷ ባላት ታማኝነት እንዳዲስ ተደነቅኩባት። ቀናሁባት።
ከዚህ ሁሉ በላይ ግን (በእኔ እና በአለም ስሌት) ዘግይታም ቢሆን አዳሜ የአለምን ምሬት የሚያጣፍጠው ፍቅርን በመስራት ስኳር መሆኑን በማወቋ ተደሰትኩላት።
🔘በሕይወት እምሻው🔘
አረ በቅንነት #Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰቦች ተባበሩ #Subscriber
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በዚህ እጅ ያልነካው ወዳጅ በማይገኝበት ክፉ ዘመን ሰላሳ አራት አመት እስኪሞላት ድረስ የማንም እጅ ሳይነካካት ከወር በፊት የተሞሸረች ልጃገረድ ወዳጅ አለችኝ።
‹‹ያላገባኝ አይነካኝም!›› ብላ….
‹‹ወንድ ልጅ ወተቱን በነፃ ካገኘ ላሚቱን አይገዛም›› ብላ…
ስንቱን የወንድ ፈንጂ በጥንቃቄ እንጣጥ ብላ፣ ስንቱን አማላይና አታላይ አምልጣ፣ እሷም እንደማንም ግጣሟን አገኘችና ጎጆ ወጣች። ተሰበሰበች። አገባች….ተነካች።
በቃል እና በእምነቷ መሰረት፣ ክብር እና ንፅህንናዋን ጠብቃ ኖረ ተዳረች። ከባሏ ተኛች።
በዚህ ዘመን ቀረ ብለን የምንገረምበት ወግ አጥባቂነቷ የአስናቀች ወርቁን ዘፈን ያስታውሰኝ ነበር። አስናቀች ቀኑን ሙሉ ከምታፈቅረው ልጅ ውላ ልክ ሲመሽ ሌላ እንዳያስብ ‹‹ልሂድ›› ስለምትል ወዳጄን የምትመስል ሴት ዘፍናልን ነበር።
‹‹ፍቅርዬ- ፍቅርዬ ደህና ሁን
ሊመሽ ስለሆነ መሄዴ ነው አሁን…..
…እኔ እንደምወድህ – ፍቅሬ ሆይ ውደደኝ
በህጋዊ ስርአት ማልድና ውሰደኝ…
አፍቅረኝ ላፍቅርህ ኑሯችን ባንድ ይሁን
እስከዚያው ድረስ ግን- ፍቅርዬ ደህና ሁን›› እያለች ዘፍናልን ነበር።
እናም…የ34 አመቷ ወዳጄም በህጋዊ ስርአት፣ በአማላጅና በምልጃ የፈለገችውና የፈለገችውን አገኘችና፣ ወሰዳትና አገባች። ተነካች።
ሰርጉ ተከናውኖ…
ጫጉላው አብቦ…
ከስንት ያመለጠው ብር አምባር ተሰብሮ ጥቂት ቀናት ካለፉ በኋላ አሁንስ ይበቃታል ብዬ ደወልኩላት። እንዴት ሆንሽ….አጥሚትና ገንፎ የት ይዘን እንምጣ ልል እና ላጫውታት ደወልኩላት።
ብዙ ሳይጠራ አነሳች።
(በቅቷታል ማለት ነው…)
ሰላምታችን ሲያልቅ ወደ አንገብጋቢውጉዳይ ገባሁና..
‹‹እህስ…ነገሩስ? እንደጠበቅሸው አገኘሽው ወይስ ቅር አለሽ?›› አልኳት።
‹‹ቅር አለሽ ወይ? ወይ ጉድ…አንቺ….ስኳር መች ይጣፍጣል?!›› ብላ መለሰችልኝ።
ከአንጀቴ ሳቅሁ።
እንዲህ ትላለች ብዬ ስላልጠበቅኩም፣ ያ ከአመታት በፊት የሰማሁት ታሪክ ላይ ያለችው ልጅንም አስታወሰችኝና ሳቅሁ።
(ታሪኩ እንዲህ ነው። ልጅቱ ለስኳር ያላት ፍቅር የትዬሌሌ ነው። ‹‹ከስኳር የሚጥም፣ ከስኳር የሚጣፍጥ ነገር በአለም ላይ…አንዳችም ነገር የለም›› የምትል አይነት። እጮኛዋ ‹‹ተይ ተጋብተን ፍቅር ስንሰራ ኋላ ሃሳብሽን ትለውጫለሽ›› ቢላትም እሷ ግን ወይ ፍንክች! በኋላ ጋብቻው ተከናውኖ ባልና ሚስት ለመጀመሪያ ጊዜ ፍቅር እየሰሩ ወደ ማገባደዱ ሲደርሱ የሚስቱን ሁኔታ ያየው ባል በእጁ የጨበጠውን ስኳር በተከፈተ አፏ ውስጥ ሙጅር ያደርጋል። ይሄን ጊዜ የስኳር ነገር የማይሆንላት ሚስቱ ምን አለች? ‹‹ውይ ውዴ…! የምን አፈር ነው አፌ ውስጥ የጨመርከው?!››)
‹‹ወይ አንቺ…እና ታዲያ ይሄን ያህል ጊዜ በመቆየትሽ ትንሽ አልተቆጨሽም ታዲያ?›› አልኳት
ለመመለስ ሰከንድ አልፈጀባትም።
‹‹በጭራሽ! መቆየቴ መቼም አይቆጨኝም….ግን እንዲህ መሆኑን ግን ነገራችሁኝ አታውቁም….››
‹‹ ብንነግርሽስ ኖሮ?››
‹‹እሱስ ምንም ለውጥ አያመጣም ነበር…ያው ምናልባት ትንሽ…ይበልጥ ልጓጓ ግን እችል ነበር……..››
ወሬያችን አልቆ ስልኩን ስዘጋ በዚህ ሁሉም ሰው ሁሉንም ሰው ለመምሰል በሚሮጥበት ጊዜ፣ ለግል አቋምና እምነቷ ባላት ታማኝነት እንዳዲስ ተደነቅኩባት። ቀናሁባት።
ከዚህ ሁሉ በላይ ግን (በእኔ እና በአለም ስሌት) ዘግይታም ቢሆን አዳሜ የአለምን ምሬት የሚያጣፍጠው ፍቅርን በመስራት ስኳር መሆኑን በማወቋ ተደሰትኩላት።
🔘በሕይወት እምሻው🔘
አረ በቅንነት #Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰቦች ተባበሩ #Subscriber
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍81❤14😁6🥰1👏1
#ሀገሬ_ኀምሳ_እግር_ናት
የሀገሬ ወንዝ ዋናው ከነ ገባሩ ሲዘረዘር በንዴት እበግናለሁ።ፉት እንለው፣ ለቅለቅ እንልበት ውሃ ፍለጋ ከከተማ እስከ ገጠር
የምንማስነውን እኛን አስቤ ብግን እላለሁ፡፡
የሀገሬ ቀንድ ከብት ቁጥር፣ ከአፍሪካ አንደኛ” ተብሎ ሲጠራ በንዴት እንተከተካለሁ፡፡ ወተት እየተራጨን በማደግ ፈንታ የላም ወተት የዋልያ ወተት ይመስል ብርቅ የሆነብንን እኛን አስቤ ትክን እላለሁ፡፡
የሀገሬን ስፋት ሳስብ እናደዳለሁ፡፡ የእኔ የምንለው ክብሪት ሣጥን ታክል ቦታ አጥተን በየፊውዳሉ ቤት በጭሰኝነት የልጅነት ሀብታችንን ለምንገብረው እኛ ተቆርቁሬ፣ በንዴት እንገረገባለሁ፡፡
ይሄ ሁሉ እያላት ለእኛ ያልተረፈችው ሀገሬ፣ ሀብት እያላት ድሃ ናት፡፡ ሀገሬ ኀምሳ እግር ናት፡፡
ያ..... ሁሉ...... እግር እያለው ዘልአለም እንደሚድኸው ቆሞ እንደማያውቀው ኀምሳ እግር፡፡
ከምትድህበት አንስቶ በኀምሳውም እግሯ የሚያቆማት ጎበዝ እስክታገኝ ሀገሬ ኀምሳ እግር ናት፡፡
🔘በሕይወት እምሻው🔘
#Subscribe #Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰቦች ተባበሩ #Subscriber
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
የሀገሬ ወንዝ ዋናው ከነ ገባሩ ሲዘረዘር በንዴት እበግናለሁ።ፉት እንለው፣ ለቅለቅ እንልበት ውሃ ፍለጋ ከከተማ እስከ ገጠር
የምንማስነውን እኛን አስቤ ብግን እላለሁ፡፡
የሀገሬ ቀንድ ከብት ቁጥር፣ ከአፍሪካ አንደኛ” ተብሎ ሲጠራ በንዴት እንተከተካለሁ፡፡ ወተት እየተራጨን በማደግ ፈንታ የላም ወተት የዋልያ ወተት ይመስል ብርቅ የሆነብንን እኛን አስቤ ትክን እላለሁ፡፡
የሀገሬን ስፋት ሳስብ እናደዳለሁ፡፡ የእኔ የምንለው ክብሪት ሣጥን ታክል ቦታ አጥተን በየፊውዳሉ ቤት በጭሰኝነት የልጅነት ሀብታችንን ለምንገብረው እኛ ተቆርቁሬ፣ በንዴት እንገረገባለሁ፡፡
ይሄ ሁሉ እያላት ለእኛ ያልተረፈችው ሀገሬ፣ ሀብት እያላት ድሃ ናት፡፡ ሀገሬ ኀምሳ እግር ናት፡፡
ያ..... ሁሉ...... እግር እያለው ዘልአለም እንደሚድኸው ቆሞ እንደማያውቀው ኀምሳ እግር፡፡
ከምትድህበት አንስቶ በኀምሳውም እግሯ የሚያቆማት ጎበዝ እስክታገኝ ሀገሬ ኀምሳ እግር ናት፡፡
🔘በሕይወት እምሻው🔘
#Subscribe #Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰቦች ተባበሩ #Subscriber
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👏21👍14❤5
#አበጁ!
...
አዳምና ሄዋን፣ ከገነት ባይወጡ፣
ያቺን ዕፀ-በለስ፣ ፍሬዋን ባይውጡ፣
አይጥመኝም ነበር፣ ሕይወት እንዳሁኑ፣
ሳይሠሩ መቀለብ፣ መኖር ሳይቦዝኑ፡፡
እንኳን ተሳሳቱ፣ እኔስ ደስ ብሎኛል፣
ሳይሠራ ‘ሚበላ፣ ወትሮም ያቆስለኛል፡፡🤔
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
...
አዳምና ሄዋን፣ ከገነት ባይወጡ፣
ያቺን ዕፀ-በለስ፣ ፍሬዋን ባይውጡ፣
አይጥመኝም ነበር፣ ሕይወት እንዳሁኑ፣
ሳይሠሩ መቀለብ፣ መኖር ሳይቦዝኑ፡፡
እንኳን ተሳሳቱ፣ እኔስ ደስ ብሎኛል፣
ሳይሠራ ‘ሚበላ፣ ወትሮም ያቆስለኛል፡፡🤔
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍15
#ተገላቢጦሽ
ያኔ እኮ አብረሃም
ሲኖሮ በዚህ አለም
ሁሉ ተሟልቶለት
ምንም ሳይጎሎበት
ተናግሮ ነበረ
"ለዚች ትንሽ ጊዜ
ለ ስምንት መቶ አመት
ቤትማ አልቀልስም
ድንኳን መች አነሳት"
ዛሬ የሱ ዘሮች
ለሰማንያ አመት
ህንፃውን ገንብተው
ቤታቸውን ሰርተው
ሰፈሩንም አጥረው
ከድሀው ላይ ነጥቀው
.....ይጠባበቃሉ....
ከደጅ የቆመውን
ከዘጠኙ አንዱን፡፡
🎴ዘውዱ እርቅይሁን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ያኔ እኮ አብረሃም
ሲኖሮ በዚህ አለም
ሁሉ ተሟልቶለት
ምንም ሳይጎሎበት
ተናግሮ ነበረ
"ለዚች ትንሽ ጊዜ
ለ ስምንት መቶ አመት
ቤትማ አልቀልስም
ድንኳን መች አነሳት"
ዛሬ የሱ ዘሮች
ለሰማንያ አመት
ህንፃውን ገንብተው
ቤታቸውን ሰርተው
ሰፈሩንም አጥረው
ከድሀው ላይ ነጥቀው
.....ይጠባበቃሉ....
ከደጅ የቆመውን
ከዘጠኙ አንዱን፡፡
🎴ዘውዱ እርቅይሁን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍37❤7
#ዝምተኛ_ልቦች
አምነው የወደዱ
ወደው የተካዱ
ተክደው የራዱ
ፍርሃት አንሸራቶ ቁልቁል የጣላቸው
የብቸኛ ልቦች የትነው መውደቂያቸው?
የትነው መድረካቸው?
ማነው አጃቢያቸው?
እንዴት ነው ምታቸው
የተካዱ ልቦች አጋር የራቃቸው
የሚያቀነቅኑት ምንድን ነው ዜማቸው?
የተመረኮዙት እምነት ታጥፎባቸው
ድንገት የወደቁ ፍቅር ያዳጣቸው
ሚስጥር የሚያጋሩት ሰው የበደላቸው
ብቸኝነት ሰርጎ ብቻ ያስቀራቸው
ዝምተኛ ልቦች ምን ይሆን ቋንቋቸው?
ከየት ነው ጥሪያቸው?
በየት ነው ጉዟቸው?
የት ነው መድረሻቸው?
እንደ ሰብአሰገል ጠቅሶ የሚመራቸው
የቃተቱ ልቦች የታል ኮከባቸው?
መቼም ከአምላክ ትንፋሽ ከውሃ ከአፈሩ
ከእምንት እና እውነት ከፍቅር ሲሰሩ
ዝምተኛ ልቦች ጥንቱን ሲፈጥሩ
ተገፍትረው ወድቀው
ደቀው እንዳይቀሩ
በተስፋ ጸንተው ነው ዘላለም ሊኖሩ::
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አምነው የወደዱ
ወደው የተካዱ
ተክደው የራዱ
ፍርሃት አንሸራቶ ቁልቁል የጣላቸው
የብቸኛ ልቦች የትነው መውደቂያቸው?
የትነው መድረካቸው?
ማነው አጃቢያቸው?
እንዴት ነው ምታቸው
የተካዱ ልቦች አጋር የራቃቸው
የሚያቀነቅኑት ምንድን ነው ዜማቸው?
የተመረኮዙት እምነት ታጥፎባቸው
ድንገት የወደቁ ፍቅር ያዳጣቸው
ሚስጥር የሚያጋሩት ሰው የበደላቸው
ብቸኝነት ሰርጎ ብቻ ያስቀራቸው
ዝምተኛ ልቦች ምን ይሆን ቋንቋቸው?
ከየት ነው ጥሪያቸው?
በየት ነው ጉዟቸው?
የት ነው መድረሻቸው?
እንደ ሰብአሰገል ጠቅሶ የሚመራቸው
የቃተቱ ልቦች የታል ኮከባቸው?
መቼም ከአምላክ ትንፋሽ ከውሃ ከአፈሩ
ከእምንት እና እውነት ከፍቅር ሲሰሩ
ዝምተኛ ልቦች ጥንቱን ሲፈጥሩ
ተገፍትረው ወድቀው
ደቀው እንዳይቀሩ
በተስፋ ጸንተው ነው ዘላለም ሊኖሩ::
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍40👏6🥰3
ሰው የሚማረው፣
አንድም ከፊደል፣
አንድም ከመከራ ነው፤
አንድ ቃል ከፊደል ጥበብ፣
አንድ ቃል ከመከራ መዝገብ፣
አንድም በሳር "ሀ" ብሎ፣
አንድም በአሣር "ዋ" ብሎ፤
🎴ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አንድም ከፊደል፣
አንድም ከመከራ ነው፤
አንድ ቃል ከፊደል ጥበብ፣
አንድ ቃል ከመከራ መዝገብ፣
አንድም በሳር "ሀ" ብሎ፣
አንድም በአሣር "ዋ" ብሎ፤
🎴ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍21❤4
#የማይቻል_አንድ ነገር
እዉነት - ቤት ስትሰራ
ዉሸት - ላግዝ ካለች፣
ምስማር ካቀበለች፣
"ቤቱም አልተሰራ
እዉነትም አልኖረች።
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እዉነት - ቤት ስትሰራ
ዉሸት - ላግዝ ካለች፣
ምስማር ካቀበለች፣
"ቤቱም አልተሰራ
እዉነትም አልኖረች።
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍14👏4
የራሳችሁ ጉዳይ
እኔ ግን በዛ ሰሞን እፎይታ ተሰምቶኝ ነበር።
ሳልጠፋ ስለተገኘሁ ደስ ብሎኝ ነበር።
ሸሌ መሆን የሚያጓጓኝ ሰሞን፣ የከጃጀለኝ ሰሞን አልጋ አንጣፌ ሆኜ የምሰራበት ቡና ቤት ውስጥ ያሉ የሚቀርቡኝ ሸሌዎችን ገድልና እሮሮ በታላቅ ትኩረት፣ በቀን በቀን እሰማ ነበር። ዐይ ነበር።
በመሸ ቁጥር፣ በ'ኮንደም አድርግ አታድርግ" ጭቅጭቅ፣ በጭንቅላቱ ሳይሆን በእንትኑ የሚያስብ ወንድ ጋር እየተጣሉ በፖሊስ መዳኘት አለ፣ በሚሉት የማስፈራራያ ወሬዎች ተሰላችቼ ነበር።
"በጥፊ ካልመታሁሽ ደስ አይለኝም!" እያለ፣ "ከላይም ከታችም ከሚደበድበኝ ወንድ ጋር አድሬ የከፈለኝን ገንዘብ በድብደባ ያበጠ ፊቴን ለመታከም ማዋሉ መረረኝ" በሚሉ ሴቶች ዋይታ ተማርሬ ነበር።
እሺ...ዝርዝሩ ይቅርባችሁ እና እንዲያው በደፈናው፣ በጨለመ ቁጥር ባለተራ ወንድ እላዬ ላይ ስለማይደፋደፍብኝ የእውነት ደስ ብሎኝ ነበር። ከዚህ እጣ ፈንታ ለጥቂት ስላመለጥኩ፣ ደስ ብሎኝ ነበር።
እናም፣ ቀን ቀን እየጋለ አቅልጦ እንደው ውሃ ሊያፈሰኝ በሚዳዳው ሙቀት፣ ሲመሽ ሲመሽ ጥፍር አውጥቶ ሰውነቴን በሚቦጫጭቅ ብርድ ሳልማረር፣ እዛች ኮንቴነር ውስጥ ቁጭ ብዬ ጥልፊን እጠልፍ ነበር።
በየወሩ፤ "አሁንስ በቃኝ...እንኳን ትርፍ ሊያመጣ ለሚያከስር ስራ ደግሞ!" እያሉ ከጥልፉም ከዳንቴሉም ጎራ ወጥተው ሸሌነትን የመረጡ፣ ወይም ወደ ሸሌነት የተመለሱ ጓደኞቼን እያየሁ እንኳን በንፅህና ጎዳና ለመቀጠል ብዙ ለፋሁ።
ብዙ ታተርኩ፣ ብዙ ወጣሁ፣ ብዙ ወረድኩ።
ንጹህ ስራዬ ግን ከሰው በታች አደረገኝ እንጂ ከፍ አላደረገኝም። ሱቄን የሚደጎበኙ ወንዶች ሁሉ፣ ጥልፍ የጠለፍኩበትን አልጋ ልብስ ከመግዛት ይልቅ እኔን ጠልፈው አልጋ ውስጥ ማስገባት ነበር የሚታትሩት። በአምስተኛው ወር የከሸፈውን ፕሮጀክት ተከትሎ የከሸፈውን ህልሜን ኮንቴነሩ ውስጥ ጥዬ ወደ "ሰጥቶ የመቀበል" አለም መጣሁ።
የዛሬው ሰውዬ የመጀመርያዬ ነበር።
"ሀ" ዬ አንደኛ ክፍሌ።
ሳልዋረድ መብላት ብፈልግም፣ ሳልገላመጥ መኖር ብሻም የሞከርኩት ሁሉ አልሳካ ብሎኝ ሸሌ ሆንኩ።ባላያችሁትና ባልኖራችሁት ሕይወቴ ፈርዳችሁብኝ ብትሰድቡና ብትረግሙኝም፣
ዓለም ስትፈጠር ገና ያኔ ከገበሬነት በፊት፣ ከአናጢነት በፊት፣ ከአስተማሪነት በፊት፣ ከምንም አይነት ሥራ በፊት፣ "ሲወርድና ሲዋረድ" እዚህ የደረሰውን ሥራዬ ግን በእርግማንና በስድብ ወጀብ ከምድረ ገፅ እንደማይጠፋ ታውቁታላችሁ
ምክንያቱም፣ በጨለማ ዝቅ ብዬ ያገኘሁት ገንዘብ እጄን የሚጠብቁ ቤተሰቦቼን ከፍ እንደሚያደርግልኝ አውቃለሁ።
ቀን የተጠየፉኝ ሰዎች ማታ እንደሚያመልኩኝ አውቃለሁ።
ቆሻሻው ስራዬ ንጹሕ እንጀራ እንደሚገዛ አውቃለሁ።
ስለዚህ፣ ወንድ ሊሆን የሚመጣን ወንድ ሴት ሆኜ እያስተናገድኩ እንደ ሰው እኖራለሁ። ሸሌ ነኝ።ከዛሬ ጀምሮ ሸሌ ነኝ።
✨አለቀ✨
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እኔ ግን በዛ ሰሞን እፎይታ ተሰምቶኝ ነበር።
ሳልጠፋ ስለተገኘሁ ደስ ብሎኝ ነበር።
ሸሌ መሆን የሚያጓጓኝ ሰሞን፣ የከጃጀለኝ ሰሞን አልጋ አንጣፌ ሆኜ የምሰራበት ቡና ቤት ውስጥ ያሉ የሚቀርቡኝ ሸሌዎችን ገድልና እሮሮ በታላቅ ትኩረት፣ በቀን በቀን እሰማ ነበር። ዐይ ነበር።
በመሸ ቁጥር፣ በ'ኮንደም አድርግ አታድርግ" ጭቅጭቅ፣ በጭንቅላቱ ሳይሆን በእንትኑ የሚያስብ ወንድ ጋር እየተጣሉ በፖሊስ መዳኘት አለ፣ በሚሉት የማስፈራራያ ወሬዎች ተሰላችቼ ነበር።
"በጥፊ ካልመታሁሽ ደስ አይለኝም!" እያለ፣ "ከላይም ከታችም ከሚደበድበኝ ወንድ ጋር አድሬ የከፈለኝን ገንዘብ በድብደባ ያበጠ ፊቴን ለመታከም ማዋሉ መረረኝ" በሚሉ ሴቶች ዋይታ ተማርሬ ነበር።
እሺ...ዝርዝሩ ይቅርባችሁ እና እንዲያው በደፈናው፣ በጨለመ ቁጥር ባለተራ ወንድ እላዬ ላይ ስለማይደፋደፍብኝ የእውነት ደስ ብሎኝ ነበር። ከዚህ እጣ ፈንታ ለጥቂት ስላመለጥኩ፣ ደስ ብሎኝ ነበር።
እናም፣ ቀን ቀን እየጋለ አቅልጦ እንደው ውሃ ሊያፈሰኝ በሚዳዳው ሙቀት፣ ሲመሽ ሲመሽ ጥፍር አውጥቶ ሰውነቴን በሚቦጫጭቅ ብርድ ሳልማረር፣ እዛች ኮንቴነር ውስጥ ቁጭ ብዬ ጥልፊን እጠልፍ ነበር።
በየወሩ፤ "አሁንስ በቃኝ...እንኳን ትርፍ ሊያመጣ ለሚያከስር ስራ ደግሞ!" እያሉ ከጥልፉም ከዳንቴሉም ጎራ ወጥተው ሸሌነትን የመረጡ፣ ወይም ወደ ሸሌነት የተመለሱ ጓደኞቼን እያየሁ እንኳን በንፅህና ጎዳና ለመቀጠል ብዙ ለፋሁ።
ብዙ ታተርኩ፣ ብዙ ወጣሁ፣ ብዙ ወረድኩ።
ንጹህ ስራዬ ግን ከሰው በታች አደረገኝ እንጂ ከፍ አላደረገኝም። ሱቄን የሚደጎበኙ ወንዶች ሁሉ፣ ጥልፍ የጠለፍኩበትን አልጋ ልብስ ከመግዛት ይልቅ እኔን ጠልፈው አልጋ ውስጥ ማስገባት ነበር የሚታትሩት። በአምስተኛው ወር የከሸፈውን ፕሮጀክት ተከትሎ የከሸፈውን ህልሜን ኮንቴነሩ ውስጥ ጥዬ ወደ "ሰጥቶ የመቀበል" አለም መጣሁ።
የዛሬው ሰውዬ የመጀመርያዬ ነበር።
"ሀ" ዬ አንደኛ ክፍሌ።
ሳልዋረድ መብላት ብፈልግም፣ ሳልገላመጥ መኖር ብሻም የሞከርኩት ሁሉ አልሳካ ብሎኝ ሸሌ ሆንኩ።ባላያችሁትና ባልኖራችሁት ሕይወቴ ፈርዳችሁብኝ ብትሰድቡና ብትረግሙኝም፣
ዓለም ስትፈጠር ገና ያኔ ከገበሬነት በፊት፣ ከአናጢነት በፊት፣ ከአስተማሪነት በፊት፣ ከምንም አይነት ሥራ በፊት፣ "ሲወርድና ሲዋረድ" እዚህ የደረሰውን ሥራዬ ግን በእርግማንና በስድብ ወጀብ ከምድረ ገፅ እንደማይጠፋ ታውቁታላችሁ
ምክንያቱም፣ በጨለማ ዝቅ ብዬ ያገኘሁት ገንዘብ እጄን የሚጠብቁ ቤተሰቦቼን ከፍ እንደሚያደርግልኝ አውቃለሁ።
ቀን የተጠየፉኝ ሰዎች ማታ እንደሚያመልኩኝ አውቃለሁ።
ቆሻሻው ስራዬ ንጹሕ እንጀራ እንደሚገዛ አውቃለሁ።
ስለዚህ፣ ወንድ ሊሆን የሚመጣን ወንድ ሴት ሆኜ እያስተናገድኩ እንደ ሰው እኖራለሁ። ሸሌ ነኝ።ከዛሬ ጀምሮ ሸሌ ነኝ።
✨አለቀ✨
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍56😢17🔥10👎3👏2❤1😁1
መቼስ በፕሮግራሙ ትንሽ ግራ ሳትጋቡ አትቀሩም..ይሄ የመጨረሻ ፕሮግራማችን የቀደሙት ፕሮግራሞች ቅጥያ ነው ፡፡እንግዲህ የያዝነው ትውልድን በአዲስ መልኩ መገንባት አይደል..ለዛ ደግሞ ቤተሰብ መመስረት ዋናው መሰረት ነው፡፡ እነዚህ አራት ጥንዶች የማህበሩ መስራቾች እና አባላት ናቸው፡፡ እንደምታዬቸው ሁሉም ጥንዶች ለየራሳቸው ልጅ ለማሳደግ ተረክበዋል፤ ከዛም በተጨማሪም ለሰርግ የበጀቱትን በጀት ለድርጅታችን ገቢ
አድርገዋል..ዶ/ር ሶፊያና ፕ/ዬሴፍ 400 ሺ ብር፣አቶ ታዲዬስ እና ወ/ሮ ርብቃ 1ዐዐ ሺ ብር
፣አቶ ኤልያስ እና ወ/ሮ ፎዚያ 5ዐ ሺ ብር፣በተመሳሳይ አቶ ዓላዛር እና ወ/ሮ ፅዬን 5ዐ ሺ ብር በጠቅላላው 6ዐዐ ሺ ገቢ በማድረጋቸው እኛስ ለምን ጋብቻቸውን በዚህ ፕሮግራም ላይ እውቅና አንሰጠውም በማለት
ነው እንዲህ ፊታችሁ ያቆምናቸው፡፡ ስለዚህ አንዴ በነ ሄለን ሙዚቃ ሙሽራዬ እያልን ወደ
መውጫቸው እንሸኛቸዋለን ….በዛውም ፕሮግራማችንን እናጠናቅቃለን፡፡
እናመሰግናለን፡፡
😔ተፈፀመ😔
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ። ድርሰቱ ሲያልቅ 500 #Subscriber እንገባለን ብዬ ነበር አልተሳካም አሁንም ቢሆን ድርሰቱ የተመቸው ሌላ ድርሰት #እንዲቀጥል ፍላጎት ያለው ቻናሉን #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አድርገዋል..ዶ/ር ሶፊያና ፕ/ዬሴፍ 400 ሺ ብር፣አቶ ታዲዬስ እና ወ/ሮ ርብቃ 1ዐዐ ሺ ብር
፣አቶ ኤልያስ እና ወ/ሮ ፎዚያ 5ዐ ሺ ብር፣በተመሳሳይ አቶ ዓላዛር እና ወ/ሮ ፅዬን 5ዐ ሺ ብር በጠቅላላው 6ዐዐ ሺ ገቢ በማድረጋቸው እኛስ ለምን ጋብቻቸውን በዚህ ፕሮግራም ላይ እውቅና አንሰጠውም በማለት
ነው እንዲህ ፊታችሁ ያቆምናቸው፡፡ ስለዚህ አንዴ በነ ሄለን ሙዚቃ ሙሽራዬ እያልን ወደ
መውጫቸው እንሸኛቸዋለን ….በዛውም ፕሮግራማችንን እናጠናቅቃለን፡፡
እናመሰግናለን፡፡
😔ተፈፀመ😔
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ። ድርሰቱ ሲያልቅ 500 #Subscriber እንገባለን ብዬ ነበር አልተሳካም አሁንም ቢሆን ድርሰቱ የተመቸው ሌላ ድርሰት #እንዲቀጥል ፍላጎት ያለው ቻናሉን #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍85👏18❤13🔥11🥰8