#የወርቅ_በርጩማውን_ፍስጋ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በእንዳለጌታ_ከበደ
፡
፡
(በ1996 የተፃፈ ነው ውድ አንባብያን አንዳንዴ አሁን ላይ ቋጥኝ የሚሆኑብን ነገሮች ቀለል ተደርገው ሲገለፁ ግር እንዳይላችሁ መልካም ንባብ።)
----------=======----------========
የቋንቋ መምህርት ነኝ ...
አንዳንድ ሰው፣ ጥዋት ከእንቅልፉ እንደነቃ 'ምላሱ ላይ የገባ'ን ዘፈን ቀኑን ሙሉ ሲያንጎራጉረው ይውላል፡፡
በእኔ አእምሮ ውስጥ ደግሞ ጥዋት የሰረገ ብሂል አብሮኝ ውሉ ያመሻል፡፡ ዳኛቸው ወርቁ ከፃፈው «አደፍርስ»
ልቦለድ መፅሐፍ ላይ ያገኘሁት አንድ አገላለጽ በውስጤ ታትሞ ቀርቷል፡፡
«... ያቺ በሌላዋ አገር የምትጣደፈው፣
የምትፍለቀለቀው፣ የምትንቦለቦለው ሕይወት እዚህ እፎይ ብላለች። በእርጋታ ፣ በዝግታ ታምማለች በተገማሽረ መስክ ውስጥ እንደሚብሰከሰክ ውሃ ... »
ሰሞኑን ከምንጊዜውም በላይ «ስለሀገር ጉዳይ» ያሳስበኝ ጀምሯል።የብሶቴ ምንጭ ግን ይሄ ብቻ አይደለም። ምን እንደሆነ እኔም አላውቀውም።
ሰራተኛዬ ዘሪቱ ልትሄድብኝ ነው ብዬ ስለሰጋሁ ሳይሆን አይቀርም። ወይም ደግሞ የታናሽ እህቴ የአስቴር እጮኛ 'አሜሪካ ሄድኩ' ይበል እንጂ ደቡብ አፍሪካ ገብቶ ቀበቶ በመሸጥ እንደሚተዳደር ከሚቀርቡት ሰዎች
በመስማቴም ይሆናል ወይም ደግሞ ባለቤቴ ነፍሱን ይማረውና ይሰራበት የነበረው ድርጅት 'ለሟቹ ቤተሰቦች' ብሎ የሠጠኝን ገንዘብ ምናባቴ አድርጌ የረባ
ነገር እንደምፈይድበት ግራ ስለገባኝ ይሆናል። ብቻ የሆነ ነገር ሆኛለሁ፣ ወይም ልሆን ነው።
ዘሪቱ ከሄደችብኝ ቤቴን ማን ቀጥ አድርጎ
ይይዝልኛል? ሁለቱ ልጆቼ ትምህርታቸው ላይ እንዲያተኩሩ እፈልጋለሁ። የትምህርታቸው ውጤት ዝቅ ቢል የባለቤቴ መንፈስ እንደሚከፋብኝ ስለሚሰማኝ ብቻ አይደለም። አለጊዜያቸው ለምን ከሰውነት ተራ
ይውጡ? እኔ እናታቸው እስካለሁ ድረስ! ... የስምንት ዓመት ወንድና የአምስት ዓመት ሴት ልጆች ያለ አባት
ማሳደግ ይከብድ ይሆን? አላውቅም። . .
ዘሪቱ እኔ ቤት በሰራተኛነት ተቀጥራ መስራት ከጀመረች አራት አመት ሆኗታል፡፡ ያኔ አስቴር ወደ ቤይሩት ለመሄድ ጓዝ ጉዝጓዟን መጠቅለል በጀመረችበት ሰሞን ነው ዘሪቱን ያገኘኋት- ያለተያዥም የቀጠርኩዋት። አመንኩዋት- ታመነችልኝም!
«ባለቤቷን ስለማታምነው ነው ይህቺን መልከ ጥፉ፣ይቺን ከጨለማ በባሰ ሁኔታ የጠቆረች ሴት ለሰራተኝነት
የቀጠረችው! . . .» ተብሎ ተወራ፡፡
ባለቤቴ ሾፌር ነበር፡፡ በአንድ የግል ድርጅት ውስጥ የሥራ አስኪያጁን መኪና ነበር የሚነዳው። ስለ አደጋወም ሆነ ሊሞት ሲል አይቼበት የነበረውን ስቃይ
ላለማስታወስ ለራሴ ቃል ከገባህ: ሁለት ዓመት አልፎኛል።
ጠመዝማዛወና ' እንኩዋንስ ሰወ ዝንጀሮ
አይወጣውም' የተባለለት የአላማጣ መንገድ ለስንቶች ህይወት ማለፍ ተጠያቂ ሆኖ ይሆን?! ... አለማሰብ
ነው የሚሻለው!
*
ከወራት በፊት አንዱን ቀን ፡ የባለቤቴን
የኢንሹራንስ ጉዳይ ዳር ለማድረስ ስሯሯጥ ደካክሞኝ ነበር የዋልኩት። መላ ሰውነቴ ውሃ ውስጥ እንደከረመ
ሳሙና ተልፈስፍሶ ነበር፡፡
« እቴትዬ አለችኝ ዘሪቱ።
« አቤት!»
« አይታዘቡኝና አንድ ነገር ባስቸግርዎትስ?!»
« ምን ሆነሻል?›
«ለእኔ የእርስዎን ያህል ክብር ሰጥቶ የሚያነጋግረኝ የለም! . . ከዚህ ቤት ወጥቼ ሌላ ስራ ባልጀምር ደስ ይለኛል።
ግን የነር ጉዳይ ሆኖ . . ."
«ደሞዝ አነሰኝ ለማለት ነው ይህ ሁሉ ዳርዳርታ?»
ደንገጥ ብላ «ኧረ እቴትዬ ክፍያው አያንሰኝም! ...ግን ታናሽ ወንድሜ ገጠር ከሚሆን እዚህ ሆኖ ቢሰራ ይሻለዋል:: እኔስ እስከመቼ ድረስ የሰራሁትን ሁሉ
ጥቂት ብር ብቻ አስቀርቼ ወደነሱ ልላክ?! . . .)
«ምንድነው የወንድምሽ ስራ?»
«ምንም!››
«እንዴት ምንም?!»
«በአምልኮ ነው ጊዜውን የሚያሳልፈው!»
«በአምልኮ?»
«አዎ! በተወለድኩበት አካባቢ መድረሻውን የማላውቀው አንድ ወንዝ አለ ... 'የዌራ እንደት' ብለው የሚጠሩዋት አምላክ ትኖርበታለች:: ከክፉ ነገር እንድትጠብቃቸው ... ከብቶቻቸውንም በውሃ ሙላት
ከመወሰድ እንድትጠብቅላቸው፣ ከክረምት በቀር ከዓመት እስከ ዓመት
ይገብሩላታል፡፡ ለዌራ እንደት' ክብር
ተብሎ በግ ይታረዳል፡፡ በአዝመራ ጊዜ ነጭ ገብስ በስሟ ይዘራል፡፡ ስብሉ በደረሰ ጊዜ ከሌላ ጥሬ ጋር ሳይደባለቅ
በጥንቃቄ ይቀመጣል፡፡ የግብር ወቅት ሲደርስ 'ለዌራ እንደት' ይወሰድላታል፡፡ ኧረ ብዘ ነገር ነው የሚደረግላት» አለችኝ ዘሪቱ፡፡
«እና ወንድምሽ ምን ለማግኘት ነው ጣዖቷን የሚያመልካት?» አልኩዋት ራሷን ከእምነቱ ተከታዮች ለማራቅ የምታደርገውን ጥረት ከንግግሯ እየተረዳሁ።
«የወርቅ በርጩማ ለማግኘት»
«አልገባኝም»
« ... ወንዙ ውስጥ ግዙፍ የሆነ የወርቅ በርጩማ አለ ይላሉ ወንዙ እምብርት ላይ ሁልጊዜ የሚሽከረከር ነገር አለ፡፡ እሱጋ ነው ያለው ይላሉ:: ውሃው ውስጥ
ገብተው ለማውጣት የሞከሩ ሁሉ ህይወታቸው አልፏል፡፡ዋናተኞችም ቢሆኑ! ... ከልብ 'የዌራ እንደትን ያመለከ
ሰው የወርቅ በርጩማውን ለግሉ ያደርገዋል ተብሎ ይታመናል፡፡»
«አይ አለማወቅ! ይሄማ ከሁዋለኞች ሁሉ ሁዋላ የሚያስቀር አመለካከት አይደል?»
«እንግዲህ፣ እንደዚያ ነው የሚያምኑት - ወንድሜ ደግሞ የሁላችንም ህይወት ሊለወጥ የሚችለው፣
'በርጩማወ' በእጄ ሲገባ ነው ብሎ ያምናል፡፡የወገኖቹን የእጅ ሙያ ወርሶ ልክ እንደናቴ ወንድሞች መንቀሳቀስ ሲገባው! ... በዚያ ላይ በቅርቡ ማግባት
ይፈልጋል»
«እና አሁን ምን አስበሻል? .. .»
«እዚህ ይምጣ፡፡ እንደኔ የማታ ትምህርት ጀምሮ ቁጥርና ፊደል ይለይ! የስራ ሰው ይሁን እስኪደራጅ ድረስ ብዙ ጊዜ ስለሚፈጅበት ልረዳው እፈልጋለሁ፡፡ ለሆዱ የቀን ስራ እየሰራ ለራሱ ይወቅበት!
የአንድ ወር ደሞዝ ቅድሚያ እንዲሰጠኝ ነወ፡ የምለምንዎት....."
ደስ አለችኝ! « ብርቱ ነሽ እኮ የኔ ልጅ! እኔ ደግሞ አንቺን አግዛለሁ» አልኳት።
አቤት! ያን ሰሞን ይሄ «የወርቅ በርጩማ» ነገር እንዴት መዝናኛ ሆኖን ነበር? ለእህቴ ለአስቴር በስልክ
ስነግራት «አትቀልጅ! መጥቼ እድሌን ልሞክር እንዴ? ስትል ቀለደች፡፡ እጮኛዋ ግን ምንም ስሜት አልሰጠውም።
የእህቴን እጮኛ የእህቴን ያህል አውቀዋለሁ።ከወር በፊት፣ እኔ ወደማስተምርበት መለስተኛ
ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መጥቶ፣
"ውጭ አገር ልሄድ ነው!» አለኝ «አሜሪካ . . .)ደነገጥኩ፡፡ «እናንተ ልጆች ምን እየሆናችሁ ነው?! አብዳችኋል? አስቴር ቤይሩት ሄደች:: የሄደችው
የሁለታችሁን የተሻለ መኖር የሚያስችላችሁን አቅም ለማጎልበት ነው።ያለን ይበቃናል ፍቅራችን ያኖረናል ማለት ሲገባህ ያንተም ልብ እንደ ጠበል ዕቃ ውጭ ማደር ይጀምር?!...ብዬ ተቆጣሁት።
ጥቁር ድንጋይ ላይ ውሃ የማፍሰስ ያህል ነበር! አስቴርና እጮኛዋ ከተማሪነት ዘመናቸው ጀምሮ አብረው ሲሆኑ መለያየት የሚባል ዕጣ፣ አለመስማማት የሚባል ጣጣ በሁለታቸው መሃከል መንገድ አልዘረጋም...አንድ
ቀን አስቴር 'እቴት፣ ወደ ቤይሩት ልበር ነው።የምነግርሽ እንድታውቂው ነው:: መሄድ እንዳለብኝ ከወሰንኩ በኋላ ጓደኛዬን ለማሳመን ብዙ ሰዓት ፈጅቶብኛል፡፡ ብዙ ቀናት ልበልሽ እንጂ!
እና ላንቺ እያማከርኩሽ ሳይሆን ውሳኔዬን እየነገርኩሽ ስለሆነ አለመሄድ እንደሚሻል በማሳመን እንዳታደክሚኝ አለቺኝ።
'ገንዘብ ከየት ይመጣል አስቴር?!'
'ለመሄጃ?!'
'አዎ!'
'ጓደኛዬ ከወላጆቹ የወረሰውን ቤት በኮንትራት አከራይቶታል፡፡ ከእሱ እወስዳለሁ።የምሄደው ለአንድ
ለሁለት ዓመት ያህል ነው።ሰራርቼ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በእንዳለጌታ_ከበደ
፡
፡
(በ1996 የተፃፈ ነው ውድ አንባብያን አንዳንዴ አሁን ላይ ቋጥኝ የሚሆኑብን ነገሮች ቀለል ተደርገው ሲገለፁ ግር እንዳይላችሁ መልካም ንባብ።)
----------=======----------========
የቋንቋ መምህርት ነኝ ...
አንዳንድ ሰው፣ ጥዋት ከእንቅልፉ እንደነቃ 'ምላሱ ላይ የገባ'ን ዘፈን ቀኑን ሙሉ ሲያንጎራጉረው ይውላል፡፡
በእኔ አእምሮ ውስጥ ደግሞ ጥዋት የሰረገ ብሂል አብሮኝ ውሉ ያመሻል፡፡ ዳኛቸው ወርቁ ከፃፈው «አደፍርስ»
ልቦለድ መፅሐፍ ላይ ያገኘሁት አንድ አገላለጽ በውስጤ ታትሞ ቀርቷል፡፡
«... ያቺ በሌላዋ አገር የምትጣደፈው፣
የምትፍለቀለቀው፣ የምትንቦለቦለው ሕይወት እዚህ እፎይ ብላለች። በእርጋታ ፣ በዝግታ ታምማለች በተገማሽረ መስክ ውስጥ እንደሚብሰከሰክ ውሃ ... »
ሰሞኑን ከምንጊዜውም በላይ «ስለሀገር ጉዳይ» ያሳስበኝ ጀምሯል።የብሶቴ ምንጭ ግን ይሄ ብቻ አይደለም። ምን እንደሆነ እኔም አላውቀውም።
ሰራተኛዬ ዘሪቱ ልትሄድብኝ ነው ብዬ ስለሰጋሁ ሳይሆን አይቀርም። ወይም ደግሞ የታናሽ እህቴ የአስቴር እጮኛ 'አሜሪካ ሄድኩ' ይበል እንጂ ደቡብ አፍሪካ ገብቶ ቀበቶ በመሸጥ እንደሚተዳደር ከሚቀርቡት ሰዎች
በመስማቴም ይሆናል ወይም ደግሞ ባለቤቴ ነፍሱን ይማረውና ይሰራበት የነበረው ድርጅት 'ለሟቹ ቤተሰቦች' ብሎ የሠጠኝን ገንዘብ ምናባቴ አድርጌ የረባ
ነገር እንደምፈይድበት ግራ ስለገባኝ ይሆናል። ብቻ የሆነ ነገር ሆኛለሁ፣ ወይም ልሆን ነው።
ዘሪቱ ከሄደችብኝ ቤቴን ማን ቀጥ አድርጎ
ይይዝልኛል? ሁለቱ ልጆቼ ትምህርታቸው ላይ እንዲያተኩሩ እፈልጋለሁ። የትምህርታቸው ውጤት ዝቅ ቢል የባለቤቴ መንፈስ እንደሚከፋብኝ ስለሚሰማኝ ብቻ አይደለም። አለጊዜያቸው ለምን ከሰውነት ተራ
ይውጡ? እኔ እናታቸው እስካለሁ ድረስ! ... የስምንት ዓመት ወንድና የአምስት ዓመት ሴት ልጆች ያለ አባት
ማሳደግ ይከብድ ይሆን? አላውቅም። . .
ዘሪቱ እኔ ቤት በሰራተኛነት ተቀጥራ መስራት ከጀመረች አራት አመት ሆኗታል፡፡ ያኔ አስቴር ወደ ቤይሩት ለመሄድ ጓዝ ጉዝጓዟን መጠቅለል በጀመረችበት ሰሞን ነው ዘሪቱን ያገኘኋት- ያለተያዥም የቀጠርኩዋት። አመንኩዋት- ታመነችልኝም!
«ባለቤቷን ስለማታምነው ነው ይህቺን መልከ ጥፉ፣ይቺን ከጨለማ በባሰ ሁኔታ የጠቆረች ሴት ለሰራተኝነት
የቀጠረችው! . . .» ተብሎ ተወራ፡፡
ባለቤቴ ሾፌር ነበር፡፡ በአንድ የግል ድርጅት ውስጥ የሥራ አስኪያጁን መኪና ነበር የሚነዳው። ስለ አደጋወም ሆነ ሊሞት ሲል አይቼበት የነበረውን ስቃይ
ላለማስታወስ ለራሴ ቃል ከገባህ: ሁለት ዓመት አልፎኛል።
ጠመዝማዛወና ' እንኩዋንስ ሰወ ዝንጀሮ
አይወጣውም' የተባለለት የአላማጣ መንገድ ለስንቶች ህይወት ማለፍ ተጠያቂ ሆኖ ይሆን?! ... አለማሰብ
ነው የሚሻለው!
*
ከወራት በፊት አንዱን ቀን ፡ የባለቤቴን
የኢንሹራንስ ጉዳይ ዳር ለማድረስ ስሯሯጥ ደካክሞኝ ነበር የዋልኩት። መላ ሰውነቴ ውሃ ውስጥ እንደከረመ
ሳሙና ተልፈስፍሶ ነበር፡፡
« እቴትዬ አለችኝ ዘሪቱ።
« አቤት!»
« አይታዘቡኝና አንድ ነገር ባስቸግርዎትስ?!»
« ምን ሆነሻል?›
«ለእኔ የእርስዎን ያህል ክብር ሰጥቶ የሚያነጋግረኝ የለም! . . ከዚህ ቤት ወጥቼ ሌላ ስራ ባልጀምር ደስ ይለኛል።
ግን የነር ጉዳይ ሆኖ . . ."
«ደሞዝ አነሰኝ ለማለት ነው ይህ ሁሉ ዳርዳርታ?»
ደንገጥ ብላ «ኧረ እቴትዬ ክፍያው አያንሰኝም! ...ግን ታናሽ ወንድሜ ገጠር ከሚሆን እዚህ ሆኖ ቢሰራ ይሻለዋል:: እኔስ እስከመቼ ድረስ የሰራሁትን ሁሉ
ጥቂት ብር ብቻ አስቀርቼ ወደነሱ ልላክ?! . . .)
«ምንድነው የወንድምሽ ስራ?»
«ምንም!››
«እንዴት ምንም?!»
«በአምልኮ ነው ጊዜውን የሚያሳልፈው!»
«በአምልኮ?»
«አዎ! በተወለድኩበት አካባቢ መድረሻውን የማላውቀው አንድ ወንዝ አለ ... 'የዌራ እንደት' ብለው የሚጠሩዋት አምላክ ትኖርበታለች:: ከክፉ ነገር እንድትጠብቃቸው ... ከብቶቻቸውንም በውሃ ሙላት
ከመወሰድ እንድትጠብቅላቸው፣ ከክረምት በቀር ከዓመት እስከ ዓመት
ይገብሩላታል፡፡ ለዌራ እንደት' ክብር
ተብሎ በግ ይታረዳል፡፡ በአዝመራ ጊዜ ነጭ ገብስ በስሟ ይዘራል፡፡ ስብሉ በደረሰ ጊዜ ከሌላ ጥሬ ጋር ሳይደባለቅ
በጥንቃቄ ይቀመጣል፡፡ የግብር ወቅት ሲደርስ 'ለዌራ እንደት' ይወሰድላታል፡፡ ኧረ ብዘ ነገር ነው የሚደረግላት» አለችኝ ዘሪቱ፡፡
«እና ወንድምሽ ምን ለማግኘት ነው ጣዖቷን የሚያመልካት?» አልኩዋት ራሷን ከእምነቱ ተከታዮች ለማራቅ የምታደርገውን ጥረት ከንግግሯ እየተረዳሁ።
«የወርቅ በርጩማ ለማግኘት»
«አልገባኝም»
« ... ወንዙ ውስጥ ግዙፍ የሆነ የወርቅ በርጩማ አለ ይላሉ ወንዙ እምብርት ላይ ሁልጊዜ የሚሽከረከር ነገር አለ፡፡ እሱጋ ነው ያለው ይላሉ:: ውሃው ውስጥ
ገብተው ለማውጣት የሞከሩ ሁሉ ህይወታቸው አልፏል፡፡ዋናተኞችም ቢሆኑ! ... ከልብ 'የዌራ እንደትን ያመለከ
ሰው የወርቅ በርጩማውን ለግሉ ያደርገዋል ተብሎ ይታመናል፡፡»
«አይ አለማወቅ! ይሄማ ከሁዋለኞች ሁሉ ሁዋላ የሚያስቀር አመለካከት አይደል?»
«እንግዲህ፣ እንደዚያ ነው የሚያምኑት - ወንድሜ ደግሞ የሁላችንም ህይወት ሊለወጥ የሚችለው፣
'በርጩማወ' በእጄ ሲገባ ነው ብሎ ያምናል፡፡የወገኖቹን የእጅ ሙያ ወርሶ ልክ እንደናቴ ወንድሞች መንቀሳቀስ ሲገባው! ... በዚያ ላይ በቅርቡ ማግባት
ይፈልጋል»
«እና አሁን ምን አስበሻል? .. .»
«እዚህ ይምጣ፡፡ እንደኔ የማታ ትምህርት ጀምሮ ቁጥርና ፊደል ይለይ! የስራ ሰው ይሁን እስኪደራጅ ድረስ ብዙ ጊዜ ስለሚፈጅበት ልረዳው እፈልጋለሁ፡፡ ለሆዱ የቀን ስራ እየሰራ ለራሱ ይወቅበት!
የአንድ ወር ደሞዝ ቅድሚያ እንዲሰጠኝ ነወ፡ የምለምንዎት....."
ደስ አለችኝ! « ብርቱ ነሽ እኮ የኔ ልጅ! እኔ ደግሞ አንቺን አግዛለሁ» አልኳት።
አቤት! ያን ሰሞን ይሄ «የወርቅ በርጩማ» ነገር እንዴት መዝናኛ ሆኖን ነበር? ለእህቴ ለአስቴር በስልክ
ስነግራት «አትቀልጅ! መጥቼ እድሌን ልሞክር እንዴ? ስትል ቀለደች፡፡ እጮኛዋ ግን ምንም ስሜት አልሰጠውም።
የእህቴን እጮኛ የእህቴን ያህል አውቀዋለሁ።ከወር በፊት፣ እኔ ወደማስተምርበት መለስተኛ
ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መጥቶ፣
"ውጭ አገር ልሄድ ነው!» አለኝ «አሜሪካ . . .)ደነገጥኩ፡፡ «እናንተ ልጆች ምን እየሆናችሁ ነው?! አብዳችኋል? አስቴር ቤይሩት ሄደች:: የሄደችው
የሁለታችሁን የተሻለ መኖር የሚያስችላችሁን አቅም ለማጎልበት ነው።ያለን ይበቃናል ፍቅራችን ያኖረናል ማለት ሲገባህ ያንተም ልብ እንደ ጠበል ዕቃ ውጭ ማደር ይጀምር?!...ብዬ ተቆጣሁት።
ጥቁር ድንጋይ ላይ ውሃ የማፍሰስ ያህል ነበር! አስቴርና እጮኛዋ ከተማሪነት ዘመናቸው ጀምሮ አብረው ሲሆኑ መለያየት የሚባል ዕጣ፣ አለመስማማት የሚባል ጣጣ በሁለታቸው መሃከል መንገድ አልዘረጋም...አንድ
ቀን አስቴር 'እቴት፣ ወደ ቤይሩት ልበር ነው።የምነግርሽ እንድታውቂው ነው:: መሄድ እንዳለብኝ ከወሰንኩ በኋላ ጓደኛዬን ለማሳመን ብዙ ሰዓት ፈጅቶብኛል፡፡ ብዙ ቀናት ልበልሽ እንጂ!
እና ላንቺ እያማከርኩሽ ሳይሆን ውሳኔዬን እየነገርኩሽ ስለሆነ አለመሄድ እንደሚሻል በማሳመን እንዳታደክሚኝ አለቺኝ።
'ገንዘብ ከየት ይመጣል አስቴር?!'
'ለመሄጃ?!'
'አዎ!'
'ጓደኛዬ ከወላጆቹ የወረሰውን ቤት በኮንትራት አከራይቶታል፡፡ ከእሱ እወስዳለሁ።የምሄደው ለአንድ
ለሁለት ዓመት ያህል ነው።ሰራርቼ
👍3😁1
#የወርቅ_በርጩማውን_ፍስጋ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በእንዳለጌታ_ከበደ
« . . . የአስቴርን ስቃይ ልቀንስ ብዬኮ ነው።
አስቴር እስክትመጣ ድረስ ምን ያህል ጊዜ ይፈጅባታል?አይታወቅም፡፡ ለሁለት ዓመት ብዬ አስምዬ ሸኘኋት!
ምላ ተገዝታ ሆነልኝም አልሆነልኝም ባልከኝ ጊዜ እመለሳለሁ አለችኝ።የት አለች ታዲያ?» አለኝ በመነጫነጭ፡፡
«እኛ አስቸግረናት እኮ ነው! ... ወላጆቼ ናቸው የመምጫ ጊዜዋን ያራዘሙት። እሷ ስትሄድ የችግር ቀዳዳዎቻቸው በእጥፍ በዙ» አልኩት።
«አንቺ የማታውቂው ብዙ ነገር አለ፡፡ አስቴር ጫንቃዋ መሸከም ከሚችለው በላይ ጭነት እያረፈባት እንደሆነ እያወቅሁ ዝም ማለት እንዴት ያስችለኛል?!ፍቅር ማለት ምንድነው?!»
አስቴር ከሄደች ጊዜ አንስቶ የትኛውም መ/ቤት አልተቀጠረም።ወደ የትኛውም ቦታ አስራ ሁለተኛ ክፍል መጨረሰን የሚጠቁም መረጃውን ይዞ ወዲያ
ወዲህ አላለም:: ዕወቀቱም፣ ፍላጎቱም ድፍረቱም የለውም ...
ታዲያ ለምን ዞር ዞር ብሎ እንጀራውን የሚጋግርበት ምጣድ ገዝቶ አይመለስም? የእሱ እጆች የተፈጠሩት
ሌሎች ድል ሲያደርጉ፣ ሌሎች የአሸናፊዎች አሸናፊ ሲሆነ፣ ሌሎች የሜዳሊያ ባለቤት ሲሆኑ እንዲያጨበጭቡ ብቻ ነው እንዴ?
ምን ይሰራል?
«እና ልሰናበትሽ ነው› አለኝ ሩጫውን እንደጨረሰ ሰው መታከት እየታየበት።
ይሂድ! እስኪ ይሂድና ‹‹የወርቅ በርጩማውን» ይፈልግ።
---==--
ዛሬ ምን እንደነካኝ አላውቅም። ቀንድና ጭራው የማይታይ መያዣ መጨበጫ የሌለው ሀሳብ ሲፈታተነኝ አምሽቷል፡፡
የዘሪቱ ነገር........
አገር ቤት ሄዳ በመጣች ቁጥር በቀርከሃ የተሰራ ጌጥ ታመጣልኛለች። ቢላዋ ማስቀመጫ ቄንጠኛ እቃ!የመመገቢያ እቃዎች! የሳጠራ ማስቀመጫዎች!
የወለል ምንጣፎች! የማታመጣልኝ የዕደ
ጥበብ ውጤት አልነበረም። «እናንተ አገር ይሸጣል?»ስላት «አባቴ ነው የሚሰሪው! ውሰጂላት ብሎኝ ነው»ትለኛለች።
በወር ሰባ ብር ነው የምፍላት።
ወር በሞላ ቁጥር «እትዬ ደሞዝ» አትለኝም፡፡ ዓመት ሲሞላ እኔ ዘንድ የተጠራቀመላትን ብር ትቀበለኝና አንዳንድ ነገር ገዛዝታ ለቤቶችዋ ትወስድላቸዋለች።
«የተረፈሽን ገንዘብ ምን አደረግሽበት?! ... ብዬ
እጠይቃታለሁ።
«የወላጆቹን ቤት አሳደስኩበታ ...>>
«አራት መቶ በማይሞላ ገንዘብ?! »
አዎ! በትናንሽ ጎጆ ቤቶች እኮ ነው የምንኖረው!»
ይገርመኝና ሌላ ጥያቄ አስከትላለሁ።
«የመጀመሪያ ልጅ ነሽ?!»
«ለእናቴ አዎ! ለአባቴ አይደለሁም። አባቴ
ብዙ ሚስቶች አሉት:: አምና በወር ውስጥ ሁለቱ ሚስቶች ወልደውለት የሚያበላቸው አጥቶ ሲበሳጭ
የወር ደሞዜን ላክሁለትና በጣም ተደሰተ፡፡ ባለብዙ ሚስት መሆን በኛ ጎሳ ነውር የለውም»
«የት ነበር አልሺኝ ያንቺ አገር . . .»
«ሩቅ ነው! ከአዲስ አበባ ወደ ሆሳዕና በሚወስደው መንገድ....>>
ከዘሪቱ ጋር ባወራሁ ቁጥር ትዝ የምትለኝ አስቴር ናት።
ባለፈው በፃፈችልኝ ደብዳቤ ላይ « . . . ሰሞኑን ወደ ግብፅ ሄደን ነበር፡፡ ወደ ቀጣሪዎቼ ሃገር! ለልጆቻቸው
የትውልድ ሀገራቸውን ሲያስጎበኙ እኔም «ሞግዚት»ነኝና ከጎናቸው አልጠፋሁም ነበር፡፡ የአባይን ወንዝ ሲያሳዩአቸው በደስታ ተቅበጠበጥኩ፡፡ የምሆነውን አሳጣኝ፡፡ ምን ሆነሻል ሲሉኝ «አባይ እኮ የኛ ነው አልኳቸው ሳቁ፡፡ ከት ብለው ሳቁ፡፡ ምነው ስላቸው፣ምናሉኝ መሰለሽ? «አባይ ወይ ልትለውጪው ወይ
ሊለውጥሽ ይገባል አንድ ነገር ካልሰራሽበት ያንቺ አይደለም።እኛ ከዚህ ውጪ መኖር አንችልም፤» ብለው
ስቀው ተሳለቁብኝ ..
ሌላ ጊዜ ደግሞ፣ «ዛሬም ልንሄድ ነው ተዘጋጂ»ሲሉኝ «አልሄድም» አልኳቸው:: አልሄድም ያልኳቸው አንደኛ፣ ባለፈው «አባይ የኛ ነው» በማለቴ «እሷ እኮ
ናት እንዲህ ያለችው» ብለው በብዙ ሰው ስላሳቁብኝ ሲሆን ሁለተኛ፣ ላንቺ ደብዳቤ ለመፃፍ ግዜ እንዲኖረኝ
ብዬ ነበር፡፡ «እንግዲያውስ ከኛ ጋር የማትሄጂ ከሆነ
«ብላ የስራ መዓት ቆለለችብኝ፡፡ ከጉብኝትዋ ስትመለስ ይሰራ ካለችው የተወሰነውን ብቻ ነበርና የሰራሁት
ጮኸችብኝ፡፡ ተንጨረጨረች፡፡» ድሮስ የናንተ ነገር! አባይን የሚያህል የአለማችን ታላቅ ወንዝ ከደጃችሁ
ሲያልፍ ተአምር ልትሰሩበት ቀርቶ ረሃባችሁንም አላሸነፋችሁበት፡፡.ቤት ለማፅዳት፣ መጥረጊያ ለማንሳት»
አለመስነፍሽም ይገርመኛል አለችኝ፡፡ እኔ ደግሞ ሃገር ውስጥ ያልነበረኝን ሃገር የመውደድ ስሜት ከየት እንዳመጣሁት እንጃ-ሃገሬ ስትሰደብ ያመኛል፣ እራስ
ምታት፣ ጨጓራው ኧረ ምኑ ቅጡ?» ብላ ዕፋልኛለች፡፡
አስቴር የልጅ አዋቂ ናት፡፡ ያለሷ ድጋፍ
ይኸን ጊዜ እንዴት ባለ የችግር ህይወት ኑሮአችንን እንገፋ እንደነበር ሲታወሰኝ ይዘገንነኛል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን «እቴትዬ ጡር መፍራት ደግ ነው» የሚሉ ቃላት በየደብዳቤዎቿ መነሻና መቋጫ
ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል፡፡
«ትዝ ይልሻል? አንዲት ሰራተኛችን፤
ሰራተኛ ቀጥረው ሲሞላው አንድ አመት
ሌባ ነው ይሉታል ደሞዝ ለማስቀረት!
የሚል ግጥም ያለበት ዘፈን ዘፍና ምን ማለት ፈልገሽ ነው? ብዬ ከወር ደሞዟ አስር ብር ያስቆረጥኩባትኀቀን?! አቤት ያነባችወ እንባ! ያቺ አስር ብር
ፕሮግራምዋን እንዴት አመሳቅሎባት ይሆን?!
አንጋጠው የተፉት ምራቅ ሆኗል የኔ እጣ! ያን ግጥም ዛሬ እንዴት እንደምወደው እቴትዬ! ይህቺን ባለሁለት መስመር ስንኝ ስንት አይነት አንጀት የሚበላ የሀዘን
እንጉርጉሮ አውጥቼላታለሁ መሰለሽ?! . . ባለፈው በማይረባ ሰበብ የስድስት ወር ደሞዜን እንደከለከሉኝ ነግሬሻለሁ አይደል?! .. .» ብላ ፅፋልኛለች!
• •
ወላጆቼ ሰራተኞቻቸውን ያስተዳድሩ ከነበረው እጅግ በተሻለ ሁኔታ ነው የምንከባከባቸው።በፈራረሰ
ማእድቤት - ምድጃ ስር - የተበጣጠሰ ሰሌን አንጥፌ -አይደለም የማሳድራቸው፤ የምጣድ ማሰሻ የመሰለ ብርድ
ልብስ - ያውም እግር ወይ አናት ብቻ የመሸፈን አቅም ያለውን ብርድ ልብስ ሰጥቼ አይደለም የማኖራቸው።
ትርፍራፊ አይደለም የሚበሉት።
ከ'ቡና ቤት ሴቶች' ይልቅ ለ'ቤት ሠራተኞች' የሚሰበር ልብ አለኝ፡፡ በተለይ መልከ ጥፉዎቹ ወንድን እንደተራቡት ወጣትነታቸው ሲያልፍ አቤት |
ማሳዘናቸው :: ፍቅርን እንደተቸገሩት ያርጣሉ፣ እምዬ የሚል የእምቦቃቅላ ድምፅ ይናፍቃቸዋል፡፡ አንዳንዶቹ
ደግሞ ከችግር እሸሽ ብለው ዘለው በገቡበት ቤት ይደፈራሉ፡፡ ሻሽ እየተወረወረላት-ቅባት እየተገዛላት- ርካሽ
ሸበጥ እየተቸራት፣ ካረገዘች በኋላ እጣ ፈንታዋ በእመቤትዋ ወይም በጌታዋ መባረር ይሆናል:: 'ያለ ልጅሽ ነው የምንፈልግሽ' የሚል ፈታኝ ጥያቄ ይመጣል፡፡
ቀስ በቀስ ለልመና እጅዋን ትሰጣለች:: ልጅዋም በረንዳ አድሮ በጎዳና መተዳደር ይጀምራል። ካልሆነለት፣ የእለት
ጉርሱን ሊሞላ ማጅራት መቺ ሊሆን!
እኔ እንደዚህ እንዲሆነብኝ አልሻም።
ግና ምን ዋጋ አለው?!
ዘሪቱ ልትሄድብኝ ሳይሆን አይቀርም። ከጥዋት ጀምሮ ሲቀፈኝ የዋለው ያላንዳች ምክንያት አይደለም።እናቷ የመጡት ሊወስዷት ከሆነ፣ እኔ ከምከፍላት የተሻለ
የሚከፍላት ሰው ቢገኝ ነው።
አስር ብር ልጨምርላት ይሆን?
(አንባቢዎቼ በ1996 ነው የተፃፈው የዚ ሰዓት አስር ብር ዋጋውን ለናንተው ልተወው)
ዘሪቱ እናቷን ካገኘች ጊዜ ጀምሮ «እማ! ለምንድነው የመጣሽው?» ብላ መልሳ መላልሳ ስትጠይቃቸው እናትየው ግን ስለጤንነቷና ስለ ሥራዋ ነበር
የሚያነሱባት፡፡ ዘሪቱ መወትወቷን ስትቀጥል «ማታ ስንተኛ እነግርሻለሁ» ሲሏት ሰምቻለሁ፡፡ ምንም በሹክሹክታ ቢሆን!
ዘሪቱ ተስማምታኝ ነበር፡፡ ባለቤቴ ያረፈ ጊዜ እንዴት ትንከባከበኝ እንደነበር መርሳት አልችልም፡፡ አፅናንታኛ
ለች፤
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በእንዳለጌታ_ከበደ
« . . . የአስቴርን ስቃይ ልቀንስ ብዬኮ ነው።
አስቴር እስክትመጣ ድረስ ምን ያህል ጊዜ ይፈጅባታል?አይታወቅም፡፡ ለሁለት ዓመት ብዬ አስምዬ ሸኘኋት!
ምላ ተገዝታ ሆነልኝም አልሆነልኝም ባልከኝ ጊዜ እመለሳለሁ አለችኝ።የት አለች ታዲያ?» አለኝ በመነጫነጭ፡፡
«እኛ አስቸግረናት እኮ ነው! ... ወላጆቼ ናቸው የመምጫ ጊዜዋን ያራዘሙት። እሷ ስትሄድ የችግር ቀዳዳዎቻቸው በእጥፍ በዙ» አልኩት።
«አንቺ የማታውቂው ብዙ ነገር አለ፡፡ አስቴር ጫንቃዋ መሸከም ከሚችለው በላይ ጭነት እያረፈባት እንደሆነ እያወቅሁ ዝም ማለት እንዴት ያስችለኛል?!ፍቅር ማለት ምንድነው?!»
አስቴር ከሄደች ጊዜ አንስቶ የትኛውም መ/ቤት አልተቀጠረም።ወደ የትኛውም ቦታ አስራ ሁለተኛ ክፍል መጨረሰን የሚጠቁም መረጃውን ይዞ ወዲያ
ወዲህ አላለም:: ዕወቀቱም፣ ፍላጎቱም ድፍረቱም የለውም ...
ታዲያ ለምን ዞር ዞር ብሎ እንጀራውን የሚጋግርበት ምጣድ ገዝቶ አይመለስም? የእሱ እጆች የተፈጠሩት
ሌሎች ድል ሲያደርጉ፣ ሌሎች የአሸናፊዎች አሸናፊ ሲሆነ፣ ሌሎች የሜዳሊያ ባለቤት ሲሆኑ እንዲያጨበጭቡ ብቻ ነው እንዴ?
ምን ይሰራል?
«እና ልሰናበትሽ ነው› አለኝ ሩጫውን እንደጨረሰ ሰው መታከት እየታየበት።
ይሂድ! እስኪ ይሂድና ‹‹የወርቅ በርጩማውን» ይፈልግ።
---==--
ዛሬ ምን እንደነካኝ አላውቅም። ቀንድና ጭራው የማይታይ መያዣ መጨበጫ የሌለው ሀሳብ ሲፈታተነኝ አምሽቷል፡፡
የዘሪቱ ነገር........
አገር ቤት ሄዳ በመጣች ቁጥር በቀርከሃ የተሰራ ጌጥ ታመጣልኛለች። ቢላዋ ማስቀመጫ ቄንጠኛ እቃ!የመመገቢያ እቃዎች! የሳጠራ ማስቀመጫዎች!
የወለል ምንጣፎች! የማታመጣልኝ የዕደ
ጥበብ ውጤት አልነበረም። «እናንተ አገር ይሸጣል?»ስላት «አባቴ ነው የሚሰሪው! ውሰጂላት ብሎኝ ነው»ትለኛለች።
በወር ሰባ ብር ነው የምፍላት።
ወር በሞላ ቁጥር «እትዬ ደሞዝ» አትለኝም፡፡ ዓመት ሲሞላ እኔ ዘንድ የተጠራቀመላትን ብር ትቀበለኝና አንዳንድ ነገር ገዛዝታ ለቤቶችዋ ትወስድላቸዋለች።
«የተረፈሽን ገንዘብ ምን አደረግሽበት?! ... ብዬ
እጠይቃታለሁ።
«የወላጆቹን ቤት አሳደስኩበታ ...>>
«አራት መቶ በማይሞላ ገንዘብ?! »
አዎ! በትናንሽ ጎጆ ቤቶች እኮ ነው የምንኖረው!»
ይገርመኝና ሌላ ጥያቄ አስከትላለሁ።
«የመጀመሪያ ልጅ ነሽ?!»
«ለእናቴ አዎ! ለአባቴ አይደለሁም። አባቴ
ብዙ ሚስቶች አሉት:: አምና በወር ውስጥ ሁለቱ ሚስቶች ወልደውለት የሚያበላቸው አጥቶ ሲበሳጭ
የወር ደሞዜን ላክሁለትና በጣም ተደሰተ፡፡ ባለብዙ ሚስት መሆን በኛ ጎሳ ነውር የለውም»
«የት ነበር አልሺኝ ያንቺ አገር . . .»
«ሩቅ ነው! ከአዲስ አበባ ወደ ሆሳዕና በሚወስደው መንገድ....>>
ከዘሪቱ ጋር ባወራሁ ቁጥር ትዝ የምትለኝ አስቴር ናት።
ባለፈው በፃፈችልኝ ደብዳቤ ላይ « . . . ሰሞኑን ወደ ግብፅ ሄደን ነበር፡፡ ወደ ቀጣሪዎቼ ሃገር! ለልጆቻቸው
የትውልድ ሀገራቸውን ሲያስጎበኙ እኔም «ሞግዚት»ነኝና ከጎናቸው አልጠፋሁም ነበር፡፡ የአባይን ወንዝ ሲያሳዩአቸው በደስታ ተቅበጠበጥኩ፡፡ የምሆነውን አሳጣኝ፡፡ ምን ሆነሻል ሲሉኝ «አባይ እኮ የኛ ነው አልኳቸው ሳቁ፡፡ ከት ብለው ሳቁ፡፡ ምነው ስላቸው፣ምናሉኝ መሰለሽ? «አባይ ወይ ልትለውጪው ወይ
ሊለውጥሽ ይገባል አንድ ነገር ካልሰራሽበት ያንቺ አይደለም።እኛ ከዚህ ውጪ መኖር አንችልም፤» ብለው
ስቀው ተሳለቁብኝ ..
ሌላ ጊዜ ደግሞ፣ «ዛሬም ልንሄድ ነው ተዘጋጂ»ሲሉኝ «አልሄድም» አልኳቸው:: አልሄድም ያልኳቸው አንደኛ፣ ባለፈው «አባይ የኛ ነው» በማለቴ «እሷ እኮ
ናት እንዲህ ያለችው» ብለው በብዙ ሰው ስላሳቁብኝ ሲሆን ሁለተኛ፣ ላንቺ ደብዳቤ ለመፃፍ ግዜ እንዲኖረኝ
ብዬ ነበር፡፡ «እንግዲያውስ ከኛ ጋር የማትሄጂ ከሆነ
«ብላ የስራ መዓት ቆለለችብኝ፡፡ ከጉብኝትዋ ስትመለስ ይሰራ ካለችው የተወሰነውን ብቻ ነበርና የሰራሁት
ጮኸችብኝ፡፡ ተንጨረጨረች፡፡» ድሮስ የናንተ ነገር! አባይን የሚያህል የአለማችን ታላቅ ወንዝ ከደጃችሁ
ሲያልፍ ተአምር ልትሰሩበት ቀርቶ ረሃባችሁንም አላሸነፋችሁበት፡፡.ቤት ለማፅዳት፣ መጥረጊያ ለማንሳት»
አለመስነፍሽም ይገርመኛል አለችኝ፡፡ እኔ ደግሞ ሃገር ውስጥ ያልነበረኝን ሃገር የመውደድ ስሜት ከየት እንዳመጣሁት እንጃ-ሃገሬ ስትሰደብ ያመኛል፣ እራስ
ምታት፣ ጨጓራው ኧረ ምኑ ቅጡ?» ብላ ዕፋልኛለች፡፡
አስቴር የልጅ አዋቂ ናት፡፡ ያለሷ ድጋፍ
ይኸን ጊዜ እንዴት ባለ የችግር ህይወት ኑሮአችንን እንገፋ እንደነበር ሲታወሰኝ ይዘገንነኛል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን «እቴትዬ ጡር መፍራት ደግ ነው» የሚሉ ቃላት በየደብዳቤዎቿ መነሻና መቋጫ
ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል፡፡
«ትዝ ይልሻል? አንዲት ሰራተኛችን፤
ሰራተኛ ቀጥረው ሲሞላው አንድ አመት
ሌባ ነው ይሉታል ደሞዝ ለማስቀረት!
የሚል ግጥም ያለበት ዘፈን ዘፍና ምን ማለት ፈልገሽ ነው? ብዬ ከወር ደሞዟ አስር ብር ያስቆረጥኩባትኀቀን?! አቤት ያነባችወ እንባ! ያቺ አስር ብር
ፕሮግራምዋን እንዴት አመሳቅሎባት ይሆን?!
አንጋጠው የተፉት ምራቅ ሆኗል የኔ እጣ! ያን ግጥም ዛሬ እንዴት እንደምወደው እቴትዬ! ይህቺን ባለሁለት መስመር ስንኝ ስንት አይነት አንጀት የሚበላ የሀዘን
እንጉርጉሮ አውጥቼላታለሁ መሰለሽ?! . . ባለፈው በማይረባ ሰበብ የስድስት ወር ደሞዜን እንደከለከሉኝ ነግሬሻለሁ አይደል?! .. .» ብላ ፅፋልኛለች!
• •
ወላጆቼ ሰራተኞቻቸውን ያስተዳድሩ ከነበረው እጅግ በተሻለ ሁኔታ ነው የምንከባከባቸው።በፈራረሰ
ማእድቤት - ምድጃ ስር - የተበጣጠሰ ሰሌን አንጥፌ -አይደለም የማሳድራቸው፤ የምጣድ ማሰሻ የመሰለ ብርድ
ልብስ - ያውም እግር ወይ አናት ብቻ የመሸፈን አቅም ያለውን ብርድ ልብስ ሰጥቼ አይደለም የማኖራቸው።
ትርፍራፊ አይደለም የሚበሉት።
ከ'ቡና ቤት ሴቶች' ይልቅ ለ'ቤት ሠራተኞች' የሚሰበር ልብ አለኝ፡፡ በተለይ መልከ ጥፉዎቹ ወንድን እንደተራቡት ወጣትነታቸው ሲያልፍ አቤት |
ማሳዘናቸው :: ፍቅርን እንደተቸገሩት ያርጣሉ፣ እምዬ የሚል የእምቦቃቅላ ድምፅ ይናፍቃቸዋል፡፡ አንዳንዶቹ
ደግሞ ከችግር እሸሽ ብለው ዘለው በገቡበት ቤት ይደፈራሉ፡፡ ሻሽ እየተወረወረላት-ቅባት እየተገዛላት- ርካሽ
ሸበጥ እየተቸራት፣ ካረገዘች በኋላ እጣ ፈንታዋ በእመቤትዋ ወይም በጌታዋ መባረር ይሆናል:: 'ያለ ልጅሽ ነው የምንፈልግሽ' የሚል ፈታኝ ጥያቄ ይመጣል፡፡
ቀስ በቀስ ለልመና እጅዋን ትሰጣለች:: ልጅዋም በረንዳ አድሮ በጎዳና መተዳደር ይጀምራል። ካልሆነለት፣ የእለት
ጉርሱን ሊሞላ ማጅራት መቺ ሊሆን!
እኔ እንደዚህ እንዲሆነብኝ አልሻም።
ግና ምን ዋጋ አለው?!
ዘሪቱ ልትሄድብኝ ሳይሆን አይቀርም። ከጥዋት ጀምሮ ሲቀፈኝ የዋለው ያላንዳች ምክንያት አይደለም።እናቷ የመጡት ሊወስዷት ከሆነ፣ እኔ ከምከፍላት የተሻለ
የሚከፍላት ሰው ቢገኝ ነው።
አስር ብር ልጨምርላት ይሆን?
(አንባቢዎቼ በ1996 ነው የተፃፈው የዚ ሰዓት አስር ብር ዋጋውን ለናንተው ልተወው)
ዘሪቱ እናቷን ካገኘች ጊዜ ጀምሮ «እማ! ለምንድነው የመጣሽው?» ብላ መልሳ መላልሳ ስትጠይቃቸው እናትየው ግን ስለጤንነቷና ስለ ሥራዋ ነበር
የሚያነሱባት፡፡ ዘሪቱ መወትወቷን ስትቀጥል «ማታ ስንተኛ እነግርሻለሁ» ሲሏት ሰምቻለሁ፡፡ ምንም በሹክሹክታ ቢሆን!
ዘሪቱ ተስማምታኝ ነበር፡፡ ባለቤቴ ያረፈ ጊዜ እንዴት ትንከባከበኝ እንደነበር መርሳት አልችልም፡፡ አፅናንታኛ
ለች፤
👍6
#የወርቅ_በርጩማውን_ፍለጋ
፡
፡
#ክፍል_ሦስት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በእንዳለጌታ_ከበደ
...እናቷ ቀጠሉ፡፡ « . . . እንዴት እየኖርኩ እንደሆነ ብታይልኝ! የሰፈር ሰው ያሾፍብኛል ብጤዎቻችን ሊያሳብዱኝ ደርሰዋል . . .»
«አሁን ደግሞ ምን ሆናችሁ? ማለቂያ የለው የናንተ ጣጣ!»
ገንዘብ አይደለም የጎደለብን ልጄ! ከአፍሽ
ነጥቀሽ አይደል የምታጎርሽን? ዕድሜሽን ያርዝመው እንጂ ስራ ከጀመርሽ በኋላ ሰፈርተኛ የሚቀናብን ሆነናል
ተንቀባርረን ከሰው ጋር እንቀላቀላለን በፊት የአፈር ገንፎ ይመስላሉ እያሉ ይሳለቁብን የነበሩ ሁሉ አሁን
አፋቸውን ይዘዋል፡ ዕድሜ ላንቺ!»
ጆሮዬን ቀስሬ ማዳመጤን ቀጥያለሁ:: የእናትና የልጅ የሹክሹክታ ድምፅ፡፡
ከየጣሪያው ስር ስንት አይነት አቤቱታ አለ? ስንት አይነት የተከፋ ልብ? ስንት አይነት አፅናኝ ያጣ ልቅሶ? ልብን የሚያጨልም መልሶ መላልሶ፡፡
«አጥሩን ኣሳጠርኩት:: ቤቱን አሳደስኩት:: አሁን ደግሞ ታናሽሽ ሊያገባ ነው አግዢው አላችሁኝ።ስንቱን ቀዳዳ ልሽፍን? እኔስ እማ? እኔስ! ... ለእኔስ?! »
በእንባ ሳትታጠብ አልቀረችም፡፡ ድምፅዋ ነገረኝ፡፡
«ከወንድምሽ ጋር ተጣልተናል ... ተኮራርፈናል! ባንቺ ጉዳይም ተቀያይመናል»
__«በእኔ ጉዳይ? ለምን?!»
«እህትህን ለምን ታስቸግራታለህ? . . .
ለኛ በመጨነቅ ዕድሜዋን ልትገፋ ነወይ!
· . . ስለው
"እኔ ትዳር ልመሰርት ስል ነው ወይ እንደዚህ አይነት እንድታመነታና እንዳትረዳኝ የሚያደርጋት ሃሳብ
የምታመነጨው?' ብሎ ተቆጥቶ አኮረፈ .
ዘሪቱ «እሺ አሁን እኔ ምን እንዳደርግ ነው
የምትፈልጊው?» አለች።
«የሰርግህን መሉ ወጪ እሸፍንልሃለሁ ብለሽ ደብዳቤ ጻፈለት፡፡ ቁጥርና ፊደል ታውቂበት የለ? »
«እንዴ? የወንድሜን የሰርግ ወጪ ለመሸፈንኮ ቢያንስ ሁለት ሶስት ዓመት መስራት አለብኝ ያውም የደሞዝ ጭማሪ ካገኘሁ! .. .ከየት አመጣለሁ እማ? .
በእርግጥ ታሳዝኚኛለሽ ግን ... »
አሳዘነችኝ፡፡ ይህቺ ከተወለደች ሃያ አምስት ዓመት ያስቆጠረች የማትመስል ሴት ስንት መከራ ተሸክማለች?
ቆይ ደሞዟን ...
«ለሱ አታስቢ!» አሉ እናቷ
«ለምኑ?»
«ለወንድምሽ ሰርግ ወጪ»
«ምን አዲስ ነገር ተገኝቶ ነው የማላስበው? እናንተ ሃሳባችሁን ሁሉ እኔ ጫንቃ ላይ ጥላችሁ አይደል በሰላም
ዕንቅልፋችሁን የምትለጥጡት?! መስራት
የሚገባችሁን ያህል ለመስራት ሰንፋችሁ በኔ ገንዘብ የከርሞ እቅድ ትነድፋላችሁ! ...››
« ይኸውልሽ ዘሪቱ፣ ጅማ ያሉት የቀርከሃ ሶፋ የሚሠሩ ወንድሞቼ ተደራጂበት፣ ነግጂበት ብለው የላኩልኝ ሁለት መቶ ብር አለ፡፡ ለወንድምሽ ' ለአንዳንድ
ጉዳይ ማሟያ' ብለሽ ትልኪለታለሽ፡፡ ከማግባትህ በፊት ስራ መያዝ አለብህ' ብለሽ - ገንዘቡን 'ተሳፈርበት ወደኔ
ናበት' ትይዋለሽ፡፡ ከኪስሽ እንዳወጣሽው እንጂ እኔ እንደሰጠሁሽ ወፍ እንዳይሰማ!»
አንዳንዴ የምታመነጨው ሃሳብኮ
«አይ እማዬ . . .
«ምን ላድርግ? ብቻሽን ስትለፊ እያየሁ እጄን አጣጥፌ አልቀመጥ! ... የምሰጥሽን ብር ከላክሽለት
ከተማ ገብቶ መስራት ብዙ ገንዘብ የማያስገኝ ይመስለዋል»
የተስማሙ መሰለኝ።
እኔም እፎይ ብዬ ዘሪቱ እንደማትሄድብኝ እርግጠኛ ሆኜ በባለቤቴ ሞት ምክንያት ያገኘሁትን ብር ምን መስራት እንዳለብኝ እያውጠነጠንኩ፣ የለውጥ ቀን ቅርብ
እንደሆነ አስተውዬ . . . ወደ መኝታ ቤቴ ልሄድ ስል ስልኩ ጮኸ።
ደነገጥኩ፡፡
በዚህ ሰዓት የሚደወልልኝ ከአስቴር ነው::
አስቴር ምን ሆና ይሆን? ስፈራ ስቸር ስልኩን አነሳሁት። ልክ ነኝ።
ረጅም የሆነ ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ፡
«እቴትዬ!» አለችኝ:: አቤት ድምዕዋ ውስጥ ያለው ፍቅር! በናፍቆት የተሞላ ዜማ! እንደዚህች ያለችዋን እህቴን በባዕድ አገር እንድትጎሳቆል መፍቀዱ ምን ሆኜ ነው?
«ወዬ!»
‹ደወለልኝ!! »
«ጓደኛሽ?››
«አዎ! ከደቡብ አፍሪካ! ... አሳዘነኝ:: ተላቀስን፡፡
እንዳያሳስበኝ ብለ አጽናናኝ:: የተባባልነወን እፅፍልሻለሁ ... እሺ እቴትዬ!»
«አይዟችሁ ይነጋል . . .»
«እንዴት ነው እቴት ቤተሰብ አቤቱታ ማሰማት አልጀመረም? . . ባለፈው የሰራሁበትን ብር ሁሉ ለጓደኛዬ ላክሁለት፡፡ ከወላጆቹ የወረሰውን ቤት አሳድሶ በኮንትራት ለሆቴል አከራይቶት እኮ ነው፤ በደቡብ አፍሪካ አድርጎ አሜሪካ ለመግባት ስንቁን የቋጠረው! .
ስንደራጅ ቤቱን እኛ እንስራበታለን!»
:
«ይሁን እስኪ እንግዲህ . . .»
«እቴትዬ! . . . ሁልጊዜ እጠይቅሻለሁ ብዬ እየረሳሁ!»
«ምን?››
«ሰራተኛሽ ዘሪቱ አጫውታሽ ያዝናናሽኝ ያ
የወርቅ በርጩማ ነገር የት ደረሰ? ለወንድሜ ተበረከተለት?»
ተሳሳቅን::
«ለምን ጠየቅሽኝ?»
«ወደሃገር ቤት ስገባ የራሴን የወርቅ በርጩማ ለመስራት ላቤን ማፍሰስ እንዳለብኝ ይሰማኛል፡፡ በከንቱ
ምኞት የሚገኝ ሳይሆን ጠንክሮ የመስራት ውጤት ነው ያ የወርቅ በርጩማ!»
ያለችበት ሃገር ስራን አለመናቅን አስተምሯታል፡፡ ሰው ትልቅ የሚባለው ጊዜውን በተግባር መተርጎም የቻለ እንደሆነ መሆኑን ዕውቀትና ልምድ ቀስማለች።ይሄ ነው ብላ ልታሳየኝ የማትችለው ዲግሪ እንደተበረከተላትም ተረዳሁ:: ከመሪር ሕይወት የተገኘ
ዲግሪ!
«አሪፍ ሃሳብ ነው!» አልኳት!
ትንሽ ቆይታ «እቴትዬ! መርሮኛል! ትንሽ
ሰራርቼ እመጣለሁ ላብድ ጥቂት ነው የቀረኝ ..በየጊዜው የጓደኞቼ ቁጥር ሲቀንስ፣በሙቅ ውሃ ሲነፍሩ፣
ከፎቅ ሲወረወሩ አሟሟታቸው ሲከፋ እያየሁ እንዴት እንዴት ሆኜ ነው እዚህ በሰው አገር የምኖረው »
አለችኝ።
« ለምን አትመጪም? ነይ እዚህ! ዛሬ ነገ አትበይ! እኛም በስጋት አለቅንኮ! የግድ ቤተሰቦችሽ እንዲያልፍላቸው ያንቺ ህይወት ማለፍ አለበት?»
«አይ እቴትዬ! ...ዛሬ ነገ ሳትይ ነይ' አልሺኝ?
ምን ይዤ? መጥቼስ ምን ሰርቼ ልበላ?!»
«አንድ የመጣልኝን ሃሳብ ልንገርሽ?» አልኳት ለጥቂት ደቂቃ ሳሰላስል ቆይቼ።
«ምንድነው?»
«ላበድርሽ ነው! መለስተኛ ንግድ ሊያስጀምርሽ የሚችል ብር! .. ጓደኛሽ በውርስ ያገኘውን ቤት ወደ
ንግድ ተቋም የመለወጥ ዕቅድ አላችሁ አይደል? እረዳችኋለሁ!»
«ከየት አምጥተሽ?» እንደተገረመች ያስታውቃል::
«ለማንም እንዳትነግሪ! . . . ቤተሰብም ቢሆን እንዳያውቀው! ባለቤቴ ይሰራበት የነበረው ድርጅት ኢንሹራንስ ከፍሎኛል፡፡ ስለዚህ እሰጥሽና - ገንዘቡን
ትሰሪበትና - ዕቁብ ገብተሽ ትከፍይኛለሽ .. .»
«አይ እቴትዬ!» ከድምፅዋ ሃሳቤን እንደወደደችው ያስታውቃል፡፡
ስልኩን ከዘጋሁት በኋላ ነው፣ መፍትሄውን
የኮረጅኩት ከዘሪቱና ከእናቷ እንደሆነ የታወሰኝ!
በተገማሸረ መስክ ውስጥ እንደሚብሰከሰክ ውሃ
. . እፎይ ብላ የተረጋጋች የምትመስለዋ
ህይወታችን መንቀሳቀስ የምትጀምርበት ቀን ሩቅ እንደማይሆን ተሰማኝ፡፡
የዛሬዋን ማታ ወደድኳት፡፡
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሦስት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በእንዳለጌታ_ከበደ
...እናቷ ቀጠሉ፡፡ « . . . እንዴት እየኖርኩ እንደሆነ ብታይልኝ! የሰፈር ሰው ያሾፍብኛል ብጤዎቻችን ሊያሳብዱኝ ደርሰዋል . . .»
«አሁን ደግሞ ምን ሆናችሁ? ማለቂያ የለው የናንተ ጣጣ!»
ገንዘብ አይደለም የጎደለብን ልጄ! ከአፍሽ
ነጥቀሽ አይደል የምታጎርሽን? ዕድሜሽን ያርዝመው እንጂ ስራ ከጀመርሽ በኋላ ሰፈርተኛ የሚቀናብን ሆነናል
ተንቀባርረን ከሰው ጋር እንቀላቀላለን በፊት የአፈር ገንፎ ይመስላሉ እያሉ ይሳለቁብን የነበሩ ሁሉ አሁን
አፋቸውን ይዘዋል፡ ዕድሜ ላንቺ!»
ጆሮዬን ቀስሬ ማዳመጤን ቀጥያለሁ:: የእናትና የልጅ የሹክሹክታ ድምፅ፡፡
ከየጣሪያው ስር ስንት አይነት አቤቱታ አለ? ስንት አይነት የተከፋ ልብ? ስንት አይነት አፅናኝ ያጣ ልቅሶ? ልብን የሚያጨልም መልሶ መላልሶ፡፡
«አጥሩን ኣሳጠርኩት:: ቤቱን አሳደስኩት:: አሁን ደግሞ ታናሽሽ ሊያገባ ነው አግዢው አላችሁኝ።ስንቱን ቀዳዳ ልሽፍን? እኔስ እማ? እኔስ! ... ለእኔስ?! »
በእንባ ሳትታጠብ አልቀረችም፡፡ ድምፅዋ ነገረኝ፡፡
«ከወንድምሽ ጋር ተጣልተናል ... ተኮራርፈናል! ባንቺ ጉዳይም ተቀያይመናል»
__«በእኔ ጉዳይ? ለምን?!»
«እህትህን ለምን ታስቸግራታለህ? . . .
ለኛ በመጨነቅ ዕድሜዋን ልትገፋ ነወይ!
· . . ስለው
"እኔ ትዳር ልመሰርት ስል ነው ወይ እንደዚህ አይነት እንድታመነታና እንዳትረዳኝ የሚያደርጋት ሃሳብ
የምታመነጨው?' ብሎ ተቆጥቶ አኮረፈ .
ዘሪቱ «እሺ አሁን እኔ ምን እንዳደርግ ነው
የምትፈልጊው?» አለች።
«የሰርግህን መሉ ወጪ እሸፍንልሃለሁ ብለሽ ደብዳቤ ጻፈለት፡፡ ቁጥርና ፊደል ታውቂበት የለ? »
«እንዴ? የወንድሜን የሰርግ ወጪ ለመሸፈንኮ ቢያንስ ሁለት ሶስት ዓመት መስራት አለብኝ ያውም የደሞዝ ጭማሪ ካገኘሁ! .. .ከየት አመጣለሁ እማ? .
በእርግጥ ታሳዝኚኛለሽ ግን ... »
አሳዘነችኝ፡፡ ይህቺ ከተወለደች ሃያ አምስት ዓመት ያስቆጠረች የማትመስል ሴት ስንት መከራ ተሸክማለች?
ቆይ ደሞዟን ...
«ለሱ አታስቢ!» አሉ እናቷ
«ለምኑ?»
«ለወንድምሽ ሰርግ ወጪ»
«ምን አዲስ ነገር ተገኝቶ ነው የማላስበው? እናንተ ሃሳባችሁን ሁሉ እኔ ጫንቃ ላይ ጥላችሁ አይደል በሰላም
ዕንቅልፋችሁን የምትለጥጡት?! መስራት
የሚገባችሁን ያህል ለመስራት ሰንፋችሁ በኔ ገንዘብ የከርሞ እቅድ ትነድፋላችሁ! ...››
« ይኸውልሽ ዘሪቱ፣ ጅማ ያሉት የቀርከሃ ሶፋ የሚሠሩ ወንድሞቼ ተደራጂበት፣ ነግጂበት ብለው የላኩልኝ ሁለት መቶ ብር አለ፡፡ ለወንድምሽ ' ለአንዳንድ
ጉዳይ ማሟያ' ብለሽ ትልኪለታለሽ፡፡ ከማግባትህ በፊት ስራ መያዝ አለብህ' ብለሽ - ገንዘቡን 'ተሳፈርበት ወደኔ
ናበት' ትይዋለሽ፡፡ ከኪስሽ እንዳወጣሽው እንጂ እኔ እንደሰጠሁሽ ወፍ እንዳይሰማ!»
አንዳንዴ የምታመነጨው ሃሳብኮ
«አይ እማዬ . . .
«ምን ላድርግ? ብቻሽን ስትለፊ እያየሁ እጄን አጣጥፌ አልቀመጥ! ... የምሰጥሽን ብር ከላክሽለት
ከተማ ገብቶ መስራት ብዙ ገንዘብ የማያስገኝ ይመስለዋል»
የተስማሙ መሰለኝ።
እኔም እፎይ ብዬ ዘሪቱ እንደማትሄድብኝ እርግጠኛ ሆኜ በባለቤቴ ሞት ምክንያት ያገኘሁትን ብር ምን መስራት እንዳለብኝ እያውጠነጠንኩ፣ የለውጥ ቀን ቅርብ
እንደሆነ አስተውዬ . . . ወደ መኝታ ቤቴ ልሄድ ስል ስልኩ ጮኸ።
ደነገጥኩ፡፡
በዚህ ሰዓት የሚደወልልኝ ከአስቴር ነው::
አስቴር ምን ሆና ይሆን? ስፈራ ስቸር ስልኩን አነሳሁት። ልክ ነኝ።
ረጅም የሆነ ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ፡
«እቴትዬ!» አለችኝ:: አቤት ድምዕዋ ውስጥ ያለው ፍቅር! በናፍቆት የተሞላ ዜማ! እንደዚህች ያለችዋን እህቴን በባዕድ አገር እንድትጎሳቆል መፍቀዱ ምን ሆኜ ነው?
«ወዬ!»
‹ደወለልኝ!! »
«ጓደኛሽ?››
«አዎ! ከደቡብ አፍሪካ! ... አሳዘነኝ:: ተላቀስን፡፡
እንዳያሳስበኝ ብለ አጽናናኝ:: የተባባልነወን እፅፍልሻለሁ ... እሺ እቴትዬ!»
«አይዟችሁ ይነጋል . . .»
«እንዴት ነው እቴት ቤተሰብ አቤቱታ ማሰማት አልጀመረም? . . ባለፈው የሰራሁበትን ብር ሁሉ ለጓደኛዬ ላክሁለት፡፡ ከወላጆቹ የወረሰውን ቤት አሳድሶ በኮንትራት ለሆቴል አከራይቶት እኮ ነው፤ በደቡብ አፍሪካ አድርጎ አሜሪካ ለመግባት ስንቁን የቋጠረው! .
ስንደራጅ ቤቱን እኛ እንስራበታለን!»
:
«ይሁን እስኪ እንግዲህ . . .»
«እቴትዬ! . . . ሁልጊዜ እጠይቅሻለሁ ብዬ እየረሳሁ!»
«ምን?››
«ሰራተኛሽ ዘሪቱ አጫውታሽ ያዝናናሽኝ ያ
የወርቅ በርጩማ ነገር የት ደረሰ? ለወንድሜ ተበረከተለት?»
ተሳሳቅን::
«ለምን ጠየቅሽኝ?»
«ወደሃገር ቤት ስገባ የራሴን የወርቅ በርጩማ ለመስራት ላቤን ማፍሰስ እንዳለብኝ ይሰማኛል፡፡ በከንቱ
ምኞት የሚገኝ ሳይሆን ጠንክሮ የመስራት ውጤት ነው ያ የወርቅ በርጩማ!»
ያለችበት ሃገር ስራን አለመናቅን አስተምሯታል፡፡ ሰው ትልቅ የሚባለው ጊዜውን በተግባር መተርጎም የቻለ እንደሆነ መሆኑን ዕውቀትና ልምድ ቀስማለች።ይሄ ነው ብላ ልታሳየኝ የማትችለው ዲግሪ እንደተበረከተላትም ተረዳሁ:: ከመሪር ሕይወት የተገኘ
ዲግሪ!
«አሪፍ ሃሳብ ነው!» አልኳት!
ትንሽ ቆይታ «እቴትዬ! መርሮኛል! ትንሽ
ሰራርቼ እመጣለሁ ላብድ ጥቂት ነው የቀረኝ ..በየጊዜው የጓደኞቼ ቁጥር ሲቀንስ፣በሙቅ ውሃ ሲነፍሩ፣
ከፎቅ ሲወረወሩ አሟሟታቸው ሲከፋ እያየሁ እንዴት እንዴት ሆኜ ነው እዚህ በሰው አገር የምኖረው »
አለችኝ።
« ለምን አትመጪም? ነይ እዚህ! ዛሬ ነገ አትበይ! እኛም በስጋት አለቅንኮ! የግድ ቤተሰቦችሽ እንዲያልፍላቸው ያንቺ ህይወት ማለፍ አለበት?»
«አይ እቴትዬ! ...ዛሬ ነገ ሳትይ ነይ' አልሺኝ?
ምን ይዤ? መጥቼስ ምን ሰርቼ ልበላ?!»
«አንድ የመጣልኝን ሃሳብ ልንገርሽ?» አልኳት ለጥቂት ደቂቃ ሳሰላስል ቆይቼ።
«ምንድነው?»
«ላበድርሽ ነው! መለስተኛ ንግድ ሊያስጀምርሽ የሚችል ብር! .. ጓደኛሽ በውርስ ያገኘውን ቤት ወደ
ንግድ ተቋም የመለወጥ ዕቅድ አላችሁ አይደል? እረዳችኋለሁ!»
«ከየት አምጥተሽ?» እንደተገረመች ያስታውቃል::
«ለማንም እንዳትነግሪ! . . . ቤተሰብም ቢሆን እንዳያውቀው! ባለቤቴ ይሰራበት የነበረው ድርጅት ኢንሹራንስ ከፍሎኛል፡፡ ስለዚህ እሰጥሽና - ገንዘቡን
ትሰሪበትና - ዕቁብ ገብተሽ ትከፍይኛለሽ .. .»
«አይ እቴትዬ!» ከድምፅዋ ሃሳቤን እንደወደደችው ያስታውቃል፡፡
ስልኩን ከዘጋሁት በኋላ ነው፣ መፍትሄውን
የኮረጅኩት ከዘሪቱና ከእናቷ እንደሆነ የታወሰኝ!
በተገማሸረ መስክ ውስጥ እንደሚብሰከሰክ ውሃ
. . እፎይ ብላ የተረጋጋች የምትመስለዋ
ህይወታችን መንቀሳቀስ የምትጀምርበት ቀን ሩቅ እንደማይሆን ተሰማኝ፡፡
የዛሬዋን ማታ ወደድኳት፡፡
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2