አትሮኖስ
280K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
477 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

//
ራሄል በወላጆቿ ቤት ከመዋኛ ገንዳ አጠገብ ከእናትና አባቷ ጋር ተቀምጣ የጥዋት ፀሀይ እየሞቀች ነው፡፡

ፀጋ   ‹‹ አበባ ስጪኝ?››ስትል እህቷን ጠየቀች፡፡

ራሄል ከተቀመጠችበት ተነሳችና   የፀሐይ መነፅሯን ወደ ጭንቅላቷ ገፋ በማድረግ   እህቷ የፈለገችውን  አበባ ቀነጠሰችና በትናንሽ እጆቾ ውስጥ አስቀመጠችላት…ፀጋ በደስታ ፈነጠዘች፡፡
ሮቤል እና አዲሷ ረዳት የፋውንዴሽኑን ስራ ከአሰበችው በላይ  በጥሩ ብቃት እየመሩላት እንደሆነ ለሁለት ቀን ወደቢሮ ተመልሳ ባደረገችው የስራ ግምገማ መረዳት ችላለች፡፡
…እህቷን ለማስታመም በሆስፒታል ባሳለፈቻቸው አስር ቀናት ውስጥ ምንም የጎደለ እና ሳይሰራ የተወዘፈ ስራ አልነበረም…እና አሁንም ለሌላ አንድ ሰምንት ታናሽ እህቷ በደንብ እስክታገግም አብራት እንድትሆንና ቀለል ያሉ  ስራዎችን እዛው እቤት ሆና እንድትሰራ ፈቅደውላት እሷም ተስማምታ  ወላጇቾ ቤት ነው ያለችው፡፡

‹‹ኤሊ እመጣለሁ ያለው መቼ ነው?››ወ.ሮ ትርሀስ  መጽሃፏቸውን  ከጎኗቸው  ባለ የመስታወት ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠው ራሄልን  ጠየቋት።

‹‹ከሶስት እስከ  አራት ሰዓት እመጣለሁ ነበር ያለው ፡፡ ››መለሰች…ጸጋ  ራሷ ቀጥፋ የሰጠቻትን አበባ  ፀጉሯ መካከል ሻጠችላት…ራሄል  በፈገግታ እህቷን ወደራሷ ሳበችና ጉንጮን በመሳም‹‹ትንሿ እህቴ ..እንዲህ ስላሳመርሺኝ አመሰግናለው››አለቻት፡፡
በዛው ቅፅበት ወደግዙፉ ግቢ እየቀረበ የሚመጣ የመኪና ድምፅ ተሰማ ፡፡

‹‹የምትጠብቂው ጓደኛሽ  አለ እንዴ?››አቶ ቸርነት ጠየቁ፡፡

‹‹ አይ አይመስለኝም?››ራሄል እርግጠኛ ባለመሆን ጠየቀች፡፡

‹‹እንግዲያው አለም መጥታ ማንነቱን እስክታሳውቀን እንጠብቅ  ?››በማለት እናቷ ሳቁ።

አለም ወዲያው እየተፍለቀለቀች መጣች…‹‹ራሄል  ነይ እንግዳሽን ተቀበይ››

‹‹ማን ነው?››

‹‹አትንገሪያት ተብያለው…እራስሽ መጥተሸ እይው››አለችና ወደኪችኗ ተመለሰች፡፡

ራሄል.‹‹ማነው በወላጆቼ ቤት ከእኔ ጋር እንዲህ አይነት ጫወታ ለመጫወት የደፈረው?››በማለት ተነስታ ፀጋን ይዛ   ሄደች።ራሄል እና ፀጋ  ወደ ግቢው የመኪና ማቆሚያ አካባቢ ሲሄዴ ኤሊ ወደ ውስጥ ሲገባ ተመለከቱት  ።ራሄል እንዳየችው  በውስጧ የደስታ ማዕበል አጥለቀለቃት።

ባለመኪና ስትጠብቅ ባለሞተር ሰው በማየቷ ተደንቃ ‹‹ሄይ፣ እንዴት እዚህ ደረስክ? የሞተር ሳይክልህን ድምፅ አልሰማሁም።››አለችው…

ዔሊ ጎንበስ ብሎ በቀስታ ሳማት እና ፀጋን አንስቶ ካቀፋት በኃላ‹‹ሌላ አይነት  የመጓጓዣ ዘዴ ነው የተጠቀምኩት.››ሲል መለሰላት፡፡

‹‹ሞተርህ ተበላሸች እንዴ ?›› አለችና አይኖቾን ወደመኪና ማቆሚያ አዞረች  ከእሷ   ቀይ መኪና  አጠገብ የቆመ ባለ ሰማያዊ ቀለም  መኪና እያየች ግራ ተገባች።

‹‹ ያን መኪና  ከማን ነው የተዋሰከው? ወንድምህ እንደዚህ አይነት መኪና የለውም።››

ዔሊ ተነፈሰ። ‹‹እነሆ፣ ወ.ሮ ራሄል  ሞተሬን ሸጥኩት።››

ራሄል መኪናዋን በድጋሜ  ተመለከተች፣ ‹‹ሞተር ሳይክልህን አስወገድከው !አየህ እኔ ስለ አንተ የምወደው ያን  ነው ። ቆንጆ እና ፈጣን ተማሪ ነህ….ግን ለምን?››

…‹‹ደህና፣ በአንድ ወቅት አንድ ሰው እንዴት አንድ ኃላፊነት የሚሰማው ለዛውም የህፃናት ሀኪም የሆነ ሰው ሞተር ሳይክል ይነዳል ? የሚል  ጥያቄ ጠየቀኝ። እና ለእሱ መልስ ለመስጠት ብዬ ነው መኪና የገዛሁት፡፡››

ራሄል ወደ መኪናው ሄዳ እውነት መሆኑን ለማረጋገጥ  ትንሽ ነካችው፣ ከዚያም ወደ ዔሊ ተመለሰች፣ ››

‹‹አስደንቀኸኛል ››አለችው

‹‹ስለሞተር ሳይክሎች ያለሽን ስሜት ስለማውቅ  እናም የፍራቻሽም ምክንያት በከፊል ትክክል መሆኑን ስላመንኩበት  ነው...››

እዛው የሳሎኑ በረንዳ ላይ ካሉ ወንበሮች አንዱን እንዲቀመጥ ሳበችለት ፀጋን በክንዱ እንዳቀፈ ተቀመጠ….ከጎኑ ሌላ ወንበር ስባ ተቀመጠች፡፡

ከዛ ሳታስበውና ምንም ሳትዘጋጅበት ትልቅ  ቁም ነገር ከአንደበቱ አፈትልኮ ወጣ  ‹‹ይህን ሁሉ  በትክክለኛው መንገድ ይፋ   ማድረግ ፈልጌ ነው …ራሄል፣ ላገባሽ እፈልጋለሁ።››አላት፡፡

ጆሮዎቾን ማመን አልቻለችም…ልቧን  ደረቷን ሰንጥቆ እንዳይወጣ የፈራች ይመስል ደግፋ ያዘችው ። በውስጧ የሚንተከተከው ደስታ እና ፍቅር እና ምስጋና መውጫ ለማግኘት እየሞከሩ በአንደበቷ ላይ ተንገዋለሉ….ማልቀስ ብቻ ነው የቻለችው፡፡

‹‹ሄይ እኔ ያን ያህል መጥፎ ነገር አልተናገርኩም….ለምን ታለቅሻለሽ?››

‹‹በጣም ደስ ብሎኝ ነው…..››ስትል በለሆሳሳ መለሰችለት፡፡‹‹እወድሀለሁ ኤሊ›› ወደ እሱ ተሳበችና ጉንጩን ሳመችው..ታፋው  ላይ የተቀመጠችው ፀጋ  በደስታ እጆቿን እያጨበጨበች በሳቅ ተንከተከተች። የእሷ ሳቅና ደስታ ወደ እነሱም ተጋባ፡፡

‹‹መጀመሪያ ዝም ብዬ ለአንቺ ምንም ሳልነገርሽ ወደቤተሰቦችሽ ሽማግሌ ለመላክ አቅጄነበር …››

‹‹እንዴ የእኔን ሀሳብ ሳታውቅ ሽማግሌ ልከህ እምቢ ብልህስ?››

‹‹ያው ምን አደርጋለው የተሰበረ ልቤን  ይዤ  የብቸኝነት ኑሮዬን ቀጥላለዋ !!››ብሎ ትከሻውን ነቀነቀ።ራሄል ጣቷን ከንፈሩ ላይ አድርጋ ሳቀች።

‹‹ ስለነርከኝ ደስ ብሎኛል፣ደግሞ ስትነግረኝ  ፀጋ በመሀከላችን መገኘት በመቻሏ  ደስታዋ ድርብ  ሆኗል … ለነገሩ እኛን አንድ ያደረገች እሷ ነበረች.››

‹‹እሺ ስላልሽኝ ደስ ብሎኛል…:በዚህ ምክንያት በህይወቴ ለሆነው ነገር እግዚአብሔርን በየቀኑ አመሰግነዋለሁ:: በአንቺ ምክንያት ህይወቴ መሉ ሆኗል››

‹‹አንተ ስጦታዬ ነህ ኤሊ ›› አለችና አቀፈችው።

‹‹አሁን እናትና አባትሽን እንፈልግ።››

ተስማሙና …ተያይዘው በአረንጓዴ ተክሎች ወደተሸፈነው ግዙፉ ጊቢ  ተያይዘው እየተሳሰቁ ሄዱ፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
80👍18
አንደኛ ሰርጋቸውን ከሁለት ወር ባነሰ ጊዜ እንዲደረግ ማድረግ፡፡ሁለተኛ  ደግሞ ሰርጋቸው ተደግሶ ባል እና ሚስት ተብለው አንድ ቤት ተጠቃለው እስኪገቡ ድረስ ይሄንን ፀጋ ልጁ እንደሆነች የሚገልፀውን ደብዳቤ እንዳያገኘው ማድረግ፡፡
እነዚህን ውሳኔዎች ከወሰነች በኃላ ነው የተወሰነ መረጋጋት ስለተሰማት እንቅልፍ የወሰዳት፡፡

ተፈፀመ

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
35👍10🤔4
#የፀሎት_ፉክክር
.
ለረጅም ዘመናት
እግዚአብሔር ይስጥልኝ እየተባለበት፤
በእያንዳንዱ ሠው አፍ እግዜር ዕዳ አለበት፤
እያሉ ሠምቼ
ይኸው መጥቻለሁ
እሱ ይስጥህ እያሉ ሲልኩኝ ወዳንተ፤
በል እግዜር መፅውተኝ
ምሰፍርበት አጣሁ
ምድሩን ዘር ዘርተውት
እንኳን ለኔ ቀርቶ ቦታ የለም ላንተ፤
.
ብዛ ተባዛባት
ምድሪቱንም ሙላት ብለህ ስትልከኝ፤
ምን አስበህ ይሆን?
እንደሚታነቅ ሰው ባዶ ኪስ የላክከኝ?፤
.
ፍቃድ ትዕዛዝህን
ላከብር ልበዛ ኑሮ ልጀምር ስል፤
እንዳልከው አልሆነም
አብስትራክት ሆኗል የዚህች ምድር ምስል፤
.
ፈጣሪ ሆይ ፍረድ!
በደላቸው በዛ ትዕግስትህን አይተው፤
የገዛ መሬትህን
እየሸጡልኝ ነው በስንዝር ለክተው፤
.
ወይ ምድርህን ስጠኝ
ወይ ስንዝሩን ቀማ፤
መሬቴን ብቻ ሆኗል
የዚህች ምድር ዜማ፤
እኔ አላማረኝም
መሬትህን ውሰድ በሠው ሳትቀማ፤

🔘ልዑል ሐይሌ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍2010
?ወይስ እግዚያብሄር…?›› ትንፋሽ ወሰደችና ንግግሯን ቀጠለች….‹‹….ልጄ  ወተት ያስፈልጋታል...እኔም መብላት ባልችልም ቀምሼም ቢሆን ማደር አለብኝ...እናቴም አየር ስባ ብቻ አይደለም የምትኖረው….አንገታችን የምናስገባበትን እና ጎናችንን የምናሳርፍበት ደሳሳ ጎጆም  ከመንግስት በችሮታ የተሰጠን ሳይሆን በ6000 ብር የተከራሁት ነው..ነው ወይስ አራስ ልጄን  እና ደህነት እና በሽታ ተባብረው  ያደቀቋትን እናትኔን  ይዤ ጎዳና በመውጣት መንገድ ጠርዝ ጨርቅ አንጥፌ ልለምን?ለተቀማጭ ሰማይ ቅርቡ ነው አሉ….ዳሩ ወንድ አይደለህ.. ማስታቀፍ አንጂ መታቀፍ ምን እንደሆነ ጣጣውን እና መዓቱን የት ታውቃለህ?፡፡››

በንግግሯ ደነዘዝኩ ..ጭንቅላቴን ራስምታት ሲወቅረኝ ይታወቀኛል‹‹ይቅርታ ..ስሜታዊ ሆኜ ነው… አሁን ልጅሽን ማን ነው የሚጠብቀልሽ?››ስል ቀዝቀዝ ብዬ ለስለስ ባለ የድምፅ ቃና ጠየቅኳት፡፡

‹‹እናቴ››

‹‹አይቸገሩም?››

‹‹ታስቸግራለች..ግን ብዙ ጊዜ አዳር አልሰራም… ሁለትም ሆነ ሶስት ሰዎችን አግኝቼ ሾርት ከሳራው በኋላ ያገኘኋትን ብር ይዤ ስድስትም ሳባትም ሰዓት ወደቤቴ እገባ ነበር… ዛሬ ግን እንደዛ ስላልቀናኝ ነገ ደግሞ የግድ የቤት ኪራዬን መክፈል ስላለብኝ እና ለዛ የሚሆን በቂ ብር እጄ ላይ ስለሌለ ነው አዳር ለመስራት የወሰንኩት፡፡››

‹‹ሞባይሌን አወጣሁና ሰዓቴን አየው 5፡25 ይላል..ኪሶቼን በረበርኩና ጥዋት ለታክሲ ይሆነኛል ብዬ ሀምሳ ብር ብቻ አስቀረሁና ሌላውን መዳፎ ላይ አስጨበጥኳት.. ከተስማማንበት ሂሳብ ቢያንስ በእጥፍ ይበልጣል….

‹‹በቃ… ለልጅሽ ሂጂላት››

‹‹ለምን?››

‹‹በቃ ሂጂላት››

‹‹ቢያንስ አንዴ ተጠቀምና  ልሂድ››

‹‹አይ አልችልም ስሜቴ ደፈራርሷል››

ለመጀመሪያ ጊዜ ፈገግ አለች..ለሽርፍራፊ ሰከንድ ቢሆንም ውስጧ ያለችው አሮጊት ስትከሳ እና ከውጭ የሚታየው ወጣትነቷ ሲፈካ ታዘብኩ‹‹ በጣም ነው ማመሰግነው..በእውነት ከጭንቀት እና ከስጋት ነው የገላገልከኝ….፡፡በድኔ ብቻ ነበር እዚ ያለው…፡፡ ስጋዬም  ነፍሴም ልጄ ጋ ነበር፡፡››እየመረቀችኝ ልብሶቾን ለበሰች… ሞባይሌን ተቀብላ ቁጥሯን መዘገበች ና መለሰችልኝ‹‹ቁጥሬ  ነው ብትደውልልኝ ደስ ይለኛል›› አለችኝ፡፡

‹‹እሺ እደውልልሻለው.. ለማንኛውም አንቺ በርቺ››

‹‹ወድጄ እበረታለው..››አለችኝና ንግግሯን ቀጠለች‹‹በጣም ይገርማል ››አለችኝ፡፡

‹‹ምኑ?››

‹‹ወንዶች ስትባሉ  እንደየመልካችሁ  ባህሪያችሁም ብዛቱ ..ስንቱ አውሬ እና ማሰብ የተሳነው የአእምሮ ድኩማን አለ መሰለህ… እነሱን አስበህ በአዳም ልጆች ተስፋ ልትቆርጥ ስትል ደግሞ እንደ አንተ አይነት በግ  ያጋጥማሀል፡፡››

‹‹በግ?››አልኰኳት … ደንግጬም ተገርሜም፡፡

‹‹ይቅርታ በግ ስልህ ሞኝ ለማለት ፈልጌ አይደለም… ፡፡የዋህ እና መልካም ሰው  ለማለት ነው ..ለማኛውም ብትደውልልኝ ደስ ይለኛል ፡፡ቆንጆ እና የምታምር ልጄንም አሳይሀለው››

‹‹እሺ አይልሻለሁ..››

‹‹እሺ ቻው››ብላኝ  በራፉን ከፋታ በመውጣት መልሳ ዘጋችልኝና ሄደች፡፡እርምጃዋ ቀስ እያለ እየደበዘዘ..እየደበዘዘ ለጆሮ እየሳሳ በስተመጨረሻ ጭልም ብሎ ሲጠፋ ተሰማኝ…፡፡

ግን ነገ ወይ በማግስቱ እደውልላት ይሆን? በውስጤ የተጫረ ጥርጣሬ የወለደው ጥያቄ ነበር፡፡ልደውልላትማ ይገባል….ስለዚህች ልጅ ታሪክ ጠለቅ ብዬ ባውቅ ደስ ይለኛል.. ?እንደዛ አይነት ጉጉት በውስጤ ተፀንሷል፡፡

ተፈፀመ

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍3224
#ሞት_አያምም!!!

እኖር ብዬ ብታረድም
ለመኖር ስል ብሰደድም
እኖር ብዬ ብዋረድም
ዘጠኜ ሞቴን ብሞተው…
አንዴ እንደመኖር አይከብድም!
መኖር ከመምት አይልቅም
ሞት እንደሕይወት አይጨንቅም፡፡
………………………………
የሞተ ‹‹እሞታለሁ›› ሲል…
በጭራሽ አያውቅም ፈርቶ፡፡
ያልኖረ አያውቅም ሞቶ።
።።።።
መኖር እንጂ የሚያስፈራኝ
መኖር እንጂ የሚያስገፋኝ
መኖር እንጂ የገደለኝ
መኖር እንጂ የበደለኝ
ሞት አያምም ካቆሰለኝ
ምት አያምም ከገደለኝ!

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍125🔥2
#ቀረሽ_እንደዋዛ

እንደ ድመቶቹ
የትም እንደሚያድሩት
እንደ ስልክ እንጨቶች
እንደ ዛፍ ሀረጎች
እንደ ቤት ክዳኖች
ብርድ አቆራመደኝ
ስጠብቅ ስጠብቅ
˝ትመጫለሽ ብዬ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ
የልጅነት አይኔ ሟሟ እንደ በረዶ˝
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር
ትመጫለሽ ብዬ ባዝን ባንጎራጉር
ትወጫለሽ ብዬ በበራፍሽ ብዞር
ብርድ አቆራመደኝ
የመንገድ መብራቶች አይተው አፌዙብኝ
ውርጩ ቀለደብኝ
ጨለማው ሳቀብኝ
አለመምጣትሽን አውቀዋል ያውቃሉ
መስኮቶች ጨልመው
ቤቶች ተቆልፈው
ከተማው ሲተኛ
አይተዋል ያያሉ
አለመምጣትሽን
አውቀዋል ያውቃሉ፡፡

🔘ገብረ ክርስቶስ ደስታ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍103
አለም ትዞራለች የተባለው ሳይንስ
         አሁን የለው ዋጋ፣
አለም ዛሬ ቆማ ሰው እየዞራት ነው
         እንጀራ ፍለጋ።

🔘ስፍራዬ ጥላዬ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
🔥112
ስትመጪ
ክንዴ በስተራስጌ ክንፍ አቆጠቆጠ
የደጅ አፌ ዳገት፣ ዐይኔ ፊት ቀለጠ

ስትሄጂ
ጸሐዩ ፈረጠ፣ ቁልቁለቱ አበጠ
የቀዬው አብሪ ትል በጽልመት ተዋጠ።

በዳፍንታም አለም፣ ጠባቂ ሲተጋ
እንኳን ቀን ጨልሞ፣ ሌሊቱ ሲነጋ...

መምጣትና መሄድ ቀን ይቀያይራል፥
ምላስሽ ያጎድፋል፣ ምላስሽ ያጠራል
ትንፋሽሽ ያጠፋል፣ ትንፋሽሽ ያበራል።

  🔘ዮሐንስ ሞላ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍5
#ወህኒ

ካቻምና በመስቀል ድፎ ባርኬአለሁ።
ዘንድሮ በጩቤ አጥንት ወግቻለሁ።

          ለምን እንዳትሉ፤
           በቃ ሆነ በሉ፤
           የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።

አምና ደግ ነበርኩ ፣ ክፉ ሰው ዘንድሮ
ትናንትና ምሁር ፣ ዛሬ ግን ደንቆሮ ።

            ለምን እንዳትሉ ፤
            በቃ ሆነ በሉ ፤
            የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።

መሆን አምሮኝ ያውቃል፤ ፖለቲከኛ ሰው ፣ ኃያል የጦር መሪ ፤
ተመኝቼም ነበር ለመሆን አዝማሪ ፤
ገጣሚ ለመሆን ስንኝ ቋጥሬአለሁ ፤
ደራሲ ለመሆን ተስዬም አውቃለሁ ፤
ሞዴል አርሶአደርም ለመሆን ፈልጌ ፣
አስጠምጄ ነበር ከ 4 ኪሎ ግርጌ ።
ኢንጂነር ዶክተርም ልሆን ነበር እኮ ፤
እንደዚህ ሆንኩ እንጂ ነገር ሌላ ታኮ ።

            ለምን እንዳትሉ፤
            በቃ ሆነ በሉ ፤
            የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።

አንድ ሰው አንድ ነው ከንግዲህ አትበሉ ፤
            የሰው ልጅ ወህኒ ነው ፤
እልፍ አዕላፍ ሰዎች ታስረው የተጣሉ ፣
መውጫ አጥተው ነው እንጂ፣አንድ ሰው ውስጥ አሉ።


🔘ይስማዕከ ወርቁ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍11
#እውነት_ወደ_ኋላ

ገንዘብ ካለው ጋራ
ፍቅር አይኖርም ወይ ብለሽ ጠይቀሻል!?
እኔ ያንቺን እንጂ
የሌላን አላልኩም እጅግ ተሳስተሻል
አይኖርም አላልኩም...አይጠፋም ይኖራል
ይኖራል
ይኖራል
ግን?...
ከባለሐብት ጋር
ተፋቅራ 'ምናያት የቷም አይነት እንስት...
           'ምን ' ትሁንም 'ምንም '
የሕይወት ታሪኳን ወደኋላ ሄደን ....ጥቂት ብንገመግም
አንድ ቡና ለሁለት ....
አብራ የጠጣችው አንድ አፍቃሪ አታጣም ።

🔘ኤፍሬም ስዩም🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍61
#ያገሬ_መንታ_ገፅ

ውዷ ባለቤቴ፤
እኔም ወግ ይድረሰኝ፤
ወፍራም ሳግ ይውረሰኝ፤
አባት ልሁናቸው ውለጂልኝ መንታ፣
አንድ ሀገር የሚያድን አንዱ የሚፈታ፣
አንዱ ቤት ሚያፈርስ አንዱ 'ሚሆን ዋልታ፡፡
.
.
እንዲያ ነው እንግዲህ፤
በውላ'ጅ አካልሽ፤
መገፋት ቢተርፍሽ፣
ቢጠልዝሽ ደርሶ አካልሽን ቢያጎነው፣
ከቶ አትገረሚ፤
አንዱ ሲንድሽ ነው "ሌላ"ሽ 'ሚጠግነው፡፡

እናልሽ አለሜ፤
እናልሽ ህመሜ፤
እንዲያ ነው ዘመንሽ እንዲያ ነው ዘመኔ፣
አንቺን ሲነኩሽ ግን ታምሜያለሁ እኔ፡፡


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍8
#የኔ_ዓለም!

እንዳንቺ  ሚጣፍጥ - አንጀት የሚያረካ
ጣፋጭ የለም ለካ!
ጥዑም ናቸው ያሉኝ ማርና ቸኮሌት
ካንቺ ሲነፃፀር መረሩኝ እንደ ሬት።

#ማርያምን !

ከድምፀትሽ ልቆ - 'ሚሰማ ሙዚቃ
ከአንባሰል ከባቲ ከብሉዝ ትዝታ
ወድያም ከብሉዙ ደግሞም ከአፍሪቃ
አንድም የለም በቃ !

#ማርያምን!

ካገኘሽ ጠቁሚኝ
ከሄድሽ ብትነግሪኝ.. .
ካንቺ ጋራ ስሆን ሀዘን ጭንቄን ሽሮ
የደስታ ወሰኔን አለቅጥ አንሮ
የሚገርመኝ የለም ከዓለሟ ተፈጥሮ!

ምንድናት ጨረቃ?
ምንድናትስ ፀሀይ ?
ካንቺ አንፃር ስትታይ.. .

ሀዋሳ ላንጋኖ.. . ቢሾፍቱ ሪዞርት
እውን ካንቺ በልጠው እኔን ሊያስደስቱኝ
ኸረ በማዬ ሞት !

#ማርያምን...
የቱ ኮሜዲ ነው የትኛው ቀልደኛ
እኔን የሚያደርገኝ የወሬው ምርኮኛ?
ደግሞ ካንቺ በላይ
እኔን ለማሳሳቅ ማነው የሚደፍረው ?
ባንቺ ጨዋታ ነው
የተደበቀውን.. . ጥርሴን የምገልጠው።

#ማርያምን !
እንደውም ባጭሩ.. .
አሁን ይሄ ግጥም
የቃላት ጥርቅም
እጅግ መሳጭ ሆኖ አንባቢው ቢያደንቅም
ካንቺ ግን አይበልጥም።

ማርያምን...

🔘ሚካኤል አስጨናቂ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍93
#የተጀመረ_አንጀት
በደል ያሰለለው
ጥቃት የበዛበት
         የተገዘገዘ
የተጀመረ አንጀት
        ባልጎለደፈ ቃል
        ባልገረጀፈ ጣት
        በስሱ ካልነኩት
በፍቅር ካልዳሰሱት
       በስስት ካልያዙት
በእውቀት ካላገሙት
      በበደል ፣ በጥቃት
      ዳግም ከደፈቁት
      ደፍቀው ከጓጎጡት
የተብሰከሰከ ፣ የተጀመረ አንጀት
      እንኳንስ ሊቀጥል
ጥቂት ይበቃዋል ቆርጦ ለመለየት ።

🔘ጌትነት እንየው🔘


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍64
#ፍሰሽ

ፍሰሽ በአካላቴ እንደ ወንዙ ፍሳሽ
ወስዶ እንደሚሄደው ልክ እንደ ደራሽ
ውሰጂኝ ውሰጂኝ አስምጪኝ በሞቴ
ይነከር በፍቅርሽ ይራስ ሰውነቴ።

??

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
5👍2
#ይቅር_ታ

በትንሽ ጭንቅላት
በእንጭጭ ልቦና ፥የተጣሉ ለታ፤
ዳግም ለመመለስ
ከሰማይ ከፍ ያለ፥ዳገት ነው ይቅርታ!


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍72
#ላምላክህ_ላምላኬ!

ጀሊሉ ይዳብስህ - ይበርቱ ክንዶችህ
የማርያም ልጅ ደርሶ - ያቁምህ በእግሮችህ!
እግዜር በሽታህን - ይንቀለው ከገላህ
ፈውስ ያውርድልህ - የታመንከው አላህ!
ያደከመህ ይድከም - ይራገፍ በሽታህ
በገጽህ ላይ ይፍሰስ - ይመለስ ፈገግታህ!
ታሞ ተኛ ሲሉኝ - ላፍታ ተንበርክኬ
እንዲህ ነው የጸለይኩ - ላምላክህ ላምላኬ!!

🔘ዘውድአለም ታደሰ 🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
11👍1
#ሳንመጣ_ለመቅረት

አቤት የኛ ነገር
ዳገት ስንሻማ ከቁልቁለት ገባን
ቀኙን ስንፈልገው ከግራ ተጋባን
ማን መቶ ያግባባን?

በቃል አልባ ቅኝት በተስፋ ቃል ኪዳን
ከደገስነው ድግስ መራራ ሬት ቀዳን
ድግሱም አልቀና
አልጠገብን አልጠጣን ከቀዳነው እሬት
ይኸው ነጋ ጠባ
ማር ማር እንላለን ሳንወጣ ከምሬት
አቤት የኛ ነገር

ስንፈልግ ተጣጣን
ስንሸሽ ተቀጣን
ከመስከረም ጡቶች መከራ እየጠባን
በተራበ አንጀት ስንት በቀል አባን?
በታወረ አይናችን ስን ጊዜ አነባን?
የሆነውን ሁሉ
ያየነውን ሁሉ በማይችለው ቁጥር
አንድ ነን ሁልጊዜ ለዜሮ ስንጥር
መሰንበት ስንሻ ለመኖር ስንቃትት
በወጉ መሞትም ሆኖ አረፈው የክት
አሟሟቴን ይመር
የሚል ተረታችን ያኔ እናዳልተናቀ
ዘመን ቢቀያየር ዛሬ ተናፈቀ
ከዘመኑ በልጦ ቢንቀለቀል ግርሻት
ነገር ላይገናኝ ደጋግሞ በመሻት
ልክ እንደሁልጊዜው
በለመድነው ሙሾ በምናውቀው ተረት
መጣን ብለን እንሂድ ሳንመጣ ለመቅረት

??

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
9🔥1
#እግዜር_ዝቅ_ብሎ

አልመህ ካቀድከው - ከምኞትህ ሁላ
በአይንህ መትረህ - ልብህ ከሚሞላ
ከምድር በረከት - ስጋን ከሚያረካ
ከሰማይ ረድኤት - ነፍስን ከሚያፈካ
:
:
የትኛውን ልስጥህ - ብሎ ቢጠይቀኝ
ካንድ አንቺ በስተቀር - የቱንም አልመኝ

???

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
9👎1