አትሮኖስ
277K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
450 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሀርሜ_ኮ
:
ክፍል- #አስራ_አንድ #የመጨረሻ_ክፍል

:
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

...ሁሉ ነገር በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ ተቀያየረ …..በቤተሰቡ ውሳኔ ትርሲትን
በቋሚነት እናቴን ደግሞ በተመላላሽነት አስከትዬ በአባቴ ወደተዘጋጀልኝ መኖሪያ
ቤት ገብቼያለው…አያችሁ ሰውዬው ማለት ትቼ አባቴ እያልኩኝ ነው…ያ ማለት እኔም እየተቀየርኩ ሳይሆን አይቀርም…? በቀላል ሂሳብ የእኔንም ልብ
እየተቆጣጠረው ነው…የእናቴንማ ቆየ …መቀጣጠር፤ መገባበዝ፤ እንደ አዲስ
ፍቅረኛሞች መጎነታተል ጀምረዋል…እና በቅርብ የድሮ ፍቅራቸው ያገረሻባቸዋል
ብዬ በደንብ አሰባለው….
አባቴ ያዘጋጀልኝ ቤት ሆኜ አባቴ ባዘጋጀልኝ የህክምና መሳሪያዎች በመታገዝ
ሙከራው በከፍተኛ ጥረት እየተከናወነ ነው ..የመጣው ሽማግሌ የፈረንጅ
ዶክተር በሳምንት ሁለት ቀን ወደ ሆስፒታል ወስዶኝ ከሌሎች ዶክተሮች ጋር
በመሆን በተለያዩ ዘመን አመጣሽ የህክምና ማሽኖች በመታገዝ እንድመረመር
ያደርገኛል…ያው ይመራመሩብኛል ማለት ይቀላል..ወጣቷም ቴራፒስት በልዩ
እንክብካቤ እና ጥንቃቄ ስራዋን እየሰራች ቢሆንም ከትርሲት ግን ይሁንታን
ሳላላገኘች የእሷን ማመናጨቅና ግልምጫ አማሯታል…ቢሆንም ተስፋ
አልቆረጠችም….ይሄም ፍሬ እንደሚያፈራ ፍንጭ እያሳየ ነው..የእግሮቼ ጣቶች
ተራ በተራ መንቀሳቀስ ጀምረዋል…
ዛሬ እማዬም ሆነ ትርሲት አብረውኝ ናቸው …ጊዜው መሽቷል …..ተከታታይ ፊልም
ስናይ ስለቆየን ሳናስበው ነው አምስት ሰዓት የሆነው..እናም ሁላችንም ተዳክመናል…
‹‹በሉ ተነሱ እንተኛ ››አለች እናቴ ..ትርሲት በፊቱኑም እናቴ እንደዛ እስክትል
እየጠበቀች ያለ ይመስል ቶሎ ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ጋደም ብዬበት
ከነበረው ሶፋ ወደ ዊልቸሬ አዘዋወረቺኝና እየገፋች ወደ መኝታችን አመራን …
እናቴም ከተቀመጠችበት ተነስታ ከኃላ ስትከተለን ይሰማኛል…ከዛ ሌለኛው
መኝታ ክፍል ውስጥ ገባች፡፡ እኔና ትርሲትም መኝታ ቤታችን እንደገባን
አወላልቀንና ተቃቅፈን ለመተኛት የአስር ደቂቃ ጊዜም አላባከንም…እኔ የምጠቀምበት መኝታ ክፍል በጣም ሰፊና ሁለት አልጋ ማዶና ማዶ ሁለቱን ትይዩ ግድጋዳዎች ተጠግቶ የተዘረጋበት ነው፡፡
ሀኪሞቹ ቀኑን ሙሉ ከወዲህ ወዲያ ሲያንገላቱኝ ድክም ብሎኝ ስለነበር
ወዲያው ነው ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የወሰደኝ…ብቻ ከምን ያህል ሰዓት ቡኃላ
እንደሆነ አላውቅም ኃይለኛ የበር መንኳኳት አረ ከመንኳኳትም አለፍ ያለ
የመንጎጎት አይነት ድምጽ ነበር ከእንቅልፌ ያባነነኝ….አይኔን ስገልጥ ትርሲትም
በድንጋጤ እና በመበርገግ ‹‹ማነው… ?ምንድነው ? ››እያለች በስስ ቢጃማ
የተሸፈነ ሰውነት እያምታታች ከአልጋው ዘላ ስትወርድ የመኝታ ቤታችን በራፍ
ተበርግዶ ሲከፈት ጥቁር ጭንብል የለበሱ ሁለት ወጠምሻ ሰዎች እናቴን
ከግራና..:
ከቀኝ አንጠልጥለው እየገፈታተሩ ይዘዋት ወደ ውስጥ ገቡ..ሶስተኛ
ጓደኛቸው በአንድ እጁ ሽጉጥ በአንድ እጅ ደግሞ የሚያብረቀርቅ ጩቤ ወድሮ
ይከተላቸዋል…
‹‹ እኔን እንደፈለጋችሁ ..ልጆቼን አንዳትነኩብኝ..ልጆቼ ጫፍ
እንዳትደርሱ….››እያለች ትማፀናቸዋለች ‹‹ምንድነው ምትፈልጉት …እናቴን
ልቀቋት …የፈለጋችሁትን ይዛችሁ ውጡ››ትርሲትም እየተርበተበተች መለፍለፍ
ጀመረች…..እኔ በተኛውበት ድንዝዝ እንዳልኩ ነው …የማየው ነገር በህልም
ይሁን በእውን እርግጠኛ መሆን አቃቶኛል..እንዴት እንዲህ ሊሆን ቻለ …?
ግቢውን ሚጠብቅ ዘበኛ አለ እሱን እንዴት አለፉት….?
‹‹አትለፍልፊብን››ብሎ አንዴ በጥፊ አላሳት ትርሲትን…ፀጥ አለች….
‹‹በል እሰራት›› አለው… ሽጉጥና ጩቤ የደገነው ባዶውን ያለውን ጎደኛውን
‹‹መጀመሪያ ጎረምሳውን ባስረው አይሻለም…?››ጠየቀ ወደ እኔ እጠቆመ
‹‹ምኑን ታስረዋለህ .. ?ፈርቶ ከአልጋው ላይ መንቀሳቀስ አቅቶት በድን ሆኖ
እያየህ››መለሰለት በእኔ በማፌዝ
‹‹አረ እግዚያብሄርን ፍሩ… ልጄ መንቀሳቀስ የማይችል ዊልቸር ተጠቃሚ
ነው…››እናቴ ነች ተናጋሪዋ፡፡
‹‹አሀ እንደዛ ነው..?ስራ ቀለለልና….››አለ አንድ ሌላው እንደተባለው ከሰፊ
የጃኬት ኪሱ ውስጥ ገመድ አወጣና የትርሲትን እጆች ወደኃላ ጠምዝዞ አንድ
ላይ በማጣመር ጠፈነጋትና ከአልጋው የራስጌ ብረት ጋር አሰራት ‹‹እሷንም
ልሰራት?››ጠየቀ እናቴን እያየ..
‹‹አይ መጀመሪያ እሷኑ አፎን ክደንልኝ… አትለፍልፍብኝ ››ከአልጋው ላይ ለብሰን
የነበረውን አንሶላ መዥርጦ አወጣና በጩቤው የሚበቃውን መጠን ያህል
መጥኖ ሸረከተውና ለጓደኛው አቀበለው..
እሱም የትርሲትን አፍ በጨርቁ ጠቀጠቀና ..እናቴንም በተመሳሳይ ሁኔታ
አሰራት… በል አንተ ጠብቃቸው እኛ የሚጠቅም ዕቃ ከቤት ውስጥ እንምረጥን
በመኪናችን እንጫን …ስንጨርስ መጥተን እንነግርሀለን››ብለውት ሁለቱ
ተያይዘው ወጡ…የቀረው ጩቤውንም ሽጉጡንም በእጆቹ እያሽከረከረ የመኝታ
ቤቱን በራፍ ከውስጥ ቀረቀረና ፊት ለፊት ያለው ደረቅ ወንበር ላይ ተቀመጠና
ሶስታችንንም በማፈራረቅ መመልከት ጀመር..የተቀመጠበት መቀመጫ እኔ
ከተኛውበት አልጋ የሁለት ሜትር ያህል እርቀት አለው….ሰውዬው ሲታይ
ወጠምሻ እና አስፈሪ ነገር ነው..ምንም እንኳን በለበሰው ጭንብል ምክንያት ፊቱ
ባይታየኝም የሆነ ጥቁርና አሳፈሪ እንደሆነ እንዲሁ መገመት ችያለው
..ቀስ በቀስ እይታውን ከማፈራረቅ ወደ ማተኮር አሸጋገረው..አዎ ዓይኖቹን
ትርሲት ላይ እንደሰካ ፈዞ ቀረ …አዎ የሚያየው ደግሞ የተጋለጠ ገላ
..ስትንፈራገጥ ቢጃማዋ ወደ ላይ ስለተሰበሰበ የተራቆተ ጭኖን ነው…ድሮም
ለአመል ያህል ስውነቷን ይሸፍንላት የነበረውን ቢጃማ አሁን ጭረሽ ወደ ላይ
ተሰብስቦ ከውስጥ የለበሰች ሰማያዊ ፓንት እስኪታይ ድረስ ለእይታ
ተጋልጣለች…ትዝ ይለኛል አሁን የለበሰችውን ፓንትም ሆነ ቢጃማ የገዛችላት
እናቴ ነች.. ፡፡
ሶደሬ ሄደን በነበረበት ቀን …አሁን በዚህ ሰአት ይሄንን ማሰብ ምን ይሉታል …?
ሰውዬው በተቀመጠበት በመቁነጥነጥ ምራቅ እየዋጠ ነው..ምኑም
አላመረኝም..፡፡ቀስ ብሎ ተነሳና ቆመ‹‹አንቺ እንዴት አባሽ ታምሪያለሽ?››አለ የዛን
ጊዜ የሶስታችንም አይን በድንጋጤ ፈጠጠ..መላ ነገራችን በስጋት ታፈነ…
‹‹ይሄን ገላማ ጎደኛቼ እኪመጡ ዘና ልበልበት››
‹‹የፈራውት ደረሰ ..››አልኩ በልቤ አሁን እንዴት ነው ሚሆነው…?በምንስ ተዐምር
ነው ከዚህ ጉድ የምንወጣው…?እንዲህ ማፈቅራትን ሴት እንዴት ፊቴ
ይደፍራታል…?ከዛስ ብኃላ ሕይወታችን እንዴት ይቀጥላል…?ለመጀመሪያ ጊዜ
ያለውበትን ሁኔታ አምኜ መቀበል አቃተኝ….፡፡ ውስጤ በቁጣና በንዴት ከውስጥ
ይቀጣጠል ጀመረ … ሰውዬው በሀሳቡ እንደገፋበት ነው…የያዘውን ጩቤ ወንበር
ላይ እንዳስቀመጠ ሽጉጡን ብቻ በአንድ እጁ ቀስሮ ወደ ትርሲት ሄደና እጆቾን
ፈታቻው…እጆን አንጠለጠለና ወደ ሌለኛው አልጋ እየጎተተ ይዞት ሄደ …እጆቼን
እና አንገቴን እያወራጨው የሆነ ነገር ለማድረግ እየሞከርኩ ቢሆንም እሱ ግን
ነገሬም አላለኝ..እናቴም እጆቾም አፎም ስለተለጎመ አቅመ ቢስ ሆናለች….
ትርሲትን አልጋው ላይ ዘራራትና አንደኛው እጆን የአንዱ አልጋ ጫፍ ብረት ጋር
ሌለኛውን እጆን ከሌለኛው ብረት ጫፍ ሰትሮ አሰራት… ከዛ ደግፎ ሙሉ በሙሉ
ወደ አልጋው አወጣትና ዘረራት…እሷ በታሰረችበት በፍርሀት ጉንጮቾ ቀልተው
ፊ.ቷ በእናባ እየታጠበ… በአይኖቾ ስትለማመጠውና ስትለምንው ሳይ ውስጤ
ተገለባበጠ..ምንው አምላክ ለ5 ደቂቃ በተአምሩ ጤነኛ ቢያደርገኝ…?በዚህ
ሰዓት የመፅሀፍ ቅዱሱ ሳምሶን ነው ትዝ ያለኝ… በፍቅረኛው ደሊላ ተታሎ
ኃይሉን አጥቶ በጠላቶቹ እጅ ወድቆ በነበረበት በዛ ክፉ ደቂቃ የተሰማው ስሜት
ነው አሁን እኔንም እየተተሰማኝ ያለው.
#ወንጀልና_ቅጣት #የመጨረሻ_ክፍል
:
ክፍል-ሶስት

:
:
በ ሕይወት እምሻዉ

...ሃጥያቴን በብቅል ግፊት ከተናዘዝኩ በኋላ መቼም ሰው አታደርገኝም…የኔ እና የእሷ ነገር አለቀ ደቀቀ ብዬ…ሂሳቤን አገኛለሁ ብዬ ስጠብቅ ሲሻት ተደብራ ከመጋገር፣ ሲሻት ከሰላምታ ያላለፈ ነገር ባለመናገር ከመቅጣት በቀር ትታኝ አልሄደችም።
እንደ ድሮው ቤቴ ትመጣለች፣ ስደውል ታነሳለች፣ እንገናኝ ስላት ታገኘኛለች። አብራኝ መተኛት ሲቀራት አብራኝ ትሆናለች። ሰብሬያት እንዳልሰበርኳት፣ አኩርፋኝ እንዳላኮረፈችኝ ትሆናለች። ዝም ስትለኝ ሰአቱ ቀን ይሆንብኛል። ቀኑ ሳምንት….ቅጣቴ ይሄ ነው? የሃጥያቴ ክፍያ በዝምታ መንገብገብ ነው?
ሶስት ቀን በሶስት አመታት ፍጥነት እየተጎተተ ካለፈ በኋላ ቁርጤን ልወቅ ብዬ ወሰንኩ። ቃተኛ ቁጭ ብለን ጥብስ ፍርፍራችንን በተለመደው ዝምታ ስንበላ
– ቤዚ…አልኳት
– እ….
መስረቄን ካወቀች ወዲህ ወዬዎቿ…በ እ…ተተክተዋል። ምንድነው እ ብሎ ነገር? ላናግርህ አልፈልግም ስለዚህ ከአንዲት ፊደል በቀር አይገባህም ነው?
– ይቅር ብለሽኛል? አልኳት ጥብስ ፍርፍሩን መብላትም ማየትም አቁሜ እያየኋት
– እ?
ኡፋ! …..የምን እ ነው?
– ይቅርታ አድርገሽልኛል ወይ….
– እዚህ ሰው ፊት ስለሱ ማውራት አልፈልግም…ቤት ስንሄድ እናወራለን….አለችኝ …ለአስተናጋጁ ሲሆን ከብርሃን የተሰራ የሚመስል ቀይ ዳማ ፊቷ ለኔ ሲሆን ባንዴ የሚዳምንላት እንዴት ነው?
ዝም ብያት እስክንጨርስ ጠበቅኩ።
ቤት ገባን። መልሼ ጠየቅኳት።
– አላውቅም…እያሰብኩበት ነው….አለችኝና ወደ መኝታ ቤት ሄደች።
ጓደኖቼን አማከርኩ። ይቅር ባትልህ አብራህ አትቆይም..ያደረግከው ነገር እኮ ከባድ ነው ትንሽ ታገስ…እሷ ሆና ነው እንጂ ሌላ ሴት ብትሆን ይሄኔ ቆርጣልህ ነበር…ምናምን ሲሉኝ የዝምታ ቅጣቴን በፀጋ ለመቀበል ወስኜ ቆየሁ።
ትንሽ ጊዜ ካለፈ በኋላ በአንዱ ቀነ ከመሬት ተነስታ ላንጋኖ እንሂድ ምናምን ብላ ወጠረችኝ።
– ለምን አልኳት
– እኔ ስለፈለግኩ አለችኝ። ፊቷን ሳየው ግን ‹‹ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛህ እና የፈለግኩትን ነገር ማድረግ ስላለብህ›› ተብሎ የተፃፈ መሰለኝ። እጄ ላይ ብዙ ብር አልነበረምና
– ደሞዝ ስቀበል…ከአስር ቀን በኋላ ብንሄድስ? አልኳት በሚለማመጥ ድምፅ…
– እኔ አሁን ነው መሄድ የፈለግኩት…ካልፈለግህ አልፈልግም በል….ብስጭትጭት አደረጋት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ፣ ከጓደኛዬ ብር ተበደርኩና ሄድን።
ላንጋኖ ስንደርስ አይቼ የማላውቀውን ክር ሊሆን ትንሽ የቀረው ጡትና ቂጥ በአግባቡ የማይይዘ ‹‹የዋና ልብስ›› ለብሳ ልክ ብቻዋን እንደመጣች…ልክ ወንድ ልታጠመድ ታጥባ ተቀሽራ እንደወጣች ሴት ቢቹ ላይ ስትንቧችበት ዝም ብዬ አየኋት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ብጉራቸውን እያፈረጡ ተጠግተዋት ሰልክ ቁጥር እየጠየቋት እንደሆነ የሚያስታውቁ ወንዶች ሲያንዣብቡባት፣ ሲያወሯት፣ በሚጢጢ ጨርቅ የተሸፈነ ምንተእፍረትዋን በአይናቸው ሲያወልቁ እያየሁ ዝም አልኳት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ማታ ክፍላችን ገብተን ለማንም ኤግዚቢሽን ያቀረበችውን ገላዋን ለመንካት እንኳን ሰትከለክለኝ…እንደ እሾህ ስትሸሸኝ….አትንካኝ ሬዲ አይደለሁም ብላ ፍቅርን ስትነፍገኝ ዝም አልኳት።
አዲሳባ ተመልሰን የማልወደው ጫጫታም ካፌ እየወሰደች ለሰአታት አርፍዳ ስትጎልተኝ፣ አምስት ደቂቃ ዘግይቼ ቤት ከገባሁ አንበሳ ሆና ስትቆጣኝ፣ ከጓደኞቼ እንድቆራረጥ አትሄድም ብላ ስታስቀረኝ፣ የዘመዶቿን ሰርግ ይዛኝ ሄዳ ብቻዬን ትታኝ ስትረሳኝ፣ ሃጥያቴን ነግራቸው የናቁኝ ሴት ጓደኞቿን በሙሉ አምጥታ (አራት ናቸው) የሁለት መቶ ሃምሳ ብር ክትፎ ስታስጋብዘኝ…ከሌላ ሴት ተኝታቸለሁ እና ቅጣቴን ልቀበል…ሂሳቤን ላግኝ ብዬ ዝም አልኳት።
ይባስ ብላ አንዷ ቀለብላባ ጓደኛዋ በንቀትም በሴሰኝነትም ተነድታ ስልክም እየደወለች፣ ቤቴም ‹‹ቤዛ የለችም›› ብላ የሌለችበተትን ሰአት መርጥ እየመጣች እንድተኛት ስትጋብዘኝ…ከአንዷ ጋር ከማገጥክ ከእኛስ ጋር ብትማግጥ በሚል ሁኔታ ስትቀበጠበጥብኝ ጥፋቱ የኔ ነው ብዬ ዝም አልኳት።
ከሳምንታት በኋላ ግን እጅ እጅ እያለኝ መጣ። እኔን አስቀንታ ለመመለስ የምትለፋው፣ ላገኘችው ሰው ሁሉ ሃጥያቴን ነግራ ስሜን የምታጠፋው፣ በውሃ አረረ ፊቴን ፊት የምትነሳው፣ በሁሉም ነገር ስሜቴን የምታሸማቅቀው ነገር ከፍቅሯ እየበለጠ ነገሩ እጅ እጅ እያለኝ መጣ።
ጭራሽ አሁን ደግሞ ሃገር ውስጥ ስለሰራሁት ስህተት አልሰሙም ብዬ የተማመንኩባቸው እንደዛ የሚወዱኝ…እንደልጅ የሚንከባከቡኝ ቤተሰቦቿ ጋር ሄዳ ማውራቷ፣ ልታዋርደኝ መጨከኗ…በእኔና በእሷ ጉዳይ ማስገባቷ ልቤን አደነደነው። ልጠይቃት ይገባል። ይቅር ብለሽኛል ወይስ ቅጣቴ የእድሜ ልክ ነው? አፉ ብለሽኛል ወይስ አንቺ ካለሽበት ሕይወቴ እንዲህ ሊሆን ነው? ብዬ ልጠይቃት ይገባል።
እትዬ ሌንሴና እህቶቿ እንዲያ ባገባጠሩኝ እለት ማታ ቤት ቁጭ ብለን ወይን ስንጠጣ (ላወራት ስጀምር ነው አንዱን ጠርሙስ ጨርሳ ወደ ሁለተኛው መግባቷን ያየሁት)
– ቤዚ …አልኳት
– እ…
(እ…ን አሁንማ ለምጄዋለሁ)
– መቼ ነው እንደ ድሮው የምትሆኚልኝ? ቅጣቴ አልበዛም? አልኳት
– ያደረግከውን ነገር ረሳኸው…? ከሌላ ሴት ጋር እኮ ነው ሴክስ ያደረግከው…ሴ….ክ….ስ….
ወይኑም ነገሩም እንዳሰከራት ገባኝ።
-አውቃለሁ…አጠፋሁ…አይበቃኝም ቅጣቱ…እንዴት እንደዚህ እንቀጥላለን….ብንቀጥልስ…እስከመቼ ድሮ ለሰራሁት ጥፋት እድሜዬን ሙሉ እከፍላለሁ…
– ወር የማይሞላ ጊዜ ነው እድሜዬን ሙሉ የምትለው..
– አይደለም…
– ታዲያ…
– ማለቴ…ብንጋባ እንኳን አንድ ነገር ባጠፋሁ ቁጥር አንተ እኮ…እያልሽኝ እስከመቼ እንኖራለን…
– ሃሃ…..አሁን ነው መጋባት ያማረህ….? ደ…ፋ…ር….
ወሬያችን እንኳን እንዳሁኑ በአልኮል ፈረስ ተሳፍራ በደህናውም ጊዜ ትርጉም ያለው ነገር ሊወጣው እንደማይችል ተረዳሁና ዝም አልኳት።
– ምን ይ…ዘ…ጋ…ሃ…ል? አለች ፊደል እንደሚቆጥር ሰው ቃላቶቹን እየጎተተች…
– ጥቅም የለውም ብዬ ነው…
– ም…ኑ..
– እንዲህ ሆነሸ ማውራቱ….
– እና..ውራ…ማውራት አይደል የፈለግከው…እናውራ…
– ግዴለም ነገ ይደርሰል…
– አይ…ሆ…ን…ም አሁን እናውራ…
– ቤዚ…ይቅር
– አይ…ቀርም…እናውራ…እናወ…..ራ….
እንደለቅሶ ይሰራት ጀመር። ቤዚዬ….
– እሺ አልኳት እንዳታለቅስ…
– እሺ…ልጅቷ…እንዴት ነበረች…ጎበዝ ናት…..?
– ማ? አልኩኝ ደንገጥ ብዬ..
– እናውራ አላልክም…እናውራ….ያቺ አብረሃት የተኛሃት ልጅ…ጎበዝ ናት….ማለት…ከኔ ትበልጣለች?
ዝም አልኳት።
– ንገረኛ! እንዴት ነበረች…ትበልጠኛለች…..? ለቅሶ ጀመረች።
አቀፍኳት።
– ንገረኝ…..በለጠችኝ…ደስ አለችህ…ጎበዝ….
– ተይ ተይ በቃ…ቤዚዬ…ይቅርታ…በቃ…ይቅርታ አታልቅሺ አልኩና አጥብቄ አቅፌ ፀጉሯ ላይ…አይኖችዋን አፈራርቄ ሳምኳቸው።
– አትሳመኝ….ብላ ተፈናጥራ ተነሳች።
– እ?
– አትሳመኝ….እሷን በሳምክበት አፍ አትሳመኝ….ሚ..ኪ….ከሁሉ ሚያሳዝነኝ ምን እንደሆን ታውቃለህ…..አለችኝ ተመልሳ እየተቀመጠች።
ዝም አልኩ።
ቀጠለች-
– እወድሃለሁ…ማለቴ…ካላንተ ወንድ አልፈልግም…ጓደኞቼም ቤተሰቦቼም ቢመክሩኝም ባንተ መጨከን አቃተኝ…ሳምሪ ወንድ ልጅ አንዴ ከተልከሰከሰ ሁሌም ይልከሰከሳል…ይቅር ካልሽው እንደ ፈቃድ ነው ሚወስደው…ይቅርብሽ ብላኝ ነበር…ይሄን ታውቃለህ? እህቶቼ ለአይን ጠልተውሃል…እማዬማ ቤቴ አይምጣ ብላለች…እኔ ግን እወድሃለሁ…ልቤን ቢያመኝም…እወድሃለሁ…
– እነሱን ተያቸወ…አንቺ ከወደድሽኝ የኔ ጉዳይ ካንቺ ነው….አልኩ ፈጠን ብዬ…
– አይደለማ…..እወድሃለሁ ግን
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ ( #የመጨረሻ_ክፍል )
:
ድርሰት:-በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
ከአንደኛው መጽሀፍ መሀል ያየቻቸው ሁለት ፎቶዎች ግን ተስፈንጥራ አልጋዋን ለቃ ወለሉ ላይ እንድትቆም አደረጋት…፡፡.ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው..የምታየውን ማመን አልቻለችም..የኮማንዳሩና የወላጅ እናቷ ፎቶ ነው…አንዱ ፎቶ ሁለቱም በዋና ልብስ ሆነው ሙሉ በሙሉ አቅፎት መዋኛ ገንዳ ውስጥ ሆነው የተነሱት ነው…ሌላው ደግሞ ከንፈር ለከንፈር እየተሳሳሙ…… ይሄን ያህል ሄደዋል ብላ አታስብም ነበር ..ስልኮን አነሳችና ደወለች..እሮዝ ጋር ነው..ተነሳ..?
‹‹አሁኑኑ እፈልግሻለው››
‹‹ምነው ልጄ ምን ሆንሺብኝ..?››
‹‹መቀባጠሩን ተይና በአስቸኮይ ኩማደሩ ቤት ነይ››ስልኩን ጠረቀመችው
ሮዝ የለበሰችውን የለሊት ቢጃማ እንኳን ለመቀየር ጊዜ ማባከን አልፈለገችም…ብን ብላ ነው ግቢውን ለቃ ወደኩማንደሩ ቤት የበረረችው ..ልጄን… ልጄን ምን አደረክብኝ....?የሳሎኑን በር በርግዳ ከፈተችና ወደውስጥ ገባች…
‹‹ምን አደረገብኝ ..?ምነ ሆንሺብኝ ..?ተንደርድራ ልትጠመጠምባት ስትል ገፍትራ ከላዬ አራቀቻት….››
‹‹ይሄ የመቼ ፎቶ ነው....?››ሄለን ነች ጠያቂዋ
‹‹የቱ..? እኔጃ..››ግራ ተጋብታ መለሰች
በእጇ የያዘችውን ፎቶ ወረወረችላት .ደረቷ ላይ አርፎ ወደመሬት ወደቀ… ጎንበስ ብላ አነሳችውና ተመለከተችው..
‹‹እሺ መንም አልጀመርንም ብለሽኝ አልነበር..?››ሄለን ነች በሽሙጥ የጠየቀቻት
‹‹ያው ድሮ እኮ ነው…ግን ከተለያየን ብዙ አመት አልፎናል..?››
‹‹በቀደምለታ የመጣሽው እንታረቅ ልትይው ነበር....?››
‹‹አረበፍጽም ..ስንለያይ ተጣልተን ስለነበረ ቂም ይዞብኛል..አንቺን በማጥቃት እንዳይቀለኝ ስለፈራው ከአንቺ እንዲርቅ ልለምነው ነው…››
‹‹ኦኬ አሁን በጣም ገባኝ….ለመሆኑ ኩማደሩን እንደማፈቅረው ታቂያለሽ..?››
‹‹አታደርጊውም ልጄ..እኔ በህይወት እያለው አታደርጊውም››
‹‹አትጠራጠሪ አደርገዋለው..እንደውም ማግባት ሁሉ የምፈልገው እሱን ነው››
‹‹አረ ተይ ልጄ…እራስሽን ወጥመድ ውስጥ ለምን ትከቺያለሽ....?እሱ እኮ ውስጡ በቀል እንጂ ፍቅር የለበትም…..››
እሱ እኔን አይመለከተኝም…እንደውም እኔም አንቺን ለመበቀል ስለምፈልግ ጥሩ አጋጣሚ ነው…ለመሆኑ ምን ያል ብትበድይው ነው .. ..?ለነገሩ አንቺ አይደለሽ ምንም ብታደርጊው አይደንቀኝም….ለማንኛመው ከዛሬ ጀምሮ በመሀከላችን እንዳትገቢ ልነግርሽ ነው..አሁን የድሮ ፎቶሽን ይዘሽ ወጭልኝ…;››
‹‹በፈጠረሽ ልጄ›› እግሯ ላይ ተደፋች..
‹‹ምንም ብታርጊ ሀሳቤን አታስቀይሪኝም…ምን አልባት በአንድ ነገር..››
‹‹ምንድነው ልጄ …የፈለግሽውን ጠይቂኝ..ከዚህ ሰይጣን ራቂለኝ እንጂ ያልሺኝን ሁሉ አደርጋለው››
‹‹ያው የእኔን ጥያቄ ታውቂያለሽ… ተመሳሳይና የማይቀየር ነው…የአባቴን ማንነት ከነገርሺኝ እተወዋለው…››
‹‹አባቴን....?››ከተደፋችበት ተነሳችና መቀመጫ ይዛ ተቀመጠች
‹‹አዎ ንገሪኝ..ከእሱ እንድርቅ ከፈለግሽ ንገሪኝ››
‹‹እሺ ቁጭ በይ….ነግርሻለው››
ሁለቱም ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀመጡ
‹‹እንግዲያው ንገሪኝ ካልሽ ምርጫ የለኝም ነግርሻለው….ግን ለምትሰሚው ነገር እራስሽን አዘጋጂ››
‹‹ግድ የለሽም መግቢያውን ተይና ወደዋናው ታሪክ በቀጥታ ግቢልኝ››
‹‹ይሄውልሽ ልጄ ግማሽ ዕድሜዬን ይሄንን ታሪክ ለሌላ ሰው ይቅርና ለእኔው ለእራሴው ለመናገር ስሸሸው የኖርኩትን ነገር ነው፡፡ይሄው ዛሬ ሳልወድ በግድ ለመናገር ተገድጄያለው፡፡እስከዛሬ ነገሩን ሚስጥር አድርጌው የኖርኩት ለእናቴ ስል ነበር..አሁን ደግሞ ለመናገር የተገደድኩት ለአንቺ ለልጄ ስል ነው..ከእናቴ ስሜትና ደህንነት ይልቅ የልጄን ስሜት እና ደህንነት አስቀድሜ ነው..መቼስ አናቴ ልጅ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ስለምታውቅ ይቅር ትለኛለች ብዬ አስባለው፡፡
ማንኛውም የሰው ልጅ በትዝታ ፈረስ ፊቱን ወደ ኃላው አዙሮ ትናንትናውን ሲያይ መዝለል የሚፈልገው ወይም አለማሰብ የሚመኘው ወይም ምነው ባልኖርኩት ኖሮ ብሎ የሚጠየፈው በጊዜዎች ክፍተት መሀከል የተከወነ ጨለማ ታሪክ ይኖረዋል፡፡የእኔን የተለየ የሚያደርገው ግን ያለፈ ህይወቴ ውስጥ የተከሰተው ጠባሳ አይደለም መሰረዝ እንዲደበዝዝ ማድረግ እንኳን የማይቻል ስለሆነ ዕድለኛ አይደለውም፡፡
ልጄ አንቺ ለእኔ ማለት የበደሌ ምልክት፤ የክስረቴ ትርፍ ነሽ፡፡ሰው ህይወቱን የሚያሳጣው …ማንነትን የሚያወድመው ነገር ከስሮ በዛው ልክ ህይወቱን የሚያለመልምለት እና ለመኖሩ ምክንያት የሆነ ነገር ያተርፋል…እኔ ማለት እንዲያ ነኝ..የነገ ተስፋዬን፤ለመኖር የሚረዳኝን ሞራሌን፤ማንነቴን አጥቼ በምትኩ ግን አንቺን አገኘው፡፡
‹‹አረ የምትይው ነገር ምንም እየገባኝ አይደለም…››መለሰችላት ሄለን
‹‹የእኔ ህይወት ለእኔም ለእራሴ ብዙ ጊዜ አይገባኝም፡፡ግን ቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ልግባ፡፡አንቺን የወለድኩሽ ተደፍሬ ነው፡፡መቼ? ገና 15 ዓመት ሳይሞላኝ፡፡ማን የደፈረኝ ይመስልሻል..?የምትወጂው አጓቴ ነው፡፡ላስተምርሽ ብሎ ከእናቴ በአደራ ተቀብሎ አዲሳባ ወስዶ ደፈረኝ ..አስረገዘኝ …››
‹አጎቴ!!!!.. አጎቴ ማለት የማዬ ወንድም … አንቺን››
‹‹አዎ አጎቴ እኔን …ያ ማለት ደግሞ አንቺ የእሱ ልጅ ነሽ… አባትሽ ነው፡፡
‹‹እኔ አላምንም…››ሄለን ምትሆነው ምትናገረው ነገር ጠፋት
‹‹ልጄ ነፍስ ካወቅሽበት ጊዜ አንስቶ አባቴ ማን ነው ?ብለሽ ስትጠይቂኝ..የተለያየ ሰበብ እየፈጠርኩ ልነግርሽ ያልቻልኩት ነገሩ ለሰሚውም ግራ ሰለሆነብኝ ነው፡፡ ልጄ እስቲ አስቢው በገዛ አጐቴ ተደፍሬ አንቺን እንደወለድኩሽ ስትሰሚ በአንቺ ሰነ-ልቦና ላይ የሚያደርሰውን መረበሽና ተፅዕኖ በምን ማረጋገጥ እችላለው? እንደእኔ ስብርብር ብትይብኝስ.?.ከሁሉም በላይ ደግሞ ይሄ ጉዳይ እናቴ ጆሮ ይሄ ዜና ቢደርስስ ?የገዛ መንትያ ወንድሟ ከመሀጸኖ ፈልቅቃ አምጣ የወለደቻትን እና አደራ አሳድግልኝ ብላ ያስረከበቻትን ጨቅላ ልጆን በድልዱም ቢላዎ ገዝግዞ እንዳረዳት እና ህይወቷን እንዳበከተባት ብትረዳ በድንጋጤ ህይወቷ ባያልፍ እንኳን ጨርቋን ጥላ ማበዶ ይቀራል ብለሽ ታስቢያለሽ…?.ለዚህ ነው ከአንቺ ጋር ስጋጭ እና ስጣላ የኖርኩት፡፡ ለዚህ ነው እራሴን እንደ ጥፋጠኛ አስቆጥሬ ስባልግ እና ስንዘላዘል በገዛ ስህተቴ እደወለድኩሽ እዲታሰብ አድርጌ ግማሽ ዕድሜዬን እንደጋጠወጥ እና እንደ አለሌ ሸርሙጣ እየታሰብኩ በመኖር እራሴን ያሰቃየውት...እርግጥ አልዋሽም ሸርሙጣ የሚለው ስም አይገባኝም አልልሽም..በደንብ ይገባኛል..፡፡ግን በሽታ ሆኖብኝ ነው፡፡ከመደፈሬ ጋር የተፀናወተኝ እኔ እራሴ የምጠየፈው እና የምፀፀትበት ክፉ በሽታዬ ነው፡፡
ልጄ እንግዲህ እውነቱ ይሄ ነው፡፡አባትሽ የምትወጂው አጐትሽ ነው..ከአሁን ቡኃላስ እሱን መውደድሽን ትቀጥያለሽ…?እንግዲህ እሱ የአንቺ ጉዳይ ነው፡፡እኔን ግን ካጠፋውት በላይ ስቀጣ የኖርኩ ሚስኪን እናት ነኝና እባክሽ ይቅር በይኝ እና ቀሪ ህይወቴን ትንሽም ቢሆን ተስፋ እንዲኖራት እርጂኝ፡፡ከእዚህ ሰውዬ ራቂ..እሱን በጣም በድዬዋለው….ሊያገባኝ ሲዘጋጅ ነው ጥዬው ወደአዲስ አበባ የገባውት ..ስለዚህ ለአመታት ሊበቀልኝ ሲጥር እደነበረ አውቃለው..እና ልጄ ….
…ሄለን ከተቀመጠችበት ተነስታ ተንደርድራ ነው እግሯ ላይ የተደፋችባት….‹‹እማዬ የምትችይ ከሆነ ይቅር በይኝ..ባክሽ ይቅር በይኝ››እየነፈረቀች ተማፀነቻት
ሮዝ ከገባችበት መደንዘዝ ውስጥ እንደምንም ነቃችና እሷም ተከትላት ቁጢጥ በማለት ልጆን ከተደፋችበት አንስታት አቀፈቻት… አገላብጣ ሳመቻት ‹‹ልጄ ….ልጄ
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)

#የመጨረሻ_ክፍል


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


‹‹በል አስወጣቸው››ዳግላስ አንቦረቀ፡፡
‹‹ምን እየሆነ ነው ምን አጠፋን?››ኑሀሚ በተመሳሳይ የድምፅ ቃና  ጠየቀችው፡፡
‹‹ጠላቶቼ ይሄንን ቦታ እንዴት ሊያውቁት ቻሉ?››
‹‹እኛ ታዲያ ምን እናውቃለን? የራስህን ሰዎች አትመረምርም››
‹‹መሳሪያውን ወደ ግንባሯ ደቀነና‹‹እንደንዴቴ ሶስታችሁንም እዚህ ግንባር ግንባረችሁን ደፍቼያችሁ እሄድ ነበር፡፡ግን እንዳደረሳችሁብኝ ኪሳራ በሰላም እና በቀላሉ መሞት አይገባችሁም…ሶስታችሁም እባክህ ግደለን እያላችው በየቀኑ እንድትለምኑኝ ነው የማደርገው…በተለይ አንቺን…በሉ ያዟቸው..››

እሱን ከበው የነበሩ ጋንግስተሮች ወደቤት ውስጥ ገቡን ሶስቱንም እየገፈተሩ ወደውጭ አስወጣቸው…..በኮሪደሩ አልፈው ሳሎን ገቡ …ከዛ በደረጃው ወደግራውንድ ይዘዋቸው ሄዱ…ሰው ሁሉ ይተረማመሳል….መሳሪያዎች ከመጋዘን እየወጡ ይታደላሉ..ሀገር ወራሪ መጥቶ ለፊልሚያ እየተሰናዱ ነው የሚመስለው….ወደምድር ቤት ይዘዋቸው ወረዱ….ምድር ቤት ያለው  ትርምስ ከግራውንዱም ይብሳል….የተመረቱትን ኮኬይን አሰተካክለው ካርቶን ውስጥ በማስገባት ያሽጋሉ… ሌሎች ደግሞ የታሸገውን ወደጥግ እየወሰዱ ይደረድራሉ….ዳግላስ  እነኑሀሚን ለጠባቂዎቹ ተዋቸውና እያንቧረቀ ትእዛዝ በመስጠት ወደሰራተኞቹ ሄደ፡፡
‹‹እንዴ ይሄን ሁሉ ኮኬይን የሚደረድሩት እንዴት ሊየደርጉት ነው?››ምስራቅ ነች በሹክሹክታ የጠየቀችው፡፡
ኑሀሚን‹‹አልገባኝም ….ምን አልባት…..››ብላ ግምቷን መናገር ስትጀምር ያልጠበቁት ነገር ከፊት ለፊታቸው ተመለከቱ፡፡ የምድር ቤቱ ጥግ ላይ ያለ ወለል እንዴት አድርገውት እንደሆነ አይታወቅም ሲከፈት አዩ…
‹‹እንዴ!! ከዚህ በታች እቤት አለ እንዴ?››ናኦል ነው በገረሜታ የተናገረው፡፡
‹‹አይ እቤት አይመስለኝም….ከዚህ አካባቢ                                   ማምለጫ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ነው፡፡
‹‹አንቺ እውነትሽን ሳይሆን አይቀርም…››
ስትል ሰዎች በካርቶን የታሸገውን ካርቶን እየተሸከሙ በተከፈተው ወለል በመሄድ እንደመሰላል  ባለ ብረት እየተንጠለጠሉ ወደታች መውረድ ጀመሩ፡፡፡
‹‹ሰዎች ትክክል ነኝ…ይሄ ከዚህ ስፍራ ማምለጫ የምድር ውስጥ መንገድ ነው….እናም እኛንም በዛ ውስጥ ይዘውን ሊሄዱ ነው››ኑሀሚ ነች ተናጋሪዋ፡፡
ምስራቅ‹‹የሆነ ነገር ማድረግ አለብን ..እዛ ውስጥ ይዘውን ገብተው ከዚህ ካስመለጡን እንዳለው ለወራት አስቃይቶ ነው የሚገድለን..መሞታችን ካልቀረ ደግሞ እዚሁ ለማምለጥ እየሞከርን ብንሞት ይሻላል››
‹‹ትክክል ነሽ ለማምለጥ መሞከሪያ ጊዜው አሁን ነው››ናኦልም በምስራቅ ሀሳብ ተስማማች፡፡
ምስራቅ ‹‹ናኦል››ስትል ተጣራች፡፡
‹‹በጣም ነው የምወድህ እሺ፣ማለቴ አፈቅርሀለው››አለችው፡፡
‹‹አውቃለው እኔም አፈቅርሻለው…ግን እያስፈራሺኝ ነው››
‹‹አትፍራ….ኑሀሚ አንቺንም ወድሻለው››
አቦ አንቺ ደግሞ አትረብሺኝ …ኑዛዜ አስመሰልሺው….ትኩረቴን እየበታተንሺው ነው…..ተመልከቱ እነዛ ሁለት ሰዎች ለእያንዳንዱ ሰው የእጅ ቦንብ እያደሉ ነው….ሲቀርብን በፍጥነት የተወሰነ ቦንብ በእጃችን ማስገባት አለብን…ከዛ…..››ኑሀሚ ንግግሯን ሳታገባድድ ምስራቅ ወደጎን ተስፈንጥራ  ጠረጴዛ ስር ሾልካ በመግባት ስትሰወር እነሱን ሲጠብቁ የነበሩ ጠባቂዎች የሚወስዱት እርምጃ ግራ ገብቷቸው ወዲህ ወዲያ ሲራወጡ ኑሀሚ የናኦልን ክን ድ ይዛ በግራ በኩል ስትሮጥ ከጠባቂዎቹ አንዱ ተወርውሮ የናኦል እግር ላይ ተጠምጥሞ አስቀረው….ኑሀሚ ወንድሟን ለቃ ሩጫዋን ቀጠለችና ከኮኬይኑ ካርቶን ጀርባ ተሰወረች….አንዱ መሳሪየውን ደቅኖ ተከተላት…በአየር ላይ ተንሳፈፈችን ጉሮሮውን ዘጋችለት…እጥፍጥፍ ብሎ ስሯ ወደቀ..መሳሪያውን ተቀበለችና ምላጩን ተጭና ዝም ብላ አንደቀደቀችው…እቅዷ ትርምስ መፍጠር ነው…ያሰበችው ተሳካላት፡፡ ሰው በፊትም ስጋትና ድንጋጤ ላይ የነበሩ ሰራተኞች የመሳሪያ መንደቅደቅ ሲሰሙ ሚይዙት የሚጨብጡት ጠፍቷቸው ከወዲህ ወዲያ መተረማመስ ጀመሩ ፡፡ይህ ደግሞ ለነኑሀሚ ጥሩ ሁኔታ ፈጠረላቸው፡፡
///
ወደቀኝ ታጥፋ ጠረጴዛ ተከልላ የተሰወረችው ምስራቅ ተንሸራታ ቦንብ የምታድለው እንስት ላይ ነው የተከመረችባት …ልጅቷ በድንጋጤ ቦንብ ያለበትን ካርቶን ለቀቀችው፡፡ መሬት ወድቆ ተዘረገፈ….ምስራቅ ልጅቷን በአንድ እጇ ይዛ በሌላ እጆሶስት ሚሆኑ ቦንቦችን ያዘች….ከግራ በኩል ይተኮስባት ጀመር..ምርጫ ስላልነበራት ልጅቶን ከፊት ለፊቷ  አቆመቻት…የሚተኮሰው ጥይት ሁሉ ልጅቷ ሰውነት ውስጥ ተሰገሰገ….ምስራቅ ወደኃላ አፈገፈገችና ቦታዋን ለቀቀች….ተኳሹ መሬት ላይ ከተዘረገፍት ቦንቦች አንድን አገኘው….አካባቢው ባልተጠበቀ ፍንዳታ ተናጋ…ዋና ዋና መብራቶቹ ጠፉና ጭላንጭል ድንግዝግዝ ብርሀን ብቻ ቀረ… ምድር ቤቱ በጥቁር ጭስ ተዋጠ…ምስራቅም ኑሀሚም በየፊናቸው  ናኦልን ሲፈልጉ ድንገት ተገናኙ….

‹‹ናኦልን አይተሸዋል…?››ኑሀሚ ነች ጠያቂዋ፡፡
‹‹አላየሁትም እየፈለኩት ነው፡፡ወደውጭ ይዘውት ወጥተው ሊሆን ይችላል›››ምስራቅ መለሰች፡
‹‹አይ በምድር ውስጥ ይዘውት ገብተው ከሆነስ..?እኔ ወደእዛ ልሂድ አንቺ ወደውጭ ውጪና ፈልጊው፡፡››
‹‹እርግጠኛ ነሽ….?››
‹‹አዎ ጊዜ አናጥፋ…››ተስማሙ……
ምስራቅ ወደውጭ መውጫው ከሚራኮቱት ሰዎች ጋር እየተጋፋች ስትሄድ ኑሀሚ ደግሞ ወደውስጠኛው የምድር ውስጥ መሹለኩያ ሮጠች…..፡፡
ኑሀሚ አስር ሜትር ርቀት ሲቀራት ወደእሷ ተተኮሰባት… ወደግራዋ ተስፈነጠረችና የሆነ የብረት ካዝና ስር ከለላ ይዛ እራሷን ለመከላከከል መተኮስ ጀመረች…

‹‹አንቺ ሸርሙጣ..ነይ ውጪ››የዳግላስ ድምፅ መሆኑን ለየች….እልክ ተናነቃት፡

‹‹እየተኮሰች ተሸለክልካ በመሀከላቸው ያለውን ርቀት ወደሳባት ሜትር አጠበበች…፡፡አሁን በግልፅ እየታያት ነው….አልማ ተኮሰች…ሆዱን ቦተረፈችው…አጎራና መሬት ተዘረረ…..፡፡ከግራና ከቀኝ ጠባቂዎች ወጡና ግማሹ ወደእሷ እየተኮሱ ለጓደኞቻቸው ሽፋን መስጠት ጀመሩ፡፡ ሁለቱ ደግሞ በደም የጨቀየውን ዳግላስን  እየጎተቱ ወደተከፈተው ጉድጎድ አስገቡት…ወደታች ይዘውት ወረዱ.፡፡ከዛ  እነሱ ተከተሉ…አንዱን ግንባሩን ብላ አስቀረችው፡፡ወደጉድጓዱ ተስፈነጠረች…ወንድሟን ይዘውት ሄደው ከሆነ መከተል አለባት…አንድ እርምጃ ሲቀራት እንዴት እንደሆነ በማታውቀው ዘዴ ወለሉ ተመልሶ ተዘጋ ፡፡ወደውስጥ የሚያሾልክ ምንም አይነት ቀዳዳ ሆነ ክፍተት በአካባቢው የለም፡፡መሳረያውን በወለሉ ላይ አርከፈከፈች…በንዴትና ተስፋ መቁረጥ በጉልበቷ ተናበረከከች…በዚህ ጊዜ ከኃላዋ አንድ በጣም ደስ የሚል ከገነት የመሰላ የጥሪ ድምፅ ሰማች‹‹…ኑሀም ኑሀሚ››
‹‹ዞር አለች››
‹‹ኑሀሚ ካርሎስ ነኝ››
ተንደርድራ ድምፅ ወደሰማችበት አካባቢ ተስፈነጠረች…..ኦ እራሱ ነው….በወገቡ ዙሪያ ቦንብ ደርድሮ  እንደዘንዶ የተጠመዘዘ ዝናር በጀርባው አንጠልጥሎ ዘመናዊ አውቶማቲክ መሳሪውን ደቅኖ አገኘችው…ተጠመጠመችበትና ከንፈሩ ላይ ተጣበቀች….