#ወንጀልና_ቅጣት
:
ክፍል-አንድ
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻው
እትዬ ሌንሴ ፊት ነሱኝ።
ለወትሮው ከፊልድ ምናምን ስመለስ እንኳን ኬሻ ሙሉ ከሰል፣ ሶስት አራት ኪሎ ቲማቲም ወይ ሽንኩርት ወይ ደግሞ ጎመን ምናምን ይዤ መጥቼ የመኪናዬን ጲጵ ሲሰሙ ጠብ እርግፍ ብለው ያስተናግዱኝ ነበር። ቤት ያፈራውን ጭኮ፣ ቅንጬ ወይም ፍርፍር በፍጥነት አቅርበው በግድ ያስበሉኝ ነበር።
ዛሬ ግን በተወደደ ከሰል ከየትና የት ካለ ኩሊ ራሴ አውርጄ (እጄ ከሰል በከሰል ሆኗል) ሳሎናቸው ስገባ እዛ…ሁልጊዜ የሚቀመጡበት አሮጌ ፎቴ ላይ የሚወደውን ሰው መርዶ የሰማ ሰው መስለው ተጎልተዋል።
ሃሳብ ገብቷቸው አልሰሙኝ ይሆን?
ሁሌም ወፍራም ላስቲክ የሚለብሰውን ምንጣፋቸውን በጭቃ ጫማዬ እንዳላቆሽሽ እየተሳቀቅኩ፣ ከሰል በከሰል የሆነ እጄን እነዳንከረፈፍኩ አጠገባቸው ደርሼ ሰላም ልላቸው ብጠጋቸው እያዩኝ እንደማያዩ መስለው ፊት ነሱኝ።
ምን አጥፍቼ ነው?
– እንዴት ሰነበቱ እትዬ ሌንሴ ከማለቴ
– አረ ምንጣፌን! ምንጣፌን አታቆሽሽብኝ እንጂ…ለራሴ ሰራተኛም የለኝ… አሉኝና ደልዳላ ሰውነታቸውን እያሞናደሉ ወደ ጓዳ ገቡ።
አረ ፊት መንሳት!
መጥፎ ሰው አይደለሁም። ያው እንደሁሉም ሰው ስህተትና ጥቂት ደደብነት ባያጣኝም መጥፎ ሰው አይደለሁም። አንድ መጥፎ ነገር ያደረገ ሰው መጥፎ ሰው ነው? አይመስለኝም።
የፍቅረኛዬ እናት እትዬ ሌንሴ ለምን እንደተናደዱብኝ የጠረጠርኩት ባዶው ሳሎን ውስጥ ጥለውኝ ጓዳ በገቡ በደቂቃዎች ውስጥ ነው። ቤዛ የሰራሁትን ስህተት ነግራቸው ነው።
ወሬኛ።
እጆቼን እንዳንከረፈፍኩ መታጠቢያ ውሃ ፍለጋ ደጅ ወጣሁ።
የቤዛ ታላቅ እህት ምህረት ፊቷን ካመጣሁት ከሰል አጥቁራ ጠበቀችኝ።
– አረ ውሃ ፈልገሽ አስታጥቢኝ በናትሽ አልኳት ሰላምታ ለመስጠም ሳልሞክር። በአይኖቿ ሰማይ ድረስ አጉናኝ መሬት ስታፈርጠኝ ይታወቀኛል። (እሷም ሰምታለች ማለት ነው። )
– ውሃ የለችም…ቤትህ ታጠብ…ብላኝ በረንዳ ላይ ያስቀመጥኩትን ኬሻ ሙሉ ከሰል ልክ እንደሰው ገላምጣው ጥላኝ ወደ ቤት ገባች።
ይህችን ይወዳል ሚካኤል!
በሁለቱም ሁኔታ እየተበሳጨሁ ያመጣሁትን ከሰል ብድግ አድርገህ ለራስህ እናት ውሰድ ውሰድ እያለኝ ወደ መኪናዬ ስሄድ የቤዛ ትንሽ እህት እምነት ገጠመችኝ። እኔንና እጆቼን አመሳቅላ አይታ…
– ምነው ውሃ የለም እንዴ በቤቱ? አለችኝ (ይህችኛዋ ገና አልሰማችም ማለት ነው)
– ማዘርም ምህረትም ፊት ነሱኝ…ማን ያስታጥበኝ…አልኳት አይን አይኗን እያየሁ
– አውነታቸውን ነው ለነገሩ…እንዳንተ አይነቱ ቆሻሻ እንኳን በጆግ ውሃ በአባይም ቢታጠብ አይነፃ! አለችና መልስ እንኳን ሳትጠብቅ እየተመናቀረች ጥላኝ ሄደች። (ሰምታለች)
አሁን ነገሩ ፍንትው አለልኝ። የወሬ ሰንሰለቱ ተገለጠልኝ። ቤዛ እና ቤተሰቧ እንደማይለያይ መንጋ ናቸው። የሚያስቡት አንድ ላይ። የሚስቁት አንድ ላይ። የሚያኮርፉት አንድ ላይ። የሚወዱት አንድ ላይ። የሚጠሉት አንድ ላይ። ወሬ አይደባበቁ…ምስጢር አያውቁ…ብሽቆች።
መኪናዬ ውስጥ ገብቼ በአንዱ ቁራጭ ፎጣ የእጆቼን ከሰል ለማስለቀቅ ስሞክር ንዴቴ ጨመረ።
ለምን ነገረቻቸው?
ይቅር ብዬሃለሁ ምናምን ብላኝ ለምን ስለስህተቴ ለቤተሰቧ ነገረች? ስለግል ጉዳያችን ለቤተሰብ ቱስ ማለቱ…እኔን ከማስገመት በቀር ምንድነው ትርጉሙ? ቤት ቤት ከወንጀሌ የማይመጣጠን የምትቀጣኝ ቅጣት አንሶ ይወዱኝ በነበሩ ቤተሰቦቿ ዘንድ ቀልዬ እንድታይ ለማድረግ?
…ነገሩ ቆይቷል። ማለቴ አንድ አምስት ወር አልፎታል። አብረን መኖረ ሲቀረን ሳንጋባ የተጋባን ጥንዶች ሆነን ነበር። ቤተሰብ ያውቀኛል። ቤተሰብ ያውቃታል። ከሳምንቱ አብዛኛውን ቀን አብረን ውለን እናድራለን። ጉሮ ወሸባዬ እና አሸወይና እና የማዘጋጃ ቤት ፊርማ ሲቀር ተጋብተናል ሊባል ይችል ነበር። በዛው ሰሞን ከየት መጣ ሳልለው ቤዛ አድርጋ የማታውቀውን የ‹‹እንጋባ›› ንዝንዛዋን መጀመሪያ ለዘብ፣ በኋላ ክርር አድርጋ ጀመረች።
አይኗ ከቬሎ ሱቆች፣ ሃሳቧ ከሰርግ አልላቀቅ አለ። እኔ ደግሞ ላገባ (ት) አልፈለግኩም። ስለማልወዳት አይደለም። እወዳታለሁ። ላገባት የማልፈልገው እንደወደድኳት መቆየት ስለምፈልግ ነው።
ከአምስቱ የቅርብ ጓደኞቼ ሶስቱን ሚዜ ሆኜ ድሬያለሁ። ከተጋቡ ወዲህ በደስታቸው ፈንታ የጨመረው ቦርጭና ንጭንጫቸው ብቻ ነው። ጋኔን አይደለም ያገቡት። ያፈቀሯቸውን ሴቶች ነው ያገቡት። ግን አንድም ቀን ስለትዳር ወይ ስለሚስት በጎ ነገር ሲወጣቸው አላየሁም። አልሰማሁም።
ቅልጥ ያለ ፑል እየተጫወትን ተደውሎ ይጠራሉ።
…ዳይፐር እንዳትረሳ…ምጣዱ እንደገና ተበላሽቷል። …የውሃ ዛሬ መክፈል አለብህ….ባቢ ትኩሳት አለው…የእማማ ማህበር እኮ ዛሬ ነው…
ቶሎ ና።
ቶሎ ድረስ።
አሁኑኑ እንድትመጣ።
እንዳታረፍድ።
እንዳታመሽ። …
እንዲህ ያሉ ትእዛዞች በሚበዙበት የጭቆና አገዛዝ ወድቀዋል። እኔ ደግሞ ነፃነቴን አጥብቄ የምወድ ሰው ነኝ። ድንበር፣ መስመር፣ ሰአት እላፊ አልወድም። ትእዛዝ ይጎረብጠኛል። መሆን አለበት ያመኛል። እንዲህ አድርግ ይረብሸኛል።
ቤዛንም ነፃነቴንም እወዳለሁና የትዳርን እግረ-ሙቅ ‹ትንሽ እንቆይ›› ምናምን ብዬ በጨዋኛ እምቢ አልኳት።
አቤት አለዋወጥ! ተለዋወጠችብኝ። ለሕይወቷ የሰጋች እስስት እንዲደዚሀ አትለዋወጥም። ይባስ ብላ…
– እማዬ ወንድ ልጅ የሚፈልገውን ነገር ሁሉ ከትዳር በፊት ካገኘ አያገባሽም ብላኛለች ብላ ለሁለት ወር ተኩል የምወደውን፣ የምኖርለትን ገላዋን ከለከለችኝ።
አበድኩ። ማለቴ በጣም አበድኩ። የገዛ ገርልፍሬንዴ ጭኖች መሃ ለመግባት የትዳር የምስክር ወረቀት ስጠየቅ ጊዜ በጣም ተናደድኩ።
ደግሞ እኮ ልታሰቃየኝ አብራኝ ታድራለች። ልክ ዛሬ ራራችልኝ..ፈቀደችልኝ፣ ቅጣቴ ሊያበቃ ነው ምናምን ብዬ ሁለመናዬ እንደ ጅብራ ሲገተር እንደ ታናሸ ወንድም ግንባሬን ስማኝ ራሷን በመአት ትራሶች አጥራ ትተኛለች።
ከይሲ አይደለች?
ብላት- ብሰራት ሁለት ወር ተኩል ሙሉ ራሷን ነፈገችኝ። አስቡት፤ ወንድ ነኝ። ወጣት ነኝ። ከቆንጆ ሴት አጠገብ የተኛሁ ወጣት ወንድ ነኝ። የፍትወት ፍላጎት ብቻ ሳይሆን ትዝታ አለኝ።
ከይሲ ናት።
ቢሆንም አይኔ ሌላ አላማተረም። ልቤ ለሌላ አልነሆለለም። ቅጣቱ እንዲቀልልኝ፣ በምህረቷ እንድትጎበኘኝ ብሞት አድርጌ የማላውቀውን በፊልም እንደማያቸው ወንዶች አበባ ምናምን እየገዛሁ እሰጣት ጀመር። መብራት ሳይጠፋ ሻማ ምናምን ለኩሼ፣ ወይን ቀድቼ ላሳዝናት ሞከርኩ። እሷ ግን ፍንክች አላለችም።
ገላዋን እያዛጋሁ ሳምንታት አለፉ።
አንጎሌና ገላዬ ሌላ ማሰብ በማይችልበት በዚህ ከፍተኛ የወሲብ ድርቅ ጊዜ ነው የቢሯችን ኤች አር አፈር ይብላና ሄርሜላን የቀጠረው።
ኦ…ሄርሜላ!
ለድርጅቱ በገንዘብ ያዥነት የተቀጠረች ሳይሆን ለኔ በፈተናነት የመጣች ትመስል ነበር። የሆነች እንከን አልባ ነገር። ሹ…ል እና ትልልቅ ጡቶች። ሙትት ያለ አንጀት። በቀጭን ወገቧ እህህህ…እያለች በመከራ የምትጎትተው ትልቅ ቂጥ። ስስ ግን ሳሙኝ፣ ግመጡኝ የሚል ከንፈር። …
ሄርሜላ.....
💫ይቀጥላል💫
Like👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
:
ክፍል-አንድ
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻው
እትዬ ሌንሴ ፊት ነሱኝ።
ለወትሮው ከፊልድ ምናምን ስመለስ እንኳን ኬሻ ሙሉ ከሰል፣ ሶስት አራት ኪሎ ቲማቲም ወይ ሽንኩርት ወይ ደግሞ ጎመን ምናምን ይዤ መጥቼ የመኪናዬን ጲጵ ሲሰሙ ጠብ እርግፍ ብለው ያስተናግዱኝ ነበር። ቤት ያፈራውን ጭኮ፣ ቅንጬ ወይም ፍርፍር በፍጥነት አቅርበው በግድ ያስበሉኝ ነበር።
ዛሬ ግን በተወደደ ከሰል ከየትና የት ካለ ኩሊ ራሴ አውርጄ (እጄ ከሰል በከሰል ሆኗል) ሳሎናቸው ስገባ እዛ…ሁልጊዜ የሚቀመጡበት አሮጌ ፎቴ ላይ የሚወደውን ሰው መርዶ የሰማ ሰው መስለው ተጎልተዋል።
ሃሳብ ገብቷቸው አልሰሙኝ ይሆን?
ሁሌም ወፍራም ላስቲክ የሚለብሰውን ምንጣፋቸውን በጭቃ ጫማዬ እንዳላቆሽሽ እየተሳቀቅኩ፣ ከሰል በከሰል የሆነ እጄን እነዳንከረፈፍኩ አጠገባቸው ደርሼ ሰላም ልላቸው ብጠጋቸው እያዩኝ እንደማያዩ መስለው ፊት ነሱኝ።
ምን አጥፍቼ ነው?
– እንዴት ሰነበቱ እትዬ ሌንሴ ከማለቴ
– አረ ምንጣፌን! ምንጣፌን አታቆሽሽብኝ እንጂ…ለራሴ ሰራተኛም የለኝ… አሉኝና ደልዳላ ሰውነታቸውን እያሞናደሉ ወደ ጓዳ ገቡ።
አረ ፊት መንሳት!
መጥፎ ሰው አይደለሁም። ያው እንደሁሉም ሰው ስህተትና ጥቂት ደደብነት ባያጣኝም መጥፎ ሰው አይደለሁም። አንድ መጥፎ ነገር ያደረገ ሰው መጥፎ ሰው ነው? አይመስለኝም።
የፍቅረኛዬ እናት እትዬ ሌንሴ ለምን እንደተናደዱብኝ የጠረጠርኩት ባዶው ሳሎን ውስጥ ጥለውኝ ጓዳ በገቡ በደቂቃዎች ውስጥ ነው። ቤዛ የሰራሁትን ስህተት ነግራቸው ነው።
ወሬኛ።
እጆቼን እንዳንከረፈፍኩ መታጠቢያ ውሃ ፍለጋ ደጅ ወጣሁ።
የቤዛ ታላቅ እህት ምህረት ፊቷን ካመጣሁት ከሰል አጥቁራ ጠበቀችኝ።
– አረ ውሃ ፈልገሽ አስታጥቢኝ በናትሽ አልኳት ሰላምታ ለመስጠም ሳልሞክር። በአይኖቿ ሰማይ ድረስ አጉናኝ መሬት ስታፈርጠኝ ይታወቀኛል። (እሷም ሰምታለች ማለት ነው። )
– ውሃ የለችም…ቤትህ ታጠብ…ብላኝ በረንዳ ላይ ያስቀመጥኩትን ኬሻ ሙሉ ከሰል ልክ እንደሰው ገላምጣው ጥላኝ ወደ ቤት ገባች።
ይህችን ይወዳል ሚካኤል!
በሁለቱም ሁኔታ እየተበሳጨሁ ያመጣሁትን ከሰል ብድግ አድርገህ ለራስህ እናት ውሰድ ውሰድ እያለኝ ወደ መኪናዬ ስሄድ የቤዛ ትንሽ እህት እምነት ገጠመችኝ። እኔንና እጆቼን አመሳቅላ አይታ…
– ምነው ውሃ የለም እንዴ በቤቱ? አለችኝ (ይህችኛዋ ገና አልሰማችም ማለት ነው)
– ማዘርም ምህረትም ፊት ነሱኝ…ማን ያስታጥበኝ…አልኳት አይን አይኗን እያየሁ
– አውነታቸውን ነው ለነገሩ…እንዳንተ አይነቱ ቆሻሻ እንኳን በጆግ ውሃ በአባይም ቢታጠብ አይነፃ! አለችና መልስ እንኳን ሳትጠብቅ እየተመናቀረች ጥላኝ ሄደች። (ሰምታለች)
አሁን ነገሩ ፍንትው አለልኝ። የወሬ ሰንሰለቱ ተገለጠልኝ። ቤዛ እና ቤተሰቧ እንደማይለያይ መንጋ ናቸው። የሚያስቡት አንድ ላይ። የሚስቁት አንድ ላይ። የሚያኮርፉት አንድ ላይ። የሚወዱት አንድ ላይ። የሚጠሉት አንድ ላይ። ወሬ አይደባበቁ…ምስጢር አያውቁ…ብሽቆች።
መኪናዬ ውስጥ ገብቼ በአንዱ ቁራጭ ፎጣ የእጆቼን ከሰል ለማስለቀቅ ስሞክር ንዴቴ ጨመረ።
ለምን ነገረቻቸው?
ይቅር ብዬሃለሁ ምናምን ብላኝ ለምን ስለስህተቴ ለቤተሰቧ ነገረች? ስለግል ጉዳያችን ለቤተሰብ ቱስ ማለቱ…እኔን ከማስገመት በቀር ምንድነው ትርጉሙ? ቤት ቤት ከወንጀሌ የማይመጣጠን የምትቀጣኝ ቅጣት አንሶ ይወዱኝ በነበሩ ቤተሰቦቿ ዘንድ ቀልዬ እንድታይ ለማድረግ?
…ነገሩ ቆይቷል። ማለቴ አንድ አምስት ወር አልፎታል። አብረን መኖረ ሲቀረን ሳንጋባ የተጋባን ጥንዶች ሆነን ነበር። ቤተሰብ ያውቀኛል። ቤተሰብ ያውቃታል። ከሳምንቱ አብዛኛውን ቀን አብረን ውለን እናድራለን። ጉሮ ወሸባዬ እና አሸወይና እና የማዘጋጃ ቤት ፊርማ ሲቀር ተጋብተናል ሊባል ይችል ነበር። በዛው ሰሞን ከየት መጣ ሳልለው ቤዛ አድርጋ የማታውቀውን የ‹‹እንጋባ›› ንዝንዛዋን መጀመሪያ ለዘብ፣ በኋላ ክርር አድርጋ ጀመረች።
አይኗ ከቬሎ ሱቆች፣ ሃሳቧ ከሰርግ አልላቀቅ አለ። እኔ ደግሞ ላገባ (ት) አልፈለግኩም። ስለማልወዳት አይደለም። እወዳታለሁ። ላገባት የማልፈልገው እንደወደድኳት መቆየት ስለምፈልግ ነው።
ከአምስቱ የቅርብ ጓደኞቼ ሶስቱን ሚዜ ሆኜ ድሬያለሁ። ከተጋቡ ወዲህ በደስታቸው ፈንታ የጨመረው ቦርጭና ንጭንጫቸው ብቻ ነው። ጋኔን አይደለም ያገቡት። ያፈቀሯቸውን ሴቶች ነው ያገቡት። ግን አንድም ቀን ስለትዳር ወይ ስለሚስት በጎ ነገር ሲወጣቸው አላየሁም። አልሰማሁም።
ቅልጥ ያለ ፑል እየተጫወትን ተደውሎ ይጠራሉ።
…ዳይፐር እንዳትረሳ…ምጣዱ እንደገና ተበላሽቷል። …የውሃ ዛሬ መክፈል አለብህ….ባቢ ትኩሳት አለው…የእማማ ማህበር እኮ ዛሬ ነው…
ቶሎ ና።
ቶሎ ድረስ።
አሁኑኑ እንድትመጣ።
እንዳታረፍድ።
እንዳታመሽ። …
እንዲህ ያሉ ትእዛዞች በሚበዙበት የጭቆና አገዛዝ ወድቀዋል። እኔ ደግሞ ነፃነቴን አጥብቄ የምወድ ሰው ነኝ። ድንበር፣ መስመር፣ ሰአት እላፊ አልወድም። ትእዛዝ ይጎረብጠኛል። መሆን አለበት ያመኛል። እንዲህ አድርግ ይረብሸኛል።
ቤዛንም ነፃነቴንም እወዳለሁና የትዳርን እግረ-ሙቅ ‹ትንሽ እንቆይ›› ምናምን ብዬ በጨዋኛ እምቢ አልኳት።
አቤት አለዋወጥ! ተለዋወጠችብኝ። ለሕይወቷ የሰጋች እስስት እንዲደዚሀ አትለዋወጥም። ይባስ ብላ…
– እማዬ ወንድ ልጅ የሚፈልገውን ነገር ሁሉ ከትዳር በፊት ካገኘ አያገባሽም ብላኛለች ብላ ለሁለት ወር ተኩል የምወደውን፣ የምኖርለትን ገላዋን ከለከለችኝ።
አበድኩ። ማለቴ በጣም አበድኩ። የገዛ ገርልፍሬንዴ ጭኖች መሃ ለመግባት የትዳር የምስክር ወረቀት ስጠየቅ ጊዜ በጣም ተናደድኩ።
ደግሞ እኮ ልታሰቃየኝ አብራኝ ታድራለች። ልክ ዛሬ ራራችልኝ..ፈቀደችልኝ፣ ቅጣቴ ሊያበቃ ነው ምናምን ብዬ ሁለመናዬ እንደ ጅብራ ሲገተር እንደ ታናሸ ወንድም ግንባሬን ስማኝ ራሷን በመአት ትራሶች አጥራ ትተኛለች።
ከይሲ አይደለች?
ብላት- ብሰራት ሁለት ወር ተኩል ሙሉ ራሷን ነፈገችኝ። አስቡት፤ ወንድ ነኝ። ወጣት ነኝ። ከቆንጆ ሴት አጠገብ የተኛሁ ወጣት ወንድ ነኝ። የፍትወት ፍላጎት ብቻ ሳይሆን ትዝታ አለኝ።
ከይሲ ናት።
ቢሆንም አይኔ ሌላ አላማተረም። ልቤ ለሌላ አልነሆለለም። ቅጣቱ እንዲቀልልኝ፣ በምህረቷ እንድትጎበኘኝ ብሞት አድርጌ የማላውቀውን በፊልም እንደማያቸው ወንዶች አበባ ምናምን እየገዛሁ እሰጣት ጀመር። መብራት ሳይጠፋ ሻማ ምናምን ለኩሼ፣ ወይን ቀድቼ ላሳዝናት ሞከርኩ። እሷ ግን ፍንክች አላለችም።
ገላዋን እያዛጋሁ ሳምንታት አለፉ።
አንጎሌና ገላዬ ሌላ ማሰብ በማይችልበት በዚህ ከፍተኛ የወሲብ ድርቅ ጊዜ ነው የቢሯችን ኤች አር አፈር ይብላና ሄርሜላን የቀጠረው።
ኦ…ሄርሜላ!
ለድርጅቱ በገንዘብ ያዥነት የተቀጠረች ሳይሆን ለኔ በፈተናነት የመጣች ትመስል ነበር። የሆነች እንከን አልባ ነገር። ሹ…ል እና ትልልቅ ጡቶች። ሙትት ያለ አንጀት። በቀጭን ወገቧ እህህህ…እያለች በመከራ የምትጎትተው ትልቅ ቂጥ። ስስ ግን ሳሙኝ፣ ግመጡኝ የሚል ከንፈር። …
ሄርሜላ.....
💫ይቀጥላል💫
Like👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
👍11
#ወንጀልና_ቅጣት
:
ክፍል-ሁለት
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻዉ
...ፈተናዬን ሲያበዙት ፊልድ በሄድኩ ቁጥር ስልጠናው ላይ አበል ትክፈል ብለው አብረው ይልኩናል። ሃዋሳ ላይ ለትንሽ አመለጥኳት….መቀሌ ላይ ለጥቂት ሳትኳት፣ አርባምንጭ በመከራ አለፍኳት …ደሴ ግን…ደሴ ላይ ግን ብርዱና ውበቷ አሲረውብኝ ወደቅኩላት። ቀመስኳት። አጣጣምኳት። የተመኘሁትን ጡት እንደ መንፈቅ ልጅ መጠመጥኩ። የጓጓሁለትን ወገብ አቀፍኩ። የቋመጥኩለትን መቀመጫ ጨብጥኩ። ያለምኩትን ከንፈር ጎረስኩ።
ሲነጋ በአንሶላ ተጠቅልላ አይን አይኔን ስታየኝ ነቃሁ። ከባይተዋር ሰው ጋር ባይተዋር አልጋ ላይ ተኝቴ ሲነጋብኝ ፍንጣሪ የጥፋተኝነት ስሜት ስላልተሰማኝ ጥፋተኝነት ተሰማኝ። ትራሴን ተንተርሼ እንደተኛሁ ፣ እንዴት አደርሽ እንኳን ሳልላት-
– ስሚ ሄርሜላ…ትላንት…ስህተት ነው የሰራነው….እኔ እጮኛ አለኝ…አልኳት
– አራቴ ስህተት አለ? ሃሃ….አለችና ያን ከንፈሯን ይዛ ወደከንፈሬ ስትጠጋ ሸሸት ብዬ..
– የምሬን ነው…ስህተት ነው….እጮኛዬን እወዳታለሁ…አልኩ
በፍፁም ግዴለሽነት ከአልጋ ውስጥ ውስጥ መለመላዋን ወጥታ ፈት ለፊቴ ቆመች። ከእኔ በፊት እዚህ ቦታ ሺህ ጊዜ የቆመች፣ ሺህ ጊዜ የሌላን ሰው ገላ አቅፋ ያደረች ልምድ ያላት አሳሳች ትመስላለች።
– አንድ ነገር አንዴ ከሆነ ስህተት ከተደጋገመ ውሳኔ ነው የሚባለው….ለማንኛውም ይመችህ…ሰአት ሄዷል …ልታጠብ…ብላ ታላቅ ቂጧን እያገላበጠች ወደ መታጠቢያው ክፍል ሄደች…
ምንድነው ያለችው?
አዲሳባ ስመለስና ቤዛን ሳገኛት ፀፀት ይሰማኛል፣ የሰራሁት ሃጥያት ያሰቃየኛል ብዬ ጠብቄ ነበር። ያልተለወጠው ግትር ባህሪዋ ይሆን የኔ አይኑን በጨው ያጠበ ባለጌ ሰው መሆን ሽውም አላለኝ። የሄርሜላን ሴትነት ያገኘው ወንድነቴ ምሱን አገኘ መሰለኝ በትራስ ታጥሮ የሚተኛው የቤዛ ገላ አላጓጓው አለ። ማስፈራሪያና ቅጣቷ አልሰማው አለ።
ሄርሜላን በማስታገሻነት በወሰድኩ አንድ ሳምንት ካለፈ ይመስለኛል ቤዛ ባንዱ ምሽት እንደለመደችው ልታሰቃየኝ ስትሞክር ቀድሜያት ግንባሯን ሳምኩና ጀርባዬን ሰጥቼያት ተኛሁ። ደቂቃም ሳይቆይ በቀጫጭን ጣቶቿ ጀርባዬን ትዳብስ…እጆቿን ወደ ጉያዬ ትሰድ ጀመር።
ዝም አልኳት።
በግድ ወደ እሷ ገልብጣኝ-
– ሚኪዬ…አለችኝ በመኝታ ቤት ድምፅዋ…
– አቤት…አልኩ ቡዝ ያሉ ውብ አይኖቿን እያየሁ። ወደ ግራ ያዘነበለ አንገቷን፣ ጫፋቸው የከረረ ጡቶችዋን በስስ ካናቴራዋ ውስጥ እየታዘብኩ።
– አልናፈቅኩህም?…
– ናፍቀሽኛል….
– ምነው መጠየቅ እንኳን ተውክ ታዲያ…
– ጠይቄ ጠይቄ ሰለቸኛ!
ዘላ ተከመረችብኝ።
ቅጣቴ ባልጠበቅኩት ሁኔታ ተቋጭቶ የኔ ወደሆነው ቦታ እንድዘልቅ ተፈቀደልኝ።
ከዚያ ምሽት በኋላ እኔና ቤዛ የበፊቶቹ ሚኪና ቤዛ ሆንን። የአግባኝ ጥያቄዋ ከጭቅጭቅነት ወደ ልመና ዝቅ ብሎ አንጀት በሚበላ ሁኔታ የምታቀርበው ተማፅኖ ብቻ ሆነ። ከንግግር ይልቅ በሌላ መልኩ የምትገፋብኝ ረቂቅ አጀንዳ ሆነ። ሶፋ እንደመቀየር፣ የኩሽና ኮተት እንደማሟላት፣ ምጣድ እንደመግዛት፣ ሰፋ ያለ ቤት እንከራይ እንደማለት አይነት ረቂቅ አጀንዳ።
ግፊቷን ችዬ መደበኛ ሕይወት ወደመኖሬ ስመለስ አድብቶ የቆየው የአግባኝ ጥያቄዋ ተመልሶ መጣ። እጅ እጅ አለኝ።
– አንቺ ቆይ ለምን አትረጋጊም….እኔ ዝግጁ ሳልሆን ባገባሽ ጥሩ የሚሆን ይመስልሻል? አልኩ በአንዱ ቀን የጋለ ጭቅጭቅ ስንጀምር
– ምንድነው ምትጠብቀው? ቤትህ ተሟልቷል። ታውቀኛለሁ። አውቅሃለሁ። እንዋደዳለን…ምንድነው ምትጠብቀው…ከዚህ ወዲህ አዲስ ፀባይ አይኖረኝም…ለምን አታገባኝም…እጆቿን እያወናጨፈች….
– እንተዋወቃለን? እርግጠኛ ነሽ?
– ምን ማለት ነው ይሄ ደግሞ?
– ምንም ማለት አይደለም ግን ምን ያጣድፈናል?
– ምን ያጣድፈናል? ሶስት አመት በላይ አብረን ቆየን…ምን ይጎትተናል?
– ገና ነው..
– ገና አይደለም…ወይ አሁን ታገባኛለህ…ወይ እንለያያለን…በቃ…
– በቃ?!
– አዎ በቃ….
– ይሄው ነው ቤዛ?
– ይሄው ነው…እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም፡ ውሳኔው ያንተ ነው….
የመኝታ ቤት በሩን ያለርህራሄ ድርግም አድርጋ ዘግታው እዛው ዋለች።
እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም። እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም። እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም።
ሱቅ ሄጄ ስድሰት ቢራ ይዤ መጣሁና አንዱን ከፍቼ መጠጣት ጀመርኩ።
የመጨረሻ ጠርሙሴን ሳጋምስ ወደ ሳሎን ብቅ አለች።
አጠገቤ ቁጭ አለች። አንዴ እኔን አንዴ ባዶ የቢራ ጠርሙሶቹን አየችና
– ሚኪ….አለችኝ
– አቤት….
– አትወደኝም?….
– እወድሻለሁ…ግን ይሄን ማስፈራራት ማቆም አለብሽ…ትዳር አንደዚህ አይቆይም….
– የምን ማስፈራራት?
– ሴክስ የለም ምናምን….ብቸኛው የቅጣት መሳሪያሽ እሱ ይመስላል…ጥሩ አይደለም…..አልኩ ጠርሙሱን ጠረጴዛ ላይ አስቀምጬ እያየኋት…
– ጥሩ አይደለም ማለት…
– ማለት…የራበው ልጅ ምግብ ሰርቆም ቢሆን ይበላል…
ብድግ አለች።
– ምን አልክ አንተ!? ጮኸችብኝ።
– ምን አልኩ? ያልኩትን ነገር ለማሰብ ሞከርኩ። ምንድነው ያልኩት…
– የራበው ልጅ ምግብ ፍለጋ ይሰርቃል ማለት ምንድነው?
ወየው! ምንድነው ያልኩት? ምንድነው ያልኩት?
– ምንም ማለት አይደለም…አባባል ነው…
– አባባልማ አይደለም…በደንብ አስበህበት ነው የተናገርከው…
ወየው!
– ንገረኛ!
– ምን ልንገርሽ?
– ሰርቀሃል?
– እ?
– ሰርቀሃል ወይ?
ስድስቱ ቢራ ይሆን ግዴለሽነቴ ወይ ሁለቱም አዎ አልኳት። አልገርምም? አንዴ አምልጦኛል እና አዎ ሰርቄያለሁ አልኳት። ከግድግዳ መጋጨት ሲቀራት ሁሉን ነገር ሆነች። አለቀሰች። ጮኸች። በጥፊ ልትለኝ ሞከረች። ደጅ ወጣች። ተመልሳ ገባች። አለቀሰች። ጮኸች። ፀጉሯን ይዛ አቀርቅራ ብዙ የማይሰማኝ ነገር አለች።
አሳዘነችኝ። በጣም አሳዘነችኝ። ግን ደግሞ አስርባ ሄርሜላን እንድበላ ያደረገችኝ እሷ ናት በሚል ወልጋዳ ይሁን ትክክለኛ ሰበብ ፀፀት ሳይሰማኝ ቀረ። ገፍትራ ሄርሜላ ጉድጓድ የከተተችኝ እሷ ናት….ምናምን እያልኩ በመናገሬ ሳልፀፀት ዝም ብዬ የምትሆነውን አየሁ። ምናልባት የማላውቀው የልቤ ክፍል ለትዳር ዝግጁ ባለመሆኔ አላገባህም ብላ እንድትተወኝ…ሙሉ ነጻነቴን እንድታቀዳጀኝ ፈልጎ ይሆናል…ምናልባት….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
ክፍል-ሁለት
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻዉ
...ፈተናዬን ሲያበዙት ፊልድ በሄድኩ ቁጥር ስልጠናው ላይ አበል ትክፈል ብለው አብረው ይልኩናል። ሃዋሳ ላይ ለትንሽ አመለጥኳት….መቀሌ ላይ ለጥቂት ሳትኳት፣ አርባምንጭ በመከራ አለፍኳት …ደሴ ግን…ደሴ ላይ ግን ብርዱና ውበቷ አሲረውብኝ ወደቅኩላት። ቀመስኳት። አጣጣምኳት። የተመኘሁትን ጡት እንደ መንፈቅ ልጅ መጠመጥኩ። የጓጓሁለትን ወገብ አቀፍኩ። የቋመጥኩለትን መቀመጫ ጨብጥኩ። ያለምኩትን ከንፈር ጎረስኩ።
ሲነጋ በአንሶላ ተጠቅልላ አይን አይኔን ስታየኝ ነቃሁ። ከባይተዋር ሰው ጋር ባይተዋር አልጋ ላይ ተኝቴ ሲነጋብኝ ፍንጣሪ የጥፋተኝነት ስሜት ስላልተሰማኝ ጥፋተኝነት ተሰማኝ። ትራሴን ተንተርሼ እንደተኛሁ ፣ እንዴት አደርሽ እንኳን ሳልላት-
– ስሚ ሄርሜላ…ትላንት…ስህተት ነው የሰራነው….እኔ እጮኛ አለኝ…አልኳት
– አራቴ ስህተት አለ? ሃሃ….አለችና ያን ከንፈሯን ይዛ ወደከንፈሬ ስትጠጋ ሸሸት ብዬ..
– የምሬን ነው…ስህተት ነው….እጮኛዬን እወዳታለሁ…አልኩ
በፍፁም ግዴለሽነት ከአልጋ ውስጥ ውስጥ መለመላዋን ወጥታ ፈት ለፊቴ ቆመች። ከእኔ በፊት እዚህ ቦታ ሺህ ጊዜ የቆመች፣ ሺህ ጊዜ የሌላን ሰው ገላ አቅፋ ያደረች ልምድ ያላት አሳሳች ትመስላለች።
– አንድ ነገር አንዴ ከሆነ ስህተት ከተደጋገመ ውሳኔ ነው የሚባለው….ለማንኛውም ይመችህ…ሰአት ሄዷል …ልታጠብ…ብላ ታላቅ ቂጧን እያገላበጠች ወደ መታጠቢያው ክፍል ሄደች…
ምንድነው ያለችው?
አዲሳባ ስመለስና ቤዛን ሳገኛት ፀፀት ይሰማኛል፣ የሰራሁት ሃጥያት ያሰቃየኛል ብዬ ጠብቄ ነበር። ያልተለወጠው ግትር ባህሪዋ ይሆን የኔ አይኑን በጨው ያጠበ ባለጌ ሰው መሆን ሽውም አላለኝ። የሄርሜላን ሴትነት ያገኘው ወንድነቴ ምሱን አገኘ መሰለኝ በትራስ ታጥሮ የሚተኛው የቤዛ ገላ አላጓጓው አለ። ማስፈራሪያና ቅጣቷ አልሰማው አለ።
ሄርሜላን በማስታገሻነት በወሰድኩ አንድ ሳምንት ካለፈ ይመስለኛል ቤዛ ባንዱ ምሽት እንደለመደችው ልታሰቃየኝ ስትሞክር ቀድሜያት ግንባሯን ሳምኩና ጀርባዬን ሰጥቼያት ተኛሁ። ደቂቃም ሳይቆይ በቀጫጭን ጣቶቿ ጀርባዬን ትዳብስ…እጆቿን ወደ ጉያዬ ትሰድ ጀመር።
ዝም አልኳት።
በግድ ወደ እሷ ገልብጣኝ-
– ሚኪዬ…አለችኝ በመኝታ ቤት ድምፅዋ…
– አቤት…አልኩ ቡዝ ያሉ ውብ አይኖቿን እያየሁ። ወደ ግራ ያዘነበለ አንገቷን፣ ጫፋቸው የከረረ ጡቶችዋን በስስ ካናቴራዋ ውስጥ እየታዘብኩ።
– አልናፈቅኩህም?…
– ናፍቀሽኛል….
– ምነው መጠየቅ እንኳን ተውክ ታዲያ…
– ጠይቄ ጠይቄ ሰለቸኛ!
ዘላ ተከመረችብኝ።
ቅጣቴ ባልጠበቅኩት ሁኔታ ተቋጭቶ የኔ ወደሆነው ቦታ እንድዘልቅ ተፈቀደልኝ።
ከዚያ ምሽት በኋላ እኔና ቤዛ የበፊቶቹ ሚኪና ቤዛ ሆንን። የአግባኝ ጥያቄዋ ከጭቅጭቅነት ወደ ልመና ዝቅ ብሎ አንጀት በሚበላ ሁኔታ የምታቀርበው ተማፅኖ ብቻ ሆነ። ከንግግር ይልቅ በሌላ መልኩ የምትገፋብኝ ረቂቅ አጀንዳ ሆነ። ሶፋ እንደመቀየር፣ የኩሽና ኮተት እንደማሟላት፣ ምጣድ እንደመግዛት፣ ሰፋ ያለ ቤት እንከራይ እንደማለት አይነት ረቂቅ አጀንዳ።
ግፊቷን ችዬ መደበኛ ሕይወት ወደመኖሬ ስመለስ አድብቶ የቆየው የአግባኝ ጥያቄዋ ተመልሶ መጣ። እጅ እጅ አለኝ።
– አንቺ ቆይ ለምን አትረጋጊም….እኔ ዝግጁ ሳልሆን ባገባሽ ጥሩ የሚሆን ይመስልሻል? አልኩ በአንዱ ቀን የጋለ ጭቅጭቅ ስንጀምር
– ምንድነው ምትጠብቀው? ቤትህ ተሟልቷል። ታውቀኛለሁ። አውቅሃለሁ። እንዋደዳለን…ምንድነው ምትጠብቀው…ከዚህ ወዲህ አዲስ ፀባይ አይኖረኝም…ለምን አታገባኝም…እጆቿን እያወናጨፈች….
– እንተዋወቃለን? እርግጠኛ ነሽ?
– ምን ማለት ነው ይሄ ደግሞ?
– ምንም ማለት አይደለም ግን ምን ያጣድፈናል?
– ምን ያጣድፈናል? ሶስት አመት በላይ አብረን ቆየን…ምን ይጎትተናል?
– ገና ነው..
– ገና አይደለም…ወይ አሁን ታገባኛለህ…ወይ እንለያያለን…በቃ…
– በቃ?!
– አዎ በቃ….
– ይሄው ነው ቤዛ?
– ይሄው ነው…እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም፡ ውሳኔው ያንተ ነው….
የመኝታ ቤት በሩን ያለርህራሄ ድርግም አድርጋ ዘግታው እዛው ዋለች።
እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም። እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም። እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም።
ሱቅ ሄጄ ስድሰት ቢራ ይዤ መጣሁና አንዱን ከፍቼ መጠጣት ጀመርኩ።
የመጨረሻ ጠርሙሴን ሳጋምስ ወደ ሳሎን ብቅ አለች።
አጠገቤ ቁጭ አለች። አንዴ እኔን አንዴ ባዶ የቢራ ጠርሙሶቹን አየችና
– ሚኪ….አለችኝ
– አቤት….
– አትወደኝም?….
– እወድሻለሁ…ግን ይሄን ማስፈራራት ማቆም አለብሽ…ትዳር አንደዚህ አይቆይም….
– የምን ማስፈራራት?
– ሴክስ የለም ምናምን….ብቸኛው የቅጣት መሳሪያሽ እሱ ይመስላል…ጥሩ አይደለም…..አልኩ ጠርሙሱን ጠረጴዛ ላይ አስቀምጬ እያየኋት…
– ጥሩ አይደለም ማለት…
– ማለት…የራበው ልጅ ምግብ ሰርቆም ቢሆን ይበላል…
ብድግ አለች።
– ምን አልክ አንተ!? ጮኸችብኝ።
– ምን አልኩ? ያልኩትን ነገር ለማሰብ ሞከርኩ። ምንድነው ያልኩት…
– የራበው ልጅ ምግብ ፍለጋ ይሰርቃል ማለት ምንድነው?
ወየው! ምንድነው ያልኩት? ምንድነው ያልኩት?
– ምንም ማለት አይደለም…አባባል ነው…
– አባባልማ አይደለም…በደንብ አስበህበት ነው የተናገርከው…
ወየው!
– ንገረኛ!
– ምን ልንገርሽ?
– ሰርቀሃል?
– እ?
– ሰርቀሃል ወይ?
ስድስቱ ቢራ ይሆን ግዴለሽነቴ ወይ ሁለቱም አዎ አልኳት። አልገርምም? አንዴ አምልጦኛል እና አዎ ሰርቄያለሁ አልኳት። ከግድግዳ መጋጨት ሲቀራት ሁሉን ነገር ሆነች። አለቀሰች። ጮኸች። በጥፊ ልትለኝ ሞከረች። ደጅ ወጣች። ተመልሳ ገባች። አለቀሰች። ጮኸች። ፀጉሯን ይዛ አቀርቅራ ብዙ የማይሰማኝ ነገር አለች።
አሳዘነችኝ። በጣም አሳዘነችኝ። ግን ደግሞ አስርባ ሄርሜላን እንድበላ ያደረገችኝ እሷ ናት በሚል ወልጋዳ ይሁን ትክክለኛ ሰበብ ፀፀት ሳይሰማኝ ቀረ። ገፍትራ ሄርሜላ ጉድጓድ የከተተችኝ እሷ ናት….ምናምን እያልኩ በመናገሬ ሳልፀፀት ዝም ብዬ የምትሆነውን አየሁ። ምናልባት የማላውቀው የልቤ ክፍል ለትዳር ዝግጁ ባለመሆኔ አላገባህም ብላ እንድትተወኝ…ሙሉ ነጻነቴን እንድታቀዳጀኝ ፈልጎ ይሆናል…ምናልባት….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍10
#ወንጀልና_ቅጣት #የመጨረሻ_ክፍል
:
ክፍል-ሶስት
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻዉ
...ሃጥያቴን በብቅል ግፊት ከተናዘዝኩ በኋላ መቼም ሰው አታደርገኝም…የኔ እና የእሷ ነገር አለቀ ደቀቀ ብዬ…ሂሳቤን አገኛለሁ ብዬ ስጠብቅ ሲሻት ተደብራ ከመጋገር፣ ሲሻት ከሰላምታ ያላለፈ ነገር ባለመናገር ከመቅጣት በቀር ትታኝ አልሄደችም።
እንደ ድሮው ቤቴ ትመጣለች፣ ስደውል ታነሳለች፣ እንገናኝ ስላት ታገኘኛለች። አብራኝ መተኛት ሲቀራት አብራኝ ትሆናለች። ሰብሬያት እንዳልሰበርኳት፣ አኩርፋኝ እንዳላኮረፈችኝ ትሆናለች። ዝም ስትለኝ ሰአቱ ቀን ይሆንብኛል። ቀኑ ሳምንት….ቅጣቴ ይሄ ነው? የሃጥያቴ ክፍያ በዝምታ መንገብገብ ነው?
ሶስት ቀን በሶስት አመታት ፍጥነት እየተጎተተ ካለፈ በኋላ ቁርጤን ልወቅ ብዬ ወሰንኩ። ቃተኛ ቁጭ ብለን ጥብስ ፍርፍራችንን በተለመደው ዝምታ ስንበላ
– ቤዚ…አልኳት
– እ….
መስረቄን ካወቀች ወዲህ ወዬዎቿ…በ እ…ተተክተዋል። ምንድነው እ ብሎ ነገር? ላናግርህ አልፈልግም ስለዚህ ከአንዲት ፊደል በቀር አይገባህም ነው?
– ይቅር ብለሽኛል? አልኳት ጥብስ ፍርፍሩን መብላትም ማየትም አቁሜ እያየኋት
– እ?
ኡፋ! …..የምን እ ነው?
– ይቅርታ አድርገሽልኛል ወይ….
– እዚህ ሰው ፊት ስለሱ ማውራት አልፈልግም…ቤት ስንሄድ እናወራለን….አለችኝ …ለአስተናጋጁ ሲሆን ከብርሃን የተሰራ የሚመስል ቀይ ዳማ ፊቷ ለኔ ሲሆን ባንዴ የሚዳምንላት እንዴት ነው?
ዝም ብያት እስክንጨርስ ጠበቅኩ።
ቤት ገባን። መልሼ ጠየቅኳት።
– አላውቅም…እያሰብኩበት ነው….አለችኝና ወደ መኝታ ቤት ሄደች።
ጓደኖቼን አማከርኩ። ይቅር ባትልህ አብራህ አትቆይም..ያደረግከው ነገር እኮ ከባድ ነው ትንሽ ታገስ…እሷ ሆና ነው እንጂ ሌላ ሴት ብትሆን ይሄኔ ቆርጣልህ ነበር…ምናምን ሲሉኝ የዝምታ ቅጣቴን በፀጋ ለመቀበል ወስኜ ቆየሁ።
ትንሽ ጊዜ ካለፈ በኋላ በአንዱ ቀነ ከመሬት ተነስታ ላንጋኖ እንሂድ ምናምን ብላ ወጠረችኝ።
– ለምን አልኳት
– እኔ ስለፈለግኩ አለችኝ። ፊቷን ሳየው ግን ‹‹ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛህ እና የፈለግኩትን ነገር ማድረግ ስላለብህ›› ተብሎ የተፃፈ መሰለኝ። እጄ ላይ ብዙ ብር አልነበረምና
– ደሞዝ ስቀበል…ከአስር ቀን በኋላ ብንሄድስ? አልኳት በሚለማመጥ ድምፅ…
– እኔ አሁን ነው መሄድ የፈለግኩት…ካልፈለግህ አልፈልግም በል….ብስጭትጭት አደረጋት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ፣ ከጓደኛዬ ብር ተበደርኩና ሄድን።
ላንጋኖ ስንደርስ አይቼ የማላውቀውን ክር ሊሆን ትንሽ የቀረው ጡትና ቂጥ በአግባቡ የማይይዘ ‹‹የዋና ልብስ›› ለብሳ ልክ ብቻዋን እንደመጣች…ልክ ወንድ ልታጠመድ ታጥባ ተቀሽራ እንደወጣች ሴት ቢቹ ላይ ስትንቧችበት ዝም ብዬ አየኋት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ብጉራቸውን እያፈረጡ ተጠግተዋት ሰልክ ቁጥር እየጠየቋት እንደሆነ የሚያስታውቁ ወንዶች ሲያንዣብቡባት፣ ሲያወሯት፣ በሚጢጢ ጨርቅ የተሸፈነ ምንተእፍረትዋን በአይናቸው ሲያወልቁ እያየሁ ዝም አልኳት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ማታ ክፍላችን ገብተን ለማንም ኤግዚቢሽን ያቀረበችውን ገላዋን ለመንካት እንኳን ሰትከለክለኝ…እንደ እሾህ ስትሸሸኝ….አትንካኝ ሬዲ አይደለሁም ብላ ፍቅርን ስትነፍገኝ ዝም አልኳት።
አዲሳባ ተመልሰን የማልወደው ጫጫታም ካፌ እየወሰደች ለሰአታት አርፍዳ ስትጎልተኝ፣ አምስት ደቂቃ ዘግይቼ ቤት ከገባሁ አንበሳ ሆና ስትቆጣኝ፣ ከጓደኞቼ እንድቆራረጥ አትሄድም ብላ ስታስቀረኝ፣ የዘመዶቿን ሰርግ ይዛኝ ሄዳ ብቻዬን ትታኝ ስትረሳኝ፣ ሃጥያቴን ነግራቸው የናቁኝ ሴት ጓደኞቿን በሙሉ አምጥታ (አራት ናቸው) የሁለት መቶ ሃምሳ ብር ክትፎ ስታስጋብዘኝ…ከሌላ ሴት ተኝታቸለሁ እና ቅጣቴን ልቀበል…ሂሳቤን ላግኝ ብዬ ዝም አልኳት።
ይባስ ብላ አንዷ ቀለብላባ ጓደኛዋ በንቀትም በሴሰኝነትም ተነድታ ስልክም እየደወለች፣ ቤቴም ‹‹ቤዛ የለችም›› ብላ የሌለችበተትን ሰአት መርጥ እየመጣች እንድተኛት ስትጋብዘኝ…ከአንዷ ጋር ከማገጥክ ከእኛስ ጋር ብትማግጥ በሚል ሁኔታ ስትቀበጠበጥብኝ ጥፋቱ የኔ ነው ብዬ ዝም አልኳት።
ከሳምንታት በኋላ ግን እጅ እጅ እያለኝ መጣ። እኔን አስቀንታ ለመመለስ የምትለፋው፣ ላገኘችው ሰው ሁሉ ሃጥያቴን ነግራ ስሜን የምታጠፋው፣ በውሃ አረረ ፊቴን ፊት የምትነሳው፣ በሁሉም ነገር ስሜቴን የምታሸማቅቀው ነገር ከፍቅሯ እየበለጠ ነገሩ እጅ እጅ እያለኝ መጣ።
ጭራሽ አሁን ደግሞ ሃገር ውስጥ ስለሰራሁት ስህተት አልሰሙም ብዬ የተማመንኩባቸው እንደዛ የሚወዱኝ…እንደልጅ የሚንከባከቡኝ ቤተሰቦቿ ጋር ሄዳ ማውራቷ፣ ልታዋርደኝ መጨከኗ…በእኔና በእሷ ጉዳይ ማስገባቷ ልቤን አደነደነው። ልጠይቃት ይገባል። ይቅር ብለሽኛል ወይስ ቅጣቴ የእድሜ ልክ ነው? አፉ ብለሽኛል ወይስ አንቺ ካለሽበት ሕይወቴ እንዲህ ሊሆን ነው? ብዬ ልጠይቃት ይገባል።
እትዬ ሌንሴና እህቶቿ እንዲያ ባገባጠሩኝ እለት ማታ ቤት ቁጭ ብለን ወይን ስንጠጣ (ላወራት ስጀምር ነው አንዱን ጠርሙስ ጨርሳ ወደ ሁለተኛው መግባቷን ያየሁት)
– ቤዚ …አልኳት
– እ…
(እ…ን አሁንማ ለምጄዋለሁ)
– መቼ ነው እንደ ድሮው የምትሆኚልኝ? ቅጣቴ አልበዛም? አልኳት
– ያደረግከውን ነገር ረሳኸው…? ከሌላ ሴት ጋር እኮ ነው ሴክስ ያደረግከው…ሴ….ክ….ስ….
ወይኑም ነገሩም እንዳሰከራት ገባኝ።
-አውቃለሁ…አጠፋሁ…አይበቃኝም ቅጣቱ…እንዴት እንደዚህ እንቀጥላለን….ብንቀጥልስ…እስከመቼ ድሮ ለሰራሁት ጥፋት እድሜዬን ሙሉ እከፍላለሁ…
– ወር የማይሞላ ጊዜ ነው እድሜዬን ሙሉ የምትለው..
– አይደለም…
– ታዲያ…
– ማለቴ…ብንጋባ እንኳን አንድ ነገር ባጠፋሁ ቁጥር አንተ እኮ…እያልሽኝ እስከመቼ እንኖራለን…
– ሃሃ…..አሁን ነው መጋባት ያማረህ….? ደ…ፋ…ር….
ወሬያችን እንኳን እንዳሁኑ በአልኮል ፈረስ ተሳፍራ በደህናውም ጊዜ ትርጉም ያለው ነገር ሊወጣው እንደማይችል ተረዳሁና ዝም አልኳት።
– ምን ይ…ዘ…ጋ…ሃ…ል? አለች ፊደል እንደሚቆጥር ሰው ቃላቶቹን እየጎተተች…
– ጥቅም የለውም ብዬ ነው…
– ም…ኑ..
– እንዲህ ሆነሸ ማውራቱ….
– እና..ውራ…ማውራት አይደል የፈለግከው…እናውራ…
– ግዴለም ነገ ይደርሰል…
– አይ…ሆ…ን…ም አሁን እናውራ…
– ቤዚ…ይቅር
– አይ…ቀርም…እናውራ…እናወ…..ራ….
እንደለቅሶ ይሰራት ጀመር። ቤዚዬ….
– እሺ አልኳት እንዳታለቅስ…
– እሺ…ልጅቷ…እንዴት ነበረች…ጎበዝ ናት…..?
– ማ? አልኩኝ ደንገጥ ብዬ..
– እናውራ አላልክም…እናውራ….ያቺ አብረሃት የተኛሃት ልጅ…ጎበዝ ናት….ማለት…ከኔ ትበልጣለች?
ዝም አልኳት።
– ንገረኛ! እንዴት ነበረች…ትበልጠኛለች…..? ለቅሶ ጀመረች።
አቀፍኳት።
– ንገረኝ…..በለጠችኝ…ደስ አለችህ…ጎበዝ….
– ተይ ተይ በቃ…ቤዚዬ…ይቅርታ…በቃ…ይቅርታ አታልቅሺ አልኩና አጥብቄ አቅፌ ፀጉሯ ላይ…አይኖችዋን አፈራርቄ ሳምኳቸው።
– አትሳመኝ….ብላ ተፈናጥራ ተነሳች።
– እ?
– አትሳመኝ….እሷን በሳምክበት አፍ አትሳመኝ….ሚ..ኪ….ከሁሉ ሚያሳዝነኝ ምን እንደሆን ታውቃለህ…..አለችኝ ተመልሳ እየተቀመጠች።
ዝም አልኩ።
ቀጠለች-
– እወድሃለሁ…ማለቴ…ካላንተ ወንድ አልፈልግም…ጓደኞቼም ቤተሰቦቼም ቢመክሩኝም ባንተ መጨከን አቃተኝ…ሳምሪ ወንድ ልጅ አንዴ ከተልከሰከሰ ሁሌም ይልከሰከሳል…ይቅር ካልሽው እንደ ፈቃድ ነው ሚወስደው…ይቅርብሽ ብላኝ ነበር…ይሄን ታውቃለህ? እህቶቼ ለአይን ጠልተውሃል…እማዬማ ቤቴ አይምጣ ብላለች…እኔ ግን እወድሃለሁ…ልቤን ቢያመኝም…እወድሃለሁ…
– እነሱን ተያቸወ…አንቺ ከወደድሽኝ የኔ ጉዳይ ካንቺ ነው….አልኩ ፈጠን ብዬ…
– አይደለማ…..እወድሃለሁ ግን
:
ክፍል-ሶስት
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻዉ
...ሃጥያቴን በብቅል ግፊት ከተናዘዝኩ በኋላ መቼም ሰው አታደርገኝም…የኔ እና የእሷ ነገር አለቀ ደቀቀ ብዬ…ሂሳቤን አገኛለሁ ብዬ ስጠብቅ ሲሻት ተደብራ ከመጋገር፣ ሲሻት ከሰላምታ ያላለፈ ነገር ባለመናገር ከመቅጣት በቀር ትታኝ አልሄደችም።
እንደ ድሮው ቤቴ ትመጣለች፣ ስደውል ታነሳለች፣ እንገናኝ ስላት ታገኘኛለች። አብራኝ መተኛት ሲቀራት አብራኝ ትሆናለች። ሰብሬያት እንዳልሰበርኳት፣ አኩርፋኝ እንዳላኮረፈችኝ ትሆናለች። ዝም ስትለኝ ሰአቱ ቀን ይሆንብኛል። ቀኑ ሳምንት….ቅጣቴ ይሄ ነው? የሃጥያቴ ክፍያ በዝምታ መንገብገብ ነው?
ሶስት ቀን በሶስት አመታት ፍጥነት እየተጎተተ ካለፈ በኋላ ቁርጤን ልወቅ ብዬ ወሰንኩ። ቃተኛ ቁጭ ብለን ጥብስ ፍርፍራችንን በተለመደው ዝምታ ስንበላ
– ቤዚ…አልኳት
– እ….
መስረቄን ካወቀች ወዲህ ወዬዎቿ…በ እ…ተተክተዋል። ምንድነው እ ብሎ ነገር? ላናግርህ አልፈልግም ስለዚህ ከአንዲት ፊደል በቀር አይገባህም ነው?
– ይቅር ብለሽኛል? አልኳት ጥብስ ፍርፍሩን መብላትም ማየትም አቁሜ እያየኋት
– እ?
ኡፋ! …..የምን እ ነው?
– ይቅርታ አድርገሽልኛል ወይ….
– እዚህ ሰው ፊት ስለሱ ማውራት አልፈልግም…ቤት ስንሄድ እናወራለን….አለችኝ …ለአስተናጋጁ ሲሆን ከብርሃን የተሰራ የሚመስል ቀይ ዳማ ፊቷ ለኔ ሲሆን ባንዴ የሚዳምንላት እንዴት ነው?
ዝም ብያት እስክንጨርስ ጠበቅኩ።
ቤት ገባን። መልሼ ጠየቅኳት።
– አላውቅም…እያሰብኩበት ነው….አለችኝና ወደ መኝታ ቤት ሄደች።
ጓደኖቼን አማከርኩ። ይቅር ባትልህ አብራህ አትቆይም..ያደረግከው ነገር እኮ ከባድ ነው ትንሽ ታገስ…እሷ ሆና ነው እንጂ ሌላ ሴት ብትሆን ይሄኔ ቆርጣልህ ነበር…ምናምን ሲሉኝ የዝምታ ቅጣቴን በፀጋ ለመቀበል ወስኜ ቆየሁ።
ትንሽ ጊዜ ካለፈ በኋላ በአንዱ ቀነ ከመሬት ተነስታ ላንጋኖ እንሂድ ምናምን ብላ ወጠረችኝ።
– ለምን አልኳት
– እኔ ስለፈለግኩ አለችኝ። ፊቷን ሳየው ግን ‹‹ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛህ እና የፈለግኩትን ነገር ማድረግ ስላለብህ›› ተብሎ የተፃፈ መሰለኝ። እጄ ላይ ብዙ ብር አልነበረምና
– ደሞዝ ስቀበል…ከአስር ቀን በኋላ ብንሄድስ? አልኳት በሚለማመጥ ድምፅ…
– እኔ አሁን ነው መሄድ የፈለግኩት…ካልፈለግህ አልፈልግም በል….ብስጭትጭት አደረጋት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ፣ ከጓደኛዬ ብር ተበደርኩና ሄድን።
ላንጋኖ ስንደርስ አይቼ የማላውቀውን ክር ሊሆን ትንሽ የቀረው ጡትና ቂጥ በአግባቡ የማይይዘ ‹‹የዋና ልብስ›› ለብሳ ልክ ብቻዋን እንደመጣች…ልክ ወንድ ልታጠመድ ታጥባ ተቀሽራ እንደወጣች ሴት ቢቹ ላይ ስትንቧችበት ዝም ብዬ አየኋት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ብጉራቸውን እያፈረጡ ተጠግተዋት ሰልክ ቁጥር እየጠየቋት እንደሆነ የሚያስታውቁ ወንዶች ሲያንዣብቡባት፣ ሲያወሯት፣ በሚጢጢ ጨርቅ የተሸፈነ ምንተእፍረትዋን በአይናቸው ሲያወልቁ እያየሁ ዝም አልኳት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ማታ ክፍላችን ገብተን ለማንም ኤግዚቢሽን ያቀረበችውን ገላዋን ለመንካት እንኳን ሰትከለክለኝ…እንደ እሾህ ስትሸሸኝ….አትንካኝ ሬዲ አይደለሁም ብላ ፍቅርን ስትነፍገኝ ዝም አልኳት።
አዲሳባ ተመልሰን የማልወደው ጫጫታም ካፌ እየወሰደች ለሰአታት አርፍዳ ስትጎልተኝ፣ አምስት ደቂቃ ዘግይቼ ቤት ከገባሁ አንበሳ ሆና ስትቆጣኝ፣ ከጓደኞቼ እንድቆራረጥ አትሄድም ብላ ስታስቀረኝ፣ የዘመዶቿን ሰርግ ይዛኝ ሄዳ ብቻዬን ትታኝ ስትረሳኝ፣ ሃጥያቴን ነግራቸው የናቁኝ ሴት ጓደኞቿን በሙሉ አምጥታ (አራት ናቸው) የሁለት መቶ ሃምሳ ብር ክትፎ ስታስጋብዘኝ…ከሌላ ሴት ተኝታቸለሁ እና ቅጣቴን ልቀበል…ሂሳቤን ላግኝ ብዬ ዝም አልኳት።
ይባስ ብላ አንዷ ቀለብላባ ጓደኛዋ በንቀትም በሴሰኝነትም ተነድታ ስልክም እየደወለች፣ ቤቴም ‹‹ቤዛ የለችም›› ብላ የሌለችበተትን ሰአት መርጥ እየመጣች እንድተኛት ስትጋብዘኝ…ከአንዷ ጋር ከማገጥክ ከእኛስ ጋር ብትማግጥ በሚል ሁኔታ ስትቀበጠበጥብኝ ጥፋቱ የኔ ነው ብዬ ዝም አልኳት።
ከሳምንታት በኋላ ግን እጅ እጅ እያለኝ መጣ። እኔን አስቀንታ ለመመለስ የምትለፋው፣ ላገኘችው ሰው ሁሉ ሃጥያቴን ነግራ ስሜን የምታጠፋው፣ በውሃ አረረ ፊቴን ፊት የምትነሳው፣ በሁሉም ነገር ስሜቴን የምታሸማቅቀው ነገር ከፍቅሯ እየበለጠ ነገሩ እጅ እጅ እያለኝ መጣ።
ጭራሽ አሁን ደግሞ ሃገር ውስጥ ስለሰራሁት ስህተት አልሰሙም ብዬ የተማመንኩባቸው እንደዛ የሚወዱኝ…እንደልጅ የሚንከባከቡኝ ቤተሰቦቿ ጋር ሄዳ ማውራቷ፣ ልታዋርደኝ መጨከኗ…በእኔና በእሷ ጉዳይ ማስገባቷ ልቤን አደነደነው። ልጠይቃት ይገባል። ይቅር ብለሽኛል ወይስ ቅጣቴ የእድሜ ልክ ነው? አፉ ብለሽኛል ወይስ አንቺ ካለሽበት ሕይወቴ እንዲህ ሊሆን ነው? ብዬ ልጠይቃት ይገባል።
እትዬ ሌንሴና እህቶቿ እንዲያ ባገባጠሩኝ እለት ማታ ቤት ቁጭ ብለን ወይን ስንጠጣ (ላወራት ስጀምር ነው አንዱን ጠርሙስ ጨርሳ ወደ ሁለተኛው መግባቷን ያየሁት)
– ቤዚ …አልኳት
– እ…
(እ…ን አሁንማ ለምጄዋለሁ)
– መቼ ነው እንደ ድሮው የምትሆኚልኝ? ቅጣቴ አልበዛም? አልኳት
– ያደረግከውን ነገር ረሳኸው…? ከሌላ ሴት ጋር እኮ ነው ሴክስ ያደረግከው…ሴ….ክ….ስ….
ወይኑም ነገሩም እንዳሰከራት ገባኝ።
-አውቃለሁ…አጠፋሁ…አይበቃኝም ቅጣቱ…እንዴት እንደዚህ እንቀጥላለን….ብንቀጥልስ…እስከመቼ ድሮ ለሰራሁት ጥፋት እድሜዬን ሙሉ እከፍላለሁ…
– ወር የማይሞላ ጊዜ ነው እድሜዬን ሙሉ የምትለው..
– አይደለም…
– ታዲያ…
– ማለቴ…ብንጋባ እንኳን አንድ ነገር ባጠፋሁ ቁጥር አንተ እኮ…እያልሽኝ እስከመቼ እንኖራለን…
– ሃሃ…..አሁን ነው መጋባት ያማረህ….? ደ…ፋ…ር….
ወሬያችን እንኳን እንዳሁኑ በአልኮል ፈረስ ተሳፍራ በደህናውም ጊዜ ትርጉም ያለው ነገር ሊወጣው እንደማይችል ተረዳሁና ዝም አልኳት።
– ምን ይ…ዘ…ጋ…ሃ…ል? አለች ፊደል እንደሚቆጥር ሰው ቃላቶቹን እየጎተተች…
– ጥቅም የለውም ብዬ ነው…
– ም…ኑ..
– እንዲህ ሆነሸ ማውራቱ….
– እና..ውራ…ማውራት አይደል የፈለግከው…እናውራ…
– ግዴለም ነገ ይደርሰል…
– አይ…ሆ…ን…ም አሁን እናውራ…
– ቤዚ…ይቅር
– አይ…ቀርም…እናውራ…እናወ…..ራ….
እንደለቅሶ ይሰራት ጀመር። ቤዚዬ….
– እሺ አልኳት እንዳታለቅስ…
– እሺ…ልጅቷ…እንዴት ነበረች…ጎበዝ ናት…..?
– ማ? አልኩኝ ደንገጥ ብዬ..
– እናውራ አላልክም…እናውራ….ያቺ አብረሃት የተኛሃት ልጅ…ጎበዝ ናት….ማለት…ከኔ ትበልጣለች?
ዝም አልኳት።
– ንገረኛ! እንዴት ነበረች…ትበልጠኛለች…..? ለቅሶ ጀመረች።
አቀፍኳት።
– ንገረኝ…..በለጠችኝ…ደስ አለችህ…ጎበዝ….
– ተይ ተይ በቃ…ቤዚዬ…ይቅርታ…በቃ…ይቅርታ አታልቅሺ አልኩና አጥብቄ አቅፌ ፀጉሯ ላይ…አይኖችዋን አፈራርቄ ሳምኳቸው።
– አትሳመኝ….ብላ ተፈናጥራ ተነሳች።
– እ?
– አትሳመኝ….እሷን በሳምክበት አፍ አትሳመኝ….ሚ..ኪ….ከሁሉ ሚያሳዝነኝ ምን እንደሆን ታውቃለህ…..አለችኝ ተመልሳ እየተቀመጠች።
ዝም አልኩ።
ቀጠለች-
– እወድሃለሁ…ማለቴ…ካላንተ ወንድ አልፈልግም…ጓደኞቼም ቤተሰቦቼም ቢመክሩኝም ባንተ መጨከን አቃተኝ…ሳምሪ ወንድ ልጅ አንዴ ከተልከሰከሰ ሁሌም ይልከሰከሳል…ይቅር ካልሽው እንደ ፈቃድ ነው ሚወስደው…ይቅርብሽ ብላኝ ነበር…ይሄን ታውቃለህ? እህቶቼ ለአይን ጠልተውሃል…እማዬማ ቤቴ አይምጣ ብላለች…እኔ ግን እወድሃለሁ…ልቤን ቢያመኝም…እወድሃለሁ…
– እነሱን ተያቸወ…አንቺ ከወደድሽኝ የኔ ጉዳይ ካንቺ ነው….አልኩ ፈጠን ብዬ…
– አይደለማ…..እወድሃለሁ ግን
👍12❤1